Logo
Getu Temesgen
የወጣቶች ኢንቨስትመንት ባንክ ሊቋቋም ነው
#ethiopia | የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከአፍሪካ ልማት ባንክ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ ማስፋፊያ ባገኘው ድጋፍ፣ የወጣት ሥራ ፈጣሪዎች ኢንቨስትመንት ባንክ (Youth Entrepreneurs Investment Bank ) ለማቋቋም የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ጋር መፈራረሙ ተገለጸ፡፡

ባንኩ ወጣቶች በሥራ ፈጠራ ስነ-ምህዳሩ ላይ የሚያጋጥሟቸውን የፋይናንስና የአቅም ክፍተት የሚሞላ ነው ያሉት የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል፤ ይህም መንግስት ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ የሰጠውን ልዩ ትኩረት የሚያሳይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

አክለውም፤ "የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ብሩክ ለወጣቶቻችን ተስፋ የሆነውን ፕሮጀክት እውን ለማድረግ ለሰጡት ጠንካራ አመራር እንዲሁም የአፍሪካ ልማት ባንክ ላደረገው ድጋፍ ከልብ የመነጨ ምስጋናዬን አቀርባለሁ" ብለዋል፡፡

10 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.