14 hours ago
ማዕድን - የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ዕድገት አንዱ ምሰሶ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የለውጡ መንግሥት ትኩረት ሰጥቶ ከሰራባቸው አምስቱ የኢኮኖሚ ምሰሶዎች ውስጥ ማዕድንን በማካተቱ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ለውጥ ተመዝግቦበታል፡፡
በወርቅ፣ በወሳኝ ማዕድናት፣ በነዳጅ እና በማዳበሪያ ምርት ላይ እየተስፋፋ በመጣው የኢንቨስትመንት ለውጦች፣ ኢትዮጵያ ያላትን የተፈጥሮ ሀብት አቅም ወደ ተጨባጭ ብሔራዊ ዕድገት እየቀየረችው ትገኛለች፡፡
ለዘርፉ ከፍተኛ ትኩረት በመሰጠቱ በወርቅ፣ በድንጋይ ከሰል፣ በፖታሽ፣ ብረት እና ሴራሚክስ በመሳሰሉት ማዕድናት ረገድ ከፍተኛ ውጤት ለማስመዝገብ ተችሏል፡፡
በያዝነው ሳምንት የሲኤንኤን ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩቢዳሪ በኢትዮጵያ ላይ በሚያተኩረው ዘገባዋ በሀገሪቱ ያለውን ወርቅ ጨምሮ ከፍተኛ የብረት ማዕድናት አምራች ለመሆን እያደረገች ያለውን ጥረት አንስታለች፡፡
ኢትዮጵያ ለታላላቅ ኢንዱስትሪዎቿ ግብዓት የሚሆን የከሰል ድንጋይ ሙሉ ለሙሉ ከውጭ ስታስገባ ቆይታለች፡፡
ሆኖም ከለውጡ ወዲህ በተሰሩ አፋጣኝ ስራዎች እንደ አርጆ፣ ዮ ሆልዲንግ የመሳሰሉ የድንጋይ ከሰል ማምረቻዎችን በመገንባት ለድንጋይ ከሰል ግዢ በየዓመቱ የምታወጣውን ከ300 ሚሊየን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ማስቀረት ተችሏል፡፡
በዚህም የግብዓትና ምርት ስርጭት ፍጥነትን፣ ቅልጥፍናን እና ገቢን ለማሳደግ አስችሏል፡፡
የድንጋይ ከሰል ማምረቻዎቹ በመከፈታቸው የኢንዱስትሪዎችን ፍላጎት በሀገር ውስጥ በመተካት ከውጭ የሚገባ ምርትን ከማስቀረት ባለፈ ለአካባቢው ነዋሪዎችም የሥራ ዕድል ፈጥሯል።
በምስራቅ አፍሪካ ግዙፍ የተባለውና በደብረ ብርሃን አካባቢ የተገነባው ግራንዲውር እንዲሁም የባጀአ የሴራሚክ ማምረች ፋብሪካዎች በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ወደ ሀገር ውስጥ የምታስገባውን የግንባታ ግብዓት በሀገር ውስጥ ለመተካት አስችሏል፡፡
በኢትዮጵያ ግዙፉ የለሚ ሲሚንቶ ፋብሪካ ተጠናቅቆ አገልግሎት መጀመሩ ሌላው በዘርፉ የተመዘገበ ባለ ብዙ ፋይዳ ስኬት ነው፡፡ ፋብሪካው የሀገር ውስጥ የግንባታ ግብዓት እጥረትን ከመቅረፉ ባሻገር የገበያ ዋጋን በማረጋጋት ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ነው፡፡
የማዕድን ዘርፍ ለብቻው የሚቆም ሳይሆን ከሌሎች ዘርፎች ጋር የሚተሳሰር እና ተመጋጋቢነትን የሚፈጥር ነው፡፡
ዘርፉ ከነበረበት ደካማ አፈጻጸም ተነስቶ በአሁኑ ወቅት የሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት ስትራቴጂካዊ ምሰሶዎች አንዱ መሆን የቻለበትን የትራንስፎርሜሽን ጉዞ ላይ ይገኛል፡፡
በቁርጠኛ ማሻሻያዎች፣ በገበያ መልሶ ማዋቀር እና እሴትን መጨመር በሚያስችሉ ኢንቨስትመንቶች በመታገዝ ዘርፉ ከፍተኛ የወጪ ንግድ ገቢን እያስገኘ፣ የገቢ ምርቶችን ጥገኝነት እየቀነሰ እና ለኢንዱስትሪ ልማት አዳዲስ ዕድሎችን እየፈጠረ ይገኛል፡፡
በአጠቃላይ የማዕድን ዘርፍ የውጭ ኢንቨስትመንት ለመሳብ፣ ለተኪ ምርት ዕድገት፣ ለስራ ዕድል ፈጠራ፣ ለወጪ ንግድና ለዘርፎች የጎንዮሽ ትስስር ማደግ ግዙፍ አቅም መፍጠር ችሏል፡፡
በቴዎድሮስ ሳህለ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የለውጡ መንግሥት ትኩረት ሰጥቶ ከሰራባቸው አምስቱ የኢኮኖሚ ምሰሶዎች ውስጥ ማዕድንን በማካተቱ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ለውጥ ተመዝግቦበታል፡፡
በወርቅ፣ በወሳኝ ማዕድናት፣ በነዳጅ እና በማዳበሪያ ምርት ላይ እየተስፋፋ በመጣው የኢንቨስትመንት ለውጦች፣ ኢትዮጵያ ያላትን የተፈጥሮ ሀብት አቅም ወደ ተጨባጭ ብሔራዊ ዕድገት እየቀየረችው ትገኛለች፡፡
ለዘርፉ ከፍተኛ ትኩረት በመሰጠቱ በወርቅ፣ በድንጋይ ከሰል፣ በፖታሽ፣ ብረት እና ሴራሚክስ በመሳሰሉት ማዕድናት ረገድ ከፍተኛ ውጤት ለማስመዝገብ ተችሏል፡፡
በያዝነው ሳምንት የሲኤንኤን ጋዜጠኛ ቪክቶሪያ ሩቢዳሪ በኢትዮጵያ ላይ በሚያተኩረው ዘገባዋ በሀገሪቱ ያለውን ወርቅ ጨምሮ ከፍተኛ የብረት ማዕድናት አምራች ለመሆን እያደረገች ያለውን ጥረት አንስታለች፡፡
ኢትዮጵያ ለታላላቅ ኢንዱስትሪዎቿ ግብዓት የሚሆን የከሰል ድንጋይ ሙሉ ለሙሉ ከውጭ ስታስገባ ቆይታለች፡፡
ሆኖም ከለውጡ ወዲህ በተሰሩ አፋጣኝ ስራዎች እንደ አርጆ፣ ዮ ሆልዲንግ የመሳሰሉ የድንጋይ ከሰል ማምረቻዎችን በመገንባት ለድንጋይ ከሰል ግዢ በየዓመቱ የምታወጣውን ከ300 ሚሊየን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ማስቀረት ተችሏል፡፡
በዚህም የግብዓትና ምርት ስርጭት ፍጥነትን፣ ቅልጥፍናን እና ገቢን ለማሳደግ አስችሏል፡፡
የድንጋይ ከሰል ማምረቻዎቹ በመከፈታቸው የኢንዱስትሪዎችን ፍላጎት በሀገር ውስጥ በመተካት ከውጭ የሚገባ ምርትን ከማስቀረት ባለፈ ለአካባቢው ነዋሪዎችም የሥራ ዕድል ፈጥሯል።
በምስራቅ አፍሪካ ግዙፍ የተባለውና በደብረ ብርሃን አካባቢ የተገነባው ግራንዲውር እንዲሁም የባጀአ የሴራሚክ ማምረች ፋብሪካዎች በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ወደ ሀገር ውስጥ የምታስገባውን የግንባታ ግብዓት በሀገር ውስጥ ለመተካት አስችሏል፡፡
በኢትዮጵያ ግዙፉ የለሚ ሲሚንቶ ፋብሪካ ተጠናቅቆ አገልግሎት መጀመሩ ሌላው በዘርፉ የተመዘገበ ባለ ብዙ ፋይዳ ስኬት ነው፡፡ ፋብሪካው የሀገር ውስጥ የግንባታ ግብዓት እጥረትን ከመቅረፉ ባሻገር የገበያ ዋጋን በማረጋጋት ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ነው፡፡
የማዕድን ዘርፍ ለብቻው የሚቆም ሳይሆን ከሌሎች ዘርፎች ጋር የሚተሳሰር እና ተመጋጋቢነትን የሚፈጥር ነው፡፡
ዘርፉ ከነበረበት ደካማ አፈጻጸም ተነስቶ በአሁኑ ወቅት የሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት ስትራቴጂካዊ ምሰሶዎች አንዱ መሆን የቻለበትን የትራንስፎርሜሽን ጉዞ ላይ ይገኛል፡፡
በቁርጠኛ ማሻሻያዎች፣ በገበያ መልሶ ማዋቀር እና እሴትን መጨመር በሚያስችሉ ኢንቨስትመንቶች በመታገዝ ዘርፉ ከፍተኛ የወጪ ንግድ ገቢን እያስገኘ፣ የገቢ ምርቶችን ጥገኝነት እየቀነሰ እና ለኢንዱስትሪ ልማት አዳዲስ ዕድሎችን እየፈጠረ ይገኛል፡፡
በአጠቃላይ የማዕድን ዘርፍ የውጭ ኢንቨስትመንት ለመሳብ፣ ለተኪ ምርት ዕድገት፣ ለስራ ዕድል ፈጠራ፣ ለወጪ ንግድና ለዘርፎች የጎንዮሽ ትስስር ማደግ ግዙፍ አቅም መፍጠር ችሏል፡፡
በቴዎድሮስ ሳህለ
22 hours ago
የኤቦላ ቫይረስ በአሳሳቢ ሁኔታ እየተሰራጨ ነው ሲል ድንበር የለሽ የሐኪሞች ቡድን አሳወቀ
የዛሬ ሁለት ወራት ተኩል ገደማ በኮንጎ የተከሰተው የኤቦላ ቫይረስ ወረርሽኝ በአሳሳቢና ባልተጠበቀ ሁኔታ በሀገሪቱ እየተሰራጨ ነው ሲል ድንበር የለሽ የሐኪሞች ቡድን በምህፃሩ MSF አስታወቀ።
ድርጅቱ እንደሚለው በሽታውን ለመከላከል የህክምና ባለሞያዎች ያላሰለሰ ጥረት እያደረጉ ቢሆንም፤ ወረርሽኙ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በአሳሳቢ ሁኔታ እየተሰራጨ ይገኛል።
እስካሁን ከ3 ሺህ 600 በላይ ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው በላቦራቶሪ ተረጋገጧል፤ ቁጥራቸው 1 ሺህ 500 የሚጠጋ ሰዎችም ሞተዋል።
በአሁኑ ጊዜ ዋናው ተግዳሮት ባለሥልጣናት በበሽታው ከተያዙ ሰዎች ጋር ግንኙነት ያላቸውን ሰዎች መለየት እንደተሳናቸው መሆኑ ነው።
ቡንያ በተባለው አካባቢ የሚገኝ የህክምና ማዕከል ውስጥ ከሚገኙት በሽተኞች ውስጥ 90 በመቶው ከዚህ ቀደም በኤቦላ ቫይረስ ከተያዙ ሰዎች ጋር ንክኪ እንዳላቸው የሚታወቅ ነገር የለም።
የዓለም የጤና ድርጅት ዋና ኃላፊ ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም ከመንግሥት ኃላፊዎችና ከሰብአዊ ድርጅቶች ጋር ለመነጋገር ዛሬ ወደ ኮንጎ ኪንሻሳ ሄደዋል።
ዶክተር ቴዎድሮስ የኤቦላ ወረርሽኝ ከተሰከሰተ ወዲህ ወደ ኮንጎ ሲጓዙ የዛሬው ለሁለተኛ ጊዜ ነው።
Seledadotio
Seledadotio
የዛሬ ሁለት ወራት ተኩል ገደማ በኮንጎ የተከሰተው የኤቦላ ቫይረስ ወረርሽኝ በአሳሳቢና ባልተጠበቀ ሁኔታ በሀገሪቱ እየተሰራጨ ነው ሲል ድንበር የለሽ የሐኪሞች ቡድን በምህፃሩ MSF አስታወቀ።
ድርጅቱ እንደሚለው በሽታውን ለመከላከል የህክምና ባለሞያዎች ያላሰለሰ ጥረት እያደረጉ ቢሆንም፤ ወረርሽኙ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በአሳሳቢ ሁኔታ እየተሰራጨ ይገኛል።
እስካሁን ከ3 ሺህ 600 በላይ ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው በላቦራቶሪ ተረጋገጧል፤ ቁጥራቸው 1 ሺህ 500 የሚጠጋ ሰዎችም ሞተዋል።
በአሁኑ ጊዜ ዋናው ተግዳሮት ባለሥልጣናት በበሽታው ከተያዙ ሰዎች ጋር ግንኙነት ያላቸውን ሰዎች መለየት እንደተሳናቸው መሆኑ ነው።
ቡንያ በተባለው አካባቢ የሚገኝ የህክምና ማዕከል ውስጥ ከሚገኙት በሽተኞች ውስጥ 90 በመቶው ከዚህ ቀደም በኤቦላ ቫይረስ ከተያዙ ሰዎች ጋር ንክኪ እንዳላቸው የሚታወቅ ነገር የለም።
የዓለም የጤና ድርጅት ዋና ኃላፊ ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም ከመንግሥት ኃላፊዎችና ከሰብአዊ ድርጅቶች ጋር ለመነጋገር ዛሬ ወደ ኮንጎ ኪንሻሳ ሄደዋል።
ዶክተር ቴዎድሮስ የኤቦላ ወረርሽኝ ከተሰከሰተ ወዲህ ወደ ኮንጎ ሲጓዙ የዛሬው ለሁለተኛ ጊዜ ነው።
Seledadotio
Seledadotio
3 days ago
“ታሪክ በትዝታ ላይ የተጫነ ሸክም አይደለም-የነፍስ መገለጥ እንጂ”
ጋዜጠኛ ዮናስ አየለ እንደጻፈው
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ከአሚኮ ጋር ያደረጉትን ቃለምልልስ አዳምጬ እንደጨረስኩ በቃለ ምልልሱ በርዕሰ ጉዳይ ደረጃ ጎልተው ከወጡ ዋና ዋና ጭብጦች መካከል አንዱ ነገረ ታሪክ እንደሆነ ተሰምቶኛል፡፡ ታሪክ-የሀገር ውስጥና የውጭ፤ የሩቅና የቅርብ ዘመን! ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያንጸባረቁትን ሚዛናዊና አምክኖአዊ የታሪክ እይታና ድምዳሜያቸውን አለማድነቅ ንፉግነት ነው፡፡ የአሥራ ዘጠነኛው ክፍለ ዘመን እንግሊዛዊ የታሪክ ጸሐፊና ፖለቲከኛ ሎርድ አክተን “History is not a burden on the memory but an illumination of the soul” ብሎ ሲጽፍ “ታሪክ የነፍስ መገለጥ እንጂ በትዝታ ላይ የተጫነ ሸክም አይደለም” ማለቱ ነበር፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያነሷቸው የታሪክ አንኳር ጉዳዮች እስከዛሬ ድረስ በሀገራችን የታሪክ አጻጻፍ(Historiography) እና በሕዝባዊ ትርክቶቻችን(በሚዲያዎችን ጭምር) በሚገባቸው ልክ ያልተወሱ፤ ቢወሱም ፈራ ተባ እየተባሉ የሚጠቀሱ፤ አለፍሲልም ባልተገባ የፖለቲካ እይታ ደንቃራ ተደርገው የተወሰዱ የታሪክ ግርዶሽ(eclipse of the history) ሆነው የኖሩ ስብራቶቻችን ነበሩ፡፡ ከነዚህ ቁልፍ ጉዳዮች መካከል ዋነኛዎቹ አንዱ የሕዝቦች ትስስር እና መስተጋብር ታሪክ ሲሆን ሌላኛው በአገረ መንግስት ምሥረታ ውስጥ የሸዋ ጂኦ-ስትራቴጂካዊ ሚናን የተመለከቱት ናቸው፡፡
በመጀመሪያ የአማራና የኦሮሞ ሕዝቦች በኩታ ገጠም ቀዬዎቻቸው እና የታሪክ እድል በፈጠረላቸው የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የባህል አጋጣሚዎች እንደሌሎች ማህበረሰቦች ሁሉ መጋባት መዋለዳቸው፤መተሳሰር መዋሀዳቸው ሀቅ የመሆኑን ያህል የታሪክ ጥናት እና የትርክቶቻችን ማጠንጠኛ አለመሆናቸው ይታወቃል፡፡ ከዚህ በባሰ ሁኔታ ደግሞ በነገሥታቱ መካከል የነበረው የፖለቲካ ጋብቻና የመሪዎቻችን ማህበራዊ መሠረት ጉዳይ ነውር እስኪመስል በእውነታው ልክ ሳይጠናና፣ሳይነገርለት ዘመናት አልፈዋል ፡፡ በሌላ በኩል በሸዋና አካባቢው ለረዥም ዘመን የኖሩ ሕዝቦች በአገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት የተጫወቱት ሚናና የሚጋሩት ቀደምት የሥልጣኔ ባለቤትነት (ታሪክ ሰሪነት-Agency) ግጥምጥሞሽ በሀገር መሪ ደረጃ መወሳታቸው እጅግ ጉልህ ፋይዳ ያለው ጉዳይ ነው ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያነሷቸው የታሪክ እውነታዎች ያለጥርጥር ታሪካችንንና የታሪክ ምልከታችንን ደጋግመን መመርምር እንዳለብን የሚያስገነዝቡና የወገንተኝነት ጥያቄ በሚነሳባቸው ሃይማኖታዊ የታሪክ ምንጮች እንኳን የተቀመጡ ገሃድ እውነታዎች ናቸው፡፡ መመርመር ለሚፈልግ አጥኚ እነዚህ የታሪክ እውነታዎች በየነገሥታቱ ዜና መዋዕሎች (የዐጼ አምደ ጽዮን፣ ዐጼ ሱስንዮስ፣የዐጼ ገላውዲዮስ፣ የዐጼ ሠርጸ ድንግል ወዘተ)፤ የሃይማኖት ሰነዶች፣ የታሪከ ነገሥት ቅጂዎች፣ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩ አውሮፓውያን ተጓዦችና ጸሐፊያን (ፍራንስስኮ አልቫሬዝ፣ ፔድሮ ፔዝ፣ ማኑኤል አልሜዳ፣ ጄሮኒሞ ሎቦ፣ ጀምስ ብሩስ፣ ኮንቲ ሮሲኒ ወዘተ ) መዝግበው በተውልን ሰነዶች ሰፍረው የምናገኛቸው፤ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፉ የኖሩ ቱባ መረጃዎች ናቸው፡፡
ፍራንሲስኮ አልቫሬዝ የተወልን የጽሑፍ ሰነድና ሌሎች ሀገርኛ የቃል መረጃ ምንጮች ዐፄ ልብነድንግል(1498-1532 ዓ.ም.) እንደ መሪ የአማራና የኦሮሞ ብቻ ሳይሆን ምናልባትም የሌሎች ሕዝቦችም ማህበራዊ ዳራ የነበራቸው ንጉሠ ነገሥት እንደሆኑ የሚያስረዱ ሲሆን አልቫሬዝ የንጉሱ የእናት ወንድም የነበሩት አጎታቸው ዶሪ ባህረ ነጋሽ ኦሮሞ እንደነበሩና ባህረ ነጋሽ ዶሪ ሲሞቱ ሥልጣኑ በቀጥታ ወደልጃቸው ቡሎ መሸጋገሩን ጭምር በአይኑ ያየውን ጽፏል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በትኩረት መታየት የሚገባው ጉዳይ ስለዐጼ ልብነ ድንግል የጦር አዛዦች የተነገሩ የቃል መረጃዎች ናቸወ፡፡ ከእነዚህ መካከል የንጉሠ ነገሥቱ ሠራዊት የቦረንትቻ ባሕል ያውቅ እንደነበር በተክለጻዲቅ መኩሪያ መጻፉና ከዐጼ ልብነድንግል የጦር አዛዦች አንዱ የነበረው ቱሉ ደገልሀን በመራው ከኢማም አሕመድ ጋር የተካሄደ ጦርነት የዐጼው ጦር ሲያፈገፍግ ንጉሠ ነገሥቱ “ሁሉም ቢፈራ ቱሉ እንዴት ፈራ? ” ማለታቸው ስለሠራዊታቸው ሥብጥር የሚነግረን ነገር አለ፡፡
ኦቶማን ቱርኮችን እና የዘመኑ ተላላኪዎቻቸውን ለመዋጋት የንጉሠ ነገሥቱ ሠራዊት አንድ አካል ሆነው እስከ ኤርትራ ድረስ ዘምተው ስለነበሩ የኦሮሞ ተዋጊዎች ተጋድሎ የዐጼ ሠርጸድንግል(1542-1590 ዓ.ም.) ዜና መዋእል በግልጽ አስፍሯል፡፡ እነዚህ የኦሮሞና የሌሎች ሕዝቦች ተወላጅ ወታደሮች ትግራይ እንጢጮ አካባቢ ያካሄዱትን አውደ ውጊያ ዜና መዋዕሉ ይተርካል፡፡ ለመንግሥታቸውና ለሀገራቸው እስከባሕር ጠረፍ ድረስ ዘምተው ዋጋ መክፈላቸውም ተመዝግቧል፡፡ የዐጼ ሱስንዮስ(1607-1632 ዓ.ም.) ዜና መዋእል እና በዘመኑ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩ የአውሮፓ(የፖርቱጋል) ተጓዦች የጻፏቸው የመረጃ ምንጮች ንጉሠ ነገሥቱ ግንደበረት፣ሐምቦና አካባቢው ቤታቸው እንደነበር፤ አጎታቸው ለማሞ እንደሚባል፣ ወላጅ እናታቸው(ሐመልማል ወርቅ) የአዛዥ ኩሎ ልጅ የነበረች፤ የዚሁ የሐመልማል ወርቅ ጎሳ ተወላጅ የሆነ ቡኮ የተባለ ኦሮሞና ሠራዊቱ ለአባይ ቅርብ የሆነች ምዕራብ ሸዋ ላይ ዐጼ ሱስንዮስ ሲያገኙት የነበረውን ደስታና የፍቅሩን ጽናት ዜና መዋዕሉ ሳይሰስት ጽፎታል፡፡ ዐጼ ፋሲል(ከ1632 እስከ 1667 ዓ.ም.) አባቱ ሱስንዮስ እናቱ የወሎ ቃሉ ሰው(እቴጌ ሥልጣን ሞገሳ የሚል ስም የተሰጣት) እንደሆነች የታሪክ ምንጮች ያስረዱናል፡፡ በ1620ዎቹ ዓመታት ጀምሮ በኢትዮጵያ ይኖር የነበረው ፖርቱጋላዊ ቄስ ጄሮኒሞ ሎቦ ስለዐጼ ፋሲል እናትና ኦሮሞ ዘመዶቻቸው በአይን ምስክርነት የሚያውቀውን ጽፏል፡፡ የእቴጌ ሥልጣን ሞገሳ አያት ስለብዝሀ ሃይማኖት አስፈላጊነት የነበራቸውን ግልጽ ፖሊሲ ጭምር ሎቦ ዘግቦታል፡፡ የዐጼ በካፋ(1721-1730 ዓ.ም.) እና የዐጼ ኢዮአስ(1747-1761 ዓ.ም.) ጎንደር መቼም ለሕዝቦች ውህደትና ትስስር ጥሩ ማሳያ ነበረች፡፡ የየጁ ኦሮሞ ገዢ የነበረው የአሚቶ ሴት ልጅ ዝነኛዋ ውቢት ልጇ ዐጼ አዮአስ ነበር፡፡ ኢዮአስ ከኦሮሞ አጎቱ ከደጃች ሉቦ ጋር ሥልጣኑን በጎንደር እንዴት እንዳጸና፤ የቤተ መንግሥቱም የሥራ ቋንቋ አፋን ኦሮሞ እንደነበረ የንጉሠ ነገሥቱ ዜና መዋዕልና በጀምስ ብሩስ ቅጽ ሁለት መጽሀፍ የተመዘገቡ የታሪክ መረጃዎች ያስረዱናል፡፡
መነሻውን ወሎ በማድረግ ጎንደር ጸንቶ የኖረው የየጁ ሥርወ መንግሥት(ወረ ሼኮች) መሥራቾች የመርሳው አባ ጌትዬ፣ የልጃቸው ጓንጉል አባ ሴሩ እንዲሁም የልጅ ልጃቸው የራስ አሊ ጓንጉል(አሊ ትልቁ) ታሪክ በኢዮአስ ዜና መዋዕል፣ በጀምስ ብሩስ መጽሐፍና በሌሎች በርካታ ሰነዶች ታሪካቸው ተዘግቧል፡፡ በኋላ ላይ በሽፈራው በቀለ(ፕሮፌሰር) እና ሞላ ትኩዬ የቀረቡ ጥልቅ ጥናቶች ይህን እውነት በዝርዝር ያስረዱናል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው እንደጠቀሱት የእነዚህ መሪዎች የፖለቲካ ጋብቻ ታሪክ የሚያሳየን በሄዱበት አገር ሁሉ የሕዝቦች ትሥሥር እና የፖለቲካ ጋብቻ የኖረ ታሪካችን እና የጉልበታችን ምንጭ እንደነበረ ነው፡፡ በዳግማዊ ዐጼ ቴዎድሮስ ዘመን የተጻፉ የታሪክ ሰነዶች የወሎዋ ገዢ ወርቂቱ ወዳጆ(የማመዶች ሥርወ መንግሥት መሪ የኢማም አሊ አባ ቡላ ባለቤት) ንጉሥ ምኒልክ ከመቅደላ እስር ቤት እንዲያመልጡ ያደረጉ፤ አጃቢ ሠራዊት አሰማርተው ምኒልክን እስከሸዋ የሸኙ እንደነበሩ በዋናነት ከጸሓፌ ትእዛዝ ገብረ ሥላሴ ታሪከ ዘመን ዘ ዳግማዊ ምኒልክ ዜና መዋዕል እና በመቅደላ አምባ እስር ላይ የነበሩ አውሮፓውያን ከጻፏቸው መረጃዎች እንረዳለን፡፡
ሥልጣኔዎቻችን ሁሉ ተደምረን ያሳካናቸው እንደሆነ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው አንስተዋል፡፡ የዐድዋ ዘመቻና ድሉ ለዚህ አንዱ ማሳያ እንደሆነ ተጨባጭ የታሪክ ምንጮች ያስረዱናል፡፡ በ1888 ዓ.ም. ለዓድዋ ዘመቻ ከመላው ኢትዮጵያ የተመመው ሠረዊት ወፍላ ላይ የነበረው ሠልፍ የንጉሠ ነገሥቱ ዜና መዋዕል እንኳን እንዲህ ይገልጸዋል፡፡ “የመኳንንቱ የጦር መሣሪያ፣ወርቁ፣ ጣፋ፣ ብሩ፣ ሙጣው፣ ጫሜው፣ ሎሚታውና ኩፊታው፣ ከሌቻው፣ ወርቅ ለምዱ እንደጸሐይ ሲያበራ ዋለ፡፡” እንደጸሐይ የበራውን ሕብረ ባሕልና ሕብረ ማንነት ትርክቶቻችን በልኩ አጉልተው ያውቃሉ?
ሸዋና አካባቢው(ወሎን ጨምሮ) እንደ አንድ ጂዞ ስትራቴጂ ሥፍራ የሕዝቦች ውህደትና ትስስር መሠረት ሆኖት የመልክዓ ምድር መገኛው ለግብርና እና ለውጭ ንግድ የተመቸ በመሆኑ በኢትዮጵያ አገረ መንግሥት ግንባታ ታሪክ ውስጥ ቁልፍ ቦታ ይዞ መኖሩን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው መግቢያ አስታውሰውናል፡፡ ሸዋና አካባቢው ከመንግሥታት ምስረታ ጋር በተገናኘ ከዘጠነኛው አንስቶ እስካሁን ያለው ረዥም የታሪክ ጉዞ በርግጥም ሊነገር፣ ሊተነተን የአደባባይ ትርክት አካል ሊደረግ የሚገባው እውነት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሸዋ ሡልጣኔት ምስረታ( እ.አ..አ.896 ዓ.ም.) እስከ ዓድዋ ድል(1888 ዓ.ም.) ሥላወሷቸው የአርጎባ(የወላስማ/ወሊ አስማ ሥርወ መንግሥት)፣ የአማራ(ሰለሞናዊ ሥርወ መንግሥት)፣ ኦሮሞ(ቱለማው በተለይ)፣ወርጂ፣ ጉራጌ፣ ጋፋት፣ ወዘተ ሕዝቦች ትስስርም ይሁን የፖለቲካ ጋብቻ የተመለከተ ታሪክ ከበቂ በላይ የታሪክ ማስረጃ ምንጮች ቢኖሩንም በታሪክ ግርዶሹ ምክንያት የወል ትርክት አካል መሆን አልቻለም፡፡
ኤንሪኮ ቼሩሊ ከሐረር አግኝቶ ያሳተመው በአረብኛ የተጻፈው የሸዋ ሡልጣኔት ዜና መዋዕል እንደሚያመለክተው ሡልጣኔቱን እ.አ.አ. በ896/7 የመሰረቱት የማህዙሚ ጎሳ አባላት ናቸው፡፡ መንግሥታቸውም ከ9ኛው እስከ 13ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ በተከታታይ በገዙ አሥራ አራት ሱልጣኖች እንደጸና የታሪክ መረጃ ምንጮች ያመለክታሉ፡፡ የሸዋ ሙስሊም ሡልጣኔቱ መቀመጫ ከተማ ከአዲስ አበባ በስተሰሜን ምሥራቅ 70 ኪሎ ሜትር ላይ የምትገኝ ወለላ የተባለች ሥፍራ እንደነበረች የጆርጅ ደብሊው ቢ ሀንቲንግፎርድ(1989) ጥናት ያመለክታል፡፡ የማህዙሚ ሥርወ መንግሥት ከመጨረሻዎቹ መሪዎች አንዱ የነበረው ሡልጣን ድልመራህ ወርጂዎች የይኖሩበት በነበረው አካባቢ በ1270ዎቹ በነበረ የርስ በርስ ጦርነት ድል ሳይቀናው ሲቀር ሕይወቱን ለማትረፍ ዐጼ(የአማራ ገዥ?) እንደሄደ ይህው የአረብኛ ዜና መዋእል ያስረዳል፡፡ የማህዙሚዎች የሸዋ ሡልጣኔት የተተካው በዋናነት የአርጎባዎች አገር በሆነው ይፋት(ዊፋት) ላይ በወላስማዎች ነበር፡፡ ወላስማዎች ከአጎራባቾቻው ጋር እየተጋቡ፣ እየተስማሙም እየተጋጩም የይፋት ሡልጣኔትን ከ13ኛው እስከ 15ኛው ክፍለ ዘመን ከሸዋ እስከ ምሥራቃዊ የኢትዮጵያ ጠረፍ እንዳስተዳደሩ ስፍር ቁጥር የሌለው የሰነድ( የኢብን ካልዱን ተማሪ የነበረው አል ማቅሪዚ ጽሑፍ- ኪታብ አል ኢልማም)፣ የአርኪዮሎጂና የቃል መረጃ ምንጮች አሉ፡፡
መነሻውን ሰሜን ሸዋ እና ደቡብ ወሎ ያደረገው የክርስቲያኑ ሰሎሞናዊ ሥርወ መንግሥት በአካባቢው ያሉ ሕዝቦች ተዋህደው ከ13ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በጋራ የመሠረቱት እንደሆነ አያጠያይቅም፡፡ አማራዎች፤ አርጎባዎች፣ ወርጂዎች፣ ጋፋቶች፣ ጉራጌዎች እና ኦሮሞዎች፣ አፋሮች፣ ሐረሪዎች ወዘተ በዚህ የሸዋ መንግሥታት የተጽዕኖ ምህዳር(Orbit) ውስጥ እንደሚገኙ ዜና መዋእሎች፣ የሃይማኖት ሰነዶች፣ የአርኪዮሎጂ ማስረጃዎች ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፉ የኖሩ የቃል መረጃ ምንጮች ያመለክታሉ፡፡ ለምሳሌ ታደሠ ታምራት(ፕሮፌሠር) ከ13ኛው እስከ 16ኛው ክፍለ ዘመን የቤተ ክርስቲያንና መንግሥትን ግንኙነት ታሪክ ባጠኑበት መጽሐፋቸው የገላንና ያያ ሰዎች ሸዋ ውስጥ በ13ኛው ክፍለ ዘመን በኦዳ ዛፍ (ኮቢል የሚባል ዋርካ) ሥር ሃይማኖታዊ ሥርዓት ይፈጽሙ እንደነበር ገድለ አቡነ ቀውስጦስን ጠቅሰው ጽፈዋል(ገጽ 184)፡፡ ሸዋ የባለ ብዙ ማንነት ሕዝቦች ሀገር ከመሆኗ ባሻገር በ16ኛው ክፍለ ዘመን የተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች ላይ መረጃ የተወልን መነኩሴው አባ ባህሪይ እንደገለጸው “ሸዋ የመንግሥት ሀገር ነች” (ገጽ 130)፡፡ በየዘመናቱ ከሸዋ የተነሱ የፖለቲካ ኃይሎች፣ ፈረሰኛ ሠራዊታቸውን ይዘው በሰሜን እስከ ኤርትራ(በዐጼ ሠርጸ ድንግል ዘመን- የኤርትራዋ ባሬንቱ የዚህ የታሪክ ሂደት ውርስ አይደለችም ማለት አይቻልም፡፡) በምሥራቅ እስከ ዘይላ(ከዐጼ አምደጽዮን እስከ ገላውዲዮስ ዘመን)፣ በምዕራብ እስከ ሱዳን ፋዞግሊ(ዐጼ ሱስንዮስ ዘመን) በደቡብ እስከ ሞያሌ ተንቀሳቅሰው በአገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት ውስጥ ቁልፍ ሚና ተጫተዋል፡፡
እነዚህ የሸዋ እና አካባቢው ሕዝቦችና ገዢዎች ትልቁን ንቅናቄያቸውን ያደረጉት ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ዐጼ ምኒልክና ራስ ጎበና ዳጬ የቱለማ ኦሮሞ፤ የሸዋ አማራ እና የሌሎችም ውህድ የሆነ ጦራቸውን አዝምተው ወሎ ወግተው ወረኢሉን የመንሥታቸው መቀመጫ ያደረጉት አርሲ፣ወለጋ፣ከሐረር ከመዝመታቸው በፊት ነበር፡፡ የመጫ ኦሮሞ ተወላጁን የጎጃሙን ንጉስ ተክለሃይማኖት(አዳል ተሰማ) በቱለማው መሪ ራስ ጎበና ዳጪ እምባቦ ላይ ያስገበሩት የጂኦ ፖለቲካዊ እና የሕዝቦች ትስስር እድሎች ጉልበት ፈጥሮላቸው፤ ኃይል አጎናጽፏቸው እንጂ በአጋጣሚ አይደለም፡፡ በርግጥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የፖለቲካችን ደንቃራነት የፈጠረውን የታሪክ ግርዶሽ ያሸነፉ ፋና ወጊ ጥናቾች መውጣት ጀምረዋል፡፡ አንዱ “Invisible Actors: The Oromo and the Creation of Modern Ethiopia(1855-1913)” በሚል ርዕስ በብሪያን ጀምስ ዬትስ(2002) በኤሊኖይስ ዩኒቨርሲቲ ከተጠናው እጅግ ጠቃሚ የዶክትሬት ዲግሪ ማሟያ ጥናት ሲሆን ሌላው የደቻሳ አበበ(ዶ/ር) ጎበና ወታደራዊና ፖለቲካዊ ሕይወት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው የዘመናዊት ኢትዮጵያን እውን መሆን ያለ ምኒልክና ያለ ጎበና እንደማይታሰብ ሲጠቅሱ ይህንን እውነታ ማጉላታቸው ይመስለኛል፡፡
የሕዝቦች ትስስርና የፖለቲካ ጋብቻ በአማራና በኦሮሞ ሕዝብ መስተጋብር ብቻ የታጠረ አልነበረም-ሊሆንም አይችልም፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ባህልና ሥልጣኔ መጋመዱ ረቂቅ ነው፡፡ ከጥንታዊ አክሱም ዘመን ጀምሮ በዝነኞቹ የአክሱም መቃብር ሀውልቶች እና በላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ላይ ከምናገኛቸው የኪነ ሕንጻ ትእምርቶች(Symbols) መካከል የውሸት በሮች (False Doors) እና የውሸት መስኮቶች(False windows) የሙታን መንፈስ(ኤከራ) መመላለሻ እንደሆኑ በጥናት የተረጋገጠ ነው (ቢትራይስ ፕሌይን Annales d'Éthiopie 1965) ፡፡ ይህ የኤከራዎች መመላለስና የመነጋገር ባህል እና እምነት ከደቡባዊ ግብጽ አንስቶ እስከ ሰሜን ኬንያ ድረስ በሚኖሩ የኩሽ ሕዝቦች በሰፊው የሚታወቅ ረዥም ዘመን ያስቆጠረ ልምምድ ነው፡፡
ሌላው በልኩ ያልተጠና እና በትርክቶቻችን ውስጥ ትኩረት ያልተሰጠው በሕዝቦች መካከል ያለ ሥልጣኔ ትስስር ታሪክ የእያንዳዱን የዛግዌ ነገሥታት የሥልጣን ዘመናትን የተመለከተ ነው፡፡ ከታሪክ ነገሥት፣ ከልዩ ልዩ ዜና መዋዕሎች፣ ከፖርቱጋል ተጓዦች(ፓኤዝና አልሜዳ) ከብሪቲሽ ሙዝየም እንዲሁም ከኮንቲ ሮሲኒ የተገኙት ምንጮች የሚረጋግጡት የሁሉም የዛግዌ ዐጼዎች( ከአንድ ሁለቱ በስተቀር) የሥልጣን ዘመን 40፤40 ዓመታት ነበር፡፡ ይህ ጉዳይ በኦሮሞ የገዳ ሥርዓት የአንድ ትውልድ የሥልጣን ዑደት ጋር አንድ አይነት የሆነው በአጋጣሚ ነው ወይስ ዛግዌዎች እና ኦሮሞዎች የኩሽ ሕዝቦች በመሆናቸው ቀዳሚ ከሆነው የጋራ ሥልጣኔያቸው የሚቀዳ የአስተዳደር ሥርዓት ነው? እነዚህስ ሀቆች የወል ትርክቶቻችን መመሆን አለመቻላቸው በፖለቲካ ደንቃራነት የተፈጠረ የታሪክ ግርዶሽ(eclipse of history) እንጂ ሌላ ምን ሊባል ይችላል? በላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትና እና በሸዋ በሚገኘው የአዳዲ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ኪነሕንጻ መካከል ያለው ፍጹም ተመሳሳይነት ምንጩ ምንድነው? ሊጠና፣ ሊነገር ልንማርበት ይገባል፡፡
በርግጥም ታሪካችን ትዝታችን ላይ የተጫነ ሸክም ሳይሆን የነፍስ መገለጥ ነው የሚያሰኘው የሕዝቦች ትሥሥር፣ ውህደት የሥልጣኔ መጋራትና መወራረስ ታሪክ መታወቁ መንፈስን ሃርነት ማውጣቱ ይመስለኛል፡፡
ጋዜጠኛ ዮናስ አየለ እንደጻፈው
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ከአሚኮ ጋር ያደረጉትን ቃለምልልስ አዳምጬ እንደጨረስኩ በቃለ ምልልሱ በርዕሰ ጉዳይ ደረጃ ጎልተው ከወጡ ዋና ዋና ጭብጦች መካከል አንዱ ነገረ ታሪክ እንደሆነ ተሰምቶኛል፡፡ ታሪክ-የሀገር ውስጥና የውጭ፤ የሩቅና የቅርብ ዘመን! ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያንጸባረቁትን ሚዛናዊና አምክኖአዊ የታሪክ እይታና ድምዳሜያቸውን አለማድነቅ ንፉግነት ነው፡፡ የአሥራ ዘጠነኛው ክፍለ ዘመን እንግሊዛዊ የታሪክ ጸሐፊና ፖለቲከኛ ሎርድ አክተን “History is not a burden on the memory but an illumination of the soul” ብሎ ሲጽፍ “ታሪክ የነፍስ መገለጥ እንጂ በትዝታ ላይ የተጫነ ሸክም አይደለም” ማለቱ ነበር፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያነሷቸው የታሪክ አንኳር ጉዳዮች እስከዛሬ ድረስ በሀገራችን የታሪክ አጻጻፍ(Historiography) እና በሕዝባዊ ትርክቶቻችን(በሚዲያዎችን ጭምር) በሚገባቸው ልክ ያልተወሱ፤ ቢወሱም ፈራ ተባ እየተባሉ የሚጠቀሱ፤ አለፍሲልም ባልተገባ የፖለቲካ እይታ ደንቃራ ተደርገው የተወሰዱ የታሪክ ግርዶሽ(eclipse of the history) ሆነው የኖሩ ስብራቶቻችን ነበሩ፡፡ ከነዚህ ቁልፍ ጉዳዮች መካከል ዋነኛዎቹ አንዱ የሕዝቦች ትስስር እና መስተጋብር ታሪክ ሲሆን ሌላኛው በአገረ መንግስት ምሥረታ ውስጥ የሸዋ ጂኦ-ስትራቴጂካዊ ሚናን የተመለከቱት ናቸው፡፡
በመጀመሪያ የአማራና የኦሮሞ ሕዝቦች በኩታ ገጠም ቀዬዎቻቸው እና የታሪክ እድል በፈጠረላቸው የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የባህል አጋጣሚዎች እንደሌሎች ማህበረሰቦች ሁሉ መጋባት መዋለዳቸው፤መተሳሰር መዋሀዳቸው ሀቅ የመሆኑን ያህል የታሪክ ጥናት እና የትርክቶቻችን ማጠንጠኛ አለመሆናቸው ይታወቃል፡፡ ከዚህ በባሰ ሁኔታ ደግሞ በነገሥታቱ መካከል የነበረው የፖለቲካ ጋብቻና የመሪዎቻችን ማህበራዊ መሠረት ጉዳይ ነውር እስኪመስል በእውነታው ልክ ሳይጠናና፣ሳይነገርለት ዘመናት አልፈዋል ፡፡ በሌላ በኩል በሸዋና አካባቢው ለረዥም ዘመን የኖሩ ሕዝቦች በአገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት የተጫወቱት ሚናና የሚጋሩት ቀደምት የሥልጣኔ ባለቤትነት (ታሪክ ሰሪነት-Agency) ግጥምጥሞሽ በሀገር መሪ ደረጃ መወሳታቸው እጅግ ጉልህ ፋይዳ ያለው ጉዳይ ነው ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያነሷቸው የታሪክ እውነታዎች ያለጥርጥር ታሪካችንንና የታሪክ ምልከታችንን ደጋግመን መመርምር እንዳለብን የሚያስገነዝቡና የወገንተኝነት ጥያቄ በሚነሳባቸው ሃይማኖታዊ የታሪክ ምንጮች እንኳን የተቀመጡ ገሃድ እውነታዎች ናቸው፡፡ መመርመር ለሚፈልግ አጥኚ እነዚህ የታሪክ እውነታዎች በየነገሥታቱ ዜና መዋዕሎች (የዐጼ አምደ ጽዮን፣ ዐጼ ሱስንዮስ፣የዐጼ ገላውዲዮስ፣ የዐጼ ሠርጸ ድንግል ወዘተ)፤ የሃይማኖት ሰነዶች፣ የታሪከ ነገሥት ቅጂዎች፣ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩ አውሮፓውያን ተጓዦችና ጸሐፊያን (ፍራንስስኮ አልቫሬዝ፣ ፔድሮ ፔዝ፣ ማኑኤል አልሜዳ፣ ጄሮኒሞ ሎቦ፣ ጀምስ ብሩስ፣ ኮንቲ ሮሲኒ ወዘተ ) መዝግበው በተውልን ሰነዶች ሰፍረው የምናገኛቸው፤ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፉ የኖሩ ቱባ መረጃዎች ናቸው፡፡
ፍራንሲስኮ አልቫሬዝ የተወልን የጽሑፍ ሰነድና ሌሎች ሀገርኛ የቃል መረጃ ምንጮች ዐፄ ልብነድንግል(1498-1532 ዓ.ም.) እንደ መሪ የአማራና የኦሮሞ ብቻ ሳይሆን ምናልባትም የሌሎች ሕዝቦችም ማህበራዊ ዳራ የነበራቸው ንጉሠ ነገሥት እንደሆኑ የሚያስረዱ ሲሆን አልቫሬዝ የንጉሱ የእናት ወንድም የነበሩት አጎታቸው ዶሪ ባህረ ነጋሽ ኦሮሞ እንደነበሩና ባህረ ነጋሽ ዶሪ ሲሞቱ ሥልጣኑ በቀጥታ ወደልጃቸው ቡሎ መሸጋገሩን ጭምር በአይኑ ያየውን ጽፏል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በትኩረት መታየት የሚገባው ጉዳይ ስለዐጼ ልብነ ድንግል የጦር አዛዦች የተነገሩ የቃል መረጃዎች ናቸወ፡፡ ከእነዚህ መካከል የንጉሠ ነገሥቱ ሠራዊት የቦረንትቻ ባሕል ያውቅ እንደነበር በተክለጻዲቅ መኩሪያ መጻፉና ከዐጼ ልብነድንግል የጦር አዛዦች አንዱ የነበረው ቱሉ ደገልሀን በመራው ከኢማም አሕመድ ጋር የተካሄደ ጦርነት የዐጼው ጦር ሲያፈገፍግ ንጉሠ ነገሥቱ “ሁሉም ቢፈራ ቱሉ እንዴት ፈራ? ” ማለታቸው ስለሠራዊታቸው ሥብጥር የሚነግረን ነገር አለ፡፡
ኦቶማን ቱርኮችን እና የዘመኑ ተላላኪዎቻቸውን ለመዋጋት የንጉሠ ነገሥቱ ሠራዊት አንድ አካል ሆነው እስከ ኤርትራ ድረስ ዘምተው ስለነበሩ የኦሮሞ ተዋጊዎች ተጋድሎ የዐጼ ሠርጸድንግል(1542-1590 ዓ.ም.) ዜና መዋእል በግልጽ አስፍሯል፡፡ እነዚህ የኦሮሞና የሌሎች ሕዝቦች ተወላጅ ወታደሮች ትግራይ እንጢጮ አካባቢ ያካሄዱትን አውደ ውጊያ ዜና መዋዕሉ ይተርካል፡፡ ለመንግሥታቸውና ለሀገራቸው እስከባሕር ጠረፍ ድረስ ዘምተው ዋጋ መክፈላቸውም ተመዝግቧል፡፡ የዐጼ ሱስንዮስ(1607-1632 ዓ.ም.) ዜና መዋእል እና በዘመኑ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩ የአውሮፓ(የፖርቱጋል) ተጓዦች የጻፏቸው የመረጃ ምንጮች ንጉሠ ነገሥቱ ግንደበረት፣ሐምቦና አካባቢው ቤታቸው እንደነበር፤ አጎታቸው ለማሞ እንደሚባል፣ ወላጅ እናታቸው(ሐመልማል ወርቅ) የአዛዥ ኩሎ ልጅ የነበረች፤ የዚሁ የሐመልማል ወርቅ ጎሳ ተወላጅ የሆነ ቡኮ የተባለ ኦሮሞና ሠራዊቱ ለአባይ ቅርብ የሆነች ምዕራብ ሸዋ ላይ ዐጼ ሱስንዮስ ሲያገኙት የነበረውን ደስታና የፍቅሩን ጽናት ዜና መዋዕሉ ሳይሰስት ጽፎታል፡፡ ዐጼ ፋሲል(ከ1632 እስከ 1667 ዓ.ም.) አባቱ ሱስንዮስ እናቱ የወሎ ቃሉ ሰው(እቴጌ ሥልጣን ሞገሳ የሚል ስም የተሰጣት) እንደሆነች የታሪክ ምንጮች ያስረዱናል፡፡ በ1620ዎቹ ዓመታት ጀምሮ በኢትዮጵያ ይኖር የነበረው ፖርቱጋላዊ ቄስ ጄሮኒሞ ሎቦ ስለዐጼ ፋሲል እናትና ኦሮሞ ዘመዶቻቸው በአይን ምስክርነት የሚያውቀውን ጽፏል፡፡ የእቴጌ ሥልጣን ሞገሳ አያት ስለብዝሀ ሃይማኖት አስፈላጊነት የነበራቸውን ግልጽ ፖሊሲ ጭምር ሎቦ ዘግቦታል፡፡ የዐጼ በካፋ(1721-1730 ዓ.ም.) እና የዐጼ ኢዮአስ(1747-1761 ዓ.ም.) ጎንደር መቼም ለሕዝቦች ውህደትና ትስስር ጥሩ ማሳያ ነበረች፡፡ የየጁ ኦሮሞ ገዢ የነበረው የአሚቶ ሴት ልጅ ዝነኛዋ ውቢት ልጇ ዐጼ አዮአስ ነበር፡፡ ኢዮአስ ከኦሮሞ አጎቱ ከደጃች ሉቦ ጋር ሥልጣኑን በጎንደር እንዴት እንዳጸና፤ የቤተ መንግሥቱም የሥራ ቋንቋ አፋን ኦሮሞ እንደነበረ የንጉሠ ነገሥቱ ዜና መዋዕልና በጀምስ ብሩስ ቅጽ ሁለት መጽሀፍ የተመዘገቡ የታሪክ መረጃዎች ያስረዱናል፡፡
መነሻውን ወሎ በማድረግ ጎንደር ጸንቶ የኖረው የየጁ ሥርወ መንግሥት(ወረ ሼኮች) መሥራቾች የመርሳው አባ ጌትዬ፣ የልጃቸው ጓንጉል አባ ሴሩ እንዲሁም የልጅ ልጃቸው የራስ አሊ ጓንጉል(አሊ ትልቁ) ታሪክ በኢዮአስ ዜና መዋዕል፣ በጀምስ ብሩስ መጽሐፍና በሌሎች በርካታ ሰነዶች ታሪካቸው ተዘግቧል፡፡ በኋላ ላይ በሽፈራው በቀለ(ፕሮፌሰር) እና ሞላ ትኩዬ የቀረቡ ጥልቅ ጥናቶች ይህን እውነት በዝርዝር ያስረዱናል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው እንደጠቀሱት የእነዚህ መሪዎች የፖለቲካ ጋብቻ ታሪክ የሚያሳየን በሄዱበት አገር ሁሉ የሕዝቦች ትሥሥር እና የፖለቲካ ጋብቻ የኖረ ታሪካችን እና የጉልበታችን ምንጭ እንደነበረ ነው፡፡ በዳግማዊ ዐጼ ቴዎድሮስ ዘመን የተጻፉ የታሪክ ሰነዶች የወሎዋ ገዢ ወርቂቱ ወዳጆ(የማመዶች ሥርወ መንግሥት መሪ የኢማም አሊ አባ ቡላ ባለቤት) ንጉሥ ምኒልክ ከመቅደላ እስር ቤት እንዲያመልጡ ያደረጉ፤ አጃቢ ሠራዊት አሰማርተው ምኒልክን እስከሸዋ የሸኙ እንደነበሩ በዋናነት ከጸሓፌ ትእዛዝ ገብረ ሥላሴ ታሪከ ዘመን ዘ ዳግማዊ ምኒልክ ዜና መዋዕል እና በመቅደላ አምባ እስር ላይ የነበሩ አውሮፓውያን ከጻፏቸው መረጃዎች እንረዳለን፡፡
ሥልጣኔዎቻችን ሁሉ ተደምረን ያሳካናቸው እንደሆነ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው አንስተዋል፡፡ የዐድዋ ዘመቻና ድሉ ለዚህ አንዱ ማሳያ እንደሆነ ተጨባጭ የታሪክ ምንጮች ያስረዱናል፡፡ በ1888 ዓ.ም. ለዓድዋ ዘመቻ ከመላው ኢትዮጵያ የተመመው ሠረዊት ወፍላ ላይ የነበረው ሠልፍ የንጉሠ ነገሥቱ ዜና መዋዕል እንኳን እንዲህ ይገልጸዋል፡፡ “የመኳንንቱ የጦር መሣሪያ፣ወርቁ፣ ጣፋ፣ ብሩ፣ ሙጣው፣ ጫሜው፣ ሎሚታውና ኩፊታው፣ ከሌቻው፣ ወርቅ ለምዱ እንደጸሐይ ሲያበራ ዋለ፡፡” እንደጸሐይ የበራውን ሕብረ ባሕልና ሕብረ ማንነት ትርክቶቻችን በልኩ አጉልተው ያውቃሉ?
ሸዋና አካባቢው(ወሎን ጨምሮ) እንደ አንድ ጂዞ ስትራቴጂ ሥፍራ የሕዝቦች ውህደትና ትስስር መሠረት ሆኖት የመልክዓ ምድር መገኛው ለግብርና እና ለውጭ ንግድ የተመቸ በመሆኑ በኢትዮጵያ አገረ መንግሥት ግንባታ ታሪክ ውስጥ ቁልፍ ቦታ ይዞ መኖሩን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው መግቢያ አስታውሰውናል፡፡ ሸዋና አካባቢው ከመንግሥታት ምስረታ ጋር በተገናኘ ከዘጠነኛው አንስቶ እስካሁን ያለው ረዥም የታሪክ ጉዞ በርግጥም ሊነገር፣ ሊተነተን የአደባባይ ትርክት አካል ሊደረግ የሚገባው እውነት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሸዋ ሡልጣኔት ምስረታ( እ.አ..አ.896 ዓ.ም.) እስከ ዓድዋ ድል(1888 ዓ.ም.) ሥላወሷቸው የአርጎባ(የወላስማ/ወሊ አስማ ሥርወ መንግሥት)፣ የአማራ(ሰለሞናዊ ሥርወ መንግሥት)፣ ኦሮሞ(ቱለማው በተለይ)፣ወርጂ፣ ጉራጌ፣ ጋፋት፣ ወዘተ ሕዝቦች ትስስርም ይሁን የፖለቲካ ጋብቻ የተመለከተ ታሪክ ከበቂ በላይ የታሪክ ማስረጃ ምንጮች ቢኖሩንም በታሪክ ግርዶሹ ምክንያት የወል ትርክት አካል መሆን አልቻለም፡፡
ኤንሪኮ ቼሩሊ ከሐረር አግኝቶ ያሳተመው በአረብኛ የተጻፈው የሸዋ ሡልጣኔት ዜና መዋዕል እንደሚያመለክተው ሡልጣኔቱን እ.አ.አ. በ896/7 የመሰረቱት የማህዙሚ ጎሳ አባላት ናቸው፡፡ መንግሥታቸውም ከ9ኛው እስከ 13ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ በተከታታይ በገዙ አሥራ አራት ሱልጣኖች እንደጸና የታሪክ መረጃ ምንጮች ያመለክታሉ፡፡ የሸዋ ሙስሊም ሡልጣኔቱ መቀመጫ ከተማ ከአዲስ አበባ በስተሰሜን ምሥራቅ 70 ኪሎ ሜትር ላይ የምትገኝ ወለላ የተባለች ሥፍራ እንደነበረች የጆርጅ ደብሊው ቢ ሀንቲንግፎርድ(1989) ጥናት ያመለክታል፡፡ የማህዙሚ ሥርወ መንግሥት ከመጨረሻዎቹ መሪዎች አንዱ የነበረው ሡልጣን ድልመራህ ወርጂዎች የይኖሩበት በነበረው አካባቢ በ1270ዎቹ በነበረ የርስ በርስ ጦርነት ድል ሳይቀናው ሲቀር ሕይወቱን ለማትረፍ ዐጼ(የአማራ ገዥ?) እንደሄደ ይህው የአረብኛ ዜና መዋእል ያስረዳል፡፡ የማህዙሚዎች የሸዋ ሡልጣኔት የተተካው በዋናነት የአርጎባዎች አገር በሆነው ይፋት(ዊፋት) ላይ በወላስማዎች ነበር፡፡ ወላስማዎች ከአጎራባቾቻው ጋር እየተጋቡ፣ እየተስማሙም እየተጋጩም የይፋት ሡልጣኔትን ከ13ኛው እስከ 15ኛው ክፍለ ዘመን ከሸዋ እስከ ምሥራቃዊ የኢትዮጵያ ጠረፍ እንዳስተዳደሩ ስፍር ቁጥር የሌለው የሰነድ( የኢብን ካልዱን ተማሪ የነበረው አል ማቅሪዚ ጽሑፍ- ኪታብ አል ኢልማም)፣ የአርኪዮሎጂና የቃል መረጃ ምንጮች አሉ፡፡
መነሻውን ሰሜን ሸዋ እና ደቡብ ወሎ ያደረገው የክርስቲያኑ ሰሎሞናዊ ሥርወ መንግሥት በአካባቢው ያሉ ሕዝቦች ተዋህደው ከ13ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በጋራ የመሠረቱት እንደሆነ አያጠያይቅም፡፡ አማራዎች፤ አርጎባዎች፣ ወርጂዎች፣ ጋፋቶች፣ ጉራጌዎች እና ኦሮሞዎች፣ አፋሮች፣ ሐረሪዎች ወዘተ በዚህ የሸዋ መንግሥታት የተጽዕኖ ምህዳር(Orbit) ውስጥ እንደሚገኙ ዜና መዋእሎች፣ የሃይማኖት ሰነዶች፣ የአርኪዮሎጂ ማስረጃዎች ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፉ የኖሩ የቃል መረጃ ምንጮች ያመለክታሉ፡፡ ለምሳሌ ታደሠ ታምራት(ፕሮፌሠር) ከ13ኛው እስከ 16ኛው ክፍለ ዘመን የቤተ ክርስቲያንና መንግሥትን ግንኙነት ታሪክ ባጠኑበት መጽሐፋቸው የገላንና ያያ ሰዎች ሸዋ ውስጥ በ13ኛው ክፍለ ዘመን በኦዳ ዛፍ (ኮቢል የሚባል ዋርካ) ሥር ሃይማኖታዊ ሥርዓት ይፈጽሙ እንደነበር ገድለ አቡነ ቀውስጦስን ጠቅሰው ጽፈዋል(ገጽ 184)፡፡ ሸዋ የባለ ብዙ ማንነት ሕዝቦች ሀገር ከመሆኗ ባሻገር በ16ኛው ክፍለ ዘመን የተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች ላይ መረጃ የተወልን መነኩሴው አባ ባህሪይ እንደገለጸው “ሸዋ የመንግሥት ሀገር ነች” (ገጽ 130)፡፡ በየዘመናቱ ከሸዋ የተነሱ የፖለቲካ ኃይሎች፣ ፈረሰኛ ሠራዊታቸውን ይዘው በሰሜን እስከ ኤርትራ(በዐጼ ሠርጸ ድንግል ዘመን- የኤርትራዋ ባሬንቱ የዚህ የታሪክ ሂደት ውርስ አይደለችም ማለት አይቻልም፡፡) በምሥራቅ እስከ ዘይላ(ከዐጼ አምደጽዮን እስከ ገላውዲዮስ ዘመን)፣ በምዕራብ እስከ ሱዳን ፋዞግሊ(ዐጼ ሱስንዮስ ዘመን) በደቡብ እስከ ሞያሌ ተንቀሳቅሰው በአገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት ውስጥ ቁልፍ ሚና ተጫተዋል፡፡
እነዚህ የሸዋ እና አካባቢው ሕዝቦችና ገዢዎች ትልቁን ንቅናቄያቸውን ያደረጉት ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ዐጼ ምኒልክና ራስ ጎበና ዳጬ የቱለማ ኦሮሞ፤ የሸዋ አማራ እና የሌሎችም ውህድ የሆነ ጦራቸውን አዝምተው ወሎ ወግተው ወረኢሉን የመንሥታቸው መቀመጫ ያደረጉት አርሲ፣ወለጋ፣ከሐረር ከመዝመታቸው በፊት ነበር፡፡ የመጫ ኦሮሞ ተወላጁን የጎጃሙን ንጉስ ተክለሃይማኖት(አዳል ተሰማ) በቱለማው መሪ ራስ ጎበና ዳጪ እምባቦ ላይ ያስገበሩት የጂኦ ፖለቲካዊ እና የሕዝቦች ትስስር እድሎች ጉልበት ፈጥሮላቸው፤ ኃይል አጎናጽፏቸው እንጂ በአጋጣሚ አይደለም፡፡ በርግጥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የፖለቲካችን ደንቃራነት የፈጠረውን የታሪክ ግርዶሽ ያሸነፉ ፋና ወጊ ጥናቾች መውጣት ጀምረዋል፡፡ አንዱ “Invisible Actors: The Oromo and the Creation of Modern Ethiopia(1855-1913)” በሚል ርዕስ በብሪያን ጀምስ ዬትስ(2002) በኤሊኖይስ ዩኒቨርሲቲ ከተጠናው እጅግ ጠቃሚ የዶክትሬት ዲግሪ ማሟያ ጥናት ሲሆን ሌላው የደቻሳ አበበ(ዶ/ር) ጎበና ወታደራዊና ፖለቲካዊ ሕይወት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው የዘመናዊት ኢትዮጵያን እውን መሆን ያለ ምኒልክና ያለ ጎበና እንደማይታሰብ ሲጠቅሱ ይህንን እውነታ ማጉላታቸው ይመስለኛል፡፡
የሕዝቦች ትስስርና የፖለቲካ ጋብቻ በአማራና በኦሮሞ ሕዝብ መስተጋብር ብቻ የታጠረ አልነበረም-ሊሆንም አይችልም፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ባህልና ሥልጣኔ መጋመዱ ረቂቅ ነው፡፡ ከጥንታዊ አክሱም ዘመን ጀምሮ በዝነኞቹ የአክሱም መቃብር ሀውልቶች እና በላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ላይ ከምናገኛቸው የኪነ ሕንጻ ትእምርቶች(Symbols) መካከል የውሸት በሮች (False Doors) እና የውሸት መስኮቶች(False windows) የሙታን መንፈስ(ኤከራ) መመላለሻ እንደሆኑ በጥናት የተረጋገጠ ነው (ቢትራይስ ፕሌይን Annales d'Éthiopie 1965) ፡፡ ይህ የኤከራዎች መመላለስና የመነጋገር ባህል እና እምነት ከደቡባዊ ግብጽ አንስቶ እስከ ሰሜን ኬንያ ድረስ በሚኖሩ የኩሽ ሕዝቦች በሰፊው የሚታወቅ ረዥም ዘመን ያስቆጠረ ልምምድ ነው፡፡
ሌላው በልኩ ያልተጠና እና በትርክቶቻችን ውስጥ ትኩረት ያልተሰጠው በሕዝቦች መካከል ያለ ሥልጣኔ ትስስር ታሪክ የእያንዳዱን የዛግዌ ነገሥታት የሥልጣን ዘመናትን የተመለከተ ነው፡፡ ከታሪክ ነገሥት፣ ከልዩ ልዩ ዜና መዋዕሎች፣ ከፖርቱጋል ተጓዦች(ፓኤዝና አልሜዳ) ከብሪቲሽ ሙዝየም እንዲሁም ከኮንቲ ሮሲኒ የተገኙት ምንጮች የሚረጋግጡት የሁሉም የዛግዌ ዐጼዎች( ከአንድ ሁለቱ በስተቀር) የሥልጣን ዘመን 40፤40 ዓመታት ነበር፡፡ ይህ ጉዳይ በኦሮሞ የገዳ ሥርዓት የአንድ ትውልድ የሥልጣን ዑደት ጋር አንድ አይነት የሆነው በአጋጣሚ ነው ወይስ ዛግዌዎች እና ኦሮሞዎች የኩሽ ሕዝቦች በመሆናቸው ቀዳሚ ከሆነው የጋራ ሥልጣኔያቸው የሚቀዳ የአስተዳደር ሥርዓት ነው? እነዚህስ ሀቆች የወል ትርክቶቻችን መመሆን አለመቻላቸው በፖለቲካ ደንቃራነት የተፈጠረ የታሪክ ግርዶሽ(eclipse of history) እንጂ ሌላ ምን ሊባል ይችላል? በላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትና እና በሸዋ በሚገኘው የአዳዲ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ኪነሕንጻ መካከል ያለው ፍጹም ተመሳሳይነት ምንጩ ምንድነው? ሊጠና፣ ሊነገር ልንማርበት ይገባል፡፡
በርግጥም ታሪካችን ትዝታችን ላይ የተጫነ ሸክም ሳይሆን የነፍስ መገለጥ ነው የሚያሰኘው የሕዝቦች ትሥሥር፣ ውህደት የሥልጣኔ መጋራትና መወራረስ ታሪክ መታወቁ መንፈስን ሃርነት ማውጣቱ ይመስለኛል፡፡
5 days ago
7 days ago
ኢትዮጵያና አዘርባጃን፣ ከዲፕሎማሲ ወደ ስትራቴጂካዊ አጋርነት
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ኢትዮጵያና አዘርባጃን ጠንካራ ዲፕሎማሲዊ ግንኙት እየገነቡ መጥተዋል፡፡
በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚገኙት እነዚህ ሁለት ሀገራት የፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ኢንቨስትመንት፣ የመከላከያ እና የቴክኖሎጂ ትብብሮችን ወደ ጠንካራና አዲስ ምዕራፍ ለማሳደግ እየሰሩ ናቸው።
ሀገራቱ የሶቪየት ኅብረት መፍረስን ተከትሎ አዘርባጃን ሪፐብሊክ ራሷን የቻለች ሀገር ከሆነች በኋላ ግንኙነታቸውን ቀስ በቀስ እያጠናከሩ መጥተዋል።
ኢትዮጵያና አዘርባጃን ለበርካታ ዓመታት በዘለቀው ግንኙነታቸው የየሀገራቱ ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት ጉብኝቶችን አድርገዋል፡፡
ሕዳር 2017 ዓ.ም አዘርባጃን ባስተናገደችው የተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ (ኮፕ29) ለመሳተፍ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ወደ ባኩ ተጉዘው ነበር፡፡
በቆታቸውም የአዘርባጃንን የዲጂታል አገልግሎት አሰጣጥ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡
እንዲሁም በ2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ 3ኛው የኢትዮ-አዘርባጃን የፖለቲካ ምክክር መድረክ የተካሄደ ሲሆን÷ መድረኩ የሁለቱን ሀገራት የፖለቲካ ትስስር ወደ ከፍተኛ ደረጃ መድረሱን የሚያመላክት ነበር፡፡
በመቀጠልም የካቲት 2018 ዓ.ም ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የባኩ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ወደ አዲስ ምዕራፍ ከፍ አድርጓል።
በዚህ ሳምንት ደግሞ የአዘርባጃን ሪፐብሊክ የፓርላማ አፈ ጉባዔ ሳሂባ ጋፋሮቫ ኢትዮጵያን እየጎበኙ የሚገኙ ሲሆን÷ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና ከፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔዎች ጋር መክረዋል፡፡
ኢትዮጵያና አዘርባጃን በታሪክና በጂኦግራፊያዊ አቀማመጣቸው ቢለያዩም በርካታ የጋራ ባህሪያት አሏቸው።
ሁለቱም ጂኦፖለቲካዊ ፉክክር ባሉባቸው ቀጣናዎች ይገኛሉ፤ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ፤ አዘርባጃን ደግሞ በደቡብ ካውካሰስ ክልል፡፡ በየቀጣናቸው ሁለቱም ሀገራት ለሰላምና ደህንነት ቁልፍ ሚና እየተጫወቱ ነው፡፡
በዓለም አቀፍ ፖለቲካም ሁለቱ ሀገራት ከምሥራቅና ከምዕራቡ ዓለማት ጋር ሚዛኑን የጠበቀ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲን ይከተላሉ፡፡
ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን መሠረተ ልማትን፣ ዲጂታል ሽግግርን፣ ኢንዱስትሪን እና የውጭ ኢንቨስትመንትን ለልማትና ዕድገታቸው ትኩረት ሰጥተው እየሰሩባቸው ያሉ ዘርፎች ናቸው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አዘርባጃንን በጎበኙበት ወቅት የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ኢልሃም አሊየቭ የሀገራቱን ግንኙነት አስመልክተው ሲገልጹ፣ "አጋርነታችን በርካታ ጠቃሚ ጉዳዮችን ያካተተ ነው" ነበር ያሉት።
ሁለቱ ሀገራት በኢኮኖሚ፣ በወታደራዊ፣ በኢንቨስትመንት፣ በቴክኖሎጂ፣ በአየር ንብረት ለውጥ እና በሌሎች ዘርፎች ግንኙነታቸው እያደገ መምጣቱን መሪዎቹ በተለያዩ ጊዜያት ገልጸዋል፡፡
ፕሬዚዳንት ኢልሃም አሊየቭ ብልፅግና ፓርቲ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ማሸነፉን አስመልክቶ በላኩት የደስታ መልዕክት፣ "በአዘርባጃን እና በኢትዮጵያ መካከል ያለው ግንኙነት በአዎንታዊ አቅጣጫ እያደገ መሆኑ የሚያስደስት ነው" በማለት የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት በአዲስ መልክ እየተጠናከረ መምጣቱን አንስተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በጉብኝታቸው ወቅት እንዳሉት÷ ባለፉት ዓመታት ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በአቪዬሽን፣ በኢንዱስትሪ ፓርኮችና በነጻ የንግድ ቀጣናዎች ረገድ የተከናወኑ የጋራ የኢኮኖሚዊ ትብብሮች፣ የሁለቱን ሀገራት አጋርነት እያደገ መምጣት ያመለከተ ነው ብለዋል።
ሁለቱ ሀገራት አንደኛቸው ከሌላኛው በበርካታ ዘርፎች ልምዶችን እየተለዋወጡ ሲሆን÷ ለአብነትም ኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከአዘርባጃኑ አሳን ክድመት (ASAN Khidmet) የመንግሥት ዲጂታል አገልግሎት ልምድ የተወሰደ የዲጂታል አሰራር ሥርዓት ነው።
አዘርባጃን በበኩሏ በኢትዮጵያ በኩል ወደ አፍሪካ ገበያ ለመግባት ጥሩ መደላድል ታገኛለች። በዚህ መልኩ ሁለቱ ሀገራት የጋራ ጥቅምን በማስፋት በዓለም ኢኮኖሚና ጂኦፖለቲካ አወቃቀር ውስጥ ይበልጥ የሚጎለብት አጋርነት ሊገነቡ ይችላሉ።
ሁለቱ ሀገራት የሚጋሯቸው የልማት ርዕይ፣ የመሠረተ ልማት ግንባታ፣ የዲጂታል ሽግግር፣ የኢኮኖሚ ብዝሃነት እና ቀጣናዊ ትብብሮች ግንኙነታቸውን ከፍ ወዳለ ስትራቴጂካዊ አጋርነት የሚያሳድግ ነው።
በቴዎድሮስ ሳህለ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ኢትዮጵያና አዘርባጃን ጠንካራ ዲፕሎማሲዊ ግንኙት እየገነቡ መጥተዋል፡፡
በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚገኙት እነዚህ ሁለት ሀገራት የፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ፣ ኢንቨስትመንት፣ የመከላከያ እና የቴክኖሎጂ ትብብሮችን ወደ ጠንካራና አዲስ ምዕራፍ ለማሳደግ እየሰሩ ናቸው።
ሀገራቱ የሶቪየት ኅብረት መፍረስን ተከትሎ አዘርባጃን ሪፐብሊክ ራሷን የቻለች ሀገር ከሆነች በኋላ ግንኙነታቸውን ቀስ በቀስ እያጠናከሩ መጥተዋል።
ኢትዮጵያና አዘርባጃን ለበርካታ ዓመታት በዘለቀው ግንኙነታቸው የየሀገራቱ ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት ጉብኝቶችን አድርገዋል፡፡
ሕዳር 2017 ዓ.ም አዘርባጃን ባስተናገደችው የተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ (ኮፕ29) ለመሳተፍ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ወደ ባኩ ተጉዘው ነበር፡፡
በቆታቸውም የአዘርባጃንን የዲጂታል አገልግሎት አሰጣጥ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡
እንዲሁም በ2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ 3ኛው የኢትዮ-አዘርባጃን የፖለቲካ ምክክር መድረክ የተካሄደ ሲሆን÷ መድረኩ የሁለቱን ሀገራት የፖለቲካ ትስስር ወደ ከፍተኛ ደረጃ መድረሱን የሚያመላክት ነበር፡፡
በመቀጠልም የካቲት 2018 ዓ.ም ላይ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የባኩ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ወደ አዲስ ምዕራፍ ከፍ አድርጓል።
በዚህ ሳምንት ደግሞ የአዘርባጃን ሪፐብሊክ የፓርላማ አፈ ጉባዔ ሳሂባ ጋፋሮቫ ኢትዮጵያን እየጎበኙ የሚገኙ ሲሆን÷ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና ከፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔዎች ጋር መክረዋል፡፡
ኢትዮጵያና አዘርባጃን በታሪክና በጂኦግራፊያዊ አቀማመጣቸው ቢለያዩም በርካታ የጋራ ባህሪያት አሏቸው።
ሁለቱም ጂኦፖለቲካዊ ፉክክር ባሉባቸው ቀጣናዎች ይገኛሉ፤ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ፤ አዘርባጃን ደግሞ በደቡብ ካውካሰስ ክልል፡፡ በየቀጣናቸው ሁለቱም ሀገራት ለሰላምና ደህንነት ቁልፍ ሚና እየተጫወቱ ነው፡፡
በዓለም አቀፍ ፖለቲካም ሁለቱ ሀገራት ከምሥራቅና ከምዕራቡ ዓለማት ጋር ሚዛኑን የጠበቀ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲን ይከተላሉ፡፡
ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን መሠረተ ልማትን፣ ዲጂታል ሽግግርን፣ ኢንዱስትሪን እና የውጭ ኢንቨስትመንትን ለልማትና ዕድገታቸው ትኩረት ሰጥተው እየሰሩባቸው ያሉ ዘርፎች ናቸው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አዘርባጃንን በጎበኙበት ወቅት የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ኢልሃም አሊየቭ የሀገራቱን ግንኙነት አስመልክተው ሲገልጹ፣ "አጋርነታችን በርካታ ጠቃሚ ጉዳዮችን ያካተተ ነው" ነበር ያሉት።
ሁለቱ ሀገራት በኢኮኖሚ፣ በወታደራዊ፣ በኢንቨስትመንት፣ በቴክኖሎጂ፣ በአየር ንብረት ለውጥ እና በሌሎች ዘርፎች ግንኙነታቸው እያደገ መምጣቱን መሪዎቹ በተለያዩ ጊዜያት ገልጸዋል፡፡
ፕሬዚዳንት ኢልሃም አሊየቭ ብልፅግና ፓርቲ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ማሸነፉን አስመልክቶ በላኩት የደስታ መልዕክት፣ "በአዘርባጃን እና በኢትዮጵያ መካከል ያለው ግንኙነት በአዎንታዊ አቅጣጫ እያደገ መሆኑ የሚያስደስት ነው" በማለት የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት በአዲስ መልክ እየተጠናከረ መምጣቱን አንስተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በጉብኝታቸው ወቅት እንዳሉት÷ ባለፉት ዓመታት ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በአቪዬሽን፣ በኢንዱስትሪ ፓርኮችና በነጻ የንግድ ቀጣናዎች ረገድ የተከናወኑ የጋራ የኢኮኖሚዊ ትብብሮች፣ የሁለቱን ሀገራት አጋርነት እያደገ መምጣት ያመለከተ ነው ብለዋል።
ሁለቱ ሀገራት አንደኛቸው ከሌላኛው በበርካታ ዘርፎች ልምዶችን እየተለዋወጡ ሲሆን÷ ለአብነትም ኢትዮጵያ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ከአዘርባጃኑ አሳን ክድመት (ASAN Khidmet) የመንግሥት ዲጂታል አገልግሎት ልምድ የተወሰደ የዲጂታል አሰራር ሥርዓት ነው።
አዘርባጃን በበኩሏ በኢትዮጵያ በኩል ወደ አፍሪካ ገበያ ለመግባት ጥሩ መደላድል ታገኛለች። በዚህ መልኩ ሁለቱ ሀገራት የጋራ ጥቅምን በማስፋት በዓለም ኢኮኖሚና ጂኦፖለቲካ አወቃቀር ውስጥ ይበልጥ የሚጎለብት አጋርነት ሊገነቡ ይችላሉ።
ሁለቱ ሀገራት የሚጋሯቸው የልማት ርዕይ፣ የመሠረተ ልማት ግንባታ፣ የዲጂታል ሽግግር፣ የኢኮኖሚ ብዝሃነት እና ቀጣናዊ ትብብሮች ግንኙነታቸውን ከፍ ወዳለ ስትራቴጂካዊ አጋርነት የሚያሳድግ ነው።
በቴዎድሮስ ሳህለ
8 days ago
የመከረ ቤቱን አጠናከረ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሀገራችን በአንድ ግዙፍ የታሪክ ምዕራፍ እጥፋት ላይ ትገኛለች፡፡ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ የውስጥ ጉዳዮቿን የሀገር ልጆች ቁጭ ብለው ተመካክረው ሀገር ሊያጸኑ ተሰባስበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የምክክሩን አስፈላጊነት በተመለከተ ሲናገሩ፣ "ለልጆቿ ኩራት የሆነች፣ ተስፋ ያላት ምድር ለማድረግ አንድንችል ምክክሩ በእጅጉ ያስፈልጋል" ነው ያሉት፡፡
ኢትዮጵያ በርካታ ብሔር ብሔረሰቦች የሚኖሩባት ባለ ብዝሃ ባህል፣ ብዝሃ ታሪክ፣ ብዝሃ ማህበረ ኢኮኖሚ ሀገር እንደመሆኗ በዘመናት ጉዞዋ የልማት፣ የአስተዳደራዊ እና ሌሎች አለመግባባቶች እንደሚኖሩ ይጠበቃል፡፡
የእነዚህን በህዝቦች መካል የሚስተዋሉ ልዩነቶች አለመግባባቶችና ጥያቄዎች በዘላቂነት በመፍታት ህብረ ብሔራዊ አንድነቷ የተጠበቀ፣ የበለጸገችና የታፈረች ኢትዮጵያን ለትውልድ ለማስተላለፍ ምክክሩ እጅግ ያስፈልጋል።
ብሔራዊ ምክክሩ የታለመለትን ግብ እንዲመታ እና ሀገር እንድትጸና ለማድረግ የሁሉምን ህብረተሰብ ክፍሎች ያካተተ እና ያሳተፈ እንዲሆን ተደርጓል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የምክክር ሂደቱ፣ "በፖለቲካ ልሂቃን መካከል የሚደረግ ብቻ ሳይሆን የሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፎ ያገናዘበ፣ በኢትዮጵያውያን የተመራ ሀገር በቀል መፍትሄዎችን ለማፍለቅ ታልሞ የሚከናወን ይሆናል" ባሉት መሰረት የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ምሁራን፣ ሴቶች፣ ወጣቶች፣ ሠራተኞች፣ አካል ጉዳተኞች፣ እንዲሁም ተፈናቃዮች እንዲሳተፉ ተደርጓል።
የተለያዩ የዘርፉ ምሁራን በምክክርና ውይይት ሂደት የአካታችነት እና አሳታፊነትን ፋይዳ ያሰምሩበታል፡፡ በስዊዝፒስ የድርድር ፕሮግራም ኃላፊ የሆኑት ዴቪድ ላንዝ የአንድን ሀገር መሰረታዊ ማንነትና የአስተዳደር ስርዓት ለመወያየት የሚያስችል ሁሉን አቀፍ አሰራር ከሌለ፣ ከዚያ በኋላ የሚደረጉ ማናቸውም ውሳኔዎች ወይም ተቋማዊ ማሻሻያዎች በአሸዋ ላይ እንደተገነባ ቤት ይሆናሉ ይላሉ፡፡
ኢትዮጵያ ሀገር በቀል የሆኑ በዘመናት ተሞክረው እና ተፈትነው በውጤታማነት የዘለቁ የልዩነትና የግጭት መፍቻ ስርዓቶች ባለቤት እንደመሆኗ አሁን እየተካሄደ ያለው የምክክር ጉባኤ የእነዚህ እሴቶች አዲስ ምዕራፍ መገለጫ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡
ምክክሩ ሁሉም ሃሳቡን የሚገልፅበት፣ የሌሎች ጥያቄዎችና ቅሬታዎች የሚደምጥበት፣ በጋራ መፍትሄ የሚፈለግበትና የጋራ መግባባት ላይ የሚደረስበት በመሆኑ ውጤቱም ዘላቂና ሀገርን የሚያጸና ነው፡፡
በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እና በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር መላው ኢትዮጵያውያን በአንድ ዜማ ተግባብተው ታሪክ እንደሰሩ ሁሉ በሀገራዊ መግባባትና ሀገር መፅናት ጉዳይም ተመሳሳይ ድል የመቀዳጀት ጉዞ ላይ ናቸው።
ይህ ለአፍሪካውያን ብሎም ለዓለም ተምሳሌት ሊሆን የሚችል የኢትጵያውያን፣ በኢትዮጵያውያን ለኢትዮጵያውያን የተዘጋጀ ታሪካዊ መድረክ የበለጸገች ህብረ ብሔራዊ ኢትዮጵያን ለትውልድ ለማስተላለፍ ፅኑ መሰረት ይጥላል።
የምክክር ሂደቱ በስኬት እስኪጠናቀቅ፣ ኢትዮጵያውያን ከሊቅ እስከ ደቂቅ የሚጠበቅባቸውን ሚና ሊወጡ ይገባል፡፡
በቴዎድሮስ ሳህለ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሀገራችን በአንድ ግዙፍ የታሪክ ምዕራፍ እጥፋት ላይ ትገኛለች፡፡ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ የውስጥ ጉዳዮቿን የሀገር ልጆች ቁጭ ብለው ተመካክረው ሀገር ሊያጸኑ ተሰባስበዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የምክክሩን አስፈላጊነት በተመለከተ ሲናገሩ፣ "ለልጆቿ ኩራት የሆነች፣ ተስፋ ያላት ምድር ለማድረግ አንድንችል ምክክሩ በእጅጉ ያስፈልጋል" ነው ያሉት፡፡
ኢትዮጵያ በርካታ ብሔር ብሔረሰቦች የሚኖሩባት ባለ ብዝሃ ባህል፣ ብዝሃ ታሪክ፣ ብዝሃ ማህበረ ኢኮኖሚ ሀገር እንደመሆኗ በዘመናት ጉዞዋ የልማት፣ የአስተዳደራዊ እና ሌሎች አለመግባባቶች እንደሚኖሩ ይጠበቃል፡፡
የእነዚህን በህዝቦች መካል የሚስተዋሉ ልዩነቶች አለመግባባቶችና ጥያቄዎች በዘላቂነት በመፍታት ህብረ ብሔራዊ አንድነቷ የተጠበቀ፣ የበለጸገችና የታፈረች ኢትዮጵያን ለትውልድ ለማስተላለፍ ምክክሩ እጅግ ያስፈልጋል።
ብሔራዊ ምክክሩ የታለመለትን ግብ እንዲመታ እና ሀገር እንድትጸና ለማድረግ የሁሉምን ህብረተሰብ ክፍሎች ያካተተ እና ያሳተፈ እንዲሆን ተደርጓል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የምክክር ሂደቱ፣ "በፖለቲካ ልሂቃን መካከል የሚደረግ ብቻ ሳይሆን የሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፎ ያገናዘበ፣ በኢትዮጵያውያን የተመራ ሀገር በቀል መፍትሄዎችን ለማፍለቅ ታልሞ የሚከናወን ይሆናል" ባሉት መሰረት የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ምሁራን፣ ሴቶች፣ ወጣቶች፣ ሠራተኞች፣ አካል ጉዳተኞች፣ እንዲሁም ተፈናቃዮች እንዲሳተፉ ተደርጓል።
የተለያዩ የዘርፉ ምሁራን በምክክርና ውይይት ሂደት የአካታችነት እና አሳታፊነትን ፋይዳ ያሰምሩበታል፡፡ በስዊዝፒስ የድርድር ፕሮግራም ኃላፊ የሆኑት ዴቪድ ላንዝ የአንድን ሀገር መሰረታዊ ማንነትና የአስተዳደር ስርዓት ለመወያየት የሚያስችል ሁሉን አቀፍ አሰራር ከሌለ፣ ከዚያ በኋላ የሚደረጉ ማናቸውም ውሳኔዎች ወይም ተቋማዊ ማሻሻያዎች በአሸዋ ላይ እንደተገነባ ቤት ይሆናሉ ይላሉ፡፡
ኢትዮጵያ ሀገር በቀል የሆኑ በዘመናት ተሞክረው እና ተፈትነው በውጤታማነት የዘለቁ የልዩነትና የግጭት መፍቻ ስርዓቶች ባለቤት እንደመሆኗ አሁን እየተካሄደ ያለው የምክክር ጉባኤ የእነዚህ እሴቶች አዲስ ምዕራፍ መገለጫ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡
ምክክሩ ሁሉም ሃሳቡን የሚገልፅበት፣ የሌሎች ጥያቄዎችና ቅሬታዎች የሚደምጥበት፣ በጋራ መፍትሄ የሚፈለግበትና የጋራ መግባባት ላይ የሚደረስበት በመሆኑ ውጤቱም ዘላቂና ሀገርን የሚያጸና ነው፡፡
በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እና በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር መላው ኢትዮጵያውያን በአንድ ዜማ ተግባብተው ታሪክ እንደሰሩ ሁሉ በሀገራዊ መግባባትና ሀገር መፅናት ጉዳይም ተመሳሳይ ድል የመቀዳጀት ጉዞ ላይ ናቸው።
ይህ ለአፍሪካውያን ብሎም ለዓለም ተምሳሌት ሊሆን የሚችል የኢትጵያውያን፣ በኢትዮጵያውያን ለኢትዮጵያውያን የተዘጋጀ ታሪካዊ መድረክ የበለጸገች ህብረ ብሔራዊ ኢትዮጵያን ለትውልድ ለማስተላለፍ ፅኑ መሰረት ይጥላል።
የምክክር ሂደቱ በስኬት እስኪጠናቀቅ፣ ኢትዮጵያውያን ከሊቅ እስከ ደቂቅ የሚጠበቅባቸውን ሚና ሊወጡ ይገባል፡፡
በቴዎድሮስ ሳህለ
Sponsored by
Surafel
9 days ago
#ቤተልሔም_ሸረፈዲን - " የልጅ ልብና የአዋቂ ጆሮ ያላት "
( የአልፎ ሂያጁ ማስታወሻ )
**********************************************
ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ
#በመጨረሻም ፦ ጽሑፉ ለፌስቡክ ረጅም ( አረፍ አረፍ እየተባለ ተነቦ የሚያልቅ ) ነው ። አጥሮ ሁሉም ጋ ከሚደርስ ረዝሞ የሚመለከታቸውና የሚያስፈልጋቸው ቢያነቡት መርጬ ነው ። ሆነ ብዬ ነው ማለት ነው ። ይሁን ። እንግዲህ እያረፋችሁም ፣ እያለፋችሁም አንብቡት ።
ለግጥምም ፣ ለዜማም አልፎ ሂያጅ ነኝ። ( በተለይ ) ለግጥም አልፎ ሂያጅ መሆኔ ያስቆጨኛል ። ግጥም ምኞቴ ነው ፤ ጉድለቴም ። ማንም እንደሚሰማውና እንደሚረዳው ነኝ ። አዚያዚያምን መረዳትም ላይ ጨዋ አላዋቂ ነኝ ። ቤተልሔም ሸረፈዲን " ደስተኛ " ብላ ስለሰየመችው አዲሱ አልበሟ የተሰማኝን ልላችሁ ነው ዳር ዳር የምለው ።
እኔ የምለው ፣ ቤተልሔም ሸረፈዲን ግን ስንት ዓመቷ ነው ? በቅርቡ ትንሽ ልጅ አልነበረችም እንዴ ? ከመቼው አደገች ? ከምኔው አብባ አፈራች ? አልበሟ በተለቀቀበት " ኩራ ስትሪም " ላይ ገጣሚው ናትናኤል ግርማቸው ( ናቲ ) እንደ ገጣሚነቱ ቃላት ቆጥቦና ሀሳቡን አስውቦ " የልጅ ልብና የአዋቂ ጆሮ አላት
" እንዳላት ሆና ነው የመጣችው ። የጥበብ ስራ አመዛኙን ሁለቱን ይፈልጋል ። እውቀትም ፣ ተሰጥዖም በዝቶ ኖሯቸው የትም ሳይደርሱ የቀሩ " እገሌ ፣ እገሌ " የምንላቸው ጥቂት የማይባሉ የጥበብ ሰዎች በየአልባሌው ወድቀው ቀርተዋል ። እስቲ እነዚህን ሰዎች አስቧቸው ። የህጻን ልብም ፣ የአዋቂ ጆሮም አታገኙባቸውም ።
10 ዘፈኖች የያዘው " ደስተኛ " አልበም ናትናኤል ግርማቸውና ታምሩ አማረ በጥምረት ፕሮዲዩስ ያደረጉት ነው ። ከጀርባቸው ደግሞ ከብዙ ጥበባትና የጥበብ ሰዎች ጀርባ ያለው ዘላለም ኩራባቸው " ኩራ ስትሪም " ን ይዞ አለ ። ቅንብሩን ፣ ሚክሲንግ እና አሬንጅመንቱን ታምሩ አማረ ፣ ግጥሞቹን ( በሙሉ ) ናትናኤል ግርማቸው ( ናቲ ) ፣ " ባለቤቴ " እና " እንዴት " ዜማዎችን ዮሴፍ በቀለ ( ጆ ) ፣ " አይታለፍም " ዜማ እሱባለው ይታየው ( የሺ ) ፣ የቀሪዎቹን 7 ስራዎች ዜማዎች በምህረተአብ ደስታ ሲፈጠሩ ከእነዚህ ውስጥ የእበሙ መጠሪያ የሆነው " ደስተኛ " ን ዜማ ናቲና ምህረተአብ በጋራ ሰርተዋቸዋል ።
በአሁኑ ጊዜ አንድ ነጠላ ዜማ መስራት የምረቃ ፕሮግራም ያዘጋጃል ፤ ወዳጅ ዘመድ ያጠራራል ፤ " ሰይፉ በኢቢኤስ " ላይ ያስቀርባል ፤ ማህበራዊ ሚዲያው ላይ አላስቆም አላስቀምጥ ያስብላል ። አልበም መስራት ( አድማጭ ያልተቀበለውም ቢሆን እንኳ ) እንደ አራሷ ሴት " ምጡን ተዪው ፤ ልጁን እዪው " እየተባለና የስቃዩ ጊዜ እየተረሳ እንጂ ደጋግሞ በስሜት ሞቶ መነሳት ነው ። የሚያገጫጭ ፣ የሚያነጫንጭ ፣ የሚያቀያይምንና " ሁለተኛ ብንገናኝ ! " የሚያባብል ነው ። የምጡ ጊዜ አልፎ ልጁ ሲታይ እየተረሳ ነው አንዱ ሙዚቀኛ ከሌላው ጋር የኖረው ። ቤተልሔም መልካሞችና ህልም ያላቸው ሙያተኞች እጅ ላይ አሳርፏት እንጂ ጀምሮ አለመጨረስ ፣ ወድቆ አለመነሳትም አለ ። ገና በመጀመሪያው አልበም ፣ በትንሽ እድሜ ፣ በጀማሪነት አረዳድ እንዲህ ያለ ስኬታማ አልበም መስራት ደጋግሞ የማያጋጥም ነው ። ህብስት ጥሩነህ እነ አየለ ማሞ ( ማንዶሊን ) እና ታንጎ ሙዚቃ ቤትን እንዳገኘችው አይነት እድለኛነት ይጠይቃል ። የናቲ እና ታምሩ ጥምረት ደግሞ የእነ ኤሌክራትን እና አምባሰልን ዘመን ያስታውሰናል ።
ናቲ " ኩራ ስትሪም " ላይ 4 ዓመት ስላለፈው " ደስተኛ " አልበም ሲናገር " አልበሙን ጀምረነው ባልነው ጊዜ ያልጨረስነው እኛ በዚያ ውስጥ እየተሰራን ስለነበረ ነው " ይለዋል ። ፕሮዲዩሰሮቹ በምን በምን እንደተሰሩ አላውቅም ። ቤተልሔምን ግን በእርግጥም ሰርተዋታል ። አፈሩን ቆፍረውና አልመው ፣ አቡክተው ቤተልሔምን እንደ ውቡ ሸክላ አስጊጠው ሰርተዋታል ። እሷ እንደምትለውም ትንሿ ቤተልሔም " ከብዙ ልምምድ በኋላ የመጣ አልበም " ባለቤት እንትሆን አድርገዋታል ። ቤተልሔም ሸረፈዲን የተባለች ጥንቅቅ ፣ ጥፍጥ ያለ ስራ ያላት ድምጻዊትን ለዘመኑ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ( ? ) አበርክተዋል ። አሁን የኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ቤተልሔም ሸረፈዲን የምትባል ብስል ፣ ትክን ያለች ድምጻዊት አለችለት ። ቤተልሔም ስለ አዲሱ አልበሟ ለኩራ ስትሪም ስትናገር " ይሄን አልበም እንደ መጀመሪያም ፣ እንደ መጨረሻም ስራ አድርጌ ነው የማየው ። " ብላለች ።
ናትናኤል ግርማቸው ገጣሚነት ተሰጥቶታል ። ገጣሚነቱ የቃላት ድርደራ ሳይሆን የሀሳብ ስፋት የታደለው ነው ። ናቲን በራሄል ጌቱ " ኢትዮጵያዬ " ነው ያወቅኩት ። የራሷን የራሄል ጌቱን " ያገሬ ሰው " ፣ በኋላም " ወረት " ን ሰርቶ አስደንቆኛል ። ናቲን በራሄል ጌቱ ( በስራዎቿ ) በኩል ነው ያገኘሁት ። ይህ ሰው ነው ደግሞ ከታምሩ አማረ ጋር ሆኖ ቤተልሔም ሸረፈዲንን ያገኛት ። ሁለቱ በፕሮዲዩሰርነት ባይከሰቱ ቤተልሔም ሸረፈዲን ቢያንስ በዚህ ጊዜ አትወለድም ። የጀርባ አቅሟን ባላውቅም የ10 ግጥም ፣ የ10 ዜማ ፣ የ10 ዜማዎች ቅንብር ፣ ሚክሲንግ እና ማስተሪንግ ክፍያን አትወጣውም ( ብዬ እገምታለሁ ) ። ከሁሉም በላይ ደግሞ ዘላለም ኩራባቸውን አታገኘውም ። ዘላለም ኩራባቸው ወደ ሙዚቃ ማምረት ስራ ሲገባ ከገንዘብ የነፍስ ጥሪ ትርፉን አስቦ እንደሚሆን አምናለሁ ። ካሁን ቀደም በተናጠል ሲያደርግ የነበረውን ሙያውንና ሙያተኛውን እንደ ታላቅ ወንድም አጋር የመሆን ዝንባሌውን ተቋማዊ ቅርጽ ሰጥቶት መምጣቱ ይመስለኛል ። ቤተልሔም እድለኛ ናት ። እነ ንዋይ ደበበ ፣ ሀመልማል አባተ ፣ ጸሐዬ ዮሀንስ እና ዘመንኞቻቸው በመጡበት መንገድ ነው የመጣችው ። ሌላም እድለኛነት ( ከችሎታ ጋር ) አላት ።እነ ጠረፍ ካሳሁን ፣ ራሄል ጌቱ ፣ ለምለም ኃ/ሚካኤል ፣ ዘቢባ ግርማ ተሰርተው የወጡበት " የኛ " ፕሮጀክት ፣ የእነ አይዳ አሸናፊ እጅም አርፎባታል ።
ከአስሩ የ " ደስተኛ " አልበም ስራዎች በተሸከመው ሀሳብ ( ለእኔ ) " ባለቤቴ " ን የሚያህልልኝ አላገኘሁም ። ለዚህ ዘፈን ከ " ባለቤቴ " ይልቅ " አትክልተኛው " ስምም ሆኖልኛል ። ምናልባት ግን " አትክልተኛው " ለዘፈን ርዕስነት ያንስ ( አይሆን ) እንደሆን አላውቅም ። ሙሉ ዘፈኑን ስንሰማው ገጸባሕሪዋ በምናቧ ከዋለለችለት የምናብ ባለቤቷ ይልቅ የሰው ያልሆነ ፣ ለሰው አዕምሮ " ሞኝ " የሚባል ፣ ለፍጽምና የቀረበ በዝናብም ፣ በጸሐይም ስራውን የማያስተጓጉል ፣ ብርሀን መርጦ የማይመጣ ፣ በጭለማ የማይሸሸግ ፣ የማግኘትም ፣ የማጣትም ጊዜ ወዳጅ ፣ እንደ አምላክ ያለ ብርቱ ሰው ነው ። ባለቤትነቱ ህልም ሲሆን ብርቱ አትክልተኝነቱ ግን እውን ነው ። ይህ ሰው ትትርናውና ቸርነቱ እንደ አምላክ ያለ ነው ። ከማንም ፣ ከምንም የማይጠብቅ ። መስጠት ብቻ የሆነ ። በአበቦቹ መሐል ብቻ አይደለም ያለው ። ልብ ባለበት ሁሉ ነው ።
" በዝናብ አካሉም በዶፉ እየረሰረሰ
የአትክልቶቹን ስር ሲያጠጣ የልምዱን ውሀ እያፈሰሰ
አሉት የማን ነው ጅል ያን አትክልተኛ
ሳቁበት እንደሞኝ ወይኔ
አላወቁም የእሱ ዝናብ መጣ ቀረ
ንፍገትን ለልቡ እንዳላስተማረ ።
*************************
አሰብኩት ከሆነ እንዲህ ለአትክልቱ
እንዴት መልካም ይሆን ለሚወዳት ሚስቱ "
ያለችውን ብርቱና ቸር ሰው ነው . . .
" ቢዘንብም ቢያካፋም ከጎኔ የማይጠፋ
እንደ ባለ አጸዱ ጽኑ ለመውደዱ
ሳላውቅህ ልንገርህ የነገ ውሀ አጣጬ
አርገኝ እንዳልከስም ፍቅርን ተጠምቼ "
እያለች ምኞቷን ፣ መሻቷን ፣ የወደፊት ህልሟን ትነግረናለች ። መልካምነት መስጠት ብቻ ሳይሆን መቀበልንም ይፈልጋል ። ምርጥ ዘር ምርጥ አፈርንም ይፈልጋል ። በተዘራበት ሁሉ አይበቅልም ። እንደ እሷ የሚረዳ ካልተገኘ ሌሎቹ እንዳሉት " የማነው ሞኝ ? " ያስብላል ።
በርዕሰ ጉዳይ ደረጃ የዚህ የወደድኩት ብርቱ አትክልተኛ ተቃራኒ ቢሆንም የእኔ ከ1ኛ - 3ኛ " ቻው ( ዎ ) " ነው ።
" አልነበረም ከዓይን የተሰወረ
መንገድህን ሳላየው መች ቀረ
ሰነባብቷል መንፈስህ ሸፍቷል
ልቤን ልብህ ቻው ካለው ቆይቷል ።
አልታወጀም እንጂ ፊትም የእኛ ነገር
የተለያየነው አብረን ሆነን ነበር ።
እንባዬ ተማጽኖህ እንዳያስታርቀን
ያለቀው ያኔ ነው ልብህ የሄደ ቀን ።
እያንዳንዱን ቀናት በእንባ እየሰፈርኩኝ
ቻው ስልህ ኖሬያለሁ እየሸራረፍኩኝ ።
ዛሬም ለበደልህ አረከኝ ጣል ጣል
ቻው ማለት ብቻ ነው የቀረኝ አንድ ቃል ። "
ይኽ መቸም በየፍቅር ጎጆው ፣ በየትዳር ማጀቱ ፣ በየጓደኝነቱና ወዳጅነቱ አደባባይ የሚታይ የወቅቱ እውነታ ነው ። በየግንኙነታችን " ቻው ማለት ብቻ ነው የቀረኝ አንድ ቃል " ። አብዛኛዎቻችን አንድ ላይ ቆመናል እንጂ አብረን አይደለንም ። " አንድ ላይ ብንሆንም ተለያይተናል " እንዳለው ድምጻዊው ። እግሮቻችን ብቻ አብረው ይጓዛሉ ፤ አካላችን አንድ ላይ ይታያል ፤ ነፍስ የሌለው ስጋ ነው ። አብረን ውለን እናድራለን ፤ በልባችን ግን ተለያይተናል ። አልታወቀን ይሆናል እንጂ እንደ ግልም ፣ እንደ ሀገርም እንዲህ ሆነናል ። ለዚህ ነው አሁን ያለንበት ላይ ያለነው ። ለዚህ ነው በየሰበቡ ሕይወት የሚታክተን ። ለዚህ ነው መኖር ትግል ፣ አብሮነት መተናነቅ የሚሆንብን ( የሆነብን ) ። የቤተልሔም ሸረፈዲን " ቻው " ለአንድ ተፈቃሪ ወንድ የተሰራም ቢሆን ሀሳቡ ግን እዚህ ድረስም የሚመጣ ነው ። ናቲ " ቃሉ ከዜማው ጋር ነው የመጣው " ያለውና ራሷን ድምጻዊቷን አስለቅሶ የተገለጠው " ቻው " ገና ብዙውን ልብ የሚነካ ስራ ይሆናል ።
" ልቤን " ን ላልወደው አስቤ ነበረ መሰለኝ ። የእድሜም ፣ የፍላጎትም ጉዳይ ሆኖ ፈጠን ላሉ ምቶች አልደነግጥ ሆኖ ይሆናል እንጂ ምን ሆኜ ነው ዜማው ፣ ምቱ ፣ በተለይ የድምጻዊቷ አዘፋፈን ከፍ ብሎ የታየበትን ይህን ስራ " ይቆየኝ " ያልኩት ? ባልወደውና ደጋግሜ ባልሰማው ይቆጨኝ ነበር ። ( ለነገሩ ካልወደድኩት ለምን ይቆጨኛል ? ) " ደስተኛ " ርዕስና ሀሳቡ ደስተኛ ካልሆነች ፣ " አልወድሽም " ከተባለችና ከተገፋች ገጸባህሪ የተገኘ ነው ። " ቢከፋም ፣ ቢለማም ባለኝ ደስተኛ ነኝ " ትላለች ። " አልወድሽም " ተብላና " ብትጎዘጉዝ አበባ ዛሬ አይረባ " ያለች ሴት ራሷን ማታለል ሳይሆን " ቢከፋም ፣ ቢለማም ባለኝ ደስተኛ ነኝ " ስትል ካዋጣትና ከተቻላት ያድርግላት ። ከእሷ እንባና የልብ ስብራት ምን ጉዳይ አለን ? ብቻ ከአፏ ሳይሆን ከልቧ ይሁን ።
" እንደ ውሀ መውረድ ፣ እንደ ጸሐይ መውጣት
እንደ ጊዜው መክነፍ ፣ እንደ አሸዋ መብዛት
እውነታ መሆኑን ቅንጣት ሳልጠረጥር
እኔስ አምነዋለሁ የልብህን ፍቅር "
ያለችበት " አካልዬ " ለረጋ ያለ ሙዚቃ አፍቃሪ ይሁነኝ ተብሎ የተቀመረ ስራ ነው ። በምርጤነት ከተቀበልኳቸው መካከል አንዱ ነው ።
አንደኛው ሙዚቃ አስተያየት መስጫ ውስጥ ገብቼ ሳነብ " የዚህ አልበም ትልቁ ችግሩ ውስጡ ያሉት ዘፈኖች 10 ብቻ መሆናቸው ነው " ሲል " አድናቆቱን " ገልጿል ። እኔም እንደዚያ ሆኖ ይሰማኛል ። ከአስሩ ሰባቱን ስራዎች በልዩ ሁኔታ ወድጃቸዋለሁ ። አንዱ የዋለልኩበትና ሁለቱ ደግሞ ልብ ያልሰጠኋቸው ናቸው ። ይህ በአንድ አለበም ውስጥ ከበቂ በላይ ስኬታማነት ነው ። ከብዙ ዓመት በኋላ ተሟልቶ ያገኙሁት ምርጤ ነው " ደስተኛ " አልበም ።
እዚህ አልበም ላይ ያለኝ አንድ ( ግላዊ ) ቅሬታ አስሩም ስራዎች የተቃራኒ ጾታ ፍቅር ላይ ብቻ ያተኮሩ መሆናቸው ነው ። እንዳይሆኑ የሚከለክል ደንብ የለም ። ፕሮዲዩሰሮቹ የቤተልሔምን እድሜና የፍቅር ጊዜዋን አስበው ያደረጉት ሊሆን ይችላል ። ያም ቢሆን በዚህ ውጥንቅጡ የወጣ የመከራ ጊዜ ፣ በብዙ ሰው ሰራሽና የአስተሳሰብ ሰንሰለት እግር ከወርች ታስረን መሔጃ ባጣንበት ዘመንና ሀገር ፣ ላለንበት ጊዜ ፣ ለስሜታችን ፣ ለህመማችን ፣ ለሰለለው ተስፋችን የሚሆን አንድ ስራ ልናጣ አይገባም ብዬ አስባለሁ ። ናቲና ምህረተአብ ለራሄል ጌቱ እንደሰጧት " ያገሬ ሰው " ያለ ስራ ቢመርቁልን እንዴት መልካም ነበረ ?
ከቀናት በፊት አስቴር አወቀ ( በድጋሚ ስራዎቿም ቢሆን ) በትንሿ ቤተልሔም ሸረፈዲን ላይ ተደርባ አልበሟን መልቀቋ አስፈርቶኝ ነበረ ። ይህን የመሰለ አልበም ፣ የ4 ዓመት የሚነገርና የማይነገር እልህ አስጨራሽ ድካም መና እንዳይቀር ሰግቼ ነበረ ። ስጋቴ ስጋት ብቻ ሆኖ ቀርቷል ። ቤተልሔም የዋርካው ጥላ ሳያርፍባት አልፋለች ። ገና ገና ትቀጥላለች ፤ ትቀጣጠላለች ።
( የአልፎ ሂያጁ ማስታወሻ )
**********************************************
ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ
#በመጨረሻም ፦ ጽሑፉ ለፌስቡክ ረጅም ( አረፍ አረፍ እየተባለ ተነቦ የሚያልቅ ) ነው ። አጥሮ ሁሉም ጋ ከሚደርስ ረዝሞ የሚመለከታቸውና የሚያስፈልጋቸው ቢያነቡት መርጬ ነው ። ሆነ ብዬ ነው ማለት ነው ። ይሁን ። እንግዲህ እያረፋችሁም ፣ እያለፋችሁም አንብቡት ።
ለግጥምም ፣ ለዜማም አልፎ ሂያጅ ነኝ። ( በተለይ ) ለግጥም አልፎ ሂያጅ መሆኔ ያስቆጨኛል ። ግጥም ምኞቴ ነው ፤ ጉድለቴም ። ማንም እንደሚሰማውና እንደሚረዳው ነኝ ። አዚያዚያምን መረዳትም ላይ ጨዋ አላዋቂ ነኝ ። ቤተልሔም ሸረፈዲን " ደስተኛ " ብላ ስለሰየመችው አዲሱ አልበሟ የተሰማኝን ልላችሁ ነው ዳር ዳር የምለው ።
እኔ የምለው ፣ ቤተልሔም ሸረፈዲን ግን ስንት ዓመቷ ነው ? በቅርቡ ትንሽ ልጅ አልነበረችም እንዴ ? ከመቼው አደገች ? ከምኔው አብባ አፈራች ? አልበሟ በተለቀቀበት " ኩራ ስትሪም " ላይ ገጣሚው ናትናኤል ግርማቸው ( ናቲ ) እንደ ገጣሚነቱ ቃላት ቆጥቦና ሀሳቡን አስውቦ " የልጅ ልብና የአዋቂ ጆሮ አላት
" እንዳላት ሆና ነው የመጣችው ። የጥበብ ስራ አመዛኙን ሁለቱን ይፈልጋል ። እውቀትም ፣ ተሰጥዖም በዝቶ ኖሯቸው የትም ሳይደርሱ የቀሩ " እገሌ ፣ እገሌ " የምንላቸው ጥቂት የማይባሉ የጥበብ ሰዎች በየአልባሌው ወድቀው ቀርተዋል ። እስቲ እነዚህን ሰዎች አስቧቸው ። የህጻን ልብም ፣ የአዋቂ ጆሮም አታገኙባቸውም ።
10 ዘፈኖች የያዘው " ደስተኛ " አልበም ናትናኤል ግርማቸውና ታምሩ አማረ በጥምረት ፕሮዲዩስ ያደረጉት ነው ። ከጀርባቸው ደግሞ ከብዙ ጥበባትና የጥበብ ሰዎች ጀርባ ያለው ዘላለም ኩራባቸው " ኩራ ስትሪም " ን ይዞ አለ ። ቅንብሩን ፣ ሚክሲንግ እና አሬንጅመንቱን ታምሩ አማረ ፣ ግጥሞቹን ( በሙሉ ) ናትናኤል ግርማቸው ( ናቲ ) ፣ " ባለቤቴ " እና " እንዴት " ዜማዎችን ዮሴፍ በቀለ ( ጆ ) ፣ " አይታለፍም " ዜማ እሱባለው ይታየው ( የሺ ) ፣ የቀሪዎቹን 7 ስራዎች ዜማዎች በምህረተአብ ደስታ ሲፈጠሩ ከእነዚህ ውስጥ የእበሙ መጠሪያ የሆነው " ደስተኛ " ን ዜማ ናቲና ምህረተአብ በጋራ ሰርተዋቸዋል ።
በአሁኑ ጊዜ አንድ ነጠላ ዜማ መስራት የምረቃ ፕሮግራም ያዘጋጃል ፤ ወዳጅ ዘመድ ያጠራራል ፤ " ሰይፉ በኢቢኤስ " ላይ ያስቀርባል ፤ ማህበራዊ ሚዲያው ላይ አላስቆም አላስቀምጥ ያስብላል ። አልበም መስራት ( አድማጭ ያልተቀበለውም ቢሆን እንኳ ) እንደ አራሷ ሴት " ምጡን ተዪው ፤ ልጁን እዪው " እየተባለና የስቃዩ ጊዜ እየተረሳ እንጂ ደጋግሞ በስሜት ሞቶ መነሳት ነው ። የሚያገጫጭ ፣ የሚያነጫንጭ ፣ የሚያቀያይምንና " ሁለተኛ ብንገናኝ ! " የሚያባብል ነው ። የምጡ ጊዜ አልፎ ልጁ ሲታይ እየተረሳ ነው አንዱ ሙዚቀኛ ከሌላው ጋር የኖረው ። ቤተልሔም መልካሞችና ህልም ያላቸው ሙያተኞች እጅ ላይ አሳርፏት እንጂ ጀምሮ አለመጨረስ ፣ ወድቆ አለመነሳትም አለ ። ገና በመጀመሪያው አልበም ፣ በትንሽ እድሜ ፣ በጀማሪነት አረዳድ እንዲህ ያለ ስኬታማ አልበም መስራት ደጋግሞ የማያጋጥም ነው ። ህብስት ጥሩነህ እነ አየለ ማሞ ( ማንዶሊን ) እና ታንጎ ሙዚቃ ቤትን እንዳገኘችው አይነት እድለኛነት ይጠይቃል ። የናቲ እና ታምሩ ጥምረት ደግሞ የእነ ኤሌክራትን እና አምባሰልን ዘመን ያስታውሰናል ።
ናቲ " ኩራ ስትሪም " ላይ 4 ዓመት ስላለፈው " ደስተኛ " አልበም ሲናገር " አልበሙን ጀምረነው ባልነው ጊዜ ያልጨረስነው እኛ በዚያ ውስጥ እየተሰራን ስለነበረ ነው " ይለዋል ። ፕሮዲዩሰሮቹ በምን በምን እንደተሰሩ አላውቅም ። ቤተልሔምን ግን በእርግጥም ሰርተዋታል ። አፈሩን ቆፍረውና አልመው ፣ አቡክተው ቤተልሔምን እንደ ውቡ ሸክላ አስጊጠው ሰርተዋታል ። እሷ እንደምትለውም ትንሿ ቤተልሔም " ከብዙ ልምምድ በኋላ የመጣ አልበም " ባለቤት እንትሆን አድርገዋታል ። ቤተልሔም ሸረፈዲን የተባለች ጥንቅቅ ፣ ጥፍጥ ያለ ስራ ያላት ድምጻዊትን ለዘመኑ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ( ? ) አበርክተዋል ። አሁን የኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ቤተልሔም ሸረፈዲን የምትባል ብስል ፣ ትክን ያለች ድምጻዊት አለችለት ። ቤተልሔም ስለ አዲሱ አልበሟ ለኩራ ስትሪም ስትናገር " ይሄን አልበም እንደ መጀመሪያም ፣ እንደ መጨረሻም ስራ አድርጌ ነው የማየው ። " ብላለች ።
ናትናኤል ግርማቸው ገጣሚነት ተሰጥቶታል ። ገጣሚነቱ የቃላት ድርደራ ሳይሆን የሀሳብ ስፋት የታደለው ነው ። ናቲን በራሄል ጌቱ " ኢትዮጵያዬ " ነው ያወቅኩት ። የራሷን የራሄል ጌቱን " ያገሬ ሰው " ፣ በኋላም " ወረት " ን ሰርቶ አስደንቆኛል ። ናቲን በራሄል ጌቱ ( በስራዎቿ ) በኩል ነው ያገኘሁት ። ይህ ሰው ነው ደግሞ ከታምሩ አማረ ጋር ሆኖ ቤተልሔም ሸረፈዲንን ያገኛት ። ሁለቱ በፕሮዲዩሰርነት ባይከሰቱ ቤተልሔም ሸረፈዲን ቢያንስ በዚህ ጊዜ አትወለድም ። የጀርባ አቅሟን ባላውቅም የ10 ግጥም ፣ የ10 ዜማ ፣ የ10 ዜማዎች ቅንብር ፣ ሚክሲንግ እና ማስተሪንግ ክፍያን አትወጣውም ( ብዬ እገምታለሁ ) ። ከሁሉም በላይ ደግሞ ዘላለም ኩራባቸውን አታገኘውም ። ዘላለም ኩራባቸው ወደ ሙዚቃ ማምረት ስራ ሲገባ ከገንዘብ የነፍስ ጥሪ ትርፉን አስቦ እንደሚሆን አምናለሁ ። ካሁን ቀደም በተናጠል ሲያደርግ የነበረውን ሙያውንና ሙያተኛውን እንደ ታላቅ ወንድም አጋር የመሆን ዝንባሌውን ተቋማዊ ቅርጽ ሰጥቶት መምጣቱ ይመስለኛል ። ቤተልሔም እድለኛ ናት ። እነ ንዋይ ደበበ ፣ ሀመልማል አባተ ፣ ጸሐዬ ዮሀንስ እና ዘመንኞቻቸው በመጡበት መንገድ ነው የመጣችው ። ሌላም እድለኛነት ( ከችሎታ ጋር ) አላት ።እነ ጠረፍ ካሳሁን ፣ ራሄል ጌቱ ፣ ለምለም ኃ/ሚካኤል ፣ ዘቢባ ግርማ ተሰርተው የወጡበት " የኛ " ፕሮጀክት ፣ የእነ አይዳ አሸናፊ እጅም አርፎባታል ።
ከአስሩ የ " ደስተኛ " አልበም ስራዎች በተሸከመው ሀሳብ ( ለእኔ ) " ባለቤቴ " ን የሚያህልልኝ አላገኘሁም ። ለዚህ ዘፈን ከ " ባለቤቴ " ይልቅ " አትክልተኛው " ስምም ሆኖልኛል ። ምናልባት ግን " አትክልተኛው " ለዘፈን ርዕስነት ያንስ ( አይሆን ) እንደሆን አላውቅም ። ሙሉ ዘፈኑን ስንሰማው ገጸባሕሪዋ በምናቧ ከዋለለችለት የምናብ ባለቤቷ ይልቅ የሰው ያልሆነ ፣ ለሰው አዕምሮ " ሞኝ " የሚባል ፣ ለፍጽምና የቀረበ በዝናብም ፣ በጸሐይም ስራውን የማያስተጓጉል ፣ ብርሀን መርጦ የማይመጣ ፣ በጭለማ የማይሸሸግ ፣ የማግኘትም ፣ የማጣትም ጊዜ ወዳጅ ፣ እንደ አምላክ ያለ ብርቱ ሰው ነው ። ባለቤትነቱ ህልም ሲሆን ብርቱ አትክልተኝነቱ ግን እውን ነው ። ይህ ሰው ትትርናውና ቸርነቱ እንደ አምላክ ያለ ነው ። ከማንም ፣ ከምንም የማይጠብቅ ። መስጠት ብቻ የሆነ ። በአበቦቹ መሐል ብቻ አይደለም ያለው ። ልብ ባለበት ሁሉ ነው ።
" በዝናብ አካሉም በዶፉ እየረሰረሰ
የአትክልቶቹን ስር ሲያጠጣ የልምዱን ውሀ እያፈሰሰ
አሉት የማን ነው ጅል ያን አትክልተኛ
ሳቁበት እንደሞኝ ወይኔ
አላወቁም የእሱ ዝናብ መጣ ቀረ
ንፍገትን ለልቡ እንዳላስተማረ ።
*************************
አሰብኩት ከሆነ እንዲህ ለአትክልቱ
እንዴት መልካም ይሆን ለሚወዳት ሚስቱ "
ያለችውን ብርቱና ቸር ሰው ነው . . .
" ቢዘንብም ቢያካፋም ከጎኔ የማይጠፋ
እንደ ባለ አጸዱ ጽኑ ለመውደዱ
ሳላውቅህ ልንገርህ የነገ ውሀ አጣጬ
አርገኝ እንዳልከስም ፍቅርን ተጠምቼ "
እያለች ምኞቷን ፣ መሻቷን ፣ የወደፊት ህልሟን ትነግረናለች ። መልካምነት መስጠት ብቻ ሳይሆን መቀበልንም ይፈልጋል ። ምርጥ ዘር ምርጥ አፈርንም ይፈልጋል ። በተዘራበት ሁሉ አይበቅልም ። እንደ እሷ የሚረዳ ካልተገኘ ሌሎቹ እንዳሉት " የማነው ሞኝ ? " ያስብላል ።
በርዕሰ ጉዳይ ደረጃ የዚህ የወደድኩት ብርቱ አትክልተኛ ተቃራኒ ቢሆንም የእኔ ከ1ኛ - 3ኛ " ቻው ( ዎ ) " ነው ።
" አልነበረም ከዓይን የተሰወረ
መንገድህን ሳላየው መች ቀረ
ሰነባብቷል መንፈስህ ሸፍቷል
ልቤን ልብህ ቻው ካለው ቆይቷል ።
አልታወጀም እንጂ ፊትም የእኛ ነገር
የተለያየነው አብረን ሆነን ነበር ።
እንባዬ ተማጽኖህ እንዳያስታርቀን
ያለቀው ያኔ ነው ልብህ የሄደ ቀን ።
እያንዳንዱን ቀናት በእንባ እየሰፈርኩኝ
ቻው ስልህ ኖሬያለሁ እየሸራረፍኩኝ ።
ዛሬም ለበደልህ አረከኝ ጣል ጣል
ቻው ማለት ብቻ ነው የቀረኝ አንድ ቃል ። "
ይኽ መቸም በየፍቅር ጎጆው ፣ በየትዳር ማጀቱ ፣ በየጓደኝነቱና ወዳጅነቱ አደባባይ የሚታይ የወቅቱ እውነታ ነው ። በየግንኙነታችን " ቻው ማለት ብቻ ነው የቀረኝ አንድ ቃል " ። አብዛኛዎቻችን አንድ ላይ ቆመናል እንጂ አብረን አይደለንም ። " አንድ ላይ ብንሆንም ተለያይተናል " እንዳለው ድምጻዊው ። እግሮቻችን ብቻ አብረው ይጓዛሉ ፤ አካላችን አንድ ላይ ይታያል ፤ ነፍስ የሌለው ስጋ ነው ። አብረን ውለን እናድራለን ፤ በልባችን ግን ተለያይተናል ። አልታወቀን ይሆናል እንጂ እንደ ግልም ፣ እንደ ሀገርም እንዲህ ሆነናል ። ለዚህ ነው አሁን ያለንበት ላይ ያለነው ። ለዚህ ነው በየሰበቡ ሕይወት የሚታክተን ። ለዚህ ነው መኖር ትግል ፣ አብሮነት መተናነቅ የሚሆንብን ( የሆነብን ) ። የቤተልሔም ሸረፈዲን " ቻው " ለአንድ ተፈቃሪ ወንድ የተሰራም ቢሆን ሀሳቡ ግን እዚህ ድረስም የሚመጣ ነው ። ናቲ " ቃሉ ከዜማው ጋር ነው የመጣው " ያለውና ራሷን ድምጻዊቷን አስለቅሶ የተገለጠው " ቻው " ገና ብዙውን ልብ የሚነካ ስራ ይሆናል ።
" ልቤን " ን ላልወደው አስቤ ነበረ መሰለኝ ። የእድሜም ፣ የፍላጎትም ጉዳይ ሆኖ ፈጠን ላሉ ምቶች አልደነግጥ ሆኖ ይሆናል እንጂ ምን ሆኜ ነው ዜማው ፣ ምቱ ፣ በተለይ የድምጻዊቷ አዘፋፈን ከፍ ብሎ የታየበትን ይህን ስራ " ይቆየኝ " ያልኩት ? ባልወደውና ደጋግሜ ባልሰማው ይቆጨኝ ነበር ። ( ለነገሩ ካልወደድኩት ለምን ይቆጨኛል ? ) " ደስተኛ " ርዕስና ሀሳቡ ደስተኛ ካልሆነች ፣ " አልወድሽም " ከተባለችና ከተገፋች ገጸባህሪ የተገኘ ነው ። " ቢከፋም ፣ ቢለማም ባለኝ ደስተኛ ነኝ " ትላለች ። " አልወድሽም " ተብላና " ብትጎዘጉዝ አበባ ዛሬ አይረባ " ያለች ሴት ራሷን ማታለል ሳይሆን " ቢከፋም ፣ ቢለማም ባለኝ ደስተኛ ነኝ " ስትል ካዋጣትና ከተቻላት ያድርግላት ። ከእሷ እንባና የልብ ስብራት ምን ጉዳይ አለን ? ብቻ ከአፏ ሳይሆን ከልቧ ይሁን ።
" እንደ ውሀ መውረድ ፣ እንደ ጸሐይ መውጣት
እንደ ጊዜው መክነፍ ፣ እንደ አሸዋ መብዛት
እውነታ መሆኑን ቅንጣት ሳልጠረጥር
እኔስ አምነዋለሁ የልብህን ፍቅር "
ያለችበት " አካልዬ " ለረጋ ያለ ሙዚቃ አፍቃሪ ይሁነኝ ተብሎ የተቀመረ ስራ ነው ። በምርጤነት ከተቀበልኳቸው መካከል አንዱ ነው ።
አንደኛው ሙዚቃ አስተያየት መስጫ ውስጥ ገብቼ ሳነብ " የዚህ አልበም ትልቁ ችግሩ ውስጡ ያሉት ዘፈኖች 10 ብቻ መሆናቸው ነው " ሲል " አድናቆቱን " ገልጿል ። እኔም እንደዚያ ሆኖ ይሰማኛል ። ከአስሩ ሰባቱን ስራዎች በልዩ ሁኔታ ወድጃቸዋለሁ ። አንዱ የዋለልኩበትና ሁለቱ ደግሞ ልብ ያልሰጠኋቸው ናቸው ። ይህ በአንድ አለበም ውስጥ ከበቂ በላይ ስኬታማነት ነው ። ከብዙ ዓመት በኋላ ተሟልቶ ያገኙሁት ምርጤ ነው " ደስተኛ " አልበም ።
እዚህ አልበም ላይ ያለኝ አንድ ( ግላዊ ) ቅሬታ አስሩም ስራዎች የተቃራኒ ጾታ ፍቅር ላይ ብቻ ያተኮሩ መሆናቸው ነው ። እንዳይሆኑ የሚከለክል ደንብ የለም ። ፕሮዲዩሰሮቹ የቤተልሔምን እድሜና የፍቅር ጊዜዋን አስበው ያደረጉት ሊሆን ይችላል ። ያም ቢሆን በዚህ ውጥንቅጡ የወጣ የመከራ ጊዜ ፣ በብዙ ሰው ሰራሽና የአስተሳሰብ ሰንሰለት እግር ከወርች ታስረን መሔጃ ባጣንበት ዘመንና ሀገር ፣ ላለንበት ጊዜ ፣ ለስሜታችን ፣ ለህመማችን ፣ ለሰለለው ተስፋችን የሚሆን አንድ ስራ ልናጣ አይገባም ብዬ አስባለሁ ። ናቲና ምህረተአብ ለራሄል ጌቱ እንደሰጧት " ያገሬ ሰው " ያለ ስራ ቢመርቁልን እንዴት መልካም ነበረ ?
ከቀናት በፊት አስቴር አወቀ ( በድጋሚ ስራዎቿም ቢሆን ) በትንሿ ቤተልሔም ሸረፈዲን ላይ ተደርባ አልበሟን መልቀቋ አስፈርቶኝ ነበረ ። ይህን የመሰለ አልበም ፣ የ4 ዓመት የሚነገርና የማይነገር እልህ አስጨራሽ ድካም መና እንዳይቀር ሰግቼ ነበረ ። ስጋቴ ስጋት ብቻ ሆኖ ቀርቷል ። ቤተልሔም የዋርካው ጥላ ሳያርፍባት አልፋለች ። ገና ገና ትቀጥላለች ፤ ትቀጣጠላለች ።
10 days ago
የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ምላሽና ቀጣናዊ ፋይዳው
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ባለፉት አስርት ዓመታት በሰላም ማስከበር፣ በግጭት አፈታት፣ በኤሌክትሪክ ኃይል ወጪ ንግድ፣ በቀጣናዊ ትስስር እና በንግድ ትብብር ረገድ ያበረከተችው አስተዋጽኦ ለጎረቤቶቿ ብሎም ለቀጣናው የምትሰጠውን ከፍ ያለ ትኩረት ያሳያል።
ኢትዮጵያ በታሪኳ የትኛውንም ጎረቤት ሀገር ወርራ አታውቅም፡፡ ከጎረቤቶቿ ጋር ያላት ግንኙነት ሰላማዊና በትብብር ላይ የተመሰረተ ሆኖ ቆይቷል፡፡
ጎረቤቶቿ ሰላም በራቃቸው ጊዜ ሁሉ፣ ሰላም ለማስከበር ቀድማ በመገኘት ትታወቃለች፡፡ ይህንንም በደቡብ ሱዳን፣ በሱዳን፣ በሶማሊያ እንዲሁም ከጎረቤቶቿ ራቅ ብላም በላይቤሪያ፣ በሩዋንዳ፣ በኮንጎ እና በሴራሊዮን በተግባር አስመስክራለች፡፡
በአህጉር ደረጃ ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ቀንበር ሲማቅቁ የነበሩ አፍሪካውያን ወንድም እህቶች ነጻ ለመውጣት የሚያደርጉትን ጥረት በስልጠና፣ በሎጂስቲክስና በዲፕሎማሲ መስክ ጭምር መደገፏ አሌ የማይባል ሃቅ ነው፡፡
ኢትዮጵያ ዛሬም የልማት ትሩፋቷን ለብቻዋ ዕድገትና ለውጥ የምትጠቀም ሀገር አይደለችም፡፡ ይልቁንም ልማቷን እና ለውጧን በማጋራት እና ለጎረቤቶቿ አብሮ መለወጥ እየሰራች ትገኛለች፡፡
በአፍሪካ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል አምራች ከሆኑ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ፤ ለጅቡቲ፣ ኬንያ፣ ሱዳን እና ደቡብ ሱዳን ኤሌክትሪክ እየላከች ነው።
ይህ በአካባቢው የኢንዱስትሪ ልማት፣ የከተማ እድገት እና የህዝብ ኑሮ መሻሻል ላይ ቀጥተኛ አስተዋፅኦ እያደረገ ነው።
በንግድ ረገድም ኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና እና የአፍሪካ ህብረት "አጀንዳ 2063" የሚያስቀምጧቸውን የክልላዊ ውህደት ግቦች ለማሳካት የኢንዱስትሪ ፓርኮች፣ ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች፣ የድንበር ንግድ ማዕከላት እና የትራንስፖርት ኮሪደሮችን በማስፋፋት በቀጣናዊ ትስስር ማደግና መጠናከር ላይ ግዙፍ ኢንቨስትመንት እያካሄደች ነው።
ኢትዮጵያ ለጎረቤቶቿ ሰላምና ደህንነት፣ እድገትና ልማት አበክራ የሰራቻቸው ስራዎች ለቀጣናውና ለሀገራቱ ያላትን አዎንታዊ ሚና በግልፅ ያሳያል። ሀገሪቱ የባህር በር ጥያቄዋ ምላሽ ሲያገኝ ይህ ቀጣናዊ ገንቢ ሚናዋ በምን ያህል መጠን ሊያድግና ሊባዛ እንደሚችል ለመገመት አያዳግትም፡፡
በታሪክ አጋጣሚ የኢትዮጵያ ህዝብ ህጋዊ ስልጣን በሌለው አካል ህጋዊ የባሕር በር ባለቤትነቷን እንድታጣ ተደርጓል፡፡ የመደመር መንግሥት የተፈጸመውን ኢፍትሃዊና ታሪካዊ በደል በሰላማዊና ዲፕሎማሲያዊ መንገድ የማስመለስ ጥያቄ አቅርቦ የበርካታ ሃያላን ሀገራትን ድጋፍ አግኝቷል፡፡ ኢትዮጵያ በፍጥነት እያደገ ካለው ኢኮኖሚዋና የህዝብ ቁጥሯ አንጻር የባሕር በር አማራጭ ሊኖራት ይገባል።
በ60 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የባሕር በር እያለ ኢትዮጵያ ተዘግታ ትኑር የሚል ኢፍትሐዊነት ተቀባይነት የለውም።
የባሕር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያ የንግድ መውጫ መግቢያ ብቻ ሳይሆን፤ የኢኮኖሚ ዕድገት፣ የብሔራዊ ደህንነት እና የጂኦፖለቲካ ስትራቴጂ ቁልፍ ጥያቄ በመሆኑ ጥያቄዋ መልስ እስኪያገኝ አበክራ ትሰራለች፡፡
ኢትዮጵያ የባህር በር ማግኘቷ ጥቅሙ ለእርሷ ብቻ አይደለም። በአፍሪካ ቀንድ እና በጎረቤት ሀገራት ዘንድ ከፍ ያለ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የመፍጠር ሚና ይኖረዋል፡፡
በአካባቢው የንግድ ኮሪደሮች ስለሚፈጠሩ የወደብ አገልግሎት እንዲስፋፋ፣ የተለያዩ የመሰረተ ልማት አውታሮች እንዲገነቡ በማድረግ የንግድ ትስስርና አዳዲስ የስራ ዕድሎች ለመፍጠር ያስችላል።
በተጨማሪም ኢትዮጵያ ከታዳሽ ኃይል የምታመነጨው ኤሌክትሪክ ለቀጣናው በበቂ ሁኔታ ማቅረቧ ኢንዱስትሪዎችን ለማስፋፋትና የካርቦን ልቀትን ለመቀነስ ይረዳል።
ከዚህ ባሻገር የቀጣናዊ ሰላምና ጸጥታን በተመለከተ የጋራ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እያደገ ሲመጣ በሀገራት መካከል ከግጭት ይልቅ ትብብር እንዲጨምር ያደርጋል። ሀገራት በንግድ፣ በኢንቨስትመንት እና በመሠረተ ልማት በተጠናከረ ሁኔታ ሲተሳሰሩ ሰላምን የመጠበቅ ፍላጎታቸውም በዛው ልክ ይጨምራል።
የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ምላሽ ማግኘት የአፍሪካ ህብረት "አጀንዳ 2063" የሚጠይቀውን ቀጣናዊ ትስስር ለማጠናከር፣ የነፃ ንግድ ቀጣና ለመመስረት እና የመሠረተ ልማት ትስስርን ለማሳካት ጠንካራ መሠረት ለመጣል ያግዛል።
በመሆኑም የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ አፋጣኝ መልስ እንዲያገኝ ለማድረግ ሀገራት፣ ዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊ እና ቀጣናዊ ተቋማት ድጋፋቸውን ሊያጠናክሩ ይገባል፡፡
በቴዎድሮስ ሳህለ
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ባለፉት አስርት ዓመታት በሰላም ማስከበር፣ በግጭት አፈታት፣ በኤሌክትሪክ ኃይል ወጪ ንግድ፣ በቀጣናዊ ትስስር እና በንግድ ትብብር ረገድ ያበረከተችው አስተዋጽኦ ለጎረቤቶቿ ብሎም ለቀጣናው የምትሰጠውን ከፍ ያለ ትኩረት ያሳያል።
ኢትዮጵያ በታሪኳ የትኛውንም ጎረቤት ሀገር ወርራ አታውቅም፡፡ ከጎረቤቶቿ ጋር ያላት ግንኙነት ሰላማዊና በትብብር ላይ የተመሰረተ ሆኖ ቆይቷል፡፡
ጎረቤቶቿ ሰላም በራቃቸው ጊዜ ሁሉ፣ ሰላም ለማስከበር ቀድማ በመገኘት ትታወቃለች፡፡ ይህንንም በደቡብ ሱዳን፣ በሱዳን፣ በሶማሊያ እንዲሁም ከጎረቤቶቿ ራቅ ብላም በላይቤሪያ፣ በሩዋንዳ፣ በኮንጎ እና በሴራሊዮን በተግባር አስመስክራለች፡፡
በአህጉር ደረጃ ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ቀንበር ሲማቅቁ የነበሩ አፍሪካውያን ወንድም እህቶች ነጻ ለመውጣት የሚያደርጉትን ጥረት በስልጠና፣ በሎጂስቲክስና በዲፕሎማሲ መስክ ጭምር መደገፏ አሌ የማይባል ሃቅ ነው፡፡
ኢትዮጵያ ዛሬም የልማት ትሩፋቷን ለብቻዋ ዕድገትና ለውጥ የምትጠቀም ሀገር አይደለችም፡፡ ይልቁንም ልማቷን እና ለውጧን በማጋራት እና ለጎረቤቶቿ አብሮ መለወጥ እየሰራች ትገኛለች፡፡
በአፍሪካ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል አምራች ከሆኑ ሀገራት መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ፤ ለጅቡቲ፣ ኬንያ፣ ሱዳን እና ደቡብ ሱዳን ኤሌክትሪክ እየላከች ነው።
ይህ በአካባቢው የኢንዱስትሪ ልማት፣ የከተማ እድገት እና የህዝብ ኑሮ መሻሻል ላይ ቀጥተኛ አስተዋፅኦ እያደረገ ነው።
በንግድ ረገድም ኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና እና የአፍሪካ ህብረት "አጀንዳ 2063" የሚያስቀምጧቸውን የክልላዊ ውህደት ግቦች ለማሳካት የኢንዱስትሪ ፓርኮች፣ ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖች፣ የድንበር ንግድ ማዕከላት እና የትራንስፖርት ኮሪደሮችን በማስፋፋት በቀጣናዊ ትስስር ማደግና መጠናከር ላይ ግዙፍ ኢንቨስትመንት እያካሄደች ነው።
ኢትዮጵያ ለጎረቤቶቿ ሰላምና ደህንነት፣ እድገትና ልማት አበክራ የሰራቻቸው ስራዎች ለቀጣናውና ለሀገራቱ ያላትን አዎንታዊ ሚና በግልፅ ያሳያል። ሀገሪቱ የባህር በር ጥያቄዋ ምላሽ ሲያገኝ ይህ ቀጣናዊ ገንቢ ሚናዋ በምን ያህል መጠን ሊያድግና ሊባዛ እንደሚችል ለመገመት አያዳግትም፡፡
በታሪክ አጋጣሚ የኢትዮጵያ ህዝብ ህጋዊ ስልጣን በሌለው አካል ህጋዊ የባሕር በር ባለቤትነቷን እንድታጣ ተደርጓል፡፡ የመደመር መንግሥት የተፈጸመውን ኢፍትሃዊና ታሪካዊ በደል በሰላማዊና ዲፕሎማሲያዊ መንገድ የማስመለስ ጥያቄ አቅርቦ የበርካታ ሃያላን ሀገራትን ድጋፍ አግኝቷል፡፡ ኢትዮጵያ በፍጥነት እያደገ ካለው ኢኮኖሚዋና የህዝብ ቁጥሯ አንጻር የባሕር በር አማራጭ ሊኖራት ይገባል።
በ60 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የባሕር በር እያለ ኢትዮጵያ ተዘግታ ትኑር የሚል ኢፍትሐዊነት ተቀባይነት የለውም።
የባሕር በር ጉዳይ ለኢትዮጵያ የንግድ መውጫ መግቢያ ብቻ ሳይሆን፤ የኢኮኖሚ ዕድገት፣ የብሔራዊ ደህንነት እና የጂኦፖለቲካ ስትራቴጂ ቁልፍ ጥያቄ በመሆኑ ጥያቄዋ መልስ እስኪያገኝ አበክራ ትሰራለች፡፡
ኢትዮጵያ የባህር በር ማግኘቷ ጥቅሙ ለእርሷ ብቻ አይደለም። በአፍሪካ ቀንድ እና በጎረቤት ሀገራት ዘንድ ከፍ ያለ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የመፍጠር ሚና ይኖረዋል፡፡
በአካባቢው የንግድ ኮሪደሮች ስለሚፈጠሩ የወደብ አገልግሎት እንዲስፋፋ፣ የተለያዩ የመሰረተ ልማት አውታሮች እንዲገነቡ በማድረግ የንግድ ትስስርና አዳዲስ የስራ ዕድሎች ለመፍጠር ያስችላል።
በተጨማሪም ኢትዮጵያ ከታዳሽ ኃይል የምታመነጨው ኤሌክትሪክ ለቀጣናው በበቂ ሁኔታ ማቅረቧ ኢንዱስትሪዎችን ለማስፋፋትና የካርቦን ልቀትን ለመቀነስ ይረዳል።
ከዚህ ባሻገር የቀጣናዊ ሰላምና ጸጥታን በተመለከተ የጋራ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እያደገ ሲመጣ በሀገራት መካከል ከግጭት ይልቅ ትብብር እንዲጨምር ያደርጋል። ሀገራት በንግድ፣ በኢንቨስትመንት እና በመሠረተ ልማት በተጠናከረ ሁኔታ ሲተሳሰሩ ሰላምን የመጠበቅ ፍላጎታቸውም በዛው ልክ ይጨምራል።
የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ምላሽ ማግኘት የአፍሪካ ህብረት "አጀንዳ 2063" የሚጠይቀውን ቀጣናዊ ትስስር ለማጠናከር፣ የነፃ ንግድ ቀጣና ለመመስረት እና የመሠረተ ልማት ትስስርን ለማሳካት ጠንካራ መሠረት ለመጣል ያግዛል።
በመሆኑም የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ አፋጣኝ መልስ እንዲያገኝ ለማድረግ ሀገራት፣ ዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊ እና ቀጣናዊ ተቋማት ድጋፋቸውን ሊያጠናክሩ ይገባል፡፡
በቴዎድሮስ ሳህለ
10 days ago
የቲክቶኮ ድምቀት በመድረክ ትያትር መጣ!
ቴዎድሮስ ሸዋንግዛው በኢትዮጵያ የድራማ ታሪክ ውስጥ በአዲስ አይነት መንገድ የመጣ ምርጥ ተዋናይ ደራሲና አዘጋጅም ጭምር ነው።
( በአሌክስ ዘመላክ)
ፍላሎት ፣ ትራፊኳና ከአፍ ሰመያመልጥ የተሰኙ ፊልሞች ላይ በመሪ ተዋናይነት ተሳትፏል እንዲሁም አዲስ ድባብ ፤ደባል አማች፤የእቴጌ ማጀት ፤ጎረቤታሞቹ የተሰኙ ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማዎች የተወሰኑት ላይ በፅሁፍ በዝግጅት የተሳተፈ ሲሆን ሁሉም ላይ የትወና አቅሙን አሳይቷል ።
ቴዎድሮስ ከቅርብ ጊዜአት ወዲህ ዘመኑ በፈጠረለት የ ቲክቶክ ፕላትፎርም በመጠቀም እጅግ በተዋበ መንገድ ማህበራዊ፤ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዩችን በማንሳት በድራማ መልክ በማቅረብ ተወዳጅነትን እያተረፈ ይገኛል።
ባሳለፍነው ሰኞ ሃምሌ 13/2018 ዓም በአለም ሲኒማ የተመረቀው መልቲ ትያትር ላይ ከሌሎች ምርጥ ተዋናዮች ጋር በመሆን ድንቅ ብቃቱን አሳይቷል ።የሰውነቱ ቀጠን ማለት መድረክ ላይ እንዳይታይ አላገደውም ይልቁንም መድረኩ ላይ ገዝፎ ይታያል ።
የኮሜዲ ዘውግ ያለው "መልቲ" ትያትር በመልቲ የትያትር ቡድን ተደርሶ በስንታየሁ ታዬ (ፋቡላ) የተዘጋጀ ነው።
የታሪክ ማጠንጠኛውን በዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ላይ ያደረገው ትያትሩ ከአመታት በፊት በአዲስ አበባ ቴአርትና ባህል አዳራሽ-ማዘጋጃ ቤት ለዕይታ በቅቶ በተመልካቾች ዘንድ ከፍ ያለ አድናቆትና ተወዳጅነትን ማግኘት ችሎም ነበር።
ዘመኑን በሚመጥንና በአዳዲስ ሀሳቦች ዳግም የተዘጋጀው ትያትሩ ምትኩ በቀለ፣ ኤልሻዳይ ከበደ፣ ሱራፌል ብስራት፣ ቴዎድሮስ ሸዋንግዛው፣ አቤል ሰለሞን ፣ እየሩሳሌም ነስሩና ፌቨን ኪዳነ ማሪያም ይተውኑበታል።
መልቲ ዘወትር ሰኞ በ 12:00 ሰዓት በዓለም ሲኒማ ለዕይታ ይበቃል።
ቴዎድሮስ ሸዋንግዛው በኢትዮጵያ የድራማ ታሪክ ውስጥ በአዲስ አይነት መንገድ የመጣ ምርጥ ተዋናይ ደራሲና አዘጋጅም ጭምር ነው።
( በአሌክስ ዘመላክ)
ፍላሎት ፣ ትራፊኳና ከአፍ ሰመያመልጥ የተሰኙ ፊልሞች ላይ በመሪ ተዋናይነት ተሳትፏል እንዲሁም አዲስ ድባብ ፤ደባል አማች፤የእቴጌ ማጀት ፤ጎረቤታሞቹ የተሰኙ ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማዎች የተወሰኑት ላይ በፅሁፍ በዝግጅት የተሳተፈ ሲሆን ሁሉም ላይ የትወና አቅሙን አሳይቷል ።
ቴዎድሮስ ከቅርብ ጊዜአት ወዲህ ዘመኑ በፈጠረለት የ ቲክቶክ ፕላትፎርም በመጠቀም እጅግ በተዋበ መንገድ ማህበራዊ፤ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዩችን በማንሳት በድራማ መልክ በማቅረብ ተወዳጅነትን እያተረፈ ይገኛል።
ባሳለፍነው ሰኞ ሃምሌ 13/2018 ዓም በአለም ሲኒማ የተመረቀው መልቲ ትያትር ላይ ከሌሎች ምርጥ ተዋናዮች ጋር በመሆን ድንቅ ብቃቱን አሳይቷል ።የሰውነቱ ቀጠን ማለት መድረክ ላይ እንዳይታይ አላገደውም ይልቁንም መድረኩ ላይ ገዝፎ ይታያል ።
የኮሜዲ ዘውግ ያለው "መልቲ" ትያትር በመልቲ የትያትር ቡድን ተደርሶ በስንታየሁ ታዬ (ፋቡላ) የተዘጋጀ ነው።
የታሪክ ማጠንጠኛውን በዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ላይ ያደረገው ትያትሩ ከአመታት በፊት በአዲስ አበባ ቴአርትና ባህል አዳራሽ-ማዘጋጃ ቤት ለዕይታ በቅቶ በተመልካቾች ዘንድ ከፍ ያለ አድናቆትና ተወዳጅነትን ማግኘት ችሎም ነበር።
ዘመኑን በሚመጥንና በአዳዲስ ሀሳቦች ዳግም የተዘጋጀው ትያትሩ ምትኩ በቀለ፣ ኤልሻዳይ ከበደ፣ ሱራፌል ብስራት፣ ቴዎድሮስ ሸዋንግዛው፣ አቤል ሰለሞን ፣ እየሩሳሌም ነስሩና ፌቨን ኪዳነ ማሪያም ይተውኑበታል።
መልቲ ዘወትር ሰኞ በ 12:00 ሰዓት በዓለም ሲኒማ ለዕይታ ይበቃል።
10 days ago
የቲክቶኮ ድምቀት በመድረክ ትያትር መጣ!
ቴዎድሮስ ሸዋንግዛው በኢትዮጵያ የድራማ ታሪክ ውስጥ በአዲስ አይነት መንገድ የመጣ ምርጥ ተዋናይ ደራሲና አዘጋጅም ጭምር ነው።
( በአሌክስ ዘመላክ)
ፍላሎት ፣ ትራፊኳና ከአፍ ሰመያመልጥ የተሰኙ ፊልሞች ላይ በመሪ ተዋናይነት ተሳትፏል እንዲሁም አዲስ ድባብ ፤ደባል አማች፤የእቴጌ ማጀት ፤ጎረቤታሞቹ የተሰኙ ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማዎች የተወሰኑት ላይ በፅሁፍ በዝግጅት የተሳተፈ ሲሆን ሁሉም ላይ የትወና አቅሙን አሳይቷል ።
ቴዎድሮስ ከቅርብ ጊዜአት ወዲህ ዘመኑ በፈጠረለት የ ቲክቶክ ፕላትፎርም በመጠቀም እጅግ በተዋበ መንገድ ማህበራዊ፤ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዩችን በማንሳት በድራማ መልክ በማቅረብ ተወዳጅነትን እያተረፈ ይገኛል።
ባሳለፍነው ሰኞ ሃምሌ 13/2018 ዓም በአለም ሲኒማ የተመረቀው መልቲ ትያትር ላይ ከሌሎች ምርጥ ተዋናዮች ጋር በመሆን ድንቅ ብቃቱን አሳይቷል ።የሰውነቱ ቀጠን ማለት መድረክ ላይ እንዳይታይ አላገደውም ይልቁንም መድረኩ ላይ ገዝፎ ይታያል ።
የኮሜዲ ዘውግ ያለው "መልቲ" ትያትር በመልቲ የትያትር ቡድን ተደርሶ በስንታየሁ ታዬ (ፋቡላ) የተዘጋጀ ነው።
የታሪክ ማጠንጠኛውን በዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ላይ ያደረገው ትያትሩ ከአመታት በፊት በአዲስ አበባ ቴአርትና ባህል አዳራሽ-ማዘጋጃ ቤት ለዕይታ በቅቶ በተመልካቾች ዘንድ ከፍ ያለ አድናቆትና ተወዳጅነትን ማግኘት ችሎም ነበር።
ዘመኑን በሚመጥንና በአዳዲስ ሀሳቦች ዳግም የተዘጋጀው ትያትሩ ምትኩ በቀለ፣ ኤልሻዳይ ከበደ፣ ሱራፌል ብስራት፣ ቴዎድሮስ ሸዋንግዛው፣ አቤል ሰለሞን ፣ እየሩሳሌም ነስሩና ፌቨን ኪዳነ ማሪያም ይተውኑበታል።
መልቲ ዘወትር ሰኞ በ 12:00 ሰዓት በዓለም ሲኒማ ለዕይታ ይበቃል።
ቴዎድሮስ ሸዋንግዛው በኢትዮጵያ የድራማ ታሪክ ውስጥ በአዲስ አይነት መንገድ የመጣ ምርጥ ተዋናይ ደራሲና አዘጋጅም ጭምር ነው።
( በአሌክስ ዘመላክ)
ፍላሎት ፣ ትራፊኳና ከአፍ ሰመያመልጥ የተሰኙ ፊልሞች ላይ በመሪ ተዋናይነት ተሳትፏል እንዲሁም አዲስ ድባብ ፤ደባል አማች፤የእቴጌ ማጀት ፤ጎረቤታሞቹ የተሰኙ ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማዎች የተወሰኑት ላይ በፅሁፍ በዝግጅት የተሳተፈ ሲሆን ሁሉም ላይ የትወና አቅሙን አሳይቷል ።
ቴዎድሮስ ከቅርብ ጊዜአት ወዲህ ዘመኑ በፈጠረለት የ ቲክቶክ ፕላትፎርም በመጠቀም እጅግ በተዋበ መንገድ ማህበራዊ፤ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዩችን በማንሳት በድራማ መልክ በማቅረብ ተወዳጅነትን እያተረፈ ይገኛል።
ባሳለፍነው ሰኞ ሃምሌ 13/2018 ዓም በአለም ሲኒማ የተመረቀው መልቲ ትያትር ላይ ከሌሎች ምርጥ ተዋናዮች ጋር በመሆን ድንቅ ብቃቱን አሳይቷል ።የሰውነቱ ቀጠን ማለት መድረክ ላይ እንዳይታይ አላገደውም ይልቁንም መድረኩ ላይ ገዝፎ ይታያል ።
የኮሜዲ ዘውግ ያለው "መልቲ" ትያትር በመልቲ የትያትር ቡድን ተደርሶ በስንታየሁ ታዬ (ፋቡላ) የተዘጋጀ ነው።
የታሪክ ማጠንጠኛውን በዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ላይ ያደረገው ትያትሩ ከአመታት በፊት በአዲስ አበባ ቴአርትና ባህል አዳራሽ-ማዘጋጃ ቤት ለዕይታ በቅቶ በተመልካቾች ዘንድ ከፍ ያለ አድናቆትና ተወዳጅነትን ማግኘት ችሎም ነበር።
ዘመኑን በሚመጥንና በአዳዲስ ሀሳቦች ዳግም የተዘጋጀው ትያትሩ ምትኩ በቀለ፣ ኤልሻዳይ ከበደ፣ ሱራፌል ብስራት፣ ቴዎድሮስ ሸዋንግዛው፣ አቤል ሰለሞን ፣ እየሩሳሌም ነስሩና ፌቨን ኪዳነ ማሪያም ይተውኑበታል።
መልቲ ዘወትር ሰኞ በ 12:00 ሰዓት በዓለም ሲኒማ ለዕይታ ይበቃል።
11 days ago
በካናዳ የሚኖሩ የዳያስፖራ አባላት በኢትዮጵያ ኢንቨስት የማድረግ ፍላጎት እንዳላቸው ገለፁ
**********************
በካናዳ ካልጋሪና ብሩክስ ከተሞች የሚኖሩ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አባላት በሀገራቸው ባሉ ሰፊ የኢንቨስትመንት አማራጮች ላይ ተሳትፏቸውን ለማሳደግና ተጠቃሚ ለመሆን ያላቸውን ፍላጎት ገልፀዋል።
በካናዳ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ባዘጋጀው የዳያስፖራ መድረክ ላይ፣ መንግሥት ለውጭ ነዋሪዎች ያመቻቻቸው አዳዲስ የኢንቨስትመንት ዕድሎች፣ የህግ ማዕቀፎች እና የአገልግሎት ማሻሻያዎች ላይ ሰፊ ምክክር ተደርጓል።
በውይይቱ ላይ የተሳተፉት የዳያስፖራ አባላት፣ መንግሥት የዜጎችን ተሳትፎ ለማጠናከር እያደረጋቸው ያሉትን የፖሊሲ ማሻሻያዎች አድንቀዋል።
በተለይም በአሁኑ ወቅት የኮሪደር ልማትን ጨምሮ በመላ ኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ሀገሪቱን ወደ ተሻለ የእድገት ምዕራፍ እያሸጋገሯት መሆኑን ጠቅሰው፤ በተጨማሪም የ«መሶብ» የአንድ ማዕከል አገልግሎት ስራ መጀመር መንግሥት አሰራርን ለማዘመንና ለማቀላጠፍ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ትልቅ እርምጃ መሆኑን አውስተዋል።
በካናዳ የኢትዮጵያ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ቴዎድሮስ ግርማ በበኩላቸው፣ ዳያስፖራው በሀገሩ ሁለንተናዊ ልማት ላይ የድርሻውን እንዲወጣ መንግሥት የፈጠራቸውን ምቹ መደላድሎች በዝርዝር አብራርተዋል።
መንግሥት የዳያስፖራውን ጥያቄዎች መነሻ በማድረግ የአገልግሎት አሰጣጡን ይበልጥ ዘመናዊ፣ ግልጽና ቀልጣፋ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን መግለፃቸውን በካናዳ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ አመልክቷል።
አምባሳደሩ አክለውም፣ የዳያስፖራ አባላት በመካከላቸው ያሉ ልዩነቶችን ወደ ጎን በመተው፣ እውቀትና ገንዘባቸውን አቀናጅተው በትላልቅ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ላይ በጋራ እንዲሰማሩ ጥሪ አቅርበዋል።
**********************
በካናዳ ካልጋሪና ብሩክስ ከተሞች የሚኖሩ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አባላት በሀገራቸው ባሉ ሰፊ የኢንቨስትመንት አማራጮች ላይ ተሳትፏቸውን ለማሳደግና ተጠቃሚ ለመሆን ያላቸውን ፍላጎት ገልፀዋል።
በካናዳ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ባዘጋጀው የዳያስፖራ መድረክ ላይ፣ መንግሥት ለውጭ ነዋሪዎች ያመቻቻቸው አዳዲስ የኢንቨስትመንት ዕድሎች፣ የህግ ማዕቀፎች እና የአገልግሎት ማሻሻያዎች ላይ ሰፊ ምክክር ተደርጓል።
በውይይቱ ላይ የተሳተፉት የዳያስፖራ አባላት፣ መንግሥት የዜጎችን ተሳትፎ ለማጠናከር እያደረጋቸው ያሉትን የፖሊሲ ማሻሻያዎች አድንቀዋል።
በተለይም በአሁኑ ወቅት የኮሪደር ልማትን ጨምሮ በመላ ኢትዮጵያ እየተከናወኑ ያሉ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ሀገሪቱን ወደ ተሻለ የእድገት ምዕራፍ እያሸጋገሯት መሆኑን ጠቅሰው፤ በተጨማሪም የ«መሶብ» የአንድ ማዕከል አገልግሎት ስራ መጀመር መንግሥት አሰራርን ለማዘመንና ለማቀላጠፍ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ትልቅ እርምጃ መሆኑን አውስተዋል።
በካናዳ የኢትዮጵያ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ቴዎድሮስ ግርማ በበኩላቸው፣ ዳያስፖራው በሀገሩ ሁለንተናዊ ልማት ላይ የድርሻውን እንዲወጣ መንግሥት የፈጠራቸውን ምቹ መደላድሎች በዝርዝር አብራርተዋል።
መንግሥት የዳያስፖራውን ጥያቄዎች መነሻ በማድረግ የአገልግሎት አሰጣጡን ይበልጥ ዘመናዊ፣ ግልጽና ቀልጣፋ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን መግለፃቸውን በካናዳ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ አመልክቷል።
አምባሳደሩ አክለውም፣ የዳያስፖራ አባላት በመካከላቸው ያሉ ልዩነቶችን ወደ ጎን በመተው፣ እውቀትና ገንዘባቸውን አቀናጅተው በትላልቅ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ላይ በጋራ እንዲሰማሩ ጥሪ አቅርበዋል።
12 days ago
የዳግማዊ ቴዎድሮስ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የቀድሞ መምህራን የምስጋና ፕሮግራም ተካሄደ
#ethiopia | በደብረታቦር ከተማ የሚገኘው የዳግማዊ ቴዎድሮስ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የቀድሞ ተማሪዎች፣ በትውልድ ግንባታ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የቀድሞ መምህራኖቻቸው የምስጋናና የእውቅና መርሃ ግብር አካሂደዋል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የመንግሥት ኃላፊዎች፣ የቀድሞ መምህራን፣ የቀድሞ ተማሪዎችና ሌሎች የተጋበዙ እንግዶች ተገኝተዋል።
የፕሮግራሙ አዘጋጅ ኮሚቴ አስተባባሪና በደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ የጉናና ጣና ልማት ዳይሬክተር ዶክተር ጥላሁን አዱኛ፣ በ1962 ዓ.ም. ትምህርት ቤቱ ከመከፈቱ በፊት የደብረታቦርና አካባቢው ተማሪዎች ለ2ኛ ደረጃ ትምህርት ወደ ሌሎች ከተሞች በመሄድ ብዙ ችግር እንደነበረባቸው አስታውሰው፣ ትምህርት ቤቱ ከተከፈተ በኋላ ይህን እንግልት ማስቀረቱን ገልጸዋል።
መምህራን የአገር ባለውለታዎች እንደሆኑ ጠቅሰው፣ ፕሮግራሙ የቀድሞ መምህራኑን "አለንላችሁ" ለማለት፣ ያበረከቱትን አስተዋጽኦ ለመዘከርና የአሁኑን መምህራን ለማበረታታት መዘጋጀቱን አስረድተዋል።
የደብረታቦር ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ሀይለኢየሱስ ሰለሞን በበኩላቸው፣ መምህራን ጥሩ ዜጋን በመፍጠር ለአገር እድገት የማይተካ ሚና እንዳበረከቱ ገልጸው፣ እንደዚህ ዓይነቱ የምስጋና መርሃ ግብር በቀጣይም ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል። የከተማ አስተዳደሩም የቀድሞ መምህራንን በተለያዩ መንገዶች ለመደገፍ ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል።
የከተማው ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ እየበሩ አእምሮ በበኩላቸው፣ የቀድሞ ተማሪዎች መምህራኖቻቸውን በዚህ መልኩ ማመስገናቸው አርአያ የሚሆን ተግባር መሆኑን ጠቅሰው፣ የትውልድ ግንባታ ሥራ በትብብር ሊጠናከር እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ተመስጋኝ የነበሩት የቀድሞ መምህራንም፣ ተማሪዎቻቸው ወደ ተሻለ ደረጃ ደርሰው ዛሬ አስታውሰው በማክበራቸው ታላቅ ደስታ እንደተሰማቸው ገልጸው፣ የአሁኑ መምህራንም ስነ-ምግባር የታነፀና ለአገሩ የሚጠቅም ትውልድ ለማፍራት ተግተው እንዲሰሩ አሳስበዋል።
በፕሮግራሙ መጨረሻ ለቀድሞ መምህራን የእውቅና ሰርተፍኬትና የገንዘብ ሽልማት የተበረከተ ሲሆን፣ የመርሃ ግብሩ ስኬት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላትም እውቅናና ሽልማት ተሰጥቷቸዋል።
ደብረታቦር ኮሙኒኬሽን
#ethiopia | በደብረታቦር ከተማ የሚገኘው የዳግማዊ ቴዎድሮስ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የቀድሞ ተማሪዎች፣ በትውልድ ግንባታ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የቀድሞ መምህራኖቻቸው የምስጋናና የእውቅና መርሃ ግብር አካሂደዋል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የመንግሥት ኃላፊዎች፣ የቀድሞ መምህራን፣ የቀድሞ ተማሪዎችና ሌሎች የተጋበዙ እንግዶች ተገኝተዋል።
የፕሮግራሙ አዘጋጅ ኮሚቴ አስተባባሪና በደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ የጉናና ጣና ልማት ዳይሬክተር ዶክተር ጥላሁን አዱኛ፣ በ1962 ዓ.ም. ትምህርት ቤቱ ከመከፈቱ በፊት የደብረታቦርና አካባቢው ተማሪዎች ለ2ኛ ደረጃ ትምህርት ወደ ሌሎች ከተሞች በመሄድ ብዙ ችግር እንደነበረባቸው አስታውሰው፣ ትምህርት ቤቱ ከተከፈተ በኋላ ይህን እንግልት ማስቀረቱን ገልጸዋል።
መምህራን የአገር ባለውለታዎች እንደሆኑ ጠቅሰው፣ ፕሮግራሙ የቀድሞ መምህራኑን "አለንላችሁ" ለማለት፣ ያበረከቱትን አስተዋጽኦ ለመዘከርና የአሁኑን መምህራን ለማበረታታት መዘጋጀቱን አስረድተዋል።
የደብረታቦር ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ሀይለኢየሱስ ሰለሞን በበኩላቸው፣ መምህራን ጥሩ ዜጋን በመፍጠር ለአገር እድገት የማይተካ ሚና እንዳበረከቱ ገልጸው፣ እንደዚህ ዓይነቱ የምስጋና መርሃ ግብር በቀጣይም ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል። የከተማ አስተዳደሩም የቀድሞ መምህራንን በተለያዩ መንገዶች ለመደገፍ ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል።
የከተማው ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ እየበሩ አእምሮ በበኩላቸው፣ የቀድሞ ተማሪዎች መምህራኖቻቸውን በዚህ መልኩ ማመስገናቸው አርአያ የሚሆን ተግባር መሆኑን ጠቅሰው፣ የትውልድ ግንባታ ሥራ በትብብር ሊጠናከር እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
ተመስጋኝ የነበሩት የቀድሞ መምህራንም፣ ተማሪዎቻቸው ወደ ተሻለ ደረጃ ደርሰው ዛሬ አስታውሰው በማክበራቸው ታላቅ ደስታ እንደተሰማቸው ገልጸው፣ የአሁኑ መምህራንም ስነ-ምግባር የታነፀና ለአገሩ የሚጠቅም ትውልድ ለማፍራት ተግተው እንዲሰሩ አሳስበዋል።
በፕሮግራሙ መጨረሻ ለቀድሞ መምህራን የእውቅና ሰርተፍኬትና የገንዘብ ሽልማት የተበረከተ ሲሆን፣ የመርሃ ግብሩ ስኬት አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላትም እውቅናና ሽልማት ተሰጥቷቸዋል።
ደብረታቦር ኮሙኒኬሽን
Sponsored by
Surafel
13 days ago
በሽብር ወንጀል የተከሰሱት እነ አቶ ክርስቲያን ታደለ እና 52 ተከሳሾች የተከሰሱበትን ክስ ይከላከሉ ወይስ በነጻ ይሰናበቱ የሚለው ጉዳይ ላይ ብይን ሳይሰጥበት በድጋሚ ተራዘመ።
በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙት የቀድሞ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል አቶ ክርስቲያን ታደለ፣ የቀድሞ የአማራ ክልል ምክር ቤት አባል አቶ ዮሐንስ ቧያለው እንዲሁም ዶ/ር ካሳ ተሻገር፣ ዶ/ር ጫኔ ከበደን ጨምሮ በድምሩ 52 ተከሳሾች የፍርድ ውሳኔ ሳያገኙ ላለፉት ሦስት ዓመታት ገደማ በእስር ላይ ይገኛሉ።
ክሱ የተመሠረተው መጋቢት 2016 ዓ.ም ሲሆን፣ ጉዳዩ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሕገ መንግሥትና ፀረ-ሽብር ወንጀሎች ችሎት እየታየ ይገኛል።
ተከሳሾቹ በተለያዩ ወቅቶች ካለባቸው የጤና ችግር ጋር በተያያዘ፣ ከቤተሰብ ጥየቃ፣ ከሰብአዊ መብት ሁኔታ፣ እና ሌሎችም ደረሰብን በማለት በሚያቀርቧቸው ቅሬታዎች ዙሪያ ችሎቱ የተለያዩ ቀጠሮዎችን በመስጠት ጉዳያቸውን ሲመለከት የቆየ በመሆኑ የተከሰሱበትን ዋናው የክስ መዝገብን የማየት ሂደት በተለዋጭ ቀጠሮዎች ከ 4 ጊዜ በላይ ሲራዘም ቆይቷል።
በዋናው የሽብር ክስ መዝገብ ላይ ብይን ለመስጠት ቀደም ሲል ለሐምሌ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ቀጠሮ ተይዞ የነበረ ቢሆንም፣ ችሎቱ ጉዳዩን በተጨማሪ ዝግጅት አጠቃሎ ለማቅረብ ለዛሬ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ለተለዋጭ ቀጠሮ አስተላልፎት ነበር።
ችሎቱ ዛሬ የሚሰጠው ብይን ተከሳሾቹ የተከሰሱበትን ክስ ይከላከሉ ወይስ የነጻ ይሰናበቱ የሚለውን ጥያቄ የሚመልስ እንደሚሆን ቢጠበቅም በድጋሚ በተለዋጭ ቀጠሮ ለ ጥቅምት 6/2019 ዓም በመስጠት ውሳኔውን አራዝሞታል።
ፍርድ ቤቱ ብይኑን ማጠናቀቁን ገልጾ ነበር፤ ይሁን እንጂ የተወሰኑ ተከሳሾች በችሎት ባለመገኘታቸው ብይኑን ለንባብ ማቅረብ እንደማይችል በመግለጽ ንባቡን አላደረገም።
በዛሬው ችሎት ፍርድ ቤቱ ያሰማዋል ተብሎ ሲጠበቅ ከነበረው ብይን በተጨማሪ ከተከሳሾቹ አንዱ ከሆኑት ከዶ/ር ካሳ ተሻገር እና ከጋዜጠኛ ቴዎድሮስ ስልክ ቁጥር ጋር በተያያዘ ቁጥራቸውን ሌላ ሰው እየተጠቀመበት መሆኑን በመግለጽ ከእዚህ ቀደም በችሎቱ ያቀረቡትን ቅሬታ በተመለከተ ኢትዮ ቴሌኮም ለችሎቱ ይሰጠዋል ተብሎ የሚጠበቀውን ምላሽ የመስማት ጉዳይ ነበር።
ከዶ/ር ካሳ ተሻገር እና ከጋዜጠኛ ቴዎድሮስ ስልክ ቁጥሮች ጋር በተያያዘ ኢትዮ ቴሌኮም የላከውን ምላሽ ችሎቱ በንባብ አሰምቶታል።
በምላሹ መሠረት፣ የሁለቱ ተከሳሾች ስልክ ቁጥሮች ለረዥም ጊዜ ከአገልግሎት ውጭ በመቆየታቸው በኩባንያው አሠራር መሠረት ጊዜው አልፎበት (expire አድርጎ) ለሌሎች አዳዲስ ተጠቃሚዎች መዘዋወራቸውን ኢትዮ ቴሌኮም አረጋግጧል።
በዋናው ጉዳይ ላይ የሚጠበቀው ብይን ተከሳሾቹ አቃቤ ሕግ ባቀረበባቸው ማስረጃ ላይ ተመስርተው ክሱን ሊከላከሉ ይገባል ወይስ አቃቤ ሕግ ክሱን በበቂ ማስረጃ ስላላስረዳ በነጻ ሊሰናበቱ ይገባል የሚለውን ጥያቄ የሚመልስ ነው።
የተከሳሾች ጠበቃ የሆኑት አቶ ሰለሞን ገዛኸኝ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል "ተከሳሾቹ ከእዚህ ቀደም በችሎት ውሎዎች ላይ አቃቤ ሕግ ካቀረባቸው የድምጽ፣ የጽሑፍ እና የፎረንሲክ ማስረጃዎች ጋር በተያያዘ አስተያየታቸውን ማቅረባቸውን"ገልጸዋል።
ፍርድ ቤቱ የተከሳሾችን ይህን አስተያየት እና አቃቤ ሕግ ያቀረበውን ማስረጃ መርምሮ፣ ማስረጃው ክሱን በበቂ ሁኔታ የሚያስረዳ ሆኖ ካገኘው ተከሳሾቹ እንዲከላከሉ፣ ካላገኘውም ተከሳሾቹ ያለ ተጨማሪ ክርክር በነጻ እንዲሰናበቱ ብይን የሚሰጥበት ይሆናል ተብሎ ይጠበቅ ነበር ብለውናል።
ይሁን እንጂ ፍርድ ቤቱ የተከሳሾችን ሙሉ ተገኝነት መሠረት በማድረግ ብይኑን ወደ ጥቅምት 6 ቀን 2019 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቶ ችሎቱን ዘግቷል።
የበጀት ዓመቱ መጠናቀቁን ተከትሎ የዳኝነት አገልግሎት ክብደትና ውስብስብነት ከግምት ውስጥ በማስገባት የፌዴራል የመጀመሪያ፣ ከፍተኛና ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች በየአመቱ ከነሐሴ 1 እስከ መስከረም 30 ለ2 ወራት በከፊል ዝግ ሆነው የሚቆዩ መሆኑ ይታወቃል።
tikvahethiopia
በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙት የቀድሞ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል አቶ ክርስቲያን ታደለ፣ የቀድሞ የአማራ ክልል ምክር ቤት አባል አቶ ዮሐንስ ቧያለው እንዲሁም ዶ/ር ካሳ ተሻገር፣ ዶ/ር ጫኔ ከበደን ጨምሮ በድምሩ 52 ተከሳሾች የፍርድ ውሳኔ ሳያገኙ ላለፉት ሦስት ዓመታት ገደማ በእስር ላይ ይገኛሉ።
ክሱ የተመሠረተው መጋቢት 2016 ዓ.ም ሲሆን፣ ጉዳዩ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሕገ መንግሥትና ፀረ-ሽብር ወንጀሎች ችሎት እየታየ ይገኛል።
ተከሳሾቹ በተለያዩ ወቅቶች ካለባቸው የጤና ችግር ጋር በተያያዘ፣ ከቤተሰብ ጥየቃ፣ ከሰብአዊ መብት ሁኔታ፣ እና ሌሎችም ደረሰብን በማለት በሚያቀርቧቸው ቅሬታዎች ዙሪያ ችሎቱ የተለያዩ ቀጠሮዎችን በመስጠት ጉዳያቸውን ሲመለከት የቆየ በመሆኑ የተከሰሱበትን ዋናው የክስ መዝገብን የማየት ሂደት በተለዋጭ ቀጠሮዎች ከ 4 ጊዜ በላይ ሲራዘም ቆይቷል።
በዋናው የሽብር ክስ መዝገብ ላይ ብይን ለመስጠት ቀደም ሲል ለሐምሌ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ቀጠሮ ተይዞ የነበረ ቢሆንም፣ ችሎቱ ጉዳዩን በተጨማሪ ዝግጅት አጠቃሎ ለማቅረብ ለዛሬ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ለተለዋጭ ቀጠሮ አስተላልፎት ነበር።
ችሎቱ ዛሬ የሚሰጠው ብይን ተከሳሾቹ የተከሰሱበትን ክስ ይከላከሉ ወይስ የነጻ ይሰናበቱ የሚለውን ጥያቄ የሚመልስ እንደሚሆን ቢጠበቅም በድጋሚ በተለዋጭ ቀጠሮ ለ ጥቅምት 6/2019 ዓም በመስጠት ውሳኔውን አራዝሞታል።
ፍርድ ቤቱ ብይኑን ማጠናቀቁን ገልጾ ነበር፤ ይሁን እንጂ የተወሰኑ ተከሳሾች በችሎት ባለመገኘታቸው ብይኑን ለንባብ ማቅረብ እንደማይችል በመግለጽ ንባቡን አላደረገም።
በዛሬው ችሎት ፍርድ ቤቱ ያሰማዋል ተብሎ ሲጠበቅ ከነበረው ብይን በተጨማሪ ከተከሳሾቹ አንዱ ከሆኑት ከዶ/ር ካሳ ተሻገር እና ከጋዜጠኛ ቴዎድሮስ ስልክ ቁጥር ጋር በተያያዘ ቁጥራቸውን ሌላ ሰው እየተጠቀመበት መሆኑን በመግለጽ ከእዚህ ቀደም በችሎቱ ያቀረቡትን ቅሬታ በተመለከተ ኢትዮ ቴሌኮም ለችሎቱ ይሰጠዋል ተብሎ የሚጠበቀውን ምላሽ የመስማት ጉዳይ ነበር።
ከዶ/ር ካሳ ተሻገር እና ከጋዜጠኛ ቴዎድሮስ ስልክ ቁጥሮች ጋር በተያያዘ ኢትዮ ቴሌኮም የላከውን ምላሽ ችሎቱ በንባብ አሰምቶታል።
በምላሹ መሠረት፣ የሁለቱ ተከሳሾች ስልክ ቁጥሮች ለረዥም ጊዜ ከአገልግሎት ውጭ በመቆየታቸው በኩባንያው አሠራር መሠረት ጊዜው አልፎበት (expire አድርጎ) ለሌሎች አዳዲስ ተጠቃሚዎች መዘዋወራቸውን ኢትዮ ቴሌኮም አረጋግጧል።
በዋናው ጉዳይ ላይ የሚጠበቀው ብይን ተከሳሾቹ አቃቤ ሕግ ባቀረበባቸው ማስረጃ ላይ ተመስርተው ክሱን ሊከላከሉ ይገባል ወይስ አቃቤ ሕግ ክሱን በበቂ ማስረጃ ስላላስረዳ በነጻ ሊሰናበቱ ይገባል የሚለውን ጥያቄ የሚመልስ ነው።
የተከሳሾች ጠበቃ የሆኑት አቶ ሰለሞን ገዛኸኝ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል "ተከሳሾቹ ከእዚህ ቀደም በችሎት ውሎዎች ላይ አቃቤ ሕግ ካቀረባቸው የድምጽ፣ የጽሑፍ እና የፎረንሲክ ማስረጃዎች ጋር በተያያዘ አስተያየታቸውን ማቅረባቸውን"ገልጸዋል።
ፍርድ ቤቱ የተከሳሾችን ይህን አስተያየት እና አቃቤ ሕግ ያቀረበውን ማስረጃ መርምሮ፣ ማስረጃው ክሱን በበቂ ሁኔታ የሚያስረዳ ሆኖ ካገኘው ተከሳሾቹ እንዲከላከሉ፣ ካላገኘውም ተከሳሾቹ ያለ ተጨማሪ ክርክር በነጻ እንዲሰናበቱ ብይን የሚሰጥበት ይሆናል ተብሎ ይጠበቅ ነበር ብለውናል።
ይሁን እንጂ ፍርድ ቤቱ የተከሳሾችን ሙሉ ተገኝነት መሠረት በማድረግ ብይኑን ወደ ጥቅምት 6 ቀን 2019 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቶ ችሎቱን ዘግቷል።
የበጀት ዓመቱ መጠናቀቁን ተከትሎ የዳኝነት አገልግሎት ክብደትና ውስብስብነት ከግምት ውስጥ በማስገባት የፌዴራል የመጀመሪያ፣ ከፍተኛና ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች በየአመቱ ከነሐሴ 1 እስከ መስከረም 30 ለ2 ወራት በከፊል ዝግ ሆነው የሚቆዩ መሆኑ ይታወቃል።
tikvahethiopia
16 days ago
የአቤን አንጀት የምታርሰው ሙዚቃ
#ethiopia | ሁለገቡ የጥበብ ሰው አበበ ብርሃኔ ግጥምና ዜማቸው በሌሎች ከተሰሩ የሙዚቃ ስራዎች መካከል የሚወደው አንድ ሙዚቃ አለ።
አቤ እጅግ ከሚወዳቸው የሙዚቃ ስራዎች መካከል የቴዎድሮስ ታደሰን "ሰርካለም" የተሰኘው ሙዚቃ ሙዚቃ እንደሆነ በአንድ ወቅት ከጋዜጠኛ ሔኖክ ወ/ገብርኤል ጋር በሙዚቀኞች ብፌ ፕሮግራም ላይ በነበረው ቆይታ ተናግሮ ነበር።
ይህ ሙዚቃ ለአቤ ሁሉ ነገሩ ነው።
የጥበብ ሰው አበበ ብርሃኔ የቴዎድሮስ ታደሰን "ሰርካለም" ሲያዳምጥ ልክ በውስጡ የተደበቀ በቃላት ሊገለጽ የማይችል ጥልቅ ስሜት የሚቀሰቀስበት ይመስላል።
አበበ ብርሃኔ በሙዚቃ ዓለም ውስጥ ከ800 በላይ የግጥምና የዜማ ስራዎች የሰራ ታላቅ የጥበብ ሰው ነው።
በይልማ ገ/አብ እና በዜማ ደራሲው አበበ መለሰ የተሰራው ይህ ሰርካለም ሙዚቃ ስራ ግን ለአበበ ብርሀኔ ቀዳሚ የሙዚቃ ምርጫ ነው።
የቴዎድሮስ ታደሰን "ሰርካለም" ሲሰማ ምርጫው መሆኑን ከመመስከር ወደ ኋላ አይልም።
ለእርሱ ይህ ሙዚቃ ከአድማጭነት አልፎ የህይወት አጋሩ ሆኗል።
አበበ ለዚህ ሙዚቃ ያለው ክብር እንደ ተራ አድናቂ አይደለም።
ሙዚቃው ሲጀምር አበበ ወደ ትዝታው ጥግ ይጓዛል።
"ሰርካለም" ለእርሱ እንደ አንድ ታሪካዊ መጽሐፍ ገጾች ያለፉትን ጣፋጭና መራራ የህይወት ምዕራፎች ሁሉ እያገላበጠ የሚያስታውሰው ነው።
የሙዚቃው ዜማና የቴዎድሮስ ታደሰ ድምፅ በአበበ ልብ ውስጥ ልዩ የሆነ የመረጋጋት ስሜት ይፈጥራል የአንጀቱ መታረሻም ይኸው ነው።
"ሰርካለም" የጥበብ ጥግ ነው። በሙዚቃው ውስጥ የሚሰማው የፍቅር የናፍቆትና የህይወት ትርጉም ከአበበ የጥበብ እይታ ጋር ይዋሃዳል።
አበበ በግርምት ሲናገር እንዲህ ይላል
እንዴት እንዲህ አይነት ሙዚቃ ይሰራል የሚል።
የግጥሙ ጥልቀት የዜማው ጥራት እና ውበት ይደንቀኛልም ይላል።
"ሰርካለም" ለእርሱ የትላንት ናፍቆቱ የዛሬ ኩራቱ እና የነገ ተስፋው የሆነ ሙዚቃ ይመስላል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #ኢትዮጵያሙዚቃሰርካለም #አበበብርሀኔቴዎድሮስታደሰ #ይልማገብረአብአበበመለሰ
#ethiopia | ሁለገቡ የጥበብ ሰው አበበ ብርሃኔ ግጥምና ዜማቸው በሌሎች ከተሰሩ የሙዚቃ ስራዎች መካከል የሚወደው አንድ ሙዚቃ አለ።
አቤ እጅግ ከሚወዳቸው የሙዚቃ ስራዎች መካከል የቴዎድሮስ ታደሰን "ሰርካለም" የተሰኘው ሙዚቃ ሙዚቃ እንደሆነ በአንድ ወቅት ከጋዜጠኛ ሔኖክ ወ/ገብርኤል ጋር በሙዚቀኞች ብፌ ፕሮግራም ላይ በነበረው ቆይታ ተናግሮ ነበር።
ይህ ሙዚቃ ለአቤ ሁሉ ነገሩ ነው።
የጥበብ ሰው አበበ ብርሃኔ የቴዎድሮስ ታደሰን "ሰርካለም" ሲያዳምጥ ልክ በውስጡ የተደበቀ በቃላት ሊገለጽ የማይችል ጥልቅ ስሜት የሚቀሰቀስበት ይመስላል።
አበበ ብርሃኔ በሙዚቃ ዓለም ውስጥ ከ800 በላይ የግጥምና የዜማ ስራዎች የሰራ ታላቅ የጥበብ ሰው ነው።
በይልማ ገ/አብ እና በዜማ ደራሲው አበበ መለሰ የተሰራው ይህ ሰርካለም ሙዚቃ ስራ ግን ለአበበ ብርሀኔ ቀዳሚ የሙዚቃ ምርጫ ነው።
የቴዎድሮስ ታደሰን "ሰርካለም" ሲሰማ ምርጫው መሆኑን ከመመስከር ወደ ኋላ አይልም።
ለእርሱ ይህ ሙዚቃ ከአድማጭነት አልፎ የህይወት አጋሩ ሆኗል።
አበበ ለዚህ ሙዚቃ ያለው ክብር እንደ ተራ አድናቂ አይደለም።
ሙዚቃው ሲጀምር አበበ ወደ ትዝታው ጥግ ይጓዛል።
"ሰርካለም" ለእርሱ እንደ አንድ ታሪካዊ መጽሐፍ ገጾች ያለፉትን ጣፋጭና መራራ የህይወት ምዕራፎች ሁሉ እያገላበጠ የሚያስታውሰው ነው።
የሙዚቃው ዜማና የቴዎድሮስ ታደሰ ድምፅ በአበበ ልብ ውስጥ ልዩ የሆነ የመረጋጋት ስሜት ይፈጥራል የአንጀቱ መታረሻም ይኸው ነው።
"ሰርካለም" የጥበብ ጥግ ነው። በሙዚቃው ውስጥ የሚሰማው የፍቅር የናፍቆትና የህይወት ትርጉም ከአበበ የጥበብ እይታ ጋር ይዋሃዳል።
አበበ በግርምት ሲናገር እንዲህ ይላል
እንዴት እንዲህ አይነት ሙዚቃ ይሰራል የሚል።
የግጥሙ ጥልቀት የዜማው ጥራት እና ውበት ይደንቀኛልም ይላል።
"ሰርካለም" ለእርሱ የትላንት ናፍቆቱ የዛሬ ኩራቱ እና የነገ ተስፋው የሆነ ሙዚቃ ይመስላል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #ኢትዮጵያሙዚቃሰርካለም #አበበብርሀኔቴዎድሮስታደሰ #ይልማገብረአብአበበመለሰ
16 days ago
ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም መዘናጋት አያስፈልግም አሉ?
#ethiopia | በትራፊክ አደጋ አበረታች ለውጥ እየተመዘገበ ቢሆንም መዘናጋት ግና አያስፈልግም ብለዋል።
የአለም ጤና ድርጅ ሊቀመንበር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም በዓለም አቀፍ ደረጃ በትራፊክ አደጋ የሚደርሰው የሞት መጠን በ21 በመቶ መቀነሱ ተናግረዋል።
ቢሆንም የሰው ህይወትን ሙሉ በሙሉ ለመታደግ የበለጠ የተቀናጀ እና ጠንካራ እርምጃ እንደሚያስፈልግ ነው የገለፁት።
ይህ አበረታች ለውጥ ሀገራት በዘመናዊ እና ደህንነቱ በተጠበቀ የመንገድ መሠረተ ልማት ላይ ኢንቨስት ሲያደርጉ ውጤታማ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል የሚያሳይ ማሳያ ነው ብለዋል።
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) የዓለም አቀፍ የመንገድ ደህንነት ከፍተኛ ደረጃ ስብሰባ ላይ የተገኙት ሀገራት በመንገድ ደህንነት ጉዳይ ከፍተኛ ለውጥ እያስመዘገቡ ይገኛል ነው የተባለው።
ሀገራት የሚያወጧቸው ህጎችና ደንቦች ዜጋ ተኮር ማድረግ አለባቸው ብለዋል።
ተሽከርካሪዎች ለሰው ልጅ ደህንነት እና ለግለሰቦች እንቅስቃሴ ቅድሚያ በሚሰጥ መልኩ እንዲነደፉ የሚያበረታታ ነው።
በትራፊክ አደጋ የሚደርስው የዜጎች ሞት ቀላል በሆኑ ህጎች መከላከል የሚቻል መሆኑ መታሰብ ይኖርበታል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #worldhealthorganization #drtewodrosadehanom #roadaccidentsummit
#ethiopia | በትራፊክ አደጋ አበረታች ለውጥ እየተመዘገበ ቢሆንም መዘናጋት ግና አያስፈልግም ብለዋል።
የአለም ጤና ድርጅ ሊቀመንበር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም በዓለም አቀፍ ደረጃ በትራፊክ አደጋ የሚደርሰው የሞት መጠን በ21 በመቶ መቀነሱ ተናግረዋል።
ቢሆንም የሰው ህይወትን ሙሉ በሙሉ ለመታደግ የበለጠ የተቀናጀ እና ጠንካራ እርምጃ እንደሚያስፈልግ ነው የገለፁት።
ይህ አበረታች ለውጥ ሀገራት በዘመናዊ እና ደህንነቱ በተጠበቀ የመንገድ መሠረተ ልማት ላይ ኢንቨስት ሲያደርጉ ውጤታማ ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል የሚያሳይ ማሳያ ነው ብለዋል።
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) የዓለም አቀፍ የመንገድ ደህንነት ከፍተኛ ደረጃ ስብሰባ ላይ የተገኙት ሀገራት በመንገድ ደህንነት ጉዳይ ከፍተኛ ለውጥ እያስመዘገቡ ይገኛል ነው የተባለው።
ሀገራት የሚያወጧቸው ህጎችና ደንቦች ዜጋ ተኮር ማድረግ አለባቸው ብለዋል።
ተሽከርካሪዎች ለሰው ልጅ ደህንነት እና ለግለሰቦች እንቅስቃሴ ቅድሚያ በሚሰጥ መልኩ እንዲነደፉ የሚያበረታታ ነው።
በትራፊክ አደጋ የሚደርስው የዜጎች ሞት ቀላል በሆኑ ህጎች መከላከል የሚቻል መሆኑ መታሰብ ይኖርበታል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #worldhealthorganization #drtewodrosadehanom #roadaccidentsummit
21 days ago
“ዕድሜ ለህልም እንቅፋት አይደለም”፦ የ62 ዓመቱ አባት ከልጃቸው ጋር የ12ኛ ክፍል ፈተናን እየወሰዱ ነው
*********************
ዕድሜ ለህልም መሳካት ማነቆ ሳይሆን ለቁርጠኝነት መለኪያ መሆኑን በተግባር እያሳዩ የሚገኙት የ62 ዓመቱ አቶ ዩሱፍ ኢብራሂም፣ በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የብዙዎችን ትኩረት ስበዋል።
ከሶማሊ ክልል ሲቲ ዞን ጎታ ቢቄ ወረዳ የመጡት አቶ ዩሱፍ፣ ከገዛ ልጃቸው ጋር በመሆን በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የፈተና አዳራሽ በመገኘት የዕውቀት ጉዟቸውን እያከናወኑ ይገኛሉ።
አባትና ልጅ በአንድ የፈተና ጣቢያ መፈተናቸው ለፈተናው አዳራሽ ልዩ ድምቀት የፈጠረ ሲሆን፣ አቶ ዩሱፍ ከልጆቻቸውና ከልጅ ልጆቻቸው እኩያ ከሆኑ ወጣቶች ጋር ጎን ለጎን ተቀምጠው መፈተናቸው ታላቅ ክብርና ደስታ እንደሰጣቸው ይናገራሉ።
አቶ ዩሱፍ በዚህ ዕድሜያቸው ፈተናውን ለመውሰድ የወሰኑት የራሳቸውን ህልም ለማሳካት ብቻ ሳይሆን፣ በትምህርታቸው ተስፋ ለሚቆርጡ ወጣቶች አርአያ በመሆን መነቃቃትን ለመፍጠር ጭምር ነው።
“ትምህርት የሀገር ፍቅር መገለጫ ነው” የሚሉት አቶ ዩሱፍ፣ ለግለሰብም ሆነ ለሀገር እድገት ትምህርት ዋነኛው ቁልፍ መሆኑን በጽኑ ያምናሉ። ተማሪዎች በሙሉ በትምህርታቸው በርትተው በመማር፣ ነገ አመርቂ ውጤት በማምጣት ሀገራቸውን በታማኝነት ማገልገል እንዳለባቸውም መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
የአቶ ዩሱፍ የዕውቀት ጉዞ በዚህ የ12ኛ ክፍል ፈተና ላይ የሚያበቃ አይደለም። ፈተናውን በከፍተኛ ውጤት በማለፍ ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም በመግባት፣ የጀመሩትን የዕውቀት ጉዞ የመቀጠልና በዩኒቨርሲቲ የመመረቅ ትልቅ ራዕይ ሰንቀዋል።
የ62 ዓመቱ አባት ይህ ታሪካዊ ርምጃ፣ ትምህርት ለማንኛውም ዕድሜ የሰው ልጅ የላቀ መዳረሻ መሆኑን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል።
በቴዎድሮስ ታደሰ
#ኢትዮጵያ #ኢትዮጵያትማር #ethiopia #education
*********************
ዕድሜ ለህልም መሳካት ማነቆ ሳይሆን ለቁርጠኝነት መለኪያ መሆኑን በተግባር እያሳዩ የሚገኙት የ62 ዓመቱ አቶ ዩሱፍ ኢብራሂም፣ በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የብዙዎችን ትኩረት ስበዋል።
ከሶማሊ ክልል ሲቲ ዞን ጎታ ቢቄ ወረዳ የመጡት አቶ ዩሱፍ፣ ከገዛ ልጃቸው ጋር በመሆን በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የፈተና አዳራሽ በመገኘት የዕውቀት ጉዟቸውን እያከናወኑ ይገኛሉ።
አባትና ልጅ በአንድ የፈተና ጣቢያ መፈተናቸው ለፈተናው አዳራሽ ልዩ ድምቀት የፈጠረ ሲሆን፣ አቶ ዩሱፍ ከልጆቻቸውና ከልጅ ልጆቻቸው እኩያ ከሆኑ ወጣቶች ጋር ጎን ለጎን ተቀምጠው መፈተናቸው ታላቅ ክብርና ደስታ እንደሰጣቸው ይናገራሉ።
አቶ ዩሱፍ በዚህ ዕድሜያቸው ፈተናውን ለመውሰድ የወሰኑት የራሳቸውን ህልም ለማሳካት ብቻ ሳይሆን፣ በትምህርታቸው ተስፋ ለሚቆርጡ ወጣቶች አርአያ በመሆን መነቃቃትን ለመፍጠር ጭምር ነው።
“ትምህርት የሀገር ፍቅር መገለጫ ነው” የሚሉት አቶ ዩሱፍ፣ ለግለሰብም ሆነ ለሀገር እድገት ትምህርት ዋነኛው ቁልፍ መሆኑን በጽኑ ያምናሉ። ተማሪዎች በሙሉ በትምህርታቸው በርትተው በመማር፣ ነገ አመርቂ ውጤት በማምጣት ሀገራቸውን በታማኝነት ማገልገል እንዳለባቸውም መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
የአቶ ዩሱፍ የዕውቀት ጉዞ በዚህ የ12ኛ ክፍል ፈተና ላይ የሚያበቃ አይደለም። ፈተናውን በከፍተኛ ውጤት በማለፍ ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም በመግባት፣ የጀመሩትን የዕውቀት ጉዞ የመቀጠልና በዩኒቨርሲቲ የመመረቅ ትልቅ ራዕይ ሰንቀዋል።
የ62 ዓመቱ አባት ይህ ታሪካዊ ርምጃ፣ ትምህርት ለማንኛውም ዕድሜ የሰው ልጅ የላቀ መዳረሻ መሆኑን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል።
በቴዎድሮስ ታደሰ
#ኢትዮጵያ #ኢትዮጵያትማር #ethiopia #education
21 days ago
አሜሪካ ጎንደር ገባች
#ethiopia | በኢትዮጵያ የዩናይትድ ስቴትስ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ታሪካዊቷ የጎንደር ከተማ የገቡ ሲሆን በቦታውም ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
አምባሳደሩ ጎንደር ሲደርሱ የከተማዋ ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው፣ የአማራ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ሞላ መልካሙ፣ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር አሥራት ዓፀደወይን እንዲሁም ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥትና የዩኒቨርሲቲው የሥራ ኃላፊዎች በክብር ተቀብለዋቸዋል።
አምባሳደር ማሲንጋ እና የሚመሩት የልዑካን ቡድን በቆይታቸው በጎንደር ከተማ በዩኒቨርሲቲው አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እንዲሁም በዓፄ ቴዎድሮስ ግቢ በሚገኘው የሃሪ ኤስ ትሩማን አሜሪካን ኮርነር የቤተ-መጻሕፍት ማዕከል ጉብኝት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በጎንደር ከተማ ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ መረጃ መሠረት ከዚህ በተጨማሪም በትምህርት፣ በምርምር፣ በጤና አገልግሎትና በተቋማዊ አጋርነት ዘርፎች ያለውን የሁለትዮሽ ትብብር ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ከዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች ጋር ሰፊ ውይይት የሚያደርጉ ሲሆን የጎንደር ዩኒቨርሲቲም ይህ ጉብኝት በኢትዮጵያና በዩናይትድ ስቴትስ መካከል ያለውን ታሪካዊና ዘላቂ አጋርነት ይበልጥ የሚያጠናክር እንደሚሆን ያለውን ጽኑ እምነት ገልጿል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | በኢትዮጵያ የዩናይትድ ስቴትስ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ታሪካዊቷ የጎንደር ከተማ የገቡ ሲሆን በቦታውም ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
አምባሳደሩ ጎንደር ሲደርሱ የከተማዋ ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው፣ የአማራ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ሞላ መልካሙ፣ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር አሥራት ዓፀደወይን እንዲሁም ሌሎች ከፍተኛ የመንግሥትና የዩኒቨርሲቲው የሥራ ኃላፊዎች በክብር ተቀብለዋቸዋል።
አምባሳደር ማሲንጋ እና የሚመሩት የልዑካን ቡድን በቆይታቸው በጎንደር ከተማ በዩኒቨርሲቲው አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እንዲሁም በዓፄ ቴዎድሮስ ግቢ በሚገኘው የሃሪ ኤስ ትሩማን አሜሪካን ኮርነር የቤተ-መጻሕፍት ማዕከል ጉብኝት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በጎንደር ከተማ ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ መረጃ መሠረት ከዚህ በተጨማሪም በትምህርት፣ በምርምር፣ በጤና አገልግሎትና በተቋማዊ አጋርነት ዘርፎች ያለውን የሁለትዮሽ ትብብር ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ከዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች ጋር ሰፊ ውይይት የሚያደርጉ ሲሆን የጎንደር ዩኒቨርሲቲም ይህ ጉብኝት በኢትዮጵያና በዩናይትድ ስቴትስ መካከል ያለውን ታሪካዊና ዘላቂ አጋርነት ይበልጥ የሚያጠናክር እንደሚሆን ያለውን ጽኑ እምነት ገልጿል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
Sponsored by
Surafel
22 days ago
ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) አድናቂዎቹን አመስግኗል
#ethiopia | የኢትዮጵያ ሙዚቃ ንጉሥ በመባል የሚታወቀው ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ)፣ በሙዚቃው ዓለም የቆየባቸውን 25 ዓመታት አስመልክቶ ለደጋፊዎቹ የምስጋና መልእክት አስተላለፈ።
ድምጻዊው ዛሬ ባሰራጨው የጽሑፍ መልእክት የሙዚቃ ጉዞው የጀመረበትን 25ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ፣ ላለፉት ዓመታት በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር የሚገኙ አድናቂዎቹ ላሳዩት የማይቀንስ ፍቅርና ድጋፍ በልዑል እግዚአብሔር ስም ምስጋናውን አቅርቧል።
ቴዲ አፍሮ በመልእክቱ እንዳስታወሰው፣ ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ከግማሽ በላይ በሙዚቃ ህይወቱ ውስጥ በነበሩት ውጣ ውረዶች፣ ስኬቶች እና ተግዳሮቶች ጊዜ ሁሉ አድናቂዎቹ ለእርሱ የነበራቸው ጽኑ ወዳጅነትና የማይጠፋ ፍቅር ትልቅ ጉልበት እንደሆነው ገልጿል።
የሙዚቃው ዓለም እውቅና ያተረፈለትና በርካታ ተወዳጅ አልበሞችን ለአድማጭ ያደረሰው ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን፣ አድናቂዎቹ ላሳዩት ቀጣይነት ያለው ፍቅር ያለውን አክብሮት በመግለጽ ለወደፊቱም ሙዚቃዊ ስራዎቹን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አመላክቷል።
"ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር! ፍቅር ያሸንፋል!" በሚል መፈክር መልእክቱን የቋጨው ድምጻዊው፣ በአድናቂዎቹ ዘንድ ያለውን ትልቅ አክብሮት በምስጋና አረጋግጧል።
#ethiopia #getutemesgen #getunews #ethiopiamusic #ድምጻዊቴዎድሮስካሳሁን
#ethiopia | የኢትዮጵያ ሙዚቃ ንጉሥ በመባል የሚታወቀው ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ)፣ በሙዚቃው ዓለም የቆየባቸውን 25 ዓመታት አስመልክቶ ለደጋፊዎቹ የምስጋና መልእክት አስተላለፈ።
ድምጻዊው ዛሬ ባሰራጨው የጽሑፍ መልእክት የሙዚቃ ጉዞው የጀመረበትን 25ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ፣ ላለፉት ዓመታት በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር የሚገኙ አድናቂዎቹ ላሳዩት የማይቀንስ ፍቅርና ድጋፍ በልዑል እግዚአብሔር ስም ምስጋናውን አቅርቧል።
ቴዲ አፍሮ በመልእክቱ እንዳስታወሰው፣ ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ከግማሽ በላይ በሙዚቃ ህይወቱ ውስጥ በነበሩት ውጣ ውረዶች፣ ስኬቶች እና ተግዳሮቶች ጊዜ ሁሉ አድናቂዎቹ ለእርሱ የነበራቸው ጽኑ ወዳጅነትና የማይጠፋ ፍቅር ትልቅ ጉልበት እንደሆነው ገልጿል።
የሙዚቃው ዓለም እውቅና ያተረፈለትና በርካታ ተወዳጅ አልበሞችን ለአድማጭ ያደረሰው ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን፣ አድናቂዎቹ ላሳዩት ቀጣይነት ያለው ፍቅር ያለውን አክብሮት በመግለጽ ለወደፊቱም ሙዚቃዊ ስራዎቹን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አመላክቷል።
"ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር! ፍቅር ያሸንፋል!" በሚል መፈክር መልእክቱን የቋጨው ድምጻዊው፣ በአድናቂዎቹ ዘንድ ያለውን ትልቅ አክብሮት በምስጋና አረጋግጧል።
#ethiopia #getutemesgen #getunews #ethiopiamusic #ድምጻዊቴዎድሮስካሳሁን
22 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢትዮጵያ ሙዚቃ ንጉሥ በመባል የሚታወቀው ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ)፣ በሙዚቃው ዓለም የቆየባቸውን 25 ዓመታት አስመልክቶ ለደጋፊዎቹ የምስጋና መልእክት አስተላለፈ።
ድምጻዊው ዛሬ ባሰራጨው የጽሑፍ መልእክት የሙዚቃ ጉዞው የጀመረበትን 25ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ፣ ላለፉት ዓመታት በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር የሚገኙ አድናቂዎቹ ላሳዩት የማይቀንስ ፍቅርና ድጋፍ በልዑል እግዚአብሔር ስም ምስጋናውን አቅርቧል። ቴዲ አፍሮ በመልእክቱ እንዳስታወሰው፣ ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ከግማሽ በላይ በሙዚቃ ህይወቱ ውስጥ በነበሩት ውጣ ውረዶች፣ ስኬቶች እና ተግዳሮቶች ጊዜ ሁሉ አድናቂዎቹ ለእርሱ የነበራቸው ጽኑ ወዳጅነትና የማይጠፋ ፍቅር ትልቅ ጉልበት እንደሆነው ገልጿል።
የሙዚቃው ዓለም እውቅና ያተረፈለትና በርካታ ተወዳጅ አልበሞችን ለአድማጭ ያደረሰው ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን፣ አድናቂዎቹ ላሳዩት ቀጣይነት ያለው ፍቅር ያለውን አክብሮት በመግለጽ ለወደፊቱም ሙዚቃዊ ስራዎቹን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አመላክቷል።
"ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር! ፍቅር ያሸንፋል!" በሚል መፈክር መልእክቱን የቋጨው ድምጻዊው፣ በአድናቂዎቹ ዘንድ ያለውን ትልቅ አክብሮት በምስጋና አረጋግጧል።
ድምጻዊው ዛሬ ባሰራጨው የጽሑፍ መልእክት የሙዚቃ ጉዞው የጀመረበትን 25ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ፣ ላለፉት ዓመታት በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር የሚገኙ አድናቂዎቹ ላሳዩት የማይቀንስ ፍቅርና ድጋፍ በልዑል እግዚአብሔር ስም ምስጋናውን አቅርቧል። ቴዲ አፍሮ በመልእክቱ እንዳስታወሰው፣ ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ከግማሽ በላይ በሙዚቃ ህይወቱ ውስጥ በነበሩት ውጣ ውረዶች፣ ስኬቶች እና ተግዳሮቶች ጊዜ ሁሉ አድናቂዎቹ ለእርሱ የነበራቸው ጽኑ ወዳጅነትና የማይጠፋ ፍቅር ትልቅ ጉልበት እንደሆነው ገልጿል።
የሙዚቃው ዓለም እውቅና ያተረፈለትና በርካታ ተወዳጅ አልበሞችን ለአድማጭ ያደረሰው ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን፣ አድናቂዎቹ ላሳዩት ቀጣይነት ያለው ፍቅር ያለውን አክብሮት በመግለጽ ለወደፊቱም ሙዚቃዊ ስራዎቹን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አመላክቷል።
"ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር! ፍቅር ያሸንፋል!" በሚል መፈክር መልእክቱን የቋጨው ድምጻዊው፣ በአድናቂዎቹ ዘንድ ያለውን ትልቅ አክብሮት በምስጋና አረጋግጧል።
23 days ago
ዛሬ ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ደማቅ ቀን ነው። አድማጮች በሙዚቃው የሚወዱት፣ ግጥምና ዜማውን በራሱ የሚቃኘው ተወዳጁ ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) የተወለደበት ቀን ነው።
የትውልድ እና እድገቱ አዲስ አበባ የሆነው ቴዲ፣ ከ1ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ትምህርቱን የተከታተለውም እዚሁ ከተማ ነው። ለሙዚቃ ባለው ከፍተኛ ፍቅር እና ባሳየው የፈጠራ ብቃት፣ በኢትዮጵያ ሙዚቃ ታሪክ ውስጥ ስሙ በጉልህ እንዲሰፍር አድርጎታል።
"ፍቅር ያሸንፋል" በሚለው አባባሉ የሚታወቀውና በአድናቂዎቹ ዘንድ ትልቅ ስፍራ ያለው ቴዲ፣ ከውጫዊ ተጽዕኖዎች ይልቅ ትኩረቱን ሙዚቃው ላይ ብቻ በማድረግ ለሙዚቃው ኢንዱስትሪ ትልቅ አሻራ ጥሏል።
ዛሬ የተወለድክበት ቀን ነውና፣ ለቀጣይ የኪነ-ጥበብ ስራዎችህ መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን። እንኳን ተወለድክ!
የትውልድ እና እድገቱ አዲስ አበባ የሆነው ቴዲ፣ ከ1ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ትምህርቱን የተከታተለውም እዚሁ ከተማ ነው። ለሙዚቃ ባለው ከፍተኛ ፍቅር እና ባሳየው የፈጠራ ብቃት፣ በኢትዮጵያ ሙዚቃ ታሪክ ውስጥ ስሙ በጉልህ እንዲሰፍር አድርጎታል።
"ፍቅር ያሸንፋል" በሚለው አባባሉ የሚታወቀውና በአድናቂዎቹ ዘንድ ትልቅ ስፍራ ያለው ቴዲ፣ ከውጫዊ ተጽዕኖዎች ይልቅ ትኩረቱን ሙዚቃው ላይ ብቻ በማድረግ ለሙዚቃው ኢንዱስትሪ ትልቅ አሻራ ጥሏል።
ዛሬ የተወለድክበት ቀን ነውና፣ ለቀጣይ የኪነ-ጥበብ ስራዎችህ መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን። እንኳን ተወለድክ!
24 days ago
"ገላ ገላ" አስቱካን እካችሁ
የሰው ልጅ ነፍስ የምትተነፍስበት ጥልቅ ውቅያኖስ "ሙዚቃ"
"ሙዚቃ" እና "ፍቅር" ደግሞ ተነጣጥለው የማይታዩ፣ አንዱ ለአንዱ የተፈጠሩ፣ የሰማይ እና የምድር ያህል የተሳሰሩ የነፍስ ቋንቋዎች ናቸው።
ከትላንት እስከ ዛሬ... ከካሴት ክር እስከ ዲጂታል ዘመን፣ ቴክኖሎጂው ቢለዋወጥም፣ ትውልድ ቢተካካም እነዚህን ሁለት መለኮታዊ ጸጋዎች በአንድ ልብ አዋህዳ፣ ስሜትን በዜማ ሸምና ያቀረበችልን የዘመናቶች ፈርጥ—እሷ አስቴር አወቀ ናት!
የትውልድን ልብ ያንኳኳች፣ ማዕበል እና ጸጥታን በድምጿ ያስማማች የኢትዮጵያ የሙዚቃ ጸጋ! አስቴር የ"ሶል" (Soul)
የፍቅር ንግሥት በድምጿ ጅረት ውስጥ የሰውን ልጅ ጥልቅ የልብ ጓዳ የምትፈትሽ፣ ስንከፋ አባባይ፣ ስንደሰት አጀብ ባይ የሆነች የዘመን ሀብት ናት።
ትዝታን ብቻ አይቀሰቅሱም፤ ገና ሳንኖረው የናፈቀንን፣ በቃላት የማይገለጸውን ያንን ጥልቅ ናፍቆት (መናፍቅነት) በውስጣችን ይፈጥራሉ። "ፍቅር" የሚለውን ቃል ስታዜመው፣ የፍቅርን ፊደል ያልቆጠረው እንኳ በፍቅር ይነድፋል፤ ገና ያላየነውን የፍቅር ብስራት በሙዚቃዋ እንድንኖረው፣ ያላጣጣመነውን ስሜት በምናባችን እንድንስለው ታደርገናለች። ድምጿ ሲሰማ የሌለብን ትዝታ ይጭንብናል፣ የሌለ ስንብት ያስለቅሰናል፣ ገና ያልመጣ ተስፋ ያስፈነድቀናል።
ትላንት አባቶቻችን እና እናቶቻችን ያደመጧትን፣ ዛሬ እኛ በፍቅር እንሰማታለን፤ ነገም ልጆቻችን ይወርሷታል። ጊዜ የማይሽራት፣ ዘመን የማያልፍባት ተወዳጅ አርቲስት!
እስኪ አንድ ሁለቲቱን እንምልክት
"ለመድክ ወይ" የተሰኘውን ይህን ልብ ሰባሪ እና ስሜት አንጀት ሰርስሮ የሚገባ የሙዚቃ ስራ ስናዳምጥ፣ የሰውን ልጅ የፍቅር ስነ-ልቦና፣ የልብ ስብራትን (Heartbreak) እና የመለየትን መራር እውነት በሚያስገርም ጥልቀት ስትፈትሸው እናገኛለን።
ይህ ዘፈን ተራ የሙዚቃ ዜማ አይደለም፤ ይልቁንም አንዲት በፍቅር የተከዳች፣ ማመን ያቃታት እና በትዝታ እስር ቤት ውስጥ የቀረች ነፍስ የምታሰማው የውስጥ ጩኸት ነው።
የዚህን ድንቅ ዘፈን ጥልቅ መልእክት በበሰለ የኪነ-ጥበብ መነጽር ስንተነትነው የሚከተሉትን ህያው እውነታዎች እናገኛለን
1. "ለመድክ ወይ?" ይህ ጥያቄ ተራ መጠይቅ አይደለም። የድንጋጤ እና የመገረም ጩኸት
ያለኔ መኖርን ቻልከው? እኔ ገና የትላንቱን አብሮነታችንን መርሳት አቅቶኝ በትዝታ እሳት እየነደድኩ፣ አንተ ግን እንዴት ያለምንም ህመም የክህደት እና የመገረም ስሜት ነው አንድ ሰው የነፍሱን ግማሽ አድርጎ ያሰበው አካል አዲስ ህይወት በአንድ ጀንበር የሚፈጠረውን የአእምሮ ንዝረት ያሳያል
አስቴር ይህንን ሚዛን የሳተ ፍቅር በጉልህ ታሳያለች።
በፍቅር መለያየት ውስጥ እጅግ አሳማሚው ነገር የህመሙ አለመመጣጠን ነው።
ለአንዱ (ለአፍቃሪዋ) ፍቅር የህይወት መሰረት፣ እስትንፋስ እና አለም ሲሆን፤ ለሌላኛው (ለተፈቃሪው) ግን ፍቅር ጊዜያዊ ማረፊያ፣ በቀላሉ ሊተካ እና ሊረሳ የሚችል ተራ ክስተት ሆኖ እናገኘዋለን። "እኔ እንዲህ ሆኜ፣ አንተ እንዴት ሆንክ?" የሚለው የዘፈኑ የጀርባ አጥንት ይህንን የስሜት መራራቅ ያጋልጣል።ያ የለመደችው ድምፅ፣ ያ የለመደችው መዓዛ በድንገት ሲቋረጥ ነፍስ ባዶ ትቀራለች። አስቴር በዚህ ዘፈኗ፣ መለየቱን አምና ለመቀበል የሚደረገውን የውስጥ ትግል እና የትዝታን አረመኔነት በቃላቷ ትስላለች። "ልመዳ" እንዴት ከባድ እንደሆነና ያንን ማቋረጥ ደግሞ ሞት መሆኑን ልክ አንዲት ሴት ብቻዋን ክፍሏ ውስጥ ሆና የምታነባውን፣ የምታቃስተውን እና ከራሷ ጋር የምታደርገውን ሙግት በዜማ ልክ ሰፍታ ታለብሰናለች።
የናፍቆትን እሳት እና የልብን መታለል ያለምንም ማለዘቢያ ፊት ለፊት
ለመድክ ወይ" የፍቅርን የጨለመ ገፅ ሚያዳምጣት ሁሉ የተወሳሰበ የሰው ልጅ ስሜት ወስዳ
የቆሰለ ልብ ያለው ሁሉ፣ በዚህ ዘፈን ውስጥ የራሱን እንባ ያገኛል!
"ገላ ገላ" በረቂቅ ቃላት የተሳለበት የፍቅር ጸሎት ።
ይህ ዘፈን ተራ የቃላት ድርደራ ሳይሆን፣ አንዲት የሰው ልጅ ነፍስ በፍቅር ስትገዛ፣ ስትማረክ እና ራሷን አሳልፋ ስትሰጥ የሚኖራትን ጥልቅ ስነ-ልቦናዊ እና ስጋዊ ውህደት የሚያሳይ ህያው ማሳያ ነው።
ገላ—የነፍስ ማረፊያ፣ የስሜት መግለጫ እና የፍቅር ቤተ-መቅደስ ነው።
አስቴር "ገላ" ስትል፣ መነካካትን ብቻ ሳይሆን፣ ሁለት ነፍሶች አንድ የሚሆኑበትን፣ መለያየት የሌለበትን ያንን የመጨረሻውን የፍቅር ልዕልና (Intimacy) እየጠራች ነው። ለእሷ ህይወት የሚዘራ፣ ግን ደግሞ ናፍቆትን የሚያባብስ ጣፋጭ እስር ቤት ነው።
አንድ የምታውቀው ፍጹም እውነት ቢኖር የራሷን የልብ ትርታ ነው።
የሷ "ሆድ" (ውስጧ/ነፍሷ) ለእሱ መገዛቱን አምና መቀበሏ፣ በፍቅር ውስጥ ያለውን ያለምንም ቅድመ-ሁኔታ ራስን አሳልፎ የመስጠት ጀግንነት ያሳያል።ፍቅር ከስሜት አልፎ ወደ "መኖር እና አለመኖር" ትርጉም ይሸጋገራል። ፍቅር የልብ ምት ብቻ ሳይሆን፣ ወደ ሳንባ ገብቶ የሚያኖራት ኦክስጅኗ ሆኗል።
የነፍስ ኑዛዜ ነው ገና ያላፈቀረውን "እንዲህ ያለ ጥልቅ ፍቅር ባገኘሁ" ብሎ እንዲመኝ ሲያደርግ፤ ያፈቀረውን ደግሞ የልቡን ቋንቋ አግኝቶለታል።የሰውን ልጅ ድብቅ እና ጥልቅ የልብ ጓዳ ገብታ፣ ትበረብራልች
በሥራ መክበርን" በተግባር በማሳየቷ እንጂ! 40የልማሳ ዓመታት ሙሉ በመድረክ ላይ መቆየት፣ 28 አልበሞችን ማበርከት... ይህ ቁጥር ብቻ አይደለም፤ የትጋት፣ ለጥበብ የመገዛት እና የተሰጥኦ ጥግ ነው። አስቴር ጥበብን ከትጋት ጋር አጣምራ፣ የሰራችው ስራ ሁሉ ወርቅ ሆኖላት፣ በኢትዮጵያውያን ልብ ውስጥ ለዘላለም የነገሰች የጥበብ ጀግና ናት። "ሙዚቃ" ፍቅር ነው፤ "ፍቅርም" ሙዚቃ ነው። ሁለቱም ደግሞ በአንድነት ሲጣመሩ "አስቴር አወቀ" የሚል ትርጉም ይሰጡናል።
ክብር በሥራዋ ለከበረችው...
ክብር ጥበብን አክብራ ላስከበረችን...
ክብር ትውልድን በዜማ እና በፍቅር ላዋሃደችው...ክብርም በስራሽ ሁሉ እድንወድሽ ላደረጉት በስራዎችሽ አሻራቸውን ላኖሩ ከቴዎድሮስ መኩሪያ ላስቱካ
የሰው ልጅ ነፍስ የምትተነፍስበት ጥልቅ ውቅያኖስ "ሙዚቃ"
"ሙዚቃ" እና "ፍቅር" ደግሞ ተነጣጥለው የማይታዩ፣ አንዱ ለአንዱ የተፈጠሩ፣ የሰማይ እና የምድር ያህል የተሳሰሩ የነፍስ ቋንቋዎች ናቸው።
ከትላንት እስከ ዛሬ... ከካሴት ክር እስከ ዲጂታል ዘመን፣ ቴክኖሎጂው ቢለዋወጥም፣ ትውልድ ቢተካካም እነዚህን ሁለት መለኮታዊ ጸጋዎች በአንድ ልብ አዋህዳ፣ ስሜትን በዜማ ሸምና ያቀረበችልን የዘመናቶች ፈርጥ—እሷ አስቴር አወቀ ናት!
የትውልድን ልብ ያንኳኳች፣ ማዕበል እና ጸጥታን በድምጿ ያስማማች የኢትዮጵያ የሙዚቃ ጸጋ! አስቴር የ"ሶል" (Soul)
የፍቅር ንግሥት በድምጿ ጅረት ውስጥ የሰውን ልጅ ጥልቅ የልብ ጓዳ የምትፈትሽ፣ ስንከፋ አባባይ፣ ስንደሰት አጀብ ባይ የሆነች የዘመን ሀብት ናት።
ትዝታን ብቻ አይቀሰቅሱም፤ ገና ሳንኖረው የናፈቀንን፣ በቃላት የማይገለጸውን ያንን ጥልቅ ናፍቆት (መናፍቅነት) በውስጣችን ይፈጥራሉ። "ፍቅር" የሚለውን ቃል ስታዜመው፣ የፍቅርን ፊደል ያልቆጠረው እንኳ በፍቅር ይነድፋል፤ ገና ያላየነውን የፍቅር ብስራት በሙዚቃዋ እንድንኖረው፣ ያላጣጣመነውን ስሜት በምናባችን እንድንስለው ታደርገናለች። ድምጿ ሲሰማ የሌለብን ትዝታ ይጭንብናል፣ የሌለ ስንብት ያስለቅሰናል፣ ገና ያልመጣ ተስፋ ያስፈነድቀናል።
ትላንት አባቶቻችን እና እናቶቻችን ያደመጧትን፣ ዛሬ እኛ በፍቅር እንሰማታለን፤ ነገም ልጆቻችን ይወርሷታል። ጊዜ የማይሽራት፣ ዘመን የማያልፍባት ተወዳጅ አርቲስት!
እስኪ አንድ ሁለቲቱን እንምልክት
"ለመድክ ወይ" የተሰኘውን ይህን ልብ ሰባሪ እና ስሜት አንጀት ሰርስሮ የሚገባ የሙዚቃ ስራ ስናዳምጥ፣ የሰውን ልጅ የፍቅር ስነ-ልቦና፣ የልብ ስብራትን (Heartbreak) እና የመለየትን መራር እውነት በሚያስገርም ጥልቀት ስትፈትሸው እናገኛለን።
ይህ ዘፈን ተራ የሙዚቃ ዜማ አይደለም፤ ይልቁንም አንዲት በፍቅር የተከዳች፣ ማመን ያቃታት እና በትዝታ እስር ቤት ውስጥ የቀረች ነፍስ የምታሰማው የውስጥ ጩኸት ነው።
የዚህን ድንቅ ዘፈን ጥልቅ መልእክት በበሰለ የኪነ-ጥበብ መነጽር ስንተነትነው የሚከተሉትን ህያው እውነታዎች እናገኛለን
1. "ለመድክ ወይ?" ይህ ጥያቄ ተራ መጠይቅ አይደለም። የድንጋጤ እና የመገረም ጩኸት
ያለኔ መኖርን ቻልከው? እኔ ገና የትላንቱን አብሮነታችንን መርሳት አቅቶኝ በትዝታ እሳት እየነደድኩ፣ አንተ ግን እንዴት ያለምንም ህመም የክህደት እና የመገረም ስሜት ነው አንድ ሰው የነፍሱን ግማሽ አድርጎ ያሰበው አካል አዲስ ህይወት በአንድ ጀንበር የሚፈጠረውን የአእምሮ ንዝረት ያሳያል
አስቴር ይህንን ሚዛን የሳተ ፍቅር በጉልህ ታሳያለች።
በፍቅር መለያየት ውስጥ እጅግ አሳማሚው ነገር የህመሙ አለመመጣጠን ነው።
ለአንዱ (ለአፍቃሪዋ) ፍቅር የህይወት መሰረት፣ እስትንፋስ እና አለም ሲሆን፤ ለሌላኛው (ለተፈቃሪው) ግን ፍቅር ጊዜያዊ ማረፊያ፣ በቀላሉ ሊተካ እና ሊረሳ የሚችል ተራ ክስተት ሆኖ እናገኘዋለን። "እኔ እንዲህ ሆኜ፣ አንተ እንዴት ሆንክ?" የሚለው የዘፈኑ የጀርባ አጥንት ይህንን የስሜት መራራቅ ያጋልጣል።ያ የለመደችው ድምፅ፣ ያ የለመደችው መዓዛ በድንገት ሲቋረጥ ነፍስ ባዶ ትቀራለች። አስቴር በዚህ ዘፈኗ፣ መለየቱን አምና ለመቀበል የሚደረገውን የውስጥ ትግል እና የትዝታን አረመኔነት በቃላቷ ትስላለች። "ልመዳ" እንዴት ከባድ እንደሆነና ያንን ማቋረጥ ደግሞ ሞት መሆኑን ልክ አንዲት ሴት ብቻዋን ክፍሏ ውስጥ ሆና የምታነባውን፣ የምታቃስተውን እና ከራሷ ጋር የምታደርገውን ሙግት በዜማ ልክ ሰፍታ ታለብሰናለች።
የናፍቆትን እሳት እና የልብን መታለል ያለምንም ማለዘቢያ ፊት ለፊት
ለመድክ ወይ" የፍቅርን የጨለመ ገፅ ሚያዳምጣት ሁሉ የተወሳሰበ የሰው ልጅ ስሜት ወስዳ
የቆሰለ ልብ ያለው ሁሉ፣ በዚህ ዘፈን ውስጥ የራሱን እንባ ያገኛል!
"ገላ ገላ" በረቂቅ ቃላት የተሳለበት የፍቅር ጸሎት ።
ይህ ዘፈን ተራ የቃላት ድርደራ ሳይሆን፣ አንዲት የሰው ልጅ ነፍስ በፍቅር ስትገዛ፣ ስትማረክ እና ራሷን አሳልፋ ስትሰጥ የሚኖራትን ጥልቅ ስነ-ልቦናዊ እና ስጋዊ ውህደት የሚያሳይ ህያው ማሳያ ነው።
ገላ—የነፍስ ማረፊያ፣ የስሜት መግለጫ እና የፍቅር ቤተ-መቅደስ ነው።
አስቴር "ገላ" ስትል፣ መነካካትን ብቻ ሳይሆን፣ ሁለት ነፍሶች አንድ የሚሆኑበትን፣ መለያየት የሌለበትን ያንን የመጨረሻውን የፍቅር ልዕልና (Intimacy) እየጠራች ነው። ለእሷ ህይወት የሚዘራ፣ ግን ደግሞ ናፍቆትን የሚያባብስ ጣፋጭ እስር ቤት ነው።
አንድ የምታውቀው ፍጹም እውነት ቢኖር የራሷን የልብ ትርታ ነው።
የሷ "ሆድ" (ውስጧ/ነፍሷ) ለእሱ መገዛቱን አምና መቀበሏ፣ በፍቅር ውስጥ ያለውን ያለምንም ቅድመ-ሁኔታ ራስን አሳልፎ የመስጠት ጀግንነት ያሳያል።ፍቅር ከስሜት አልፎ ወደ "መኖር እና አለመኖር" ትርጉም ይሸጋገራል። ፍቅር የልብ ምት ብቻ ሳይሆን፣ ወደ ሳንባ ገብቶ የሚያኖራት ኦክስጅኗ ሆኗል።
የነፍስ ኑዛዜ ነው ገና ያላፈቀረውን "እንዲህ ያለ ጥልቅ ፍቅር ባገኘሁ" ብሎ እንዲመኝ ሲያደርግ፤ ያፈቀረውን ደግሞ የልቡን ቋንቋ አግኝቶለታል።የሰውን ልጅ ድብቅ እና ጥልቅ የልብ ጓዳ ገብታ፣ ትበረብራልች
በሥራ መክበርን" በተግባር በማሳየቷ እንጂ! 40የልማሳ ዓመታት ሙሉ በመድረክ ላይ መቆየት፣ 28 አልበሞችን ማበርከት... ይህ ቁጥር ብቻ አይደለም፤ የትጋት፣ ለጥበብ የመገዛት እና የተሰጥኦ ጥግ ነው። አስቴር ጥበብን ከትጋት ጋር አጣምራ፣ የሰራችው ስራ ሁሉ ወርቅ ሆኖላት፣ በኢትዮጵያውያን ልብ ውስጥ ለዘላለም የነገሰች የጥበብ ጀግና ናት። "ሙዚቃ" ፍቅር ነው፤ "ፍቅርም" ሙዚቃ ነው። ሁለቱም ደግሞ በአንድነት ሲጣመሩ "አስቴር አወቀ" የሚል ትርጉም ይሰጡናል።
ክብር በሥራዋ ለከበረችው...
ክብር ጥበብን አክብራ ላስከበረችን...
ክብር ትውልድን በዜማ እና በፍቅር ላዋሃደችው...ክብርም በስራሽ ሁሉ እድንወድሽ ላደረጉት በስራዎችሽ አሻራቸውን ላኖሩ ከቴዎድሮስ መኩሪያ ላስቱካ
25 days ago
የዜጎችን ሕይወት በዘላቂነት የሚያሻሽሉ ተግባራት ተከናውነዋል - አቶ ሙስጠፋ ሙሀመድ
****************
የሶማሊ ክልል የሴክተር መሥሪያ ቤቶች፣ የዞን እና የከተማ አስተዳደሮች የ2018 በጀት ዓመት አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ በስኬት ተጠናቅቋል።
በዚሁ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ላይ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፋ ሙሀመድ፤ በበጀት ዓመቱ በሥራ አፈጻጸም የታዩ ጠንካራ ጎኖችን አጠናክሮ ማስቀጠልና የተመዘገቡ ድክመቶችንም ደረጃ በደረጃ እያረሙ ለበለጠ ስኬትና ልማት መትጋት እንደሚገባ አሳስበዋል።
በተለይም የዜጎችን ሕይወት በዘላቂነት የሚያሻሽሉ፣ እንዲሁም ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን በከፍተኛ ደረጃ የሚያጎለብቱ ተግባራት ላይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ሊሠራ እንደሚገባ በአጽንኦት ገልጸዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ አክለውም፣ ሀገራዊ ለውጡን ማግስት ጀምሮ በክልሉ በመንገድ መሠረተ-ልማት፣ በውኃ አቅርቦት፣ በጤና አገልግሎት እና በዘላቂ ሰላም ግንባታ ዘርፎች የተመዘገቡ ታሪካዊ ዕድገቶችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በአሁኑ ወቅት በክልሉ የልማት ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ከጊዜ ወደ ጊዜ ትልቅ እምርታ እያሳየ እንደሚገኝ የጠቀሱት አቶ ሙስጠፋ፤ በቀጣይም ማንኛውም ልማታዊ ፕሮጀክት በተቀመጠለት የጊዜ ገደብና የጥራት ደረጃ ተጠናቆ ለሕዝብ አገልግሎት እንዲበቃ በቁርጠኝነት መሥራት እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል።
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ኡስማን በበኩላቸው፤ መንግሥት በተለያዩ ዘርፎች የሕዝባዊ አገልግሎት አሰጣጥን ለማቅለልና ለማዘመን በርካታ መዋቅራዊ የአሠራር ማሻሻዮችን እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በዚህም መሠረት በክልሉ በስፋት የተጀመረውን የ"ፋይዳ" (ብሔራዊ) መታወቂያ አገልግሎት እስከ ታችኛው የቀበሌ መዋቅር ድረስ በስፋት ተደራሽ ለማድረግ የተጀመሩ ስኬታማ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አመልክተዋል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ ተነሳሽነት እየተገበረ በሚገኘው የ"ኢትዮ ኮደርስ" የስልጠና ፕሮግራም አማካኝነት የበርካታ የክልሉ ወጣቶችና ዜጎችን የዲጂታል ክህሎት ማሳደግ መቻሉን ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ገልጸው፤ ይህንን ዘመናዊ ዲጂታል ንቅናቄ በቀጣይም ይበልጥ ለማስፋፋት በትኩረት እንደሚሠራ ጠቁመዋል።
በተጨማሪም በ"ኢትዮጵያ ታምርት" ብሔራዊ ንቅናቄ አማካኝነት በሶማሊ ክልል የሚገኘውን የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ይበልጥ ማነቃቃትና ማገዝ መቻሉን አብራርተዋል።
በቴዎድሮስ ታደሰ
****************
የሶማሊ ክልል የሴክተር መሥሪያ ቤቶች፣ የዞን እና የከተማ አስተዳደሮች የ2018 በጀት ዓመት አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ በስኬት ተጠናቅቋል።
በዚሁ የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ላይ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፋ ሙሀመድ፤ በበጀት ዓመቱ በሥራ አፈጻጸም የታዩ ጠንካራ ጎኖችን አጠናክሮ ማስቀጠልና የተመዘገቡ ድክመቶችንም ደረጃ በደረጃ እያረሙ ለበለጠ ስኬትና ልማት መትጋት እንደሚገባ አሳስበዋል።
በተለይም የዜጎችን ሕይወት በዘላቂነት የሚያሻሽሉ፣ እንዲሁም ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን በከፍተኛ ደረጃ የሚያጎለብቱ ተግባራት ላይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ሊሠራ እንደሚገባ በአጽንኦት ገልጸዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ አክለውም፣ ሀገራዊ ለውጡን ማግስት ጀምሮ በክልሉ በመንገድ መሠረተ-ልማት፣ በውኃ አቅርቦት፣ በጤና አገልግሎት እና በዘላቂ ሰላም ግንባታ ዘርፎች የተመዘገቡ ታሪካዊ ዕድገቶችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በአሁኑ ወቅት በክልሉ የልማት ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ከጊዜ ወደ ጊዜ ትልቅ እምርታ እያሳየ እንደሚገኝ የጠቀሱት አቶ ሙስጠፋ፤ በቀጣይም ማንኛውም ልማታዊ ፕሮጀክት በተቀመጠለት የጊዜ ገደብና የጥራት ደረጃ ተጠናቆ ለሕዝብ አገልግሎት እንዲበቃ በቁርጠኝነት መሥራት እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል።
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ኡስማን በበኩላቸው፤ መንግሥት በተለያዩ ዘርፎች የሕዝባዊ አገልግሎት አሰጣጥን ለማቅለልና ለማዘመን በርካታ መዋቅራዊ የአሠራር ማሻሻዮችን እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በዚህም መሠረት በክልሉ በስፋት የተጀመረውን የ"ፋይዳ" (ብሔራዊ) መታወቂያ አገልግሎት እስከ ታችኛው የቀበሌ መዋቅር ድረስ በስፋት ተደራሽ ለማድረግ የተጀመሩ ስኬታማ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አመልክተዋል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ ተነሳሽነት እየተገበረ በሚገኘው የ"ኢትዮ ኮደርስ" የስልጠና ፕሮግራም አማካኝነት የበርካታ የክልሉ ወጣቶችና ዜጎችን የዲጂታል ክህሎት ማሳደግ መቻሉን ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ ገልጸው፤ ይህንን ዘመናዊ ዲጂታል ንቅናቄ በቀጣይም ይበልጥ ለማስፋፋት በትኩረት እንደሚሠራ ጠቁመዋል።
በተጨማሪም በ"ኢትዮጵያ ታምርት" ብሔራዊ ንቅናቄ አማካኝነት በሶማሊ ክልል የሚገኘውን የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ይበልጥ ማነቃቃትና ማገዝ መቻሉን አብራርተዋል።
በቴዎድሮስ ታደሰ
30 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ዶክተር ቴዎድሮስ አድሀኖም የተሸለሙትን 50,000.00 ዶላር በትግራይ ክልል ለሚንቀሳቀሱ 2 ድርጅቶች አበረከቱ፡፡ የአለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴዎድሮስ አድሀኖም እ.ኤአ በ2023 ከሚችጋን ዩኒቨርስቲ 50 ሺህ ዶላር የተበረከተላቸው መሆኑ ይታወሳል፡፡ ይህንን ገንዘብ በትግራይ ክልል ለሚንቀሳቀሱና በጦርነት ጉዳት የደረሰባቸው ሴቶችን መልሶ በማቋቋም ስራ ላይ ለተሰማሩ ሁለት ድርጅቶች መለገሳቸው ተገልጿል፡፡
ይህን አስመልክቶ ዛሬ በመቀሌ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ እንደተገለፀው ገንዘቡ የተሰጣቸው ማምስ ፎር ማምስ እና የትግራይ ሴቶች ማህበር ናቸው፡፡ ሁለቱ ድርጅቶች ከዚህ ገንዘብ ውስጥ እያንዳንዳቸው 2.6 ሚሊዮን ብር መቀበላቸውን በጋዜጣዊ መግለጫው ወቅት ተናግረዋል፡፡ የማምስ ፎር ማምስ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አሸናፊ አስመላሽ ሲናገሩ ይህ ድጋፍ የተደረገው የትግራይ እናቶች በጣም አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ባሉበት ወቅት መሆኑን ገልፀው ገንዘቡ ሴቶችን መልሶ ለማቋቋም ለሚያደርጉት ጥረት እንደሚያግዛቸው አስረድተዋል፡፡
የትግራይ ሴቶች ማህበር ሊቀመንበር ወይዘሮ አበባ ገብረስላሴ በበኩላቸው ማህበራቸው 2.6 ሚሊዮን ብር መቀበሉን ገልፀው፣ ይህንን ገንዘብ በማህበራቸው አማካኝነት በመረጡት መስክ ስልጠና እየወሰዱ ለሚገኙት ሴቶች ስራ ማስጀመሪያ ለእያንዳንዳቸው 65000 ብር እንደሚሰጡ አስታውቀዋል፡፡ ሁለቱም ድርጅቶች ዶክተር ቴዎድሮስ ላደረጉት ለዚህ በጎ ተግባር ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
ይህን አስመልክቶ ዛሬ በመቀሌ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ እንደተገለፀው ገንዘቡ የተሰጣቸው ማምስ ፎር ማምስ እና የትግራይ ሴቶች ማህበር ናቸው፡፡ ሁለቱ ድርጅቶች ከዚህ ገንዘብ ውስጥ እያንዳንዳቸው 2.6 ሚሊዮን ብር መቀበላቸውን በጋዜጣዊ መግለጫው ወቅት ተናግረዋል፡፡ የማምስ ፎር ማምስ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አሸናፊ አስመላሽ ሲናገሩ ይህ ድጋፍ የተደረገው የትግራይ እናቶች በጣም አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ባሉበት ወቅት መሆኑን ገልፀው ገንዘቡ ሴቶችን መልሶ ለማቋቋም ለሚያደርጉት ጥረት እንደሚያግዛቸው አስረድተዋል፡፡
የትግራይ ሴቶች ማህበር ሊቀመንበር ወይዘሮ አበባ ገብረስላሴ በበኩላቸው ማህበራቸው 2.6 ሚሊዮን ብር መቀበሉን ገልፀው፣ ይህንን ገንዘብ በማህበራቸው አማካኝነት በመረጡት መስክ ስልጠና እየወሰዱ ለሚገኙት ሴቶች ስራ ማስጀመሪያ ለእያንዳንዳቸው 65000 ብር እንደሚሰጡ አስታውቀዋል፡፡ ሁለቱም ድርጅቶች ዶክተር ቴዎድሮስ ላደረጉት ለዚህ በጎ ተግባር ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
1 month ago
እንጅባራ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ ለ14ኛ ጊዜ ያሰለጠናቸውን 818 እጩ መምህራንን አስመረቀ።
#ethiopia | በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የአዊ ብሄ/አስ ዋና አሥተዳዳሪ እና የኮሌጁ ቦርድ ሰብሳቢ ቴዎድሮስ እንዳለው ፥ በትምህርት ሥርዓቱ ላይ የገጠመውን ስብራት ለመጠገን ከተመራቂዎች ብዙ ይጠበቃል ብለዋል።
ቃልኪዳናችሁ እውን እንዲሆን እስከአሁን ያገኛችሁትን እውቀት ትውልዱ ላይ ብርሃን እንዲያበራ ከራሳችሁ ጋር የተስማማችሁ ሁኑ ሲሉም አሳስበዋል ።
ተመራቂ እጩ መምህራን ልጆች የሚፈልጉትን እውቀት ለማስጨበጥ የተዘጋጃችሁ ብቁ ትውልዶች ናችሁ ነው ያሉት።
ትውልዱ ላይ በተሰጣችሁ አደራና በገባችሁት ቃል ኪዳን ላይ አተኩራችሁ ስሩ ብለዋል።
"ሀገር ካለች ሁሉም አለ ያሉት ዋና አስተዳዳሪው በምክንያት የምታምኑ እና ከሁሉም ከግለሰባዊ ጉዳይ ሀገራችሁን አስቀድሙ "ነው ያሉት።
ወደ ፊት ሀገራቸውን እና ሕዝባቸውን በዕውቀታቸው እንዲያገለግሉም መልዕክት አስተላልፈዋል።
የመምህራን ትምህርት ኮሌጅ ዲን ጌታቸው አድማስ፥ተመራቂዎች ከብዙ አመታት ትጋትና ጥረት በኋላ ለምረቃት በመድረሳችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።
መምህራን ትምህርት ኮሌጅ ከተመሠረተ ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ በዲፕሎማ መርሐ ግብር ከ30ሺህ በላይ ምሩቃንን ለሀገር አበርክቷል።
በ2018ዓ.ም በተለያዩ የትምህርት መስኮች ለ14 ዙር በመደበኛው፣በኤክስቴንሽንና በክረምት መርሃ ግብር በዲግሪና በዲፕሎማ ያሠለጠናቸውን 818 እጩ መምህራንን ነው ያስመረቀው።
ከነዚህም ውስጥ በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት የሰለጠኑ ለመጀመሪያ ጊዜ 322 መምህራንን በዲግሪ በማስመረቅ አዲስ የስኬት ምዕራፍ ላይ መድረሱን አቶ ጌታቸው ተናግረዋል።
ኮሌጁ ከመማር ማስተማር ፣ምርምርና የማህበረሰብ አገልግሎት ጎን ለግን ራሱን ለማስተዳደር በተለያዩ የገቢ ማስገኛ ልማቶች ላይ እየተሳተፈ እንደሚገኝ ገልጸዋል ።
ተመራቂዎች የእናንተ አስተምህሮ የነገዋን ኢትዮጲያ የሚቀርፅ ነው ብለዋል። ስለሆነም በመምህርነት ሙያችሁ የትውልድንና የሀገርን አደራ እንድትወጡ ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
መምህር ማለት ህዝብን የመገንባት ተልዕኮ ነው ያሉት ዲኑ የዛሬ የዲግሪና የዲፕሎማ ሰርትፍኬት የጉዞ መጨረሻ ሳይሆን የአዲስ ሀላፊነት መጀመሪያ ነው ብለዋል።
ወላጆች የኢኮኖሚ ችግር ተቋቁማችሁ ለልጆቻችሁ ትምህርት ቅድሚያ ሰጣችሁ አስተምራችኋልና ክብር ይገባችኋል ።
በትምህርት የመገንባት ሂደት ላይ የተሳተፉትን መምህራን ፣የኮሌጁ አመራሮች እና ሰራተኞች ዲኑ አመስግነዋል።
ተመራቂ ተማሪዎች ከኮሌጁ ባገኙት ዕውቀት እና ክህሎት ለአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ተግበራ የሚጠበቅባቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል።
ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ እጩ መምህራን የዋንጫና የሜዳልያ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
#ethiopia | በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የአዊ ብሄ/አስ ዋና አሥተዳዳሪ እና የኮሌጁ ቦርድ ሰብሳቢ ቴዎድሮስ እንዳለው ፥ በትምህርት ሥርዓቱ ላይ የገጠመውን ስብራት ለመጠገን ከተመራቂዎች ብዙ ይጠበቃል ብለዋል።
ቃልኪዳናችሁ እውን እንዲሆን እስከአሁን ያገኛችሁትን እውቀት ትውልዱ ላይ ብርሃን እንዲያበራ ከራሳችሁ ጋር የተስማማችሁ ሁኑ ሲሉም አሳስበዋል ።
ተመራቂ እጩ መምህራን ልጆች የሚፈልጉትን እውቀት ለማስጨበጥ የተዘጋጃችሁ ብቁ ትውልዶች ናችሁ ነው ያሉት።
ትውልዱ ላይ በተሰጣችሁ አደራና በገባችሁት ቃል ኪዳን ላይ አተኩራችሁ ስሩ ብለዋል።
"ሀገር ካለች ሁሉም አለ ያሉት ዋና አስተዳዳሪው በምክንያት የምታምኑ እና ከሁሉም ከግለሰባዊ ጉዳይ ሀገራችሁን አስቀድሙ "ነው ያሉት።
ወደ ፊት ሀገራቸውን እና ሕዝባቸውን በዕውቀታቸው እንዲያገለግሉም መልዕክት አስተላልፈዋል።
የመምህራን ትምህርት ኮሌጅ ዲን ጌታቸው አድማስ፥ተመራቂዎች ከብዙ አመታት ትጋትና ጥረት በኋላ ለምረቃት በመድረሳችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።
መምህራን ትምህርት ኮሌጅ ከተመሠረተ ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ በዲፕሎማ መርሐ ግብር ከ30ሺህ በላይ ምሩቃንን ለሀገር አበርክቷል።
በ2018ዓ.ም በተለያዩ የትምህርት መስኮች ለ14 ዙር በመደበኛው፣በኤክስቴንሽንና በክረምት መርሃ ግብር በዲግሪና በዲፕሎማ ያሠለጠናቸውን 818 እጩ መምህራንን ነው ያስመረቀው።
ከነዚህም ውስጥ በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት የሰለጠኑ ለመጀመሪያ ጊዜ 322 መምህራንን በዲግሪ በማስመረቅ አዲስ የስኬት ምዕራፍ ላይ መድረሱን አቶ ጌታቸው ተናግረዋል።
ኮሌጁ ከመማር ማስተማር ፣ምርምርና የማህበረሰብ አገልግሎት ጎን ለግን ራሱን ለማስተዳደር በተለያዩ የገቢ ማስገኛ ልማቶች ላይ እየተሳተፈ እንደሚገኝ ገልጸዋል ።
ተመራቂዎች የእናንተ አስተምህሮ የነገዋን ኢትዮጲያ የሚቀርፅ ነው ብለዋል። ስለሆነም በመምህርነት ሙያችሁ የትውልድንና የሀገርን አደራ እንድትወጡ ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
መምህር ማለት ህዝብን የመገንባት ተልዕኮ ነው ያሉት ዲኑ የዛሬ የዲግሪና የዲፕሎማ ሰርትፍኬት የጉዞ መጨረሻ ሳይሆን የአዲስ ሀላፊነት መጀመሪያ ነው ብለዋል።
ወላጆች የኢኮኖሚ ችግር ተቋቁማችሁ ለልጆቻችሁ ትምህርት ቅድሚያ ሰጣችሁ አስተምራችኋልና ክብር ይገባችኋል ።
በትምህርት የመገንባት ሂደት ላይ የተሳተፉትን መምህራን ፣የኮሌጁ አመራሮች እና ሰራተኞች ዲኑ አመስግነዋል።
ተመራቂ ተማሪዎች ከኮሌጁ ባገኙት ዕውቀት እና ክህሎት ለአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ተግበራ የሚጠበቅባቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል።
ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ እጩ መምህራን የዋንጫና የሜዳልያ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
1 month ago
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ወደ ራስ-ገዝነት፤ ከልቀት ማዕከልነት እስከ ዘመናዊ ግብርና እና ዲጂታላይዜሽን
#ethiopia | የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከሀገሪቱ ቀዳሚ ተቋማት አንዱ በመሆን ወደ ሙሉ ራስ-ገዝነት ለመሸጋገር የሚያስችሉትን ሰፊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ማጠናቀቁን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት አስራት አጸደወይን (ዶ/ር) ገለጹ።
ፕሬዝዳንቱ እንደገለጹት፣ ይህ የራስ-ገዝነት ጉዞ ተቋሙ የተሻለ አካዳሚያዊ፣ አስተዳደራዊ እና የፋይናንስ ነጻነት ጎናጽፎ የላቀ ተልዕኮውን እንዲያሳካ ሰፊ በር ይከፍትለታል። ለዚህም ስኬት ይረዳ ዘንድ በዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብና በከተማው ምክር ቤት ደረጃ ሰፊ የግንዛቤ ፈጠራ ስራዎች መከናወናቸውን ያነሱት አስራት (ዶ/ር)፣ ራስ-ገዝነት ነጻነትን ብቻ ሳይሆን ተጠያቂነትንም አብሮ የሚያሰፍን መሆኑን አስገንዝበዋል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ በሽግግሩ ወቅት መመሪያ የሚሆኑ 55 ያህል ልዩ ልዩ ስትራቴጂካዊ ፖሊሲዎችና ሰነዶች ተዘጋጅተው ለትምህርት ሚኒስቴር ገቢ መደረጋቸውንና በውጭ ባለሙያዎች በተደረገው የዝግጁነት ግምገማም ዩኒቨርሲቲው እጅግ አበረታች ውጤት ማስመዝገቡን በኩራት ገልጸዋል።
ዩኒቨርሲቲው ከመንግስት የሚገኘውን የፋይናንስ ድጋፍ በሂደት በመቀነስ ራሱን ለመቻል የገቢ ምንጮቹን እያሰፋ መሆኑን ፕሬዝዳንቱ አስረድተዋል። በዚህም መሰረት በ"እቴጌ ምንትዋብ ንግድና ማማከር ኢንተርፕራይዝ" ስር ደረጃቸውን የጠበቁ እንደ ማተሚያ ቤት፣ ሞዴል ፋርማሲ፣ የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ (ICT) እና የምህንድስና ማማከር አገልግሎቶችን ጨምሮ ወደ አስር የሚጠጉ የገቢ ማስገኛ ዲፓርትመንቶች ተቋቁመው ስራ ጀምረዋል።
አስራት (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ እነዚህ ተቋማት ለዩኒቨርሲቲው ተጨማሪ ሀብት ከመፍጠርና ለአካባቢው ወጣቶች የስራ እድል ከመስጠት ባለፈ፣ ለተማሪዎች እንደ ተግባራዊ መማሪያ ቤተ-ሙከራ በመሆን እያገለገሉ ይገኛሉ።
በተጨማሪም ጥራታቸውን የጠበቁ ምርቶችና መድኃኒቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ የአካባቢውን የገበያ ዋጋ በማረጋጋት ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን አብራርተዋል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ቀደም ሲል በጤናው ዘርፍ ብቻ ከነበረው የልቀት ማዕከልነት ወጥቶ አሁን ላይ በ11 ኮሌጆች ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ፕሬዝዳንቱ ጠቁመዋል። በተለይም በከተማ ግብርና ዙሪያ በአጼ ቴዎድሮስና በፋሲል ግቢዎች እንዲሁም በጎርጎራ ጣቢያ ሰፋፊ የአትክልት፣ ፍራፍሬና የቡና ልማት ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።
አርሶ አደሩን በዘመናዊ የግብርና ቴክኖሎጂ ለማደራጀትና አመለካከቱን ለመቀየር የትራክተሮችና የኮምባይነር ሀርቨስተር አቅርቦቶችን በማመቻቸት የግብርና መካናይዜሽን ስራዎችን እያስተዋወቁ መሆናቸውን አስራት (ዶ/ር) ጠቅሰዋል።
ዩኒቨርሲቲው በየዓመቱ የገበሬዎች ቀንን በማክበር የልምድ ልውውጥ መድረኮችንና ኤግዚቢሽኖችን እያዘጋጀ ሲሆን፣ ይህም ማህበረሰቡ የተመጣጠነ ምግብ እንዲያገኝና የአካባቢው ምርታማነት እንዲያድግ ትልቅ መነቃቃት መፍጠሩን አብራርተዋል።
በመጨረሻም ተቋሙ የሀገሪቱን የዲጂታል 2030 እቅድ ለማሳካት በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ፕሬዝዳንቱ አረጋግጠዋል።
ለዚህም ይረዳ ዘንድ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) የምርምር ማዕከል መከፈቱንና በዘርፉ የማስተርስና የፒኤችዲ ፕሮግራሞች መጀመራቸውን ገልጸዋል። ዩኒቨርሲቲው አሰራሩን ሙሉ በሙሉ ወረቀት አልባ (paperless) ለማድረግ የፋይናንስ፣ የግዢ፣ የንብረት አስተዳደርና የምርምር ግምገማዎችን በዘመናዊ ዲጂታል ሲስተሞች ማከናወን መጀመሩን አስራት (ዶ/ር) አስታውቀዋል።
ይህ የቴክኖሎጂ ሽግግር አላስፈላጊ ወጪዎችን በከፍተኛ ደረጃ የመቀነስ፣ ውጤታማነትን የማሳደግና ተጠያቂነትን የማስፈን አቅም እንዳለው የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፣ በአሁኑ ወቅት ግንባታው እየተጠናቀቀ የሚገኘው ዘመናዊ የዳታ ሴንተርና የዋን ካርድ (One Card) ሲስተም መሰረተ ልማቶች ተቋሙን ይበልጥ ወደላቀ የዲጂታል ምዕራፍ እንደሚያሸጋግሩት እምነታቸውን ገልጸዋል።
በጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia #gondaruniversity #education #የጎንደርዩኒቨርሲቲ
#ethiopia | የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከሀገሪቱ ቀዳሚ ተቋማት አንዱ በመሆን ወደ ሙሉ ራስ-ገዝነት ለመሸጋገር የሚያስችሉትን ሰፊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ማጠናቀቁን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት አስራት አጸደወይን (ዶ/ር) ገለጹ።
ፕሬዝዳንቱ እንደገለጹት፣ ይህ የራስ-ገዝነት ጉዞ ተቋሙ የተሻለ አካዳሚያዊ፣ አስተዳደራዊ እና የፋይናንስ ነጻነት ጎናጽፎ የላቀ ተልዕኮውን እንዲያሳካ ሰፊ በር ይከፍትለታል። ለዚህም ስኬት ይረዳ ዘንድ በዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብና በከተማው ምክር ቤት ደረጃ ሰፊ የግንዛቤ ፈጠራ ስራዎች መከናወናቸውን ያነሱት አስራት (ዶ/ር)፣ ራስ-ገዝነት ነጻነትን ብቻ ሳይሆን ተጠያቂነትንም አብሮ የሚያሰፍን መሆኑን አስገንዝበዋል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ በሽግግሩ ወቅት መመሪያ የሚሆኑ 55 ያህል ልዩ ልዩ ስትራቴጂካዊ ፖሊሲዎችና ሰነዶች ተዘጋጅተው ለትምህርት ሚኒስቴር ገቢ መደረጋቸውንና በውጭ ባለሙያዎች በተደረገው የዝግጁነት ግምገማም ዩኒቨርሲቲው እጅግ አበረታች ውጤት ማስመዝገቡን በኩራት ገልጸዋል።
ዩኒቨርሲቲው ከመንግስት የሚገኘውን የፋይናንስ ድጋፍ በሂደት በመቀነስ ራሱን ለመቻል የገቢ ምንጮቹን እያሰፋ መሆኑን ፕሬዝዳንቱ አስረድተዋል። በዚህም መሰረት በ"እቴጌ ምንትዋብ ንግድና ማማከር ኢንተርፕራይዝ" ስር ደረጃቸውን የጠበቁ እንደ ማተሚያ ቤት፣ ሞዴል ፋርማሲ፣ የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ (ICT) እና የምህንድስና ማማከር አገልግሎቶችን ጨምሮ ወደ አስር የሚጠጉ የገቢ ማስገኛ ዲፓርትመንቶች ተቋቁመው ስራ ጀምረዋል።
አስራት (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ እነዚህ ተቋማት ለዩኒቨርሲቲው ተጨማሪ ሀብት ከመፍጠርና ለአካባቢው ወጣቶች የስራ እድል ከመስጠት ባለፈ፣ ለተማሪዎች እንደ ተግባራዊ መማሪያ ቤተ-ሙከራ በመሆን እያገለገሉ ይገኛሉ።
በተጨማሪም ጥራታቸውን የጠበቁ ምርቶችና መድኃኒቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ የአካባቢውን የገበያ ዋጋ በማረጋጋት ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን አብራርተዋል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ቀደም ሲል በጤናው ዘርፍ ብቻ ከነበረው የልቀት ማዕከልነት ወጥቶ አሁን ላይ በ11 ኮሌጆች ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ፕሬዝዳንቱ ጠቁመዋል። በተለይም በከተማ ግብርና ዙሪያ በአጼ ቴዎድሮስና በፋሲል ግቢዎች እንዲሁም በጎርጎራ ጣቢያ ሰፋፊ የአትክልት፣ ፍራፍሬና የቡና ልማት ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።
አርሶ አደሩን በዘመናዊ የግብርና ቴክኖሎጂ ለማደራጀትና አመለካከቱን ለመቀየር የትራክተሮችና የኮምባይነር ሀርቨስተር አቅርቦቶችን በማመቻቸት የግብርና መካናይዜሽን ስራዎችን እያስተዋወቁ መሆናቸውን አስራት (ዶ/ር) ጠቅሰዋል።
ዩኒቨርሲቲው በየዓመቱ የገበሬዎች ቀንን በማክበር የልምድ ልውውጥ መድረኮችንና ኤግዚቢሽኖችን እያዘጋጀ ሲሆን፣ ይህም ማህበረሰቡ የተመጣጠነ ምግብ እንዲያገኝና የአካባቢው ምርታማነት እንዲያድግ ትልቅ መነቃቃት መፍጠሩን አብራርተዋል።
በመጨረሻም ተቋሙ የሀገሪቱን የዲጂታል 2030 እቅድ ለማሳካት በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ፕሬዝዳንቱ አረጋግጠዋል።
ለዚህም ይረዳ ዘንድ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) የምርምር ማዕከል መከፈቱንና በዘርፉ የማስተርስና የፒኤችዲ ፕሮግራሞች መጀመራቸውን ገልጸዋል። ዩኒቨርሲቲው አሰራሩን ሙሉ በሙሉ ወረቀት አልባ (paperless) ለማድረግ የፋይናንስ፣ የግዢ፣ የንብረት አስተዳደርና የምርምር ግምገማዎችን በዘመናዊ ዲጂታል ሲስተሞች ማከናወን መጀመሩን አስራት (ዶ/ር) አስታውቀዋል።
ይህ የቴክኖሎጂ ሽግግር አላስፈላጊ ወጪዎችን በከፍተኛ ደረጃ የመቀነስ፣ ውጤታማነትን የማሳደግና ተጠያቂነትን የማስፈን አቅም እንዳለው የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፣ በአሁኑ ወቅት ግንባታው እየተጠናቀቀ የሚገኘው ዘመናዊ የዳታ ሴንተርና የዋን ካርድ (One Card) ሲስተም መሰረተ ልማቶች ተቋሙን ይበልጥ ወደላቀ የዲጂታል ምዕራፍ እንደሚያሸጋግሩት እምነታቸውን ገልጸዋል።
በጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia #gondaruniversity #education #የጎንደርዩኒቨርሲቲ
1 month ago
ከ170 በላይ ለጎርፍ አደጋ ተጋላጭ የሆኑ ሰዎች እንዲነሱ መደረጉ ተገለፀ
በድሬዳዋ በክረምት ወቅት በተለያየ ጊዜ ጎርፍ እንደሚከሰት የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር መንገዶች ባለስልጣን አስታውቋል።
የባለስልጣኑ ስራ አስኪያጅ አቶ ቴዎድሮስ ፍቅሬ እንደገለፁት ይህ ሁኔታ ዳግም አደጋ እንዳያስከትል ስድስት ቦታዎችን ቀድሞ በመለየት የተለያዩ ስራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል።
የችግሩን አሳሳቢነት በመረዳት በበጋ ወቅት ጀምሮ ለጎርፍ አደጋ ተጋላጭ ናቸው ተብለው የተለዩ ከ 170 በላይ ሰዎች ለጊዜያዊነት ወደ ሌላ ቦታ እንዲሰፍሩ መደረጉን ገልፀዋል።
ጎርፍ የሚበዛባቸው አካባቢዎች አስቀድሞ እርከን እየተሰራላቸው እንደሆነና በከተማዋ ከጥገና ባለፈ ማህበረሰቡ በቂ የሆነ ግንዛቤ እንዲያገኝ እየተደረገ መሆኑንም አስረድተዋል።
ከዚህ በፊት በከተማዋ የጎርፍ አደጋ ሲከሰት ብዙ ንብረትን ጨምሮ በሰዎች ላይ ከፍተኛ የሆነ ጉዳት እንደሚያስከትል የገለፁት አቶ ቴዎድሮስ፣ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ይህ ችግር እየተቀረፈ መምጣቱን ገልጸዋል።
አሐዱ_
በድሬዳዋ በክረምት ወቅት በተለያየ ጊዜ ጎርፍ እንደሚከሰት የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር መንገዶች ባለስልጣን አስታውቋል።
የባለስልጣኑ ስራ አስኪያጅ አቶ ቴዎድሮስ ፍቅሬ እንደገለፁት ይህ ሁኔታ ዳግም አደጋ እንዳያስከትል ስድስት ቦታዎችን ቀድሞ በመለየት የተለያዩ ስራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል።
የችግሩን አሳሳቢነት በመረዳት በበጋ ወቅት ጀምሮ ለጎርፍ አደጋ ተጋላጭ ናቸው ተብለው የተለዩ ከ 170 በላይ ሰዎች ለጊዜያዊነት ወደ ሌላ ቦታ እንዲሰፍሩ መደረጉን ገልፀዋል።
ጎርፍ የሚበዛባቸው አካባቢዎች አስቀድሞ እርከን እየተሰራላቸው እንደሆነና በከተማዋ ከጥገና ባለፈ ማህበረሰቡ በቂ የሆነ ግንዛቤ እንዲያገኝ እየተደረገ መሆኑንም አስረድተዋል።
ከዚህ በፊት በከተማዋ የጎርፍ አደጋ ሲከሰት ብዙ ንብረትን ጨምሮ በሰዎች ላይ ከፍተኛ የሆነ ጉዳት እንደሚያስከትል የገለፁት አቶ ቴዎድሮስ፣ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ይህ ችግር እየተቀረፈ መምጣቱን ገልጸዋል።
አሐዱ_
Sponsored by
Surafel
1 month ago
እንደገና የተወለደው ቀበና…
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የእንጦጦ-ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በቅርቡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ከንቲባ አዳነች አቤቤ በተገኙበት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል፡፡
በ87 ነጥብ 6 ሔክታር መሬት ያረፈው እና 10 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው ፕሮጀክቱ የወንዝ መከላከያ ግንቦችን፣ ዘመናዊ ድልድዮችን እና ሰፊ አረንጓዴ ሥፍራዎችን ይዟል።
ይህ ቀበናን ውብ ገጽታ ያለበሰው እና የትውልድ ዐሻራ ያረፈበት ፕሮጀክት ነዋሪዎቿን አስደስቷል።
የቀበና ነዋሪዎቹ አቶ አለማየሁ፣ አቶ አወቀ እና ወ/ሮ መሰሉ ስለ ቀበና ልማት ድሮና ዘንድሮን እያነሱ ከፋና ፖድካስት ጋር ቆይታ አድርገዋል፡፡
አቶ አወቀ÷ የነዋሪው ቁጥር እየጨመረ ሲመጣ ንጹህ የነበረው የቀበና ወንዝ እየተበከለ እና የመጸዳጃ ቤት ፍሳሽ እየተለቀቀበት ቀድሞ የነበረውን ውበትና ገፅታውን እንዳጣ ያስታውሳሉ፡፡ በዚህ ምክንያት ለነዋሪው የማይመች እና ጤናን የሚነሳ ሆነ ይላሉ፡፡
ቀበና አካባቢ ተወልደው ላለፉት 49 ዓመታት የኖሩት ወ/ሮ መሰሉ በበኩላቸው÷ የቀበና የቀድሞ ገፅታ በጫካ የተሸፈነ መሆኑን ይናገራሉ። በቀበና ወንዝ ቅዳሜ እና እሑድ ልጆች ጊዜያቸውን በዋና እና ሌሎች ጨዋታዎች የሚያሳልፉበት እንደነበር ያስታውሳሉ።
በሒደትም ቦታው መበከሉንና ለመዋኘት ቀርቶ ለማየት ደስ ወደማይል ገጽታ መቀየሩን ነው የሚያስረዱት፡፡
ሌላው የቀበና ነዋሪ አቶ አለማየሁ በ1959 ዓ.ም ነው በቀበና የተወለዱት፡፡ ስለአከባቢውም ብዙ ትዝታ አላቸው፡፡ መንገዱ አስቸጋሪ ስለነበር እና በአንድ ወቅት አዳልጧቸው ቀበና ወንዝ ውስጥ በመግባታቸው ከስራ እንደቀሩ ያስታውሳሉ፡፡ አሁን ያ ሁሉ ተለውጦ እንዲህ ተውቦ በማየታቸው "ራሴን እንደ እድለኛ እቆጥረዋለሁ" ይላሉ፡፡
"ቀደምት ሰዎች እኔ ያየሁትን ቢያዩ" ሲሉ ቁጭታቸውን የገለፁት ነዋሪው በተወለዱበት ቦታ ላይ በአሁኑ ወቅት ውብ የህጻናት መጫወቻ መሰራቱን በማየታቸው እንደተደሰቱ ተናግረዋል። አቶ አለማየሁ በዚህ ምክንያት "አባቴ እዛ ቦታ ላይ ሐውልት እንደተሰራለት እቆጥረዋለሁ" ሲሉም የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል፡፡
ወ/ሮ መሰሉ በተሰራው ልማት የቀበና ገጽታ ተለውጦ በማየታቸው መደሰታቸውን ገልጸው÷ ልጆች እና ወጣቶች ምቹና ጤናማ በሆነ አካባቢ እንዲያድጉ ያስችላል ብለዋል፡፡
በልማቱ ቀበና ውበት መላበሷ እንዳስደሰታቸው የሚናገሩት አቶ አወቀ÷ የአካባቢው ማሕበረሰብ ከልማቱ ተጠቃሚ በመሆኑ ሊጠብቀውና ሊንከባከበው ይገባል ሲሉ አስገንዝበዋል፡፡
ቀበና ድምጻዊ ጸሀዬ ዮሐንስ የተወለደባት፣ የቦረቀባት፣ የዋኘባትና ያዜመላት መሆኗን የገለጹት አቶ አወቀ÷ "ጸሐዬ ቀበና ላይ የሙዚቃ ድግስ አዘጋጅቶ ቀበናን ቀበና ማሰኘት አለበት" ነው ያሉት፡፡
በቴዎድሮስ ሳህለ
የቀበና ነዋሪዎች ከፋና ፖድካስት ጋር ያደረጉትን ቆይታ ለመከታተል ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ https://youtube.com/watch?...
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የእንጦጦ-ቀበና የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በቅርቡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ከንቲባ አዳነች አቤቤ በተገኙበት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል፡፡
በ87 ነጥብ 6 ሔክታር መሬት ያረፈው እና 10 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው ፕሮጀክቱ የወንዝ መከላከያ ግንቦችን፣ ዘመናዊ ድልድዮችን እና ሰፊ አረንጓዴ ሥፍራዎችን ይዟል።
ይህ ቀበናን ውብ ገጽታ ያለበሰው እና የትውልድ ዐሻራ ያረፈበት ፕሮጀክት ነዋሪዎቿን አስደስቷል።
የቀበና ነዋሪዎቹ አቶ አለማየሁ፣ አቶ አወቀ እና ወ/ሮ መሰሉ ስለ ቀበና ልማት ድሮና ዘንድሮን እያነሱ ከፋና ፖድካስት ጋር ቆይታ አድርገዋል፡፡
አቶ አወቀ÷ የነዋሪው ቁጥር እየጨመረ ሲመጣ ንጹህ የነበረው የቀበና ወንዝ እየተበከለ እና የመጸዳጃ ቤት ፍሳሽ እየተለቀቀበት ቀድሞ የነበረውን ውበትና ገፅታውን እንዳጣ ያስታውሳሉ፡፡ በዚህ ምክንያት ለነዋሪው የማይመች እና ጤናን የሚነሳ ሆነ ይላሉ፡፡
ቀበና አካባቢ ተወልደው ላለፉት 49 ዓመታት የኖሩት ወ/ሮ መሰሉ በበኩላቸው÷ የቀበና የቀድሞ ገፅታ በጫካ የተሸፈነ መሆኑን ይናገራሉ። በቀበና ወንዝ ቅዳሜ እና እሑድ ልጆች ጊዜያቸውን በዋና እና ሌሎች ጨዋታዎች የሚያሳልፉበት እንደነበር ያስታውሳሉ።
በሒደትም ቦታው መበከሉንና ለመዋኘት ቀርቶ ለማየት ደስ ወደማይል ገጽታ መቀየሩን ነው የሚያስረዱት፡፡
ሌላው የቀበና ነዋሪ አቶ አለማየሁ በ1959 ዓ.ም ነው በቀበና የተወለዱት፡፡ ስለአከባቢውም ብዙ ትዝታ አላቸው፡፡ መንገዱ አስቸጋሪ ስለነበር እና በአንድ ወቅት አዳልጧቸው ቀበና ወንዝ ውስጥ በመግባታቸው ከስራ እንደቀሩ ያስታውሳሉ፡፡ አሁን ያ ሁሉ ተለውጦ እንዲህ ተውቦ በማየታቸው "ራሴን እንደ እድለኛ እቆጥረዋለሁ" ይላሉ፡፡
"ቀደምት ሰዎች እኔ ያየሁትን ቢያዩ" ሲሉ ቁጭታቸውን የገለፁት ነዋሪው በተወለዱበት ቦታ ላይ በአሁኑ ወቅት ውብ የህጻናት መጫወቻ መሰራቱን በማየታቸው እንደተደሰቱ ተናግረዋል። አቶ አለማየሁ በዚህ ምክንያት "አባቴ እዛ ቦታ ላይ ሐውልት እንደተሰራለት እቆጥረዋለሁ" ሲሉም የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል፡፡
ወ/ሮ መሰሉ በተሰራው ልማት የቀበና ገጽታ ተለውጦ በማየታቸው መደሰታቸውን ገልጸው÷ ልጆች እና ወጣቶች ምቹና ጤናማ በሆነ አካባቢ እንዲያድጉ ያስችላል ብለዋል፡፡
በልማቱ ቀበና ውበት መላበሷ እንዳስደሰታቸው የሚናገሩት አቶ አወቀ÷ የአካባቢው ማሕበረሰብ ከልማቱ ተጠቃሚ በመሆኑ ሊጠብቀውና ሊንከባከበው ይገባል ሲሉ አስገንዝበዋል፡፡
ቀበና ድምጻዊ ጸሀዬ ዮሐንስ የተወለደባት፣ የቦረቀባት፣ የዋኘባትና ያዜመላት መሆኗን የገለጹት አቶ አወቀ÷ "ጸሐዬ ቀበና ላይ የሙዚቃ ድግስ አዘጋጅቶ ቀበናን ቀበና ማሰኘት አለበት" ነው ያሉት፡፡
በቴዎድሮስ ሳህለ
የቀበና ነዋሪዎች ከፋና ፖድካስት ጋር ያደረጉትን ቆይታ ለመከታተል ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ https://youtube.com/watch?...
1 month ago
አድናቂም ወዳጅ ይሆናል!
ጊዜው በ90 ዎቹ መጀመሪያ ግድም ነው፡፡ በቢሾፍቱ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪ ሳለን በሀገራችን ታዋቂ ከሚባሉት የሙዚቃ ባንዶች አንዱ የሜጋ አምፊ ቲያትር ራሚድ ባንድ ነበር።
አንድ ቀን ዝነኛው ራሚድ ባንድ የሙዚቃ ድግሱን ለማቅረብ፣ ከአዲስ አበባ ወደ ቢሾፍቱ መጥቶ ነበር፡፡ ከባንዱ ጋር ዝግጅታቸውን ሊያቀርቡ ከመጡት ተወዳጅና ታዋቂ አርቲስቶች መካከል፡- ላፎንቴኖች ፣ ጎሳዬ ተስፋዬ ፣ ፍቅርአዲስ ነቃጥበብ፣ መልካሙ ተበጀ ፣ ጀማል መሀመድ(አቺኩዳ)፣ ፀደንያ ገ/ማርቆስ ፣ ማናልቦሽ ዲቦ፣ ደረጀና ሀብቴ፣ጥላሁን እልፍነህ ፣ ዘውዱ በቀለና ፊሊፕ ማርቲን ይገኙበታል፡፡
የሙዚቃ ዝግጅቱን ለመታደም የከተማችን ነዋሪ በወረፋ ነበር ወደ አዳራሹ የገባው፡፡ እኔም ዝግጅቱን በገጉት ሲጠባበቁ ከነበሩት መካከል አንዱ ነኝ፡፡ አርቲስቶችን ለማስፈረም ሁሉ በኪሴ በቂ ወረቀቶችን ይዤ ነበር የገባሁት፡፡ በወቅቱ ሁሉንም አርቲስቶች የማደንቅ ቢሆንም፣ በተለይ ደግሞ ኮሜዲያን ደረጀንና ሃብቴን ለማየትና ከተቻለም ለማስፈረም በእጅጉ ጓጉቼ ነበር።
በመጨረሻም በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው ታላቅ የሙዚቃ ድግስ በይፋ ተጀመረ፡፡ እውነት ለመናገር አንድም ቤቱ የቀረ የቢሾፍቱ ነዋሪ ያለ አይመስልም ነበር፡፡ በቴሌቪዥን መስኮት ብቻ የምናቃቸው ተወዳጅና ዝነኛ ድምጻውያን በየተራ መድረክ ላይ እየወጡ አቀነቀኑ፡፡ ታዳሚው አብሯቸው እየዘፈነ እንደጉድ ጨፈረ፡፡ አዳራሹን በአንድ እግሩ አቆመው፡፡
የመድረክ አጋፋሪው ጥላሁን እልፍነህ፣ በመቀጠል ሥራቸውን የሚያቀርቡት ሁለቱ ተወዳጅ ኮሜዲያን እንደሆኑ ሲያስተዋውቅ፣ ታዳሚው በጩኸትና በፉጨት ደስታውንና ፍቅሩን ገለጸ፡፡ ደረጀና ሃብቴም ወደ መድረኩ ወጥተው በማያልቀው ቀልዳቸውና ለዛቸው አዳራሹን በሳቅ ሞሉት፡፡
ሥራቸውን አቅርበው እንደጨረሱ ከተጠገጠገው ሰው መሃል እንዴት ተፈትልኬ እንደወጣሁ ሳላውቀው፣ ራሴን መድረኩ አጠገብ አገኘሁት፡፡ ከዚያም አሻቅቤ ወደ ደረጀና ሃብቴ እየተመለከትኩ፣ "ፈርሙልኝ" አልኳቸው - ያዘጋጀሁትን ወረቀት ዘርግቼ፡፡ አንዳቸው ስሜን ጠየቁኝ፡፡ ነገርኳቸው፡፡ ከዚያም ከመድረኩ ጀርባ (ባክ ስቴጅ)ይዘውኝ ገቡ። እዚያ ሌሎችም ታዋቂ አርቲስቶች ነበሩ፡፡ አጋጣሚውን ተጠቅሜ ሁሉንም አስፈረምኳቸው፡፡
ተልዕኮዬን አጠናቅቄ ከመሄዴ በፊት ግን ኮሜዲያን ሀብቴ ምትኩ ለእነርሱ ከተዘጋጀው ሳንዱች ላይ አንስቶ እንድበላ ጋበዘኝ፡፡ በጣም ነበር ደስ ያለኝ፡፡ በአንዳች በማላውቀው ስሜት ተጥለቅልቄ ነበር፡፡ በቲቪ ብቻ እያየኋቸው የማደንቃቸውና የምወዳቸው ደረጀና ሀብቴ፣ የቅርብ ጓደኞቼ የሆኑ ያህል ተሰምቶኝ ነበር ብል ፈጽሞ አላጋነንኩም፡፡
ከዚያን ጊዜ በኋላ ታዲያ ደረጀና ሃብቴ እንዲሁም ሌሎች አርቲስቶች የፈረሙልኝን ወረቀት ት/ቤት ድረስ በመውሰድ ለጓደኞቼ እያሳየሁ፣ "ደረጃዬን" እንዲያውቁልኝ እጋጋጥ እንደነበር አስታውሳለሁ፡፡ "እኔኮ ከደረጄና ሃብቴ ጋር ጓደኛ ነኝ" እያልኩኝ፣ አብሬያቸው ሳንድዊች መብላቴን ሁሉ በማስረጃነት አቀርብ ነበር፡፡
ይሄ ሁሉ የሆነው በታዳጊነት ዕድሜ ላይ ነው - በተማሪነት ዘመን፡፡ ዛሬ ላይ ተወዳጁ ኮሜዲያን ደረጀ የቅርብ ጓደኛዬና ወዳጄ ብቻ ሳይሆን ወንድሜም ጭምር ነው፡፡
ደሬ፤ እንኳን ተወለድክልን !
ረዥም ዕድሜና ጤና እመኝልሃለሁ!
አክባሪህና ወዳጅህ ቴዎድሮስ ታደሰ አየለ
ጊዜው በ90 ዎቹ መጀመሪያ ግድም ነው፡፡ በቢሾፍቱ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪ ሳለን በሀገራችን ታዋቂ ከሚባሉት የሙዚቃ ባንዶች አንዱ የሜጋ አምፊ ቲያትር ራሚድ ባንድ ነበር።
አንድ ቀን ዝነኛው ራሚድ ባንድ የሙዚቃ ድግሱን ለማቅረብ፣ ከአዲስ አበባ ወደ ቢሾፍቱ መጥቶ ነበር፡፡ ከባንዱ ጋር ዝግጅታቸውን ሊያቀርቡ ከመጡት ተወዳጅና ታዋቂ አርቲስቶች መካከል፡- ላፎንቴኖች ፣ ጎሳዬ ተስፋዬ ፣ ፍቅርአዲስ ነቃጥበብ፣ መልካሙ ተበጀ ፣ ጀማል መሀመድ(አቺኩዳ)፣ ፀደንያ ገ/ማርቆስ ፣ ማናልቦሽ ዲቦ፣ ደረጀና ሀብቴ፣ጥላሁን እልፍነህ ፣ ዘውዱ በቀለና ፊሊፕ ማርቲን ይገኙበታል፡፡
የሙዚቃ ዝግጅቱን ለመታደም የከተማችን ነዋሪ በወረፋ ነበር ወደ አዳራሹ የገባው፡፡ እኔም ዝግጅቱን በገጉት ሲጠባበቁ ከነበሩት መካከል አንዱ ነኝ፡፡ አርቲስቶችን ለማስፈረም ሁሉ በኪሴ በቂ ወረቀቶችን ይዤ ነበር የገባሁት፡፡ በወቅቱ ሁሉንም አርቲስቶች የማደንቅ ቢሆንም፣ በተለይ ደግሞ ኮሜዲያን ደረጀንና ሃብቴን ለማየትና ከተቻለም ለማስፈረም በእጅጉ ጓጉቼ ነበር።
በመጨረሻም በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው ታላቅ የሙዚቃ ድግስ በይፋ ተጀመረ፡፡ እውነት ለመናገር አንድም ቤቱ የቀረ የቢሾፍቱ ነዋሪ ያለ አይመስልም ነበር፡፡ በቴሌቪዥን መስኮት ብቻ የምናቃቸው ተወዳጅና ዝነኛ ድምጻውያን በየተራ መድረክ ላይ እየወጡ አቀነቀኑ፡፡ ታዳሚው አብሯቸው እየዘፈነ እንደጉድ ጨፈረ፡፡ አዳራሹን በአንድ እግሩ አቆመው፡፡
የመድረክ አጋፋሪው ጥላሁን እልፍነህ፣ በመቀጠል ሥራቸውን የሚያቀርቡት ሁለቱ ተወዳጅ ኮሜዲያን እንደሆኑ ሲያስተዋውቅ፣ ታዳሚው በጩኸትና በፉጨት ደስታውንና ፍቅሩን ገለጸ፡፡ ደረጀና ሃብቴም ወደ መድረኩ ወጥተው በማያልቀው ቀልዳቸውና ለዛቸው አዳራሹን በሳቅ ሞሉት፡፡
ሥራቸውን አቅርበው እንደጨረሱ ከተጠገጠገው ሰው መሃል እንዴት ተፈትልኬ እንደወጣሁ ሳላውቀው፣ ራሴን መድረኩ አጠገብ አገኘሁት፡፡ ከዚያም አሻቅቤ ወደ ደረጀና ሃብቴ እየተመለከትኩ፣ "ፈርሙልኝ" አልኳቸው - ያዘጋጀሁትን ወረቀት ዘርግቼ፡፡ አንዳቸው ስሜን ጠየቁኝ፡፡ ነገርኳቸው፡፡ ከዚያም ከመድረኩ ጀርባ (ባክ ስቴጅ)ይዘውኝ ገቡ። እዚያ ሌሎችም ታዋቂ አርቲስቶች ነበሩ፡፡ አጋጣሚውን ተጠቅሜ ሁሉንም አስፈረምኳቸው፡፡
ተልዕኮዬን አጠናቅቄ ከመሄዴ በፊት ግን ኮሜዲያን ሀብቴ ምትኩ ለእነርሱ ከተዘጋጀው ሳንዱች ላይ አንስቶ እንድበላ ጋበዘኝ፡፡ በጣም ነበር ደስ ያለኝ፡፡ በአንዳች በማላውቀው ስሜት ተጥለቅልቄ ነበር፡፡ በቲቪ ብቻ እያየኋቸው የማደንቃቸውና የምወዳቸው ደረጀና ሀብቴ፣ የቅርብ ጓደኞቼ የሆኑ ያህል ተሰምቶኝ ነበር ብል ፈጽሞ አላጋነንኩም፡፡
ከዚያን ጊዜ በኋላ ታዲያ ደረጀና ሃብቴ እንዲሁም ሌሎች አርቲስቶች የፈረሙልኝን ወረቀት ት/ቤት ድረስ በመውሰድ ለጓደኞቼ እያሳየሁ፣ "ደረጃዬን" እንዲያውቁልኝ እጋጋጥ እንደነበር አስታውሳለሁ፡፡ "እኔኮ ከደረጄና ሃብቴ ጋር ጓደኛ ነኝ" እያልኩኝ፣ አብሬያቸው ሳንድዊች መብላቴን ሁሉ በማስረጃነት አቀርብ ነበር፡፡
ይሄ ሁሉ የሆነው በታዳጊነት ዕድሜ ላይ ነው - በተማሪነት ዘመን፡፡ ዛሬ ላይ ተወዳጁ ኮሜዲያን ደረጀ የቅርብ ጓደኛዬና ወዳጄ ብቻ ሳይሆን ወንድሜም ጭምር ነው፡፡
ደሬ፤ እንኳን ተወለድክልን !
ረዥም ዕድሜና ጤና እመኝልሃለሁ!
አክባሪህና ወዳጅህ ቴዎድሮስ ታደሰ አየለ
1 month ago
ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲያዊ ጥረት ከ35 በላይ የተዘረፉ ቅርሶቿን ማስመለሷን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ተናገሩ
ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ባከናወነችው ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት በተለያዩ ጊዜያት ተዘርፈውና ተሰርቀው ከአገር ወጥተው የነበሩ ከ35 በላይ ውድና ታሪካዊ ቅርሶቿን ማስመለስ መቻሏን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ “አዲሱ የኢኮኖሚ ሞተር” በሚል በቱሪዝም ዙሪያ ባደረጉት ቆይታ፤ይህ ስኬት መንግሥት ለቱሪዝም ዘርፉ ከሰጠው ትኩረት ጎን ለጎን የሀገሪቱን ክብርና የታሪክ ባለቤትነት ለማረጋገጥ የወሰደው ቁርጠኛ እርምጃ ውጤት መሆኑን ገልጸዋል።
ከተመለሱት ታዋቂ ቅርሶች መካከል በታሪክ የመጀመሪያዋ በኢትዮጵያውያን የተሠራችው የ"ፀሐይ" አውሮፕላን ከጣሊያን መመለሷን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያውያንን የጀግንነት ታሪክ የሚዘክረው የአፄ ቴዎድሮስ የራስ ፀጉር እንዲሁም በርካታ ጥንታዊ የብራና መጻሕፍት፣ መስቀሎችና ልዩ ልዩ የቤተክርስቲያን ንዋያተ ቅድሳት ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ተደርጓል ብለዋል።
የቅርሶች የማስመለስ ሂደት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በአሁኑ ወቅትም የአፄ ኃይለ ሥላሴን የዙፋን መቀመጫ ጨምሮ ሌሎች ቀሪ ውድ ቅርሶችን ለማስመለስ ከተለያዩ ሀገራትና ተቋማት ጋር የዲፕሎማሲ ንግግር እየተደረገ መሆኑንጠቁመዋል።
ይህም በቅርቡ ውጤት እንደሚገኝበትና ተጨማሪ የታሪክ ጸጋዎች ወደ ሀገር እንደሚገቡ ተስፋቸውን ገልጸዋል።
በቅርሶች አያያዝ ላይ በአንዳንድ ወገኖች የሚነሱ ሥጋቶችን በተመለከተም፣ መንግሥት ቅርስን የሚያጠፋ ሳይሆን የጠፋውን የሚመልስና የፈረሰውን የሚያድስ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አጽንኦት ሰጥተዋል።
ቀደም ሲል እንደ እዳ ታይተው ተዘግተውና ተረስተው የነበሩጥንታዊ ቤተመንግሥቶች ዛሬ ላይ ታድሰው ለትውልድ ዕውቀትና ለሀገር ገቢ ምንጭ እየሆኑ መሆናቸውን በአብነት ጠቅሰዋል።
ይህም ለወደፊቱ የቱሪዝም ኢንዱስትሪ አዲስ ተስፋን ከመፍጠሩም በላይ፤ትውልዱ የሀገሩን ጥልቅ ታሪክ በቅርበት እንዲያውቅና እንዲያከብር ትልቅ ዕድል የሚከፍት መሆኑን አመላክተዋል።
Ethio Fm
ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ባከናወነችው ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት በተለያዩ ጊዜያት ተዘርፈውና ተሰርቀው ከአገር ወጥተው የነበሩ ከ35 በላይ ውድና ታሪካዊ ቅርሶቿን ማስመለስ መቻሏን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ “አዲሱ የኢኮኖሚ ሞተር” በሚል በቱሪዝም ዙሪያ ባደረጉት ቆይታ፤ይህ ስኬት መንግሥት ለቱሪዝም ዘርፉ ከሰጠው ትኩረት ጎን ለጎን የሀገሪቱን ክብርና የታሪክ ባለቤትነት ለማረጋገጥ የወሰደው ቁርጠኛ እርምጃ ውጤት መሆኑን ገልጸዋል።
ከተመለሱት ታዋቂ ቅርሶች መካከል በታሪክ የመጀመሪያዋ በኢትዮጵያውያን የተሠራችው የ"ፀሐይ" አውሮፕላን ከጣሊያን መመለሷን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያውያንን የጀግንነት ታሪክ የሚዘክረው የአፄ ቴዎድሮስ የራስ ፀጉር እንዲሁም በርካታ ጥንታዊ የብራና መጻሕፍት፣ መስቀሎችና ልዩ ልዩ የቤተክርስቲያን ንዋያተ ቅድሳት ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ተደርጓል ብለዋል።
የቅርሶች የማስመለስ ሂደት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በአሁኑ ወቅትም የአፄ ኃይለ ሥላሴን የዙፋን መቀመጫ ጨምሮ ሌሎች ቀሪ ውድ ቅርሶችን ለማስመለስ ከተለያዩ ሀገራትና ተቋማት ጋር የዲፕሎማሲ ንግግር እየተደረገ መሆኑንጠቁመዋል።
ይህም በቅርቡ ውጤት እንደሚገኝበትና ተጨማሪ የታሪክ ጸጋዎች ወደ ሀገር እንደሚገቡ ተስፋቸውን ገልጸዋል።
በቅርሶች አያያዝ ላይ በአንዳንድ ወገኖች የሚነሱ ሥጋቶችን በተመለከተም፣ መንግሥት ቅርስን የሚያጠፋ ሳይሆን የጠፋውን የሚመልስና የፈረሰውን የሚያድስ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አጽንኦት ሰጥተዋል።
ቀደም ሲል እንደ እዳ ታይተው ተዘግተውና ተረስተው የነበሩጥንታዊ ቤተመንግሥቶች ዛሬ ላይ ታድሰው ለትውልድ ዕውቀትና ለሀገር ገቢ ምንጭ እየሆኑ መሆናቸውን በአብነት ጠቅሰዋል።
ይህም ለወደፊቱ የቱሪዝም ኢንዱስትሪ አዲስ ተስፋን ከመፍጠሩም በላይ፤ትውልዱ የሀገሩን ጥልቅ ታሪክ በቅርበት እንዲያውቅና እንዲያከብር ትልቅ ዕድል የሚከፍት መሆኑን አመላክተዋል።
Ethio Fm
1 month ago
ያልተዘመረለት ጀግና!
* በኢትዮጵያ 30 ትምህርት ቤት አስገንብቷል
***
የአቶ አዲስ ገሠሠ አጭር የሕይወት ታሪክ
#ethiopia | አቶ አዲስ ገሰሰ ከአባታቸው ከግራዝማች ገሰሰ መንገሻ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ አስናቀች መልሴ ጥር 8 ቀን 1945 ዓ.ም. በቀድሞው ኢሊባቦር ጠቅላይ ግዛት ጎሬ ከተማ ተወለዱ፡፡
እስከ 9ነኛ ክፍል በጎሬ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ት/ቤት ከተማሩ በኋላ፤ የ10ኛ ክፍል ትምህርታቸውን አዲስ አበባ በዳግማዊ ምንሊክ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተምረው፤ ወደ ጅማ በመሄድ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በሚያዝያ 27 2ተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከታትለዋል፡፡
አቶ አዲሱ ገሰሰ በህይወታቸው ትልቅ ቦታ የሚሰጡትና “ ስብዕናዬን በዲሲፕሊን ገንብቶታል” የሚሉትን የኢትዮጵያ አየር ኃይልን በ1961 ዓ.ም. በመቀላቀል ከወታደራዊ ስልጠና ጋር በበረራ ቴክኒሻንነት ተመርቀዋል፡፡
በሙያቸው አንድ ዓመት ካገለገሉ በኋላ፤ በ1964 ዓ.ም. ነፃ የትምህርት እድል በማግኘታቸው ወደ አሜሪካ ሀገር ሺካጎ ከተማ በማቅናት በራንቱል ኤርፎርስ ቤዝ፤ እና በቴክሳስ ላክላንድ ኤርፎርስ ቤዝ ትምህርታቸውን አጠናቀው ተመርቀዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ በወጣትነት ዘመናቸው ያን ጊዜ ሉፕ ኮሌጅ በሚባለው ሃሮልድ ዋሺንግተን ዩኒቨርሲቲ የሜካኒካል ኢንጅነሪንግ ትምህርታቸውን ተከታትለዋል፡፡ በመቀጠልም በኖርዝ ኢስተርን ኢሊኖይ ዩኒቨርሲቲ በማኔጅመንት ትምህርታቸውን አጠናቀዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ ወንድሞቻቸውን ሙሉጌታ ገሰሰን፤ ዘለቀ ገሰሰንና ጓደኞቻቸውን እነ መላኩ ረታን ወደ ሺካጎ ካመጡ በኋላ ዳሎል ባንድን መስርተዋል፡፡ አቶ አዲስ ገሰሰ በሚማሩበት ኖርዝ ኢስተርን ኢሊኖይ ዩኒቨርሲቲ የጥቁር ታሪክ ወር /Black History Month/ በሚል መጠሪያ በየዓመቱ የካቲት ወር ላይ በተለያየ መዘክር በሚከበር በዓል ላይ፤ ዳሎል ባንድ ሙዚቃ እንዲያቀርብ በማስቻል የሙዚቃ ማኔጅመንት የህይወት ጉዟቸውን ሀ ብለው ጀመሩ፡፡
በመቀጠልም ዳሎል ባንድን ይዘው በዋሺንግተን፤ በሎስ አንጀለስ እና በመላው አሜሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ ለኢትዮጵያውያን-በኢትዮጵያ ባንድ የሙዚቃ ኮንሰርት በማቅረብ ፈር ቀዳጅ እና ውጤታማ ስራ ሰርተዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ ሙዚቃን ማኔጅ በማድረግ ጉዟቸው የእውቁን የሬጌ ሙዚቃ ንጉስ የቦብ ማርሌን ቤተሰብ ሃብትና ንብረቱን በማስተዳደር ብቻ ሳይሆን፤ የቦብን ልጆች በስነ ምግባር ኮትኮቶ ለማሳደግ ከአሜሪካ ኒውዮርክ -ጃማይካ ኪንግስተን እየተመላለሱ በትጋትና በታማኝነት ኃላፊነታቸውን ተወጥተዋል፡፡
በዚያን ጊዜም ዘመን አይሽሬውን የቦብ ማርሌይ “ሌጀንድ አልበም" እንዲሰራ ባቀረቡት ንድፈ-ሃሳብ መሰረት ከአይላንድ ሪከርዲንግ ጋር በመፈራረም ውጤማ ስራ ሰርተዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ በቦብ ማርሌይ ቤተሰቦች የተዘጋጁትንና ከምድር ዳር እስከ ምድር ዳር ድረስ የተደረጉትን ዓለም አቀፍ የሬጌ ሙዚቃ ኮንሰርቶች ሃሳብ ከመጠንሰስ ጀምሮ ለሃያ ሁለት ዓመታት ያክል ስራውን በሃላፊነት መርተዋል፡፡ አስተዳድረዋል፡፡
በዚሁ የአስተዳደር ዘመናቸው በዘረጉት መንገድ እስካሁን ድረስ በየዓመቱ የሚደረገውን ዓለም አቀፍ የሬጌ ሙዚቃ ፌስቲቫል በማይናወጥ መሰረት ላይ አፅንተዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ ዚጊ ማርሌይን ከጃማይካ… የነዘለቀን ገሰሰን ዳሎል ባንድ ደግሞ ከሺካጎ ወደኒዮርክ በማምጣት ካጣመሩ በኋላ ፤ ከሲግማ ስቱዲዮ እና ከቨርጂኒያ ሪከርድስ ጋር ውል በመፈራረም በአሜሪካ ምድር ቁጥር አንድ ተደማጭ የነበረውን ኮንሺየስ ፓርቲ አልበም እንዲለቀቅ አድርገዋል፡፡
በአልበሙ ከተካተቱት ስራዎች መካከል ቱሞሮ ፒውፕል የተሰኘው ሙዚቃ በዓለም ላይ እጅግ ከመወደዱ የተነሳ ብዙዎች እንደ ብሔራዊ መዝሙር ያዜሙት ነበር፡፡
በአቶ አዲስ ገሰሰ ማናጀርነት በተመራው በዚሁ የሙዚቃ አልበም ዚጊ ማርሌይ የአሜሪካንን ትልቁን ግራሚ አዋርድ ሽልማት ሲያገኝ፤ የኢትዮጵያው ዳሎል ባንድ ደግሞ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደ ባንድ የግራሚ ሽልማት እንዲወስድ በማስቻል ታሪክ የማይረሳውን ስራ ሰርተዋል፡፡
ለሀገራቸው ኢትዮጵያ የተለየ ፍቅር የነበራቸው አቶ አዲስ ገሰሰ ከወንድማቸው ከአርቲስት ዘለቀ ገሰሰ ጋር በመሆን የቦብ ማርሊ 60ኛ ዓመት የልደት በዓሉን ለመዘከር የሚዘጋጀውን “አፍሪካ ዩናይት” ዓለም አቀፍ የሙዚቃ ዝግጅት ኢትዮጵያን መዳረሻ በማድረግና አንድ አመት የፈጀ የዘመቻ /ካምፔይን/ በመስራት ፤ በ1997 ዓ.ም. መስቀል አደባባይ የተካሄደውን የሙዚቃ ፌስቲቫል ስኬታማ እንዲሆን አስችለዋል፡፡ በዚሁ ፌስቲቫል ላይ የቀድሞውን ጠቅላይ ሚኒስትር ጨምሮ ሪታ ማርሌይና አምስቱ የቦብ ልጆች ተገኝተዋል፡፡
ይኸው ፌስቲቫል በፈጠረው መልካም አጋጣሚም ሀገራችንን በዓለም ዙሪያ ለማስተዋወቅ፤ የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግና ኢንቨስመንት ለመሳብ በማለም ከ50 በላይ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎችን ጋብዘው የራሳቸውን የዜግነት ድርሻ ተወጥተዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ በሙዚቃ ማኔጅመንት የሕይወት ጉዟቸው ያካበቱትን እውቀትና ልምድ ተጠቅመው ተሰጥዎ ያላቸውን ልጆች በመቃኘት ሀገራቸውን በሙዚቃው ኢንደስትሪ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ለማድረግ ትልቅ ህልም ነበራቸው፡፡ ለዚህም ቴዎድሮስ ካሳሁን /ቴዲ አፍሮን/ከመጀመሪያው አልበሙ ጀምሮ ማኔጅመንቱን በመያዝ ፤ እንዲሁም እጅጋየው ሽባባው /ጂጂን/ ከአጋራቸው ፓልም ሪከርዲንግ ጋር በመሆን ተወዳጅ የሆነ አልበሟን እንድተሰራ ያደረጉት አስተዋፅኦ የሚጠቀስ ነው፡፡
ይሄም ብቻ ሳይሆን ጃኖ ባንድን በመመስረት ለልጆቹ ውጤታማነት አቶ አዲስ ገሰሰ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳሉ፡፡ አቶ አዲስ “ጃናናይት” የተባለ ተሰጥዎ ያላቸውን ሴቶች የያዘ ባንድ መስርተው ስኬታማ ለማድረግ ያደረጉት ጥረትም የሚወሳ ነው፡፡
በሙዚቃ ኢንዱስትሪው- እጅግ ገዝፈው፤ በተለያየ የአድናቆት ቃል የሚጠሩት አቶ አዲስ ገሰሰ ከሀገራችን ውጪ እንደ ዚጊ ማርሌ፤ ስቴፈን ማርሌ፤ ሎረን ሂል፣ ፊል ኮሊንስ፣ ኧርዝ ዊንድ ኤንድ ፋየር እና ሌሎችንም በርካታ የሙዚቃ ከዋክብትን በማግኘትና በማስተዳደር በዓለም አቀፍ ደረጃ የብዙ ታላላቅ የሙዚቃ ሰዎች ስራን መስመር አሲዘዋል።
አቶ አዲስ ገሰሰ መደበኛ መኖሪያቸውን ወደ ኢትዮጵያ ካዞሩ በኋላ በሆቴሊንግ ዘርፍ በመሰማራት ላየንስ ዴን ሆቴልን፤ በማእድን ዘርፍም ዩኒቨርሳል ማይኒንግን፤ በግብርና መስክ አድሶጌት ኩባንያን በማቋቋም ለሀገራቸው እድገት ቀን ከሌት ያለእረፍት ሰርተዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ በሙዚቃ ማኔጅመንትና በኢንቨስትመንት ስራቸው ብቻ ሳይሆን በበጎ አድራጎታቸውም አርአያነት ያለው ተግባር ፈፅመዋል፡፡ በግል ከደገፏቸው ግለሰቦች በተጨማሪ በሀገራችን በተለያዩ ወቅቶች በተፈጠሩ ሰብአዊ ችግሮች ቀድመው በመድረስ ያደረጉት አስተዋፅኦ የሚጠቀስ ነው፡፡
በዋናነትም ከወንድማቸው ዘለቀ ገሰሰ ጋር በመሆን በተለያዩ ገጠራማ አካባቢዎች 30 ትምህርት ቤቶችን አሰርተዋል፡፡
አቶ አዲስ ስለእነኚሁ በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ስላሰሯቸው 30 ትምህርት ቤቶች ሲናገሩ “ተስፋ ሳልቆርጥ በፅናት የታገልኩበት በጎ ተግባር በመሆኑ ያስደስተኛል” ይሉ ነበር፡፡
ቤተ-ክርስቲያን በጠራቻቸው ጊዜ ሁሉ እየተገኙም በመላው ኢትዮጵያ አዳዲስ ቤተክርስቲያኖችን በማሰራት ፤ የተጎዱ ገዳማትንና ቤተክርስቲያኖችን በማደስ ፤ የተዘጉ ቤተክርስቲያኖችን በማስከፈት፤ የቤተክርስቲያኖችን ንዋየ ቅዱሳን በማሟላትና የካህናት ደሞዝን በመክፈል እስከ ህይወት ፍፃሜያቸው ድረስ ድምፃቸውን አጥፍተው አገልግለዋል፡፡
አቶ አዲሱ ገሰሰ በማህበራዊ ህይወታቸው ቀልድ አዋቂ፤ ተጫዋች እና በቀላሉ ከሰዎች ጋር ተግባብተው የመኖር ፀጋ የነበራቸው ሲሆን ከሁሉም ግን ሰው አካባሪ እና ስነ-ምግባር ያለው ቀረቤታቸው ተወዳጅና በሰው ልብ አይረሴ አድርጓቸዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ ከወ/ሮ ሶስና ሽፈራው ጋር በነበራቸው የፀና ትዳር አንድ ወንድና አንዲት ሴት ልጅ አፍርተዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ፤ በአሜሪካ ሀገር ኒውጄርሲ ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል፡፡
የቀብር ሥነ ስርዓቱ ዛሬ፣ ሰኔ 20 ቀን 2018ዓ.ም በ6:00 ሰዓት በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጽሟል።
አቶ አዲስ ገሰሰን ከአጠገቡ ሳትለዩ ላስታመማችሁትና ለጠየቃችሁት ወዳጅ ዘመዶች ልዑል እግዚአብሔር ብድራችሁን ይከፈላችሁ፡፡
የአቶ አዲስ ገሰሰን ነፍስ ልዑል እግዚአብሔር በአፀደ ገነት ከደጋጎቹ አብርሃም ይስሐቅ እና ያቆብ ጎን ያሳርፍልን፡፡
ለቤተሰቡ፤ ለወዳጆቹ፤ ለዘመዶቹ፤ ለሙያ አጋሮቹ፤ ለአድናቂዎቹ ሁሉ መፅናናቱን ይስጣቸው፡፡
* በኢትዮጵያ 30 ትምህርት ቤት አስገንብቷል
***
የአቶ አዲስ ገሠሠ አጭር የሕይወት ታሪክ
#ethiopia | አቶ አዲስ ገሰሰ ከአባታቸው ከግራዝማች ገሰሰ መንገሻ እና ከእናታቸው ከወይዘሮ አስናቀች መልሴ ጥር 8 ቀን 1945 ዓ.ም. በቀድሞው ኢሊባቦር ጠቅላይ ግዛት ጎሬ ከተማ ተወለዱ፡፡
እስከ 9ነኛ ክፍል በጎሬ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ት/ቤት ከተማሩ በኋላ፤ የ10ኛ ክፍል ትምህርታቸውን አዲስ አበባ በዳግማዊ ምንሊክ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተምረው፤ ወደ ጅማ በመሄድ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በሚያዝያ 27 2ተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከታትለዋል፡፡
አቶ አዲሱ ገሰሰ በህይወታቸው ትልቅ ቦታ የሚሰጡትና “ ስብዕናዬን በዲሲፕሊን ገንብቶታል” የሚሉትን የኢትዮጵያ አየር ኃይልን በ1961 ዓ.ም. በመቀላቀል ከወታደራዊ ስልጠና ጋር በበረራ ቴክኒሻንነት ተመርቀዋል፡፡
በሙያቸው አንድ ዓመት ካገለገሉ በኋላ፤ በ1964 ዓ.ም. ነፃ የትምህርት እድል በማግኘታቸው ወደ አሜሪካ ሀገር ሺካጎ ከተማ በማቅናት በራንቱል ኤርፎርስ ቤዝ፤ እና በቴክሳስ ላክላንድ ኤርፎርስ ቤዝ ትምህርታቸውን አጠናቀው ተመርቀዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ በወጣትነት ዘመናቸው ያን ጊዜ ሉፕ ኮሌጅ በሚባለው ሃሮልድ ዋሺንግተን ዩኒቨርሲቲ የሜካኒካል ኢንጅነሪንግ ትምህርታቸውን ተከታትለዋል፡፡ በመቀጠልም በኖርዝ ኢስተርን ኢሊኖይ ዩኒቨርሲቲ በማኔጅመንት ትምህርታቸውን አጠናቀዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ ወንድሞቻቸውን ሙሉጌታ ገሰሰን፤ ዘለቀ ገሰሰንና ጓደኞቻቸውን እነ መላኩ ረታን ወደ ሺካጎ ካመጡ በኋላ ዳሎል ባንድን መስርተዋል፡፡ አቶ አዲስ ገሰሰ በሚማሩበት ኖርዝ ኢስተርን ኢሊኖይ ዩኒቨርሲቲ የጥቁር ታሪክ ወር /Black History Month/ በሚል መጠሪያ በየዓመቱ የካቲት ወር ላይ በተለያየ መዘክር በሚከበር በዓል ላይ፤ ዳሎል ባንድ ሙዚቃ እንዲያቀርብ በማስቻል የሙዚቃ ማኔጅመንት የህይወት ጉዟቸውን ሀ ብለው ጀመሩ፡፡
በመቀጠልም ዳሎል ባንድን ይዘው በዋሺንግተን፤ በሎስ አንጀለስ እና በመላው አሜሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ ለኢትዮጵያውያን-በኢትዮጵያ ባንድ የሙዚቃ ኮንሰርት በማቅረብ ፈር ቀዳጅ እና ውጤታማ ስራ ሰርተዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ ሙዚቃን ማኔጅ በማድረግ ጉዟቸው የእውቁን የሬጌ ሙዚቃ ንጉስ የቦብ ማርሌን ቤተሰብ ሃብትና ንብረቱን በማስተዳደር ብቻ ሳይሆን፤ የቦብን ልጆች በስነ ምግባር ኮትኮቶ ለማሳደግ ከአሜሪካ ኒውዮርክ -ጃማይካ ኪንግስተን እየተመላለሱ በትጋትና በታማኝነት ኃላፊነታቸውን ተወጥተዋል፡፡
በዚያን ጊዜም ዘመን አይሽሬውን የቦብ ማርሌይ “ሌጀንድ አልበም" እንዲሰራ ባቀረቡት ንድፈ-ሃሳብ መሰረት ከአይላንድ ሪከርዲንግ ጋር በመፈራረም ውጤማ ስራ ሰርተዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ በቦብ ማርሌይ ቤተሰቦች የተዘጋጁትንና ከምድር ዳር እስከ ምድር ዳር ድረስ የተደረጉትን ዓለም አቀፍ የሬጌ ሙዚቃ ኮንሰርቶች ሃሳብ ከመጠንሰስ ጀምሮ ለሃያ ሁለት ዓመታት ያክል ስራውን በሃላፊነት መርተዋል፡፡ አስተዳድረዋል፡፡
በዚሁ የአስተዳደር ዘመናቸው በዘረጉት መንገድ እስካሁን ድረስ በየዓመቱ የሚደረገውን ዓለም አቀፍ የሬጌ ሙዚቃ ፌስቲቫል በማይናወጥ መሰረት ላይ አፅንተዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ ዚጊ ማርሌይን ከጃማይካ… የነዘለቀን ገሰሰን ዳሎል ባንድ ደግሞ ከሺካጎ ወደኒዮርክ በማምጣት ካጣመሩ በኋላ ፤ ከሲግማ ስቱዲዮ እና ከቨርጂኒያ ሪከርድስ ጋር ውል በመፈራረም በአሜሪካ ምድር ቁጥር አንድ ተደማጭ የነበረውን ኮንሺየስ ፓርቲ አልበም እንዲለቀቅ አድርገዋል፡፡
በአልበሙ ከተካተቱት ስራዎች መካከል ቱሞሮ ፒውፕል የተሰኘው ሙዚቃ በዓለም ላይ እጅግ ከመወደዱ የተነሳ ብዙዎች እንደ ብሔራዊ መዝሙር ያዜሙት ነበር፡፡
በአቶ አዲስ ገሰሰ ማናጀርነት በተመራው በዚሁ የሙዚቃ አልበም ዚጊ ማርሌይ የአሜሪካንን ትልቁን ግራሚ አዋርድ ሽልማት ሲያገኝ፤ የኢትዮጵያው ዳሎል ባንድ ደግሞ ለመጀመሪያ ጊዜ እንደ ባንድ የግራሚ ሽልማት እንዲወስድ በማስቻል ታሪክ የማይረሳውን ስራ ሰርተዋል፡፡
ለሀገራቸው ኢትዮጵያ የተለየ ፍቅር የነበራቸው አቶ አዲስ ገሰሰ ከወንድማቸው ከአርቲስት ዘለቀ ገሰሰ ጋር በመሆን የቦብ ማርሊ 60ኛ ዓመት የልደት በዓሉን ለመዘከር የሚዘጋጀውን “አፍሪካ ዩናይት” ዓለም አቀፍ የሙዚቃ ዝግጅት ኢትዮጵያን መዳረሻ በማድረግና አንድ አመት የፈጀ የዘመቻ /ካምፔይን/ በመስራት ፤ በ1997 ዓ.ም. መስቀል አደባባይ የተካሄደውን የሙዚቃ ፌስቲቫል ስኬታማ እንዲሆን አስችለዋል፡፡ በዚሁ ፌስቲቫል ላይ የቀድሞውን ጠቅላይ ሚኒስትር ጨምሮ ሪታ ማርሌይና አምስቱ የቦብ ልጆች ተገኝተዋል፡፡
ይኸው ፌስቲቫል በፈጠረው መልካም አጋጣሚም ሀገራችንን በዓለም ዙሪያ ለማስተዋወቅ፤ የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግና ኢንቨስመንት ለመሳብ በማለም ከ50 በላይ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎችን ጋብዘው የራሳቸውን የዜግነት ድርሻ ተወጥተዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ በሙዚቃ ማኔጅመንት የሕይወት ጉዟቸው ያካበቱትን እውቀትና ልምድ ተጠቅመው ተሰጥዎ ያላቸውን ልጆች በመቃኘት ሀገራቸውን በሙዚቃው ኢንደስትሪ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ ለማድረግ ትልቅ ህልም ነበራቸው፡፡ ለዚህም ቴዎድሮስ ካሳሁን /ቴዲ አፍሮን/ከመጀመሪያው አልበሙ ጀምሮ ማኔጅመንቱን በመያዝ ፤ እንዲሁም እጅጋየው ሽባባው /ጂጂን/ ከአጋራቸው ፓልም ሪከርዲንግ ጋር በመሆን ተወዳጅ የሆነ አልበሟን እንድተሰራ ያደረጉት አስተዋፅኦ የሚጠቀስ ነው፡፡
ይሄም ብቻ ሳይሆን ጃኖ ባንድን በመመስረት ለልጆቹ ውጤታማነት አቶ አዲስ ገሰሰ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳሉ፡፡ አቶ አዲስ “ጃናናይት” የተባለ ተሰጥዎ ያላቸውን ሴቶች የያዘ ባንድ መስርተው ስኬታማ ለማድረግ ያደረጉት ጥረትም የሚወሳ ነው፡፡
በሙዚቃ ኢንዱስትሪው- እጅግ ገዝፈው፤ በተለያየ የአድናቆት ቃል የሚጠሩት አቶ አዲስ ገሰሰ ከሀገራችን ውጪ እንደ ዚጊ ማርሌ፤ ስቴፈን ማርሌ፤ ሎረን ሂል፣ ፊል ኮሊንስ፣ ኧርዝ ዊንድ ኤንድ ፋየር እና ሌሎችንም በርካታ የሙዚቃ ከዋክብትን በማግኘትና በማስተዳደር በዓለም አቀፍ ደረጃ የብዙ ታላላቅ የሙዚቃ ሰዎች ስራን መስመር አሲዘዋል።
አቶ አዲስ ገሰሰ መደበኛ መኖሪያቸውን ወደ ኢትዮጵያ ካዞሩ በኋላ በሆቴሊንግ ዘርፍ በመሰማራት ላየንስ ዴን ሆቴልን፤ በማእድን ዘርፍም ዩኒቨርሳል ማይኒንግን፤ በግብርና መስክ አድሶጌት ኩባንያን በማቋቋም ለሀገራቸው እድገት ቀን ከሌት ያለእረፍት ሰርተዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ በሙዚቃ ማኔጅመንትና በኢንቨስትመንት ስራቸው ብቻ ሳይሆን በበጎ አድራጎታቸውም አርአያነት ያለው ተግባር ፈፅመዋል፡፡ በግል ከደገፏቸው ግለሰቦች በተጨማሪ በሀገራችን በተለያዩ ወቅቶች በተፈጠሩ ሰብአዊ ችግሮች ቀድመው በመድረስ ያደረጉት አስተዋፅኦ የሚጠቀስ ነው፡፡
በዋናነትም ከወንድማቸው ዘለቀ ገሰሰ ጋር በመሆን በተለያዩ ገጠራማ አካባቢዎች 30 ትምህርት ቤቶችን አሰርተዋል፡፡
አቶ አዲስ ስለእነኚሁ በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ስላሰሯቸው 30 ትምህርት ቤቶች ሲናገሩ “ተስፋ ሳልቆርጥ በፅናት የታገልኩበት በጎ ተግባር በመሆኑ ያስደስተኛል” ይሉ ነበር፡፡
ቤተ-ክርስቲያን በጠራቻቸው ጊዜ ሁሉ እየተገኙም በመላው ኢትዮጵያ አዳዲስ ቤተክርስቲያኖችን በማሰራት ፤ የተጎዱ ገዳማትንና ቤተክርስቲያኖችን በማደስ ፤ የተዘጉ ቤተክርስቲያኖችን በማስከፈት፤ የቤተክርስቲያኖችን ንዋየ ቅዱሳን በማሟላትና የካህናት ደሞዝን በመክፈል እስከ ህይወት ፍፃሜያቸው ድረስ ድምፃቸውን አጥፍተው አገልግለዋል፡፡
አቶ አዲሱ ገሰሰ በማህበራዊ ህይወታቸው ቀልድ አዋቂ፤ ተጫዋች እና በቀላሉ ከሰዎች ጋር ተግባብተው የመኖር ፀጋ የነበራቸው ሲሆን ከሁሉም ግን ሰው አካባሪ እና ስነ-ምግባር ያለው ቀረቤታቸው ተወዳጅና በሰው ልብ አይረሴ አድርጓቸዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ ከወ/ሮ ሶስና ሽፈራው ጋር በነበራቸው የፀና ትዳር አንድ ወንድና አንዲት ሴት ልጅ አፍርተዋል፡፡
አቶ አዲስ ገሰሰ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ፤ በአሜሪካ ሀገር ኒውጄርሲ ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል፡፡
የቀብር ሥነ ስርዓቱ ዛሬ፣ ሰኔ 20 ቀን 2018ዓ.ም በ6:00 ሰዓት በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጽሟል።
አቶ አዲስ ገሰሰን ከአጠገቡ ሳትለዩ ላስታመማችሁትና ለጠየቃችሁት ወዳጅ ዘመዶች ልዑል እግዚአብሔር ብድራችሁን ይከፈላችሁ፡፡
የአቶ አዲስ ገሰሰን ነፍስ ልዑል እግዚአብሔር በአፀደ ገነት ከደጋጎቹ አብርሃም ይስሐቅ እና ያቆብ ጎን ያሳርፍልን፡፡
ለቤተሰቡ፤ ለወዳጆቹ፤ ለዘመዶቹ፤ ለሙያ አጋሮቹ፤ ለአድናቂዎቹ ሁሉ መፅናናቱን ይስጣቸው፡፡
Sponsored by
Surafel
Comments