2 hours ago
''ሰውየውን ማግኘት እፈልጋለሁ''
#ethiopia | የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራኑ ከፍተኛ መንፈሳዊ መሪ ሞጅታባ ኻሚኒ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ለመፍጠር ፍላጎት እንዳላቸው የገለጹ ሲሆን፣ የውይይቱ መሳካት ግን በሁለቱ ሀገራት መካከል በተጀመሩት ስምምነቶች ውጤት ላይ እንደሚወሰን አስታውቀዋል።
ፕሬዝደንት ትራምፕ በነጩ ቤተ መንግስት በሰጡት ቃለ ምልልስ፣ የኢራንን ሃይማኖታዊ መሪ ለማግኘት ፍላጎት እንዳላቸውና ስብሰባው ሊካሄድ የሚችለው ዋሽንግተንና ቴህራን በኒውክሌር ፕሮግራም፣ በዩራኒየም ክምችት፣ በክልላዊ ደህንነትና በተኩስ አቁም ጉዳዮች ላይ ስምምነት ላይ መድረስ ሲችሉ ብቻ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ከ1979 የኢራን አብዮት በኋላ በሁለቱ ሀገራት መካከል የነበረውን የረጅም ጊዜ ውጥረት ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ይህ የታሰበው መገናኘት እውን ቢሆን በዓለም አቀፍ ፖለቲካ ላይ ታሪካዊ ለውጥ ሊያመጣ እንደሚችል ተነግሯል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#አሜሪካ #ኢራን #ዶናልድትራምፕ #ሞጅታባኻሚኒ #ዓለምአቀፍዲፕሎማሲ #የኒውክሌርውል #ዋሽንግተን #ቴህራን
#ethiopia | የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራኑ ከፍተኛ መንፈሳዊ መሪ ሞጅታባ ኻሚኒ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ለመፍጠር ፍላጎት እንዳላቸው የገለጹ ሲሆን፣ የውይይቱ መሳካት ግን በሁለቱ ሀገራት መካከል በተጀመሩት ስምምነቶች ውጤት ላይ እንደሚወሰን አስታውቀዋል።
ፕሬዝደንት ትራምፕ በነጩ ቤተ መንግስት በሰጡት ቃለ ምልልስ፣ የኢራንን ሃይማኖታዊ መሪ ለማግኘት ፍላጎት እንዳላቸውና ስብሰባው ሊካሄድ የሚችለው ዋሽንግተንና ቴህራን በኒውክሌር ፕሮግራም፣ በዩራኒየም ክምችት፣ በክልላዊ ደህንነትና በተኩስ አቁም ጉዳዮች ላይ ስምምነት ላይ መድረስ ሲችሉ ብቻ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ከ1979 የኢራን አብዮት በኋላ በሁለቱ ሀገራት መካከል የነበረውን የረጅም ጊዜ ውጥረት ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ይህ የታሰበው መገናኘት እውን ቢሆን በዓለም አቀፍ ፖለቲካ ላይ ታሪካዊ ለውጥ ሊያመጣ እንደሚችል ተነግሯል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#አሜሪካ #ኢራን #ዶናልድትራምፕ #ሞጅታባኻሚኒ #ዓለምአቀፍዲፕሎማሲ #የኒውክሌርውል #ዋሽንግተን #ቴህራን
3 hours ago
''ሰውየውን ማግኘት እፈልጋለሁ''
#ethiopia | የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራኑ ከፍተኛ መንፈሳዊ መሪ ሞጅታባ ኻሚኒ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ለመፍጠር ፍላጎት እንዳላቸው የገለጹ ሲሆን፣ የውይይቱ መሳካት ግን በሁለቱ ሀገራት መካከል በተጀመሩት ስምምነቶች ውጤት ላይ እንደሚወሰን አስታውቀዋል።
ፕሬዝደንት ትራምፕ በነጩ ቤተ መንግስት በሰጡት ቃለ ምልልስ፣ የኢራንን ሃይማኖታዊ መሪ ለማግኘት ፍላጎት እንዳላቸውና ስብሰባው ሊካሄድ የሚችለው ዋሽንግተንና ቴህራን በኒውክሌር ፕሮግራም፣ በዩራኒየም ክምችት፣ በክልላዊ ደህንነትና በተኩስ አቁም ጉዳዮች ላይ ስምምነት ላይ መድረስ ሲችሉ ብቻ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ከ1979 የኢራን አብዮት በኋላ በሁለቱ ሀገራት መካከል የነበረውን የረጅም ጊዜ ውጥረት ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ይህ የታሰበው መገናኘት እውን ቢሆን በዓለም አቀፍ ፖለቲካ ላይ ታሪካዊ ለውጥ ሊያመጣ እንደሚችል ተነግሯል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#አሜሪካ #ኢራን #ዶናልድትራምፕ #ሞጅታባኻሚኒ #ዓለምአቀፍዲፕሎማሲ #የኒውክሌርውል #ዋሽንግተን #ቴህራን
#ethiopia | የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራኑ ከፍተኛ መንፈሳዊ መሪ ሞጅታባ ኻሚኒ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ለመፍጠር ፍላጎት እንዳላቸው የገለጹ ሲሆን፣ የውይይቱ መሳካት ግን በሁለቱ ሀገራት መካከል በተጀመሩት ስምምነቶች ውጤት ላይ እንደሚወሰን አስታውቀዋል።
ፕሬዝደንት ትራምፕ በነጩ ቤተ መንግስት በሰጡት ቃለ ምልልስ፣ የኢራንን ሃይማኖታዊ መሪ ለማግኘት ፍላጎት እንዳላቸውና ስብሰባው ሊካሄድ የሚችለው ዋሽንግተንና ቴህራን በኒውክሌር ፕሮግራም፣ በዩራኒየም ክምችት፣ በክልላዊ ደህንነትና በተኩስ አቁም ጉዳዮች ላይ ስምምነት ላይ መድረስ ሲችሉ ብቻ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ከ1979 የኢራን አብዮት በኋላ በሁለቱ ሀገራት መካከል የነበረውን የረጅም ጊዜ ውጥረት ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ይህ የታሰበው መገናኘት እውን ቢሆን በዓለም አቀፍ ፖለቲካ ላይ ታሪካዊ ለውጥ ሊያመጣ እንደሚችል ተነግሯል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#አሜሪካ #ኢራን #ዶናልድትራምፕ #ሞጅታባኻሚኒ #ዓለምአቀፍዲፕሎማሲ #የኒውክሌርውል #ዋሽንግተን #ቴህራን
7 hours ago
ሰላም፣ ደህና አደራችሁ?
የስልጣን ምንጭ እና ባለቤት….
ኢትዮጵያ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በተሳካ ሁኔታ አካሂዳለች። በዕለቱ ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ በነፃነት ይወክለኛል የሚለውን በመምረጥ፤ የኃይል አማራጭን ለተከተሉት ጆሮ ባለመስጠት ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መጎለበት ያለውን ውግንና አሳይቷል፡፡
በቅድመ ምርጫ ወቅት መራጩ የተፎካካሪ አካላትን ፖሊሲ፣ ስትራቴጂ እና እሳቤዎች በሚገባ ሲከታተል ቆይቷል፡፡ ሲያሰላስል ቆይቶም በምርጫው ዕለት ይወክለኛል የሚለውን በምስጢር በካርዱ ወስኗል፡፡ አሁን የምርጫውን ውጤት በመጠባበቅ ላይ ይገኛል፡፡ ይህ ዴሞክራሲያዊ እሳቤ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ህዝብ ብዙ የትግል ታሪኮችን አሳልፏል፡፡ ረዥም የሰላምና የልማት መንገድ የሚያስኬደውን አቅሙንም በዚሁ ውስብስብ ሂደት ሲያጣ ኖሯል፡፡ የዘንድሮው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ህዝቡ ከኃይል ይልቅ ሰላምን፣ ከጠብመንጃ ይልቅ የምርጫ ካርድን እንደሚመርጥ በግልጽ አስመስክሯል፡፡ ይህ ለምርጫ ያለው ቦታ እያደገ መምጣቱን ያሳየ ነው፡፡ ለዚያም ነው ብርድ፣ ዝናብ፣ ፀሐይ፣ ህመም፣ ኀዘን፣ ሙቀት፣ እርጅና እና ማስፈራሪያ ሳይገድበው ወጥቶ ድምጹን ይወክለኛል ለሚለውና ለሚሻው የሰጠው፡፡
እኔ አውቅልሀለሁ ለሚሉት፣ አይዞን እኔ ለራሴ አውቃለሁ ብሏል፡፡ ይህ የህልውና ጉዳይ ነው፡፡ የዴሞክራሲ ጥማት፡፡ የጥይት አረር በቃኝ ያለበት ውሳኔ፡፡
ሂደቱን ለማደናቀፍ ግዝትና ግዞት ቢኖርም በዕለቱ ኢትዮጵያውያን በሀገራቸው የወደፊት ዕጣ ፈንታ ላይ በቀጥታ በመወሰን በየትኛውም ቦታ ይወክለኛል ላሉት ተመራጭ ድምጻቸውን ሰጥተዋል፡፡ በዚህ ሂደት የስልጣን ምንጭ እና ባለቤትነታቸውንም አረጋግጠዋል፡፡
ይህንንም ያደረጉት ዴሞክራሲ ህዝብ - በህዝብ - ለህዝብ የሚመራበት ስርዓት ስለሆነ ነው፡፡ በዚህም ስለራሳቸው ጉዳይ ከባዳ ባእድ በማምጣት ሳይሆን፣ ራሳቸው በራሳቸው ጉዳይ የወሰኑበት ነው፡፡ ዝም ብሎ ለታዘበ ሰው ኢትዮጵያውያን ምርጫ፣ ዜጎች በሀገሪቱ ፖለቲካዊ እና አስተዳደራዊ ውሳኔዎች ላይ በቀጥታ የሚሳተፉበት ዋና መድረክ እንደሆነ እንደገባቸው ይረዳል፡፡ የስልጣን ምንጭ እና ባለቤት እንደሆነም እንዲሁ፡፡ ለዚህም ነው ከአዋካቢዎች ይልቅ በእርጋታ በካርዳቸው የሚወክላቸውን ለመምረጥ የወሰኑት፡፡
ምርጫ ለኢትዮጵያውያን የይስሙላና የቅንጦት አይደለም፡፡ የህልውና ጉዳይ ነው፡፡ የስልጣን ውክልናቸውን የሚያስተላልፉበት መንገድ፡፡ ይህም ነባሩን የኃይል ልማድ ገርስሶ፣ ዴሞክራሲያዊ እሳቤው ሚዛን መድፋቱን ያሳያል፡፡ በምርጫ ድምፅ ተጠቅሞ ውክልናና ስልጣን የሚሰጥበት እና የሚነሳበት መሆኑ ፍንትው ብሎ ታይቶታል፡፡
በምርጫ ወቅት የታየውን የህዝብ መሻት የገባው ተመራጭ እንደ መራጩ ጨዋ ሆኖ ቃሉን ይጠብቃል፡፡ ህዝቡም ትወክለኛለህ ብሎ በድምጹ ስልጣን የሰጠውን አካል፣ ምን ሰራህልኝ ብሎም ይጠይቃል፡፡ ምርጫ ተጠያቂነትን ያረጋግጣል ማለት ነው፡፡ ህዝቡ በስልጣን ላይ ያሉ መሪዎችን ስራ የሚገመግምበት እና ካላገለገሉት በጠብ መንጃ ሳይሆን ምርጫ ሲካሄድ ጠብቆ በሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ መንገድ በካርዱ ይቀጣቸዋል፡፡
የተመራጭ ኃላፊነት ላልመረጠውም ነው፡፡ በዕለቱ እድሜው የደረሰ ዜጋ ያለ ምንም ልዩነት የመምረጥ እና የመመረጥ መብቱን ተጠቅሞ መርጧል፡፡ ያልመረጠውና ድምጹን ለተሸናፊ የሰጠም፣ ዜጋ ስለሆነ እኩል መስተናገድን ይሻል፤ መብቱም ነው፡፡ ቀጣይም ምርጫ አለና፡፡
የዘንድሮው ምርጫ ሂደቱ ትክክለኛ እንደነበር በርካቶች መስክረውለታል፡፡ የምርጫ አስፈጻሚው አካልም ገለልተኛ እና ግልጽ አሰራር ያለው ስለመሆኑ የአፍሪካ ሕብረት፣ የኢጋድና የሀገር ውስጥ የምርጫ ታዛቢዎች መስክረውለታል፡፡ታዛቢዎቹ ምርጫ ቦርድ ገለልተኛነቱን በቅድመ ምርጫና በምርጫ ዕለት ሥራዎች አስመስክሯል ብለዋል፡፡ ቦርዱ ይህንኑ በማጠናከር አሁንም የድህረ ምርጫ ስራዎችን እየሠራ ይገኛል፡፡
ህዝቡ ዴሞክራሲያዊ መንገድ መሻቱን ካርድ በማውጣት፣ በነቂስ ወጥቶ በመምረጥ አሳይቷል፡፡ ይህ የስልጡንነት መገለጫ ነው፡፡ ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር እንዲካሄድ በድምፁ ስለወሰነ፡፡ በዚሁ መሠረት የሚመረጠው አካል ከባድ የቤት ሥራ ይጠብቀዋል፡፡ የልማት፣ የሕግ የበላይነት፣ ሰላምና ደህንነትን የማስፈን፣ አገልግሎት አሰጣጥን ማዘመን፣ ዴሞክራሲያዊ እና ሰብዓዊ መብቶችን ማክበርና ማስከበር፣ ሉዓላዊነት፣ ብሔራዊ ክብር፣ ሀገራዊ አንድነት፣ ብቻ ብዙ ብዙ፡፡
እናማ መራጩ የድርሻውን ከተወጣ፣ ተመራጩ የሚሰጠውን ህጋዊ ውክልና መወጣቱ የግድ ነው፡፡ ውክልናው በየአምስት ዓመቱ የሚታደስ ኮንትራት በመሆኑ፣ ተመራጭ በቅድመ ምርጫ ወቅት በየሚዲያው ቃል የገባውን ሁሉ ህዝቡ ቆጥሮ ይዟል፡፡ አሸናፊነቱ በምርጫ ቦርድ ይፋ ሲደረግና መንግሥት ሲመሠርትም ገና የሚገባው መሀላ አለ፤ ህዝቡ ይህንንም ይከትባል፡፡ቃል የሚገባውም ድምጽ ለሰጠው ብቻ ሳይሆን ላልመረጠውም ነው፡፡ በቀጣይ ልቡን ለመግዛት፡፡ ተመራጩ ቃሉን ከጠበቀ ህዝቡ የስልጣን ምንጭና ባለቤት ስለሆነ የአምስት ዓመት ኮንትራቱን ያድስለታል፡፡ ቃላባይ ከሆነ ግን የካበተ ባህል፣ ታሪክ፣ ፍልስፍናና ጥብቅ ማህበራዊ እሴት ያለው ሰላምና ዴሞክራሲ መወዳዱ ህዝብ በሰላማዊ መንገድ ይወስናል፡፡ ስለዚህ ወደ ስልጣን የሚያደርሰውም የሚመልሰውም መንገድ ቃልን መጠበቅና ምርጫ ብቻ ነው ማለት ነው፡፡
መችም በዘንድሮው ምርጫ ካርድ ወስዶ ምንም ሳያሰናክለው በነቂስ ወጥቶ የመረጠውን ህዝብ ያየና የሰማ ሌላ መንገድ አያስብም፡፡ ወጥቶ ጢሻ ያለውም ቢመለስ፤ ያሰበም ካለ የህዝቡን ስነልቦና የበላይነት ቢረዳ ይበጀዋል፡፡ ምክንያቱም ሥልጣን ለመያዝ ህዝብን ማሳመንና በካርድ መመረጥ ብቻ በቂ ስለሆነ፡፡ የስልጣን ምንጭ እና ባለቤት፣ ሰጪም ነሺም ህዝብ ነውና፡፡
ኑ ሀገር እንሥራ!
የስልጣን ምንጭ እና ባለቤት….
ኢትዮጵያ ሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በተሳካ ሁኔታ አካሂዳለች። በዕለቱ ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ በነፃነት ይወክለኛል የሚለውን በመምረጥ፤ የኃይል አማራጭን ለተከተሉት ጆሮ ባለመስጠት ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መጎለበት ያለውን ውግንና አሳይቷል፡፡
በቅድመ ምርጫ ወቅት መራጩ የተፎካካሪ አካላትን ፖሊሲ፣ ስትራቴጂ እና እሳቤዎች በሚገባ ሲከታተል ቆይቷል፡፡ ሲያሰላስል ቆይቶም በምርጫው ዕለት ይወክለኛል የሚለውን በምስጢር በካርዱ ወስኗል፡፡ አሁን የምርጫውን ውጤት በመጠባበቅ ላይ ይገኛል፡፡ ይህ ዴሞክራሲያዊ እሳቤ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ህዝብ ብዙ የትግል ታሪኮችን አሳልፏል፡፡ ረዥም የሰላምና የልማት መንገድ የሚያስኬደውን አቅሙንም በዚሁ ውስብስብ ሂደት ሲያጣ ኖሯል፡፡ የዘንድሮው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ህዝቡ ከኃይል ይልቅ ሰላምን፣ ከጠብመንጃ ይልቅ የምርጫ ካርድን እንደሚመርጥ በግልጽ አስመስክሯል፡፡ ይህ ለምርጫ ያለው ቦታ እያደገ መምጣቱን ያሳየ ነው፡፡ ለዚያም ነው ብርድ፣ ዝናብ፣ ፀሐይ፣ ህመም፣ ኀዘን፣ ሙቀት፣ እርጅና እና ማስፈራሪያ ሳይገድበው ወጥቶ ድምጹን ይወክለኛል ለሚለውና ለሚሻው የሰጠው፡፡
እኔ አውቅልሀለሁ ለሚሉት፣ አይዞን እኔ ለራሴ አውቃለሁ ብሏል፡፡ ይህ የህልውና ጉዳይ ነው፡፡ የዴሞክራሲ ጥማት፡፡ የጥይት አረር በቃኝ ያለበት ውሳኔ፡፡
ሂደቱን ለማደናቀፍ ግዝትና ግዞት ቢኖርም በዕለቱ ኢትዮጵያውያን በሀገራቸው የወደፊት ዕጣ ፈንታ ላይ በቀጥታ በመወሰን በየትኛውም ቦታ ይወክለኛል ላሉት ተመራጭ ድምጻቸውን ሰጥተዋል፡፡ በዚህ ሂደት የስልጣን ምንጭ እና ባለቤትነታቸውንም አረጋግጠዋል፡፡
ይህንንም ያደረጉት ዴሞክራሲ ህዝብ - በህዝብ - ለህዝብ የሚመራበት ስርዓት ስለሆነ ነው፡፡ በዚህም ስለራሳቸው ጉዳይ ከባዳ ባእድ በማምጣት ሳይሆን፣ ራሳቸው በራሳቸው ጉዳይ የወሰኑበት ነው፡፡ ዝም ብሎ ለታዘበ ሰው ኢትዮጵያውያን ምርጫ፣ ዜጎች በሀገሪቱ ፖለቲካዊ እና አስተዳደራዊ ውሳኔዎች ላይ በቀጥታ የሚሳተፉበት ዋና መድረክ እንደሆነ እንደገባቸው ይረዳል፡፡ የስልጣን ምንጭ እና ባለቤት እንደሆነም እንዲሁ፡፡ ለዚህም ነው ከአዋካቢዎች ይልቅ በእርጋታ በካርዳቸው የሚወክላቸውን ለመምረጥ የወሰኑት፡፡
ምርጫ ለኢትዮጵያውያን የይስሙላና የቅንጦት አይደለም፡፡ የህልውና ጉዳይ ነው፡፡ የስልጣን ውክልናቸውን የሚያስተላልፉበት መንገድ፡፡ ይህም ነባሩን የኃይል ልማድ ገርስሶ፣ ዴሞክራሲያዊ እሳቤው ሚዛን መድፋቱን ያሳያል፡፡ በምርጫ ድምፅ ተጠቅሞ ውክልናና ስልጣን የሚሰጥበት እና የሚነሳበት መሆኑ ፍንትው ብሎ ታይቶታል፡፡
በምርጫ ወቅት የታየውን የህዝብ መሻት የገባው ተመራጭ እንደ መራጩ ጨዋ ሆኖ ቃሉን ይጠብቃል፡፡ ህዝቡም ትወክለኛለህ ብሎ በድምጹ ስልጣን የሰጠውን አካል፣ ምን ሰራህልኝ ብሎም ይጠይቃል፡፡ ምርጫ ተጠያቂነትን ያረጋግጣል ማለት ነው፡፡ ህዝቡ በስልጣን ላይ ያሉ መሪዎችን ስራ የሚገመግምበት እና ካላገለገሉት በጠብ መንጃ ሳይሆን ምርጫ ሲካሄድ ጠብቆ በሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ መንገድ በካርዱ ይቀጣቸዋል፡፡
የተመራጭ ኃላፊነት ላልመረጠውም ነው፡፡ በዕለቱ እድሜው የደረሰ ዜጋ ያለ ምንም ልዩነት የመምረጥ እና የመመረጥ መብቱን ተጠቅሞ መርጧል፡፡ ያልመረጠውና ድምጹን ለተሸናፊ የሰጠም፣ ዜጋ ስለሆነ እኩል መስተናገድን ይሻል፤ መብቱም ነው፡፡ ቀጣይም ምርጫ አለና፡፡
የዘንድሮው ምርጫ ሂደቱ ትክክለኛ እንደነበር በርካቶች መስክረውለታል፡፡ የምርጫ አስፈጻሚው አካልም ገለልተኛ እና ግልጽ አሰራር ያለው ስለመሆኑ የአፍሪካ ሕብረት፣ የኢጋድና የሀገር ውስጥ የምርጫ ታዛቢዎች መስክረውለታል፡፡ታዛቢዎቹ ምርጫ ቦርድ ገለልተኛነቱን በቅድመ ምርጫና በምርጫ ዕለት ሥራዎች አስመስክሯል ብለዋል፡፡ ቦርዱ ይህንኑ በማጠናከር አሁንም የድህረ ምርጫ ስራዎችን እየሠራ ይገኛል፡፡
ህዝቡ ዴሞክራሲያዊ መንገድ መሻቱን ካርድ በማውጣት፣ በነቂስ ወጥቶ በመምረጥ አሳይቷል፡፡ ይህ የስልጡንነት መገለጫ ነው፡፡ ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር እንዲካሄድ በድምፁ ስለወሰነ፡፡ በዚሁ መሠረት የሚመረጠው አካል ከባድ የቤት ሥራ ይጠብቀዋል፡፡ የልማት፣ የሕግ የበላይነት፣ ሰላምና ደህንነትን የማስፈን፣ አገልግሎት አሰጣጥን ማዘመን፣ ዴሞክራሲያዊ እና ሰብዓዊ መብቶችን ማክበርና ማስከበር፣ ሉዓላዊነት፣ ብሔራዊ ክብር፣ ሀገራዊ አንድነት፣ ብቻ ብዙ ብዙ፡፡
እናማ መራጩ የድርሻውን ከተወጣ፣ ተመራጩ የሚሰጠውን ህጋዊ ውክልና መወጣቱ የግድ ነው፡፡ ውክልናው በየአምስት ዓመቱ የሚታደስ ኮንትራት በመሆኑ፣ ተመራጭ በቅድመ ምርጫ ወቅት በየሚዲያው ቃል የገባውን ሁሉ ህዝቡ ቆጥሮ ይዟል፡፡ አሸናፊነቱ በምርጫ ቦርድ ይፋ ሲደረግና መንግሥት ሲመሠርትም ገና የሚገባው መሀላ አለ፤ ህዝቡ ይህንንም ይከትባል፡፡ቃል የሚገባውም ድምጽ ለሰጠው ብቻ ሳይሆን ላልመረጠውም ነው፡፡ በቀጣይ ልቡን ለመግዛት፡፡ ተመራጩ ቃሉን ከጠበቀ ህዝቡ የስልጣን ምንጭና ባለቤት ስለሆነ የአምስት ዓመት ኮንትራቱን ያድስለታል፡፡ ቃላባይ ከሆነ ግን የካበተ ባህል፣ ታሪክ፣ ፍልስፍናና ጥብቅ ማህበራዊ እሴት ያለው ሰላምና ዴሞክራሲ መወዳዱ ህዝብ በሰላማዊ መንገድ ይወስናል፡፡ ስለዚህ ወደ ስልጣን የሚያደርሰውም የሚመልሰውም መንገድ ቃልን መጠበቅና ምርጫ ብቻ ነው ማለት ነው፡፡
መችም በዘንድሮው ምርጫ ካርድ ወስዶ ምንም ሳያሰናክለው በነቂስ ወጥቶ የመረጠውን ህዝብ ያየና የሰማ ሌላ መንገድ አያስብም፡፡ ወጥቶ ጢሻ ያለውም ቢመለስ፤ ያሰበም ካለ የህዝቡን ስነልቦና የበላይነት ቢረዳ ይበጀዋል፡፡ ምክንያቱም ሥልጣን ለመያዝ ህዝብን ማሳመንና በካርድ መመረጥ ብቻ በቂ ስለሆነ፡፡ የስልጣን ምንጭ እና ባለቤት፣ ሰጪም ነሺም ህዝብ ነውና፡፡
ኑ ሀገር እንሥራ!
15 hours ago
ችሎት ውስጥ የተፈፀመ አሰቃቂ ግድያ‼
ዛሬ ረፋድ ላይ በሆለታ ወልመራ ወረዳ ፍርድ ቤት ውስጥ በተፈጸመ ጥቃት፣ የዕለቱን የችሎት ውሳኔ በማንበብ ላይ የነበሩ ዳኛ እና አንዲት ተከራካሪ ህይወታቸው ማለፉን አክሰስ ቱ ጃስቲስ ኢኒሼቲቭ - ኢትዮጵያ አስታውቋል።
እንደ ምንጩ መረጃ፣ የቤተሰብ ክርክር ጉዳይን በመመልከት ላይ የነበሩት ዳኛ ወርቄ ፈካንሳ የፍርድ ውሳኔውን እያነበቡ ባሉበት ወቅት፣ ተከሳሹ በድንገት ባወጣው ሽጉጥ ዳኛዋን በጥይት በመምታት ህይወታቸውን ቀጥፏል።
በዚሁ አጋጣሚ በችሎቱ ላይ በጉዳዩ ላይ ይከራከሩ የነበሩት (ተከራካሪዋ) በተመሳሳይ ሁኔታ በተከሳሹ በተተኮሰ ጥይት ወዲያውኑ ህይወታቸው አልፏል።
የሕግ ባለሙያዎችና ማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ድርጊቱን በጽኑ ያኮነኑ ሲሆን፤ ዳኞችና የሕግ ባለሙያዎች በሥራ ገበታቸው ላይ አስተማማኝ የደህንነት ጥበቃ ሊደረግላቸው እንደሚገባ በርካቶች በመጻፍ ላይ ይገኛሉ።
“አንድ ግለሰብ ታጥቆ ወደ ፍርድ ቤት አዳራሽ መግባት መቻሉ፣ የፍርድ ቤቶችን የጸጥታና የፍተሻ አሰራር ምን ያህል ደካማ እንደሆነ በአሳዛኝ ሁኔታ አሳይቷል” በማለት አክሰስ ቱ ጃስቲስ ኢኒሼቲቭ የድርጊቱን አሳሳቢነት ገልጿል።
Seledadotio
Seledadotio
ዛሬ ረፋድ ላይ በሆለታ ወልመራ ወረዳ ፍርድ ቤት ውስጥ በተፈጸመ ጥቃት፣ የዕለቱን የችሎት ውሳኔ በማንበብ ላይ የነበሩ ዳኛ እና አንዲት ተከራካሪ ህይወታቸው ማለፉን አክሰስ ቱ ጃስቲስ ኢኒሼቲቭ - ኢትዮጵያ አስታውቋል።
እንደ ምንጩ መረጃ፣ የቤተሰብ ክርክር ጉዳይን በመመልከት ላይ የነበሩት ዳኛ ወርቄ ፈካንሳ የፍርድ ውሳኔውን እያነበቡ ባሉበት ወቅት፣ ተከሳሹ በድንገት ባወጣው ሽጉጥ ዳኛዋን በጥይት በመምታት ህይወታቸውን ቀጥፏል።
በዚሁ አጋጣሚ በችሎቱ ላይ በጉዳዩ ላይ ይከራከሩ የነበሩት (ተከራካሪዋ) በተመሳሳይ ሁኔታ በተከሳሹ በተተኮሰ ጥይት ወዲያውኑ ህይወታቸው አልፏል።
የሕግ ባለሙያዎችና ማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ድርጊቱን በጽኑ ያኮነኑ ሲሆን፤ ዳኞችና የሕግ ባለሙያዎች በሥራ ገበታቸው ላይ አስተማማኝ የደህንነት ጥበቃ ሊደረግላቸው እንደሚገባ በርካቶች በመጻፍ ላይ ይገኛሉ።
“አንድ ግለሰብ ታጥቆ ወደ ፍርድ ቤት አዳራሽ መግባት መቻሉ፣ የፍርድ ቤቶችን የጸጥታና የፍተሻ አሰራር ምን ያህል ደካማ እንደሆነ በአሳዛኝ ሁኔታ አሳይቷል” በማለት አክሰስ ቱ ጃስቲስ ኢኒሼቲቭ የድርጊቱን አሳሳቢነት ገልጿል።
Seledadotio
Seledadotio
20 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) አሜሪካ ከሶማሊላንድ ጋር ያላትን ግንኙነት በይፋዊ የዲፕሎማሲ እውቅና ላይ ሳይሆን በተግባራዊ የኢኮኖሚና የደህንነት አጋርነት ላይ መሠረት በማድረግ እያሳደገች መምጣቷን አንድ አዲስ የጥናት ሰነድ አጋለጠ። ተመራማሪ ሳሚያ መሐመድ ባቀረቡት በዚህ ትንተና አሜሪካ የሶማሊያን የግዛት አንድነትና ሉዓላዊነት በይፋዊ መግለጫዎቿ ብታስከብርም፤ በተግባር ግን የሶማሊላንድን አስተማማኝ የደህንነትና የኢኮኖሚ አጋርነት በመገንዘብ ግንኙነቷን ደረጃ በደረጃ እያሻሻለች ይገኛል።
ይህ የፖሊሲ ለውጥ ድንገተኛ ወይም አብዮታዊ ሳይሆን የሶማሊላንድን መረጋጋት፣ የአስተዳደር አቅምና ስትራቴጂካዊ መልክዓ ምድር ግምት ውስጥ ያስገባ ቀስ በቀስ የሚደረግ የፖሊሲ ማስተካከያ መሆኑ ተጠቅሷል። በተለይም የበርበራ ወደብ በአካባቢው ካሉ መጨናነቅ የሚታይባቸው ወደቦች እንደ አማራጭ ሆኖ ማገልገል መቻሉ እና ለንግድና ትራንስፖርት ያለው ከፍተኛ ጠቀሜታ በአሜሪካ መንግሥት በኩል አዎንታዊ እይታን አትርፎለታል። ሆኖም ይህ አካሄድ በሞቃዲሾ ከሚገኘው የሶማሊያ ፌዴራላዊ መንግሥት ጋር ውጥረት ላለመፍጠር ሲባል፣ ሙሉ የዲፕሎማሲ እውቅና ከመስጠት ይልቅ በጥንቃቄ የተመጠነ የመካከለኛ መንገድ ስትራቴጂን የሚከተል ነው።
ጥናቱ እንደሚያብራራው በዘመናዊው የዓለም አቀፍ ግንኙነት አገራት አጋሮቻቸውን የሚመዝኑት በይፋዊ የዲፕሎማሲ ማዕረጋቸው ብቻ ሳይሆን፣ በተግባራዊ ብቃታቸው፣ አስተማማኝነታቸውና አገልግሎት ሰጪነታቸው ነው። በዚህ ረገድ ሶማሊላንድ መረጋጋትን በማስፈን፣ የጸረ-ሽብር ግቦችን በመደገፍ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎችን በማቀላጠፍ ያሳየችው አንጻራዊ ስኬት፣ ለአሜሪካ ተመራጭ እና ጠቃሚ ተግባራዊ አጋር እንድትሆን አስችሏታል። ይህ ማለት የፖለቲካው ሉዓላዊነት ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ተመልሷል ማለት ሳይሆን፣ መሬት ላይ ካለው እውነታ ጋር የሚጣጣም የፖሊሲ አተገባበር እየታየ መሆኑን ያሳያል።
በሌላ በኩል ጥናቱ ለሶማሊላንድ የማስጠንቀቂያ መልእክትም አስተላልፏል። ምቹ መልክዓ ምድር ወይም ስትራቴጂካዊ ቦታ መኖር ብቻውን ቀጣይነት ላለው ዓለም አቀፍ ትብብር ዋስትና እንደማይሆን እና ይህም ጠንካራ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የደህንነት ተቋማዊ አቅምን በማጎልበት መታገዝ እንዳለበት አሳስቧል። በተጨማሪም ይህ የአሜሪካ አዲስ አካሄድ በአካባቢው ሀገራት በተለይም በጅቡቲ ላይ ጫና ሊፈጥር እንደሚችል ተጠቁሟል። የአሜሪካ አማራጭ የመሠረተ ልማት ማዕከሎችን መፈለግ የጅቡቲን ጠቀሜታ ባያሳጣም፣ ቀጠናዊ ፉክክሩን በማጠናከር ሀገራቱ ተወዳዳሪነታቸውን እንዲያሳድጉ ያስገድዳቸዋል ተብሏል።
አሜሪካ የሶማሊላንድን ጉዳይ ከዳር እንደቆመ የፖለቲካ ጥያቄ ከማየት ይልቅ፣ በቀጠናው የደህንነትና የኢኮኖሚ ዕድገት ላይ ጉልህ አስተዋጽኦ ሊያበረክት የሚችል ወሳኝ ተዋናይ አድርጋ እየቆጠረችው መምጣቷን የጥናት ሰነዱ ያትታል። ይህ ሂደት በቅርብ ጊዜ ውስጥ የሕግ እና የዲፕሎማሲ እውቅናን ላያመጣ ቢችልም፣ በአፍሪካ ቀንድ ጂኦ-ፖለቲካ ውስጥ ሶማሊላንድ ያላት ሥፍራ እያደገ መምጣቱን የሚያሳይ ታሪካዊ ማሳያ መሆኑ ተገልጿል።
ይህ የፖሊሲ ለውጥ ድንገተኛ ወይም አብዮታዊ ሳይሆን የሶማሊላንድን መረጋጋት፣ የአስተዳደር አቅምና ስትራቴጂካዊ መልክዓ ምድር ግምት ውስጥ ያስገባ ቀስ በቀስ የሚደረግ የፖሊሲ ማስተካከያ መሆኑ ተጠቅሷል። በተለይም የበርበራ ወደብ በአካባቢው ካሉ መጨናነቅ የሚታይባቸው ወደቦች እንደ አማራጭ ሆኖ ማገልገል መቻሉ እና ለንግድና ትራንስፖርት ያለው ከፍተኛ ጠቀሜታ በአሜሪካ መንግሥት በኩል አዎንታዊ እይታን አትርፎለታል። ሆኖም ይህ አካሄድ በሞቃዲሾ ከሚገኘው የሶማሊያ ፌዴራላዊ መንግሥት ጋር ውጥረት ላለመፍጠር ሲባል፣ ሙሉ የዲፕሎማሲ እውቅና ከመስጠት ይልቅ በጥንቃቄ የተመጠነ የመካከለኛ መንገድ ስትራቴጂን የሚከተል ነው።
ጥናቱ እንደሚያብራራው በዘመናዊው የዓለም አቀፍ ግንኙነት አገራት አጋሮቻቸውን የሚመዝኑት በይፋዊ የዲፕሎማሲ ማዕረጋቸው ብቻ ሳይሆን፣ በተግባራዊ ብቃታቸው፣ አስተማማኝነታቸውና አገልግሎት ሰጪነታቸው ነው። በዚህ ረገድ ሶማሊላንድ መረጋጋትን በማስፈን፣ የጸረ-ሽብር ግቦችን በመደገፍ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎችን በማቀላጠፍ ያሳየችው አንጻራዊ ስኬት፣ ለአሜሪካ ተመራጭ እና ጠቃሚ ተግባራዊ አጋር እንድትሆን አስችሏታል። ይህ ማለት የፖለቲካው ሉዓላዊነት ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ተመልሷል ማለት ሳይሆን፣ መሬት ላይ ካለው እውነታ ጋር የሚጣጣም የፖሊሲ አተገባበር እየታየ መሆኑን ያሳያል።
በሌላ በኩል ጥናቱ ለሶማሊላንድ የማስጠንቀቂያ መልእክትም አስተላልፏል። ምቹ መልክዓ ምድር ወይም ስትራቴጂካዊ ቦታ መኖር ብቻውን ቀጣይነት ላለው ዓለም አቀፍ ትብብር ዋስትና እንደማይሆን እና ይህም ጠንካራ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የደህንነት ተቋማዊ አቅምን በማጎልበት መታገዝ እንዳለበት አሳስቧል። በተጨማሪም ይህ የአሜሪካ አዲስ አካሄድ በአካባቢው ሀገራት በተለይም በጅቡቲ ላይ ጫና ሊፈጥር እንደሚችል ተጠቁሟል። የአሜሪካ አማራጭ የመሠረተ ልማት ማዕከሎችን መፈለግ የጅቡቲን ጠቀሜታ ባያሳጣም፣ ቀጠናዊ ፉክክሩን በማጠናከር ሀገራቱ ተወዳዳሪነታቸውን እንዲያሳድጉ ያስገድዳቸዋል ተብሏል።
አሜሪካ የሶማሊላንድን ጉዳይ ከዳር እንደቆመ የፖለቲካ ጥያቄ ከማየት ይልቅ፣ በቀጠናው የደህንነትና የኢኮኖሚ ዕድገት ላይ ጉልህ አስተዋጽኦ ሊያበረክት የሚችል ወሳኝ ተዋናይ አድርጋ እየቆጠረችው መምጣቷን የጥናት ሰነዱ ያትታል። ይህ ሂደት በቅርብ ጊዜ ውስጥ የሕግ እና የዲፕሎማሲ እውቅናን ላያመጣ ቢችልም፣ በአፍሪካ ቀንድ ጂኦ-ፖለቲካ ውስጥ ሶማሊላንድ ያላት ሥፍራ እያደገ መምጣቱን የሚያሳይ ታሪካዊ ማሳያ መሆኑ ተገልጿል።
Sponsored by
Surafel
20 hours ago
በአዲስ አበባ ከተማ ወተትን ጨምሮ የባልትና ውጤቶችን ከበዓድ ነገሮች ጋር የመቀላቀል ተግባር በስፋት እየተስተዋለ ይገኛል ተባለ
#ethiopia | በአዲስ አበባ ከተማ ወተት ፣ ማር ፣ ቅቤን ጨምሮ ሌሎች የባልትና ውጤቶችን ከበዓድ ነገሮች ጋር የመቀላቀል ድርጊት በስፋት እንደሚስተዋል የአዲስ አበባ ከተማ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን አስታውቋል።ከብስራት ሬዲዮ ጋር ቆይታ ያደረጉት በባለስልጣኑ የምግብና ጤና ነክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት አቶ እስጢፋኖስ ጌታቸው እንደገለፁት የምግብ ክለሳ የምግብን ጥራትና ደህንነት ወይም ንጥረ ይዘት የሚያሳንስ ህገወጥ ድርጊት ነው።
ይህም ለትርፍ ሲባል ውሃ፣ ኬሚካል እና ሌሎች ያልተፈቀዱ ንጥረ ነገሮችን ወደ ምግብ በመጨመር የምግብን ተፈጥሯዊ ይዘት መለወጥ መሆኑን አስረድተዋል ።ይህ አይነቱ ተግባር የምግብ መመረዝን፣ የሆድና የአንጀት ሕመሞችን፣ የጉበትና የኩላሊት ጉዳት እንዲሁም የረጅም ጊዜ የጤና ችግሮችን ሊያስከትል እንደሚችል ተጠቁሟል ።
ባለስልጣኑ ይህን ችግር ለመቆጣጠር መደበኛ ፍተሻ፣ የላብራቶሪ ምርመራ እና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ አቶ እስጢፋኖስ ገልፀው በህግ ላይ የተመሰረቱ የክትትል እርምጃዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ጨምረው ለጣቢያችን ተናግረዋል ።
በተጨማሪም በህገወጥ የምግብ ክለሳ ተግባር ላይ የተሰማሩ አካላት ሲገኙ ምርቶቻቸውን የማስወገድ ፣ የንግድ ፈቃዳቸውን የማገድና የመሰረዝ እንዲሁም ሌሎች ህጋዊ እርምጃዎች እንደሚወሰድባቸው ባለስልጣኑ አስታውቋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | በአዲስ አበባ ከተማ ወተት ፣ ማር ፣ ቅቤን ጨምሮ ሌሎች የባልትና ውጤቶችን ከበዓድ ነገሮች ጋር የመቀላቀል ድርጊት በስፋት እንደሚስተዋል የአዲስ አበባ ከተማ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን አስታውቋል።ከብስራት ሬዲዮ ጋር ቆይታ ያደረጉት በባለስልጣኑ የምግብና ጤና ነክ ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት አቶ እስጢፋኖስ ጌታቸው እንደገለፁት የምግብ ክለሳ የምግብን ጥራትና ደህንነት ወይም ንጥረ ይዘት የሚያሳንስ ህገወጥ ድርጊት ነው።
ይህም ለትርፍ ሲባል ውሃ፣ ኬሚካል እና ሌሎች ያልተፈቀዱ ንጥረ ነገሮችን ወደ ምግብ በመጨመር የምግብን ተፈጥሯዊ ይዘት መለወጥ መሆኑን አስረድተዋል ።ይህ አይነቱ ተግባር የምግብ መመረዝን፣ የሆድና የአንጀት ሕመሞችን፣ የጉበትና የኩላሊት ጉዳት እንዲሁም የረጅም ጊዜ የጤና ችግሮችን ሊያስከትል እንደሚችል ተጠቁሟል ።
ባለስልጣኑ ይህን ችግር ለመቆጣጠር መደበኛ ፍተሻ፣ የላብራቶሪ ምርመራ እና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ አቶ እስጢፋኖስ ገልፀው በህግ ላይ የተመሰረቱ የክትትል እርምጃዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ጨምረው ለጣቢያችን ተናግረዋል ።
በተጨማሪም በህገወጥ የምግብ ክለሳ ተግባር ላይ የተሰማሩ አካላት ሲገኙ ምርቶቻቸውን የማስወገድ ፣ የንግድ ፈቃዳቸውን የማገድና የመሰረዝ እንዲሁም ሌሎች ህጋዊ እርምጃዎች እንደሚወሰድባቸው ባለስልጣኑ አስታውቋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
21 hours ago
አዲስ አበባ ፡ የኤምኤምኤ እና የቦክስ ስፖርት ውድድር ሊካሄድ ነው
#ethiopia | በአዲስ አበባ ከተማ ከዚህ ቀደም ከተደረጉት የንክኪ ስፖርት ሁነቶች ሁሉ እጅግ ግዙፍ የሆነው የኢትዮ ፋይት ናይት የውድድር መድረክ ይፋ ሆኗል::
ዝግጅቱ የአዲስ አበባ ኪክ ቦክስ ፌዴሬሽን፣ የአዲስ አበባ ቦክስ ፌዴሬሽን እና የአዲስ አበባ ወጣቶች ስፖርት ቢሮ በጋራ በመተባበር ያዘጋጁት ሲሆን ነሀሴ 23 ቀን 2018 ዓ.ም (Aug 29/2026) በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቤንሽን ሴንተር በደመቀ ሁኔታ ይካሄዳል::
በዚህ ልዩ ስፖርታዊ ፌስቲቫል ላይ በድብልቅ ማርሻል አርት (MMA) ዘርፍ ዓለም አቀፍ እውቅና ያላቸው የውጭ ሀገር ተወዳዳሪዎች የሚሳተፉ ሲሆን ሀገራችንን ወክለው ደግሞ ቢኒያም ሽብሬ፣ ክብሮም ንጉሴ እና አገረሰላም አርባን ጨምሮ በርካታ ስፖርተኞች ወደ መድረኩ ይወርዳሉ::
በጠቅላላው ከ6 እስከ 8 የሚደርሱ ብርቱ ፍልሚያዎች የሚስተናገዱ ሲሆን ተወዳዳሪዎቹ የተመረጡት በውድድር ታሪካቸው፣ በዓለም አቀፍ ልምዳቸው፣ በአካል ብቃት ጥንካሬያቸው እና ማራኪ ትዕይንት ማሳየት በሚችሉበት ብቃታቸው ላይ ተመስርቶ ነው::
አትሌቶቹ በፌዴሬሽኑ ህግ መሰረት አስፈላጊውን የህክምና ምርመራ፣ የክብደት ልኬትና የፈቃድ አሰጣጥ ሂደቶችን ያጠናቀቁ ሲሆን ዝርዝር የክብደት መጠናቸውና ዜግነታቸው በቅርቡ ይፋ ይደረጋል::
ይህንን ታሪካዊ ፍልሚያ ለመታደም ከ8,000 እስከ 10,000 የሚደርሱ የስፖርት አፍቃሪዎች በአዳራሹ ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል::
አዘጋጆቹ የአፍሪካንና የሀገራችንን ስፖርታዊ አቅም ለዓለም የሚያስተዋውቅ፣ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀና ፍጹም ሙያዊ ብቃት የተላበሰ ዝግጅት ለማቅረብ የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ መድረሳቸውን ገልጸዋል::
የውድድሩ ዋነኛ ዓላማ የንክኪ ስፖርቶችን ከማሳደግ ባለፈ ለሀገር ውስጥ አትሌቶች ሙያዊ መድረክ መፍጠር፣ ወጣቶችን ማነሳሳት፣ ስፖርታዊ ቱሪዝምን በአዲስ አበባና በኢትዮጵያ ማስፋፋት እንዲሁም ሀገራችንን የዓለም አቀፍ ውድድሮች ማዕከል ማድረግ ነው::
ዝግጅቱ የሚስተናገድበት አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቤንሽን ሴንተር (AICC) ዘመናዊ የዲጂታል ምስልና የድምፅ መገልገያ መሳሪያዎች የተሟሉለት በመሆኑ ለታዳሚው ምቹ መዝናኛን ለመፍጠር ተመራጭ አድርጎታል::
ገራሚ ኢቨንትስ የዝግጅቱን አጠቃላይ የፕሮዳክሽን ስራ በማስተናገድ ከባለቤቶቹ ጋር በጋራ የሚሰራ ሲሆን ለአትሌቶች ስልጠና፣ ለደህንነት፣ ለቦታ ዝግጅትና ለሎጂስቲክስ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ፈሷል::
ይህንን ውድድር በኢትዮጵያና በአፍሪካ ደረጃ ተከታታይነት ባለው መልኩ ለማዘጋጀት የታቀደ በመሆኑ፣ የዝግጅቱን ጥራት ይበልጥ ለማሳደግ ሀገር በቀልና ዓለም አቀፍ ተቋማት በስፖንሰርሺፕ፣ በሚዲያ ሽፋን፣ በዲጂታል ግብይትና በቪአይፒ ተሳትፎ ላይ አብረው እንዲሰሩ ጥሪ ቀርቧል::
የመግቢያ ትኬት ዋጋንና የስርጭት ሽፋንን በተመለከተ ከሚዲያ አጋሮች ጋር ውይይት እየተደረገ ሲሆን የቴሌቪዥንና የዲጂታል ቀጥታ ስርጭት መረጃዎች በቅርቡ ይፋ የሚደረጉ ይሆናል::
#mma #boxing #ethiofightnight #sportstourism #aicc #ethiopianathletes #geramievents #sports #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በአዲስ አበባ ከተማ ከዚህ ቀደም ከተደረጉት የንክኪ ስፖርት ሁነቶች ሁሉ እጅግ ግዙፍ የሆነው የኢትዮ ፋይት ናይት የውድድር መድረክ ይፋ ሆኗል::
ዝግጅቱ የአዲስ አበባ ኪክ ቦክስ ፌዴሬሽን፣ የአዲስ አበባ ቦክስ ፌዴሬሽን እና የአዲስ አበባ ወጣቶች ስፖርት ቢሮ በጋራ በመተባበር ያዘጋጁት ሲሆን ነሀሴ 23 ቀን 2018 ዓ.ም (Aug 29/2026) በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቤንሽን ሴንተር በደመቀ ሁኔታ ይካሄዳል::
በዚህ ልዩ ስፖርታዊ ፌስቲቫል ላይ በድብልቅ ማርሻል አርት (MMA) ዘርፍ ዓለም አቀፍ እውቅና ያላቸው የውጭ ሀገር ተወዳዳሪዎች የሚሳተፉ ሲሆን ሀገራችንን ወክለው ደግሞ ቢኒያም ሽብሬ፣ ክብሮም ንጉሴ እና አገረሰላም አርባን ጨምሮ በርካታ ስፖርተኞች ወደ መድረኩ ይወርዳሉ::
በጠቅላላው ከ6 እስከ 8 የሚደርሱ ብርቱ ፍልሚያዎች የሚስተናገዱ ሲሆን ተወዳዳሪዎቹ የተመረጡት በውድድር ታሪካቸው፣ በዓለም አቀፍ ልምዳቸው፣ በአካል ብቃት ጥንካሬያቸው እና ማራኪ ትዕይንት ማሳየት በሚችሉበት ብቃታቸው ላይ ተመስርቶ ነው::
አትሌቶቹ በፌዴሬሽኑ ህግ መሰረት አስፈላጊውን የህክምና ምርመራ፣ የክብደት ልኬትና የፈቃድ አሰጣጥ ሂደቶችን ያጠናቀቁ ሲሆን ዝርዝር የክብደት መጠናቸውና ዜግነታቸው በቅርቡ ይፋ ይደረጋል::
ይህንን ታሪካዊ ፍልሚያ ለመታደም ከ8,000 እስከ 10,000 የሚደርሱ የስፖርት አፍቃሪዎች በአዳራሹ ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል::
አዘጋጆቹ የአፍሪካንና የሀገራችንን ስፖርታዊ አቅም ለዓለም የሚያስተዋውቅ፣ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀና ፍጹም ሙያዊ ብቃት የተላበሰ ዝግጅት ለማቅረብ የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ መድረሳቸውን ገልጸዋል::
የውድድሩ ዋነኛ ዓላማ የንክኪ ስፖርቶችን ከማሳደግ ባለፈ ለሀገር ውስጥ አትሌቶች ሙያዊ መድረክ መፍጠር፣ ወጣቶችን ማነሳሳት፣ ስፖርታዊ ቱሪዝምን በአዲስ አበባና በኢትዮጵያ ማስፋፋት እንዲሁም ሀገራችንን የዓለም አቀፍ ውድድሮች ማዕከል ማድረግ ነው::
ዝግጅቱ የሚስተናገድበት አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቤንሽን ሴንተር (AICC) ዘመናዊ የዲጂታል ምስልና የድምፅ መገልገያ መሳሪያዎች የተሟሉለት በመሆኑ ለታዳሚው ምቹ መዝናኛን ለመፍጠር ተመራጭ አድርጎታል::
ገራሚ ኢቨንትስ የዝግጅቱን አጠቃላይ የፕሮዳክሽን ስራ በማስተናገድ ከባለቤቶቹ ጋር በጋራ የሚሰራ ሲሆን ለአትሌቶች ስልጠና፣ ለደህንነት፣ ለቦታ ዝግጅትና ለሎጂስቲክስ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ ፈሷል::
ይህንን ውድድር በኢትዮጵያና በአፍሪካ ደረጃ ተከታታይነት ባለው መልኩ ለማዘጋጀት የታቀደ በመሆኑ፣ የዝግጅቱን ጥራት ይበልጥ ለማሳደግ ሀገር በቀልና ዓለም አቀፍ ተቋማት በስፖንሰርሺፕ፣ በሚዲያ ሽፋን፣ በዲጂታል ግብይትና በቪአይፒ ተሳትፎ ላይ አብረው እንዲሰሩ ጥሪ ቀርቧል::
የመግቢያ ትኬት ዋጋንና የስርጭት ሽፋንን በተመለከተ ከሚዲያ አጋሮች ጋር ውይይት እየተደረገ ሲሆን የቴሌቪዥንና የዲጂታል ቀጥታ ስርጭት መረጃዎች በቅርቡ ይፋ የሚደረጉ ይሆናል::
#mma #boxing #ethiofightnight #sportstourism #aicc #ethiopianathletes #geramievents #sports #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
1 day ago
የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በአርሲ በንጹሃን ላይ የተፈጸመውን ግድያና ቃጠሎ አወገዘ
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በአርሲ ዞን አሰኮ፣ ሽርካ፣ ሆንቆሎ፣ ዋቤ እና ሙኔሳ ወረዳዎች በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችና ምዕመናን ላይ የተፈጸመውን አሰቃቂ ግድያ እና የአብያተ ክርስቲያናት ቃጠሎ በጽኑ ማውገዙን አስታወቀ።
ጉባኤው በጥቃቱ የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን ገልጾ፣ ለተጎጂ ቤተሰቦች መጽናናትን ተመኝቷል።
ቀደም ሲል ተመሳሳይ ጥቃቶች እንዳይፈጸሙ ጥበቃ እንዲደረግ መጠየቁን ያስታወሰው ጉባኤው፣ አሁንም ችግሩ ባለመቀረፉ ተጨማሪ ጉዳት መድረሱ ሃዘኑን እጥፍ ድርብ እንዳደረገው ገልጿል።
በመሆኑም መንግሥት የዜጎችን ደህንነት የማረጋገጥ ተቀዳሚ ኃላፊነቱን እንዲወጣ፣ ለተፈናቀሉና ስጋት ላለባቸው ዜጎች አስተማማኝ ጥበቃ እንዲያደርግ እንዲሁም ወንጀለኞችን በአፋጣኝ ለፍርድ እንዲያቀርብ በጥብቅ አሳስቧል።
አባል ተቋማት ድርጊቱን በአንድነት እንዲያወግዙና የአካባቢው ማህበረሰብም በጋራ እንዲተጋገዝ ጥሪ አቅርቧል።
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በአርሲ ዞን አሰኮ፣ ሽርካ፣ ሆንቆሎ፣ ዋቤ እና ሙኔሳ ወረዳዎች በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችና ምዕመናን ላይ የተፈጸመውን አሰቃቂ ግድያ እና የአብያተ ክርስቲያናት ቃጠሎ በጽኑ ማውገዙን አስታወቀ።
ጉባኤው በጥቃቱ የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን ገልጾ፣ ለተጎጂ ቤተሰቦች መጽናናትን ተመኝቷል።
ቀደም ሲል ተመሳሳይ ጥቃቶች እንዳይፈጸሙ ጥበቃ እንዲደረግ መጠየቁን ያስታወሰው ጉባኤው፣ አሁንም ችግሩ ባለመቀረፉ ተጨማሪ ጉዳት መድረሱ ሃዘኑን እጥፍ ድርብ እንዳደረገው ገልጿል።
በመሆኑም መንግሥት የዜጎችን ደህንነት የማረጋገጥ ተቀዳሚ ኃላፊነቱን እንዲወጣ፣ ለተፈናቀሉና ስጋት ላለባቸው ዜጎች አስተማማኝ ጥበቃ እንዲያደርግ እንዲሁም ወንጀለኞችን በአፋጣኝ ለፍርድ እንዲያቀርብ በጥብቅ አሳስቧል።
አባል ተቋማት ድርጊቱን በአንድነት እንዲያወግዙና የአካባቢው ማህበረሰብም በጋራ እንዲተጋገዝ ጥሪ አቅርቧል።
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ልዑክ በኢትዮጵያ ጁን 1 ቀን 2026 በተካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ ያደረገውን ምልከታ መነሻ በማድረግ የመጀመሪያ ደረጃ መግለጫውን ጁን 3 ቀን 2026 በአዲስ አበባ ከተማ ይፋ አድርጓል።
ልዑኩ በቀድሞው የኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የተመራ ሲሆን፣ በቀድሞው የናይጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጄፍሪ ኦንያማ ደግሞ በምክትል ኃላፊነት ተደግፏል። ቡድኑ 61 በመቶ ሴቶችን ያካተተ 73 የአጭር ጊዜ ታዛቢዎችን የያዘ ሲሆን፣ ከ35 የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡት እነዚህ ታዛቢዎች አዲስ አበባ፣ ኦሮሚያ፣ ድሬዳዋ፣ ሲዳማ፣ ደቡብ ኢትዮጵያ፣ ሐረሪ፣ ቤንሻንጉል ጉሙዝ እና ሶማሌን ጨምሮ በስምንት የኢትዮጵያ ክልሎች ስምሪት አድርገዋል። በአጠቃላይ 27 የታዛቢ ቡድኖች በ38 የምርጫ ክልሎች በሚገኙ 495 የምርጫ ጣቢያዎች ተዘዋውረው የድምጽ አሰጣጥ ሂደቱን በቅርበት ታዝበዋል።
ከምርጫው በፊት የነበሩ ሁኔታዎችን በተመለከተ መግለጫው እንዳብራራው፣ ለምርጫው 54 በመቶ ወንዶች እና 46 በመቶ ሴቶችን ያካተተ 50.5 ሚሊዮን መራጮች የተመዘገቡ ሲሆን፣ ይህ አሃዝ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስቀምጦት ከነበረው የ40 ሚሊዮን መራጮች ግብ ብልጫ አሳይቷል። በምርጫው 47 የፖለቲካ ፓርቲዎች እና 73 በግል የገቡ ዕጩዎችን ጨምሮ በአጠቃላይ 10,934 ዕጩዎች የተወዳደሩ ቢሆንም፣ በጸጥታ ችግር ምክንያት በትግራይ ክልል እንዲሁም በአንዳንድ የኦሮሚያ እና የአማራ ክልል አካባቢዎች ምርጫው ሳይካሄድ ቀርቷል።
የድምጽ አሰጣጥ ሂደቱን በተመለከተ ታዛቢ ልዑኩ እንዳረጋገጠው፣ 70 በመቶ የሚሆኑት የምርጫ ጣቢያዎች ልክ በጠዋቱ 06:00 በሰዓቱ ተከፍተዋል። በ99 በመቶ የምርጫ ጣቢያዎች የድምጽ አሰጣጥ ሂደቱ ሰላማዊ በሆነ መንገድ የተካሄደ ሲሆን፣ በ97 በመቶ ጣቢያዎች ደግሞ የጸጥታ አካላት በስፍራው ተገኝተው ሙያዊ ሥነ-ምግባር በተላበሰ መልኩ ደህንነትን አስጠብቀዋል። ሆኖም ከምሽቱ 18:00 የድምጽ መስጫ ሰዓት መጠናቀቅ በኋላ 88 በመቶ በሚሆኑ ጣቢያዎች መራጮች አሁንም ተሰልፈው ስለነበር፣ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የድምጽ መስጫ ሰዓቱን እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ በ6 ሰዓታት እንዲራዘም አድርጓል።
የተፈናቃዮች እና የጸጥታ አካላት አባላት ልዩ የድምጽ አሰጣጥ ጁን 8 ቀን 2026 የሚካሄድ መሆኑን የጠቆመው መግለጫው፣ የመጨረሻው ይፋዊ የምርጫ ውጤት ጁን 11 ቀን 2026 ይገለጻል ተብሎ እንደሚጠበቅ አመላክቷል። በመጨረሻም የአፍሪካ ኅብረት ታዛቢ ልዑክ የኢትዮጵያ መንግሥት፣ የፖለቲካ ተዋንያን እና ሁሉም የሚመለከታቸው አካላት ሀገራዊ መግባባትን ለመፍጠር እና ዴሞክራሲን ለማጎልበት ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ የፖለቲካ ውይይት እንዲያደርጉ በማበረታታት የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን አጠቃልሏል።
ልዑኩ በቀድሞው የኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የተመራ ሲሆን፣ በቀድሞው የናይጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጄፍሪ ኦንያማ ደግሞ በምክትል ኃላፊነት ተደግፏል። ቡድኑ 61 በመቶ ሴቶችን ያካተተ 73 የአጭር ጊዜ ታዛቢዎችን የያዘ ሲሆን፣ ከ35 የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡት እነዚህ ታዛቢዎች አዲስ አበባ፣ ኦሮሚያ፣ ድሬዳዋ፣ ሲዳማ፣ ደቡብ ኢትዮጵያ፣ ሐረሪ፣ ቤንሻንጉል ጉሙዝ እና ሶማሌን ጨምሮ በስምንት የኢትዮጵያ ክልሎች ስምሪት አድርገዋል። በአጠቃላይ 27 የታዛቢ ቡድኖች በ38 የምርጫ ክልሎች በሚገኙ 495 የምርጫ ጣቢያዎች ተዘዋውረው የድምጽ አሰጣጥ ሂደቱን በቅርበት ታዝበዋል።
ከምርጫው በፊት የነበሩ ሁኔታዎችን በተመለከተ መግለጫው እንዳብራራው፣ ለምርጫው 54 በመቶ ወንዶች እና 46 በመቶ ሴቶችን ያካተተ 50.5 ሚሊዮን መራጮች የተመዘገቡ ሲሆን፣ ይህ አሃዝ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስቀምጦት ከነበረው የ40 ሚሊዮን መራጮች ግብ ብልጫ አሳይቷል። በምርጫው 47 የፖለቲካ ፓርቲዎች እና 73 በግል የገቡ ዕጩዎችን ጨምሮ በአጠቃላይ 10,934 ዕጩዎች የተወዳደሩ ቢሆንም፣ በጸጥታ ችግር ምክንያት በትግራይ ክልል እንዲሁም በአንዳንድ የኦሮሚያ እና የአማራ ክልል አካባቢዎች ምርጫው ሳይካሄድ ቀርቷል።
የድምጽ አሰጣጥ ሂደቱን በተመለከተ ታዛቢ ልዑኩ እንዳረጋገጠው፣ 70 በመቶ የሚሆኑት የምርጫ ጣቢያዎች ልክ በጠዋቱ 06:00 በሰዓቱ ተከፍተዋል። በ99 በመቶ የምርጫ ጣቢያዎች የድምጽ አሰጣጥ ሂደቱ ሰላማዊ በሆነ መንገድ የተካሄደ ሲሆን፣ በ97 በመቶ ጣቢያዎች ደግሞ የጸጥታ አካላት በስፍራው ተገኝተው ሙያዊ ሥነ-ምግባር በተላበሰ መልኩ ደህንነትን አስጠብቀዋል። ሆኖም ከምሽቱ 18:00 የድምጽ መስጫ ሰዓት መጠናቀቅ በኋላ 88 በመቶ በሚሆኑ ጣቢያዎች መራጮች አሁንም ተሰልፈው ስለነበር፣ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የድምጽ መስጫ ሰዓቱን እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ በ6 ሰዓታት እንዲራዘም አድርጓል።
የተፈናቃዮች እና የጸጥታ አካላት አባላት ልዩ የድምጽ አሰጣጥ ጁን 8 ቀን 2026 የሚካሄድ መሆኑን የጠቆመው መግለጫው፣ የመጨረሻው ይፋዊ የምርጫ ውጤት ጁን 11 ቀን 2026 ይገለጻል ተብሎ እንደሚጠበቅ አመላክቷል። በመጨረሻም የአፍሪካ ኅብረት ታዛቢ ልዑክ የኢትዮጵያ መንግሥት፣ የፖለቲካ ተዋንያን እና ሁሉም የሚመለከታቸው አካላት ሀገራዊ መግባባትን ለመፍጠር እና ዴሞክራሲን ለማጎልበት ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ የፖለቲካ ውይይት እንዲያደርጉ በማበረታታት የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን አጠቃልሏል።
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ታዋቂዋ ኢትዮጵያዊት አርቲስት መሰረት መብራቴ፣ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ አርሲ ዞን በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች ላይ እየደረሰ ያለውን ተደጋጋሚ ጥቃት፣ መፈናቀል እና ግድያ በተመለከተ መንግሥትን እና የፍትሕ አካላትን ክፉኛ የሚወቅስ ጠንካራ መልእክት አስተላለፈች። አርቲስቷ በማኅበራዊ ትስስር ገጿ ባጋራችው እና በማህበራዊ ትሥሥር ላይ በግልጽ በሚታየው ጽሁፍ፣ የዜጎችን ደህንነት ማስጠበቅ ያልቻለውን ሥርዓት እና የሕግ ማስከበር ክፍተቱን በጽኑ ተችታለች።
በመልእክቷም "የኦርቶዶክሳውያን ሞትና መከራ እስከመቼ?!" በማለት መሠረታዊ የፍትሕ ጥያቄ ያነሳች ሲሆን፣ ምስራቅ አርሲን "የደም ምድር" ስትል ገልጻዋለች። ድርጊቱ ማቆሚያ የሌለው እልቂት እና ሰሚ የሌለው ጩኸት መሆኑን የጠቀሰችው አርቲስቷ የንጹሃን ደም ፍትሕ እየጠየቀ መሆኑን በአጽንኦት አስገንዝባለች። በተለይም በመልእክቷ ላይ "ከምድራዊ ዳኛ ፍትህ ባናገኝ፣ የሰማዩ አምላክ ይፈርዳችኋል!!!" በማለት ያሰፈረችው ሐሳብ የሕግ የበላይነት መጓደልን እና ምድራዊ የፍትሕ ተቋማት የዜጎችን ደህንነት በማስጠበቅ ረገድ ያሳዩትን ደካማ አፈጻጸም በቀጥታ የሚሞግት ወሳኝ መልእክት ነው።
በቅርብ ዓመታት በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች በተለይም በምስራቅ አርሲ እና አካባቢው ማንነትን እና ሃይማኖትን መሠረት ያደረጉ ጥቃቶች መበራከታቸውን የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች፣ የሃይማኖት ተቋማት እና እንደ ኢዜማ፣ እናት ፓርቲ ያሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች በተደጋጋሚ ሲገልጹ ቆይተዋል። በእነዚህ ክስተቶች የተነሳ በርካታ ዜጎች ሕይወታቸውን ያጡ ሲሆን፣ አያሌዎች ደግሞ ከቀያቸው ተፈናቅለው ለከፍተኛ እንግልት ተዳርገዋል።
በዚህ አውድ ውስጥ የሀገሪቱ ታዋቂ ግለሰቦች እና የኪነ-ጥበብ ሰዎች ከዝምታ ወጥተው ድምፃቸውን ማሰማት መጀመራቸው ትልቅ ትርጉም አለው። እንደ መሰረት መብራቴ ያሉ ተጽዕኖ ፈጣሪ ሰዎች እንዲህ ያሉ የአደባባይ ጩኸቶችን ማሰማታቸው፣ ችግሩ ብሔራዊ ትኩረት እንዲያገኝ ከማድረጉም ባለፈ የፍትሕ ተቋማት እና የጸጥታ ኃይሎች በዜጎች ላይ እየደረሰ ያለውን ጥቃት በአፋጣኝ አምነው ተገቢውን እርምጃ እንዲወስዱ ከፍተኛ ማኅበራዊ ጫና ይፈጥራል።
አርቲስት መሰረት መብራቴ "ወገኖቼ ነፍሳችሁን በቅዱሳን እቅፍ ይቀበለው" በማለት በግፉ ሕይወታቸውን ላጡ ንጹሃን ዜጎች ያላትን ጥልቅ ሀዘን በመግለጽ መልእክቷን አጠቃላለች።
በመልእክቷም "የኦርቶዶክሳውያን ሞትና መከራ እስከመቼ?!" በማለት መሠረታዊ የፍትሕ ጥያቄ ያነሳች ሲሆን፣ ምስራቅ አርሲን "የደም ምድር" ስትል ገልጻዋለች። ድርጊቱ ማቆሚያ የሌለው እልቂት እና ሰሚ የሌለው ጩኸት መሆኑን የጠቀሰችው አርቲስቷ የንጹሃን ደም ፍትሕ እየጠየቀ መሆኑን በአጽንኦት አስገንዝባለች። በተለይም በመልእክቷ ላይ "ከምድራዊ ዳኛ ፍትህ ባናገኝ፣ የሰማዩ አምላክ ይፈርዳችኋል!!!" በማለት ያሰፈረችው ሐሳብ የሕግ የበላይነት መጓደልን እና ምድራዊ የፍትሕ ተቋማት የዜጎችን ደህንነት በማስጠበቅ ረገድ ያሳዩትን ደካማ አፈጻጸም በቀጥታ የሚሞግት ወሳኝ መልእክት ነው።
በቅርብ ዓመታት በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች በተለይም በምስራቅ አርሲ እና አካባቢው ማንነትን እና ሃይማኖትን መሠረት ያደረጉ ጥቃቶች መበራከታቸውን የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች፣ የሃይማኖት ተቋማት እና እንደ ኢዜማ፣ እናት ፓርቲ ያሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች በተደጋጋሚ ሲገልጹ ቆይተዋል። በእነዚህ ክስተቶች የተነሳ በርካታ ዜጎች ሕይወታቸውን ያጡ ሲሆን፣ አያሌዎች ደግሞ ከቀያቸው ተፈናቅለው ለከፍተኛ እንግልት ተዳርገዋል።
በዚህ አውድ ውስጥ የሀገሪቱ ታዋቂ ግለሰቦች እና የኪነ-ጥበብ ሰዎች ከዝምታ ወጥተው ድምፃቸውን ማሰማት መጀመራቸው ትልቅ ትርጉም አለው። እንደ መሰረት መብራቴ ያሉ ተጽዕኖ ፈጣሪ ሰዎች እንዲህ ያሉ የአደባባይ ጩኸቶችን ማሰማታቸው፣ ችግሩ ብሔራዊ ትኩረት እንዲያገኝ ከማድረጉም ባለፈ የፍትሕ ተቋማት እና የጸጥታ ኃይሎች በዜጎች ላይ እየደረሰ ያለውን ጥቃት በአፋጣኝ አምነው ተገቢውን እርምጃ እንዲወስዱ ከፍተኛ ማኅበራዊ ጫና ይፈጥራል።
አርቲስት መሰረት መብራቴ "ወገኖቼ ነፍሳችሁን በቅዱሳን እቅፍ ይቀበለው" በማለት በግፉ ሕይወታቸውን ላጡ ንጹሃን ዜጎች ያላትን ጥልቅ ሀዘን በመግለጽ መልእክቷን አጠቃላለች።
2 days ago
ቻናል 1 ቴሌቪዥን ይቅርታ ጠየቀ።
#fastmereja I ቻናል 1 ቴሌቪዥን ባስተላለፈው መዝናኛ ፕሮግራም ሳቢያ ህዝብን ይቅርታ ጠየቀ።
ቻናል 1 ቴሌቪዥን እሁድ ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም “እሁድን አንድ ላይ” በተሰኘው መዝናኛ ፕሮግራሙ ውስጥ፣ “ተረኛው ሐኪም” በሚል ንዑስ ክፍል “የመራቢያ አካላትን ማስዋብ ተጀመረ” በሚል ርዕስ ያሰራጨው ይዘት ከህግ እና ከህብረተሰቡ እሴት ጋር የሚቃረን መሆኑን በማመን ይፋዊ የይቅርታ መግለጫ አውጥቷል።
ጣቢያው ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፣ የቀረበው ይዘት በመገናኛ ብዙኃን አዋጅ ቁጥር 1238/2013 አንቀጾች ከተደነገጉት ግዴታዎች፣ በተለይም “ጨዋ የቋንቋ አጠቃቀም”፣ “የአካለ መጠን ያልደረሱ ህጻናትን ደህንነት መጠበቅ” እንዲሁም “የማህበረሰቡን ሞራልና ባህላዊ እሴቶች ማክበር” ከሚሉት መርሆዎች ጋር በእጅጉ የተጋጨ መሆኑን አምኗል።
የቻናል 1 ቴሌቪዥን አመራሮች፣ ፕሮግራሙ ህጻናት በሚመለከቱበት ሰዓት ያለ ቅድመ ማስጠንቀቂያ መቅረቡ እና የርዕሰ ጉዳዩን ይዘት ከማህበረሰባችን ነባራዊ ሁኔታ አንጻር ሳይመዘን መሰራጨቱ የሙያ ስነምግባር ጥሰት እንደሆነ በመግለጽ፣ ይህንን ስህተት በመፈጸማቸው የተሰማቸውን ጥልቅ ማዘን ገልጸዋል።
ጣቢያው ለወደፊቱ በህግና በስነምግባር መመሪያዎች መሰረት አገልግሎት ለመስጠት ቃል በመግባት፣ በፕሮግራሙ ሳቢያ ቅር ለተሰኙ አድማጭ ተመልካቾቹ በሙሉ ይቅርታ ጠይቋል።
#fastmereja I ቻናል 1 ቴሌቪዥን ባስተላለፈው መዝናኛ ፕሮግራም ሳቢያ ህዝብን ይቅርታ ጠየቀ።
ቻናል 1 ቴሌቪዥን እሁድ ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም “እሁድን አንድ ላይ” በተሰኘው መዝናኛ ፕሮግራሙ ውስጥ፣ “ተረኛው ሐኪም” በሚል ንዑስ ክፍል “የመራቢያ አካላትን ማስዋብ ተጀመረ” በሚል ርዕስ ያሰራጨው ይዘት ከህግ እና ከህብረተሰቡ እሴት ጋር የሚቃረን መሆኑን በማመን ይፋዊ የይቅርታ መግለጫ አውጥቷል።
ጣቢያው ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው፣ የቀረበው ይዘት በመገናኛ ብዙኃን አዋጅ ቁጥር 1238/2013 አንቀጾች ከተደነገጉት ግዴታዎች፣ በተለይም “ጨዋ የቋንቋ አጠቃቀም”፣ “የአካለ መጠን ያልደረሱ ህጻናትን ደህንነት መጠበቅ” እንዲሁም “የማህበረሰቡን ሞራልና ባህላዊ እሴቶች ማክበር” ከሚሉት መርሆዎች ጋር በእጅጉ የተጋጨ መሆኑን አምኗል።
የቻናል 1 ቴሌቪዥን አመራሮች፣ ፕሮግራሙ ህጻናት በሚመለከቱበት ሰዓት ያለ ቅድመ ማስጠንቀቂያ መቅረቡ እና የርዕሰ ጉዳዩን ይዘት ከማህበረሰባችን ነባራዊ ሁኔታ አንጻር ሳይመዘን መሰራጨቱ የሙያ ስነምግባር ጥሰት እንደሆነ በመግለጽ፣ ይህንን ስህተት በመፈጸማቸው የተሰማቸውን ጥልቅ ማዘን ገልጸዋል።
ጣቢያው ለወደፊቱ በህግና በስነምግባር መመሪያዎች መሰረት አገልግሎት ለመስጠት ቃል በመግባት፣ በፕሮግራሙ ሳቢያ ቅር ለተሰኙ አድማጭ ተመልካቾቹ በሙሉ ይቅርታ ጠይቋል።
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ወራትን ያስቆጠረውን ጦርነት ለማቆም ተጀምሮ የነበረው የተኩስ አቁም ስምምነት ድርድር ባለፈው የሳምንት መጨረሻ ያለ ምንም መሻሻል መጓተቱን ተከትሎ፣ አሜሪካ እና ኢራን አዳዲስ ጥቃቶችን መለዋወጣቸው ተነግሯል። የአሜሪካ ጦር በኢራን ላይ የራስ መከላከል ጥቃቶችን መፈጸሙን እና ወደ መርከቦች እንዲሁም የባህረ ሰላጤው ሀገራት የተተኮሱ የባሊስቲክ ሚሳኤሎችንና ድሮኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል። የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (CENTCOM) በሆርሙዝ ስትሬት በምትገኘው ቄሽም ደሴት ላይ የፈጸመው ጥቃት፣ ኢራን በመካከለኛው ምስራቅ ለሞከረችው ጥቃት አጸፋዊ ምላሽ መሆኑን ገልጿል። በዚህም የኢራን ወታደራዊ የምድር መቆጣጠሪያ ጣቢያ ዒላማ የተደረገ ሲሆን፣ በሕጋዊ መንገድ ቀጠናውን እያቋረጡ በነበሩ የሲቪል መርከበኞች ላይ የተተኮሱ ሦስት ድሮኖችን አሜሪካ አክሽፋለች። በተጨማሪም ወደ ኩዌት የተተኮሱ ሁለት የኢራን ሚሳኤሎች መንገድ ላይ ሲከሽፉ፣ ወደ ባህሬን የተተኮሱ ሦስት ሚሳኤሎች ደግሞ በአሜሪካ እና በባህሬን የአየር መከላከያ ኃይሎች መክሸፋቸው ተገልጿል።
በበኩሏ ኢራን ለአሜሪካ ጥቃት አጸፋዊ ምላሽ ለመስጠት ሚሳኤሎችን እና ድሮኖችን በመጠቀም በአንድ የቀጠናው ሀገር ውስጥ በሚገኙ የአሜሪካ ጦር ሰፈሮች እና ሄሊኮፕተሮች ላይ ጥቃት ማድረሷን አስታውቃለች። የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ (IRGC) የሆርሙዝ ስትሬትን ደህንነት ማወክ በአሜሪካ ጦር ላይ ከባድ ዋጋ ያስከፍላል ሲልም አስጠንቅቋል።
ከዚህ ቀደም የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ ሚያዝያ 13 የጀመረውን የሆርሙዝ ስትሬት የባህር ላይ እገዳ አካል በማድረግ፣ ወደ ኢራኗ ኻርግ ደሴት በማምራት ላይ በነበረችው እና በቦትስዋና ባንዲራ በምትጓዘው 'ኤም/ቲ ሌክሲ' በተሰኘች ባዶ ነዳጅ ጫኝ መርከብ ላይ ጥቃት ማድረሱን ገልጿል። የመርከቧ ሰራተኞች በ24 ሰዓታት ውስጥ የተሰጣቸውን ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ ባለመቀበላቸው፣ የአሜሪካ አውሮፕላን በመርከቧ የሞተር ክፍል ላይ የሄልፋየር ሚሳኤል የተኮሰ ሲሆን፣ አሜሪካ ይህ ጥቃት ሲፈጸም የሚያሳይ የቪዲዮ ምስል ይፋ አድርጋለች። የባህር ላይ እገዳው ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ እስካሁን 6 የንግድ መርከቦች ከጥቅም ውጪ ሲሆኑ፣ 122 መርከቦች ደግሞ አቅጣጫቸውን እንዲቀይሩ ተደርጓል።
ይህ ውጥረት የተባባሰው፣ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዚህ ሳምንት ተቺዎቻቸው ዘና እንዲሉ መክረው፣ ኢራን ስምምነት ላይ መድረስ እንደምትፈልግ እና ይህም ለአሜሪካ ጥሩ እንደሚሆን በተናገሩበት ወቅት ነው። የሲቢኤስ ኒውስ እንደዘገበው፣ ፕሬዚዳንት ትራምፕ ሊኖር ስለሚችለው የሰላም ስምምነት ማዕቀፍ ማስተካከያ እንዲደረግ ጠይቀዋል። ማስተካከያው የሆርሙዝ ስትሬትን ጉዳይ፣ ከፍተኛ ማዕድን ያለው ዩራኒየምን ከኢራን ማውጣትን እና የኢራንን የኒውክሌር ፕሮግራም በተመለከተ አዲስ ድርድር መክፈትን ያካተተ ነው። ሆኖም የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማኢል ባጋኢ ሰኞ ዕለት በሰጡት ምላሽ፣ ይህ ጉዳይ በድርድሩ ጠረጴዛ ላይ እንዳልነበረ ገልጸው፣ ዋሽንግተን ሁልጊዜ አቋሟን እንደምትቀይር እና አዳዲስ ወይም የሚጋጩ ፍላጎቶችን እንደምታቀርብ ከሰዋል።
ጦርነቱ ከጀመረ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ በአሜሪካ ኮንግረስ ፊት ቀርበው ቃላቸውን የሰጡት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ፣ አሜሪካ ስትሬቱን ክፍት ለማድረግ ስትል ለኢራን ማዕቀብ የማንሳት ጥያቄን አላቀረበችም ብለዋል። ማንኛውም ማዕቀብ የማንሳት ጉዳይ ማዕቀቦቹ በመጀመሪያ ከተጣሉበት ምክንያት፣ ማለትም ከኒውክሌር ፕሮግራማቸው ጋር የተያያዘ ቅድመ ሁኔታን መሰረት ያደረገ ነው በማለት አስረድተዋል። ኮሚቴው ውስጥ ካሉ ሴናተሮች ጋር በነበራቸው ውጥረት የበዛበት የቃላት ልውውጥ ወቅትም፣ ሚኒስትሩ ጦርነቱ አብቅቷል ማለታቸው ተዘግቧል።
በበኩሏ ኢራን ለአሜሪካ ጥቃት አጸፋዊ ምላሽ ለመስጠት ሚሳኤሎችን እና ድሮኖችን በመጠቀም በአንድ የቀጠናው ሀገር ውስጥ በሚገኙ የአሜሪካ ጦር ሰፈሮች እና ሄሊኮፕተሮች ላይ ጥቃት ማድረሷን አስታውቃለች። የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ (IRGC) የሆርሙዝ ስትሬትን ደህንነት ማወክ በአሜሪካ ጦር ላይ ከባድ ዋጋ ያስከፍላል ሲልም አስጠንቅቋል።
ከዚህ ቀደም የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ ሚያዝያ 13 የጀመረውን የሆርሙዝ ስትሬት የባህር ላይ እገዳ አካል በማድረግ፣ ወደ ኢራኗ ኻርግ ደሴት በማምራት ላይ በነበረችው እና በቦትስዋና ባንዲራ በምትጓዘው 'ኤም/ቲ ሌክሲ' በተሰኘች ባዶ ነዳጅ ጫኝ መርከብ ላይ ጥቃት ማድረሱን ገልጿል። የመርከቧ ሰራተኞች በ24 ሰዓታት ውስጥ የተሰጣቸውን ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ ባለመቀበላቸው፣ የአሜሪካ አውሮፕላን በመርከቧ የሞተር ክፍል ላይ የሄልፋየር ሚሳኤል የተኮሰ ሲሆን፣ አሜሪካ ይህ ጥቃት ሲፈጸም የሚያሳይ የቪዲዮ ምስል ይፋ አድርጋለች። የባህር ላይ እገዳው ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ እስካሁን 6 የንግድ መርከቦች ከጥቅም ውጪ ሲሆኑ፣ 122 መርከቦች ደግሞ አቅጣጫቸውን እንዲቀይሩ ተደርጓል።
ይህ ውጥረት የተባባሰው፣ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዚህ ሳምንት ተቺዎቻቸው ዘና እንዲሉ መክረው፣ ኢራን ስምምነት ላይ መድረስ እንደምትፈልግ እና ይህም ለአሜሪካ ጥሩ እንደሚሆን በተናገሩበት ወቅት ነው። የሲቢኤስ ኒውስ እንደዘገበው፣ ፕሬዚዳንት ትራምፕ ሊኖር ስለሚችለው የሰላም ስምምነት ማዕቀፍ ማስተካከያ እንዲደረግ ጠይቀዋል። ማስተካከያው የሆርሙዝ ስትሬትን ጉዳይ፣ ከፍተኛ ማዕድን ያለው ዩራኒየምን ከኢራን ማውጣትን እና የኢራንን የኒውክሌር ፕሮግራም በተመለከተ አዲስ ድርድር መክፈትን ያካተተ ነው። ሆኖም የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማኢል ባጋኢ ሰኞ ዕለት በሰጡት ምላሽ፣ ይህ ጉዳይ በድርድሩ ጠረጴዛ ላይ እንዳልነበረ ገልጸው፣ ዋሽንግተን ሁልጊዜ አቋሟን እንደምትቀይር እና አዳዲስ ወይም የሚጋጩ ፍላጎቶችን እንደምታቀርብ ከሰዋል።
ጦርነቱ ከጀመረ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ በአሜሪካ ኮንግረስ ፊት ቀርበው ቃላቸውን የሰጡት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ፣ አሜሪካ ስትሬቱን ክፍት ለማድረግ ስትል ለኢራን ማዕቀብ የማንሳት ጥያቄን አላቀረበችም ብለዋል። ማንኛውም ማዕቀብ የማንሳት ጉዳይ ማዕቀቦቹ በመጀመሪያ ከተጣሉበት ምክንያት፣ ማለትም ከኒውክሌር ፕሮግራማቸው ጋር የተያያዘ ቅድመ ሁኔታን መሰረት ያደረገ ነው በማለት አስረድተዋል። ኮሚቴው ውስጥ ካሉ ሴናተሮች ጋር በነበራቸው ውጥረት የበዛበት የቃላት ልውውጥ ወቅትም፣ ሚኒስትሩ ጦርነቱ አብቅቷል ማለታቸው ተዘግቧል።
3 days ago
በትራምፕ እና በኔታንያሁ መካከል የተካሄደው የቁጣ ስልክ ጥሪ
“ምንድነው የምታደርገው?” ትራምፕ
ኢራን በእስራኤል የሊባኖስ ዘመቻ ምክንያት ከአሜሪካ ጋር የምታደርገውን ንግግር እንደምታቋርጥ ከተናገረች በኋላ፣ በሁለቱ መሪዎች መካከል የቁጣ የስልክ ጥሪ ልውውጥ መደረጉ ተነገረ
ዶናልድ ትራምፕ ቤሩት ደቡባዊ የከተማ ዳርቻዎች ላይ የአየር ጥቃት ለመጀመር በመዛቱ ምክንያት የእስራኤሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁን በቁጣ መጋፈጣቸውን አንድ ዘገባ አመልክቷል።
በሁለቱ መሪዎች መካከል የሚደረጉ ከፍተኛ የደረጃ ውይይቶችን በተደጋጋሚ ይፋ የሚያደርገው ‘አክሲዮስ’ የተሰኘው የአሜሪካ ድረ-ገጽ እንደዘገበው፤ ሰኞ ዕለት በተደረገው የስልክ ጥሪ ላይ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት በእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ላይ “ምንድነው የምታደርገው?” በማለት በቁጣ ጮኸውባቸዋል።
በእስራኤል መገናኛ ብዙሃን መካድ የገጠመው ይህ ዘገባ፣ አንድ የአሜሪካ ባለስልጣን ትራምፕ ለኔታንያሁ የተናገሩትን ሲያጠቃልሉ፦ **“አብደሃል። እኔ ባልኖር ኖሮ አሁን እስር ቤት ነበርክ። እኔ ነኝ እያዳንኩህ ያለሁት። አሁን ሁሉም ሰው ይጠላሃል። በዚህ ምክንያት ሁሉም ሰው እስራኤልን እየጠላት ነው”ማለታቸውን ጠቅሷል።
የስልክ ጥሪው የተደረገው ኔታንያሁ የእስራኤል ጦር ወደ እስራኤል የድሮን ጥቃቶችን ለሰነዘረውና በኢራን ለሚደገፈው የሂዝቦላ ሚሊሺያ ኢላማ ለማድረግ በቤሩት ደቡባዊ ዳሂያ አካባቢ ላይ የቦምብ ጥቃት እንዲጀምር ትዕዛዝ ከሰጡ በኋላ ነው።
የእስራኤል መከላከያ ሰራዊት በደቡብ ቤሩት የሚኖሩ የሊባኖስ ሲቪሎች አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ ማሳሰቢያ የሰጠ ሲሆን፣ ይህንን ተከትሎም በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተሰደዋል።
ኢራን ማክሰኞ ዕለት በሰጠችው መግለጫ፤ እስራኤል በደቡብ ሊባኖስ እያካሄደች ባለው ዘመቻ ምክንያት ከአሜሪካ ጋር የምታደርገውን የሰላም ንግግር እንደምታቋርጥ አስታውቃለች።
ቴህራን የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥን ለመክፈትና አሜሪካ በኢራን ወደቦች ላይ የጣለችውን እገዳ ለማንሳት የሚደረጉ ድርድሮችን ለማመቻቸት ሲባል፣ ሊባኖስም የተኩስ አቁም ስምምነቱ አካል መሆን አለባት ስትል ሞግታለች።
በኮንትሮባንድና የንግግር ማቋረጥ ዙሪያ የተሰማው ይህ መግለጫ፤ ትራምፕ ተደራዳሪዎች ሊፈርሙበት የሚችሉትን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሳቸውንና እሳቸውም ለመፈረም እያሰቡበት መሆኑን ከተናገሩ ከጥቂት ቀናት በኋላ የተሰማ ሲሆን፣ በሁለቱ መሪዎች መካከል የተደረገው የስልክ ጥሪም ይህንን ተከትሎ የመጣ ነው።
ቻናል 12 (Channel 12) የተሰኘው ታዋቂና ገለልተኛ የእስራኤል የዜና አውታር ግን የጥሪውን ዝርዝር መረጃ አስተባብሏል። የጣቢያው ዋና የፖለቲካ ተንታኝ አሚት ሴጋል እንዳለው፤ ትራምፕ በኔታንያሁ ላይ ግላዊ ጥቃት እንዳልሰነዘሩና ሁለቱ መሪዎች ሂዝቦላ በእስራኤል ላይ የሚያደርገውን ጥቃት ካቆመ፣ እስራኤልም በቤሩት የከተማ ዳርቻዎች ላይ ጥቃት ከመሰንዘር እንድትቆጠብ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ገልጿል።
በኔታንያሁ እና በትራምፕ ጥምረት መካከል የተፈጠረው ውጥረት
ምንም እንኳን እስራኤል በአካባቢው የአሜሪካ ዋና አጋር ሆና ብትቀጥልም እና ሁለቱ መሪዎች በየካቲት ወር በኔታንያሁ ግፊት በኢራን ላይ በጋራ ጥቃት ቢሰነዝሩም፣ ትራምፕና ኔታንያሁ ባለፈው ጊዜ የሻከረ ግንኙነት ነበራቸው።
ትራምፕ ባለፈው ዓመት የአየር ኃይል፣ ሚሳኤሎችና ድሮኖችን ያካተተ የ12 ቀናት የጋራ ጥቃት ልውውጥ በተደረገበት ወቅት ኢራን እና እስራኤል ምን እያደረጉ እንደሆነ አያውቁም በማለት በይፋ ተቆጥተው ነበር።
ኔታንያሁ ጆ ባይደንን በ2020 ትራምፕ በተቃወሙት ምርጫ ማሸነፋቸውን ተከትሎ የእንኳን አደረሰህ መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ፣ ትራምፕ ስለ ኔታንያሁ ሲናገሩ ጠንከር ያለ የስድብ ቃል ተጠቅመው ነበር።
ትራምፕ ከተለያዩ የሪፐብሊካን ፓርቲ ክፍሎች ጫና እየገጠማቸው ነው። ለአይሁድ ደጋፊ የሆኑ አጋሮቻቸው አሜሪካ ከኢራን ጋር ባላት ግጭት የበለጠ እንድትገፋበት ሲጠይቁ፣ ሌሎች ደግሞ ከኖቬምበር የዩኤስ የአጋማሽ ዘመን ምርጫ በፊት የሚደርሰውን ኢኮኖሚያዊ ጉዳት ለመቀነስ ጦርነቱ በአስቸኳይ እንዲያበቃ ይፈልጋሉ።
ከትራምፕ ጋር የሚነጋገረውና ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆነው ፕሮ-እስራኤል የቶክ ሾው አቅራቢ ማርክ ሌቪን እንደጻፈው፤ “የኢራን አገዛዝ ከዚህ መረጃ መውጣት (Leak) ተጠቃሚ ይሆናል፣ እኛን ደካማና ለስምምነት የምንቸኩል አድርጎ ይመለከተናል - አልፎ ተርፎም ለሂዝቦላ ጥበቃ እንደመቆም ይቆጥረዋል” ብሏል።
ኔታንያሁም ቢሆኑ በፖለቲካዊ ጫና ውስጥ ናቸው።
የእስራኤል ፓርላማ በዚህ ሳምንት ክኔሴትን (Knesset) ለመበተን እና ቅድመ ምርጫ ለመጥራት የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ በመጀመሪያ ንባብ የደገፈው ሲሆን፣ በእስራኤል የደህንነት ሁኔታ ምክንያት በተደጋጋሚ ተራዝሞ የነበረው የሙስና ክስ ችሎታቸውም እንዲቀጥል ቀጠሮ ተይዟል።
“ምንድነው የምታደርገው?” ትራምፕ
ኢራን በእስራኤል የሊባኖስ ዘመቻ ምክንያት ከአሜሪካ ጋር የምታደርገውን ንግግር እንደምታቋርጥ ከተናገረች በኋላ፣ በሁለቱ መሪዎች መካከል የቁጣ የስልክ ጥሪ ልውውጥ መደረጉ ተነገረ
ዶናልድ ትራምፕ ቤሩት ደቡባዊ የከተማ ዳርቻዎች ላይ የአየር ጥቃት ለመጀመር በመዛቱ ምክንያት የእስራኤሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁን በቁጣ መጋፈጣቸውን አንድ ዘገባ አመልክቷል።
በሁለቱ መሪዎች መካከል የሚደረጉ ከፍተኛ የደረጃ ውይይቶችን በተደጋጋሚ ይፋ የሚያደርገው ‘አክሲዮስ’ የተሰኘው የአሜሪካ ድረ-ገጽ እንደዘገበው፤ ሰኞ ዕለት በተደረገው የስልክ ጥሪ ላይ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት በእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ላይ “ምንድነው የምታደርገው?” በማለት በቁጣ ጮኸውባቸዋል።
በእስራኤል መገናኛ ብዙሃን መካድ የገጠመው ይህ ዘገባ፣ አንድ የአሜሪካ ባለስልጣን ትራምፕ ለኔታንያሁ የተናገሩትን ሲያጠቃልሉ፦ **“አብደሃል። እኔ ባልኖር ኖሮ አሁን እስር ቤት ነበርክ። እኔ ነኝ እያዳንኩህ ያለሁት። አሁን ሁሉም ሰው ይጠላሃል። በዚህ ምክንያት ሁሉም ሰው እስራኤልን እየጠላት ነው”ማለታቸውን ጠቅሷል።
የስልክ ጥሪው የተደረገው ኔታንያሁ የእስራኤል ጦር ወደ እስራኤል የድሮን ጥቃቶችን ለሰነዘረውና በኢራን ለሚደገፈው የሂዝቦላ ሚሊሺያ ኢላማ ለማድረግ በቤሩት ደቡባዊ ዳሂያ አካባቢ ላይ የቦምብ ጥቃት እንዲጀምር ትዕዛዝ ከሰጡ በኋላ ነው።
የእስራኤል መከላከያ ሰራዊት በደቡብ ቤሩት የሚኖሩ የሊባኖስ ሲቪሎች አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ ማሳሰቢያ የሰጠ ሲሆን፣ ይህንን ተከትሎም በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተሰደዋል።
ኢራን ማክሰኞ ዕለት በሰጠችው መግለጫ፤ እስራኤል በደቡብ ሊባኖስ እያካሄደች ባለው ዘመቻ ምክንያት ከአሜሪካ ጋር የምታደርገውን የሰላም ንግግር እንደምታቋርጥ አስታውቃለች።
ቴህራን የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥን ለመክፈትና አሜሪካ በኢራን ወደቦች ላይ የጣለችውን እገዳ ለማንሳት የሚደረጉ ድርድሮችን ለማመቻቸት ሲባል፣ ሊባኖስም የተኩስ አቁም ስምምነቱ አካል መሆን አለባት ስትል ሞግታለች።
በኮንትሮባንድና የንግግር ማቋረጥ ዙሪያ የተሰማው ይህ መግለጫ፤ ትራምፕ ተደራዳሪዎች ሊፈርሙበት የሚችሉትን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሳቸውንና እሳቸውም ለመፈረም እያሰቡበት መሆኑን ከተናገሩ ከጥቂት ቀናት በኋላ የተሰማ ሲሆን፣ በሁለቱ መሪዎች መካከል የተደረገው የስልክ ጥሪም ይህንን ተከትሎ የመጣ ነው።
ቻናል 12 (Channel 12) የተሰኘው ታዋቂና ገለልተኛ የእስራኤል የዜና አውታር ግን የጥሪውን ዝርዝር መረጃ አስተባብሏል። የጣቢያው ዋና የፖለቲካ ተንታኝ አሚት ሴጋል እንዳለው፤ ትራምፕ በኔታንያሁ ላይ ግላዊ ጥቃት እንዳልሰነዘሩና ሁለቱ መሪዎች ሂዝቦላ በእስራኤል ላይ የሚያደርገውን ጥቃት ካቆመ፣ እስራኤልም በቤሩት የከተማ ዳርቻዎች ላይ ጥቃት ከመሰንዘር እንድትቆጠብ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ገልጿል።
በኔታንያሁ እና በትራምፕ ጥምረት መካከል የተፈጠረው ውጥረት
ምንም እንኳን እስራኤል በአካባቢው የአሜሪካ ዋና አጋር ሆና ብትቀጥልም እና ሁለቱ መሪዎች በየካቲት ወር በኔታንያሁ ግፊት በኢራን ላይ በጋራ ጥቃት ቢሰነዝሩም፣ ትራምፕና ኔታንያሁ ባለፈው ጊዜ የሻከረ ግንኙነት ነበራቸው።
ትራምፕ ባለፈው ዓመት የአየር ኃይል፣ ሚሳኤሎችና ድሮኖችን ያካተተ የ12 ቀናት የጋራ ጥቃት ልውውጥ በተደረገበት ወቅት ኢራን እና እስራኤል ምን እያደረጉ እንደሆነ አያውቁም በማለት በይፋ ተቆጥተው ነበር።
ኔታንያሁ ጆ ባይደንን በ2020 ትራምፕ በተቃወሙት ምርጫ ማሸነፋቸውን ተከትሎ የእንኳን አደረሰህ መልዕክት ካስተላለፉ በኋላ፣ ትራምፕ ስለ ኔታንያሁ ሲናገሩ ጠንከር ያለ የስድብ ቃል ተጠቅመው ነበር።
ትራምፕ ከተለያዩ የሪፐብሊካን ፓርቲ ክፍሎች ጫና እየገጠማቸው ነው። ለአይሁድ ደጋፊ የሆኑ አጋሮቻቸው አሜሪካ ከኢራን ጋር ባላት ግጭት የበለጠ እንድትገፋበት ሲጠይቁ፣ ሌሎች ደግሞ ከኖቬምበር የዩኤስ የአጋማሽ ዘመን ምርጫ በፊት የሚደርሰውን ኢኮኖሚያዊ ጉዳት ለመቀነስ ጦርነቱ በአስቸኳይ እንዲያበቃ ይፈልጋሉ።
ከትራምፕ ጋር የሚነጋገረውና ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆነው ፕሮ-እስራኤል የቶክ ሾው አቅራቢ ማርክ ሌቪን እንደጻፈው፤ “የኢራን አገዛዝ ከዚህ መረጃ መውጣት (Leak) ተጠቃሚ ይሆናል፣ እኛን ደካማና ለስምምነት የምንቸኩል አድርጎ ይመለከተናል - አልፎ ተርፎም ለሂዝቦላ ጥበቃ እንደመቆም ይቆጥረዋል” ብሏል።
ኔታንያሁም ቢሆኑ በፖለቲካዊ ጫና ውስጥ ናቸው።
የእስራኤል ፓርላማ በዚህ ሳምንት ክኔሴትን (Knesset) ለመበተን እና ቅድመ ምርጫ ለመጥራት የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ በመጀመሪያ ንባብ የደገፈው ሲሆን፣ በእስራኤል የደህንነት ሁኔታ ምክንያት በተደጋጋሚ ተራዝሞ የነበረው የሙስና ክስ ችሎታቸውም እንዲቀጥል ቀጠሮ ተይዟል።
3 days ago
⚡ "የጽምዶ ጥምረት" በርካታ የኢትዮጵያ ተቃዋሚ ቡድኖችን እያካተተ መሆኑ ተገለጠ
በኤርትራ እና ህወሃት መካከል የተጀመረውና "ጽምዶ" (Ximdo) በመባል የሚታወቀው አዲሱ የፖለቲካ ትስስር፣ አሁን ላይ በርካታ የኢትዮጵያ የታጠቁና የፖለቲካ ተቃዋሚ ቡድኖችን ወደማካተት እየሰፋ መሄዱን አፍሪካ ኢንተለጀንስ ዘግቧል።
📌 የአዲስ አበባውን ማዕከላዊ መንግስት የሚቃወሙት የህወሃት/ትግራይ መከላከያ ኃይል አመራሮች፣ በቅርቡ በሱዳን የወደብ ከተማ ፖርት ሱዳን ከተደረጉ የኤርትራ ከፍተኛ ባለስልጣናት እና ከሱዳን ጦር ኃይል ተወካዮች ጋር ስብሰባ ማድረጋቸው ተረጋግጧል።
ይህ በኤርትራ መንግስት አስተባባሪነት እየተመራ ያለው ጥምረት የህወሃትን "የአሮጌው ጎራ ጨምሮ፣ እንደ ፋኖ ያሉ፣ የኦብነግ የተገነጠሉ ክንፎችን እና ሌሎች ታዋቂ የፖለቲካ ተቃዋሚዎችን በአንድ ጥላ ስር ለማሰባሰብ እየሰራ እንደሆነ የደህንነት ምንጮች ጠቁመዋል።
የሰሜኑ ጦርነት ወቅት ኤርትራ እና ህወሃት እርስ በእርስ የገጠሙ ደመኛ ጠላቶች የነበሩ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ግን "የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው" በሚለው መርህ የአዲስ አበባውን መንግስት ለመጫንና የራሳቸውን የፖለቲካ ህልውና ለማስጠበቅ ስልታዊ ህብረት ፈጥረዋል።ይህ አዲስ የሀይሎች መሸጋሸግ በኢትዮጵያ፣ በኤርትራ እና በሱዳን መካከል ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ይበልጥ እያሻከረው ሲሆን፣ ቀጠናዊ ቀውስ ሊያስከትል ይችላል የሚል ስጋት ፈጥሯል።
Seledadotio
Seledadotio
በኤርትራ እና ህወሃት መካከል የተጀመረውና "ጽምዶ" (Ximdo) በመባል የሚታወቀው አዲሱ የፖለቲካ ትስስር፣ አሁን ላይ በርካታ የኢትዮጵያ የታጠቁና የፖለቲካ ተቃዋሚ ቡድኖችን ወደማካተት እየሰፋ መሄዱን አፍሪካ ኢንተለጀንስ ዘግቧል።
📌 የአዲስ አበባውን ማዕከላዊ መንግስት የሚቃወሙት የህወሃት/ትግራይ መከላከያ ኃይል አመራሮች፣ በቅርቡ በሱዳን የወደብ ከተማ ፖርት ሱዳን ከተደረጉ የኤርትራ ከፍተኛ ባለስልጣናት እና ከሱዳን ጦር ኃይል ተወካዮች ጋር ስብሰባ ማድረጋቸው ተረጋግጧል።
ይህ በኤርትራ መንግስት አስተባባሪነት እየተመራ ያለው ጥምረት የህወሃትን "የአሮጌው ጎራ ጨምሮ፣ እንደ ፋኖ ያሉ፣ የኦብነግ የተገነጠሉ ክንፎችን እና ሌሎች ታዋቂ የፖለቲካ ተቃዋሚዎችን በአንድ ጥላ ስር ለማሰባሰብ እየሰራ እንደሆነ የደህንነት ምንጮች ጠቁመዋል።
የሰሜኑ ጦርነት ወቅት ኤርትራ እና ህወሃት እርስ በእርስ የገጠሙ ደመኛ ጠላቶች የነበሩ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ግን "የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው" በሚለው መርህ የአዲስ አበባውን መንግስት ለመጫንና የራሳቸውን የፖለቲካ ህልውና ለማስጠበቅ ስልታዊ ህብረት ፈጥረዋል።ይህ አዲስ የሀይሎች መሸጋሸግ በኢትዮጵያ፣ በኤርትራ እና በሱዳን መካከል ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ይበልጥ እያሻከረው ሲሆን፣ ቀጠናዊ ቀውስ ሊያስከትል ይችላል የሚል ስጋት ፈጥሯል።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
3 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካ የሀገር ውስጥ ደህንነት መምሪያ እና የዜግነት እና የኢሚግሬሽን አገልግሎት አርብ ዕለት ይፋ ባደረጉት አስደንጋጭ የፖሊሲ ለውጥ ምክንያት፣ የግሪን ካርድ አመልካቾች እና የህግ ጠበቆቻቸው በከፍተኛ ውዥንብር ውስጥ ወድቀዋል። በአዲሱ የትራምፕ አስተዳደር መመሪያ መሠረት፣ በቤተሰብ ትስስር ላይ ያልተመሰረቱ አብዛኛዎቹ የግሪን ካርድ አመልካቾች በአሜሪካ ውስጥ ሆነው የነዋሪነት ፈቃዳቸውን (Adjustment of Status) ከማስተካከል ይልቅ፣ ወደ መጡበት ሀገር ተመልሰው ሂደቱን እንዲከታተሉ የሚያስገድድ ነው። ይህ የፖሊሲ ለውጥ በአሜሪካ ውስጥ ሆኖ ማመልከትን እጅግ አስገዳጅ እና ልዩ ለሆኑ ሁኔታዎች ብቻ የተገደበ በማድረጉ በስደተኞች ዘንድ ትልቅ ስጋት ፈጥሯል።
ምንም እንኳን ተቋሙ ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ ጥቅም የሚያበረክቱ የሥራ ቪዛ (H-1B) ያላቸው ግለሰቦች ወደ ሀገራቸው መመለስ እንደማይጠበቅባቸው ማብራሪያ ቢሰጥም፣ በተግባር ግን ከፍተኛ የትግበራ ክፍተት እና መደናገር እየታየ ይገኛል። የተለያዩ የኢሚግሬሽን ጠበቆች እንደገለጹት፣ ከረጅም የሳምንቱ መጨረሻ ዕረፍት በኋላ ዳግም በተጀመሩት የግሪን ካርድ ቃለ መጠይቆች ላይ አመልካቾች ያልተጠበቁ እና አዳዲስ ጥያቄዎች እየቀረቡላቸው ነው። ቃለ መጠይቅ አድራጊዎቹ አመልካቾችን ወደ አሜሪካ ሲመጡ የነበራቸው ትክክለኛ አላማ ምን እንደነበር፣ ለምን ወደ ሀገራቸው ተመልሰው እንዳላመለከቱ፣ እንዲሁም በሀገራቸው በሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ በኩል እንዳያመለክቱ ያገዳቸው ምክንያት ምን እንደሆነ የሚጠይቁ ፈታኝ ጥያቄዎችን እያነሱባቸው ይገኛሉ።
ይህ ሁኔታ የፖሊሲው አፈፃፀም ወጥ አለመሆኑን የሚያሳይ ሲሆን፣ ጉዳዩ በቅጡ ላልተነገራቸው የኢሚግሬሽን መኮንኖችም ጭምር ግራ መጋባትን ፈጥሯል። አንዳንድ መኮንኖች አዲሱን መመሪያ አጥብቀው ሲተገብሩ፣ ሌሎቹ ደግሞ ምንም አይነት አዲስ ጥያቄ ሳያነሱ የተለመደውን አሰራር እየተከተሉ መሆኑ ታውቋል። ይባስ ብሎም፣ አዲሱ ህግ ፈጽሞ የማይመለከታቸው እና ከአሜሪካዊ ዜጋ ጋር በመጋባት የግሪን ካርድ ጥያቄ ያቀረቡ አመልካቾች ሳይቀሩ ለምን ወደ ሀገራቸው ተመልሰው እንዳላመለከቱ ጥያቄ እንደገጠማቸው የአሜሪካ የኢሚግሬሽን ጠበቆች ማህበር ማጋለጡ ሁኔታውን ይበልጥ አሳሳቢ አድርጎታል። በዚህም የተነሳ፣ ማናቸውም በሂደት ላይ ያሉ አመልካቾች ወደ ቃለ መጠይቅ ከመሄዳቸው በፊት አስቸኳይ እና ጥልቅ የሆነ የህግ ምክር እንዲያገኙ ባለሙያዎች አጥብቀው እያሳሰቡ ይገኛሉ።
ምንም እንኳን ተቋሙ ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ ጥቅም የሚያበረክቱ የሥራ ቪዛ (H-1B) ያላቸው ግለሰቦች ወደ ሀገራቸው መመለስ እንደማይጠበቅባቸው ማብራሪያ ቢሰጥም፣ በተግባር ግን ከፍተኛ የትግበራ ክፍተት እና መደናገር እየታየ ይገኛል። የተለያዩ የኢሚግሬሽን ጠበቆች እንደገለጹት፣ ከረጅም የሳምንቱ መጨረሻ ዕረፍት በኋላ ዳግም በተጀመሩት የግሪን ካርድ ቃለ መጠይቆች ላይ አመልካቾች ያልተጠበቁ እና አዳዲስ ጥያቄዎች እየቀረቡላቸው ነው። ቃለ መጠይቅ አድራጊዎቹ አመልካቾችን ወደ አሜሪካ ሲመጡ የነበራቸው ትክክለኛ አላማ ምን እንደነበር፣ ለምን ወደ ሀገራቸው ተመልሰው እንዳላመለከቱ፣ እንዲሁም በሀገራቸው በሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ በኩል እንዳያመለክቱ ያገዳቸው ምክንያት ምን እንደሆነ የሚጠይቁ ፈታኝ ጥያቄዎችን እያነሱባቸው ይገኛሉ።
ይህ ሁኔታ የፖሊሲው አፈፃፀም ወጥ አለመሆኑን የሚያሳይ ሲሆን፣ ጉዳዩ በቅጡ ላልተነገራቸው የኢሚግሬሽን መኮንኖችም ጭምር ግራ መጋባትን ፈጥሯል። አንዳንድ መኮንኖች አዲሱን መመሪያ አጥብቀው ሲተገብሩ፣ ሌሎቹ ደግሞ ምንም አይነት አዲስ ጥያቄ ሳያነሱ የተለመደውን አሰራር እየተከተሉ መሆኑ ታውቋል። ይባስ ብሎም፣ አዲሱ ህግ ፈጽሞ የማይመለከታቸው እና ከአሜሪካዊ ዜጋ ጋር በመጋባት የግሪን ካርድ ጥያቄ ያቀረቡ አመልካቾች ሳይቀሩ ለምን ወደ ሀገራቸው ተመልሰው እንዳላመለከቱ ጥያቄ እንደገጠማቸው የአሜሪካ የኢሚግሬሽን ጠበቆች ማህበር ማጋለጡ ሁኔታውን ይበልጥ አሳሳቢ አድርጎታል። በዚህም የተነሳ፣ ማናቸውም በሂደት ላይ ያሉ አመልካቾች ወደ ቃለ መጠይቅ ከመሄዳቸው በፊት አስቸኳይ እና ጥልቅ የሆነ የህግ ምክር እንዲያገኙ ባለሙያዎች አጥብቀው እያሳሰቡ ይገኛሉ።
3 days ago
የኢራኑ ፕሬዚዳንት የስራ
መልቀቂያ ማቅረባቸው ተሰማ
የኢራኑ ፕሬዚዳንት ማሱድ ፔዜሽኪያን ለሀገሪቱ የበላይ መሪ ጽህፈት ቤት ይፋዊ የስራ መልቀቂያ ደብዳቤ ማስገባታቸውን ለጉዳዩ ቅርብ የሆነ ምንጭ ለኢራን ኢንተርናሽናል ገልጧል። እሁድ ዕለት በተላከው በዚህ ደብዳቤ ላይ ፕሬዝዳንቱና መንግስታቸው በሀገሪቱ ዋና ዋና እና ወሳኝ የውሳኔ አሰጣጥ ሂደቶች ውስጥ ሙሉ በሙሉ መገለላቸውን ፔዜሽኪያን አጽንኦት ሰጥተውበታል። በዚህም ምክንያት በተፈጠረው ክፍተት የኢስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ጦር ውስጥ ያሉ ጽንፈኛ አንጃዎች የሀገሪቱን ጉዳዮች እንዲቆጣጠሩ ዕድል እንደሰጣቸው ምንጩ ጠቁሟል።
ፕሬዝዳንቱ አክለውም፣ በእንዲህ ያለ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ መንግስትን መምራትም ሆነ ህጋዊ ኃላፊነታቸውን መወጣት እንደማይችሉ በመግለጽ፣ በአስቸኳይ ከስልጣናቸው ለመልቀቅ መጠየቃቸውን አስታውቀዋል።
የበላይ መሪው ሞጅታባ ኻሜኒ የፕሬዝዳንቱን መልቀቂያ ይቀበሉት አይቀበሉት እስካሁን ግልጽ ባይሆንም፣ የደብዳቤው ይዘት ግን በከፍተኛ የስልጣን እርከን ላይ ታይቶ የማይታወቅና ጥልቅ የሆነ የስልጣን ክፍፍል መኖሩን በግልጽ ያሳያል። ይህ ክስተት የመጣው በመንግስትና በኢስላማዊቷ ሪፐብሊክ ወታደራዊ-ደህንነት ተቋማት መካከል ለወራት የዘለቀው ውጥረት ከተቀሰቀሰ በኋላ ነው።
ኢራን ኢንተርናሽናል ቀደም ሲል እንደዘገበው፣ የኢስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ጦር የፕሬዝዳንቱን በርካታ ስልጣኖች ደረጃ በደረጃ በመገደብ ቁልፍ የመንግስት አካላትን በቁጥጥሩ ስር አውሏል። የውስጥ ምንጮች እንደሚሉት ከሆነ፣ ይህ ሁኔታ የፔዜሽኪያን አስተዳደር በፖለቲካዊና አስፈፃሚ የውሳኔ ማጣት አዙሪት ውስጥ እንዲገባ ያደረገው ሲሆን፣ ይህም ዲፕሎማሲያዊ ድርድሮች ወደፊት እንዳይራመዱና በካቢኔ መዋቅር ላይ የሚፈለጉ ለውጦች እንዳይተገበሩ እንቅፋት ሆኗል።
Seledadotio
መልቀቂያ ማቅረባቸው ተሰማ
የኢራኑ ፕሬዚዳንት ማሱድ ፔዜሽኪያን ለሀገሪቱ የበላይ መሪ ጽህፈት ቤት ይፋዊ የስራ መልቀቂያ ደብዳቤ ማስገባታቸውን ለጉዳዩ ቅርብ የሆነ ምንጭ ለኢራን ኢንተርናሽናል ገልጧል። እሁድ ዕለት በተላከው በዚህ ደብዳቤ ላይ ፕሬዝዳንቱና መንግስታቸው በሀገሪቱ ዋና ዋና እና ወሳኝ የውሳኔ አሰጣጥ ሂደቶች ውስጥ ሙሉ በሙሉ መገለላቸውን ፔዜሽኪያን አጽንኦት ሰጥተውበታል። በዚህም ምክንያት በተፈጠረው ክፍተት የኢስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ጦር ውስጥ ያሉ ጽንፈኛ አንጃዎች የሀገሪቱን ጉዳዮች እንዲቆጣጠሩ ዕድል እንደሰጣቸው ምንጩ ጠቁሟል።
ፕሬዝዳንቱ አክለውም፣ በእንዲህ ያለ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ መንግስትን መምራትም ሆነ ህጋዊ ኃላፊነታቸውን መወጣት እንደማይችሉ በመግለጽ፣ በአስቸኳይ ከስልጣናቸው ለመልቀቅ መጠየቃቸውን አስታውቀዋል።
የበላይ መሪው ሞጅታባ ኻሜኒ የፕሬዝዳንቱን መልቀቂያ ይቀበሉት አይቀበሉት እስካሁን ግልጽ ባይሆንም፣ የደብዳቤው ይዘት ግን በከፍተኛ የስልጣን እርከን ላይ ታይቶ የማይታወቅና ጥልቅ የሆነ የስልጣን ክፍፍል መኖሩን በግልጽ ያሳያል። ይህ ክስተት የመጣው በመንግስትና በኢስላማዊቷ ሪፐብሊክ ወታደራዊ-ደህንነት ተቋማት መካከል ለወራት የዘለቀው ውጥረት ከተቀሰቀሰ በኋላ ነው።
ኢራን ኢንተርናሽናል ቀደም ሲል እንደዘገበው፣ የኢስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ጦር የፕሬዝዳንቱን በርካታ ስልጣኖች ደረጃ በደረጃ በመገደብ ቁልፍ የመንግስት አካላትን በቁጥጥሩ ስር አውሏል። የውስጥ ምንጮች እንደሚሉት ከሆነ፣ ይህ ሁኔታ የፔዜሽኪያን አስተዳደር በፖለቲካዊና አስፈፃሚ የውሳኔ ማጣት አዙሪት ውስጥ እንዲገባ ያደረገው ሲሆን፣ ይህም ዲፕሎማሲያዊ ድርድሮች ወደፊት እንዳይራመዱና በካቢኔ መዋቅር ላይ የሚፈለጉ ለውጦች እንዳይተገበሩ እንቅፋት ሆኗል።
Seledadotio
4 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት ከሶማሌላንድ ጋር ያለውን ግንኙነት እና ትብብር ማሻሻል በሚችልባቸው መስኮች ዙሪያ የተዘጋጀ ዝርዝር ሪፖርት ለኮንግረስ ቀረበ። የ2026 የብሔራዊ ደህንነት እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የበጀት አዋጅን መሠረት አድርጎ የወጣው ይህ ሪፖርት፣ አሜሪካ የሶማሊያን ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት (ሶማሌላንድን ጨምሮ) እንደምትቀበል በድጋሚ ያረጋገጠ ሲሆን፣ በዚህ ማዕቀፍ ውስጥ ሆኖ ከሶማሌላንድ ባለስልጣናት ጋር አዎንታዊ እና ገንቢ ግንኙነቷን እንደምትቀጥል አስታውቋል። ሪፖርቱ ግንኙነቱ ሊሻሻልባቸው የሚችሉ ሦስት ዋና ዋና መስኮችን በዝርዝር አስቀምጧል፡-
በአፍሪካ ቀንድ ያለው የጸጥታ ሁኔታ አሁንም ውስብስብ መሆኑን የጠቆመው ሪፖርቱ፣ የጽንፈኛ ኃይሎች ስጋት እና የቀጠናው አለመግባባቶች አሳሳቢ እንደሆኑ ገልጿል። ይሁን እንጂ ሶማሌላንድ ከየመን እና ከባቢ ኤል-ማንደብ ባህረ ሰላጤ አቅራቢያ ያላት ስትራቴጂካዊ አቀማመጥ፣ ከቀይ ባህር እስከ ህንድ ውቅያኖስ ያለውን የንግድ እና ወታደራዊ የባህር ላይ ጉዞ ነፃነት ለማረጋገጥ ወሳኝ አጋር ያደርጋታል። በተጨማሪም የሁቲ ታጣቂዎች እና የአልቃይዳ ትልቁ ክንፍ ከሆነው አል-ሸባብ ጋር ያላቸውን ትስስር ለመቆጣጠር እና የሽብርተኞችን እንቅስቃሴ ለመግታት የሶማሌላንድ መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ አመቺ መሆኑ ተገልጿል። ለዚህም ሲባል የአሜሪካ የአፍሪካ ዕዝ (AFRICOM) ከሶማሌላንድ ባለስልጣናት ጋር መደበኛ ግንኙነት እያደረገ መሆኑ ታውቋል።
በሞቃዲሾ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ በጸጥታ፣ በሰብአዊ እርዳታ እና በኢኮኖሚ ጉዳዮች ዙሪያ ለመምከር ወደ ሶማሌላንድ መደበኛ ጉብኝቶችን እንደሚያደርግ ሪፖርቱ ጠቅሷል። ሆኖም የአሜሪካ መንግሥት ሠራተኞች ወደ ስፍራው የሚያደርጉት ጉዞ ልክ እንደሌላው የሶማሊያ ክፍል ጥብቅ የጸጥታ መስፈርቶችን የሚጠይቅ ነው። በመሆኑም የንግድ ያልሆኑ አውሮፕላኖችን እና ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቁ የጸጥታ ጥበቃዎችን መጠቀም ግድ ይላል። ይህንን ሒደት ለማቀላጠፍ ኤምባሲው ከአፍሪካ ዕዝ ወታደራዊ ሀብቶች ጋር በቅርበት በማስተባበር እየሰራ ይገኛል።
የሶማሌላንድ ባለስልጣናት አሜሪካ በማዕድን፣ በመሰረተ ልማት፣ በንግድ እና በኢኮኖሚ ዕድገት ዘርፎች ኢንቨስት እንድታደርግ ሰፊ ማበረታቻ እያደረጉ መሆኑን ሪፖርቱ አስፍሯል። የሶማሌላንድ ወደቦች በቀጠናው ላሉ ሌሎች መጨናነቅ ለሚታይባቸው ወደቦች እንደ አማራጭ ሊያገለግሉ እንደሚችሉ የተገለጸ ሲሆን፣ እየተገነባ ያለው የበርበራ አውሮፕላን ማረፊያ እና ወደብ ለሶማሌላንድም ሆነ የባህር በር ለሌላት ኢትዮጵያ የንግድ እና የትራንስፖርት ማዕከል እየሆነ መምጣቱ፣ ለአሜሪካ የኢንቨስትመንት እና የንግድ ዕድሎችን ሊፈጥር እንደሚችል ተገምቷል።
ነገር ግን የቀጠናው የጸጥታ ስጋት፣ በሶማሌላንድ ፖለቲካዊ ቁመና ላይ ያለው አለመግባባት እና ባለስልጣናቱ ከሶማሊያ ብሔራዊ መንግሥት ጋር ለመተባበር ፈቃደኛ አለመሆናቸው፣ በአሜሪካ የኢንቨስትመንት፣ የባንክ እና የንግድ እንቅስቃሴዎች ላይ ከባድ ተግዳሮት እንደፈጠረ ሪፖርቱ አብራርቷል።
በአፍሪካ ቀንድ ያለው የጸጥታ ሁኔታ አሁንም ውስብስብ መሆኑን የጠቆመው ሪፖርቱ፣ የጽንፈኛ ኃይሎች ስጋት እና የቀጠናው አለመግባባቶች አሳሳቢ እንደሆኑ ገልጿል። ይሁን እንጂ ሶማሌላንድ ከየመን እና ከባቢ ኤል-ማንደብ ባህረ ሰላጤ አቅራቢያ ያላት ስትራቴጂካዊ አቀማመጥ፣ ከቀይ ባህር እስከ ህንድ ውቅያኖስ ያለውን የንግድ እና ወታደራዊ የባህር ላይ ጉዞ ነፃነት ለማረጋገጥ ወሳኝ አጋር ያደርጋታል። በተጨማሪም የሁቲ ታጣቂዎች እና የአልቃይዳ ትልቁ ክንፍ ከሆነው አል-ሸባብ ጋር ያላቸውን ትስስር ለመቆጣጠር እና የሽብርተኞችን እንቅስቃሴ ለመግታት የሶማሌላንድ መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ አመቺ መሆኑ ተገልጿል። ለዚህም ሲባል የአሜሪካ የአፍሪካ ዕዝ (AFRICOM) ከሶማሌላንድ ባለስልጣናት ጋር መደበኛ ግንኙነት እያደረገ መሆኑ ታውቋል።
በሞቃዲሾ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ በጸጥታ፣ በሰብአዊ እርዳታ እና በኢኮኖሚ ጉዳዮች ዙሪያ ለመምከር ወደ ሶማሌላንድ መደበኛ ጉብኝቶችን እንደሚያደርግ ሪፖርቱ ጠቅሷል። ሆኖም የአሜሪካ መንግሥት ሠራተኞች ወደ ስፍራው የሚያደርጉት ጉዞ ልክ እንደሌላው የሶማሊያ ክፍል ጥብቅ የጸጥታ መስፈርቶችን የሚጠይቅ ነው። በመሆኑም የንግድ ያልሆኑ አውሮፕላኖችን እና ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቁ የጸጥታ ጥበቃዎችን መጠቀም ግድ ይላል። ይህንን ሒደት ለማቀላጠፍ ኤምባሲው ከአፍሪካ ዕዝ ወታደራዊ ሀብቶች ጋር በቅርበት በማስተባበር እየሰራ ይገኛል።
የሶማሌላንድ ባለስልጣናት አሜሪካ በማዕድን፣ በመሰረተ ልማት፣ በንግድ እና በኢኮኖሚ ዕድገት ዘርፎች ኢንቨስት እንድታደርግ ሰፊ ማበረታቻ እያደረጉ መሆኑን ሪፖርቱ አስፍሯል። የሶማሌላንድ ወደቦች በቀጠናው ላሉ ሌሎች መጨናነቅ ለሚታይባቸው ወደቦች እንደ አማራጭ ሊያገለግሉ እንደሚችሉ የተገለጸ ሲሆን፣ እየተገነባ ያለው የበርበራ አውሮፕላን ማረፊያ እና ወደብ ለሶማሌላንድም ሆነ የባህር በር ለሌላት ኢትዮጵያ የንግድ እና የትራንስፖርት ማዕከል እየሆነ መምጣቱ፣ ለአሜሪካ የኢንቨስትመንት እና የንግድ ዕድሎችን ሊፈጥር እንደሚችል ተገምቷል።
ነገር ግን የቀጠናው የጸጥታ ስጋት፣ በሶማሌላንድ ፖለቲካዊ ቁመና ላይ ያለው አለመግባባት እና ባለስልጣናቱ ከሶማሊያ ብሔራዊ መንግሥት ጋር ለመተባበር ፈቃደኛ አለመሆናቸው፣ በአሜሪካ የኢንቨስትመንት፣ የባንክ እና የንግድ እንቅስቃሴዎች ላይ ከባድ ተግዳሮት እንደፈጠረ ሪፖርቱ አብራርቷል።
4 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በፈረንሳይ ዋና ከተማ ፓሪስ በሚካሄደው የዘንድሮው የጦር መሣሪያ እና መከላከያ አውደ ርዕይ ላይ እስራኤል እንዳትሳተፍ መታገዷን ተከትሎ፣ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የዲፕሎማሲ ውጥረት ወደ አዲስ እና አሳሳቢ ምዕራፍ ተሸጋግሯል። የእስራኤል መከላከያ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው፣ የፈረንሳይ ባለስልጣናት እስራኤል ብሔራዊ ድንኳን እንዳትተክል እና የመንግስት ተወካዮቿን ወደ ዝግጅቱ እንዳትልክ በይፋ ከልክለዋል። በዚህ ውሳኔ መሰረት፣ የፈረንሳይ መንግስት የእስራኤል የመከላከያ ኩባንያዎች የአየር መከላከያ ስርአቶችን ብቻ እንዲያሳዩ የፈቀደ ሲሆን፣ ማናቸውንም የማጥቃት አቅም ያላቸውን የጦር መሳሪያዎች ማቅረብን ግን በጥብቅ አግዷል።
ይህንን ድርጊት ተከትሎ የእስራኤል መከላከያ ሚኒስቴር ውሳኔውን "አሳፋሪ" ሲል አውግዞታል። ሚኒስቴሩ እርምጃው ከፖለቲካዊ እና የንግድ ስሌቶች የመነጨ መሆኑን በመግለጽ፣ ፈረንሳይ በሌሎች ተሳታፊ ሀገራት ላይ ያልተገበረችውን አድሏዊ ክልከላ በእስራኤል ላይ ብቻ መጫኗ ዓለም አቀፍ የአውደ ርዕይ ህጎችንና መርሆዎችን የጣሰ ነው ብሏል። ከዚህም ባሻገር፣ ፈረንሳይ ቆሜላቸዋለሁ ከምትላቸው መርሆች ጋር የሚጋጭ ድርጊት እየፈጸመች መሆኑን በመሞገት፣ የታገዱት የእስራኤል አጥቂ የጦር መሳሪያዎች ዓለም አቀፍ እና ቀጠናዊ መረጋጋትን በሚያናጉ አሸባሪ ቡድኖች እና መንግስታት ላይ ያላቸውን ውጤታማነት በተግባር ያስመሰከሩ መሆናቸውን አበክሮ ተከራክሯል።
ይህ አሳሳቢ ክልከላ የመጣው በእየሩሳሌም እና በፓሪስ መካከል ያለው የፖለቲካ ትኩሳት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመጣበት ወቅት መሆኑ ጉዳዩን ይበልጥ አሳሳቢ ያደርገዋል። ባለፈው ሚያዝያ ወር፣ ፈረንሳይ የእስራኤል አውሮፕላኖች ከኢራን ጋር ለነበረው ውጊያ የፈረንሳይን የአየር ክልል እንዳይጠቀሙ መከልከሏን ተከትሎ፣ የእስራኤል መከላከያ ሚኒስቴር ከፈረንሳይ የሚያደርገውን ማናቸውንም የጦር መሳሪያ ግዢ ማቋረጡ ይታወሳል። ይህ እርምጃ የእስራኤልን ደህንነት የሚጎዳ ነው በሚል የተወሰደ የቅጣት ምላሽ እንደነበር ሚኒስቴሩ በወቅቱ አሳውቆ ነበር።
የሁለቱ ሀገራት የጦር መሳሪያ አውደ ርዕይ ውዝግብ አዲስ ክስተት አይደለም።
የፈረንሳይ ባለስልጣናት ባለፈው የ2024 አውደ ርዕይ ላይ የእስራኤል ኩባንያዎች እንዳይሳተፉ መጀመሪያ ላይ አግደው በኋላ ላይ ውሳኔውን መቀልበሳቸው አይዘነጋም። እንዲሁም በ2025ቱ የፓሪስ የአየር ትርኢት ላይ አዘጋጆቹ የእስራኤል ኩባንያዎች አጥቂ መሳሪያዎችን በሚያሳዩባቸው ማሳያዎች ዙሪያ ጥቁር የከለላ ግድግዳዎችን በመገንባት ማግለላቸው የፈጠረው ቁርሾ አሁንም ድረስ አልበረደም። የዘንድሮው ሙሉ እገዳ ግን የሁለቱን ሀገራት ወታደራዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ከምንጊዜውም በላይ ወደ ከፋ ደረጃ ሊያሸጋግረው እንደሚችል የፖለቲካ ተንታኞች እየገለጹ ይገኛሉ።
ይህንን ድርጊት ተከትሎ የእስራኤል መከላከያ ሚኒስቴር ውሳኔውን "አሳፋሪ" ሲል አውግዞታል። ሚኒስቴሩ እርምጃው ከፖለቲካዊ እና የንግድ ስሌቶች የመነጨ መሆኑን በመግለጽ፣ ፈረንሳይ በሌሎች ተሳታፊ ሀገራት ላይ ያልተገበረችውን አድሏዊ ክልከላ በእስራኤል ላይ ብቻ መጫኗ ዓለም አቀፍ የአውደ ርዕይ ህጎችንና መርሆዎችን የጣሰ ነው ብሏል። ከዚህም ባሻገር፣ ፈረንሳይ ቆሜላቸዋለሁ ከምትላቸው መርሆች ጋር የሚጋጭ ድርጊት እየፈጸመች መሆኑን በመሞገት፣ የታገዱት የእስራኤል አጥቂ የጦር መሳሪያዎች ዓለም አቀፍ እና ቀጠናዊ መረጋጋትን በሚያናጉ አሸባሪ ቡድኖች እና መንግስታት ላይ ያላቸውን ውጤታማነት በተግባር ያስመሰከሩ መሆናቸውን አበክሮ ተከራክሯል።
ይህ አሳሳቢ ክልከላ የመጣው በእየሩሳሌም እና በፓሪስ መካከል ያለው የፖለቲካ ትኩሳት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመጣበት ወቅት መሆኑ ጉዳዩን ይበልጥ አሳሳቢ ያደርገዋል። ባለፈው ሚያዝያ ወር፣ ፈረንሳይ የእስራኤል አውሮፕላኖች ከኢራን ጋር ለነበረው ውጊያ የፈረንሳይን የአየር ክልል እንዳይጠቀሙ መከልከሏን ተከትሎ፣ የእስራኤል መከላከያ ሚኒስቴር ከፈረንሳይ የሚያደርገውን ማናቸውንም የጦር መሳሪያ ግዢ ማቋረጡ ይታወሳል። ይህ እርምጃ የእስራኤልን ደህንነት የሚጎዳ ነው በሚል የተወሰደ የቅጣት ምላሽ እንደነበር ሚኒስቴሩ በወቅቱ አሳውቆ ነበር።
የሁለቱ ሀገራት የጦር መሳሪያ አውደ ርዕይ ውዝግብ አዲስ ክስተት አይደለም።
የፈረንሳይ ባለስልጣናት ባለፈው የ2024 አውደ ርዕይ ላይ የእስራኤል ኩባንያዎች እንዳይሳተፉ መጀመሪያ ላይ አግደው በኋላ ላይ ውሳኔውን መቀልበሳቸው አይዘነጋም። እንዲሁም በ2025ቱ የፓሪስ የአየር ትርኢት ላይ አዘጋጆቹ የእስራኤል ኩባንያዎች አጥቂ መሳሪያዎችን በሚያሳዩባቸው ማሳያዎች ዙሪያ ጥቁር የከለላ ግድግዳዎችን በመገንባት ማግለላቸው የፈጠረው ቁርሾ አሁንም ድረስ አልበረደም። የዘንድሮው ሙሉ እገዳ ግን የሁለቱን ሀገራት ወታደራዊ እና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ከምንጊዜውም በላይ ወደ ከፋ ደረጃ ሊያሸጋግረው እንደሚችል የፖለቲካ ተንታኞች እየገለጹ ይገኛሉ።
4 days ago
የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን የምርጫ ትዝብት ሪፖርት
#fastmereja | የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን ባወጣው የጠዋት የምርጫ ሂደት ሪፖርት መሠረት፣ 7ኛው አገራዊ ምርጫ በአብዛኞቹ ክልሎች በሰላማዊ እና በተደራጀ ሁኔታ መጀመሩ ተገልጿል። ይሁን እንጂ በአማራ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች የፀጥታ ስጋት፣ የተኩስ ድምፅ እና የምርጫ ቁሳቁስ እጥረት መከሰቱ ተመዝግቧል።
የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን በምርጫው ዕለት በሀገር አቀፍ ደረጃ 14,160 ታዛቢዎችን በማሰማራት ሂደቱን ሲከታተል ቆይቷል። የፌዴሬሽኑ ግኝቶች የሚያሳዩት ዋና ዋና ነጥቦች እንደሚከተለው ቀርበዋል፦
📌 የምርጫው አጀማመር እና ተሳትፎ፦ ምርጫው በ10 ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ምንም ዓይነት የፀጥታ ችግር ሳይገጥመው በሰላም ተጀምሯል። በብዙ የምርጫ ጣቢያዎች የመራጮች ተሳትፎ ከጠዋቱ ጀምሮ ከፍተኛ እንደነበር ታዛቢዎች ገልጸዋል።
📌 የአማራ ክልል ሁኔታ፦ በደብረ ታቦር፣ ደብረ ጎንደር እና አዊ ዞኖች የተኩስ ድምፅ መሰማቱ የተዘገበ ሲሆን፣ በክልሉ የምርጫ ቁሳቁስ እጥረት መኖሩም ተነግሯል።
📌 የጣቢያ መክፈቻ መዘግየት፦ በአማራ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ ጋምቤላ፣ ሲዳማ እና አዲስ አበባ አንዳንድ ጣቢያዎች በሰዓቱ ባለመከፈታቸው የጥቂት ደቂቃዎች መዘግየት ታይቷል።
📌 የታዛቢዎች ስምሪት፦ ፌዴሬሽኑ 14,160 ታዛቢዎችን በማሰማራት የሴቶችን ደህንነትና የምርጫ ሂደቱን ቢከታተልም፣ በሎጂስቲክስ እና በተደራሽነት ችግር ምክንያት 22,788 የምርጫ ጣቢያዎች ያለ ታዛቢ ቀርተዋል።
📌 ምክረ ሃሳብ፦ ፌዴሬሽኑ በአማራ ክልል የፀጥታ ክትትል እንዲጠናከር፣ የጎደሉ የምርጫ ቁሳቁሶች በፍጥነት እንዲሟሉ እና ለሚቀጥሉት ሰዓታት ለአረጋውያንና ለአካል ጉዳተኞች ምቹ ሁኔታ እንዲፈጠር ለሚመለከታቸው አካላት ጥሪ አቅርቧል።
ይህ ሪፖርት በኦሮሚያ እና በአዲስ አበባ ሴቶች ፌዴሬሽን የተሰበሰበውን መረጃ ጨምሮ እንደ ሀገር አቀፍ የፌዴሬሽኑ መረጃ ተቀናጅቶ የቀረበ ነው።
#fastmereja | የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን ባወጣው የጠዋት የምርጫ ሂደት ሪፖርት መሠረት፣ 7ኛው አገራዊ ምርጫ በአብዛኞቹ ክልሎች በሰላማዊ እና በተደራጀ ሁኔታ መጀመሩ ተገልጿል። ይሁን እንጂ በአማራ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች የፀጥታ ስጋት፣ የተኩስ ድምፅ እና የምርጫ ቁሳቁስ እጥረት መከሰቱ ተመዝግቧል።
የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን በምርጫው ዕለት በሀገር አቀፍ ደረጃ 14,160 ታዛቢዎችን በማሰማራት ሂደቱን ሲከታተል ቆይቷል። የፌዴሬሽኑ ግኝቶች የሚያሳዩት ዋና ዋና ነጥቦች እንደሚከተለው ቀርበዋል፦
📌 የምርጫው አጀማመር እና ተሳትፎ፦ ምርጫው በ10 ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ምንም ዓይነት የፀጥታ ችግር ሳይገጥመው በሰላም ተጀምሯል። በብዙ የምርጫ ጣቢያዎች የመራጮች ተሳትፎ ከጠዋቱ ጀምሮ ከፍተኛ እንደነበር ታዛቢዎች ገልጸዋል።
📌 የአማራ ክልል ሁኔታ፦ በደብረ ታቦር፣ ደብረ ጎንደር እና አዊ ዞኖች የተኩስ ድምፅ መሰማቱ የተዘገበ ሲሆን፣ በክልሉ የምርጫ ቁሳቁስ እጥረት መኖሩም ተነግሯል።
📌 የጣቢያ መክፈቻ መዘግየት፦ በአማራ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ ጋምቤላ፣ ሲዳማ እና አዲስ አበባ አንዳንድ ጣቢያዎች በሰዓቱ ባለመከፈታቸው የጥቂት ደቂቃዎች መዘግየት ታይቷል።
📌 የታዛቢዎች ስምሪት፦ ፌዴሬሽኑ 14,160 ታዛቢዎችን በማሰማራት የሴቶችን ደህንነትና የምርጫ ሂደቱን ቢከታተልም፣ በሎጂስቲክስ እና በተደራሽነት ችግር ምክንያት 22,788 የምርጫ ጣቢያዎች ያለ ታዛቢ ቀርተዋል።
📌 ምክረ ሃሳብ፦ ፌዴሬሽኑ በአማራ ክልል የፀጥታ ክትትል እንዲጠናከር፣ የጎደሉ የምርጫ ቁሳቁሶች በፍጥነት እንዲሟሉ እና ለሚቀጥሉት ሰዓታት ለአረጋውያንና ለአካል ጉዳተኞች ምቹ ሁኔታ እንዲፈጠር ለሚመለከታቸው አካላት ጥሪ አቅርቧል።
ይህ ሪፖርት በኦሮሚያ እና በአዲስ አበባ ሴቶች ፌዴሬሽን የተሰበሰበውን መረጃ ጨምሮ እንደ ሀገር አቀፍ የፌዴሬሽኑ መረጃ ተቀናጅቶ የቀረበ ነው።
Sponsored by
Surafel
4 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ማእከላይ ኮሚቴ ከግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለአንድ ሳምንት ያህል ሲያካሂድ የቆየውን አስቸኳይ ስብሰባ ማጠናቀቁን አስመልክቶ ይፋዊ መግለጫ አውጥቷል።
ሕወሓት ባወጣው መግለጫ ላይ እንደሰፈረው በመቐለ ከተማ በተጠናቀቀው ጉባኤ ላይ ድርጅቱ ያለበትን ወቅታዊ ቁልፍ የውስጥ ችግሮች፣ ድክመቶች እና የቀጣይ የትግል አቅጣጫዎችን በዝርዝር ገምግሟል። ማእከላይ ኮሚቴው የህዝቡን ደህንነት ለማረጋገጥ፣ ተፈናቃዮችን ወደ ቀደመ ቀያቸው ለመመለስ እና የትግራይን ሉዓላዊነት ለማስከበር የሚደረገውን ትግል አጠናክሮ ለመቀጠል መወሰኑን በመግለጫው ጠቅሷል።
በዚህ ጥልቅ ግምገማ ድርጅቱ በውስጡ የነበሩ የአመለካከትና የአሰራር ጉድለቶችን ያለአንዳች ምህረት መመርመሩን የገለጸ ሲሆን፣ ህገ-ደንብን መሰረት በማድረግ በከፍተኛ አመራሮቹ ላይ ጠንከር ያሉ የዲስፕሊን እርምጃዎችን ወስዷል። በዚህም መሰረት በስራ ላይ የነበሩ ሁለት የድርጅቱ ስራ አስፈፃሚ አባላት እና አንድ የማእከላይ ኮሚቴ አባል ከባድ ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው ሲሆን፣ ሌሎች በስራ ላይ የነበሩ አመራሮችም ከማእከላይ ኮሚቴ ተለይተው በትግል ሜዳ እንዲሰማሩና በሌሎች አዳዲስ አመራሮች እንዲተኩ ተደርጓል። ይህ እርምጃ ድርጅቱ የውስጥ አንድነቱን ለመጠበቅና የአመራር ብቃቱን ለማደስ የወሰደው ወሳኝ ፖለቲካዊ እርምጃ እንደሆነ ተመልክቷል።
በመግለጫው ማጠቃለያ ላይ እንደተመለከተው፣ ማእከላይ ኮሚቴው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ መስተዳድር የካቢኔ አባላት እና የዞን አስተዳዳሪዎች አደረጃጀትን አስመልክቶ ሰፊ ውይይት አድርጓል። ድርጅቱ አዲስ የክልል ካቢኔ እንዲዋቀር እና የአመራር ሽግግር እንዲደረግ ፍላጎት እንዳለው ያመላከተ ሲሆን፣ ይህንኑ የአመራር ለውጥ የትግራይ ምስረታ ምክር ቤት እንዲመለከተው በይፋ መምራቱን አስታውቋል። ህወሓት በምርጫ ከፍተኛ ድምፅ ያገኘና ያሸነፈ ድርጅት በመሆኑ በክልሉ አስተዳደር ውስጥ ያለውን የመሪነት ሚና በህጋዊ አሰራር ለማስፈጸም እንደሚንቀሳቀስ በመግለጽ፣ አዲሱ መዋቅር የህዝቡን ዘርፈ-ብዙ ችግሮች ለመፍታት ቁርጠኛ እንደሚሆን አረጋግጧል።
ሕወሓት ባወጣው መግለጫ ላይ እንደሰፈረው በመቐለ ከተማ በተጠናቀቀው ጉባኤ ላይ ድርጅቱ ያለበትን ወቅታዊ ቁልፍ የውስጥ ችግሮች፣ ድክመቶች እና የቀጣይ የትግል አቅጣጫዎችን በዝርዝር ገምግሟል። ማእከላይ ኮሚቴው የህዝቡን ደህንነት ለማረጋገጥ፣ ተፈናቃዮችን ወደ ቀደመ ቀያቸው ለመመለስ እና የትግራይን ሉዓላዊነት ለማስከበር የሚደረገውን ትግል አጠናክሮ ለመቀጠል መወሰኑን በመግለጫው ጠቅሷል።
በዚህ ጥልቅ ግምገማ ድርጅቱ በውስጡ የነበሩ የአመለካከትና የአሰራር ጉድለቶችን ያለአንዳች ምህረት መመርመሩን የገለጸ ሲሆን፣ ህገ-ደንብን መሰረት በማድረግ በከፍተኛ አመራሮቹ ላይ ጠንከር ያሉ የዲስፕሊን እርምጃዎችን ወስዷል። በዚህም መሰረት በስራ ላይ የነበሩ ሁለት የድርጅቱ ስራ አስፈፃሚ አባላት እና አንድ የማእከላይ ኮሚቴ አባል ከባድ ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው ሲሆን፣ ሌሎች በስራ ላይ የነበሩ አመራሮችም ከማእከላይ ኮሚቴ ተለይተው በትግል ሜዳ እንዲሰማሩና በሌሎች አዳዲስ አመራሮች እንዲተኩ ተደርጓል። ይህ እርምጃ ድርጅቱ የውስጥ አንድነቱን ለመጠበቅና የአመራር ብቃቱን ለማደስ የወሰደው ወሳኝ ፖለቲካዊ እርምጃ እንደሆነ ተመልክቷል።
በመግለጫው ማጠቃለያ ላይ እንደተመለከተው፣ ማእከላይ ኮሚቴው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ መስተዳድር የካቢኔ አባላት እና የዞን አስተዳዳሪዎች አደረጃጀትን አስመልክቶ ሰፊ ውይይት አድርጓል። ድርጅቱ አዲስ የክልል ካቢኔ እንዲዋቀር እና የአመራር ሽግግር እንዲደረግ ፍላጎት እንዳለው ያመላከተ ሲሆን፣ ይህንኑ የአመራር ለውጥ የትግራይ ምስረታ ምክር ቤት እንዲመለከተው በይፋ መምራቱን አስታውቋል። ህወሓት በምርጫ ከፍተኛ ድምፅ ያገኘና ያሸነፈ ድርጅት በመሆኑ በክልሉ አስተዳደር ውስጥ ያለውን የመሪነት ሚና በህጋዊ አሰራር ለማስፈጸም እንደሚንቀሳቀስ በመግለጽ፣ አዲሱ መዋቅር የህዝቡን ዘርፈ-ብዙ ችግሮች ለመፍታት ቁርጠኛ እንደሚሆን አረጋግጧል።
4 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ዛሬ እሁድ የኦባማ አስተዳደር ይፋዊ የዋይት ሀውስ የኢንስታግራም ገጽ ባልታወቁ የሳይበር ጠላፊዎች (ሀከሮች) ቁጥጥር ስር መዋሉን ተከትሎ አሳሳቢ እና ያልተለመዱ መልእክቶች በገጹ ላይ ሲሰራጩ አምሽተዋል። የቀድሞው ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ የራሳቸው የግል ገጽ ቢኖራቸውም፣ ይህ የሳይበር ጥቃት ያነጣጠረው አስተዳደራቸው መረጃዎችን ያስተላልፍበት በነበረው ዋናው ማህደራዊ የኢንስታግራም ገጽ ላይ ነው።
ተመልካቾችን ግራ ካጋቡት ህገ-ወጥ ልጥፎች መካከል በሰው ሰራሽ አስተውሎት የተፈጠረ አንድ ምስል የሚገኝበት ሲሆን፣ ምስሉም "ዋይት ሀውስ በሺዓዎች ቁጥጥር ስር ውሏል" የሚል ትርጉም ባለው አነጋጋሪ ጽሁፍ ታጅቦ ወጥቷል። ከዚህ በተጨማሪም ጠላፊው በገጹ የኢንስታግራም ስቶሪ (ላይ ተመሳሳይ ይዘት ያላቸውን አጫጭር መረጃዎች ሲያጋራ ነበር።
የፌስቡክ እና የኢንስታግራም አደራጅ የሆነው የሜታ (Meta) ኩባንያ ቃል አቀባይ የጥቃቱን መፈጸም በማረጋገጥ፣ በአሁኑ ሰዓት የገጹ ደህንነት ተጠብቆ ወደ ቀድሞ ሁኔታው መመለሱን አስታውቀዋል። አክለውም ጠላፊዎቹ በህገ-ወጥ መንገድ የለጠፉት መረጃ ሙሉ በሙሉ ከገጹ ላይ እንዲጠፋ መደረጉን አረጋግጠዋል።
ይህ ይፋዊ የዋይት ሀውስ ገጽ ለመጨረሻ ጊዜ ትክክለኛ መረጃ ያጋራው ዶናልድ ትራምፕ የመጀመሪያውን ፕሬዝዳንታዊ በዓለ ሲመታቸውን ባደረጉበት እ.ኤ.አ. ጥር 20 ቀን 2017 መሆኑ የሚታወስ ነው። ይህን አነጋጋሪ የሳይበር ጥቃት ማን እንደፈጸመው እስካሁን የታወቀ ነገር የለም።
ተመልካቾችን ግራ ካጋቡት ህገ-ወጥ ልጥፎች መካከል በሰው ሰራሽ አስተውሎት የተፈጠረ አንድ ምስል የሚገኝበት ሲሆን፣ ምስሉም "ዋይት ሀውስ በሺዓዎች ቁጥጥር ስር ውሏል" የሚል ትርጉም ባለው አነጋጋሪ ጽሁፍ ታጅቦ ወጥቷል። ከዚህ በተጨማሪም ጠላፊው በገጹ የኢንስታግራም ስቶሪ (ላይ ተመሳሳይ ይዘት ያላቸውን አጫጭር መረጃዎች ሲያጋራ ነበር።
የፌስቡክ እና የኢንስታግራም አደራጅ የሆነው የሜታ (Meta) ኩባንያ ቃል አቀባይ የጥቃቱን መፈጸም በማረጋገጥ፣ በአሁኑ ሰዓት የገጹ ደህንነት ተጠብቆ ወደ ቀድሞ ሁኔታው መመለሱን አስታውቀዋል። አክለውም ጠላፊዎቹ በህገ-ወጥ መንገድ የለጠፉት መረጃ ሙሉ በሙሉ ከገጹ ላይ እንዲጠፋ መደረጉን አረጋግጠዋል።
ይህ ይፋዊ የዋይት ሀውስ ገጽ ለመጨረሻ ጊዜ ትክክለኛ መረጃ ያጋራው ዶናልድ ትራምፕ የመጀመሪያውን ፕሬዝዳንታዊ በዓለ ሲመታቸውን ባደረጉበት እ.ኤ.አ. ጥር 20 ቀን 2017 መሆኑ የሚታወስ ነው። ይህን አነጋጋሪ የሳይበር ጥቃት ማን እንደፈጸመው እስካሁን የታወቀ ነገር የለም።
5 days ago
ቲክቶክ ለነገው ምርጫ መዘጋጀቱን ገለጸ
#ethiopia | ቲክቶክ በኢትዮጵያ የሚካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ የሚናፈሱ ሀሰተኛ መረጃዎችን ለመግታት እና የፕላትፎርሙን ደህንነት ለመጠበቅ ልዩ ትኩረት መስጠቱን ይፋ አደረገ።
ማህበራዊ ሚዲያው ሂደቱን ውጤታማ ለማድረግ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ (NEBE) እና ከተለያዩ የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶች ጋር በቅንጅት እየሰራ እንደሚገኝ ያስታወቀ ሲሆን፤ የዚሁ ስራ አካል በሆነው የማጣራት እርምጃ በ2025 ማጠናቀቂያ ላይ ብቻ ደንቡን የጣሱ ከ1.8 ሚሊዮን በላይ ከኢትዮጵያ የተቀረጹ ቪዲዮዎችን ማስወገዱን ዛሬ ባወጣው መግለጫ ገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#tiktok #ethiopiaelection #fakenews #nebe #ethiopia #digitalsafety #medialiteracy #ቅዳሜገበያ
#ethiopia | ቲክቶክ በኢትዮጵያ የሚካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ የሚናፈሱ ሀሰተኛ መረጃዎችን ለመግታት እና የፕላትፎርሙን ደህንነት ለመጠበቅ ልዩ ትኩረት መስጠቱን ይፋ አደረገ።
ማህበራዊ ሚዲያው ሂደቱን ውጤታማ ለማድረግ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ (NEBE) እና ከተለያዩ የሲቪክ ማህበረሰብ ድርጅቶች ጋር በቅንጅት እየሰራ እንደሚገኝ ያስታወቀ ሲሆን፤ የዚሁ ስራ አካል በሆነው የማጣራት እርምጃ በ2025 ማጠናቀቂያ ላይ ብቻ ደንቡን የጣሱ ከ1.8 ሚሊዮን በላይ ከኢትዮጵያ የተቀረጹ ቪዲዮዎችን ማስወገዱን ዛሬ ባወጣው መግለጫ ገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#tiktok #ethiopiaelection #fakenews #nebe #ethiopia #digitalsafety #medialiteracy #ቅዳሜገበያ
9 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በህንድ ኮልካታ ከተማ የሚገኘው ግዙፉ የሊዮኔል ሜሲ ሀውልት የተተከለው በዲሴምበር ወር ተጨዋቹ በአገሪቱ ውስጥ ያደረገውን ጉብኝት በማስመልከት ነበር፡፡ ይህ 21 ሜትር የሚረዝመውና ወርቃማ ቀለም የተቀባው ሀውልት በዌስት ቤንጋል ግዛት ኮልካታ ከተማ እምብርት ላይ ቆሞ ቆይቷል፡፡ ነገር ግን ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ ይህ ሀውልት በንፋስ እየወዛወዘ ይገኛል፡፡ የከተማው ማዘጋጃ ቤት ሰራተኞች ሀውልቱ እንዳይወድቅ የተለያዩ ገመዶችን በመጠቀም እንዲጠናከር አድርገውታል፡፡
ይሁን እንጂ የከተማው ባለስልጣናት ዛሬ በሰጡት መግለጫ ሀውልቱ ከዚህ በኋላ ለደህንነት አስጊ በመሆኑ እንደሚነሳ አስታውቀዋል፡፡ የዌስት ቤንጋል ግዛት የፓርላማ አባል የሆኑት ሻራዳዋት ሙከርጂ ለኤኤፍፒ ሲናገሩ ‹‹ሀውልቱ በንፋስ እየተወዛወዘ መሆኑን ሰምተናል፡፡ የግዛቱ መሀንዲሶችም ለደህንነት አስጊ መሆኑን ገልፀውልናል›› ብለዋል፡፡ ጨምረውም ‹‹ሀውልቱን ማንሳት ከማቆም የበለጠ ቀላል ነው፡፡ ስለዚህም በተቻለ ፍጥነት የምናነሳው ይሆናል›› ያሉ ሲሆን ሀውልቱ ሌላ ቦታ ስለመተከል አለመተከሉ ያሉት ነገር የለም፡፡
ህንድ 1.4 ቢሊዮን ህዝብ ያላት አገር ብትሆንም በአገሪቱ ውስጥ ተወዳጅ የሆነው ስፖርት ክሪኬትስ ነው፡፡ በእግር ኳስ ከአለም በ142ተኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን የፊፋ መረጃ ያሳያል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ አርጀንቲናዊው የ38 አመቱ የእግር ኳስ ኮከብ ሊዮኔል ሜሲ ከሳምንታት በኋላ በሚጀመረው የአለም ዋንጫ ላይ እንደሚሳተፍ እስካሁን በይፋ ማረጋገጫ አልሰጠም፡፡ በውድድሩ የሚሳተፍ ከሆነ ግን በአለም ዋንጫ ላይ 6 ጊዜ በመሳተፍ ሪከርድን የሚጋራ ይሆናል፡፡
ይሁን እንጂ የከተማው ባለስልጣናት ዛሬ በሰጡት መግለጫ ሀውልቱ ከዚህ በኋላ ለደህንነት አስጊ በመሆኑ እንደሚነሳ አስታውቀዋል፡፡ የዌስት ቤንጋል ግዛት የፓርላማ አባል የሆኑት ሻራዳዋት ሙከርጂ ለኤኤፍፒ ሲናገሩ ‹‹ሀውልቱ በንፋስ እየተወዛወዘ መሆኑን ሰምተናል፡፡ የግዛቱ መሀንዲሶችም ለደህንነት አስጊ መሆኑን ገልፀውልናል›› ብለዋል፡፡ ጨምረውም ‹‹ሀውልቱን ማንሳት ከማቆም የበለጠ ቀላል ነው፡፡ ስለዚህም በተቻለ ፍጥነት የምናነሳው ይሆናል›› ያሉ ሲሆን ሀውልቱ ሌላ ቦታ ስለመተከል አለመተከሉ ያሉት ነገር የለም፡፡
ህንድ 1.4 ቢሊዮን ህዝብ ያላት አገር ብትሆንም በአገሪቱ ውስጥ ተወዳጅ የሆነው ስፖርት ክሪኬትስ ነው፡፡ በእግር ኳስ ከአለም በ142ተኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን የፊፋ መረጃ ያሳያል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ አርጀንቲናዊው የ38 አመቱ የእግር ኳስ ኮከብ ሊዮኔል ሜሲ ከሳምንታት በኋላ በሚጀመረው የአለም ዋንጫ ላይ እንደሚሳተፍ እስካሁን በይፋ ማረጋገጫ አልሰጠም፡፡ በውድድሩ የሚሳተፍ ከሆነ ግን በአለም ዋንጫ ላይ 6 ጊዜ በመሳተፍ ሪከርድን የሚጋራ ይሆናል፡፡
10 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በደርባን ከተማ ዶክመንት በሌላቸው ስደተኞች ላይ የአፈሳ ዘመቻ ተጀመረ፡፡ በደቡብ አፍሪካ ደርባን ሲቢዲ አካባቢ የመንግስት ሀይሎች ህጋዊ ዶክመንት በሌላቸው ስደተኞች ላይ እርምጃ መውሰድ መጀመራቸውን አስታወቁ፡፡ በዚህ ዘመቻ የኢቲኪዊኒ ማዘጋጃ ቤት ከተለያዩ መንግስታዊ ኤጀንሲዎች ጋር በመተባበር እየሰራ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በዛሬው እለት ብቻ 23 ዶክመንት የሌላቸው ስደተኞች በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡
ከተያዙት ውስጥ ኢትዮጵያዊያን፣ ዚምባቡያዊያን፣ የማላዊ ዜጎችና ቻይናዊያን እንደሚገኙበት የከተማው ማዘጋጃ ቤት ገልጿል፡፡ በተጨማሪም በተደረገው ዘመቻ 5 ያህል በህገ ወጥ ስራዎች ላይ ተሰማርተው የተገኙ ሱቆች ላይ የማሸግ እርምጃ መውሰዱን አስታውቋል፡፡ ከታሸጉት ውስጥም በኢትዮጵያዊያን የሚተዳደሩ ሱቆች ይገኙበታል፡፡ ማዘጋጃ ቤቱ በመግለጫው ‹‹እነዚህ ሱቆች የህገወጥ ስደተኞች መደበቂያ፣ ህጋዊ ያልሆነ አደንዛዥ እፅ መሸጫና የሴተኛ አዳሪነት ስራዎች ሲፈፀሙባቸው የነበሩ ናቸው›› ብሏል፡፡
የደቡብ አፍሪካ መንግስት ይህንን እርምጃ መውሰድ የጀመረው በአገሪቱ ውስጥ ስደተኛ ጠል ተቃውሞው እየተቀጣጠለ መምጣቱን ተከትሎ ነው፡፡ የአገሪቱ የፀጥታና የደህንነት መስሪያ ቤቶች ትላንት ባደረጉት አስቸኳይ ስብሰባ ተቃውሞውን ለማብረድ በህገ ወጥ ስደተኞች ላይ የተቀናጀ እርምጃ እንዲወሰድ የሚል ውሳኔ ላይ የደረሱ ሲሆን ዛሬ በደርባን የተጀመረው አይነት እርምጃ በሌሎች ከተሞችም እንደሚቀጥል ከስፍራው የተሰራጩ መረጃዎች ገልፀዋል፡፡
ከተያዙት ውስጥ ኢትዮጵያዊያን፣ ዚምባቡያዊያን፣ የማላዊ ዜጎችና ቻይናዊያን እንደሚገኙበት የከተማው ማዘጋጃ ቤት ገልጿል፡፡ በተጨማሪም በተደረገው ዘመቻ 5 ያህል በህገ ወጥ ስራዎች ላይ ተሰማርተው የተገኙ ሱቆች ላይ የማሸግ እርምጃ መውሰዱን አስታውቋል፡፡ ከታሸጉት ውስጥም በኢትዮጵያዊያን የሚተዳደሩ ሱቆች ይገኙበታል፡፡ ማዘጋጃ ቤቱ በመግለጫው ‹‹እነዚህ ሱቆች የህገወጥ ስደተኞች መደበቂያ፣ ህጋዊ ያልሆነ አደንዛዥ እፅ መሸጫና የሴተኛ አዳሪነት ስራዎች ሲፈፀሙባቸው የነበሩ ናቸው›› ብሏል፡፡
የደቡብ አፍሪካ መንግስት ይህንን እርምጃ መውሰድ የጀመረው በአገሪቱ ውስጥ ስደተኛ ጠል ተቃውሞው እየተቀጣጠለ መምጣቱን ተከትሎ ነው፡፡ የአገሪቱ የፀጥታና የደህንነት መስሪያ ቤቶች ትላንት ባደረጉት አስቸኳይ ስብሰባ ተቃውሞውን ለማብረድ በህገ ወጥ ስደተኞች ላይ የተቀናጀ እርምጃ እንዲወሰድ የሚል ውሳኔ ላይ የደረሱ ሲሆን ዛሬ በደርባን የተጀመረው አይነት እርምጃ በሌሎች ከተሞችም እንደሚቀጥል ከስፍራው የተሰራጩ መረጃዎች ገልፀዋል፡፡
Sponsored by
Surafel
10 days ago
ግብፅ በቀይ ባህር ደህንነት ጉዳይ የውጭ ሀገራትን ጣልቃ ገብነት እንደማትቀበል አስታወቀች
#fastmereja I ግብፅ በቀይ ባህር እና በኤደን ባህረ ሰላጤ የፖለቲካና የደህንነት ስምምነቶች ላይ የባህሩ ተጋሪ ያልሆኑ የውጭ ሀገራት ጣልቃ መግባታቸውን ፈጽሞ እንደማትቀበል በይፋ አስታወቀች።
እሁድ ዕለት በካይሮ በተካሄደው ዘጠነኛው የግብፅ-የመን ስትራቴጂካዊ ውይይት ላይ የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብደላቲ ከየመኑ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሻያ አል-ዚንዳኒ ጋር ባደረጉት ምክክር ነው የሀገራቸውን ጽኑ ቋሚ አቋም ግልጽ ያደረጉት።
ይህ የግብፅ ውሳኔ በቀይ ባህር ቀጣና ላይ እያደገ የመጣውን የዓለም አቀፍ ኃይሎች ፍላጎትና የተፈጠረውን የጂኦፖለቲካዊ ውጥረት ተከትሎ የመጣ ሲሆን፣ የደህንነት ጥበቃው በራሳቸው በባህሩ ተጋሪ በሆኑ የቀጣናው ሀገራት ብቻ ሊመራ እንደሚገባ የሚያሳይ ነው። ውይይቱ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከርና በቀጣናው ሰላም ዙሪያ በጋራ ለመስራት ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
#fastmereja I ግብፅ በቀይ ባህር እና በኤደን ባህረ ሰላጤ የፖለቲካና የደህንነት ስምምነቶች ላይ የባህሩ ተጋሪ ያልሆኑ የውጭ ሀገራት ጣልቃ መግባታቸውን ፈጽሞ እንደማትቀበል በይፋ አስታወቀች።
እሁድ ዕለት በካይሮ በተካሄደው ዘጠነኛው የግብፅ-የመን ስትራቴጂካዊ ውይይት ላይ የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብደላቲ ከየመኑ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሻያ አል-ዚንዳኒ ጋር ባደረጉት ምክክር ነው የሀገራቸውን ጽኑ ቋሚ አቋም ግልጽ ያደረጉት።
ይህ የግብፅ ውሳኔ በቀይ ባህር ቀጣና ላይ እያደገ የመጣውን የዓለም አቀፍ ኃይሎች ፍላጎትና የተፈጠረውን የጂኦፖለቲካዊ ውጥረት ተከትሎ የመጣ ሲሆን፣ የደህንነት ጥበቃው በራሳቸው በባህሩ ተጋሪ በሆኑ የቀጣናው ሀገራት ብቻ ሊመራ እንደሚገባ የሚያሳይ ነው። ውይይቱ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከርና በቀጣናው ሰላም ዙሪያ በጋራ ለመስራት ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
10 days ago
የሴቶች እኩልነት በተግባር…
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የተሻለችና የበለፀገች ኢትዮጵያን ለመገንባት የሴቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎ ወሳኝ ነው።
የመደመር ዕሳቤ ለሴቶች እኩልነትና ፍትሐዊ ተጠቃሚነት፣ ለሕፃናት መብት፣ ለደህንነትና ብሩህ ዓለም የሚታገል የጠራ አስተሳሰብ እና ጽኑ አቋም አለው።
ባለፉት ዓመታት በሚሊየን የሚቆጠሩ ሴቶች የፖለቲካ ተዋናይ እንዲሁም የሀብት ባለቤት እንዲሆኑ በርካታ የሪፎርም ሥራዎች ተከናውነዋል።
ቀደም ሲል ከፖለቲካውና ከኢኮኖሚው ማዕከል ተገልለው የነበሩ ሴቶች በሀገር ግንባታ ሂደት እንደ አጋር እና ተረጂ ሳይሆን እንደ ዋና ባለቤትና አንቀሳቃሽ ኃይል እንዲሆኑ ተደርጓል።
መንግሥት የእናቶችን ጫና ለመቀነስ ባከናወናቸው ሥራዎች ሕፃናት የምገባና ምቹ የመማሪያ አካባቢዎች ተሟልቶላቸው እንዲማሩ ለማድረግ ሥራዎችን ጀምሯል።
የእናቶችና የሕፃናት ሆስፒታል፣ የሴቶች ተሃድሶና ልህቀት ማዕከል እንዲሁም የእንጀራ መጋገሪያ ፋብሪካዎችን በመገንባት የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሰፊ እንቅስቃሴ ተደርጓል።
“ሴቶች ሲበለጽጉ ሀገር ትበለፅጋለች” የሚለውን መርሕ በተግባር ለማዋል በተደረገው ጥረት ይበል የሚያሰኝ ውጤት የተገኘ ሲሆን፥ የሴቶች ውሳኔ ሰጪነትን ከተራ ተሳትፎነት ወደ ማዕከላዊ ተዋናይነት ማሳደግ ተችሏል።
የሴቶች ተሳትፎ በፌዴራል ደረጃ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሴቶች ውክልና 42 በመቶ፤ በክልል ምክር ቤቶች ደግሞ 45 በመቶ ደርሷል።
በአስፈጻሚ ደረጃ ከሚመደቡ የፌዴራል የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውስጥ 51 በመቶው ሴቶች ሲሆኑ፥ 30 በመቶው ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የተቋማት ኃላፊዎችና አምባሳደሮች ደግሞ ሴቶች ናቸው።
በአጠቃላይ በዴሞክራሲ ተቋማት፣ በፍርድ ቤቶች፣ በከንቲባነትና በአስተዳዳሪነት ደረጃ በኃላፊነት ተመድበው እንዲሠሩ ተደርጓል።
አሁን ላይ ሴቶች በቤተሰብና በአካባቢ ማሕበረሰብ ውስጥ የመደመጥ እና የመወሰን አቅማቸው 60 በመቶ ደርሷል።
ይህ ተጨባጭ ተሳትፎ በሀገራዊ የፖሊሲ ቀረጻና በውሳኔ አሰጣጥ ሂደቶች ላይ ቀጥተኛ ተጽዕኖ እንዲኖራቸው ዕድል ፈጥሯል።
በኢኮኖሚ ዘርፍ በተወሰደው የሪፎርም እርምጃ የሴቶች የመሬት ባለቤትነትና የፋይናንስ ተጠቃሚነት ተረጋግጧል።
የሴቶች የባንክ ሒሳብ የመክፈት መጠን ከ20 በመቶ ወደ 43 በመቶ አድጓል።
13 ሚሊየን የሚሆኑት ሴቶች በብድርና ቁጠባ ማሕበራት ተደራጅተው 30 ቢሊየን የሚደርስ ብር ለመቆጠብ የቻሉ ሲሆን፥ 7 ሚሊየን የሚሆኑ ሴቶች ደግሞ የመሬት ባለቤትነታቸው ተረጋግጧል።
የሴቶችን ደህንነት በማረጋገጥ ዙሪያ በተሰራው ሥራ ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግሥታት የሥነ ሕዝብ ፈንድ ሽልማት እና እውቅና ለማግኘት በቅታለች።
በጤናው ዘርፍ የሴቶች የሥነ ተዋልዶ ጤና አገልግሎት ላይ መሠረታዊ ዕድገት የተመዘገበ ሲሆን፤ በትምህርት ዘርፍም የሴቶች ተሳትፎ በመጀመሪያና በሁለተኛ ደረጃ ከወንዶች እኩል ሆኗል።
በዲጂታል ዘርፍ የሞባይል ስልክ ተጠቃሚ የሆኑ ሴቶች ድርሻ 49 በመቶ የደረሰ ሲሆን፥ ከእነዚህ ውስጥ 36 በመቶ የሚሆኑት ለፋይናንስ ግብይት እየተጠቀሙበት ይገኛሉ።
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የተሻለችና የበለፀገች ኢትዮጵያን ለመገንባት የሴቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎ ወሳኝ ነው።
የመደመር ዕሳቤ ለሴቶች እኩልነትና ፍትሐዊ ተጠቃሚነት፣ ለሕፃናት መብት፣ ለደህንነትና ብሩህ ዓለም የሚታገል የጠራ አስተሳሰብ እና ጽኑ አቋም አለው።
ባለፉት ዓመታት በሚሊየን የሚቆጠሩ ሴቶች የፖለቲካ ተዋናይ እንዲሁም የሀብት ባለቤት እንዲሆኑ በርካታ የሪፎርም ሥራዎች ተከናውነዋል።
ቀደም ሲል ከፖለቲካውና ከኢኮኖሚው ማዕከል ተገልለው የነበሩ ሴቶች በሀገር ግንባታ ሂደት እንደ አጋር እና ተረጂ ሳይሆን እንደ ዋና ባለቤትና አንቀሳቃሽ ኃይል እንዲሆኑ ተደርጓል።
መንግሥት የእናቶችን ጫና ለመቀነስ ባከናወናቸው ሥራዎች ሕፃናት የምገባና ምቹ የመማሪያ አካባቢዎች ተሟልቶላቸው እንዲማሩ ለማድረግ ሥራዎችን ጀምሯል።
የእናቶችና የሕፃናት ሆስፒታል፣ የሴቶች ተሃድሶና ልህቀት ማዕከል እንዲሁም የእንጀራ መጋገሪያ ፋብሪካዎችን በመገንባት የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሰፊ እንቅስቃሴ ተደርጓል።
“ሴቶች ሲበለጽጉ ሀገር ትበለፅጋለች” የሚለውን መርሕ በተግባር ለማዋል በተደረገው ጥረት ይበል የሚያሰኝ ውጤት የተገኘ ሲሆን፥ የሴቶች ውሳኔ ሰጪነትን ከተራ ተሳትፎነት ወደ ማዕከላዊ ተዋናይነት ማሳደግ ተችሏል።
የሴቶች ተሳትፎ በፌዴራል ደረጃ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሴቶች ውክልና 42 በመቶ፤ በክልል ምክር ቤቶች ደግሞ 45 በመቶ ደርሷል።
በአስፈጻሚ ደረጃ ከሚመደቡ የፌዴራል የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውስጥ 51 በመቶው ሴቶች ሲሆኑ፥ 30 በመቶው ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የተቋማት ኃላፊዎችና አምባሳደሮች ደግሞ ሴቶች ናቸው።
በአጠቃላይ በዴሞክራሲ ተቋማት፣ በፍርድ ቤቶች፣ በከንቲባነትና በአስተዳዳሪነት ደረጃ በኃላፊነት ተመድበው እንዲሠሩ ተደርጓል።
አሁን ላይ ሴቶች በቤተሰብና በአካባቢ ማሕበረሰብ ውስጥ የመደመጥ እና የመወሰን አቅማቸው 60 በመቶ ደርሷል።
ይህ ተጨባጭ ተሳትፎ በሀገራዊ የፖሊሲ ቀረጻና በውሳኔ አሰጣጥ ሂደቶች ላይ ቀጥተኛ ተጽዕኖ እንዲኖራቸው ዕድል ፈጥሯል።
በኢኮኖሚ ዘርፍ በተወሰደው የሪፎርም እርምጃ የሴቶች የመሬት ባለቤትነትና የፋይናንስ ተጠቃሚነት ተረጋግጧል።
የሴቶች የባንክ ሒሳብ የመክፈት መጠን ከ20 በመቶ ወደ 43 በመቶ አድጓል።
13 ሚሊየን የሚሆኑት ሴቶች በብድርና ቁጠባ ማሕበራት ተደራጅተው 30 ቢሊየን የሚደርስ ብር ለመቆጠብ የቻሉ ሲሆን፥ 7 ሚሊየን የሚሆኑ ሴቶች ደግሞ የመሬት ባለቤትነታቸው ተረጋግጧል።
የሴቶችን ደህንነት በማረጋገጥ ዙሪያ በተሰራው ሥራ ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግሥታት የሥነ ሕዝብ ፈንድ ሽልማት እና እውቅና ለማግኘት በቅታለች።
በጤናው ዘርፍ የሴቶች የሥነ ተዋልዶ ጤና አገልግሎት ላይ መሠረታዊ ዕድገት የተመዘገበ ሲሆን፤ በትምህርት ዘርፍም የሴቶች ተሳትፎ በመጀመሪያና በሁለተኛ ደረጃ ከወንዶች እኩል ሆኗል።
በዲጂታል ዘርፍ የሞባይል ስልክ ተጠቃሚ የሆኑ ሴቶች ድርሻ 49 በመቶ የደረሰ ሲሆን፥ ከእነዚህ ውስጥ 36 በመቶ የሚሆኑት ለፋይናንስ ግብይት እየተጠቀሙበት ይገኛሉ።
10 days ago
የአይኤምኤፍ (IMF) የብር ምንዛሬ ሙሉ በሙሉ በገበያ እንዲወሰንና ድጎማዎች እንዲነሱ ጠየቀ
#fastmereja I የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ልዑክ በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም ላይ ያደረገውን አምስተኛ ግምገማ በአዲስ አበባ አጠናቋል። ድርጅቱ የኢትዮጵያ መንግስት የብርን የውጭ ምንዛሬ ተመን ሙሉ በሙሉ ለገበያ ፍላጎትና አቅርቦት እንዲተው፣ የመንግስት ቀጥተኛ ድጎማዎችን በሂደት እንዲያስወግድ እና የሀገር ውስጥ ታክስ ስብሰባን በከፍተኛ ሁኔታ እንዲያሳድግ ጠይቋል።
ይህ የአይኤምኤፍ ጥያቄ ተግባራዊ መሆን መጀመሩን ተከትሎ፣ ውሳኔው በተራው ህዝብ እና በንግዱ ማህበረሰብ ላይ ፈጣንና ከፍተኛ ጫና እያሳደረ ይገኛል። የብር የመግዛት አቅም መውረድ፣ የዋጋ ንረት መናር እና የኑሮ ውድነት መባባስ ዋነኛ ማሳያዎች ናቸው።
በተጨማሪም መንግስት የታክስ ገቢውን ለማሳደግ የጀመረው ጥብቅ ቁጥጥር፣ መደበኛውን የታክስ ህግ የማስከበር ሂደት ወደ አስገዳጅ የቀየረው ይመስላል ሲሉ የዘርፉ ባለሙያዎች ስጋታቸውን ገልጸዋል።
ምንም እንኳን ማሻሻያው የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ መረጋጋትን ያመጣል ተብሎ በዓለም አቀፍ ተቋማት ቢታመንም፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ ግን ማህበረሰቡን እና የግሉን ዘርፍ ክፉኛ እየፈተነ ይገኛል። መንግስት በበኩሉ የድሆችን ጫና ለመቀነስ የማህበራዊ ደህንነት መረቦችን እንደሚዘረጋ ቀደም ሲል መግለጹ ይታወሳል።
ዘገባው የአዲስ ፎርቹን ነው።
#fastmereja I የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ልዑክ በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም ላይ ያደረገውን አምስተኛ ግምገማ በአዲስ አበባ አጠናቋል። ድርጅቱ የኢትዮጵያ መንግስት የብርን የውጭ ምንዛሬ ተመን ሙሉ በሙሉ ለገበያ ፍላጎትና አቅርቦት እንዲተው፣ የመንግስት ቀጥተኛ ድጎማዎችን በሂደት እንዲያስወግድ እና የሀገር ውስጥ ታክስ ስብሰባን በከፍተኛ ሁኔታ እንዲያሳድግ ጠይቋል።
ይህ የአይኤምኤፍ ጥያቄ ተግባራዊ መሆን መጀመሩን ተከትሎ፣ ውሳኔው በተራው ህዝብ እና በንግዱ ማህበረሰብ ላይ ፈጣንና ከፍተኛ ጫና እያሳደረ ይገኛል። የብር የመግዛት አቅም መውረድ፣ የዋጋ ንረት መናር እና የኑሮ ውድነት መባባስ ዋነኛ ማሳያዎች ናቸው።
በተጨማሪም መንግስት የታክስ ገቢውን ለማሳደግ የጀመረው ጥብቅ ቁጥጥር፣ መደበኛውን የታክስ ህግ የማስከበር ሂደት ወደ አስገዳጅ የቀየረው ይመስላል ሲሉ የዘርፉ ባለሙያዎች ስጋታቸውን ገልጸዋል።
ምንም እንኳን ማሻሻያው የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ መረጋጋትን ያመጣል ተብሎ በዓለም አቀፍ ተቋማት ቢታመንም፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ ግን ማህበረሰቡን እና የግሉን ዘርፍ ክፉኛ እየፈተነ ይገኛል። መንግስት በበኩሉ የድሆችን ጫና ለመቀነስ የማህበራዊ ደህንነት መረቦችን እንደሚዘረጋ ቀደም ሲል መግለጹ ይታወሳል።
ዘገባው የአዲስ ፎርቹን ነው።
10 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ሚያዚያ 13 እና 14፣ 2018 ዓ.ም. በአማራ ክልል ርዕሰ ከተማ ባህር ዳር ያደረጉትን ይፋዊ የስራ ጉብኝት አስመልክቶ በአዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ከአንድ ወር በኋላ ዛሬ የቪድዮ መግለጫ አውጥቷል። ኤምባሲው በትዊተር (ኤክስ) ገጹ እንዳስታወቀው፣ ይህ የአምባሳደሩ ጉብኝት አሜሪካ ለአማራ ህዝብ ሰላም፣ ደህንነት እና ብልጽግና ያላትን ዘላቂ ቁርጠኝነት በተግባር ያሳየ ነው።
አምባሳደር ማሲንጋ ጣና ሀይቅ ዳርቻ ላይ ሆነው በሰጡት እና ኤምባሲው ባጋራው የቪዲዮ መልዕክት ላይ፣ በስልጣን ዘመናቸው ለመጀመሪያ ጊዜ የአማራ ክልልን ርዕሰ ከተማ ለመጎብኘት በመቻላቸው የተሰማቸውን ከፍተኛ ደስታ ገልጸዋል። በቆይታቸውም ከህዝቡ እና ከባለስልጣናቱ እጅግ ደማቅ እና ሞቅ ያለ አቀባበል እንደተደረፈላቸው ተናግረዋል።
አምባሳደሩ በንግግራቸው ክልሉ እና ህዝቡ እጅግ ፈታኝ የሆኑ ጊዜያትን ማሳለፋቸውን እና ከፍተኛ ስቃይ ውስጥ መቆየታቸውን አስምረውበታል። "ይህ ቀጠና ብዙ መከራዎችን እንዳሳለፈ ግልጽ ነው፤ ብዙ ስቃይ ነበረ። ይህንን ችላ ማለትም ሆነ መካድ አንችልም" በማለት ያለውን ነባራዊ ሁኔታ አምነዋል። ይሁን እንጂ፣ ከፖለቲካ መሪዎች አልፎ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እና ተራ ዜጎች ጋር ባደረጉት ውይይት፣ ህዝቡ የተሻለ ነገን ተስፋ ከማድረግ ባለፈ ይህ አሁን ያለው ቀውስ በተቻለ ፍጥነት እንዲያበቃ በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚጠብቅ መገንዘባቸውን አብራርተዋል።
አምባሳደር ማሲንጋ በጉብኝታቸው ወቅት የኤም.ኤስ.ኤ የፋብሪካ ማዕከልን ተዘዋውረው ተመልክተዋል። ይህ ተቋም እንስሳት መኖ እና የምግብ ዘይት በማምረት ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ ከፍተኛ ጥራት ያለውን የፕሮቲን ምርት ወደ አሜሪካ እና ሌሎች ሀገራት ጭምር በመላክ ላይ ይገኛል። አምባሳደሩ ድርጅቱ በዚህ ፈታኝ ወቅት ውስጥ ሆኖም በአብዛኛው ከአሜሪካ በመጣ ቴክኖሎጂ፣ ፈጠራ እና ኢንቨስትመንት በመጠቀም የባህር ዳርን እና የአማራን ብቻ ሳይሆን የመላው ኢትዮጵያን ኢኮኖሚ በመለወጥ ላይ እንደሚገኝ ገልጸው አድናቆታቸውን ችረዋል።
አክለውም አምባሳደሩ በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ (በተለይም በኢትዮጵያ ጨርቃጨርቅ እና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት) ሰፊ ጊዜ አሳልፈዋል። ተቋሙ የገጠመውን ፈተና ወደ መልካም እድል በመቀየር ከፍተኛ ጥራት ያለው ትምህርት እየሰጠ በመሆኑ፣ በአሁኑ ወቅት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ለሚያጠናቅቁ ተማሪዎች ተመራጭ ዩኒቨርሲቲ መሆን መቻሉን ተናግረዋል። አሜሪካም ዩኒቨርሲቲው ራሱን የቻለ ተቋም ለመሆን የጀመረውን ጉዞ በመደገፍ አብራ ለመስራት በጉጉት እንደምትጠብቅ አስታውቀዋል።
አምባሳደር ማሲንጋ አደረኩት ባሉት የሁለት ቀናት ጉብኝት፣ የአማራ ህዝብ አሁን ካለበት ቀውስ አገግሞ በቀጣዮቹ ዓመታት ለመበልጸግ ዝግጁ እና ሙሉ አቅም ያለው መሆኑን በሚገባ እንዳመኑበት በማረጋገጥ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
አምባሳደር ማሲንጋ ጣና ሀይቅ ዳርቻ ላይ ሆነው በሰጡት እና ኤምባሲው ባጋራው የቪዲዮ መልዕክት ላይ፣ በስልጣን ዘመናቸው ለመጀመሪያ ጊዜ የአማራ ክልልን ርዕሰ ከተማ ለመጎብኘት በመቻላቸው የተሰማቸውን ከፍተኛ ደስታ ገልጸዋል። በቆይታቸውም ከህዝቡ እና ከባለስልጣናቱ እጅግ ደማቅ እና ሞቅ ያለ አቀባበል እንደተደረፈላቸው ተናግረዋል።
አምባሳደሩ በንግግራቸው ክልሉ እና ህዝቡ እጅግ ፈታኝ የሆኑ ጊዜያትን ማሳለፋቸውን እና ከፍተኛ ስቃይ ውስጥ መቆየታቸውን አስምረውበታል። "ይህ ቀጠና ብዙ መከራዎችን እንዳሳለፈ ግልጽ ነው፤ ብዙ ስቃይ ነበረ። ይህንን ችላ ማለትም ሆነ መካድ አንችልም" በማለት ያለውን ነባራዊ ሁኔታ አምነዋል። ይሁን እንጂ፣ ከፖለቲካ መሪዎች አልፎ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እና ተራ ዜጎች ጋር ባደረጉት ውይይት፣ ህዝቡ የተሻለ ነገን ተስፋ ከማድረግ ባለፈ ይህ አሁን ያለው ቀውስ በተቻለ ፍጥነት እንዲያበቃ በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚጠብቅ መገንዘባቸውን አብራርተዋል።
አምባሳደር ማሲንጋ በጉብኝታቸው ወቅት የኤም.ኤስ.ኤ የፋብሪካ ማዕከልን ተዘዋውረው ተመልክተዋል። ይህ ተቋም እንስሳት መኖ እና የምግብ ዘይት በማምረት ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ ከፍተኛ ጥራት ያለውን የፕሮቲን ምርት ወደ አሜሪካ እና ሌሎች ሀገራት ጭምር በመላክ ላይ ይገኛል። አምባሳደሩ ድርጅቱ በዚህ ፈታኝ ወቅት ውስጥ ሆኖም በአብዛኛው ከአሜሪካ በመጣ ቴክኖሎጂ፣ ፈጠራ እና ኢንቨስትመንት በመጠቀም የባህር ዳርን እና የአማራን ብቻ ሳይሆን የመላው ኢትዮጵያን ኢኮኖሚ በመለወጥ ላይ እንደሚገኝ ገልጸው አድናቆታቸውን ችረዋል።
አክለውም አምባሳደሩ በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ (በተለይም በኢትዮጵያ ጨርቃጨርቅ እና ፋሽን ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት) ሰፊ ጊዜ አሳልፈዋል። ተቋሙ የገጠመውን ፈተና ወደ መልካም እድል በመቀየር ከፍተኛ ጥራት ያለው ትምህርት እየሰጠ በመሆኑ፣ በአሁኑ ወቅት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ለሚያጠናቅቁ ተማሪዎች ተመራጭ ዩኒቨርሲቲ መሆን መቻሉን ተናግረዋል። አሜሪካም ዩኒቨርሲቲው ራሱን የቻለ ተቋም ለመሆን የጀመረውን ጉዞ በመደገፍ አብራ ለመስራት በጉጉት እንደምትጠብቅ አስታውቀዋል።
አምባሳደር ማሲንጋ አደረኩት ባሉት የሁለት ቀናት ጉብኝት፣ የአማራ ህዝብ አሁን ካለበት ቀውስ አገግሞ በቀጣዮቹ ዓመታት ለመበልጸግ ዝግጁ እና ሙሉ አቅም ያለው መሆኑን በሚገባ እንዳመኑበት በማረጋገጥ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
Sponsored by
Surafel
10 days ago
አሁን በስራ ላይ ያሉ ሁሉም አሽከርካሪዎች ሰልጥነው የብቃት ምዘና አንዲወስዱ የሚያስገድድ ዘመናዊ የቁጥጥር ሥርዓት ሊዘረጋ ነው፡፡
ሁሉም አሽከርካሪዎች እንደገና እንዲሰለጥኑና እንዲመዘኑ በማድረግ ብቃታቸውን እንዲያረጋግጡ የሚያስችል I አጠቃላይ የሰነድ ዝግጅት ተጠናቋል ያለው የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ነው፡፡
ይህ አዲስ አሰራር ከተለመደው አሰራር በተለየ መልኩ ሙሉ በሙሉ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ፣ የምዘና ሂደቱ በዲጂታል ሲስተም እንዲመራ ተደርጎ ተቀርጿል ሲል ሚኒስቴር መ/ቤቱ መባህበራዊ ትስስር ገጹ ባወጣው መገለጫ ላይ ጠቅሷል ።
አሽከርካሪዎች ፈተናውን ከመውሰዳቸው በፊት ቅድሚያ ስልጠና ይወስዳሉ ተብሏል ።
በዚሁ መሰረት ይህንን ሀገራዊ ፕሮጀክት በይፋ ወደ ትግበራ ለማስገባት በተለይም አጠቃላይ የአሽከርካሪዎች ምዝገባ እና ስልጠና በተመለከተ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ከኤስ ዲ ኤስ ሴፍቲ ኤንድ ድራይቪንግ ስኪልስ ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችለውን የስራ ውል ስምምነት መፈረማቸው ተሰምቷል።
በመሆኑም ይህ "ሀገር አቀፍ የአሽከርካሪዎች የብቃት ምዘና፣ የስልጠና እና የደህንነት ማሻሻያ ፕሮጀክት" የመንገድ የትራፊክ ደህንነትን በማጠናከር ረገድ የጎላ ሚና ይኖረዋል ተብሎ ተገምቷል፡፡
ማናቸውም አሽከርካሪዎች በሙሉ አዲሱን የብቃት ምዘና በመውሰድ እና በተቀመጠው መስፈርት መሰረት ብቃታቸውን በተጨባጭ በማረጋገጥ ብቻ እንዲያሽከረክሩ የሚያስገድድ ዘመናዊ የቁጥጥር ሥርዓት ይዘረጋል ተብሏል።
ይህ አሰራር የመንገድ ደህንነትን በከፍተኛ ደረጃ በማሻሻል ዜጎቻችን ብሎም ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች በመንገድ የትራፊክ አደጋ ምክንያት ሞትና የአካል ጉዳት እንዲሁም የንብረት ውድመት ለመቀነስ ጉልህ አስተዋፅኦ የሚያበረክት መሆኑ ከፍተኛ እምነት ተጥሎበታል።
በመሆኑም ሁሉም አሽከርካሪ በዚህ ሂደት የሚያልፍ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ በተለይም ለዚህ ዙር በቅድሚያ ማንኛውም የንግድ ተሽከርካሪ የሚያሽከረክር አሽከርካሪ የምዝገባና የስልጠና እንዲሁም የምዘና ሂደቱ በቅርቡ ስለሚጀመር ሁሉም ዝግጁ እንዲሆን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አሳስቧል።
Sheger Fm
ሁሉም አሽከርካሪዎች እንደገና እንዲሰለጥኑና እንዲመዘኑ በማድረግ ብቃታቸውን እንዲያረጋግጡ የሚያስችል I አጠቃላይ የሰነድ ዝግጅት ተጠናቋል ያለው የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ነው፡፡
ይህ አዲስ አሰራር ከተለመደው አሰራር በተለየ መልኩ ሙሉ በሙሉ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ፣ የምዘና ሂደቱ በዲጂታል ሲስተም እንዲመራ ተደርጎ ተቀርጿል ሲል ሚኒስቴር መ/ቤቱ መባህበራዊ ትስስር ገጹ ባወጣው መገለጫ ላይ ጠቅሷል ።
አሽከርካሪዎች ፈተናውን ከመውሰዳቸው በፊት ቅድሚያ ስልጠና ይወስዳሉ ተብሏል ።
በዚሁ መሰረት ይህንን ሀገራዊ ፕሮጀክት በይፋ ወደ ትግበራ ለማስገባት በተለይም አጠቃላይ የአሽከርካሪዎች ምዝገባ እና ስልጠና በተመለከተ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ከኤስ ዲ ኤስ ሴፍቲ ኤንድ ድራይቪንግ ስኪልስ ጋር በትብብር ለመስራት የሚያስችለውን የስራ ውል ስምምነት መፈረማቸው ተሰምቷል።
በመሆኑም ይህ "ሀገር አቀፍ የአሽከርካሪዎች የብቃት ምዘና፣ የስልጠና እና የደህንነት ማሻሻያ ፕሮጀክት" የመንገድ የትራፊክ ደህንነትን በማጠናከር ረገድ የጎላ ሚና ይኖረዋል ተብሎ ተገምቷል፡፡
ማናቸውም አሽከርካሪዎች በሙሉ አዲሱን የብቃት ምዘና በመውሰድ እና በተቀመጠው መስፈርት መሰረት ብቃታቸውን በተጨባጭ በማረጋገጥ ብቻ እንዲያሽከረክሩ የሚያስገድድ ዘመናዊ የቁጥጥር ሥርዓት ይዘረጋል ተብሏል።
ይህ አሰራር የመንገድ ደህንነትን በከፍተኛ ደረጃ በማሻሻል ዜጎቻችን ብሎም ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች በመንገድ የትራፊክ አደጋ ምክንያት ሞትና የአካል ጉዳት እንዲሁም የንብረት ውድመት ለመቀነስ ጉልህ አስተዋፅኦ የሚያበረክት መሆኑ ከፍተኛ እምነት ተጥሎበታል።
በመሆኑም ሁሉም አሽከርካሪ በዚህ ሂደት የሚያልፍ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ በተለይም ለዚህ ዙር በቅድሚያ ማንኛውም የንግድ ተሽከርካሪ የሚያሽከረክር አሽከርካሪ የምዝገባና የስልጠና እንዲሁም የምዘና ሂደቱ በቅርቡ ስለሚጀመር ሁሉም ዝግጁ እንዲሆን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አሳስቧል።
Sheger Fm
10 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በኢራን እና አካባቢው ያሉትን አጠቃላይ የአሜሪካ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች የሚያስተባብረው ማዕከላዊ እዝ ባለፉት ጥቂት ሰዓታት ውስጥ ባወጣው መግለጫ፣ እነዚህ ክስተቶች ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ የተፈጸሙ መሆናቸውን እና እርምጃው የአሜሪካ ጦርን ደህንነት ለመጠበቅ ታስቦ የተወሰደ መሆኑን አስታውቋል።
አሜሪካ በጦሯ ላይ በቀጥታ ጥቃት ተሰንዝሯል እያለች አይደለም። ይልቁንም በተለይ በሚሳኤል ማስወንጨፊያ ጣቢያዎች እና ፈንጂዎችን ሊያጠምዱ በነበሩ ጀልባዎች ላይ የተወሰደው እርምጃ፣ በአካባቢው የሚገኙ ወታደሮቿን ለመጠበቅ የተደረገ 'የቅድመ መከላከል' እርምጃ መሆኑን ነው የገለጸችው።
እንዲህ ዓይነት ድርጊቶች ከዚህ ቀደምም ተከስተው ያውቃሉ። የተኩስ አቁም ስምምነቱ በተጀመረበት የመጀመሪያ ጊዜ ተመሳሳይ ክስተት አጋጥሞ የነበረ ሲሆን፣ በወቅቱ አሜሪካ ምንም ዓይነት የሰው ህይወት ጥፋት ባለመኖሩ ድርጊቱ የተኩስ አቁም ስምምነቱን እንደመጣስ እንደማይቆጠር ገልጻ ነበር።
አሁንም በተመሳሳይ በዚህኛው ክስተት፣ ምንም ዓይነት የአሜሪካ ጦር አባል እንዳልተገደለ ወይም እንዳልቆሰለ አሜሪካ አረጋግጣለች። ይህም ሁኔታው የተኩስ አቁም ስምምነቱን ወደ መጣስ ደረጃ እንደማይደርስ የሚያመላክት ነው። በመሆኑም በአሁኑ ወቅት በርካታ ሀገራትን አሳትፎ እየተካሄደ ያለውን የድርድር ሂደት የሚያስተጓጉል አይሆንም።
ይሁን እንጂ፣ክስተቱ ለሁለቱም ሀገራት አሳሳቢ ወቅት መሆኑ አይካድም። ከሁሉም በላይ ደግሞ ይህ እርምጃ የአሜሪካ ወታደራዊ ኃይል አሁንም ቢሆን ቀጠናውን ሙሉ በሙሉ እንዳልለቀቀ የሚያስታውስ ነው።
አሜሪካ በጦሯ ላይ በቀጥታ ጥቃት ተሰንዝሯል እያለች አይደለም። ይልቁንም በተለይ በሚሳኤል ማስወንጨፊያ ጣቢያዎች እና ፈንጂዎችን ሊያጠምዱ በነበሩ ጀልባዎች ላይ የተወሰደው እርምጃ፣ በአካባቢው የሚገኙ ወታደሮቿን ለመጠበቅ የተደረገ 'የቅድመ መከላከል' እርምጃ መሆኑን ነው የገለጸችው።
እንዲህ ዓይነት ድርጊቶች ከዚህ ቀደምም ተከስተው ያውቃሉ። የተኩስ አቁም ስምምነቱ በተጀመረበት የመጀመሪያ ጊዜ ተመሳሳይ ክስተት አጋጥሞ የነበረ ሲሆን፣ በወቅቱ አሜሪካ ምንም ዓይነት የሰው ህይወት ጥፋት ባለመኖሩ ድርጊቱ የተኩስ አቁም ስምምነቱን እንደመጣስ እንደማይቆጠር ገልጻ ነበር።
አሁንም በተመሳሳይ በዚህኛው ክስተት፣ ምንም ዓይነት የአሜሪካ ጦር አባል እንዳልተገደለ ወይም እንዳልቆሰለ አሜሪካ አረጋግጣለች። ይህም ሁኔታው የተኩስ አቁም ስምምነቱን ወደ መጣስ ደረጃ እንደማይደርስ የሚያመላክት ነው። በመሆኑም በአሁኑ ወቅት በርካታ ሀገራትን አሳትፎ እየተካሄደ ያለውን የድርድር ሂደት የሚያስተጓጉል አይሆንም።
ይሁን እንጂ፣ክስተቱ ለሁለቱም ሀገራት አሳሳቢ ወቅት መሆኑ አይካድም። ከሁሉም በላይ ደግሞ ይህ እርምጃ የአሜሪካ ወታደራዊ ኃይል አሁንም ቢሆን ቀጠናውን ሙሉ በሙሉ እንዳልለቀቀ የሚያስታውስ ነው።