6 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ዋሽንግተን በአፍሪካ ያላትን የመሰረተ ልማት እና የኢንቨስትመንት ተጽእኖ ከቻይና እና ሌሎች ኃያላን ሀገራት ጋር እያወዳደረች ባለችበት በአሁኑ ወቅት፣ አሜሪካ ኩባንያዎቿ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሚገነባው የ12.5 ቢሊዮን ዶላሩ የቢሾፍቱ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት ውስጥ ሚና እንዲኖራቸው እንደምትፈልግ አንድ ከፍተኛ የአሜሪካ የንግድ ሚኒስቴር ባለስልጣን ረቡዕ ዕለት አስታወቁ።
በመካከለኛው ምስራቅ እና አፍሪካ የአሜሪካ የንግድ ምክትል ረዳት ሚኒስትር ማርክ ሚቼል እንዳሉት፣ ዋሽንግተን በአየር ማረፊያው ፕሮጀክት ውስጥ የአሜሪካን ተሳትፎ ለማረጋገጥ በቅርበት እየሰራች ነው። ሚቼል ይህንን የተናገሩት በአዲስ አበባ በተካሄደው የአፍሪካ ሎጂስቲክስ እና ኮሙዩኒኬሽን ሲምፖዚየም ላይ በበይነ-መረብ በሰጡት መግለጫ ሲሆን፣ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ኃላፊዎች ጋር መወያየታቸውንም ገልጸዋል። የአሜሪካ ኩባንያዎች በፕሮጀክቱ ውስጥ ምን ዓይነት ሚና ሊጫወቱ እንደሚችሉ በግልጽ ባያስቀምጡም፣ ይህ ተሳትፎ በጄኔራል ኤሌክትሪክ ሞተሮች የሚሰሩ ተጨማሪ የቦይንግ አውሮፕላኖችን ወደ መግዛት ሊያመራ እንደሚችል ጠቁመዋል። አየር መንገዱ ባለፈው ሚያዝያ ወር ቀደም ሲል ካዘዛቸው 20 ጄቶች በተጨማሪ ስድስት ተጨማሪ የቦይንግ 787-9 ድሪምላይነር አውሮፕላኖችን ለመግዛት መስማማቱ ይታወሳል።
ከአዲስ አበባ 45 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በደቡብ ምስራቅ አቅጣጫ የሚገኘው እና ባለ አራት የመሮጫ መንገድ ያለው ይህ የአየር ማረፊያ ግንባታ ባለፈው ጥር ወር የተጀመረ ሲሆን፣ በ2030 ሲጠናቀቅ "የአፍሪካ ዱባይ" ለማድረግ የታለመ ነው። ለዚህ ግዙፍ ፕሮጀክት የአፍሪካ ልማት ባንክ 500 ሚሊዮን ዶላር የገባ ሲሆን፣ ቀሪውን 8.7 ቢሊዮን ዶላር የማፈላለጉን ጥረት እየመራ ይገኛል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ባለፈው ሚያዝያ ወር እንደተናገሩት፣ የአሜሪካ የፋይናንስ ተቋማት በፕሮጀክቱ ውስጥ ለመሳተፍ ፍላጎት አሳይተዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘም ሚቼል፣ የአሜሪካን አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ቴክኖሎጂ ምርቶችን ወደ ውጭ የመላክ ጥረት አካል በመሆን የንግድ ሚኒስቴሩ ከኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጋር ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር እየሰራ መሆኑን አክለው ገልጸዋል።
በመካከለኛው ምስራቅ እና አፍሪካ የአሜሪካ የንግድ ምክትል ረዳት ሚኒስትር ማርክ ሚቼል እንዳሉት፣ ዋሽንግተን በአየር ማረፊያው ፕሮጀክት ውስጥ የአሜሪካን ተሳትፎ ለማረጋገጥ በቅርበት እየሰራች ነው። ሚቼል ይህንን የተናገሩት በአዲስ አበባ በተካሄደው የአፍሪካ ሎጂስቲክስ እና ኮሙዩኒኬሽን ሲምፖዚየም ላይ በበይነ-መረብ በሰጡት መግለጫ ሲሆን፣ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ኃላፊዎች ጋር መወያየታቸውንም ገልጸዋል። የአሜሪካ ኩባንያዎች በፕሮጀክቱ ውስጥ ምን ዓይነት ሚና ሊጫወቱ እንደሚችሉ በግልጽ ባያስቀምጡም፣ ይህ ተሳትፎ በጄኔራል ኤሌክትሪክ ሞተሮች የሚሰሩ ተጨማሪ የቦይንግ አውሮፕላኖችን ወደ መግዛት ሊያመራ እንደሚችል ጠቁመዋል። አየር መንገዱ ባለፈው ሚያዝያ ወር ቀደም ሲል ካዘዛቸው 20 ጄቶች በተጨማሪ ስድስት ተጨማሪ የቦይንግ 787-9 ድሪምላይነር አውሮፕላኖችን ለመግዛት መስማማቱ ይታወሳል።
ከአዲስ አበባ 45 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በደቡብ ምስራቅ አቅጣጫ የሚገኘው እና ባለ አራት የመሮጫ መንገድ ያለው ይህ የአየር ማረፊያ ግንባታ ባለፈው ጥር ወር የተጀመረ ሲሆን፣ በ2030 ሲጠናቀቅ "የአፍሪካ ዱባይ" ለማድረግ የታለመ ነው። ለዚህ ግዙፍ ፕሮጀክት የአፍሪካ ልማት ባንክ 500 ሚሊዮን ዶላር የገባ ሲሆን፣ ቀሪውን 8.7 ቢሊዮን ዶላር የማፈላለጉን ጥረት እየመራ ይገኛል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ባለፈው ሚያዝያ ወር እንደተናገሩት፣ የአሜሪካ የፋይናንስ ተቋማት በፕሮጀክቱ ውስጥ ለመሳተፍ ፍላጎት አሳይተዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘም ሚቼል፣ የአሜሪካን አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ቴክኖሎጂ ምርቶችን ወደ ውጭ የመላክ ጥረት አካል በመሆን የንግድ ሚኒስቴሩ ከኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጋር ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር እየሰራ መሆኑን አክለው ገልጸዋል።
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ዛሬ በመካሄድ ላይ ባለው ሀገራዊ ምርጫ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ስልጣናቸውን ዳግም እንደሚያረጋግጡ በሰፊው ቢጠበቅም፣ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የተፈጠሩት የጸጥታ ስጋቶች ዳግም ግጭት ሊቀሰቅሱ ይችላሉ የሚል ከባድ ፍርሃት አሳድረዋል። እያደገ በመጣው የፀጥታ ችግር እና የፖለቲካ ውጥረት ምክንያት በተወሰኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ፈጽሞ ላይካሄድ እንደሚችል መረጃዎች ያመለክታሉ።
ምንም እንኳን የሁለት ዓመቱን አውዳሚ የእርስ በርስ ጦርነት ያስቆመው የሰላም ስምምነት እ.ኤ.አ. በ2022 ቢፈረምም፣ በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል በትግራይ ክልል አሁንም የፖለቲካ ትኩሳት እያየለ ይገኛል። በተለይም ከጦርነቱ በፊት የነበረው የክልሉ ምክር ቤት በቅርቡ ዳግም መመለሱን ተከትሎ፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ መንግስት እና በክልሉ መሪዎች መካከል ያለው የፖለቲካ ተጽዕኖ ፈጣሪነት ሽኩቻ አሁንም እንዳልበረደ እና ቀጣይነት ያለው ፉክክር መኖሩን ቁልጭ አድርጎ ያሳያል።
ከፖለቲካው ውጥረት ጎን ለጎን መንግስት እያካሄደ ያለው የኢኮኖሚ ማሻሻያ በምርጫው ወቅት እንደ ትልቅ ስኬት ሲነሳ ይታያል። የአፍሪካ ልማት ባንክ ባወጣው የትንበያ ሪፖርት መሠረት፣ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ2025-26 በጀት ዓመት 7.8 በመቶ፣ እንዲሁም በ2026-27 በ8.5 በመቶ ዕድገት ያስመዘግባል ተብሎ ይጠበቃል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ነፃ በማድረግ እና ለውጭ ኩባንያዎች ክፍት በማድረግ ሰፊ ዘመቻ ያካሄዱ ሲሆን፣ ባለፈው ዓመት የስቶክ ማርኬት ዳግም ማስጀመራቸው እና የመንግስት የልማት ድርጅቶችን የገቢ ማስገኛ አቅም ማሳደጋቸው የዚሁ ማሻሻያ አካል ነው። ይሁን እንጂ ይህ የኢኮኖሚ ተስፋ እና ዕድገት የአፍሪካ ልማት ባንክ "ከአቅም በላይ የሆነ" ሲል በገለጸው እጅግ አሳሳቢ እና ከባድ በሆነ የሀገሪቱ የውጭ ዕዳ ጫና ክፉኛ እየተፈተነ ይገኛል።
ምንም እንኳን የሁለት ዓመቱን አውዳሚ የእርስ በርስ ጦርነት ያስቆመው የሰላም ስምምነት እ.ኤ.አ. በ2022 ቢፈረምም፣ በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል በትግራይ ክልል አሁንም የፖለቲካ ትኩሳት እያየለ ይገኛል። በተለይም ከጦርነቱ በፊት የነበረው የክልሉ ምክር ቤት በቅርቡ ዳግም መመለሱን ተከትሎ፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ መንግስት እና በክልሉ መሪዎች መካከል ያለው የፖለቲካ ተጽዕኖ ፈጣሪነት ሽኩቻ አሁንም እንዳልበረደ እና ቀጣይነት ያለው ፉክክር መኖሩን ቁልጭ አድርጎ ያሳያል።
ከፖለቲካው ውጥረት ጎን ለጎን መንግስት እያካሄደ ያለው የኢኮኖሚ ማሻሻያ በምርጫው ወቅት እንደ ትልቅ ስኬት ሲነሳ ይታያል። የአፍሪካ ልማት ባንክ ባወጣው የትንበያ ሪፖርት መሠረት፣ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ2025-26 በጀት ዓመት 7.8 በመቶ፣ እንዲሁም በ2026-27 በ8.5 በመቶ ዕድገት ያስመዘግባል ተብሎ ይጠበቃል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ነፃ በማድረግ እና ለውጭ ኩባንያዎች ክፍት በማድረግ ሰፊ ዘመቻ ያካሄዱ ሲሆን፣ ባለፈው ዓመት የስቶክ ማርኬት ዳግም ማስጀመራቸው እና የመንግስት የልማት ድርጅቶችን የገቢ ማስገኛ አቅም ማሳደጋቸው የዚሁ ማሻሻያ አካል ነው። ይሁን እንጂ ይህ የኢኮኖሚ ተስፋ እና ዕድገት የአፍሪካ ልማት ባንክ "ከአቅም በላይ የሆነ" ሲል በገለጸው እጅግ አሳሳቢ እና ከባድ በሆነ የሀገሪቱ የውጭ ዕዳ ጫና ክፉኛ እየተፈተነ ይገኛል።
3 months ago
'አፍሪካ ሪ' ግማሽ ክፍለ ዘመኑን በአዲስ አበባ አከበረ
#ethiopia | በአፍሪካ ግዙፉ የጠለፋ ዋስትና ሰጪ ተቋም የሆነው ''አፍሪካ ሪ'' ፣ የተመሠረተበትን 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል እና 180ኛ መደበኛ የቦርድ ስብሰባውን በአፍሪካ መዲና አዲስ አበባ አካሂዷል።
እ.ኤ.አ በየካቲት 24 ቀን 1976 በያውንዴ ካሜሩን በአፍሪካ አንድነት ድርጅት (OAU) አባል በነበሩ 36 ሀገራት ጥረት የተመሠረተው ይህ ተቋም፣ ባለፉት 50 ዓመታት ውስጥ ለአህጉሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገትና ለኢንሹራንስ ዘርፉ መጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ሲያበረክት ቆይቷል።
ተቋሙ ባለፉት 50 ዓመታት ከ500 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚገመት የመልሶ መድን ሽፋን በተለያዩ ዘርፎች ሰጥቷል።
በ2025 በታሪኩ ከፍተኛ የተባለውን 199 ሚሊዮን ዶላር የተጣራ ትርፍ ያስመዘገበ ሲሆን፣ አጠቃላይ ሀብቱም 2.69 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል።
በአሁኑ ወቅት 42 የአፍሪካ ሀገራትን፣ የአፍሪካ ልማት ባንክን እና 112 የመድን ኩባንያዎችን በአክሲዮን ባለቤትነት ይዟል።
ተቋሙ ከዓለም አቀፍ ደረጃ አሰጣጥ ተቋማት (S&P እና AM Best) የ "A" (ጠንካራ/Excellent) ደረጃን አግኝቷል።
ኢትዮጵያ በተቋሙ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ቦታ ያላት ሲሆን፣ አፍሪካ ሪ ከ2011 ጀምሮ በአዲስ አበባ የራሱን ቢሮ ከፍቶ እየሠራ ይገኛል።
በአሁኑ ወቅት በካሳንቺስ አካባቢ ያስገነባው አዲሱ ሕንፃ ተቋሙ በኢትዮጵያ ያለውን የረጅም ጊዜ ኢንቨስትመንትና ቁርጠኝነት የሚያሳይ ሆኗል።
በተጨማሪም ተቋሙ ለኢትዮጵያ የመድን ኩባንያዎች የቴክኒክና የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን በመስጠት ላይ ይገኛል።
ባለፈው ምሽት በስካይላይት ሆቴል በተካሄደ ደማቅ የጋላ ኮክቴል ሥነ-ሥርዓት የቦርድ አባላት፣ የኢትዮጵያ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች እና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት ታድመዋል።
የአፍሪካ ሪ ዋና መሥሪያ ቤት በሌጎስ ናይጄሪያ ቢሆንም፣ በቀጣዩ ወር ሰኔ 2026 በአቡጃ አዲስ የመሥሪያ ቤት ሕንፃ እንደሚመረቅ ታውቋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#ethiopia | በአፍሪካ ግዙፉ የጠለፋ ዋስትና ሰጪ ተቋም የሆነው ''አፍሪካ ሪ'' ፣ የተመሠረተበትን 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል እና 180ኛ መደበኛ የቦርድ ስብሰባውን በአፍሪካ መዲና አዲስ አበባ አካሂዷል።
እ.ኤ.አ በየካቲት 24 ቀን 1976 በያውንዴ ካሜሩን በአፍሪካ አንድነት ድርጅት (OAU) አባል በነበሩ 36 ሀገራት ጥረት የተመሠረተው ይህ ተቋም፣ ባለፉት 50 ዓመታት ውስጥ ለአህጉሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገትና ለኢንሹራንስ ዘርፉ መጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ሲያበረክት ቆይቷል።
ተቋሙ ባለፉት 50 ዓመታት ከ500 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚገመት የመልሶ መድን ሽፋን በተለያዩ ዘርፎች ሰጥቷል።
በ2025 በታሪኩ ከፍተኛ የተባለውን 199 ሚሊዮን ዶላር የተጣራ ትርፍ ያስመዘገበ ሲሆን፣ አጠቃላይ ሀብቱም 2.69 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል።
በአሁኑ ወቅት 42 የአፍሪካ ሀገራትን፣ የአፍሪካ ልማት ባንክን እና 112 የመድን ኩባንያዎችን በአክሲዮን ባለቤትነት ይዟል።
ተቋሙ ከዓለም አቀፍ ደረጃ አሰጣጥ ተቋማት (S&P እና AM Best) የ "A" (ጠንካራ/Excellent) ደረጃን አግኝቷል።
ኢትዮጵያ በተቋሙ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ቦታ ያላት ሲሆን፣ አፍሪካ ሪ ከ2011 ጀምሮ በአዲስ አበባ የራሱን ቢሮ ከፍቶ እየሠራ ይገኛል።
በአሁኑ ወቅት በካሳንቺስ አካባቢ ያስገነባው አዲሱ ሕንፃ ተቋሙ በኢትዮጵያ ያለውን የረጅም ጊዜ ኢንቨስትመንትና ቁርጠኝነት የሚያሳይ ሆኗል።
በተጨማሪም ተቋሙ ለኢትዮጵያ የመድን ኩባንያዎች የቴክኒክና የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን በመስጠት ላይ ይገኛል።
ባለፈው ምሽት በስካይላይት ሆቴል በተካሄደ ደማቅ የጋላ ኮክቴል ሥነ-ሥርዓት የቦርድ አባላት፣ የኢትዮጵያ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች እና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት ታድመዋል።
የአፍሪካ ሪ ዋና መሥሪያ ቤት በሌጎስ ናይጄሪያ ቢሆንም፣ በቀጣዩ ወር ሰኔ 2026 በአቡጃ አዲስ የመሥሪያ ቤት ሕንፃ እንደሚመረቅ ታውቋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
3 months ago
አፍሪካ ሪ 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩውን በአዲስ አበባ አከበረ!
#fastmereja : በአህጉሪቱ ቀዳሚው የኢንሹራንስ ተቋም የሆነዉ አፍሪካ ሪ (Africa Re) የተመሰረተበትን 50ኛ ዓመት ወርቃማ ኢዮቤልዩ እና 180ኛውን የቦርድ ስብሰባ አስመልክቶ በትላንትናዉ እለት በስካይላይት ሆቴል በተካሄደዉ የጋላ ኮክቴል አቀባበል በደማቅ ሁኔታ አክብሯል።
በአህጉሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ ትልቅ ስም ያለው ይህ ተቋም፣ ግማሽ ክፍለ ዘመን ያስቆጠረውን የስኬት ጉዞ በአፍሪካ የፖለቲካ መዲና አዲስ አበባ ማክበሩ የኢትዮጵያን የመድን ገበያ ያለውን ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ የሚያሳይ መሆኑ ተገልጿል።
እ.ኤ.አ. በ1976 በካሜሩን ያውንዴ የተመሰረተው አፍሪካ ሪ፣ በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ በድጋሚ መድን ዘርፍ ከቀዳሚዎቹ 40 ተቋማት ተርታ የተሰለፈ ግዙፍ ተቋም ነው፡፡
ድርጅቱ በአሁኑ ወቅት የ42 አፍሪካ አገራት እና የአፍሪካ ልማት ባንክ፣ከ110 በላይ አፍሪካውያን የመድን ኩባንያዎች፤እንዲሁም ከፈረንሳይ፣ ከጀርመን እና ከካናዳ የመጡ ዓለም አቀፍ አጋሮች ባለቤትነት ያለበት ተቋም ሲሆን በ2025 በታሪኩ ከፍተኛ የተባለውን 1.34 ቢሊዮን ዶላርየፕሪሚየም ገቢ ያስመዘገበ ሲሆን፣ 199 ሚሊዮን ዶላር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱም ነዉ የተገለፀዉ።
የቦርድ ሰብሳቢው አቶ ሙስታፋ ኩሊባሊ (Mr. Moustapha Coulibaly) ለበዓሉ በሰጡት መግለጫ፣ “ይህ ወርቃማ ኢዮቤልዩ ለተቋሙ ብስለትን፣ ጥንካሬንና ጥበብን ይወክላል። አፍሪካ ሪ ከተቋምነት ባለፈ አፍሪካውያን በራሳቸው ሲተማመኑ ምን ዓይነት ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ውጤት ማምጣት እንደሚችሉ ያሳየ የስኬት ታሪካችን ነው'' ብለዋል።
አቶ ሙስታፋ አክለውም ተቋሙ እ.ኤ.አ. በ2030 የገቢ መጠኑን ወደ 2.5 ቢሊዮን ዶላር፣ በ2035 ደግሞ 5 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ግዙፍ ራዕይ ሰንቆ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ሪ ታሪክ ውስጥ ጉልህ ስፍራ እንዳላት የተገለፀ ሲሆን ድርጅቱ በአሁኑ ወቅት በካሳንቺስ አካባቢ የገነባው ዘመናዊ ሕንፃ ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑ እንዲሁም ተቋሙ በኢትዮጵያ ያለውን የኢንሹራንስ ዘርፍ ለማጠናከር በግብርና መድንና በቴክኒክ ዘርፎች ለአገር በቀል ኩባንያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን እየሰጠ እንደሚገኝ ነዉ የተገለፀዉ።
በስካይላይት ሆቴል በተካሄደዉ የጋላ ኮክቴል ግብዣ ላይ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ የአፍሪካ የፋይናንስ መሪዎችና ታዋቂ የንግድ ሰዎች የተገኙ ሲሆን ይህም መድረክ አፍሪካ ሪ ወደፊት በአህጉሪቱና በኢትዮጵያ በሚኖረው የኢንቨስትመንት አቅጣጫዎች ላይ ውይይት የሚደረግበት እንደሚሆን ተነግሯል።
አፍሪካ ሪ ባለፉት 50 ዓመታት ውስጥ በአህጉሪቱ ለሚከናወኑ የኢነርጂ፣ የግብርና፣ የቤት ልማትና የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ከ500 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚገመት የመድን ዋስትና ሽፋን (Cover) መስጠቱ ይታወሳል።
#fastmereja : በአህጉሪቱ ቀዳሚው የኢንሹራንስ ተቋም የሆነዉ አፍሪካ ሪ (Africa Re) የተመሰረተበትን 50ኛ ዓመት ወርቃማ ኢዮቤልዩ እና 180ኛውን የቦርድ ስብሰባ አስመልክቶ በትላንትናዉ እለት በስካይላይት ሆቴል በተካሄደዉ የጋላ ኮክቴል አቀባበል በደማቅ ሁኔታ አክብሯል።
በአህጉሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ ትልቅ ስም ያለው ይህ ተቋም፣ ግማሽ ክፍለ ዘመን ያስቆጠረውን የስኬት ጉዞ በአፍሪካ የፖለቲካ መዲና አዲስ አበባ ማክበሩ የኢትዮጵያን የመድን ገበያ ያለውን ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ የሚያሳይ መሆኑ ተገልጿል።
እ.ኤ.አ. በ1976 በካሜሩን ያውንዴ የተመሰረተው አፍሪካ ሪ፣ በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ በድጋሚ መድን ዘርፍ ከቀዳሚዎቹ 40 ተቋማት ተርታ የተሰለፈ ግዙፍ ተቋም ነው፡፡
ድርጅቱ በአሁኑ ወቅት የ42 አፍሪካ አገራት እና የአፍሪካ ልማት ባንክ፣ከ110 በላይ አፍሪካውያን የመድን ኩባንያዎች፤እንዲሁም ከፈረንሳይ፣ ከጀርመን እና ከካናዳ የመጡ ዓለም አቀፍ አጋሮች ባለቤትነት ያለበት ተቋም ሲሆን በ2025 በታሪኩ ከፍተኛ የተባለውን 1.34 ቢሊዮን ዶላርየፕሪሚየም ገቢ ያስመዘገበ ሲሆን፣ 199 ሚሊዮን ዶላር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱም ነዉ የተገለፀዉ።
የቦርድ ሰብሳቢው አቶ ሙስታፋ ኩሊባሊ (Mr. Moustapha Coulibaly) ለበዓሉ በሰጡት መግለጫ፣ “ይህ ወርቃማ ኢዮቤልዩ ለተቋሙ ብስለትን፣ ጥንካሬንና ጥበብን ይወክላል። አፍሪካ ሪ ከተቋምነት ባለፈ አፍሪካውያን በራሳቸው ሲተማመኑ ምን ዓይነት ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ውጤት ማምጣት እንደሚችሉ ያሳየ የስኬት ታሪካችን ነው'' ብለዋል።
አቶ ሙስታፋ አክለውም ተቋሙ እ.ኤ.አ. በ2030 የገቢ መጠኑን ወደ 2.5 ቢሊዮን ዶላር፣ በ2035 ደግሞ 5 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ግዙፍ ራዕይ ሰንቆ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ሪ ታሪክ ውስጥ ጉልህ ስፍራ እንዳላት የተገለፀ ሲሆን ድርጅቱ በአሁኑ ወቅት በካሳንቺስ አካባቢ የገነባው ዘመናዊ ሕንፃ ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑ እንዲሁም ተቋሙ በኢትዮጵያ ያለውን የኢንሹራንስ ዘርፍ ለማጠናከር በግብርና መድንና በቴክኒክ ዘርፎች ለአገር በቀል ኩባንያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን እየሰጠ እንደሚገኝ ነዉ የተገለፀዉ።
በስካይላይት ሆቴል በተካሄደዉ የጋላ ኮክቴል ግብዣ ላይ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ የአፍሪካ የፋይናንስ መሪዎችና ታዋቂ የንግድ ሰዎች የተገኙ ሲሆን ይህም መድረክ አፍሪካ ሪ ወደፊት በአህጉሪቱና በኢትዮጵያ በሚኖረው የኢንቨስትመንት አቅጣጫዎች ላይ ውይይት የሚደረግበት እንደሚሆን ተነግሯል።
አፍሪካ ሪ ባለፉት 50 ዓመታት ውስጥ በአህጉሪቱ ለሚከናወኑ የኢነርጂ፣ የግብርና፣ የቤት ልማትና የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ከ500 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚገመት የመድን ዋስትና ሽፋን (Cover) መስጠቱ ይታወሳል።
3 months ago
የአፍሪካ ፎርዋርድ 2026 ጉባኤ፦ ከአሮጌው የእርዳታ ዘይቤ ወደ አዲስ የኢኮኖሚና የቴክኖሎጂ ትብብር
*****************
በፈረንሳይ እና በአፍሪካ አህጉር መካከል ያለውን ዲፕሎማሲያዊና ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት ወደ አዲስ ምዕራፍ ለማሸጋገር ያለመው "አፍሪካ ፎርዋርድ" ጉባኤ በኬንያ መዲና ናይሮቢ በደመቀ ሁኔታ መጀመሩን ገልጸናል።
"አፍሪካ ፎርዋርድ፡ የአፍሪካ-ፈረንሳይ አጋርነት ለፈጠራ እና ለዕድገት" በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው ይህ ጉባኤ፣ ለበርካታ ዓመታት ሲተገበር ከቆየውና "ፍራንኮ-አፍሪካ" ተብሎ ከሚጠራው የተለመደ ግንኙነት ወጥቶ ሁሉንም የአፍሪካ ሀገራት ያካተተ አዲስ ስትራቴጂ ለመቅረጽ ያለመ ታሪካዊ መድረክ ነው።
ጉባኤው ፈረንሳይኛ ተናጋሪ ባልሆኑ እንደ ኬንያ ባሉ ሀገራት መካሄዱ፣ ፈረንሳይ ከአህጉሪቱ ጋር ያላትን ትብብር ይበልጥ ለማስፋትና ከአዳዲስ የኢኮኖሚ ማዕከላት ጋር ለመተሳሰር የጀመረችውን ቁርጠኝነት በተግባር የሚያሳይ ነው ተብሏል።
የጉባኤው ዋነኛ ግብም በአፍሪካ እና በፈረንሳይ መካከል ያለውን የኢኮኖሚ ትብብር ማጠናከር፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ማፋጠን እና በጋራ ክብር ላይ የተመሰረተ እኩል አጋርነትን መፍጠር እንደሆነ ታውቋል።
የዘንድሮው የአፍሪካ ፎርዋርድ ጉባኤ በሰባት ዋና ዋና ዘርፎች ላይ ትኩረቱን አድርጎ እየመከረ ይገኛል።
አፍሪካን የጥሬ ዕቃ ላኪ ከመሆን አውጥቶ ወደ አረንጓዴ ኢንዱስትሪ ማዕከልነት ለማሸጋገር የሚያስችለው የኢነርጂ ሽግግር፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ለአፍሪካ የሚሰጡትን ድጋፍ እንዲያሻሽሉ የሚጠይቀው የፋይናንስ ሥርዓት ለውጥ እና የባሕር ላይ ኢኮኖሚ ልማት በውይይቱ ከተነሱት ዐበይት ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ።
በዘላቂ ግብርና እና የምግብ ዋስትና፣ በሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) እና በዲጂታል ቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት እንዲሁም ጠንካራ የጤና ሥርዓት በመገንባት ረገድ አህጉሪቱ የራሷን ክትባትና መድኃኒት ማምረት የምትችልበትን ሁኔታ በዝርዝር እየተመለከተ ይገኛል።
ሰላምና ደኅንነትን እንደ ልማት መሠረት በመውሰድ አህጉራዊ የሰላም ማስከበር ጥረቶችን መደገፍም ሌላው የውይይቱ አንኳር ሆኖ ቀርቧል።
በዚህ ታሪካዊ ጉባኤ ላይ ከ30 በላይ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች እና የዓለም አቀፍ ተቋማት ኃላፊዎች ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የጉባኤው አስተናጋጅ የሆኑት የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ እና የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል።
እንደ ሩዋንዳው ፕሬዚዳንት ፖል ካጋሜ ያሉ መሪዎችም በተለያዩ የውይይት መድረኮች ላይ የመሪነት ሚናቸውን እየተወጡ ነው።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ፣ እንዲሁም የአፍሪካ ልማት ባንክ እና የዓለም ንግድ ድርጅት መሪዎች መገኘት ለውይይቱ ዓለም አቀፋዊ ክብደት ሰጥቶታል።
ከፖለቲካ መሪዎቹ ባሻገር እንደ አሊኮ ዳንጎቴ እና ስትራይቭ ማሲዪዋ ያሉ የአፍሪካ ባለሀብቶች ከፈረንሳይ ኩባንያዎች ጋር በቀጥታ ኢንቨስትመንት ዙሪያ እየመከሩ ነው።
ይህም ጉባኤው ከተለመደው የፖለቲካ ንግግር ባለፈ ወደ ተግባራዊ የኢኮኖሚ ትብብር መሸጋገሩን የሚያረጋግጥ እንደሆነ ነው መረጃዎች የሚያሳዩት።
በለሚ ታደሰ
#africa #france #africaforward2026 #economiccooperation #partnership #ebc
*****************
በፈረንሳይ እና በአፍሪካ አህጉር መካከል ያለውን ዲፕሎማሲያዊና ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት ወደ አዲስ ምዕራፍ ለማሸጋገር ያለመው "አፍሪካ ፎርዋርድ" ጉባኤ በኬንያ መዲና ናይሮቢ በደመቀ ሁኔታ መጀመሩን ገልጸናል።
"አፍሪካ ፎርዋርድ፡ የአፍሪካ-ፈረንሳይ አጋርነት ለፈጠራ እና ለዕድገት" በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው ይህ ጉባኤ፣ ለበርካታ ዓመታት ሲተገበር ከቆየውና "ፍራንኮ-አፍሪካ" ተብሎ ከሚጠራው የተለመደ ግንኙነት ወጥቶ ሁሉንም የአፍሪካ ሀገራት ያካተተ አዲስ ስትራቴጂ ለመቅረጽ ያለመ ታሪካዊ መድረክ ነው።
ጉባኤው ፈረንሳይኛ ተናጋሪ ባልሆኑ እንደ ኬንያ ባሉ ሀገራት መካሄዱ፣ ፈረንሳይ ከአህጉሪቱ ጋር ያላትን ትብብር ይበልጥ ለማስፋትና ከአዳዲስ የኢኮኖሚ ማዕከላት ጋር ለመተሳሰር የጀመረችውን ቁርጠኝነት በተግባር የሚያሳይ ነው ተብሏል።
የጉባኤው ዋነኛ ግብም በአፍሪካ እና በፈረንሳይ መካከል ያለውን የኢኮኖሚ ትብብር ማጠናከር፣ የቴክኖሎጂ ሽግግርን ማፋጠን እና በጋራ ክብር ላይ የተመሰረተ እኩል አጋርነትን መፍጠር እንደሆነ ታውቋል።
የዘንድሮው የአፍሪካ ፎርዋርድ ጉባኤ በሰባት ዋና ዋና ዘርፎች ላይ ትኩረቱን አድርጎ እየመከረ ይገኛል።
አፍሪካን የጥሬ ዕቃ ላኪ ከመሆን አውጥቶ ወደ አረንጓዴ ኢንዱስትሪ ማዕከልነት ለማሸጋገር የሚያስችለው የኢነርጂ ሽግግር፣ ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ለአፍሪካ የሚሰጡትን ድጋፍ እንዲያሻሽሉ የሚጠይቀው የፋይናንስ ሥርዓት ለውጥ እና የባሕር ላይ ኢኮኖሚ ልማት በውይይቱ ከተነሱት ዐበይት ጉዳዮች መካከል ይጠቀሳሉ።
በዘላቂ ግብርና እና የምግብ ዋስትና፣ በሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) እና በዲጂታል ቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት እንዲሁም ጠንካራ የጤና ሥርዓት በመገንባት ረገድ አህጉሪቱ የራሷን ክትባትና መድኃኒት ማምረት የምትችልበትን ሁኔታ በዝርዝር እየተመለከተ ይገኛል።
ሰላምና ደኅንነትን እንደ ልማት መሠረት በመውሰድ አህጉራዊ የሰላም ማስከበር ጥረቶችን መደገፍም ሌላው የውይይቱ አንኳር ሆኖ ቀርቧል።
በዚህ ታሪካዊ ጉባኤ ላይ ከ30 በላይ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች እና የዓለም አቀፍ ተቋማት ኃላፊዎች ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የጉባኤው አስተናጋጅ የሆኑት የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ እና የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን የመክፈቻ ንግግር አድርገዋል።
እንደ ሩዋንዳው ፕሬዚዳንት ፖል ካጋሜ ያሉ መሪዎችም በተለያዩ የውይይት መድረኮች ላይ የመሪነት ሚናቸውን እየተወጡ ነው።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ፣ እንዲሁም የአፍሪካ ልማት ባንክ እና የዓለም ንግድ ድርጅት መሪዎች መገኘት ለውይይቱ ዓለም አቀፋዊ ክብደት ሰጥቶታል።
ከፖለቲካ መሪዎቹ ባሻገር እንደ አሊኮ ዳንጎቴ እና ስትራይቭ ማሲዪዋ ያሉ የአፍሪካ ባለሀብቶች ከፈረንሳይ ኩባንያዎች ጋር በቀጥታ ኢንቨስትመንት ዙሪያ እየመከሩ ነው።
ይህም ጉባኤው ከተለመደው የፖለቲካ ንግግር ባለፈ ወደ ተግባራዊ የኢኮኖሚ ትብብር መሸጋገሩን የሚያረጋግጥ እንደሆነ ነው መረጃዎች የሚያሳዩት።
በለሚ ታደሰ
#africa #france #africaforward2026 #economiccooperation #partnership #ebc
Sponsored by
Surafel
3 months ago
ኢትዮጵያ በሙስና በየአመቱ እስከ 5 ቢሊዮን ዶላር እንደምታጣ የአፍሪካ ልማት ባንክ የ 2025 ሪፖርት ያሳያል። ይህን አሀዝ ወደ ብር ስንቀይረው 800 ቢሊዮን ብር ዘጭ ይላል። በብላክ ከመታነው ከ 1 ትሪሊዮን ብር በላይ! 5 ቢሊዮን ዶላር ማለት የኢትዮጵያ አጠቃላይ ጥቅል ምርት ወይንም GDP 4% ማለት ነው። ወይንም ኢትዮጵያ ከውጭ ንግድ ለማግኘት ካቀደቺው 9 ቢሊዮን ዶላር ከግማሽ በላይ ያክሉን የሚያክል ገንዘብ በቀማኛ ባለስልጣኖቿና ተባባሪ ባለሀብቶቿ እጥብ ተደርጋ ታጣለች ማለት ነው።
ይህ አሀዝ ኢትዮጵያ ለ 2018 በጀት ከበጀተቺው ውስጥ ግማሹን ቀርጥፎ ይበላል።
እናም ይህ የሪፖርተር አስደንጋጭ መረጃ ኢትዮጵያ ውስጥ ካለው እጅግ ስር የሰደደ ህዝቡን ያደኸየ ሙስናና ሌብነት ትንሹ ነው።
ባለስልጣን እና አርቲስቶች በአንድ ጊዜ 98 ቢሊዮን በሚዘርፉባት ሀገር እድገት ይመጣል ተብሎ ማሰብ ዘበት ነው።
ወይ ከሌብነት ወይ ከእድገት መመረጥ የመንግስት ውሳኔ ነው።
seledadotio
seledadotio
ይህ አሀዝ ኢትዮጵያ ለ 2018 በጀት ከበጀተቺው ውስጥ ግማሹን ቀርጥፎ ይበላል።
እናም ይህ የሪፖርተር አስደንጋጭ መረጃ ኢትዮጵያ ውስጥ ካለው እጅግ ስር የሰደደ ህዝቡን ያደኸየ ሙስናና ሌብነት ትንሹ ነው።
ባለስልጣን እና አርቲስቶች በአንድ ጊዜ 98 ቢሊዮን በሚዘርፉባት ሀገር እድገት ይመጣል ተብሎ ማሰብ ዘበት ነው።
ወይ ከሌብነት ወይ ከእድገት መመረጥ የመንግስት ውሳኔ ነው።
seledadotio
seledadotio
5 months ago
በኢትዮጵያ የወጣቶች ሥራ አጥነት 23% ደረሰ
#ethiopia | የአፍሪካ ልማት ባንክ ባወጣው አዲስ የስትራቴጂ ግምገማ ሪፖርት፣ በኢትዮጵያ የወጣቶች ሥራ አጥነት መጠን 23.1 በመቶ መድረሱን ይፋ አደረገ። ይህ አኃዝ ከአጠቃላይ የሀገሪቱ የሥራ አጥነት መጠን (8 በመቶ) ጋር ሲነጻጸር በሦስት እጥፍ ገደማ ብልጫ ያለው ሲሆን፣ ለሀገሪቱ የወደፊት የኢኮኖሚ ጉዞ ትልቅ ፈተና መሆኑ ተመልክቷል።
🔍 ለሥራ አጥነቱ መበራከት ዋነኛ መንስኤዎች
ባንኩ ለዚህ ከፍተኛ ቁጥር መመዝገብ በርካታ ምክንያቶችን ዘርዝሯል፦
* የክህሎትና የገበያ አለመጣጣም፦ ወጣቱ የሚቀስመው ትምህርትና ክህሎት የሥራ ገበያው ከሚፈልገው ፍላጎት ጋር አለመገናኘቱ።
* የመሠረተ ልማት ድክመት፦ የአካላዊና የዲጂታል መሠረተ ልማቶች አለመስፋፋት ለሥራ ዕድል ፈጠራ እንቅፋት መሆኑ።
* ተፈጥሯዊና ሰው ሠራሽ ችግሮች፦ በግጭት፣ በድርቅና በጎርፍ ምክንያት 8 ሚሊዮን ሕፃናትና ወጣቶች ከትምህርት ገበታቸው መራቃቸው ለወደፊቱ የሰው ኃይል ጥራት ሥጋት መፍጠሩ።
📈 የኢኮኖሚ ዕድገትና ክፍተቱ
ምንም እንኳ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በአማካይ 7.2 በመቶ ዕድገት እያሳየ ቢሆንም፣ ይህ ዕድገት ግን ለወጣቱ በቂ የሥራ ዕድል ወደ መፍጠር ሊተረጎም አልቻለም። በተለይም ሴቶችና ወጣቶች ያላቸው የሥራ አማራጭ በጣም የተገደበ መሆኑ በሪፖርቱ ተመላክቷል።
💡 የመፍትሔ አቅጣጫዎች
ባንኩ የ10 ዓመቱን የልማት ዕቅድ ለማሳካትና የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉን ለማነቃቃት የሚከተሉትን እርምጃዎች እንዲወሰዱ አሳስቧል፦
* የግል ባለሀብቱን ተሳትፎ ማጠናከር፦ የግሉ ዘርፍ ለሥራ ዕድል ፈጠራ እንዲነቃቃ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር።
* የክህሎት ማበልጸጊያ ላይ መሥራት፦ የወጣቱን አቅም ከዘመኑ የሥራ ገበያ ጋር ማጣጣም።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ኢትዮጵያ #ሥራ_አጥነት #የአፍሪካ_ልማት_ባንክ #ኢኮኖሚ #ወጣቶች #ethiopia #jobs #afdb
#ethiopia | የአፍሪካ ልማት ባንክ ባወጣው አዲስ የስትራቴጂ ግምገማ ሪፖርት፣ በኢትዮጵያ የወጣቶች ሥራ አጥነት መጠን 23.1 በመቶ መድረሱን ይፋ አደረገ። ይህ አኃዝ ከአጠቃላይ የሀገሪቱ የሥራ አጥነት መጠን (8 በመቶ) ጋር ሲነጻጸር በሦስት እጥፍ ገደማ ብልጫ ያለው ሲሆን፣ ለሀገሪቱ የወደፊት የኢኮኖሚ ጉዞ ትልቅ ፈተና መሆኑ ተመልክቷል።
🔍 ለሥራ አጥነቱ መበራከት ዋነኛ መንስኤዎች
ባንኩ ለዚህ ከፍተኛ ቁጥር መመዝገብ በርካታ ምክንያቶችን ዘርዝሯል፦
* የክህሎትና የገበያ አለመጣጣም፦ ወጣቱ የሚቀስመው ትምህርትና ክህሎት የሥራ ገበያው ከሚፈልገው ፍላጎት ጋር አለመገናኘቱ።
* የመሠረተ ልማት ድክመት፦ የአካላዊና የዲጂታል መሠረተ ልማቶች አለመስፋፋት ለሥራ ዕድል ፈጠራ እንቅፋት መሆኑ።
* ተፈጥሯዊና ሰው ሠራሽ ችግሮች፦ በግጭት፣ በድርቅና በጎርፍ ምክንያት 8 ሚሊዮን ሕፃናትና ወጣቶች ከትምህርት ገበታቸው መራቃቸው ለወደፊቱ የሰው ኃይል ጥራት ሥጋት መፍጠሩ።
📈 የኢኮኖሚ ዕድገትና ክፍተቱ
ምንም እንኳ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በአማካይ 7.2 በመቶ ዕድገት እያሳየ ቢሆንም፣ ይህ ዕድገት ግን ለወጣቱ በቂ የሥራ ዕድል ወደ መፍጠር ሊተረጎም አልቻለም። በተለይም ሴቶችና ወጣቶች ያላቸው የሥራ አማራጭ በጣም የተገደበ መሆኑ በሪፖርቱ ተመላክቷል።
💡 የመፍትሔ አቅጣጫዎች
ባንኩ የ10 ዓመቱን የልማት ዕቅድ ለማሳካትና የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉን ለማነቃቃት የሚከተሉትን እርምጃዎች እንዲወሰዱ አሳስቧል፦
* የግል ባለሀብቱን ተሳትፎ ማጠናከር፦ የግሉ ዘርፍ ለሥራ ዕድል ፈጠራ እንዲነቃቃ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር።
* የክህሎት ማበልጸጊያ ላይ መሥራት፦ የወጣቱን አቅም ከዘመኑ የሥራ ገበያ ጋር ማጣጣም።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ኢትዮጵያ #ሥራ_አጥነት #የአፍሪካ_ልማት_ባንክ #ኢኮኖሚ #ወጣቶች #ethiopia #jobs #afdb
7 months ago
የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ንድፍ ተጠናቀቀ፤ ግንባታው በጥር ወር ይጀመራል ተብሏል
💵 ለግንባታ ከሚያስፈልገው 10 ቢሊዮን ዶላር ውስጥ 20 በመቶውን አየር መንገዱ ሊሸፈን፤ ከ80 በመቶ ውስጥ የአፍሪካ ልማት ባንክ 500 ሚሊዮን ዶላሩን ፋይናንስ እንዲያደርግ እና ቀሪውን ከአበዳሪ ተቋማት ለማፈላለግ የሚያስችል ስምምነት በቅርቡ መፈረሙ ይታወሳል።
✈️ የመጀመሪያ ምዕራፍ የአውሮፕላን ማረፊያው ግንባታ ሲጠናቀቅ 60 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ይኖረዋል። የግንባታው ሁለተኛ ምዕራፍ ለአውሮፕላን ማረፊያው በዓመት 110 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ይፈጥራል።
👉 በ4 ዓመታት ውስጥ ይጠናቀቃል የተባለው የአውሮፕላን ማረፊያ፤ ሁለት ዘመናዊ ተርሚናሎች፣ ሁለት የአውሮፕላን መንደርደሪያዎች፣ የአውሮፕላን ጥገና ማዕከል፣ የካርጎ ማስተናገጃ ማዕከል፣ የበረራ መቆጣጠሪያ፣ የመንገደኞች ማስተናገጃዎች፣ ዘመናዊ ሆቴሎች እና መዝናኛዎች እንዲሁም የንግድ ማዕከላት ይኖሩታል።
Spitnik
seledadotio
seledadotio
💵 ለግንባታ ከሚያስፈልገው 10 ቢሊዮን ዶላር ውስጥ 20 በመቶውን አየር መንገዱ ሊሸፈን፤ ከ80 በመቶ ውስጥ የአፍሪካ ልማት ባንክ 500 ሚሊዮን ዶላሩን ፋይናንስ እንዲያደርግ እና ቀሪውን ከአበዳሪ ተቋማት ለማፈላለግ የሚያስችል ስምምነት በቅርቡ መፈረሙ ይታወሳል።
✈️ የመጀመሪያ ምዕራፍ የአውሮፕላን ማረፊያው ግንባታ ሲጠናቀቅ 60 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ይኖረዋል። የግንባታው ሁለተኛ ምዕራፍ ለአውሮፕላን ማረፊያው በዓመት 110 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ይፈጥራል።
👉 በ4 ዓመታት ውስጥ ይጠናቀቃል የተባለው የአውሮፕላን ማረፊያ፤ ሁለት ዘመናዊ ተርሚናሎች፣ ሁለት የአውሮፕላን መንደርደሪያዎች፣ የአውሮፕላን ጥገና ማዕከል፣ የካርጎ ማስተናገጃ ማዕከል፣ የበረራ መቆጣጠሪያ፣ የመንገደኞች ማስተናገጃዎች፣ ዘመናዊ ሆቴሎች እና መዝናኛዎች እንዲሁም የንግድ ማዕከላት ይኖሩታል።
Spitnik
seledadotio
seledadotio
7 months ago
የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ በጥር ወር ይጀምራል
***
በአፍሪካ ትልቁ የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ በጥር ወር እንደሚጀመር የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ አስታውቋል።
ከአዲስ አበባ በስተደቡብ 40 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ አቡሴራ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ በ10 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚገነባው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ 3 ሺህ 975 ሔክታር መሬት ላይ የሚያርፍ ነው።
የአውሮፕላን ማረፊያው ግንባታ በሁለት ምዕራፎች ተከፍሎ የሚካሄድ ሲሆን፤ የመጀመሪያው ምዕራፍ ሲጠናቀቅ 60 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ይኖረዋል።
ሁለተኛው ምዕራፍ ግንባታ ሲጠናቀቅ አውሮፕላን ማረፊያው በዓመት 110 ሚሊዮን መንገደኞችን ማስተናገድ ያስችላል።
የአውሮፕላን ማረፊያው ሁለት ዘመናዊ ተርሚናሎች፣ ሁለት የአውሮፕላን መንደርደሪያዎች፣ የአውሮፕላን ጥገና ማዕከል፣ የካርጎ ማስተናገጃ ማዕከል፣ የበረራ መቆጣጠሪያ፣ የመንገደኞች ማስተናገጃዎች፣ ዘመናዊ ሆቴሎች እና መዝናኛዎች እንዲሁም የንግድ ማዕከላት ይኖሩታል።
አውሮፕላን ማረፊያው ግንባታው ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ በዓለም ዙሪያ ካሉ ጥቂት እጅግ ዘመናዊ አውሮፕላን ማረፊያዎች አንዱ እንደሚሆን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ገልጿል።
ለአውሮፕላን ማረፊያው ግንባታ ከሚያስፈልገው 10 ቢሊዮን ዶላር ውስጥ 20 በመቶ የሚሆነው በአየር መንገዱ የሚሸፈን ሲሆን፤ 80 በመቶ የሚሆነው ደግሞ በአፍሪካ ልማት ባንክ እና በሌሎች ባንኮች ፋይናንስ የሚደረግ ነው።
የአፍሪካ ልማት ባንክ የ500 ሚሊዮን ዶላር ብድር ለመስጠት እና ቀሪውን ከአበዳሪ ተቋማት ለማፈላለግ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር ስምምነት መፈረሙ ይታወሳል።
በአፍሪካ ትልቁ የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በፈጣን ባቡር እና በመኪና መንገድ እንዲገናኝ ተደርጎ የሚሠራ ሲሆን፤ የመጀመሪያው ምዕራፍ ግንባታ በ4 ዓመታት ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።
አውሮፕላን ማረፊያው በኢትዮጵያ በኩል ለሚያልፉ ዓለም አቀፍ መንገደኞችም ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት መስጠት እንደሚያስችል ተገልጿል። በአፍሪካ ግዙፉን የአውሮፕላን ማረፊያ ለመገንባት የአውሮፕላን ማረፊያው ዲዛይን በመጠናቀቁ በጥር ወር መጀመሪያ ግንባታው በይፋ ይጀመራል ተብሏል።
አካባቢን የማይበክል ቴክኖሎጂ እና የፀሐይ ኃይል እንዲጠቀም፣ ዘላቂነት ያለው የቆሻሻ አወጋገድ እና የውኃ አጠቃቀም ሥርዓት እንዲኖረው ተደርጎ በዘመናዊ መልኩ የሚገነባው አውሮፕላን ማረፊያው በአካባቢ ላይ ምንም ዓይነት ጉዳት እንደማያስከትል ተነግሮለታል።
ከአውሮፕላን ማረፊያው ወደ ቦሌ የሚገነባው ፈጣን መንገድ እና ዘመናዊ የባቡር መስመር የከተማ እና የገጠር ትሥሥርን በማጠናከር የአካባቢው ማኅበረሰብ ከከተማ ጋር ያለውን ግንኙት ለማሳደግ እንደሚያግዝ ይጠበቃል።
አየር መንገዱ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያን ለመገንባት ከይዞታቸው ለሚነሱ አርሶ አደሮች 350 ሚሊዮን ዶላር ወጪ በማድረግ እጅግ ዘመናዊ ቪላ ቤቶች፣ ንግድን ጨምሮ የተለያዩ አገልግሎቶችን የሚሰጡ ሕንፃዎች፣ የአግሮ-ፕሮሰሲንግ እና የመስኖ ማዕከላትን ገንብቶ ለመስጠት እየሠራ እንደሚገኝም ተገልጿል።
በኢትዮጵያ ታሪክ በከፍተኛ ወጪ የሚገነባው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ የአፍሪካውያንን ትሥሥር በማጠናከር የአፍሪካ ኅብረት "የተዋሀደች እና የተሳሰረች አፍሪካን እውን ማድረግ" በሚል የያዘው ራዕይ እንዲሳካ ትልቅ አቅም ይሆናል።
EBC
***
በአፍሪካ ትልቁ የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ በጥር ወር እንደሚጀመር የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ አስታውቋል።
ከአዲስ አበባ በስተደቡብ 40 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ አቡሴራ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ በ10 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚገነባው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ 3 ሺህ 975 ሔክታር መሬት ላይ የሚያርፍ ነው።
የአውሮፕላን ማረፊያው ግንባታ በሁለት ምዕራፎች ተከፍሎ የሚካሄድ ሲሆን፤ የመጀመሪያው ምዕራፍ ሲጠናቀቅ 60 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ይኖረዋል።
ሁለተኛው ምዕራፍ ግንባታ ሲጠናቀቅ አውሮፕላን ማረፊያው በዓመት 110 ሚሊዮን መንገደኞችን ማስተናገድ ያስችላል።
የአውሮፕላን ማረፊያው ሁለት ዘመናዊ ተርሚናሎች፣ ሁለት የአውሮፕላን መንደርደሪያዎች፣ የአውሮፕላን ጥገና ማዕከል፣ የካርጎ ማስተናገጃ ማዕከል፣ የበረራ መቆጣጠሪያ፣ የመንገደኞች ማስተናገጃዎች፣ ዘመናዊ ሆቴሎች እና መዝናኛዎች እንዲሁም የንግድ ማዕከላት ይኖሩታል።
አውሮፕላን ማረፊያው ግንባታው ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ በዓለም ዙሪያ ካሉ ጥቂት እጅግ ዘመናዊ አውሮፕላን ማረፊያዎች አንዱ እንደሚሆን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ገልጿል።
ለአውሮፕላን ማረፊያው ግንባታ ከሚያስፈልገው 10 ቢሊዮን ዶላር ውስጥ 20 በመቶ የሚሆነው በአየር መንገዱ የሚሸፈን ሲሆን፤ 80 በመቶ የሚሆነው ደግሞ በአፍሪካ ልማት ባንክ እና በሌሎች ባንኮች ፋይናንስ የሚደረግ ነው።
የአፍሪካ ልማት ባንክ የ500 ሚሊዮን ዶላር ብድር ለመስጠት እና ቀሪውን ከአበዳሪ ተቋማት ለማፈላለግ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር ስምምነት መፈረሙ ይታወሳል።
በአፍሪካ ትልቁ የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ከቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በፈጣን ባቡር እና በመኪና መንገድ እንዲገናኝ ተደርጎ የሚሠራ ሲሆን፤ የመጀመሪያው ምዕራፍ ግንባታ በ4 ዓመታት ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።
አውሮፕላን ማረፊያው በኢትዮጵያ በኩል ለሚያልፉ ዓለም አቀፍ መንገደኞችም ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት መስጠት እንደሚያስችል ተገልጿል። በአፍሪካ ግዙፉን የአውሮፕላን ማረፊያ ለመገንባት የአውሮፕላን ማረፊያው ዲዛይን በመጠናቀቁ በጥር ወር መጀመሪያ ግንባታው በይፋ ይጀመራል ተብሏል።
አካባቢን የማይበክል ቴክኖሎጂ እና የፀሐይ ኃይል እንዲጠቀም፣ ዘላቂነት ያለው የቆሻሻ አወጋገድ እና የውኃ አጠቃቀም ሥርዓት እንዲኖረው ተደርጎ በዘመናዊ መልኩ የሚገነባው አውሮፕላን ማረፊያው በአካባቢ ላይ ምንም ዓይነት ጉዳት እንደማያስከትል ተነግሮለታል።
ከአውሮፕላን ማረፊያው ወደ ቦሌ የሚገነባው ፈጣን መንገድ እና ዘመናዊ የባቡር መስመር የከተማ እና የገጠር ትሥሥርን በማጠናከር የአካባቢው ማኅበረሰብ ከከተማ ጋር ያለውን ግንኙት ለማሳደግ እንደሚያግዝ ይጠበቃል።
አየር መንገዱ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያን ለመገንባት ከይዞታቸው ለሚነሱ አርሶ አደሮች 350 ሚሊዮን ዶላር ወጪ በማድረግ እጅግ ዘመናዊ ቪላ ቤቶች፣ ንግድን ጨምሮ የተለያዩ አገልግሎቶችን የሚሰጡ ሕንፃዎች፣ የአግሮ-ፕሮሰሲንግ እና የመስኖ ማዕከላትን ገንብቶ ለመስጠት እየሠራ እንደሚገኝም ተገልጿል።
በኢትዮጵያ ታሪክ በከፍተኛ ወጪ የሚገነባው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ የአፍሪካውያንን ትሥሥር በማጠናከር የአፍሪካ ኅብረት "የተዋሀደች እና የተሳሰረች አፍሪካን እውን ማድረግ" በሚል የያዘው ራዕይ እንዲሳካ ትልቅ አቅም ይሆናል።
EBC
8 months ago
ሁለተኛው ምዕራፍ የደቡብ ሱዳን -ኢትዮጵያ- ጂቡቲ የትራንስፖርት ኮሪደር
የአፍሪካ ልማት ባንክ ለሁለተኛው ምዕራፍ የደቡብ ሱዳን -ኢትዮጵያ- ጂቡቲ የትራንስፖርት ኮሪደር ግንባታ ማስጀመሪያ የ214 ነጥብ 47 ሚሊየን ዶላር የፋይናንስ ድጋፍ አፀደቀ።
ባንኩ ባወጣው መግለጫ 181 ነጥብ 5 ሚሊየን ዶላር በኢትዮጵያ በኩል ለሚካሄደው የፕሮጀክቱ አካል ድጋፍ ይውላል ብሏል።
ገንዘቡ ለ67 ኪሎ ሜትር የፍጥነት መንገድ ግንባታ እና የ50 ኪሎ ሜትር መጋቢ መንገዶች ማሻሻያ ይውላል።
የመንገድ ግንባታው የሀገራቱን ግንኙነት ለማጠናከር ብሎም ቀጠናዊ የንግድ ትስስር እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ እንደሚረዳ ባንኩ አስታውቋል።
seledadotio
seledadotio
የአፍሪካ ልማት ባንክ ለሁለተኛው ምዕራፍ የደቡብ ሱዳን -ኢትዮጵያ- ጂቡቲ የትራንስፖርት ኮሪደር ግንባታ ማስጀመሪያ የ214 ነጥብ 47 ሚሊየን ዶላር የፋይናንስ ድጋፍ አፀደቀ።
ባንኩ ባወጣው መግለጫ 181 ነጥብ 5 ሚሊየን ዶላር በኢትዮጵያ በኩል ለሚካሄደው የፕሮጀክቱ አካል ድጋፍ ይውላል ብሏል።
ገንዘቡ ለ67 ኪሎ ሜትር የፍጥነት መንገድ ግንባታ እና የ50 ኪሎ ሜትር መጋቢ መንገዶች ማሻሻያ ይውላል።
የመንገድ ግንባታው የሀገራቱን ግንኙነት ለማጠናከር ብሎም ቀጠናዊ የንግድ ትስስር እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ለማሳደግ እንደሚረዳ ባንኩ አስታውቋል።
seledadotio
seledadotio
10 months ago
የወጣቶች ኢንቨስትመንት ባንክ ሊቋቋም ነው
#ethiopia | የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከአፍሪካ ልማት ባንክ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ ማስፋፊያ ባገኘው ድጋፍ፣ የወጣት ሥራ ፈጣሪዎች ኢንቨስትመንት ባንክ (Youth Entrepreneurs Investment Bank ) ለማቋቋም የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ጋር መፈራረሙ ተገለጸ፡፡
ባንኩ ወጣቶች በሥራ ፈጠራ ስነ-ምህዳሩ ላይ የሚያጋጥሟቸውን የፋይናንስና የአቅም ክፍተት የሚሞላ ነው ያሉት የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል፤ ይህም መንግስት ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ የሰጠውን ልዩ ትኩረት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አክለውም፤ "የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ብሩክ ለወጣቶቻችን ተስፋ የሆነውን ፕሮጀክት እውን ለማድረግ ለሰጡት ጠንካራ አመራር እንዲሁም የአፍሪካ ልማት ባንክ ላደረገው ድጋፍ ከልብ የመነጨ ምስጋናዬን አቀርባለሁ" ብለዋል፡፡
#ethiopia | የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከአፍሪካ ልማት ባንክ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ ማስፋፊያ ባገኘው ድጋፍ፣ የወጣት ሥራ ፈጣሪዎች ኢንቨስትመንት ባንክ (Youth Entrepreneurs Investment Bank ) ለማቋቋም የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ጋር መፈራረሙ ተገለጸ፡፡
ባንኩ ወጣቶች በሥራ ፈጠራ ስነ-ምህዳሩ ላይ የሚያጋጥሟቸውን የፋይናንስና የአቅም ክፍተት የሚሞላ ነው ያሉት የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል፤ ይህም መንግስት ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ የሰጠውን ልዩ ትኩረት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
አክለውም፤ "የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ብሩክ ለወጣቶቻችን ተስፋ የሆነውን ፕሮጀክት እውን ለማድረግ ለሰጡት ጠንካራ አመራር እንዲሁም የአፍሪካ ልማት ባንክ ላደረገው ድጋፍ ከልብ የመነጨ ምስጋናዬን አቀርባለሁ" ብለዋል፡፡
Sponsored by
Surafel
11 months ago
"አፍሪካ በሙስና ምክንያት በየዓመቱ 580 ቢሊዮን ዶላር ታጣለች "የአፍሪካ ልማት ባንክ
የአፍሪካ ልማት ባንክ አፍሪካ በየዓመቱ ከ580 ቢሊዮን ዶላር በላይ በሙስና እና በህገወጥ የገንዘብ ዝውውር እንደምታጣ አስታውቋል።
የባንኩ ፕሬዝዳንት አኪንዉሚ አዴሲና (ዶ/ር) እንደገለፁት፣ ይህ ከፍተኛ የገንዘብ ብክነት የአህጉሪቱን የኢኮኖሚ ዕድገት እያሽቆለቆለ ከመሆኑም በላይ፣ ወደ 2 ትሪሊዮን ዶላር የሚጠጋውን የዕዳ ጫና ይበልጥ እያባባሰ ነው።
ፕሬዝዳንቱ ሁኔታውን "ውሃ የሚፈስበትን ባልዲ መሙላት" ሲሉ ገልጸውታል፤ ይህም የአፍሪካ ሃብት ማፍራት አለመቻሏን ያመለክታል።
በአፍሪካ ልማት ባንክ ግምት መሠረት፣ አፍሪካ በየቀኑ ከ1.6 ቢሊዮን ዶላር በላይ በህገወጥ የገንዘብ ፍሰት፣ በትልልቅ ኩባንያዎች የትርፍ መሸጋገሪያ እና በሙስና ምክንያት እንደምታጣ ተጠቁሟል።
Seledadotio
Seledadotio
የአፍሪካ ልማት ባንክ አፍሪካ በየዓመቱ ከ580 ቢሊዮን ዶላር በላይ በሙስና እና በህገወጥ የገንዘብ ዝውውር እንደምታጣ አስታውቋል።
የባንኩ ፕሬዝዳንት አኪንዉሚ አዴሲና (ዶ/ር) እንደገለፁት፣ ይህ ከፍተኛ የገንዘብ ብክነት የአህጉሪቱን የኢኮኖሚ ዕድገት እያሽቆለቆለ ከመሆኑም በላይ፣ ወደ 2 ትሪሊዮን ዶላር የሚጠጋውን የዕዳ ጫና ይበልጥ እያባባሰ ነው።
ፕሬዝዳንቱ ሁኔታውን "ውሃ የሚፈስበትን ባልዲ መሙላት" ሲሉ ገልጸውታል፤ ይህም የአፍሪካ ሃብት ማፍራት አለመቻሏን ያመለክታል።
በአፍሪካ ልማት ባንክ ግምት መሠረት፣ አፍሪካ በየቀኑ ከ1.6 ቢሊዮን ዶላር በላይ በህገወጥ የገንዘብ ፍሰት፣ በትልልቅ ኩባንያዎች የትርፍ መሸጋገሪያ እና በሙስና ምክንያት እንደምታጣ ተጠቁሟል።
Seledadotio
Seledadotio
12 months ago
አፍሪካ በሙስና ምክንያት በየዓመቱ 580 ቢሊዮን ዶላር ታጣለች - የአፍሪካ ልማት ባንክ
#ethiopia | የአፍሪካ ልማት ባንክ አፍሪካ በየዓመቱ ከ580 ቢሊዮን ዶላር በላይ በሙስና እና በህገወጥ የገንዘብ ዝውውር እንደምታጣ አስታውቋል።
የባንኩ ፕሬዝዳንት አኪንዉሚ አዴሲና (ዶ/ር) እንደገለፁት፣ ይህ ከፍተኛ የገንዘብ ብክነት የአህጉሪቱን የኢኮኖሚ ዕድገት እያሽቆለቆለ ከመሆኑም በላይ፣ ወደ 2 ትሪሊዮን ዶላር የሚጠጋውን የዕዳ ጫና ይበልጥ እያባባሰ ነው።
ፕሬዝዳንቱ ሁኔታውን "ውሃ የሚፈስበትን ባልዲ መሙላት" ሲሉ ገልጸውታል፤ ይህም የአፍሪካ ሃብት ማፍራት አለመቻሏን ያመለክታል።
በአፍሪካ ልማት ባንክ ግምት መሠረት፣ አፍሪካ በየቀኑ ከ1.6 ቢሊዮን ዶላር በላይ በህገወጥ የገንዘብ ፍሰት፣ በትልልቅ ኩባንያዎች የትርፍ መሸጋገሪያ እና በሙስና ምክንያት እንደምታጣ ተጠቁሟል ሲል ካፒታል በገጹ አስነብቧል ።
#ethiopia | የአፍሪካ ልማት ባንክ አፍሪካ በየዓመቱ ከ580 ቢሊዮን ዶላር በላይ በሙስና እና በህገወጥ የገንዘብ ዝውውር እንደምታጣ አስታውቋል።
የባንኩ ፕሬዝዳንት አኪንዉሚ አዴሲና (ዶ/ር) እንደገለፁት፣ ይህ ከፍተኛ የገንዘብ ብክነት የአህጉሪቱን የኢኮኖሚ ዕድገት እያሽቆለቆለ ከመሆኑም በላይ፣ ወደ 2 ትሪሊዮን ዶላር የሚጠጋውን የዕዳ ጫና ይበልጥ እያባባሰ ነው።
ፕሬዝዳንቱ ሁኔታውን "ውሃ የሚፈስበትን ባልዲ መሙላት" ሲሉ ገልጸውታል፤ ይህም የአፍሪካ ሃብት ማፍራት አለመቻሏን ያመለክታል።
በአፍሪካ ልማት ባንክ ግምት መሠረት፣ አፍሪካ በየቀኑ ከ1.6 ቢሊዮን ዶላር በላይ በህገወጥ የገንዘብ ፍሰት፣ በትልልቅ ኩባንያዎች የትርፍ መሸጋገሪያ እና በሙስና ምክንያት እንደምታጣ ተጠቁሟል ሲል ካፒታል በገጹ አስነብቧል ።
12 months ago
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለአዲሱ ኤርፖርት ግንባታ የ7.8 ቢሊዮን ዶላር ብድር አገኘ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቢሾፍቱ ለሚያስገነባው አዲስ አውሮፕላን ጣቢያ የ7.8 ቢሊዮን ዶላር ብድር ማግኘቱ ተገልጿል።
የአፍሪካ ልማት ባንክ ለኢትዮ ነጋሪ እንደገለጸው ለቦሾፍቱ ኤርፖርት ግንባታ 7.8 ቢሊዮን ዶላር ብድር ለመስጠት ተስማምቷል።
የብድር ስምምነቱ የፊታችን ሰኞ ነሀሴ 5 ቀን 2017 ዓ. ም በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል እንደሚፈረምም ተገልጿል።
በብድር ስምምነቱ ላይ ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት አደሲና፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከፍተኛ ሀላፊዎች እና ሌሎች እንግዶች በተገኙበት ይፈረማል ተብሏል።
ግንባታው በአምስት ዓመት ውስጥ ይጠናቀቃል የተባለው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ከ100 ሚሊዮን በላይ መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም እንዳለው ተገልጿል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ2017 ዓ.ም 7.6 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቱን አስታውቋል።
በሀገር ውስጥ በረራዎች ምክንያት ደግሞ የ28 ሚሊዮን ዶላር ኪሳራ እንደደረሰበት ከሰሞኑ መግለጹ ይታወሳል።
EthioNegari
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቢሾፍቱ ለሚያስገነባው አዲስ አውሮፕላን ጣቢያ የ7.8 ቢሊዮን ዶላር ብድር ማግኘቱ ተገልጿል።
የአፍሪካ ልማት ባንክ ለኢትዮ ነጋሪ እንደገለጸው ለቦሾፍቱ ኤርፖርት ግንባታ 7.8 ቢሊዮን ዶላር ብድር ለመስጠት ተስማምቷል።
የብድር ስምምነቱ የፊታችን ሰኞ ነሀሴ 5 ቀን 2017 ዓ. ም በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል እንደሚፈረምም ተገልጿል።
በብድር ስምምነቱ ላይ ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት አደሲና፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከፍተኛ ሀላፊዎች እና ሌሎች እንግዶች በተገኙበት ይፈረማል ተብሏል።
ግንባታው በአምስት ዓመት ውስጥ ይጠናቀቃል የተባለው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ከ100 ሚሊዮን በላይ መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም እንዳለው ተገልጿል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ2017 ዓ.ም 7.6 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቱን አስታውቋል።
በሀገር ውስጥ በረራዎች ምክንያት ደግሞ የ28 ሚሊዮን ዶላር ኪሳራ እንደደረሰበት ከሰሞኑ መግለጹ ይታወሳል።
EthioNegari
12 months ago
🇪🇹🛫የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቢሾፍቱ አቅራቢያ ለሚገነባው አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ 10 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ከውጭ ብድር ለማግኘት ማቀዱን አስታወቋል
የግንባታ ሥራው በመጪው መስከረም ወር እንደሚጀመር የተነገረ ሲሆን ለፕሮጀክቱ ከሚያስፈልገው ገንዘብ ውስጥ 80 በመቶ የሚሆነው ከውጭ የሚገኝ ብድር ሲሆን፣ የአፍሪካ ልማት ባንክ የብድር አሰባሳቢ አስተባባሪ ሆኖ ተሹሟል።
ቀሪው 20 በመቶ የሚሆነው ደግሞ ከአየር መንገዱ የውስጥ ሀብት የሚሸፈን ይሆናል ተብሏል።፡፡
የግንባታ ሥራው በመጪው መስከረም ወር እንደሚጀመር የተነገረ ሲሆን ለፕሮጀክቱ ከሚያስፈልገው ገንዘብ ውስጥ 80 በመቶ የሚሆነው ከውጭ የሚገኝ ብድር ሲሆን፣ የአፍሪካ ልማት ባንክ የብድር አሰባሳቢ አስተባባሪ ሆኖ ተሹሟል።
ቀሪው 20 በመቶ የሚሆነው ደግሞ ከአየር መንገዱ የውስጥ ሀብት የሚሸፈን ይሆናል ተብሏል።፡፡
Sponsored by
Surafel
Comments