11 hours ago
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ2018 በጀት ዓመት 118.91 ቢሊዮን ብር ገቢ ሰበሰበ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ2018 በጀት ዓመት አስመዝግቦት የነበረውን አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸም እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅዱን አስመልክቶ የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ጌቱ ገረመው ለሚዲያ አካላት መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም ተቋሙ በበጀት ዓመቱ ያቀዳቸውን አብዛኞቹን ዋና ዋና ግቦች በላቀ ደረጃ ማሳካት መቻሉን እና በተለይም በአዳዲስ ደንበኞች ትስስር ረገድ በተቋሙ ታሪክም ሆነ በአፍሪካ ደረጃ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ውጤት ማስመዝገቡን ይፋ አድርገዋል።
በበጀት ዓመቱ 800 ሺህ አዳዲስ ደንበኞችን የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ የነበረ ሲሆን፣ 664 ሺህ 505 አባወራዎችን በማገናኘት የ83.1 በመቶ ስኬት ተመዝግቧል።
ይህም አፈጻጸም ከቀደመው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ32.5 በመቶ እድገት ያሳየ ሲሆን፣ ተቋሙን በዓይነቱ ከአፍሪካ መሰል የኃይል አቅርቦት ኩባንያዎች የመሪነት ደረጃ ላይ አሰልፎታል።
በተጨማሪም የገጠር ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራሙን በማጠናከር ከዋናው ግሪድ እና ከኦፍ-ግሪድ የፀሐይ ኃይል አማራጮች 205 አዳዲስ የገጠር ቀበሌዎችንና መንደሮችን የኃይል ተጠቃሚ ማድረግ የተቻለ ሲሆን፣ ይህም በአገሪቱ አጠቃላይ የኤሌክትሪክ ተደራሽ የሆኑ የገጠር አካባቢዎችን ቁጥር ወደ 7 ሺህ 908 አድርሶታል።
በፋይናንስና በገቢ አሰባሰብ ረገድም ተቋሙ አስደናቂ ስኬት ያስመዘገበ ሲሆን፣ ከኢነርጂ ሽያጭ፣ ከአዳዲስ ደንበኞች መስተንግዶና ከሌሎች ልዩ ልዩ የገቢ ምንጮች 115.86 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ 118.91 ቢሊዮን ብር በመሰብሰብ የ103 በመቶ አፈጻጸም አሳይቷል።
ይህ የገቢ መጠን ከቀደመው በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ88.4 በመቶ ከፍተኛ እድገት ያሳየ ነው። ለዚህ አፈጻጸም መሻሻል የዲጂታል ክፍያ አማራጮች መስፋፋት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከተ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የዲጂታል ክፍያ የሚጠቀሙ ደንበኞች ቁጥር 95.3 በመቶ ደርሷል።
በተጨማሪም ተቋሙ ከስርቆትና ከኃይል ብክነት የመከላከል ሥራዎችን በማጠናከር ከ2.2 ቢሊዮን ብር በላይ ለተቋሙ ገቢ ማድረግ ችሏል።
ተቋሙ የአገልግሎት ጥራትን ለማሻሻልና የኃይል መቆራረጥን ለመቀነስ ሰፊ የዲስትሪቢዩሽን መስመሮች ማሻሻያ፣ የትራንስፎርመር ጥገናና የአቅም ማሳደግ ሥራዎችን ያከናወነ ቢሆንም፣ አሁንም የመሰረተ ልማት እርጅና፣ የግብዓትና የነዳጅ እጥረት እንዲሁም የመሰረተ ልማቶች ስርቆትና ውድመት ዋና ዋና ተግዳሮቶች እንደነበሩ ተገልጿል።
ሆኖም ተቋሙ የተደቀኑበትን ተግዳሮቶች በመቋቋም የቴክኖሎጂ ትግበራዎችን አጠናክሮ በመቀጠል፣ ለሀገር ኢኮኖሚ እድገትና ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስኬት የሚጠበቅበትን የላቀ ሚና አጠናክሮ እንደሚቀጥል ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገልጸዋል።
ጌትነት ተመስገን
#ethiopianelectricutility #eeu #ethiopia #energysector #ethiopianeconomy #digitalethiopia2030 #ruralelectrification #offgridenergy #performancereport #africaenergy
#ethiopia | የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ2018 በጀት ዓመት አስመዝግቦት የነበረውን አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸም እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅዱን አስመልክቶ የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር ጌቱ ገረመው ለሚዲያ አካላት መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም ተቋሙ በበጀት ዓመቱ ያቀዳቸውን አብዛኞቹን ዋና ዋና ግቦች በላቀ ደረጃ ማሳካት መቻሉን እና በተለይም በአዳዲስ ደንበኞች ትስስር ረገድ በተቋሙ ታሪክም ሆነ በአፍሪካ ደረጃ አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ውጤት ማስመዝገቡን ይፋ አድርገዋል።
በበጀት ዓመቱ 800 ሺህ አዳዲስ ደንበኞችን የአገልግሎቱ ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ የነበረ ሲሆን፣ 664 ሺህ 505 አባወራዎችን በማገናኘት የ83.1 በመቶ ስኬት ተመዝግቧል።
ይህም አፈጻጸም ከቀደመው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ32.5 በመቶ እድገት ያሳየ ሲሆን፣ ተቋሙን በዓይነቱ ከአፍሪካ መሰል የኃይል አቅርቦት ኩባንያዎች የመሪነት ደረጃ ላይ አሰልፎታል።
በተጨማሪም የገጠር ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራሙን በማጠናከር ከዋናው ግሪድ እና ከኦፍ-ግሪድ የፀሐይ ኃይል አማራጮች 205 አዳዲስ የገጠር ቀበሌዎችንና መንደሮችን የኃይል ተጠቃሚ ማድረግ የተቻለ ሲሆን፣ ይህም በአገሪቱ አጠቃላይ የኤሌክትሪክ ተደራሽ የሆኑ የገጠር አካባቢዎችን ቁጥር ወደ 7 ሺህ 908 አድርሶታል።
በፋይናንስና በገቢ አሰባሰብ ረገድም ተቋሙ አስደናቂ ስኬት ያስመዘገበ ሲሆን፣ ከኢነርጂ ሽያጭ፣ ከአዳዲስ ደንበኞች መስተንግዶና ከሌሎች ልዩ ልዩ የገቢ ምንጮች 115.86 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ 118.91 ቢሊዮን ብር በመሰብሰብ የ103 በመቶ አፈጻጸም አሳይቷል።
ይህ የገቢ መጠን ከቀደመው በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ88.4 በመቶ ከፍተኛ እድገት ያሳየ ነው። ለዚህ አፈጻጸም መሻሻል የዲጂታል ክፍያ አማራጮች መስፋፋት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከተ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የዲጂታል ክፍያ የሚጠቀሙ ደንበኞች ቁጥር 95.3 በመቶ ደርሷል።
በተጨማሪም ተቋሙ ከስርቆትና ከኃይል ብክነት የመከላከል ሥራዎችን በማጠናከር ከ2.2 ቢሊዮን ብር በላይ ለተቋሙ ገቢ ማድረግ ችሏል።
ተቋሙ የአገልግሎት ጥራትን ለማሻሻልና የኃይል መቆራረጥን ለመቀነስ ሰፊ የዲስትሪቢዩሽን መስመሮች ማሻሻያ፣ የትራንስፎርመር ጥገናና የአቅም ማሳደግ ሥራዎችን ያከናወነ ቢሆንም፣ አሁንም የመሰረተ ልማት እርጅና፣ የግብዓትና የነዳጅ እጥረት እንዲሁም የመሰረተ ልማቶች ስርቆትና ውድመት ዋና ዋና ተግዳሮቶች እንደነበሩ ተገልጿል።
ሆኖም ተቋሙ የተደቀኑበትን ተግዳሮቶች በመቋቋም የቴክኖሎጂ ትግበራዎችን አጠናክሮ በመቀጠል፣ ለሀገር ኢኮኖሚ እድገትና ለዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስኬት የሚጠበቅበትን የላቀ ሚና አጠናክሮ እንደሚቀጥል ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገልጸዋል።
ጌትነት ተመስገን
#ethiopianelectricutility #eeu #ethiopia #energysector #ethiopianeconomy #digitalethiopia2030 #ruralelectrification #offgridenergy #performancereport #africaenergy
1 day ago
መንግሥት ሌብነትን እና ሕገወጥነትን ለመከላከል ጠንካራ እርምጃ እየወሰደ መሆኑን ገለጸ
በኢትዮጵያ ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን ሰፊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለማደናቀፍ በሚንቀሳቀሱ እና የሀገር ሀብት በሚመዘብሩ አካላት ላይ መንግሥት የማያዳግም እርምጃ እየወሰደ መሆኑን አስታወቀ።
የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ወይዘሮ እናትዓለም መለሰ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ፈጣን ልማትና ዕድገት እንድታረጋግጥ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቅሰው፣ በዚህም ሰፋፊና አስደናቂ ሀገራዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡ በዚህ ሂደት ግን ይህ ውጤት ጉዞው አልጋ በአልጋ እንዳልነበር አመላክተዋል ። ከተለያዩ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተግዳሮቶች ባሻገር፣ ሕገ-ወጥነት እና የሙስና ተግባራት የልማቱ ዋነኛ ፈተና ሆነው መቆየታቸውንም ክብርት ሚኒስትሯ አብራርተዋል።
እንደ ሚኒስትሯ ገለጻ፣ የሕገ-ወጥነት ችግር በአንድ ወገን ብቻ የሚፈጸም ሳይሆን በርካታ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የሚያጠቃልል መሆኑን ገልጸው ከውስጥም ከውጪም ያሉ በርካታ ኃይሎች በተደራጀ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ነበር፡፡ በንግዱ ማኅበረሰብ፣ በልማት ድርጅቶች፣ በመንግሥት መዋቅር፣ በግለሰቦች እና በተገልጋዮች ጭምር በተደራጀ መንገድ በስፋት የሚታይ ነው።
እነዚህ አካላት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ከቁጥጥር ውጭ ለማድረግ በፋይናንስ እና በንግድ ሥርዐቱ ውስጥ ሰርገው በመግባት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አሻጥር ሲፈጽሙ ቆይተዋል" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ድርጊቱ ሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ እንድታጣ፣ የዋጋ ንረትና ኮንትሮባንድ እንዲባባስ እንዲሁም በፍጆታ እቃዎች ላይ ሰው ሠራሽ እጥረት እንዲፈጠር ማድረጉን አስታውቀዋል። ይህንን የተደራጀ አሻጥር ለመግታት መንግሥት እና የሚመለከታቸው የሕግ አካላት ባከናወኑት ሰፊ ኦፕሬሽን አሻጥሩን ማክሸፍ መቻሉ ተገልጿል።
በሌላ በኩል በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት እንዲሁም የሕዝብ ተቋማት ውስጥ የተሰገሰጉ ሌቦችን በማጽዳት ረገድ መንግሥት ቁርጠኛ እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝ ያስታወቁት ወ/ሮ እናትዓለም በሕዝብ ሀብት ላይ ከፍተኛ ምዝበራ የፈጸሙ እና ተቋማዊ አሻጥር በሠሩ አመራሮች እና ሌሎች የጥቅም ትስስሮችና ድርጅቶች ላይ የማያዳግም እርምጃ መወሰዱንም አስታውቀዋል። በተለይም በሚከተሉት ቁልፍ ዘርፎች ላይ በተፈጸሙ ወንጀሎች ሰፊ ማጣራት ተደርጎ ተጠያቂነት ሰፍኗል ሲሉ ገልጸዋል፡
በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት፣ እንዲሁም ልዩ ልዩ የልማት ዘርፎች ውስጥ የተፈጸሙ ዋና ዋና የሙስና እና አሻጥር ወንጀሎችን ለማረም በተወሰዱት ሰፊ ኦፕሬሽኖች እና ሕግ የማስከበር እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር በተያያዘ ማሻሻያውን ለማደናቀፍ በማሰብ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን በማከማቸት እጥረት እንዲፈጠርና ዋጋ እንዲንር ሲያደርጉ የነበሩ 13 አቅራቢ ድርጅቶች ባለቤቶች ላይ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፤ ሕገ-ወጥ ተግባር ሲፈጽሙ በነበሩ ከ7 ሺህ በላይ የንግድ ድርጅቶችና መጋዘኖች ላይ የማሸግ እርምጃ ተወስዷል።
በፋይናንስ ተቋማት እና የገንዘብ ዝውውር፡ በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ በሐዋላ እና በጥቁር ገበያ ተሳታፊ የሆኑ 169 ኢትዮጵያውያንና የውጭ ሀገር ዜጎች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተደራጀ መንገድ ከንግድ ባንክ ደንበኞች አካውንት ላይ በማጭበርበር ገንዘብ የወሰዱ 36 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው የባንክ ሒሳባቸው እንዲታገድ ተደርጓል።
ለሕገ-ወጥ ዝውውር ሽፋን ይሰጡ የነበሩ 7 የክሪፕቶ ካረንሲ መተግበሪያዎች በሀገር ውስጥ እንዳይሠሩ ሙሉ በሙሉ ታግደዋል፤ ምርት ልከው የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ያላደረጉ 29 ላኪ የንግድ ድርጅቶችና ግለሰቦች ላይም የህግ ተጠያቂነት ሰፍኗል።
በቤቲንግ እና ፊንቴክ ቢዝነሶች፡ የደንበኞችን መረጃ በመደበቅ መንግሥትን ግብር ያጭበረበሩ፣ ገቢያቸውን የሰወሩ እና ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር በፈጸሙ 38 የቤቲንግ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወስዶ ባለቤቶቻቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል፤ የእነዚህ ሕገ-ወጥ ተቋማት የባንክ ሒሳብ ታግዷል፤
በማዕድን ዘርፍ ሕገ-ወጥ ዝውውር፡ የወርቅ ምርትን ከገበያ ውጭ በኮንትሮባንድ በማስወጣት ወንጀል የተሳተፉ የመንግሥት ኃላፊዎችን፣ የፀጥታ መዋቅር አመራሮችን፣ አምራቾችን እና የውጭ ዜጎችን ጨምሮ 183 ግለሰቦች በሕግ ተጠያቂ ተደርገዋል። በወንጀሉ የተሳተፉ የውጭ ሀገር ዜጎች ከሀገር እንዲወጡ ተደርገዋል፤ ሕገ-ወጥ ወርቅ፣ የወርቅ ሚዛንና ማቅለጫ፣ የተለያዩ የውጭ ሀገራት ገንዘቦች፣ እንዲሁም የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ከነዳጅ አቅርቦት እና ሎጂስቲክስ አንጻር፡ በሕገ-ወጥ መንገድ የሽፋን ደብዳቤዎችን በማዘጋጀት፣ ነዳጅ በመደበቅ እና አየር በአየር በመሸጥ ወንጀል የተሳተፉ 38 የመንግሥት አመራሮች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተጨማሪም በሀገር አቀፍ ደረጃ በሕገ-ወጥ የነዳጅ ንግድ ላይ የተሰማሩ ከ650 በላይ ግለሰቦች፣ ማደያዎች እና አቅራቢ ኩባንያዎች ላይ የህግ እርምጃ ተወስዷል።
በአፈር ማዳበሪያ ግዢ አሻጥር፡ በተቋሙ የጥቅም ትስስር በመፍጠር ጥራት የጎደለውና ጊዜው ያለፈበት የአፈር ማዳበሪያ ግዢ እንዲፈጸም በማድረግ ሆን ብለው ችግር በፈጠሩ የግብርና ሚኒስቴር አመራሮች ላይ የወንጀል ተጠያቂነት እርምጃ ተወስዷል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (EEP)፡ ተገቢው መመሪያ በሌለበት ሁኔታ ከ36 የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች ጋር ሕገ-ወጥ የኃይል ሽያጭ ውል የፈጸሙ 4 ከፍተኛ አመራሮች ላይ እርምጃ ተወስዷል። የኤሌክትሪክ ኃይል ስርቆት የፈጸሙ ድርጅቶች እና ግለሰቦችም እንዲሁ በሕግ እንዲጠየቁ ተደርጓል።
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የሰዎች ዝውውር የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ሲስተምን በማዛባት እና ጉቦ በመቀበል ወንጀል የተሳተፉ 8 ከፍተኛ አመራሮችና ሠራተኞች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል። እንዲሁም በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ የተሰማሩ 44 ደላሎች እና አዘዋዋሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር ሲውሉ፣ ሕገ-ወጥ ፈቃድ የነበራቸው ተቋማት ሙሉ በሙሉ ታሽገዋል።
በገቢዎችና ጉምሩክ ዘርፍ፡ የግብር ውሳኔዎችን በመቀነስ፣ ሐሰተኛ ደረሰኞች በማወራረድ፣ እና በሲስተም መረጃ በማጥፋት የመንግሥት ገቢን ባሳጡ አካላት ላይ ኦፕሬሽን ተካሂዷል። በራሳቸው፣ በዘመድ እና በሹፌሮቻቸው አካውንት በመጠቀም የጥቅም ትስስር የፈጠሩ 109 ተጠርጣሪዎች ተለይተው ከእነዚህ መካከል 91 ግለሰቦች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
መንግሥት የልማት እንቅፋት የሆኑትን ሙስና እና ሌብነት እንደማንኛውም ፈተና በጽናት እየተጋፈጣቸው መሆኑን ሚኒስትሯ አረጋግጠዋል።
መንግሥት ሌብነትን ለማጥፋት ዘመናዊ አሠራሮችን በመዘርጋት እና በዲሲፕሊን የታነጸ አመራር ለመገንባት ቁርጠኛ ነው" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ሕዝቡ በስፋት የሚያነሣቸውን "ሌብነትን አስቁሙልን" ጥያቄዎች ለመመለስ የተጀመረዉ ጠንካራ እርምጃ ውጤታማ እንዲሆኑ ማኅበረሰቡ ሙስናን በማጋለጥ፣ ሕጋዊ መብቱን በመደለያ ባለመጠየቅ እና ከሕገወጦች ጋር ባለመተባበር ከመንግሥት ጎን በመቆም ሀገርን ከሕገወጥነትና ሙስና የመከላከል ታሪካዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
በኢትዮጵያ ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን ሰፊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለማደናቀፍ በሚንቀሳቀሱ እና የሀገር ሀብት በሚመዘብሩ አካላት ላይ መንግሥት የማያዳግም እርምጃ እየወሰደ መሆኑን አስታወቀ።
የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ወይዘሮ እናትዓለም መለሰ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ፈጣን ልማትና ዕድገት እንድታረጋግጥ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቅሰው፣ በዚህም ሰፋፊና አስደናቂ ሀገራዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡ በዚህ ሂደት ግን ይህ ውጤት ጉዞው አልጋ በአልጋ እንዳልነበር አመላክተዋል ። ከተለያዩ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተግዳሮቶች ባሻገር፣ ሕገ-ወጥነት እና የሙስና ተግባራት የልማቱ ዋነኛ ፈተና ሆነው መቆየታቸውንም ክብርት ሚኒስትሯ አብራርተዋል።
እንደ ሚኒስትሯ ገለጻ፣ የሕገ-ወጥነት ችግር በአንድ ወገን ብቻ የሚፈጸም ሳይሆን በርካታ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የሚያጠቃልል መሆኑን ገልጸው ከውስጥም ከውጪም ያሉ በርካታ ኃይሎች በተደራጀ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ነበር፡፡ በንግዱ ማኅበረሰብ፣ በልማት ድርጅቶች፣ በመንግሥት መዋቅር፣ በግለሰቦች እና በተገልጋዮች ጭምር በተደራጀ መንገድ በስፋት የሚታይ ነው።
እነዚህ አካላት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ከቁጥጥር ውጭ ለማድረግ በፋይናንስ እና በንግድ ሥርዐቱ ውስጥ ሰርገው በመግባት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አሻጥር ሲፈጽሙ ቆይተዋል" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ድርጊቱ ሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ እንድታጣ፣ የዋጋ ንረትና ኮንትሮባንድ እንዲባባስ እንዲሁም በፍጆታ እቃዎች ላይ ሰው ሠራሽ እጥረት እንዲፈጠር ማድረጉን አስታውቀዋል። ይህንን የተደራጀ አሻጥር ለመግታት መንግሥት እና የሚመለከታቸው የሕግ አካላት ባከናወኑት ሰፊ ኦፕሬሽን አሻጥሩን ማክሸፍ መቻሉ ተገልጿል።
በሌላ በኩል በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት እንዲሁም የሕዝብ ተቋማት ውስጥ የተሰገሰጉ ሌቦችን በማጽዳት ረገድ መንግሥት ቁርጠኛ እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝ ያስታወቁት ወ/ሮ እናትዓለም በሕዝብ ሀብት ላይ ከፍተኛ ምዝበራ የፈጸሙ እና ተቋማዊ አሻጥር በሠሩ አመራሮች እና ሌሎች የጥቅም ትስስሮችና ድርጅቶች ላይ የማያዳግም እርምጃ መወሰዱንም አስታውቀዋል። በተለይም በሚከተሉት ቁልፍ ዘርፎች ላይ በተፈጸሙ ወንጀሎች ሰፊ ማጣራት ተደርጎ ተጠያቂነት ሰፍኗል ሲሉ ገልጸዋል፡
በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት፣ እንዲሁም ልዩ ልዩ የልማት ዘርፎች ውስጥ የተፈጸሙ ዋና ዋና የሙስና እና አሻጥር ወንጀሎችን ለማረም በተወሰዱት ሰፊ ኦፕሬሽኖች እና ሕግ የማስከበር እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር በተያያዘ ማሻሻያውን ለማደናቀፍ በማሰብ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን በማከማቸት እጥረት እንዲፈጠርና ዋጋ እንዲንር ሲያደርጉ የነበሩ 13 አቅራቢ ድርጅቶች ባለቤቶች ላይ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፤ ሕገ-ወጥ ተግባር ሲፈጽሙ በነበሩ ከ7 ሺህ በላይ የንግድ ድርጅቶችና መጋዘኖች ላይ የማሸግ እርምጃ ተወስዷል።
በፋይናንስ ተቋማት እና የገንዘብ ዝውውር፡ በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ በሐዋላ እና በጥቁር ገበያ ተሳታፊ የሆኑ 169 ኢትዮጵያውያንና የውጭ ሀገር ዜጎች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተደራጀ መንገድ ከንግድ ባንክ ደንበኞች አካውንት ላይ በማጭበርበር ገንዘብ የወሰዱ 36 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው የባንክ ሒሳባቸው እንዲታገድ ተደርጓል።
ለሕገ-ወጥ ዝውውር ሽፋን ይሰጡ የነበሩ 7 የክሪፕቶ ካረንሲ መተግበሪያዎች በሀገር ውስጥ እንዳይሠሩ ሙሉ በሙሉ ታግደዋል፤ ምርት ልከው የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ያላደረጉ 29 ላኪ የንግድ ድርጅቶችና ግለሰቦች ላይም የህግ ተጠያቂነት ሰፍኗል።
በቤቲንግ እና ፊንቴክ ቢዝነሶች፡ የደንበኞችን መረጃ በመደበቅ መንግሥትን ግብር ያጭበረበሩ፣ ገቢያቸውን የሰወሩ እና ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር በፈጸሙ 38 የቤቲንግ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወስዶ ባለቤቶቻቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል፤ የእነዚህ ሕገ-ወጥ ተቋማት የባንክ ሒሳብ ታግዷል፤
በማዕድን ዘርፍ ሕገ-ወጥ ዝውውር፡ የወርቅ ምርትን ከገበያ ውጭ በኮንትሮባንድ በማስወጣት ወንጀል የተሳተፉ የመንግሥት ኃላፊዎችን፣ የፀጥታ መዋቅር አመራሮችን፣ አምራቾችን እና የውጭ ዜጎችን ጨምሮ 183 ግለሰቦች በሕግ ተጠያቂ ተደርገዋል። በወንጀሉ የተሳተፉ የውጭ ሀገር ዜጎች ከሀገር እንዲወጡ ተደርገዋል፤ ሕገ-ወጥ ወርቅ፣ የወርቅ ሚዛንና ማቅለጫ፣ የተለያዩ የውጭ ሀገራት ገንዘቦች፣ እንዲሁም የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ከነዳጅ አቅርቦት እና ሎጂስቲክስ አንጻር፡ በሕገ-ወጥ መንገድ የሽፋን ደብዳቤዎችን በማዘጋጀት፣ ነዳጅ በመደበቅ እና አየር በአየር በመሸጥ ወንጀል የተሳተፉ 38 የመንግሥት አመራሮች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተጨማሪም በሀገር አቀፍ ደረጃ በሕገ-ወጥ የነዳጅ ንግድ ላይ የተሰማሩ ከ650 በላይ ግለሰቦች፣ ማደያዎች እና አቅራቢ ኩባንያዎች ላይ የህግ እርምጃ ተወስዷል።
በአፈር ማዳበሪያ ግዢ አሻጥር፡ በተቋሙ የጥቅም ትስስር በመፍጠር ጥራት የጎደለውና ጊዜው ያለፈበት የአፈር ማዳበሪያ ግዢ እንዲፈጸም በማድረግ ሆን ብለው ችግር በፈጠሩ የግብርና ሚኒስቴር አመራሮች ላይ የወንጀል ተጠያቂነት እርምጃ ተወስዷል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (EEP)፡ ተገቢው መመሪያ በሌለበት ሁኔታ ከ36 የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች ጋር ሕገ-ወጥ የኃይል ሽያጭ ውል የፈጸሙ 4 ከፍተኛ አመራሮች ላይ እርምጃ ተወስዷል። የኤሌክትሪክ ኃይል ስርቆት የፈጸሙ ድርጅቶች እና ግለሰቦችም እንዲሁ በሕግ እንዲጠየቁ ተደርጓል።
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የሰዎች ዝውውር የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ሲስተምን በማዛባት እና ጉቦ በመቀበል ወንጀል የተሳተፉ 8 ከፍተኛ አመራሮችና ሠራተኞች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል። እንዲሁም በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ የተሰማሩ 44 ደላሎች እና አዘዋዋሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር ሲውሉ፣ ሕገ-ወጥ ፈቃድ የነበራቸው ተቋማት ሙሉ በሙሉ ታሽገዋል።
በገቢዎችና ጉምሩክ ዘርፍ፡ የግብር ውሳኔዎችን በመቀነስ፣ ሐሰተኛ ደረሰኞች በማወራረድ፣ እና በሲስተም መረጃ በማጥፋት የመንግሥት ገቢን ባሳጡ አካላት ላይ ኦፕሬሽን ተካሂዷል። በራሳቸው፣ በዘመድ እና በሹፌሮቻቸው አካውንት በመጠቀም የጥቅም ትስስር የፈጠሩ 109 ተጠርጣሪዎች ተለይተው ከእነዚህ መካከል 91 ግለሰቦች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
መንግሥት የልማት እንቅፋት የሆኑትን ሙስና እና ሌብነት እንደማንኛውም ፈተና በጽናት እየተጋፈጣቸው መሆኑን ሚኒስትሯ አረጋግጠዋል።
መንግሥት ሌብነትን ለማጥፋት ዘመናዊ አሠራሮችን በመዘርጋት እና በዲሲፕሊን የታነጸ አመራር ለመገንባት ቁርጠኛ ነው" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ሕዝቡ በስፋት የሚያነሣቸውን "ሌብነትን አስቁሙልን" ጥያቄዎች ለመመለስ የተጀመረዉ ጠንካራ እርምጃ ውጤታማ እንዲሆኑ ማኅበረሰቡ ሙስናን በማጋለጥ፣ ሕጋዊ መብቱን በመደለያ ባለመጠየቅ እና ከሕገወጦች ጋር ባለመተባበር ከመንግሥት ጎን በመቆም ሀገርን ከሕገወጥነትና ሙስና የመከላከል ታሪካዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
1 day ago
በሙስናና ሕገ-ወጥ አሠራር የተሳተፉ አካላት ላይ የሕግ እርምጃ ተወሰደ
በኢትዮጵያ ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን ሰፊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለማደናቀፍ በሚንቀሳቀሱ እና የሀገር ሀብት በሚመዘብሩ አካላት ላይ መንግሥት የማያዳግም እርምጃ እየወሰደ መሆኑን አስታወቀ።
የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ወይዘሮ እናትዓለም መለሰ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ፈጣን ልማትና ዕድገት እንድታረጋግጥ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቅሰው፣ በዚህም ሰፋፊና አስደናቂ ሀገራዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። በዚህ ሂደት ግን ይህ ውጤት ጉዞው አልጋ በአልጋ እንዳልነበር አመላክተዋል። ከተለያዩ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተግዳሮቶች ባሻገር፣ ሕገ-ወጥነት እና የሙስና ተግባራት የልማቱ ዋነኛ ፈተና ሆነው መቆየታቸውንም ክብርት ሚኒስትሯ አብራርተዋል።
እንደ ሚኒስትሯ ገለጻ፣ የሕገ-ወጥነት ችግር በአንድ ወገን ብቻ የሚፈጸም ሳይሆን በርካታ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የሚያጠቃልል መሆኑን ገልጸው ከውስጥም ከውጪም ያሉ በርካታ ኃይሎች በተደራጀ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ነበር። በንግዱ ማኅበረሰብ፣ በልማት ድርጅቶች፣ በመንግሥት መዋቅር፣ በግለሰቦች እና በተገልጋዮች ጭምር በተደራጀ መንገድ በስፋት የሚታይ ነው።
እነዚህ አካላት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ከቁጥጥር ውጭ ለማድረግ በፋይናንስ እና በንግድ ሥርዐቱ ውስጥ ሰርገው በመግባት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አሻጥር ሲፈጽሙ ቆይተዋል" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ድርጊቱ ሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ እንድታጣ፣ የዋጋ ንረትና ኮንትሮባንድ እንዲባባስ እንዲሁም በፍጆታ እቃዎች ላይ ሰው ሠራሽ እጥረት እንዲፈጠር ማድረጉን አስታውቀዋል። ይህንን የተደራጀ አሻጥር ለመግታት መንግሥት እና የሚመለከታቸው የሕግ አካላት ባከናወኑት ሰፊ ኦፕሬሽን አሻጥሩን ማክሸፍ መቻሉ ተገልጿል።
በሌላ በኩል በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት እንዲሁም የሕዝብ ተቋማት ውስጥ የተሰገሰጉ ሌቦችን በማጽዳት ረገድ መንግሥት ቁርጠኛ እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝ ያስታወቁት ወ/ሮ እናትዓለም በሕዝብ ሀብት ላይ ከፍተኛ ምዝበራ የፈጸሙ እና ተቋማዊ አሻጥር በሠሩ አመራሮች እና ሌሎች የጥቅም ትስስሮችና ድርጅቶች ላይ የማያዳግም እርምጃ መወሰዱንም አስታውቀዋል። በተለይም በሚከተሉት ቁልፍ ዘርፎች ላይ በተፈጸሙ ወንጀሎች ሰፊ ማጣራት ተደርጎ ተጠያቂነት ሰፍኗል ሲሉ ገልጸዋል።
በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት፣ እንዲሁም ልዩ ልዩ የልማት ዘርፎች ውስጥ የተፈጸሙ ዋና ዋና የሙስና እና አሻጥር ወንጀሎችን ለማረም በተወሰዱት ሰፊ ኦፕሬሽኖች እና ሕግ የማስከበር እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር በተያያዘ ማሻሻያውን ለማደናቀፍ በማሰብ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን በማከማቸት እጥረት እንዲፈጠርና ዋጋ እንዲንር ሲያደርጉ የነበሩ 13 አቅራቢ ድርጅቶች ባለቤቶች ላይ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፤ ሕገ-ወጥ ተግባር ሲፈጽሙ በነበሩ ከ7 ሺህ በላይ የንግድ ድርጅቶችና መጋዘኖች ላይ የማሸግ እርምጃ ተወስዷል።
በፋይናንስ ተቋማት እና የገንዘብ ዝውውር፡ በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ በሐዋላ እና በጥቁር ገበያ ተሳታፊ የሆኑ 169 ኢትዮጵያውያንና የውጭ ሀገር ዜጎች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተደራጀ መንገድ ከንግድ ባንክ ደንበኞች አካውንት ላይ በማጭበርበር ገንዘብ የወሰዱ 36 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው የባንክ ሒሳባቸው እንዲታገድ ተደርጓል።
ለሕገ-ወጥ ዝውውር ሽፋን ይሰጡ የነበሩ 7 የክሪፕቶ ካረንሲ መተግበሪያዎች በሀገር ውስጥ እንዳይሠሩ ሙሉ በሙሉ ታግደዋል፤ ምርት ልከው የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ያላደረጉ 29 ላኪ የንግድ ድርጅቶችና ግለሰቦች ላይም የህግ ተጠያቂነት ሰፍኗል።
በቤቲንግ እና ፊንቴክ ቢዝነሶች፡ የደንበኞችን መረጃ በመደበቅ መንግሥትን ግብር ያጭበረበሩ፣ ገቢያቸውን የሰወሩ እና ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር በፈጸሙ 38 የቤቲንግ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወስዶ ባለቤቶቻቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል፤ የእነዚህ ሕገ-ወጥ ተቋማት የባንክ ሒሳብ ታግዷል፤
በማዕድን ዘርፍ ሕገ-ወጥ ዝውውር፡ የወርቅ ምርትን ከገበያ ውጭ በኮንትሮባንድ በማስወጣት ወንጀል የተሳተፉ የመንግሥት ኃላፊዎችን፣ የፀጥታ መዋቅር አመራሮችን፣ አምራቾችን እና የውጭ ዜጎችን ጨምሮ 183 ግለሰቦች በሕግ ተጠያቂ ተደርገዋል። በወንጀሉ የተሳተፉ የውጭ ሀገር ዜጎች ከሀገር እንዲወጡ ተደርገዋል፤ ሕገ-ወጥ ወርቅ፣ የወርቅ ሚዛንና ማቅለጫ፣ የተለያዩ የውጭ ሀገራት ገንዘቦች፣ እንዲሁም የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ከነዳጅ አቅርቦት እና ሎጂስቲክስ አንጻር፡ በሕገ-ወጥ መንገድ የሽፋን ደብዳቤዎችን በማዘጋጀት፣ ነዳጅ በመደበቅ እና አየር በአየር በመሸጥ ወንጀል የተሳተፉ 38 የመንግሥት አመራሮች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተጨማሪም በሀገር አቀፍ ደረጃ በሕገ-ወጥ የነዳጅ ንግድ ላይ የተሰማሩ ከ650 በላይ ግለሰቦች፣ ማደያዎች እና አቅራቢ ኩባንያዎች ላይ የህግ እርምጃ ተወስዷል።
በአፈር ማዳበሪያ ግዢ አሻጥር፡ በተቋሙ የጥቅም ትስስር በመፍጠር ጥራት የጎደለውና ጊዜው ያለፈበት የአፈር ማዳበሪያ ግዢ እንዲፈጸም በማድረግ ሆን ብለው ችግር በፈጠሩ የግብርና ሚኒስቴር አመራሮች ላይ የወንጀል ተጠያቂነት እርምጃ ተወስዷል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (EEP)፡ ተገቢው መመሪያ በሌለበት ሁኔታ ከ36 የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች ጋር ሕገ-ወጥ የኃይል ሽያጭ ውል የፈጸሙ 4 ከፍተኛ አመራሮች ላይ እርምጃ ተወስዷል። የኤሌክትሪክ ኃይል ስርቆት የፈጸሙ ድርጅቶች እና ግለሰቦችም እንዲሁ በሕግ እንዲጠየቁ ተደርጓል።
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የሰዎች ዝውውር የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ሲስተምን በማዛባት እና ጉቦ በመቀበል ወንጀል የተሳተፉ 8 ከፍተኛ አመራሮችና ሠራተኞች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል። እንዲሁም በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ የተሰማሩ 44 ደላሎች እና አዘዋዋሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር ሲውሉ፣ ሕገ-ወጥ ፈቃድ የነበራቸው ተቋማት ሙሉ በሙሉ ታሽገዋል።
በገቢዎችና ጉምሩክ ዘርፍ፡ የግብር ውሳኔዎችን በመቀነስ፣ ሐሰተኛ ደረሰኞች በማወራረድ፣ እና በሲስተም መረጃ በማጥፋት የመንግሥት ገቢን ባሳጡ አካላት ላይ ኦፕሬሽን ተካሂዷል።
በራሳቸው፣ በዘመድ እና በሹፌሮቻቸው አካውንት በመጠቀም የጥቅም ትስስር የፈጠሩ 109 ተጠርጣሪዎች ተለይተው ከእነዚህ መካከል 91 ግለሰቦች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
መንግሥት የልማት እንቅፋት የሆኑትን ሙስና እና ሌብነት እንደማንኛውም ፈተና በጽናት እየተጋፈጣቸው መሆኑን ሚኒስትሯ አረጋግጠዋል።
መንግሥት ሌብነትን ለማጥፋት ዘመናዊ አሠራሮችን በመዘርጋት እና በዲሲፕሊን የታነጸ አመራር ለመገንባት ቁርጠኛ ነው" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ሕዝቡ በስፋት የሚያነሣቸውን "ሌብነትን አስቁሙልን" ጥያቄዎች ለመመለስ የተጀመረዉ ጠንካራ እርምጃ ውጤታማ እንዲሆኑ ማኅበረሰቡ ሙስናን በማጋለጥ፣ ሕጋዊ መብቱን በመደለያ ባለመጠየቅ እና ከሕገወጦች ጋር ባለመተባበር ከመንግሥት ጎን በመቆም ሀገርን ከሕገወጥነትና ሙስና የመከላከል ታሪካዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
Via EBC
በኢትዮጵያ ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን ሰፊ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለማደናቀፍ በሚንቀሳቀሱ እና የሀገር ሀብት በሚመዘብሩ አካላት ላይ መንግሥት የማያዳግም እርምጃ እየወሰደ መሆኑን አስታወቀ።
የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ወይዘሮ እናትዓለም መለሰ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ፈጣን ልማትና ዕድገት እንድታረጋግጥ በርካታ ሥራዎች መሠራታቸውን ጠቅሰው፣ በዚህም ሰፋፊና አስደናቂ ሀገራዊ ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል። በዚህ ሂደት ግን ይህ ውጤት ጉዞው አልጋ በአልጋ እንዳልነበር አመላክተዋል። ከተለያዩ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተግዳሮቶች ባሻገር፣ ሕገ-ወጥነት እና የሙስና ተግባራት የልማቱ ዋነኛ ፈተና ሆነው መቆየታቸውንም ክብርት ሚኒስትሯ አብራርተዋል።
እንደ ሚኒስትሯ ገለጻ፣ የሕገ-ወጥነት ችግር በአንድ ወገን ብቻ የሚፈጸም ሳይሆን በርካታ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የሚያጠቃልል መሆኑን ገልጸው ከውስጥም ከውጪም ያሉ በርካታ ኃይሎች በተደራጀ መንገድ ሲንቀሳቀሱ ነበር። በንግዱ ማኅበረሰብ፣ በልማት ድርጅቶች፣ በመንግሥት መዋቅር፣ በግለሰቦች እና በተገልጋዮች ጭምር በተደራጀ መንገድ በስፋት የሚታይ ነው።
እነዚህ አካላት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ከቁጥጥር ውጭ ለማድረግ በፋይናንስ እና በንግድ ሥርዐቱ ውስጥ ሰርገው በመግባት ከፍተኛ የኢኮኖሚ አሻጥር ሲፈጽሙ ቆይተዋል" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ድርጊቱ ሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ እንድታጣ፣ የዋጋ ንረትና ኮንትሮባንድ እንዲባባስ እንዲሁም በፍጆታ እቃዎች ላይ ሰው ሠራሽ እጥረት እንዲፈጠር ማድረጉን አስታውቀዋል። ይህንን የተደራጀ አሻጥር ለመግታት መንግሥት እና የሚመለከታቸው የሕግ አካላት ባከናወኑት ሰፊ ኦፕሬሽን አሻጥሩን ማክሸፍ መቻሉ ተገልጿል።
በሌላ በኩል በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት እንዲሁም የሕዝብ ተቋማት ውስጥ የተሰገሰጉ ሌቦችን በማጽዳት ረገድ መንግሥት ቁርጠኛ እርምጃ እየወሰደ እንደሚገኝ ያስታወቁት ወ/ሮ እናትዓለም በሕዝብ ሀብት ላይ ከፍተኛ ምዝበራ የፈጸሙ እና ተቋማዊ አሻጥር በሠሩ አመራሮች እና ሌሎች የጥቅም ትስስሮችና ድርጅቶች ላይ የማያዳግም እርምጃ መወሰዱንም አስታውቀዋል። በተለይም በሚከተሉት ቁልፍ ዘርፎች ላይ በተፈጸሙ ወንጀሎች ሰፊ ማጣራት ተደርጎ ተጠያቂነት ሰፍኗል ሲሉ ገልጸዋል።
በመንግሥት አገልግሎት ሰጪ እና አስተዳደር አካላት፣ እንዲሁም ልዩ ልዩ የልማት ዘርፎች ውስጥ የተፈጸሙ ዋና ዋና የሙስና እና አሻጥር ወንጀሎችን ለማረም በተወሰዱት ሰፊ ኦፕሬሽኖች እና ሕግ የማስከበር እርምጃዎች ተጨባጭ ውጤቶች ተመዝግበዋል። ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር በተያያዘ ማሻሻያውን ለማደናቀፍ በማሰብ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን በማከማቸት እጥረት እንዲፈጠርና ዋጋ እንዲንር ሲያደርጉ የነበሩ 13 አቅራቢ ድርጅቶች ባለቤቶች ላይ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፤ ሕገ-ወጥ ተግባር ሲፈጽሙ በነበሩ ከ7 ሺህ በላይ የንግድ ድርጅቶችና መጋዘኖች ላይ የማሸግ እርምጃ ተወስዷል።
በፋይናንስ ተቋማት እና የገንዘብ ዝውውር፡ በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ በሐዋላ እና በጥቁር ገበያ ተሳታፊ የሆኑ 169 ኢትዮጵያውያንና የውጭ ሀገር ዜጎች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተደራጀ መንገድ ከንግድ ባንክ ደንበኞች አካውንት ላይ በማጭበርበር ገንዘብ የወሰዱ 36 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው የባንክ ሒሳባቸው እንዲታገድ ተደርጓል።
ለሕገ-ወጥ ዝውውር ሽፋን ይሰጡ የነበሩ 7 የክሪፕቶ ካረንሲ መተግበሪያዎች በሀገር ውስጥ እንዳይሠሩ ሙሉ በሙሉ ታግደዋል፤ ምርት ልከው የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ያላደረጉ 29 ላኪ የንግድ ድርጅቶችና ግለሰቦች ላይም የህግ ተጠያቂነት ሰፍኗል።
በቤቲንግ እና ፊንቴክ ቢዝነሶች፡ የደንበኞችን መረጃ በመደበቅ መንግሥትን ግብር ያጭበረበሩ፣ ገቢያቸውን የሰወሩ እና ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር በፈጸሙ 38 የቤቲንግ ድርጅቶች ላይ እርምጃ ተወስዶ ባለቤቶቻቸው በቁጥጥር ስር ውለዋል፤ የእነዚህ ሕገ-ወጥ ተቋማት የባንክ ሒሳብ ታግዷል፤
በማዕድን ዘርፍ ሕገ-ወጥ ዝውውር፡ የወርቅ ምርትን ከገበያ ውጭ በኮንትሮባንድ በማስወጣት ወንጀል የተሳተፉ የመንግሥት ኃላፊዎችን፣ የፀጥታ መዋቅር አመራሮችን፣ አምራቾችን እና የውጭ ዜጎችን ጨምሮ 183 ግለሰቦች በሕግ ተጠያቂ ተደርገዋል። በወንጀሉ የተሳተፉ የውጭ ሀገር ዜጎች ከሀገር እንዲወጡ ተደርገዋል፤ ሕገ-ወጥ ወርቅ፣ የወርቅ ሚዛንና ማቅለጫ፣ የተለያዩ የውጭ ሀገራት ገንዘቦች፣ እንዲሁም የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ከነዳጅ አቅርቦት እና ሎጂስቲክስ አንጻር፡ በሕገ-ወጥ መንገድ የሽፋን ደብዳቤዎችን በማዘጋጀት፣ ነዳጅ በመደበቅ እና አየር በአየር በመሸጥ ወንጀል የተሳተፉ 38 የመንግሥት አመራሮች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ተደርጓል። በተጨማሪም በሀገር አቀፍ ደረጃ በሕገ-ወጥ የነዳጅ ንግድ ላይ የተሰማሩ ከ650 በላይ ግለሰቦች፣ ማደያዎች እና አቅራቢ ኩባንያዎች ላይ የህግ እርምጃ ተወስዷል።
በአፈር ማዳበሪያ ግዢ አሻጥር፡ በተቋሙ የጥቅም ትስስር በመፍጠር ጥራት የጎደለውና ጊዜው ያለፈበት የአፈር ማዳበሪያ ግዢ እንዲፈጸም በማድረግ ሆን ብለው ችግር በፈጠሩ የግብርና ሚኒስቴር አመራሮች ላይ የወንጀል ተጠያቂነት እርምጃ ተወስዷል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (EEP)፡ ተገቢው መመሪያ በሌለበት ሁኔታ ከ36 የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች ጋር ሕገ-ወጥ የኃይል ሽያጭ ውል የፈጸሙ 4 ከፍተኛ አመራሮች ላይ እርምጃ ተወስዷል። የኤሌክትሪክ ኃይል ስርቆት የፈጸሙ ድርጅቶች እና ግለሰቦችም እንዲሁ በሕግ እንዲጠየቁ ተደርጓል።
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የሰዎች ዝውውር የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ሲስተምን በማዛባት እና ጉቦ በመቀበል ወንጀል የተሳተፉ 8 ከፍተኛ አመራሮችና ሠራተኞች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል። እንዲሁም በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ የተሰማሩ 44 ደላሎች እና አዘዋዋሪዎች በሕግ ቁጥጥር ስር ሲውሉ፣ ሕገ-ወጥ ፈቃድ የነበራቸው ተቋማት ሙሉ በሙሉ ታሽገዋል።
በገቢዎችና ጉምሩክ ዘርፍ፡ የግብር ውሳኔዎችን በመቀነስ፣ ሐሰተኛ ደረሰኞች በማወራረድ፣ እና በሲስተም መረጃ በማጥፋት የመንግሥት ገቢን ባሳጡ አካላት ላይ ኦፕሬሽን ተካሂዷል።
በራሳቸው፣ በዘመድ እና በሹፌሮቻቸው አካውንት በመጠቀም የጥቅም ትስስር የፈጠሩ 109 ተጠርጣሪዎች ተለይተው ከእነዚህ መካከል 91 ግለሰቦች በሕግ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
መንግሥት የልማት እንቅፋት የሆኑትን ሙስና እና ሌብነት እንደማንኛውም ፈተና በጽናት እየተጋፈጣቸው መሆኑን ሚኒስትሯ አረጋግጠዋል።
መንግሥት ሌብነትን ለማጥፋት ዘመናዊ አሠራሮችን በመዘርጋት እና በዲሲፕሊን የታነጸ አመራር ለመገንባት ቁርጠኛ ነው" ያሉት ወይዘሮ እናትዓለም፤ ሕዝቡ በስፋት የሚያነሣቸውን "ሌብነትን አስቁሙልን" ጥያቄዎች ለመመለስ የተጀመረዉ ጠንካራ እርምጃ ውጤታማ እንዲሆኑ ማኅበረሰቡ ሙስናን በማጋለጥ፣ ሕጋዊ መብቱን በመደለያ ባለመጠየቅ እና ከሕገወጦች ጋር ባለመተባበር ከመንግሥት ጎን በመቆም ሀገርን ከሕገወጥነትና ሙስና የመከላከል ታሪካዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
Via EBC
2 days ago
ከ1 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ ንብረት የሰረቀው የሆስፒታሉ ጥበቃ በ7 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጣ
ተከሳሽ እንድሪያስ ቶማስ ግያ በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪና ሪፈራል ሆስፒታል የጥበቃ ሠራተኛ ሆኖ እየሰራ ሀምሌ 22 ቀን 2018 ከምሽቱ 4:00 እስከ 6፡00 ባለዉ ጊዜ የወንጀል ድርጊቱ ተፈፅሟል።
የሆስፒታሉ ንብረት የሆነውን ሶስት ማይክሮስኮፕ የእያንዳንዳቸዉ ዋጋ ሶስት መቶ ሀምሳ ሺ ብር በድምሩ አንድ ሚሊዮን ሀምሳ ሺ ብር የሚያወጣዉን ከክፍሉ ሠራተኞች ጋር በመተባበር ንብረቱ ያለበትን ክፍል በቁልፍ ከፍቶ ከወሰደ እና ንብረቱን በተቋሙ ዉስጥ ባለዉ ሳርና ሀረግ ዉስጥ ደብቆ ካቆየ በኋላ ሀምሌ 25 ከሌሊቱ 9 ሰዓት ንብረቱን ካቆየበት ሥፍራ አንስቶ እየወሰደ እያለ ከንብረቱ ጋር የተያዘ ስለሆነ ተከሳሽ በፈፀመው ከባድ ስርቆት ወንጀል ተከሷል ።
የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ፍትህ መምሪያ ዐ/ሕግ ያቀረበውን ክስ ሲያከራክር የቆየው የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተከሳሽ የቀረበበትን ክስ ሙሉ በሙሉ ያመነ መሆኑን ግምት ውስጥ በማስገባት የጥፋተኝነት ውሳኔ ሰጥቷል። ተከሳሽ የቀረበበትን ክስ ያመነ መሆኑን፣ የቤተሰብ አስተዳደር እንዲሁም ቀደም ስል የወንጀል ሪከርድ የሌለበት መሆኑን ግምት ውስጥ በማስገባት በ7 አመት ጽኑ እስራት እንድቀጣ ውሳኔ አሳልፎል።
የተሰረቀው ከአንድ ሚሊዮን በላይ ዋጋ የሚያወጣው ማይክሮስኮፕ ለኦቶና ሪፌራል ሆስፒታል ተመላሽ መደረጉን የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ኮሚኒኬሽን አስታውቋል።
Seledadotio
Seledadotio
ተከሳሽ እንድሪያስ ቶማስ ግያ በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪና ሪፈራል ሆስፒታል የጥበቃ ሠራተኛ ሆኖ እየሰራ ሀምሌ 22 ቀን 2018 ከምሽቱ 4:00 እስከ 6፡00 ባለዉ ጊዜ የወንጀል ድርጊቱ ተፈፅሟል።
የሆስፒታሉ ንብረት የሆነውን ሶስት ማይክሮስኮፕ የእያንዳንዳቸዉ ዋጋ ሶስት መቶ ሀምሳ ሺ ብር በድምሩ አንድ ሚሊዮን ሀምሳ ሺ ብር የሚያወጣዉን ከክፍሉ ሠራተኞች ጋር በመተባበር ንብረቱ ያለበትን ክፍል በቁልፍ ከፍቶ ከወሰደ እና ንብረቱን በተቋሙ ዉስጥ ባለዉ ሳርና ሀረግ ዉስጥ ደብቆ ካቆየ በኋላ ሀምሌ 25 ከሌሊቱ 9 ሰዓት ንብረቱን ካቆየበት ሥፍራ አንስቶ እየወሰደ እያለ ከንብረቱ ጋር የተያዘ ስለሆነ ተከሳሽ በፈፀመው ከባድ ስርቆት ወንጀል ተከሷል ።
የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ፍትህ መምሪያ ዐ/ሕግ ያቀረበውን ክስ ሲያከራክር የቆየው የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተከሳሽ የቀረበበትን ክስ ሙሉ በሙሉ ያመነ መሆኑን ግምት ውስጥ በማስገባት የጥፋተኝነት ውሳኔ ሰጥቷል። ተከሳሽ የቀረበበትን ክስ ያመነ መሆኑን፣ የቤተሰብ አስተዳደር እንዲሁም ቀደም ስል የወንጀል ሪከርድ የሌለበት መሆኑን ግምት ውስጥ በማስገባት በ7 አመት ጽኑ እስራት እንድቀጣ ውሳኔ አሳልፎል።
የተሰረቀው ከአንድ ሚሊዮን በላይ ዋጋ የሚያወጣው ማይክሮስኮፕ ለኦቶና ሪፌራል ሆስፒታል ተመላሽ መደረጉን የወላይታ ሶዶ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት ኮሚኒኬሽን አስታውቋል።
Seledadotio
Seledadotio
4 days ago
እኔ ውሸታም ወይም አታላይ አይደለሁም!
#ethiopia | የካምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ የሶሺዮሎጂ ትምህርት ክፍል መምህር የሆኑት ፕሮፌሰር ጄሰን አርደይ የሌሎች ምሁራን ጽሑፎች ያለ አግባብ ተጠቅመዋል በሚል ክስ ቀረበባቸው።
ክሱ በዋናነት የተነሳው በፈረንጆቹ 2015 ባዘጋጁት የመመረቂያ ጽሑፏቸው ላይ ሲሆን በዚህ ጽሁፋቸው የምሁራን ጥናቶች በቀጥታ ያለ ምንጭ ተጠቅመዋል የሚል ነው።
ፕሮፌሰሩም በፒኤችዲ ቴሲሳቸው እና ባሳተሟቸው አካዳሚያዊ ጥናቶች ላይ የቀረበባቸውን የጽሑፍ ስርቆት ክስ አስተባብለዋል።
ፕሮፌሰሩ በጥናቶቻቸው ላይ ጥቂት የአሰራር እና የቴክኒክ ስህተቶች መከሰታቸውን አምነው እኔ ግን ውሸታም ወይም አታላይ አይደለሁም ሲሉ ራሳቸውን ተከላክለዋል።
በቀደሙት ሥራዎቼ ላይ የቴክኒክና የምንጭ አጠቃቀም ስህተቶች መኖራቸውን እቀበላለሁ ለሰራኋቸው ስህተቶችም ኃላፊነቱን እወስዳለሁ ብለዋል።
ነገር ግን አካዳሚያዊ ማጭበርበር ወይም የፁሁፍ ስርቆት ፈፅመሀል የሚለው ውንጀላ ፍፁም ከእውነት የራቀና ተቀባይነት የሌለው ነው ሲሉ ተናግረዋል።
የካምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ በበኩሉ በሰጠው መግለጫ የቀረቡት አቤቱታዎች ላይ ጥልቅ ምርመራ መደረጉንና ፕሮፌሰሩ ምንም የፈፀሙት ስህተት የለም ብሏል።
ዩኒቨርሲቲው ውንጀላውን የፕሮፌሰሩን ስም ለማጠልሸት ሆን ተብሎ የተደረገ ነው ሲል ገልጾታል።
በተጨማሪም በርካታ ምሁራንና የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ለፕሮፌሰሩ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል።
ክሱ በጥቁር ምሁራን ስኬት ላይ ያተኮረ ፖለቲካዊና ርዕዮተ ዓለማዊ ጫና እንደሆነ ተናግረዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #england #cambridgeuniversity #professor
#ethiopia | የካምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ የሶሺዮሎጂ ትምህርት ክፍል መምህር የሆኑት ፕሮፌሰር ጄሰን አርደይ የሌሎች ምሁራን ጽሑፎች ያለ አግባብ ተጠቅመዋል በሚል ክስ ቀረበባቸው።
ክሱ በዋናነት የተነሳው በፈረንጆቹ 2015 ባዘጋጁት የመመረቂያ ጽሑፏቸው ላይ ሲሆን በዚህ ጽሁፋቸው የምሁራን ጥናቶች በቀጥታ ያለ ምንጭ ተጠቅመዋል የሚል ነው።
ፕሮፌሰሩም በፒኤችዲ ቴሲሳቸው እና ባሳተሟቸው አካዳሚያዊ ጥናቶች ላይ የቀረበባቸውን የጽሑፍ ስርቆት ክስ አስተባብለዋል።
ፕሮፌሰሩ በጥናቶቻቸው ላይ ጥቂት የአሰራር እና የቴክኒክ ስህተቶች መከሰታቸውን አምነው እኔ ግን ውሸታም ወይም አታላይ አይደለሁም ሲሉ ራሳቸውን ተከላክለዋል።
በቀደሙት ሥራዎቼ ላይ የቴክኒክና የምንጭ አጠቃቀም ስህተቶች መኖራቸውን እቀበላለሁ ለሰራኋቸው ስህተቶችም ኃላፊነቱን እወስዳለሁ ብለዋል።
ነገር ግን አካዳሚያዊ ማጭበርበር ወይም የፁሁፍ ስርቆት ፈፅመሀል የሚለው ውንጀላ ፍፁም ከእውነት የራቀና ተቀባይነት የሌለው ነው ሲሉ ተናግረዋል።
የካምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ በበኩሉ በሰጠው መግለጫ የቀረቡት አቤቱታዎች ላይ ጥልቅ ምርመራ መደረጉንና ፕሮፌሰሩ ምንም የፈፀሙት ስህተት የለም ብሏል።
ዩኒቨርሲቲው ውንጀላውን የፕሮፌሰሩን ስም ለማጠልሸት ሆን ተብሎ የተደረገ ነው ሲል ገልጾታል።
በተጨማሪም በርካታ ምሁራንና የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ለፕሮፌሰሩ ድጋፋቸውን ሰጥተዋል።
ክሱ በጥቁር ምሁራን ስኬት ላይ ያተኮረ ፖለቲካዊና ርዕዮተ ዓለማዊ ጫና እንደሆነ ተናግረዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #england #cambridgeuniversity #professor
4 days ago
በኦቶና ሆስፒታል የላብራቶሪ መሳሪያዎችን ሊሰርቅ የነበረ የጥበቃ ሰራተኛ እጅ ከፍንጂ ተያዘ
በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል (ኦቶና) ሦስት ወሳኝ የላብራቶሪ ማይክሮስኮፖችን አውጥቶ ለመሰወር ሲሞክር የነበረ የጥበቃ ሰራተኛ በተረኛ ጥበቃዎች ብርቱ ክትትልና ተጋድሎ እጅ ከፍንጂ መያዙ ተገለጸ።
በትላትናው እለተ የተፈጸመው ይህ ድርጊት ተራ የሕክምና ዕቃ ስርቆት ሳይሆን፣ የሺዎችን ሕይወት እና የሆስፒታሉን ዕለታዊ የሕክምና አገልግሎት ቀጥተኛ አደጋ ላይ የጣለ ከባድ ወንጀል መሆኑን ባለሙያዎች ይናገራሉ።
ተጠርጣሪው ግለሰብ የሕክምና መገልገያዎቹን ደብቆ ከሆስፒታሉ ግቢ ሊያወጣ ሲል በተረኛ ባልደረቦቹ ንቁ ክትትል በቁጥጥር ስር ውሏል። ድርጊቱ በግለሰቡ ብቻ የተፈጸመ ሳይሆን በጀርባ ያሉ አመቻቾችና አቀናባሪዎች እንዳሉበት በመጠረጠሩ፣ ወንጀሉን ያስተባበሩ አካላት በሙሉ ተለይተው ተገቢው የሕግ ትርጉም እንዲሰጣቸውና አስተማሪ ቅጣት እንዲያገኙ ጉዳዩ በትኩረት እየተከታተለ ይገኛል።
በአንድ አጠቃላይ ሆስፒታል ውስጥ ማይክሮስኮፕ ማለት የተደበቁ በሽታዎችን አውጥቶ በማሳየት የሕሙማንን ሕይወት የሚያስጥል ዋና መመርመሪያ መሳሪያ ነው።
እነዚህን መገልገያዎች ማጣት በሕሙማን ላይ የሚከተሉትን ከባድ የጤና አደጋዎች ያስከትላል፦
እንደ ወባ፣ ቲቢ እና የተለያዩ ከባድ የባክቴሪያ ኢንፌክሽኖችን በፍጥነት በመመርመር አስቸኳይ የሕክምና ውሳኔ ለመስጠት ያገለግላሉ።
የደም ማነስን (Anemia) እና የደም ካንሰርን (Leukemia) በጥንቃቄ ለይቶ ለማወቅ ወሳኝ መገልገያዎች ናቸው።
እነዚህ መሳሪያዎች ከአገልግሎት ውጭ ሲሆኑ የላብራቶሪ ውጤቶች ይዘገያሉ፤ ይህም በተለይ በፅኑ ሕሙማን፣ በሕፃናትና ነፍሰ ጡራት ሕይወት ላይ የቀጥታ አደጋ ይደቅናል።
የሕዝብና የመንግሥት ሀብት የሆኑትን የሕክምና መገልገያዎች ከስርቆትና ከእጅ አዙር ሴራ መጠበቅ የሁላችንም ኃላፊነት ነው።
በሆስፒታሉ ግቢ ውስጥ የታየው የተረኛ ጥበቃዎች ንቅናቄ የሚደነቅ ሲሆን፣ የወንጀሉ ተሳታፊዎች በሙሉ ለሕግ እንዲቀርቡ የጀመረው ክትትል ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
Via ጉርሻ page
በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል (ኦቶና) ሦስት ወሳኝ የላብራቶሪ ማይክሮስኮፖችን አውጥቶ ለመሰወር ሲሞክር የነበረ የጥበቃ ሰራተኛ በተረኛ ጥበቃዎች ብርቱ ክትትልና ተጋድሎ እጅ ከፍንጂ መያዙ ተገለጸ።
በትላትናው እለተ የተፈጸመው ይህ ድርጊት ተራ የሕክምና ዕቃ ስርቆት ሳይሆን፣ የሺዎችን ሕይወት እና የሆስፒታሉን ዕለታዊ የሕክምና አገልግሎት ቀጥተኛ አደጋ ላይ የጣለ ከባድ ወንጀል መሆኑን ባለሙያዎች ይናገራሉ።
ተጠርጣሪው ግለሰብ የሕክምና መገልገያዎቹን ደብቆ ከሆስፒታሉ ግቢ ሊያወጣ ሲል በተረኛ ባልደረቦቹ ንቁ ክትትል በቁጥጥር ስር ውሏል። ድርጊቱ በግለሰቡ ብቻ የተፈጸመ ሳይሆን በጀርባ ያሉ አመቻቾችና አቀናባሪዎች እንዳሉበት በመጠረጠሩ፣ ወንጀሉን ያስተባበሩ አካላት በሙሉ ተለይተው ተገቢው የሕግ ትርጉም እንዲሰጣቸውና አስተማሪ ቅጣት እንዲያገኙ ጉዳዩ በትኩረት እየተከታተለ ይገኛል።
በአንድ አጠቃላይ ሆስፒታል ውስጥ ማይክሮስኮፕ ማለት የተደበቁ በሽታዎችን አውጥቶ በማሳየት የሕሙማንን ሕይወት የሚያስጥል ዋና መመርመሪያ መሳሪያ ነው።
እነዚህን መገልገያዎች ማጣት በሕሙማን ላይ የሚከተሉትን ከባድ የጤና አደጋዎች ያስከትላል፦
እንደ ወባ፣ ቲቢ እና የተለያዩ ከባድ የባክቴሪያ ኢንፌክሽኖችን በፍጥነት በመመርመር አስቸኳይ የሕክምና ውሳኔ ለመስጠት ያገለግላሉ።
የደም ማነስን (Anemia) እና የደም ካንሰርን (Leukemia) በጥንቃቄ ለይቶ ለማወቅ ወሳኝ መገልገያዎች ናቸው።
እነዚህ መሳሪያዎች ከአገልግሎት ውጭ ሲሆኑ የላብራቶሪ ውጤቶች ይዘገያሉ፤ ይህም በተለይ በፅኑ ሕሙማን፣ በሕፃናትና ነፍሰ ጡራት ሕይወት ላይ የቀጥታ አደጋ ይደቅናል።
የሕዝብና የመንግሥት ሀብት የሆኑትን የሕክምና መገልገያዎች ከስርቆትና ከእጅ አዙር ሴራ መጠበቅ የሁላችንም ኃላፊነት ነው።
በሆስፒታሉ ግቢ ውስጥ የታየው የተረኛ ጥበቃዎች ንቅናቄ የሚደነቅ ሲሆን፣ የወንጀሉ ተሳታፊዎች በሙሉ ለሕግ እንዲቀርቡ የጀመረው ክትትል ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።
Via ጉርሻ page
17 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በሰሜን ቨርጂኒያ በሚገኙ የተለያዩ የስፖርት ማዕከላት (ጂሞች) አካባቢ በተሽከርካሪዎች ላይ ያነጣጠረ ተከታታይ ስርቆት ሲፈጽም ነበር የተባለ የ29 ዓመት ወጣት የአሌክሳንድሪያ ነዋሪ ወደ 200 የሚጠጉ ተደራራቢ የወንጀል ክሶች እንደተመሰረቱበት ተነገረ። ቁምነገር አያልሰው የተሰኘው ይህ ወጣት ለወራት የተደረገን ሰፊ የፖሊስ ክትትልና ምርመራ ተከትሎ ባለፈው ሰኔ 26 ቀን በቁጥጥር ሥር መዋሉን መርማሪዎች አስታውቀዋል።
ፖሊስ እንዳብራራው ተጠርጣሪው ቢያንስ ካለፈው ሚያዝያ 2026 ጀምሮ በፌርፋክስ ካውንቲ፣ በፎልስ ቸርች እና በአካባቢው በሚገኙ መኪና ማቆሚያዎች ላይ ሳይቆለፉ የተቀመጡ ተሽከርካሪዎችን በመለየት የኪስ ቦርሳዎችን፣ ጥሬ ገንዘቦችን፣ የባንክ ክሬዲት ካርዶችን እና ሌሎች የግል ንብረቶችን ሲሰርቅ ቆይቷል። ተጎጂዎች ንብረታቸው መጥፋቱን እንኳ ገና ሳያውቁ፣ ተጠርጣሪው የተሰረቁትን ካርዶች በመያዝ በፍጥነት በአቅራቢያው ከሚገኙ መደብሮች የክፍያ ስጦታ ካርዶችን (gift cards) በመግዛት ከፍተኛ የማጭበርበር ወንጀል መፈጸሙ በምርመራው ተረጋግጧል። በፌርፋክስ ካውንቲ ብቻ በሴንትሬቪል፣ በሬስተን እና በማክሊን አካባቢዎች በርካታ ተመሳሳይ የስርቆት ወንጀሎች መፈጸማቸው በፖሊስ መዝገብ ሰፍሯል።
ይህንን ተከትሎ በቁጥጥር ሥር በዋለበት ወቅት በፌርፋክስ ካውንቲ ብቻ 32 አዳዲስ ወንጀሎች የተጨመሩበት ሲሆን፣ በአጠቃላይ በተለያዩ አካባቢዎች የፈጸማቸው ተደራራቢ ወንጀሎች ክሳቸውን በአሁኑ ወቅት ወደ 200 አድርሶታል። ተጠርጣሪው ኩምነገር አያልሰው ሐምሌ 14 ቀን በፌርፋክስ ካውንቲ ለቀረቡበት ክሶች በገዛ ዋስትናው ከእስር እንዲለቀቅ የተደረገ ቢሆንም፣ በፎልስ ቸርች ፖሊስ መሥሪያ ቤት በቀረቡበት የተለዩ የወንጀል ክሶች ምክንያት በአሁኑ ወቅት በአርሊንግተን ካውንቲ እስር ቤት በጥበቃ ሥር እንደሚገኝ ታውቋል።
ይህንን መጠነ ሰፊ ስርቆት ተከትሎ የአካባቢው ፖሊስ ነዋሪዎች ንብረቶቻቸውን በጥንቃቄ እንዲጠብቁ አሳስቧል። የኪስ ቦርሳ፣ ስልክ እና የባንክ ካርዶችን መኪና ውስጥ በጭራሽ አለመተው፣ ለአጭር ጊዜ ስፖርት እንኳ ቢሆን መኪናን ሁልጊዜ መቆለፍ እና መስኮቶችን በሚገባ መዝጋት፣ እንዲሁም የግድ መኪና ውስጥ መቀመጥ ያለባቸው ዕቃዎች ካሉ መድረሻው ቦታ ከመደረሱ በፊት በስተጀርባ ዕቃ ማስቀመጫ (ትራንክ) ውስጥ ቀድሞ መደበቅ እንደሚገባ ፖሊስ ምክሩን ለግሷል።
ፖሊስ እንዳብራራው ተጠርጣሪው ቢያንስ ካለፈው ሚያዝያ 2026 ጀምሮ በፌርፋክስ ካውንቲ፣ በፎልስ ቸርች እና በአካባቢው በሚገኙ መኪና ማቆሚያዎች ላይ ሳይቆለፉ የተቀመጡ ተሽከርካሪዎችን በመለየት የኪስ ቦርሳዎችን፣ ጥሬ ገንዘቦችን፣ የባንክ ክሬዲት ካርዶችን እና ሌሎች የግል ንብረቶችን ሲሰርቅ ቆይቷል። ተጎጂዎች ንብረታቸው መጥፋቱን እንኳ ገና ሳያውቁ፣ ተጠርጣሪው የተሰረቁትን ካርዶች በመያዝ በፍጥነት በአቅራቢያው ከሚገኙ መደብሮች የክፍያ ስጦታ ካርዶችን (gift cards) በመግዛት ከፍተኛ የማጭበርበር ወንጀል መፈጸሙ በምርመራው ተረጋግጧል። በፌርፋክስ ካውንቲ ብቻ በሴንትሬቪል፣ በሬስተን እና በማክሊን አካባቢዎች በርካታ ተመሳሳይ የስርቆት ወንጀሎች መፈጸማቸው በፖሊስ መዝገብ ሰፍሯል።
ይህንን ተከትሎ በቁጥጥር ሥር በዋለበት ወቅት በፌርፋክስ ካውንቲ ብቻ 32 አዳዲስ ወንጀሎች የተጨመሩበት ሲሆን፣ በአጠቃላይ በተለያዩ አካባቢዎች የፈጸማቸው ተደራራቢ ወንጀሎች ክሳቸውን በአሁኑ ወቅት ወደ 200 አድርሶታል። ተጠርጣሪው ኩምነገር አያልሰው ሐምሌ 14 ቀን በፌርፋክስ ካውንቲ ለቀረቡበት ክሶች በገዛ ዋስትናው ከእስር እንዲለቀቅ የተደረገ ቢሆንም፣ በፎልስ ቸርች ፖሊስ መሥሪያ ቤት በቀረቡበት የተለዩ የወንጀል ክሶች ምክንያት በአሁኑ ወቅት በአርሊንግተን ካውንቲ እስር ቤት በጥበቃ ሥር እንደሚገኝ ታውቋል።
ይህንን መጠነ ሰፊ ስርቆት ተከትሎ የአካባቢው ፖሊስ ነዋሪዎች ንብረቶቻቸውን በጥንቃቄ እንዲጠብቁ አሳስቧል። የኪስ ቦርሳ፣ ስልክ እና የባንክ ካርዶችን መኪና ውስጥ በጭራሽ አለመተው፣ ለአጭር ጊዜ ስፖርት እንኳ ቢሆን መኪናን ሁልጊዜ መቆለፍ እና መስኮቶችን በሚገባ መዝጋት፣ እንዲሁም የግድ መኪና ውስጥ መቀመጥ ያለባቸው ዕቃዎች ካሉ መድረሻው ቦታ ከመደረሱ በፊት በስተጀርባ ዕቃ ማስቀመጫ (ትራንክ) ውስጥ ቀድሞ መደበቅ እንደሚገባ ፖሊስ ምክሩን ለግሷል።
Sponsored by
Surafel
18 days ago
ትራንስፎርመር ሲሰርቅ የነበረ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ
በባህር ዳር ሪጅን በአዊ ዞን እንጅባራ አገልግሎት መስጫ ማዕከል ስር በሚገኘው እንጅባራ ከተማ 02 ቀበሌ ልዩ ቦታው "ዘር ማበጠሪያ ሰፈር" በተባለ አካባቢ፣ ለማህበረሰቡ አገልግሎት የሚሰጥ ባለ 200 ኪ.ቮ.አ) ትራንስፎርመር በመዝረፍ ላይ የነበረ ግለሰብ እጅ ከፍንጅ ተያዘ።
ድርጊቱ የተፈጸመው ትናንት ሐምሌ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ከሌሊቱ 7፡00 ሰዓት ላይ አካባቢውን ሆን ብሎ ከኤሌክትሪክ ኃይል ውጭ በማድረግ መሆኑ ታውቋል።
ይህ የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማት ስርቆት ሲፈፅም የተገኘ ግለሰብ የተያዘው በአካባቢው ማህበረሰብና በጸጥታ ሃይሉ በተደረገ የተቀናጀና ንቁ ክትትል ሲሆን፣ ተጠርጣሪው ግለሰብ የፈታቸውን የትራንስፎርመር ማቴሪያል ጨምሮ በአካባቢው ፖሊስ ጣቢያ በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተደረገበት ይገኛል።
በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬና በህዝብ ሃብት የሚገነቡ የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማቶች ላይ የሚፈጸሙ መሰል ስርቆቶች ለሃይል መቆራረጥ ዋነኛ መንስኤ እየሆኑ ነው። ድርጊቱ በሃገር፣ በተቋምና በማህበረሰብ ላይ እያደረሰ ያለው ዘርፈ-ብዙ ጉዳት ከቀን ወደ ቀን እየከፋ መምጣቱም ተገልጿል።
በመሆኑም በኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማቶች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን መከላከልና መጠበቅ የሁሉም ዜጋ ሃላፊነት በመሆኑ፣ በየደረጃው የሚገኘው የህብረተሰብ ክፍል እነዚህን ውድ የልማት አውታሮች እንደ ራሱ ንብረት አድርጎ በንቃት ሊጠብቃቸውና ሊከላከልላቸው እንደሚገባ ተቋሙ ጥሪ ያቀርባል።
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
በባህር ዳር ሪጅን በአዊ ዞን እንጅባራ አገልግሎት መስጫ ማዕከል ስር በሚገኘው እንጅባራ ከተማ 02 ቀበሌ ልዩ ቦታው "ዘር ማበጠሪያ ሰፈር" በተባለ አካባቢ፣ ለማህበረሰቡ አገልግሎት የሚሰጥ ባለ 200 ኪ.ቮ.አ) ትራንስፎርመር በመዝረፍ ላይ የነበረ ግለሰብ እጅ ከፍንጅ ተያዘ።
ድርጊቱ የተፈጸመው ትናንት ሐምሌ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ከሌሊቱ 7፡00 ሰዓት ላይ አካባቢውን ሆን ብሎ ከኤሌክትሪክ ኃይል ውጭ በማድረግ መሆኑ ታውቋል።
ይህ የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማት ስርቆት ሲፈፅም የተገኘ ግለሰብ የተያዘው በአካባቢው ማህበረሰብና በጸጥታ ሃይሉ በተደረገ የተቀናጀና ንቁ ክትትል ሲሆን፣ ተጠርጣሪው ግለሰብ የፈታቸውን የትራንስፎርመር ማቴሪያል ጨምሮ በአካባቢው ፖሊስ ጣቢያ በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተደረገበት ይገኛል።
በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬና በህዝብ ሃብት የሚገነቡ የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማቶች ላይ የሚፈጸሙ መሰል ስርቆቶች ለሃይል መቆራረጥ ዋነኛ መንስኤ እየሆኑ ነው። ድርጊቱ በሃገር፣ በተቋምና በማህበረሰብ ላይ እያደረሰ ያለው ዘርፈ-ብዙ ጉዳት ከቀን ወደ ቀን እየከፋ መምጣቱም ተገልጿል።
በመሆኑም በኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማቶች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን መከላከልና መጠበቅ የሁሉም ዜጋ ሃላፊነት በመሆኑ፣ በየደረጃው የሚገኘው የህብረተሰብ ክፍል እነዚህን ውድ የልማት አውታሮች እንደ ራሱ ንብረት አድርጎ በንቃት ሊጠብቃቸውና ሊከላከልላቸው እንደሚገባ ተቋሙ ጥሪ ያቀርባል።
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
21 days ago
ሴት መስሎ በመቅረብ ስርቆት ለመፈጸም ሲንቀሳቀስ የነበረ ግለሰብ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋለ።
10/11/2018ዓ/ም | በሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ሴት መስሎ በመቅረብ ህብረተሰቡን ለመሸወድ እና የተለያየ ስርቆት ለመፈጸም ሲንቀሳቀስ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተደረገበት እንደሚገኝ የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ ጽ/ቤት አስታወቀ።
ግለሰቡ በቁጥጥር ስር ሊውል የቻለው በሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር በሜጦማ ቀበሌ ልዩ ስሙ መምህራን መንደር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ መሆኑ ታውቋል።
አቡሽ የተባለውና የትውልድ ስፍራው በምዕራብ ባደዋቾ ቆቶ ቀበሌ የሆነው ይህ ግለሰብ ወንድነቱን በመደበቅ ራሱን ሙሉ በሙሉ ወደ ሴትነት በመለወጥ ህዝብን ሲያታልል እንደነበር ተገልጿል።
ግለሰቡ የወንጀል ዓላማውን ለማሳካት የሴት ቀሚስ ፣ ሰው ሰራሽ ፀጉር (ዊግ) እና የሴት ጡት መያዣ በመጠቀም ራሱን በመለወጥ ስርቆት ለመፈጸም ሲንቀሳቀስ ነበር።
የሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አዛዥ ም/ኢ/ር አድማሱ ሱሎሮ እንደገለጹት ግለሰቡ በተደረገበት የህዝብ ጥቆማ በቁጥጥር ስር ሊውል የቻለ ሲሆን በአሁኑ ወቅትም በጸጥታ ኃይሎች ተይዞ ጥልቀት ያለው ምርመራ እየተደረገበት ይገኛል።
Via፦ ሺንሽቾ መንግስት ኮሙኒኬሽን
Seledadotio
Seledadotio
10/11/2018ዓ/ም | በሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ሴት መስሎ በመቅረብ ህብረተሰቡን ለመሸወድ እና የተለያየ ስርቆት ለመፈጸም ሲንቀሳቀስ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተደረገበት እንደሚገኝ የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ ጽ/ቤት አስታወቀ።
ግለሰቡ በቁጥጥር ስር ሊውል የቻለው በሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር በሜጦማ ቀበሌ ልዩ ስሙ መምህራን መንደር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ መሆኑ ታውቋል።
አቡሽ የተባለውና የትውልድ ስፍራው በምዕራብ ባደዋቾ ቆቶ ቀበሌ የሆነው ይህ ግለሰብ ወንድነቱን በመደበቅ ራሱን ሙሉ በሙሉ ወደ ሴትነት በመለወጥ ህዝብን ሲያታልል እንደነበር ተገልጿል።
ግለሰቡ የወንጀል ዓላማውን ለማሳካት የሴት ቀሚስ ፣ ሰው ሰራሽ ፀጉር (ዊግ) እና የሴት ጡት መያዣ በመጠቀም ራሱን በመለወጥ ስርቆት ለመፈጸም ሲንቀሳቀስ ነበር።
የሺንሽቾ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አዛዥ ም/ኢ/ር አድማሱ ሱሎሮ እንደገለጹት ግለሰቡ በተደረገበት የህዝብ ጥቆማ በቁጥጥር ስር ሊውል የቻለ ሲሆን በአሁኑ ወቅትም በጸጥታ ኃይሎች ተይዞ ጥልቀት ያለው ምርመራ እየተደረገበት ይገኛል።
Via፦ ሺንሽቾ መንግስት ኮሙኒኬሽን
Seledadotio
Seledadotio
23 days ago
⚠️ የጥንቃቄ መልእክት!
በወዳጅ ስም የተላከ የስርቆት መልእክት ሳያረጋግጡ በፍፁም ገንዘብ አይላኩ!
➡️ የማጭበርበር ድርጊቶች ሲያጋጥሙ ጥቆማዎን ወደ 9090 በአጭር የጽሑፍ መልእክት ይላኩልን።
#cybersecurity #ethiotelecom #telebirr #telebirrsuperapp #digitalafrica #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
በወዳጅ ስም የተላከ የስርቆት መልእክት ሳያረጋግጡ በፍፁም ገንዘብ አይላኩ!
➡️ የማጭበርበር ድርጊቶች ሲያጋጥሙ ጥቆማዎን ወደ 9090 በአጭር የጽሑፍ መልእክት ይላኩልን።
#cybersecurity #ethiotelecom #telebirr #telebirrsuperapp #digitalafrica #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
25 days ago
በመዲናዋ አዲስ አበባ በተለይም በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ፣ ሰሚት፣ ገርጂ እና አካባቢው ከመቼውም ጊዜ በላይ የተበራከተው የማጅራት መምታት እና የንጥቂያ ወንጀል የነዋሪውን ደህንነት ክፉኛ እየፈተነ ይገኛል። የወንጀሉ ገጽታ እና የጸጥታ አካላት እየወሰዱት ያለው እርምጃ ነዋሪዎችን እና የፖሊስ ኃላፊዎችን እያወዛገበ ሲሆን፣ የህዝቡን ስጋት እና የፖሊስን ምላሽ እንደሚከተለው አጠናቅረነዋል።
እንደ ነዋሪዎች እና ስማቸው እንዳይጠቀስ ከፈለጉ የውስጥ ፖሊስ አባላት ዘ-ሐበሻ ባገኘው መረጃ፣ የዘረፋው ወንጀል መልኩን ቀይሮ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል። ለወትሮው በምሽት ይፈጸም የነበረው ማጅራት መምታት፣ አሁን የክረምቱን መግባት እና የጠዋቱን ጨለማ እንደ ሽፋን በመጠቀም ወደ ማለዳ ተሸጋግሯል።
የዚህ አዲስ የማለዳ ላይ ጥቃት ዋነኛ ሰለባ እየሆኑ ያሉት ደግሞ፣ ጠዋት በጊዜ ወደ ቤተክርስቲያን የሚያመሩ አረጋውያን እናቶች ናቸው። ይህ በየዕለቱ እየተፈጸመ ያለ አስነዋሪ ድርጊት ቢሆንም፣ የፖሊስ የበላይ ኃላፊዎች ችግሩን ለመፍታት ከማሰብ ይልቅ ጉዳዩን አድበስብሶ ማለፍን መርጠዋል የሚል ጠንካራ ወቀሳ ከውስጥ ምንጮች ቀርቧል። "የህዝቡ ስቃይ ዝም ተብሎ ስለታለፈ እና ኃላፊዎች እርምጃ ባለመውሰዳቸው መረጃውን ለሚዲያ አድርሰናል" ያሉት የውስጥ ምንጮች፣ ተቋማዊ ቸልተኝነት መኖሩን በጽኑ ተችተዋል።
በተነሳው የ"ቸልተኝነት እና የዝምታ" ክስ ላይ ምላሽ የሰጡን የፖሊስ ኃላፊዎች፣ ተቋሙ በምንም መልኩ ዝምታን እንዳልመረጠ አስታውቀዋል። ኃላፊው ለቀረበባቸው ወቀሳ በሰጡት ምላሽ፣ ፖሊስ ወንጀለኞች በስፋት ይንቀሳቀሱባቸዋል የተባሉትን ሰሚት፣ ገርጂ እና 'ጥላሁን' የተባሉ አካባቢዎችን ለይቶ ሰፊ የጸጥታ ማስከበር አሰሳ እያካሄደ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም ወንጀለኞች የሚሰባሰቡባቸውን ህገ-ወጥ የሺሻ ቤቶችን የማፍረስ ስራ እየተሰራ ሲሆን፣ በአንድ ቀን በተደረገ ኦፕሬሽን ብቻ 80 ያህል የተሰረቁ የሞባይል ስልኮችን ማስመለስ መቻሉን ፖሊስ በምላሹ አስረድቷል። ከቀን 12 ሰዓት እስከ ሌሊቱ 1 ሰዓት ድረስ የዘለቀ ጥብቅ አሰሳ በየቀኑ እየተካሄደ መሆኑንም አክለዋል።
ከዚህ ቀደም የነበሩ አመራሮች የጸጥታ ስራዎችን ለሚዲያ ፍጆታ ይጠቀሙበት እንደነበር የወቀሱት ኃላፊው፣ "አሁን ያለው የጸጥታ መዋቅር ማወናበድ ሳይሆን በተጨባጭ ወንጀልን ከስረ-መሰረቱ ለማጥፋት ትልቅ ኦፕሬሽን እየሰራ ስለሆነ ነው እንጂ የተኛንበት ጊዜ የለም" ሲሉ ተከራክረዋል።
በፖሊስ ኃላፊው ምላሽ ውስጥ ጎልቶ የወጣው ሌላው አሳሳቢ ጉዳይ በነዚህ አካባቢዎች ያለው የውጭ ዜጎች ወንጀል ተሳትፎ ነው። ከዩጋንዳ፣ ናይጄሪያ እና ሌሎችም ሀገራት የመጡ፣ እንዲሁም ህጋዊ የጉዞ ሰነድ የሌላቸው በርካታ ስደተኞች በአካባቢው ተሰባስበው ይገኛሉ። እነዚህ የውጭ ዜጎች በስርቆት፣ በዝሙት አዳሪነት እና በተለያዩ ወንጀሎች ላይ ተሰማርተው መገኘታቸውንና ፖሊስም ህጋዊ እርምጃ እየወሰደባቸው መሆኑ ተጠቁሟል።
የህዝቡን የዕለት ተዕለት ስቃይ እና የፖሊስን ሪፖርት ጎን ለጎን ስንመዝነው፣ አንድ ትልቅ የአሰራር እና የትኩረት ክፍተት ይታያል። በአንድ በኩል ህዝቡ እና አረጋውያን እናቶች ጥቃት እየደረሰባቸው ያለው በማለዳው (ጠዋት) የጨለማ ሰዓት መሆኑን እያማረሩ ነው። በሌላ በኩል ግን ፖሊስ ትልቅ እርምጃ እየወሰድኩ ነው ብሎ ያቀረበው ማስረጃ "ከቀን 12 ሰዓት እስከ ሌሊቱ 1 ሰዓት" የሚያደርገውን አሰሳ ነው። ይህ የሚያሳየው ወንጀለኞቹ የፖሊስን የጥበቃ ሰዓት ክፍተት አጥንተው የዘረፋ ሰዓታቸውን ወደ ጠዋት ማለዳ ሲያሸጋግሩ፣ ፖሊስ ግን አሁንም ትኩረቱን ምሽት ላይ ብቻ ማድረጉን ነው።
ፖሊስ "ለሚዲያ ፍጆታ ሳይሆን በተግባር እየሰራሁ ነው" ማለቱ የሚበረታታ ቢሆንም ስኬቱ ሊለካ የሚገባው በተያዙ ስልኮች ብዛት ብቻ ሳይሆን በማለዳ ወደ ቤተክርስቲያን እና ወደ ስራ የሚወጣው ነዋሪ በሚያገኘው የደህንነት ዋስትና ነው። በመሆኑም የጸጥታ አካላት የኦፕሬሽን ስልታቸውን እና የሰዓት ስምሪታቸውን ነዋሪው እየተጠቃበት ካለው የማለዳ ሰዓት ጋር ሊያስተካክሉ ይገባል። ፖሊስ አደረግኩት የሚለው ኦፕሬሽን በተግባር የህዝቡን ስጋት እስካላቀለለ ድረስ፣ "ቸልተኝነት አለ" የሚለው የህዝብ ቅሬታ መቀጠሉ አይቀርም።
እንደ ነዋሪዎች እና ስማቸው እንዳይጠቀስ ከፈለጉ የውስጥ ፖሊስ አባላት ዘ-ሐበሻ ባገኘው መረጃ፣ የዘረፋው ወንጀል መልኩን ቀይሮ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል። ለወትሮው በምሽት ይፈጸም የነበረው ማጅራት መምታት፣ አሁን የክረምቱን መግባት እና የጠዋቱን ጨለማ እንደ ሽፋን በመጠቀም ወደ ማለዳ ተሸጋግሯል።
የዚህ አዲስ የማለዳ ላይ ጥቃት ዋነኛ ሰለባ እየሆኑ ያሉት ደግሞ፣ ጠዋት በጊዜ ወደ ቤተክርስቲያን የሚያመሩ አረጋውያን እናቶች ናቸው። ይህ በየዕለቱ እየተፈጸመ ያለ አስነዋሪ ድርጊት ቢሆንም፣ የፖሊስ የበላይ ኃላፊዎች ችግሩን ለመፍታት ከማሰብ ይልቅ ጉዳዩን አድበስብሶ ማለፍን መርጠዋል የሚል ጠንካራ ወቀሳ ከውስጥ ምንጮች ቀርቧል። "የህዝቡ ስቃይ ዝም ተብሎ ስለታለፈ እና ኃላፊዎች እርምጃ ባለመውሰዳቸው መረጃውን ለሚዲያ አድርሰናል" ያሉት የውስጥ ምንጮች፣ ተቋማዊ ቸልተኝነት መኖሩን በጽኑ ተችተዋል።
በተነሳው የ"ቸልተኝነት እና የዝምታ" ክስ ላይ ምላሽ የሰጡን የፖሊስ ኃላፊዎች፣ ተቋሙ በምንም መልኩ ዝምታን እንዳልመረጠ አስታውቀዋል። ኃላፊው ለቀረበባቸው ወቀሳ በሰጡት ምላሽ፣ ፖሊስ ወንጀለኞች በስፋት ይንቀሳቀሱባቸዋል የተባሉትን ሰሚት፣ ገርጂ እና 'ጥላሁን' የተባሉ አካባቢዎችን ለይቶ ሰፊ የጸጥታ ማስከበር አሰሳ እያካሄደ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም ወንጀለኞች የሚሰባሰቡባቸውን ህገ-ወጥ የሺሻ ቤቶችን የማፍረስ ስራ እየተሰራ ሲሆን፣ በአንድ ቀን በተደረገ ኦፕሬሽን ብቻ 80 ያህል የተሰረቁ የሞባይል ስልኮችን ማስመለስ መቻሉን ፖሊስ በምላሹ አስረድቷል። ከቀን 12 ሰዓት እስከ ሌሊቱ 1 ሰዓት ድረስ የዘለቀ ጥብቅ አሰሳ በየቀኑ እየተካሄደ መሆኑንም አክለዋል።
ከዚህ ቀደም የነበሩ አመራሮች የጸጥታ ስራዎችን ለሚዲያ ፍጆታ ይጠቀሙበት እንደነበር የወቀሱት ኃላፊው፣ "አሁን ያለው የጸጥታ መዋቅር ማወናበድ ሳይሆን በተጨባጭ ወንጀልን ከስረ-መሰረቱ ለማጥፋት ትልቅ ኦፕሬሽን እየሰራ ስለሆነ ነው እንጂ የተኛንበት ጊዜ የለም" ሲሉ ተከራክረዋል።
በፖሊስ ኃላፊው ምላሽ ውስጥ ጎልቶ የወጣው ሌላው አሳሳቢ ጉዳይ በነዚህ አካባቢዎች ያለው የውጭ ዜጎች ወንጀል ተሳትፎ ነው። ከዩጋንዳ፣ ናይጄሪያ እና ሌሎችም ሀገራት የመጡ፣ እንዲሁም ህጋዊ የጉዞ ሰነድ የሌላቸው በርካታ ስደተኞች በአካባቢው ተሰባስበው ይገኛሉ። እነዚህ የውጭ ዜጎች በስርቆት፣ በዝሙት አዳሪነት እና በተለያዩ ወንጀሎች ላይ ተሰማርተው መገኘታቸውንና ፖሊስም ህጋዊ እርምጃ እየወሰደባቸው መሆኑ ተጠቁሟል።
የህዝቡን የዕለት ተዕለት ስቃይ እና የፖሊስን ሪፖርት ጎን ለጎን ስንመዝነው፣ አንድ ትልቅ የአሰራር እና የትኩረት ክፍተት ይታያል። በአንድ በኩል ህዝቡ እና አረጋውያን እናቶች ጥቃት እየደረሰባቸው ያለው በማለዳው (ጠዋት) የጨለማ ሰዓት መሆኑን እያማረሩ ነው። በሌላ በኩል ግን ፖሊስ ትልቅ እርምጃ እየወሰድኩ ነው ብሎ ያቀረበው ማስረጃ "ከቀን 12 ሰዓት እስከ ሌሊቱ 1 ሰዓት" የሚያደርገውን አሰሳ ነው። ይህ የሚያሳየው ወንጀለኞቹ የፖሊስን የጥበቃ ሰዓት ክፍተት አጥንተው የዘረፋ ሰዓታቸውን ወደ ጠዋት ማለዳ ሲያሸጋግሩ፣ ፖሊስ ግን አሁንም ትኩረቱን ምሽት ላይ ብቻ ማድረጉን ነው።
ፖሊስ "ለሚዲያ ፍጆታ ሳይሆን በተግባር እየሰራሁ ነው" ማለቱ የሚበረታታ ቢሆንም ስኬቱ ሊለካ የሚገባው በተያዙ ስልኮች ብዛት ብቻ ሳይሆን በማለዳ ወደ ቤተክርስቲያን እና ወደ ስራ የሚወጣው ነዋሪ በሚያገኘው የደህንነት ዋስትና ነው። በመሆኑም የጸጥታ አካላት የኦፕሬሽን ስልታቸውን እና የሰዓት ስምሪታቸውን ነዋሪው እየተጠቃበት ካለው የማለዳ ሰዓት ጋር ሊያስተካክሉ ይገባል። ፖሊስ አደረግኩት የሚለው ኦፕሬሽን በተግባር የህዝቡን ስጋት እስካላቀለለ ድረስ፣ "ቸልተኝነት አለ" የሚለው የህዝብ ቅሬታ መቀጠሉ አይቀርም።
26 days ago
የሀይል ስርቆትን በተመለከተ ጥቆማ ለሚሰጥ ከተጣለው ቅጣት የ25 በመቶ ኮሚሽን እንደሚያገኝ ተገለፀ
ሀምሌ 5 ቀን 2018 ዓ.ም. (አሐዱ ሬዲዮ)፦ በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የሚፈጸሙ የኤሌክትሪክ ሀይል ስርቆትን ለመግታት እና በመሰረተ ልማት ላይ የሚደርሱ ጉዳቶችን ለመከላከል የተቀናጀ የቁጥጥር ስራ እየተከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል ።
በአገልግሎቱ የሽያጭና የደንበኞች አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ይሔይስ ስዩም
የሀይል ስርቆቱ በዋናነት የኤሌክትሪክ ቆጣሪዎች በትክክል እንዳይቆጥሩ በማድረግ ወይም መስመር ወደ ቆጣሪው ከመግባቱ በፊት በቀጥታ በመጥለፍ ወደ መኖሪያ ቤቶችና የኢንዱስትሪ ማሽኖች በመውሰድ እንደሚፈጸም ተናግረዋል ።
በ2017 በጀት ዓመት በተደረገው ከፍተኛ ክትትልና የቁጥጥር ስራ፣ የሃይል ስርቆት ጨምሮ ከባከነ ሃይል 259 ሚሊዮን ብር መሰብሰብ መቻሉንም ተናግረዋል።
የኤሌክትሪክ ሃይል ስርቆትን በዘላቂነት ለመከላከል ህብረተሰቡ ጥቆማ እንዲሰጥ የተደራጀ የአሰራር ስርዓት፣ ፖሊሲና መመሪያ ተቀርጾ ወደ ስራ መገባቱን ጠቁመዋል ።
በዚህም መሰረት የሃይል ስርቆት ለሚጠቁሙ ደንበኞች ከተጣለው ቅጣት ላይ የ25 በመቶ ኮሚሽን ክፍያ ተግባራዊ መደረግ መጀመሩ አስረድተዋል ።
ለአብነትም አንድ ከፍተኛ ኢንዱስትሪ በፈጸመው የቴክኒክ ስርቆት ምክንያት አንድ ሚሊዮን ብር ቢቀጣ፣ ጥቆማውን ያቀረበው ግለሰብ የ250 ሺህ ብር የገንዘብ ማበረታቻ በህጋዊ አሰራር ያገኛል።
የኤሌክትሪክ ኔትወርክ መሰረተ ልማት የጋራ ሀብት በመሆኑ ፣ የሃይል ስርቆት የሚፈጽሙ አካላትን በማጋለጥ ረገድ ህብረተሰቡ የበኩሉን ጥቆማ በመስጠት እንዲተባበር ጥሪ ቀርቧል።
Seledadotio
Seledadotio
ሀምሌ 5 ቀን 2018 ዓ.ም. (አሐዱ ሬዲዮ)፦ በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የሚፈጸሙ የኤሌክትሪክ ሀይል ስርቆትን ለመግታት እና በመሰረተ ልማት ላይ የሚደርሱ ጉዳቶችን ለመከላከል የተቀናጀ የቁጥጥር ስራ እየተከናወነ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል ።
በአገልግሎቱ የሽያጭና የደንበኞች አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ይሔይስ ስዩም
የሀይል ስርቆቱ በዋናነት የኤሌክትሪክ ቆጣሪዎች በትክክል እንዳይቆጥሩ በማድረግ ወይም መስመር ወደ ቆጣሪው ከመግባቱ በፊት በቀጥታ በመጥለፍ ወደ መኖሪያ ቤቶችና የኢንዱስትሪ ማሽኖች በመውሰድ እንደሚፈጸም ተናግረዋል ።
በ2017 በጀት ዓመት በተደረገው ከፍተኛ ክትትልና የቁጥጥር ስራ፣ የሃይል ስርቆት ጨምሮ ከባከነ ሃይል 259 ሚሊዮን ብር መሰብሰብ መቻሉንም ተናግረዋል።
የኤሌክትሪክ ሃይል ስርቆትን በዘላቂነት ለመከላከል ህብረተሰቡ ጥቆማ እንዲሰጥ የተደራጀ የአሰራር ስርዓት፣ ፖሊሲና መመሪያ ተቀርጾ ወደ ስራ መገባቱን ጠቁመዋል ።
በዚህም መሰረት የሃይል ስርቆት ለሚጠቁሙ ደንበኞች ከተጣለው ቅጣት ላይ የ25 በመቶ ኮሚሽን ክፍያ ተግባራዊ መደረግ መጀመሩ አስረድተዋል ።
ለአብነትም አንድ ከፍተኛ ኢንዱስትሪ በፈጸመው የቴክኒክ ስርቆት ምክንያት አንድ ሚሊዮን ብር ቢቀጣ፣ ጥቆማውን ያቀረበው ግለሰብ የ250 ሺህ ብር የገንዘብ ማበረታቻ በህጋዊ አሰራር ያገኛል።
የኤሌክትሪክ ኔትወርክ መሰረተ ልማት የጋራ ሀብት በመሆኑ ፣ የሃይል ስርቆት የሚፈጽሙ አካላትን በማጋለጥ ረገድ ህብረተሰቡ የበኩሉን ጥቆማ በመስጠት እንዲተባበር ጥሪ ቀርቧል።
Seledadotio
Seledadotio
28 days ago
ባንኩ እያጋጠመው ካለው ብልሹ አሰራርና ስርቆት ለመታደግ ከአንበሳ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ለመንግስት የህግ አስከባሪ አካላት የሚሰጥ ጥቆማ
አንበሳ ኢንተርናሽናል ባነክ አ.ማ በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ሪፐብሊክ የባንኮች መቋቋሚያ አወጅ ቁጥር 592/2000 በተከፈለ ካፒታል ብር 108.2 ቢሊየን በባለአክሲዮኖች ብዛት 3,739 ተቋቁሞ እ.ኤ.አ ጥር 6 2007 ጀምሮ በስራ ላይ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ በዚህም በተመሰረተበት የስራዘርፍ ለባለ አክሲዮኖች የትርፍ ክፍፍል በመስጠት፣ ካገኘው ትርፍ ለመንግስት ተገቢውን ግብር በመክፈል፣ በአገሪቱ ላይም የስራ አጥነት በመቀነስ እና ሌሎች ማህበራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ እንደነበረ ይታወቃል፡፡ ነገር ግን ይህ እንዳለ ሆኖ በተለያዩ ጊዜያት የተከሰቱ ያሉ አንዳንድ ብልሹ አሰራሮች በተጨባጭ እየታዩ እንደሆኑ ከሚቀርበው አመታዊ ሪፖርት እና የተለያዩ መረጃዎች መረዳት ችለናል፡፡ ድርጊቱን የሚፈፅሙት የባንኩ የበላይ የስራ ኃላፊዎችም ይሁኑ በበላይነት ባንኩን የሚመሩት ቦርዶችም ለተፈጠሩት ብልሹ አሰራሮች ተገቢውን ትኩተት በመስጠት በኃላፊነት እና በተጠያቂነት መንፈስ ከመከታተል ይልቅ ነገሮችን የማድበስበስ አዝማሚያ ነው እየታዩ ያሉት ብሎም አንዳንድ የስራ ኃላፊዎችም አገር ለቀው ሄደዋል አንዳንዶች ደሞ ሚስጢር አፍኖ ለማስቀረት የገቡት ቃልኪዳን እንዳለ በሚመስል መልኩ ጥፋቶችን በመሸፋፈን ተጨማሪ የጥፋት ድርጊታቸውን በማስቀጠል ላይ ተጠምደው ይገኛሉ፡፡ እነዚህ ከታች የተዘረዘሩት ብልሹ አሰራሮች በሚመለከታቸው ተቆጣጣሪ አካል ብሔራዊ ባንክ ይሁን ሌላ የመንግስት አስከባሪ አካል ተገቢውን ትኩረት ተሰጥቶት ምርመራ በማካሄድ አፋጣኝ እርምጃ ካልወሰደ የአገሪቱን ህግና ስርአት በመተማመን መዋእለ ነዋዩን ያፈሰሰ ባለአክሲዮን፣ ለመንግስት ለሚከፈለው የትርፍ ግብር፣ በሰራተኞች ላይ በሚያደርሰው የሞራል ጉዳት እንዲሁም እንዳጠቃላይ በአገሪቱ ጤናማ ያልሆነ የኢኮኖሚ ችግር ስርአት አልባነት ያስከትላል ብለን እናምናለን፡፡
ዋና ዋና ጥቆማዎች
1. በተለያዩ ጊዜያት ባንኩ ለአስመጪዎች የፈቀደላቸው የውጭ ምንዛሪ ተመጣጣኝ የሆነ ንብረት ወደ አገር ባለመግባቱ ምክንያት ባንኩ ከUSD 1,800,000.00፣ ከUSD 220,000.00, እና በላይ በተሰብሳቢነት ያለ ስንቅ /provision/ ከ8 ዓመት በላይ ተይዞ ይገኛል፡፡ በዚህ ምክንያት ለግለሰቦች የግል ጥቅም ሲባል የብዙሀኑ ባለአክስዮኖች እና መንግስት በግብር መልክ ሊያገኘው የሚገባው ጥቅም ወደጎን በመተው የብሔራዊ ባንክ መመሪያ FXD/07/1998 በግልፅ ተጥሰዋል፡፡
2. ለላኪዎች ፍቃድ በመስጠት ግምታቸው USD 1,100,000.00 በላይ የሚገመት ንብረት ከአገራችን ወደ ውጭ ሀገር የተላከ ሲሆን የሚጠበቅባቸውን የውጭ ምንዛሪ ሳያስገቡ ቀድመው ከባንኩ በብር የተሰጣቸው ሲሆን ሲጠበቅ የነበረው የውጭ ምንዛሪ እስካሁን ሙሉ ለሙሉ ወደ አገር ውስጥ ባለመግባቱ ባንኩ ከ7 አመት በላይ በተሰብሳቢነት ያለ ስንቅ /provision/ ይዞት ይገኛል፡፡ በዚህ ምክንያት ለግለሰቦች የግል ጥቅም ሲባል የብዙሀኑ ባለአክስዮኖች እና መንግስት በግብር መልክ ሊያገኘው የሚገባው ጥቅም ወደጎን በመተው የብሔራዊ ባንክ መመሪያ FXD/07/1998 በግልፅ ተጥሰዋል፡፡
3. ለአንድ ግለሰብ ከተሰጠው ብድር ብር 70 ሚሊዮን ውስጥ እስከ ብር 28,000,000.00 ከባንክ አሰራር ውጪ በሆነ በባንኩ ወጪ ብድሩ የተዘጋለት ሲሆን ይህም ማለት የባንኩን ሃብት ከህግና ስርአት ውጪ ለግለሰቦች ጥቅም ማዋል ሲሆን በመንግስት ግብር አከፋፈልም ይሁን በባለአክሲዮኖች ትርፍ ክፍፍል ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሰዋል፡፡ በዚህ ምክንያት ለግለሰቦች የግል ጥቅም ሲባል የብዙሀኑ ባለአክስዮኖች እና መንግስት በግብር መልክ ሊያገኘው የሚገባው ጥቅም ወደጎን በመተው የብሔራዊ ባንክ መመሪያ SBB/69/2018 በግልፅ ተጥሰዋል፡፡
4. በብድር አሰራም ቢሆን በተራ ቁጥር ሦስት ላይ እንደ አብነት ተገለፀ እንጂ እጅግ በጣም ብዙ ችግሮች እነዳሉበት ግልፅ ነው ምክንያቱም ከጠቅላላ ብድር እስከ ብር 5 ቢሊዮን የሚሆን በተበላሸ ብድር ውስጥ ገብተዋል ከነዚህ ውስጥም ዋስትና የሌላቸው እስከ ብር 2.2 ቢሊዮን በላይ የሚሆን ነው ከዚህ ውስጥም ከብር 1.6 ቢሊዮን በላይ ሳይሰበሰብ ከአንድ አመት በላይ የሆነው ማለት ነው (Loss)፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን ከአንድ አመት በላይ ሳይከፈሉ የቆዩ ብድሮች ላይ የሚወልደው ወለድም ሳይሰበሰብ በዋናው ገንዘብ ላይ እየተጨመረ ማለተም ካፒታላይዝድ እየተደረገ ከብድር አሰራር ውጪ ሪፖርት እየተደረገ ይገኛል፡፡ በዚህ ምክንያት ለግለሰቦች የግል ጥቅም ሲባል የብዙሀኑ ባለአክስዮኖች እና መንግስት በግብር መልክ ሊያገኘው የሚገባው ጥቅም ወደጎን በመተው የብሔራዊ ባንክ መመሪያ SBB/69/2018 በግልፅ ተጥሰዋል፡፡
5. እንደሚታወቀው ባንኩ በአሁኑ ሰአት ያልተከፈለ የውጭ ምንዛሪ እዳ ውስጥ እንዳለ ይታወቃል ማለትም ለተከታታይ አምስት አመት ከፍሎ ያልጨረሰው ማለት ነው ይህ የሆነበት ደሞ ከአምስት አመት በፊት በተፈቀዱ ሁለት የውጭ ምንዛሪ ማፅደቂያ ቃለ ጉባኤዎች ከባንኩ የውጭ ምንዛሪ የመሰብሰብ አቅም በላይ ሃላፊነት በጎደለው በጨበጣ የተፈቀዱት የውጭ ምንዛሪ ያመጣው ጣጣ ነው፡፡ ይህን ሁሉ የፈፀሙት የባንኩ አመራሮች ግን አንዳንዶቹ ባንኩን ጥለው ከአገር ወጥተዋል አንዳንዶቹ ደግሞ አሁንም ያለምንም ተጠያቂነት የጥፋት ተግባራቸውን በማስቀጠል ላይ ይገኛሉ፡፡
6. እነዚህ ከላይ የተዘረዘሩት እጅግ በጣም ዓይን ያወጡ ተግባታር ስለሆኑ ለጥቆማ ያህል ተገለፁ እንጂ ባነኩ በአሁኑ ሰዓት በብዙ ችግሮች ተተብትቦ በጣም አስጊ በሚባል ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡ ምርመራ በሚጀመርበት ወቅት በተለያዩ ዘዴዎች ማለትም ከሰራተኞች ጋር በመተባበት፣ በፎርጅድ ሰነዶች በመጠቀም፤ እና በተለያዩ ምክንያቶች ከባንኩ የጠፉ ገንዘቦች ስለመኖራቸው ልናረጋግጥላቹ እንወዳለን፡፡
ስለሆነም እነዚህ ከላይ የተገለፁት ችግሮች እንደመነሻ እንድትጠቀሙበት እየጠቆምን ጠቅላላ ባንኩ ያለበት
ደረጃ እጅግ አስጊ ደረጃ ላይ ስለደረሰ አንዳአነድ ችግሮችም ከድንበር ዘለል የህግ ማጣታት ጋር ስለሚያያዝ በዋነኝነት የባለድርሻዎችን መብትና ጥቅም ከማስከበር፣ በመንግስት በግብር አሰባሰብ ላይ እያስከተለ ያለውን ጉደት ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ በሰራተኞች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ላይ እየደረሰ ያለውን ጉዳት ተገቢውን ትኩረት በመስጠት የመንግስታዊ ተቆጣጣሪ አካል የሚጠበቅባችሁን ኃላፊነት እንድትጡ እና አጥፊዎች በህግ ተጠይቀው ያለአግባብ የተበተነው እና የተዘረፈው ገንዘብ እንዲመለስ የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ በአፅንኦት እንጠይቃለን፡፡
አንበሳ ኢንተርናሽናል ባነክ አ.ማ በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ሪፐብሊክ የባንኮች መቋቋሚያ አወጅ ቁጥር 592/2000 በተከፈለ ካፒታል ብር 108.2 ቢሊየን በባለአክሲዮኖች ብዛት 3,739 ተቋቁሞ እ.ኤ.አ ጥር 6 2007 ጀምሮ በስራ ላይ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ በዚህም በተመሰረተበት የስራዘርፍ ለባለ አክሲዮኖች የትርፍ ክፍፍል በመስጠት፣ ካገኘው ትርፍ ለመንግስት ተገቢውን ግብር በመክፈል፣ በአገሪቱ ላይም የስራ አጥነት በመቀነስ እና ሌሎች ማህበራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ እንደነበረ ይታወቃል፡፡ ነገር ግን ይህ እንዳለ ሆኖ በተለያዩ ጊዜያት የተከሰቱ ያሉ አንዳንድ ብልሹ አሰራሮች በተጨባጭ እየታዩ እንደሆኑ ከሚቀርበው አመታዊ ሪፖርት እና የተለያዩ መረጃዎች መረዳት ችለናል፡፡ ድርጊቱን የሚፈፅሙት የባንኩ የበላይ የስራ ኃላፊዎችም ይሁኑ በበላይነት ባንኩን የሚመሩት ቦርዶችም ለተፈጠሩት ብልሹ አሰራሮች ተገቢውን ትኩተት በመስጠት በኃላፊነት እና በተጠያቂነት መንፈስ ከመከታተል ይልቅ ነገሮችን የማድበስበስ አዝማሚያ ነው እየታዩ ያሉት ብሎም አንዳንድ የስራ ኃላፊዎችም አገር ለቀው ሄደዋል አንዳንዶች ደሞ ሚስጢር አፍኖ ለማስቀረት የገቡት ቃልኪዳን እንዳለ በሚመስል መልኩ ጥፋቶችን በመሸፋፈን ተጨማሪ የጥፋት ድርጊታቸውን በማስቀጠል ላይ ተጠምደው ይገኛሉ፡፡ እነዚህ ከታች የተዘረዘሩት ብልሹ አሰራሮች በሚመለከታቸው ተቆጣጣሪ አካል ብሔራዊ ባንክ ይሁን ሌላ የመንግስት አስከባሪ አካል ተገቢውን ትኩረት ተሰጥቶት ምርመራ በማካሄድ አፋጣኝ እርምጃ ካልወሰደ የአገሪቱን ህግና ስርአት በመተማመን መዋእለ ነዋዩን ያፈሰሰ ባለአክሲዮን፣ ለመንግስት ለሚከፈለው የትርፍ ግብር፣ በሰራተኞች ላይ በሚያደርሰው የሞራል ጉዳት እንዲሁም እንዳጠቃላይ በአገሪቱ ጤናማ ያልሆነ የኢኮኖሚ ችግር ስርአት አልባነት ያስከትላል ብለን እናምናለን፡፡
ዋና ዋና ጥቆማዎች
1. በተለያዩ ጊዜያት ባንኩ ለአስመጪዎች የፈቀደላቸው የውጭ ምንዛሪ ተመጣጣኝ የሆነ ንብረት ወደ አገር ባለመግባቱ ምክንያት ባንኩ ከUSD 1,800,000.00፣ ከUSD 220,000.00, እና በላይ በተሰብሳቢነት ያለ ስንቅ /provision/ ከ8 ዓመት በላይ ተይዞ ይገኛል፡፡ በዚህ ምክንያት ለግለሰቦች የግል ጥቅም ሲባል የብዙሀኑ ባለአክስዮኖች እና መንግስት በግብር መልክ ሊያገኘው የሚገባው ጥቅም ወደጎን በመተው የብሔራዊ ባንክ መመሪያ FXD/07/1998 በግልፅ ተጥሰዋል፡፡
2. ለላኪዎች ፍቃድ በመስጠት ግምታቸው USD 1,100,000.00 በላይ የሚገመት ንብረት ከአገራችን ወደ ውጭ ሀገር የተላከ ሲሆን የሚጠበቅባቸውን የውጭ ምንዛሪ ሳያስገቡ ቀድመው ከባንኩ በብር የተሰጣቸው ሲሆን ሲጠበቅ የነበረው የውጭ ምንዛሪ እስካሁን ሙሉ ለሙሉ ወደ አገር ውስጥ ባለመግባቱ ባንኩ ከ7 አመት በላይ በተሰብሳቢነት ያለ ስንቅ /provision/ ይዞት ይገኛል፡፡ በዚህ ምክንያት ለግለሰቦች የግል ጥቅም ሲባል የብዙሀኑ ባለአክስዮኖች እና መንግስት በግብር መልክ ሊያገኘው የሚገባው ጥቅም ወደጎን በመተው የብሔራዊ ባንክ መመሪያ FXD/07/1998 በግልፅ ተጥሰዋል፡፡
3. ለአንድ ግለሰብ ከተሰጠው ብድር ብር 70 ሚሊዮን ውስጥ እስከ ብር 28,000,000.00 ከባንክ አሰራር ውጪ በሆነ በባንኩ ወጪ ብድሩ የተዘጋለት ሲሆን ይህም ማለት የባንኩን ሃብት ከህግና ስርአት ውጪ ለግለሰቦች ጥቅም ማዋል ሲሆን በመንግስት ግብር አከፋፈልም ይሁን በባለአክሲዮኖች ትርፍ ክፍፍል ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሰዋል፡፡ በዚህ ምክንያት ለግለሰቦች የግል ጥቅም ሲባል የብዙሀኑ ባለአክስዮኖች እና መንግስት በግብር መልክ ሊያገኘው የሚገባው ጥቅም ወደጎን በመተው የብሔራዊ ባንክ መመሪያ SBB/69/2018 በግልፅ ተጥሰዋል፡፡
4. በብድር አሰራም ቢሆን በተራ ቁጥር ሦስት ላይ እንደ አብነት ተገለፀ እንጂ እጅግ በጣም ብዙ ችግሮች እነዳሉበት ግልፅ ነው ምክንያቱም ከጠቅላላ ብድር እስከ ብር 5 ቢሊዮን የሚሆን በተበላሸ ብድር ውስጥ ገብተዋል ከነዚህ ውስጥም ዋስትና የሌላቸው እስከ ብር 2.2 ቢሊዮን በላይ የሚሆን ነው ከዚህ ውስጥም ከብር 1.6 ቢሊዮን በላይ ሳይሰበሰብ ከአንድ አመት በላይ የሆነው ማለት ነው (Loss)፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን ከአንድ አመት በላይ ሳይከፈሉ የቆዩ ብድሮች ላይ የሚወልደው ወለድም ሳይሰበሰብ በዋናው ገንዘብ ላይ እየተጨመረ ማለተም ካፒታላይዝድ እየተደረገ ከብድር አሰራር ውጪ ሪፖርት እየተደረገ ይገኛል፡፡ በዚህ ምክንያት ለግለሰቦች የግል ጥቅም ሲባል የብዙሀኑ ባለአክስዮኖች እና መንግስት በግብር መልክ ሊያገኘው የሚገባው ጥቅም ወደጎን በመተው የብሔራዊ ባንክ መመሪያ SBB/69/2018 በግልፅ ተጥሰዋል፡፡
5. እንደሚታወቀው ባንኩ በአሁኑ ሰአት ያልተከፈለ የውጭ ምንዛሪ እዳ ውስጥ እንዳለ ይታወቃል ማለትም ለተከታታይ አምስት አመት ከፍሎ ያልጨረሰው ማለት ነው ይህ የሆነበት ደሞ ከአምስት አመት በፊት በተፈቀዱ ሁለት የውጭ ምንዛሪ ማፅደቂያ ቃለ ጉባኤዎች ከባንኩ የውጭ ምንዛሪ የመሰብሰብ አቅም በላይ ሃላፊነት በጎደለው በጨበጣ የተፈቀዱት የውጭ ምንዛሪ ያመጣው ጣጣ ነው፡፡ ይህን ሁሉ የፈፀሙት የባንኩ አመራሮች ግን አንዳንዶቹ ባንኩን ጥለው ከአገር ወጥተዋል አንዳንዶቹ ደግሞ አሁንም ያለምንም ተጠያቂነት የጥፋት ተግባራቸውን በማስቀጠል ላይ ይገኛሉ፡፡
6. እነዚህ ከላይ የተዘረዘሩት እጅግ በጣም ዓይን ያወጡ ተግባታር ስለሆኑ ለጥቆማ ያህል ተገለፁ እንጂ ባነኩ በአሁኑ ሰዓት በብዙ ችግሮች ተተብትቦ በጣም አስጊ በሚባል ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡ ምርመራ በሚጀመርበት ወቅት በተለያዩ ዘዴዎች ማለትም ከሰራተኞች ጋር በመተባበት፣ በፎርጅድ ሰነዶች በመጠቀም፤ እና በተለያዩ ምክንያቶች ከባንኩ የጠፉ ገንዘቦች ስለመኖራቸው ልናረጋግጥላቹ እንወዳለን፡፡
ስለሆነም እነዚህ ከላይ የተገለፁት ችግሮች እንደመነሻ እንድትጠቀሙበት እየጠቆምን ጠቅላላ ባንኩ ያለበት
ደረጃ እጅግ አስጊ ደረጃ ላይ ስለደረሰ አንዳአነድ ችግሮችም ከድንበር ዘለል የህግ ማጣታት ጋር ስለሚያያዝ በዋነኝነት የባለድርሻዎችን መብትና ጥቅም ከማስከበር፣ በመንግስት በግብር አሰባሰብ ላይ እያስከተለ ያለውን ጉደት ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ በሰራተኞች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ላይ እየደረሰ ያለውን ጉዳት ተገቢውን ትኩረት በመስጠት የመንግስታዊ ተቆጣጣሪ አካል የሚጠበቅባችሁን ኃላፊነት እንድትጡ እና አጥፊዎች በህግ ተጠይቀው ያለአግባብ የተበተነው እና የተዘረፈው ገንዘብ እንዲመለስ የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ በአፅንኦት እንጠይቃለን፡፡
Sponsored by
Surafel
1 month ago
የተገጠመለትን ጉሉኮስ ነቅሎ ከሆስፒታል ያመለጠው ታራሚ በቁጥጥር ስር ዋለ
በጂንካ ማረሚያ ተቋም በስርቆት ወንጀል ተከሶ የነበረውና በጤና ችግር ምክንያት ወደ ጂንካ ዞናል ሆስፒታል ለህክምና የገባው ታራሚ ከሆስፒታል ካመለጠ በኋላ በቁጥጥር ስር መዋሉን የጂንካ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም አስታወቀ ።
የተቋሙ አዛዥ ምክትል ኮማንደር አስቻለው ነሬሬ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት ታራሚው በስርቆት ወንጀል ተከሶ መደበኛ ቀጠሮውን እየተከታተለ የነበረ ሲሆን በጤና ችግር ምክንያት ለከፍተኛ ህክምና ወደ ጂንካ ዞናል ሆስፒታል ተልኮ ነበር ።
ታራሚው ሆስፒታል በነበረበት ወቅት በህክምና ላይ የተገጠመለትን ጉሉኮስ ነቅሎ ሌሊት 2 ሰዓት አካባቢ ማምለጡ ተገልጿል ።
መረጃ የደረሳቸዉ የማረሚያ ተቋሙ አመራሮች ከአካባቢው የፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር ባደረጉት ክትትል ከሌሊቱ 10 ሰዓት ተይዞ ቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል ።
ታራሚው በተከሰሰበትን ወንጀል በመፀፀት ህጉ የሚሰጠውን ውሳኔ ተቀብሎ መታረም ሲገባው ለህክምና በተላከበት ወቅት ማምለጡ በጉዳዩ ላይ በህግ አግባብ ምርመራ ተደርጎ ውሳኔ ይሰጣል ሲሉ ኮማንደር አሰቻለው ነሬሬ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
በጂንካ ማረሚያ ተቋም በስርቆት ወንጀል ተከሶ የነበረውና በጤና ችግር ምክንያት ወደ ጂንካ ዞናል ሆስፒታል ለህክምና የገባው ታራሚ ከሆስፒታል ካመለጠ በኋላ በቁጥጥር ስር መዋሉን የጂንካ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም አስታወቀ ።
የተቋሙ አዛዥ ምክትል ኮማንደር አስቻለው ነሬሬ ለብስራት ሬዲዮ እንደተናገሩት ታራሚው በስርቆት ወንጀል ተከሶ መደበኛ ቀጠሮውን እየተከታተለ የነበረ ሲሆን በጤና ችግር ምክንያት ለከፍተኛ ህክምና ወደ ጂንካ ዞናል ሆስፒታል ተልኮ ነበር ።
ታራሚው ሆስፒታል በነበረበት ወቅት በህክምና ላይ የተገጠመለትን ጉሉኮስ ነቅሎ ሌሊት 2 ሰዓት አካባቢ ማምለጡ ተገልጿል ።
መረጃ የደረሳቸዉ የማረሚያ ተቋሙ አመራሮች ከአካባቢው የፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር ባደረጉት ክትትል ከሌሊቱ 10 ሰዓት ተይዞ ቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል ።
ታራሚው በተከሰሰበትን ወንጀል በመፀፀት ህጉ የሚሰጠውን ውሳኔ ተቀብሎ መታረም ሲገባው ለህክምና በተላከበት ወቅት ማምለጡ በጉዳዩ ላይ በህግ አግባብ ምርመራ ተደርጎ ውሳኔ ይሰጣል ሲሉ ኮማንደር አሰቻለው ነሬሬ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
1 month ago
የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን በመስረቅ አከማችቶ የተገኘ ግለሰብ በ6 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጣ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የካ ክፍለ ከተማ ኮተቤ ኪዳነ ምህረት አካባቢ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን በመስረቅ አከማችቶ የተገኘ ግለሰብ በ6 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ተፈረደበት፡፡
የየካ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ከምስራቅ አዲስ አበባ ሪጅን ህግ ቢሮ ጋር በመተባበር ባደረጉት ኦፕሬሽን ከ3.8 ሚሊየን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸውን የኤሌክትሪክ ኬብሎች፣ አልሙኒየሞችና መዳቦች በመስረቅ ኮተቤ ኪዳነ ምህረት አካባቢ አከማችተው የተገኙ ግለሰቦች ባሳለፍነው መጋቢት ወር መጨረሻ በቁጥጥር ስር መዋላቸው ይታወሳል፡፡
በፌደራል መጀመሪያ ፍርድ ቤት የካ ምድብ ችሎት 2ኛ ወንጀል ችሎት ምስክሮችን በማዳመጥ የስርቆት ወንጀሉን የፈፀመ ግለሰብን በ6 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል፡፡
በተያያዘም በየካ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው ኬብሮን መድኃኒት ቤት አካባቢ በግንባታ ላይ ከሚገኝ ህንፃ ላይ የወደቀ ህንፃ መወጣጫ ዊንች በኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ኬብልና በትራንስፎርመር ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል፡፡
ከህንፃው 12ኛ ፎቅ ላይ የወደቀው ህንፃ መወጣጫ ዊንች በከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ ኬብል ላይ በማረፉ ከኬብሉ ጋር የተያያዘው ትራንስፎርመር የተሸከመ ኮንክሪት ፖል ከነትራንስፎርመሩ ከጥቅም ውጪ ሆኗል፡፡
ተቋሙ ጉዳት የደረሰበትን የኤሌክትሪክ ኬብልና ትራንስፎርመር በመተካት ወደ አገልግሎት ለመመለስ ከ1 ሚሊየን 9 መቶ ሺህ ብር በላይ ወጪ አድርጓል፡፡
ተቋሙ ለደረሰበት ጉዳት ካሳ ክፍያ እንዲፈፀም የምስራቅ አዲስ አበባ ሪጅን ህግ ክፍል ለየካ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መመሪያ ክስ መስርቷል፡፡
በፌደራል መጀመሪያ ፍርድ ቤት የካ ምድብ 2ኛ ፍ/ብሔር ችሎት በቀረበለት የፍ/ብሔር የክስ መዝገቡን ሲመለከት ቆይቶ ማስረጃዎችን ከመረመረ በኋላ ውሳኔ ሰቷል። በዚህም ጉዳት ያደረሰው ድርጅት ለተቋሙ 1 ሚሊየን 959 ሺህ 783 ብር የጉዳት ካሳ ክፍያ እንዲፈፅም ተወስኖበታል፡፡
በአሁኑ ሰዓት ተከሳሽ 250 ሺህ ብር ክፍያ የፈፀመ ሲሆን ቀሪውን ክፍያ ለመፈፀም በቀጠሮ ላይ ይገኛል፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የካ ክፍለ ከተማ ኮተቤ ኪዳነ ምህረት አካባቢ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን በመስረቅ አከማችቶ የተገኘ ግለሰብ በ6 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ተፈረደበት፡፡
የየካ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ከምስራቅ አዲስ አበባ ሪጅን ህግ ቢሮ ጋር በመተባበር ባደረጉት ኦፕሬሽን ከ3.8 ሚሊየን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸውን የኤሌክትሪክ ኬብሎች፣ አልሙኒየሞችና መዳቦች በመስረቅ ኮተቤ ኪዳነ ምህረት አካባቢ አከማችተው የተገኙ ግለሰቦች ባሳለፍነው መጋቢት ወር መጨረሻ በቁጥጥር ስር መዋላቸው ይታወሳል፡፡
በፌደራል መጀመሪያ ፍርድ ቤት የካ ምድብ ችሎት 2ኛ ወንጀል ችሎት ምስክሮችን በማዳመጥ የስርቆት ወንጀሉን የፈፀመ ግለሰብን በ6 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል፡፡
በተያያዘም በየካ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው ኬብሮን መድኃኒት ቤት አካባቢ በግንባታ ላይ ከሚገኝ ህንፃ ላይ የወደቀ ህንፃ መወጣጫ ዊንች በኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ኬብልና በትራንስፎርመር ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል፡፡
ከህንፃው 12ኛ ፎቅ ላይ የወደቀው ህንፃ መወጣጫ ዊንች በከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ ኬብል ላይ በማረፉ ከኬብሉ ጋር የተያያዘው ትራንስፎርመር የተሸከመ ኮንክሪት ፖል ከነትራንስፎርመሩ ከጥቅም ውጪ ሆኗል፡፡
ተቋሙ ጉዳት የደረሰበትን የኤሌክትሪክ ኬብልና ትራንስፎርመር በመተካት ወደ አገልግሎት ለመመለስ ከ1 ሚሊየን 9 መቶ ሺህ ብር በላይ ወጪ አድርጓል፡፡
ተቋሙ ለደረሰበት ጉዳት ካሳ ክፍያ እንዲፈፀም የምስራቅ አዲስ አበባ ሪጅን ህግ ክፍል ለየካ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መመሪያ ክስ መስርቷል፡፡
በፌደራል መጀመሪያ ፍርድ ቤት የካ ምድብ 2ኛ ፍ/ብሔር ችሎት በቀረበለት የፍ/ብሔር የክስ መዝገቡን ሲመለከት ቆይቶ ማስረጃዎችን ከመረመረ በኋላ ውሳኔ ሰቷል። በዚህም ጉዳት ያደረሰው ድርጅት ለተቋሙ 1 ሚሊየን 959 ሺህ 783 ብር የጉዳት ካሳ ክፍያ እንዲፈፅም ተወስኖበታል፡፡
በአሁኑ ሰዓት ተከሳሽ 250 ሺህ ብር ክፍያ የፈፀመ ሲሆን ቀሪውን ክፍያ ለመፈፀም በቀጠሮ ላይ ይገኛል፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
1 month ago
የፈተና ስርቆትን የሚጠየፍ ትውልድ በመፍጠር ሂደት ውስጥ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ ይገባል፦ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
#ethiopia | ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 16 ቀን በበይነ መረብና በወረቀት የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር ተካሂዷል።
በመድረኩ ላይ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ የፈተና ስርቆትን የሚጠየፍ ትውልድ በመፍጠር ሂደት ውስጥ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ አሳስበዋል።
በተለይም በፈተናው ሂደት ፈተና ለመስረቅም ይሁን ለማሰረቅ በሚሞክሩ አካላት ላይ ጥብቅ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን ጠቅሰው፣ ለፈተናው ስኬታማነት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርግ ገልጸዋል፡፡
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው፣ የፈተናው አጠቃላይ ሂደት ደህንነቱ የተጠበቀ፣ በሰላምና በውጤታማነት እንዲጠናቀቅ ሁሉም ባለድርሻ አካል በተባበረ እና በተቀናጀ ሁኔታ መስራት እንደሚጠበቅበት ተናግረዋል፡፡
የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከአጠቃላይ ተፈታኞች መካከል በአብዛኛው በበይነ መረብ የሚሰጥ መሆኑና የፈተና ተቋማቱም በርከት ባለ ሁኔታ በክልል ደረጃ የተደራጁ መሆናቸው ፈተናውን ልዩ እንደሚያደርገው ገልጸዋል፡፡
በመሆኑም የፈተናውን ደህንነት የማረጋገጥ ጉዳይ ከሌላው ጊዜ በተለየ ትኩረት ተሰጥቶት ሊሰራ እንደሚያስፈልግ ሚኒስትር ዴኤታዋ አስገንዝበዋል፡፡
የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መላኩ ፈንታ በበኩላቸው፣ የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ፈተና በጋራ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በስኬት እንዲጠናቀቅ የፀጥታ ዘርፉ ተገቢውን ዝግጅት ማድረጉን ገልጸዋል።
ሀገር አቀፍ ፈተናው ውጤታማ እንዲሆንና በታሰበው አግባብ እንዲጠናቀቅ በታማኝነትና በትብብር ተቀናጅቶ መስራት እንደሚያስፈልግም ምክትል ኮሚሽነር ጀነራሉ አክለው ገልፀዋል፡፡
የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 16 በበይነ መረብና በወረቀት እንደሚሰጥ አስታውሰዋል።
ይህንኑ ፈተና ለመውሰድ 563,501 ተፈታኞች መመዝገባቸውን ጠቅሰው፣ ከእነዚህ ውስጥ 306,456ቱ የተፈጥሮ ሳይንስ፣ 257,045ቱ ደግሞ የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡
በምክክር መድረኩ ላይ የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች፣ የፌዴራል ፖሊስ አመራሮችና ሌሎችም ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል ያለው ኢ ቢ ሲ ነው፡፡
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 16 ቀን በበይነ መረብና በወረቀት የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር ተካሂዷል።
በመድረኩ ላይ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ የፈተና ስርቆትን የሚጠየፍ ትውልድ በመፍጠር ሂደት ውስጥ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ አሳስበዋል።
በተለይም በፈተናው ሂደት ፈተና ለመስረቅም ይሁን ለማሰረቅ በሚሞክሩ አካላት ላይ ጥብቅ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን ጠቅሰው፣ ለፈተናው ስኬታማነት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርግ ገልጸዋል፡፡
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው፣ የፈተናው አጠቃላይ ሂደት ደህንነቱ የተጠበቀ፣ በሰላምና በውጤታማነት እንዲጠናቀቅ ሁሉም ባለድርሻ አካል በተባበረ እና በተቀናጀ ሁኔታ መስራት እንደሚጠበቅበት ተናግረዋል፡፡
የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከአጠቃላይ ተፈታኞች መካከል በአብዛኛው በበይነ መረብ የሚሰጥ መሆኑና የፈተና ተቋማቱም በርከት ባለ ሁኔታ በክልል ደረጃ የተደራጁ መሆናቸው ፈተናውን ልዩ እንደሚያደርገው ገልጸዋል፡፡
በመሆኑም የፈተናውን ደህንነት የማረጋገጥ ጉዳይ ከሌላው ጊዜ በተለየ ትኩረት ተሰጥቶት ሊሰራ እንደሚያስፈልግ ሚኒስትር ዴኤታዋ አስገንዝበዋል፡፡
የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መላኩ ፈንታ በበኩላቸው፣ የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ፈተና በጋራ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በስኬት እንዲጠናቀቅ የፀጥታ ዘርፉ ተገቢውን ዝግጅት ማድረጉን ገልጸዋል።
ሀገር አቀፍ ፈተናው ውጤታማ እንዲሆንና በታሰበው አግባብ እንዲጠናቀቅ በታማኝነትና በትብብር ተቀናጅቶ መስራት እንደሚያስፈልግም ምክትል ኮሚሽነር ጀነራሉ አክለው ገልፀዋል፡፡
የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 16 በበይነ መረብና በወረቀት እንደሚሰጥ አስታውሰዋል።
ይህንኑ ፈተና ለመውሰድ 563,501 ተፈታኞች መመዝገባቸውን ጠቅሰው፣ ከእነዚህ ውስጥ 306,456ቱ የተፈጥሮ ሳይንስ፣ 257,045ቱ ደግሞ የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡
በምክክር መድረኩ ላይ የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች፣ የፌዴራል ፖሊስ አመራሮችና ሌሎችም ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል ያለው ኢ ቢ ሲ ነው፡፡
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
1 month ago
ለከባድና ቀላል ጭነት መኪና ባለቤቶች: የጂፒኤስ መከታተያ ሥርዓት ቁልፍ ጥቅሞች 🚚📍
የጭነት መኪና ባለቤትነት፣ የከባድም ሆነ የቀላል ጭነት፣ ትልቅ ኢንቨስትመንት ነው። እነዚህ ተሽከርካሪዎች የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ የጀርባ አጥንት ሲሆኑ፣ የእነሱን እንቅስቃሴ በአግባቡ መቆጣጠር ለሥራው ስኬት ወሳኝ ነው።
በኢትዮጵያ በተለይ የነዳጅ ወጪ መናር፣ የመንገድ ሁኔታዎች እና የሎጂስቲክስ አስተዳደር የራሳቸው የሆኑ ፈተናዎች ሲሆኑ፣ የተሽከርካሪ ጂፒኤስ መከታተያ ሥርዓት ለእነዚህ ችግሮች ውጤታማ መፍትሄዎችን ይሰጣል።
ታዲያ የጂፒኤስ መከታተያ ሥርዓት ለከባድና ቀላል ጭነት መኪና ባለቤቶች የሚሰጣቸው ዋና ዋና ጥቅሞች ምንድን ናቸው? በአጭሩ እነሆ፦
የጭነት መኪናዎ ደህንነት እና ቅልጥፍና ያሳስብዎታል? ጂፒኤስ መከታተያ ዘመናዊ መፍትሄ ነው!
• ተሽከርካሪ ደህንነት 🔒: መኪናዎ የት እንዳለ በቅጽበት ይወቁ! ስርቆትን ለመከላከል እና ከተሰረቀ በፍጥነት ለማግኘት ይረዳል።
• ወጪ ቅነሳ 💰: የነዳጅ ፍጆታን ይቆጣጠሩ፣ አላስፈላጊ ወጪን ይቀንሱ። ትክክለኛውን መንገድ በመምረጥ ነዳጅ ይቆጥባሉ! ⛽
• የሥራ ቅልጥፍና 🚀: እያንዳንዱ መኪና የት እንዳለ በማወቅ ሥራዎችን በቀላሉ ያቀናብሩ። ለደንበኞችም ትክክለኛ መረጃ ይስጡ።
• አሽከርካሪ አስተዳደር 👨✈️: የአሽከርካሪዎችን የአነዳድ ዘይቤ እና የሥራ ሰዓት ይቆጣጠሩ። ደህንነትን ይጨምራል፣ ጉዳትን ይቀንሳል።
• የጥገና አስተዳደር 🛠️: የጥገና ጊዜን በማቀድ ድንገተኛ ብልሽቶችን ይቀንሱ።
በአጭሩ፣ ጂፒኤስ መከታተያ የንብረትዎን ደህንነት ለማረጋገጥ፣ ወጪ ለመቆጠብ፣ ቅልጥፍናን ለማሳደግ እና የአሽከርካሪዎችን ደህንነት ለመከታተል ወሳኝ ኢንቨስትመንት ነው! 💪
ሳሚ አውቶሞቲቭ - አስተማማኝ የመኪና ደህንነትዎ! 🛡️
🛠️ ይህን ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለማስገጠም እና ለበለጠ መረጃ አሁኑኑ ይደውሉልን! 📞
📲 ስልክ ቁጥሮች:
• 0912072874
• 0947329334
• 0913917373
• 0906015555
• 0906065151 (አዳማ)
• 0948110505 (ድሬዳዋ ቢሮ)
• +25111470 5763 (የደንበኞች አገልግሎት)
1 month ago
ከውጪ ሀገር ዜጋ ላይ የስርቆት ወንጀል ፈጽመዋል የተባሉ አራት ተጠርጣ ሪዎች ከነ ኤግዚቢቱ በቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡
የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽቱ 2 ሰዓት በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 መስቀል አደባባይ አካባቢ ሲሆን እስጢፋኖስ ተስፋዬ፣ ወንድሙ ደምሴ፣ ቦምሳ አብሳ እና ኢብራሂም አስፋው የተባሉት ተጠርጣሪዎች ኢትዮጵያን ለመጎብኘት ከመጣ አንድ የውጭ አገር ዜጋ ላይ የስርቆት ወንጀል መፈጸማቸው ተገልጿል።
ተጠርጣሪዎቹ የግል ተበዳይን ሶፍት ግዛን ብለው በማዋከብና ትኩረቱን በማሳጣት ኪሱ ውስጥ የነበረውን ግምቱ 204 ሺ ብር የሚያወጣ Iphone17pro የተሰኘ ስማርት ሞባይል ስልክ ይዘውበት መሰወራቸውን የቂርቆስ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ አስታውቋል ።
በዕለቱ ከግል ተበዳይ የስልኩ መጥፋት ሪፖርት የደረሰው የቂርቆስ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ የክትትል ቡድን በማቋቋምና ከአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ጋር በቅንጅት ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋል ክትትል መጀመሩን ጠቁሟል።
በተደረገው ፈጣን የማፈላለግና የክትትል ስራም አራቱም ተጠርጣሪዎች ስልኩን እንደያዙ ከተኙበት ደምበል ዲሲ ከሚባል አካባቢ በዚያው ሌሊት በሰዓታት ልዩነት በቁጥጥር ስር በማዋል የግል ተበዳይ ከክ/ከተማው ዋና ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ረ/ኮሚሽነር አድማሱ ኢፋ ንብረቱን የተረከቡ ሲሆን ፖሊስ ምርመራውንም እያሰፋ እንደሚገኝ ተገልጿል።
የሀገርም ውስጥም ሆነ የውጪ ሀገር ዜጎች በሠላም ወጥተው በሠላም እንዲገቡ ያለ ረፍት 24/7 የሚሰራ ቢሆንም ወንጀል ፈጻሚዎች አሳቻ ሰዓት እና ቦታ የሚጠቀሙ በመሆኑ በምሽት ለተለያዩ የግል ተግባራት ከቦታ ቦታ የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦች ንብረቶቻቸውን በአግባቡ በመያዝ ወንጀል ተፈጽሞ ሲገኝም ወዲያው ለፖሊስ ማሳወቅ እንደሚገባም የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ መልዕክቱን አስተላልፏል።
የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽቱ 2 ሰዓት በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 መስቀል አደባባይ አካባቢ ሲሆን እስጢፋኖስ ተስፋዬ፣ ወንድሙ ደምሴ፣ ቦምሳ አብሳ እና ኢብራሂም አስፋው የተባሉት ተጠርጣሪዎች ኢትዮጵያን ለመጎብኘት ከመጣ አንድ የውጭ አገር ዜጋ ላይ የስርቆት ወንጀል መፈጸማቸው ተገልጿል።
ተጠርጣሪዎቹ የግል ተበዳይን ሶፍት ግዛን ብለው በማዋከብና ትኩረቱን በማሳጣት ኪሱ ውስጥ የነበረውን ግምቱ 204 ሺ ብር የሚያወጣ Iphone17pro የተሰኘ ስማርት ሞባይል ስልክ ይዘውበት መሰወራቸውን የቂርቆስ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ አስታውቋል ።
በዕለቱ ከግል ተበዳይ የስልኩ መጥፋት ሪፖርት የደረሰው የቂርቆስ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ የክትትል ቡድን በማቋቋምና ከአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ጋር በቅንጅት ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋል ክትትል መጀመሩን ጠቁሟል።
በተደረገው ፈጣን የማፈላለግና የክትትል ስራም አራቱም ተጠርጣሪዎች ስልኩን እንደያዙ ከተኙበት ደምበል ዲሲ ከሚባል አካባቢ በዚያው ሌሊት በሰዓታት ልዩነት በቁጥጥር ስር በማዋል የግል ተበዳይ ከክ/ከተማው ዋና ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ረ/ኮሚሽነር አድማሱ ኢፋ ንብረቱን የተረከቡ ሲሆን ፖሊስ ምርመራውንም እያሰፋ እንደሚገኝ ተገልጿል።
የሀገርም ውስጥም ሆነ የውጪ ሀገር ዜጎች በሠላም ወጥተው በሠላም እንዲገቡ ያለ ረፍት 24/7 የሚሰራ ቢሆንም ወንጀል ፈጻሚዎች አሳቻ ሰዓት እና ቦታ የሚጠቀሙ በመሆኑ በምሽት ለተለያዩ የግል ተግባራት ከቦታ ቦታ የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦች ንብረቶቻቸውን በአግባቡ በመያዝ ወንጀል ተፈጽሞ ሲገኝም ወዲያው ለፖሊስ ማሳወቅ እንደሚገባም የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ መልዕክቱን አስተላልፏል።
Sponsored by
Surafel
1 month ago
የኃይል ስርቆትን የጠቆመ 25 በመቶ ኮሚሽን ያገኛል ተባለ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በከፍተኛ ወጪ የሚገነቡ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን ከስርቆትና ከጉዳት ለመጠበቅ ህብረተሰቡ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ጥሪ አቅርቧል።
ተቋሙ የኃይል ስርቆት ሲፈጸም ጥቆማ ለሚያደርጉ ዜጎች ከተጣለው ቅጣት ላይ የ25 በመቶ የኮሚሽን ክፍያ እንደሚፈጽም በይፋ አስታውቋል።
ይህ የተገለጸው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከውሃና ኢነርጂ ባለስልጣን፣ ከፖሊሲ ጥናትና ምርምር እንዲሁም ከዓለም ባንክ ጋር በመቀናጀት ለመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ባዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫና ትምህርታዊ ስልጠና ላይ ነው።
ይህ በዓይነቱ ለየት ያለ መርሃ ግብር በዋናነት ያለመው፣ የዜና አውታሮችና ጋዜጠኞች በጉዳዩ ላይ በቂ ግንዛቤ ኖሯቸው ህብረተሰቡ የኤሌክትሪክ ኃይልን በቁጠባ፣ በደህንነትና ከአደጋ ነፃ በሆነ መልኩ እንዲጠቀም የማስገንዘብ ሚናቸውን እንዲወጡ ለማድረግ ነው።
በዕለቱ የተገኙት የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ግዛው ተስፋዬ መገናኛ ብዙኃን መረጃ በመስጠትና በማሳወቅ ረገድ የማይተካ ሚና እንዳላቸው ገልጸው፣ በከፍተኛ ወጪ ተደራሽ የሚደረገውን የኤሌክትሪክ ኃይል ህብረተሰቡ ያለብክነት እንዲጠቀም በትኩረት መስራት እንደሚገባቸው አሳስበዋል።
በተቋሙ የሽያጭ እና ደንበኞች አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ይኸይስ ለዝግጅት ክፍላችን እንደገለጹት፣ ስልጠናው ደንበኞች ፍጆታቸውን እንዴት ማስላት እንደሚችሉ፣ የታሪፍ አሰራሮችን፣ የደህንነት ጥንቃቄዎችን እና ምን ዓይነት ኃይል ቆጣቢ ቁሳቁሶችን መጠቀም እንዳለባቸው ግንዛቤ ለመፍጠር ታሳቢ ያደረገ ነው።
ይህ ስልጠና የአንድ ወቅት ብቻ ሳይሆን ቀጣይነት ያለውና በየበጀት ዓመቱ በዕቅድ የሚከናወን ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም በትምህርት ቤቶች፣ በኢንዱስትሪዎችና በተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች መሰጠቱን ዳይሬክተሩ አስታውሰዋል።
ማህበረሰቡ ትክክለኛውን መረጃ እንዲያገኝ ለማድረግም በቀጣይነት ከሚዲያ አካላት ጋር በቅርበት ለመስራት መታቀዱን ጠቁመዋል።
አቶ ይኸይስ አክለውም፣ ደንበኞች የኤሌክትሪክ ፍጆታቸውን ለመቀነስና የኃይል መቆራረጥን ለማስቀረት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ጭነት የሚበዛባቸውን የዕለት ተዕለት ሰዓታት በማስወገድ፣ የኃይል ጫና የሌለባቸውን ሰዓታት በተለይም ከሌሊቱ አራት ሰዓት እስከ ጠዋት ሶስት ሰዓት ያለውን ጊዜ እንዲጠቀሙ መክረዋል።
በተጨማሪም ደረጃቸውን የጠበቁ፣ ኃይል የማይበክሉና ውጤታማ የሆኑ የኤሌክትሪክ እቃዎችንና ማሽነሪዎችን መርጦ መጠቀም እንደሚገባ አሳስበዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ማርኬቲንግ፣ ሽያጭና ደንበኞች አገልግሎት ሥራ አስፈፃሚ አቶ ኢሳያስ ደንድር እና የተቋሙ የኮሙዮኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ አንዋር አብራር በበኩላቸው፣ ከተለያዩ ዓለም አቀፍና አገር በቀል ተቋማት ጋር በመቀናጀት የተጀመረው ይህ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃዎችን ለመገናኛ ብዙኃን ተደራሽ ማድረግ ዋነኛ ኃላፊነት መሆኑን የጠቀሱት የሥራ ኃላፊዎቹ፣ በደንበኞች እና በአገልግሎት ሰጪው ተቋም መካከል ጠንካራና አስተማማኝ ድልድይ መገንባት የመረጃ ፍሰቱን ጤናማ፣ ግልጽ እና ቀልጣፋ ለማድረግ ከፍተኛ እገዛ እንደሚኖረው አስምረውበታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በከፍተኛ ወጪ የሚገነቡ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን ከስርቆትና ከጉዳት ለመጠበቅ ህብረተሰቡ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ጥሪ አቅርቧል።
ተቋሙ የኃይል ስርቆት ሲፈጸም ጥቆማ ለሚያደርጉ ዜጎች ከተጣለው ቅጣት ላይ የ25 በመቶ የኮሚሽን ክፍያ እንደሚፈጽም በይፋ አስታውቋል።
ይህ የተገለጸው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከውሃና ኢነርጂ ባለስልጣን፣ ከፖሊሲ ጥናትና ምርምር እንዲሁም ከዓለም ባንክ ጋር በመቀናጀት ለመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ባዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫና ትምህርታዊ ስልጠና ላይ ነው።
ይህ በዓይነቱ ለየት ያለ መርሃ ግብር በዋናነት ያለመው፣ የዜና አውታሮችና ጋዜጠኞች በጉዳዩ ላይ በቂ ግንዛቤ ኖሯቸው ህብረተሰቡ የኤሌክትሪክ ኃይልን በቁጠባ፣ በደህንነትና ከአደጋ ነፃ በሆነ መልኩ እንዲጠቀም የማስገንዘብ ሚናቸውን እንዲወጡ ለማድረግ ነው።
በዕለቱ የተገኙት የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ግዛው ተስፋዬ መገናኛ ብዙኃን መረጃ በመስጠትና በማሳወቅ ረገድ የማይተካ ሚና እንዳላቸው ገልጸው፣ በከፍተኛ ወጪ ተደራሽ የሚደረገውን የኤሌክትሪክ ኃይል ህብረተሰቡ ያለብክነት እንዲጠቀም በትኩረት መስራት እንደሚገባቸው አሳስበዋል።
በተቋሙ የሽያጭ እና ደንበኞች አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ይኸይስ ለዝግጅት ክፍላችን እንደገለጹት፣ ስልጠናው ደንበኞች ፍጆታቸውን እንዴት ማስላት እንደሚችሉ፣ የታሪፍ አሰራሮችን፣ የደህንነት ጥንቃቄዎችን እና ምን ዓይነት ኃይል ቆጣቢ ቁሳቁሶችን መጠቀም እንዳለባቸው ግንዛቤ ለመፍጠር ታሳቢ ያደረገ ነው።
ይህ ስልጠና የአንድ ወቅት ብቻ ሳይሆን ቀጣይነት ያለውና በየበጀት ዓመቱ በዕቅድ የሚከናወን ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም በትምህርት ቤቶች፣ በኢንዱስትሪዎችና በተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች መሰጠቱን ዳይሬክተሩ አስታውሰዋል።
ማህበረሰቡ ትክክለኛውን መረጃ እንዲያገኝ ለማድረግም በቀጣይነት ከሚዲያ አካላት ጋር በቅርበት ለመስራት መታቀዱን ጠቁመዋል።
አቶ ይኸይስ አክለውም፣ ደንበኞች የኤሌክትሪክ ፍጆታቸውን ለመቀነስና የኃይል መቆራረጥን ለማስቀረት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ጭነት የሚበዛባቸውን የዕለት ተዕለት ሰዓታት በማስወገድ፣ የኃይል ጫና የሌለባቸውን ሰዓታት በተለይም ከሌሊቱ አራት ሰዓት እስከ ጠዋት ሶስት ሰዓት ያለውን ጊዜ እንዲጠቀሙ መክረዋል።
በተጨማሪም ደረጃቸውን የጠበቁ፣ ኃይል የማይበክሉና ውጤታማ የሆኑ የኤሌክትሪክ እቃዎችንና ማሽነሪዎችን መርጦ መጠቀም እንደሚገባ አሳስበዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ማርኬቲንግ፣ ሽያጭና ደንበኞች አገልግሎት ሥራ አስፈፃሚ አቶ ኢሳያስ ደንድር እና የተቋሙ የኮሙዮኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ አንዋር አብራር በበኩላቸው፣ ከተለያዩ ዓለም አቀፍና አገር በቀል ተቋማት ጋር በመቀናጀት የተጀመረው ይህ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃዎችን ለመገናኛ ብዙኃን ተደራሽ ማድረግ ዋነኛ ኃላፊነት መሆኑን የጠቀሱት የሥራ ኃላፊዎቹ፣ በደንበኞች እና በአገልግሎት ሰጪው ተቋም መካከል ጠንካራና አስተማማኝ ድልድይ መገንባት የመረጃ ፍሰቱን ጤናማ፣ ግልጽ እና ቀልጣፋ ለማድረግ ከፍተኛ እገዛ እንደሚኖረው አስምረውበታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
2 months ago
ከማረሚያ ቤት በወጣ በ3ኛ ቀን የስርቆት ወንጀል የፈፀመው ግለሰብ በፅኑ እስራት ተቀጣ
ዳዊት በላቸው የተባለው ተከሳሽ ከዚህ ቀደም የቅሚያ ወንጀሉን የፈፀመው በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ልዩ ቦታው አረንጓዴ ሰፈር ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ሰኔ 7 ቀን 2014 ዓ/ም ነበር።
ግለሰቡ የዋጋ ግምቱ 25 ሺህ ብር የሚያወጣ ሳምሰንግ M 32 ሞባይል ከግል ተበዳይ ላይ ቀምቶ ለማምለጥ ሲሞክር በፖሊስ አባላትና በህብረተሰቡ ትብብር እጅ ከፈንጅ ተይዞ አስፈላጊውን ምርመራ ከተጣራበት በኋላ አቃቤ ህግ ክስ መስርቶበት ጉዳዩን የተመለከተው የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ቀራንዮ ምድብ ወንጀል ችሎት በ3 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ አስተላልፎበት በማረሚያ ቤት መቆየቱን በክፍለ ከተማው ፖሊስ ዋና መምሪያ የቤተል አካባቢ ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል።
የ3ዓመት የእስር ጊዜውን ጨርሶ ከማረሚያ ቤት የወጣውና ያልታረመው ይህ ግለሰብ በወጣ በ3ኛው ቀን በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ቤተል አካባቢ ከሚገኝ አንድ አፖርታማ ገብቶ 19 ሺህ ብር የሚገመቱ የተለያዩ ጫማዎችን ሰርቆ ለማምለጥ ሲሞክር ስራ ላይ በነበሩ የወንጀል መከላከል የፖሊስ አባላትና በህብረተሰቡ ትብብር እጅ ከፈንጅ መያዙን የቤተል አካባቢ ፖሊስ መምሪያ ገልጿል።
የተሰረቁት ንብረቶች በኤግዚቢት ተይዘው በግለሰቡ ላይ አስፈላጊው ምርመራ ከተጣራበት በኋላ አቃቤ ህግ ክስ መስርቶበታል፤ ጉዳዩን የተመለከተው የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ቀራንዮ ምድብ ፈጣን ወንጀል ችሎት ተከሳሹን ያስተምራል ሌሎች ወንጀል ፈፃሚዎችን ያስጠነቅቃል በማለት ሰኔ16 ቀን 2018 ዓ/ም በዋለው ችሎት በፈፀመው ደጋጋሚ የወንጀል ድርጊት በ4 አመት ከ5 ወር ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ እንዳስተላለፈበት ፖሊስ ጠቅሷል፡፡
Seledadotio
ዳዊት በላቸው የተባለው ተከሳሽ ከዚህ ቀደም የቅሚያ ወንጀሉን የፈፀመው በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ልዩ ቦታው አረንጓዴ ሰፈር ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ሰኔ 7 ቀን 2014 ዓ/ም ነበር።
ግለሰቡ የዋጋ ግምቱ 25 ሺህ ብር የሚያወጣ ሳምሰንግ M 32 ሞባይል ከግል ተበዳይ ላይ ቀምቶ ለማምለጥ ሲሞክር በፖሊስ አባላትና በህብረተሰቡ ትብብር እጅ ከፈንጅ ተይዞ አስፈላጊውን ምርመራ ከተጣራበት በኋላ አቃቤ ህግ ክስ መስርቶበት ጉዳዩን የተመለከተው የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ቀራንዮ ምድብ ወንጀል ችሎት በ3 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ አስተላልፎበት በማረሚያ ቤት መቆየቱን በክፍለ ከተማው ፖሊስ ዋና መምሪያ የቤተል አካባቢ ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል።
የ3ዓመት የእስር ጊዜውን ጨርሶ ከማረሚያ ቤት የወጣውና ያልታረመው ይህ ግለሰብ በወጣ በ3ኛው ቀን በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ቤተል አካባቢ ከሚገኝ አንድ አፖርታማ ገብቶ 19 ሺህ ብር የሚገመቱ የተለያዩ ጫማዎችን ሰርቆ ለማምለጥ ሲሞክር ስራ ላይ በነበሩ የወንጀል መከላከል የፖሊስ አባላትና በህብረተሰቡ ትብብር እጅ ከፈንጅ መያዙን የቤተል አካባቢ ፖሊስ መምሪያ ገልጿል።
የተሰረቁት ንብረቶች በኤግዚቢት ተይዘው በግለሰቡ ላይ አስፈላጊው ምርመራ ከተጣራበት በኋላ አቃቤ ህግ ክስ መስርቶበታል፤ ጉዳዩን የተመለከተው የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ቀራንዮ ምድብ ፈጣን ወንጀል ችሎት ተከሳሹን ያስተምራል ሌሎች ወንጀል ፈፃሚዎችን ያስጠነቅቃል በማለት ሰኔ16 ቀን 2018 ዓ/ም በዋለው ችሎት በፈፀመው ደጋጋሚ የወንጀል ድርጊት በ4 አመት ከ5 ወር ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ እንዳስተላለፈበት ፖሊስ ጠቅሷል፡፡
Seledadotio
2 months ago
በቅሚያ ወንጀል ተከሶ የ3 ዓመት ፍርድ ውሳኔውን ጨርሶ ከማረሚያ ቤት በወጣ በ3ኛው ቀን የስርቆት ወንጀል የፈፀመው ግለሰብ በፅኑ እስራት ተቀጣ።
ዳዊት በላቸው የተባለው ተከሳሽ ከዚህ ቀደም የቅሚያ ወንጀሉን የፈፀመው በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ልዩ ቦታው አረንጓዴ ሰፈር ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ሰኔ 7 ቀን 2014 ዓ/ም ነበር።
ግለሰቡ የዋጋ ግምቱ 25 ሺህ ብር የሚያወጣ ሳምሰንግ M 32 ሞባይል ከግል ተበዳይ ላይ ቀምቶ ለማምለጥ ሲሞክር በፖሊስ አባላትና በህብረተሰቡ ትብብር እጅ ከፈንጅ ተይዞ አስፈላጊውን ምርመራ ከተጣራበት በኋላ አቃቤ ህግ ክስ መስርቶበት ጉዳዩን የተመለከተው የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ቀራንዮ ምድብ ወንጀል ችሎት በ3 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ አስተላልፎበት በማረሚያ ቤት መቆየቱን በክፍለ ከተማው ፖሊስ ዋና መምሪያ የቤተል አካባቢ ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል።
የ3 አመት የእስር ጊዜውን ጨርሶ ከማረሚያ ቤት የወጣውና ያልታረመው ይህ ግለሰብ በወጣ በ3ኛው ቀን በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ቤተል አካባቢ ከሚገኝ አንድ አፖርታማ ገብቶ 19 ሺህ ብር የሚገመቱ የተለያዩ ጫማዎችን ሰርቆ ለማምለጥ ሲሞክር ስራ ላይ በነበሩ የወንጀል መከላከል የፖሊስ አባላትና በህብረተሰቡ ትብብር እጅ ከፈንጅ መያዙን የቤተል አካባቢ ፖሊስ መምሪያ ገልጿል።
የተሰረቁት ንብረቶች በኤግዚቢት ተይዘው በግለሰቡ ላይ አስፈላጊው ምርመራ ከተጣራበት በኋላ አቃቤ ህግ ክስ መስርቶበታል፤ ጉዳዩን የተመለከተው የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ቀራንዮ ምድብ ፈጣን ወንጀል ችሎት ተከሳሹን ያስተምራል ሌሎች ወንጀል ፈፃሚዎችን ያስጠነቅቃል በማለት ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ/ም በዋለው ችሎት በፈፀመው ደጋጋሚ የወንጀል ድርጊት በ4 አመት ከ5 ወር ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ እንዳስተላለፈበት ፖሊስ ጠቅሷል፡፡
አብዛኛው ወንጀል ፈፃሚ በማረሚያ ቤት የእስር ቆይታው በጥሩ ስነ ምግባር ታርሞና ታንፆ ወደ ማህበረሰቡ ቢቀላቀልም አንዳንድ የእጅ አመል ያለባቸው ግለሰቦች ደግሞ ከማረሚያ ቤት ወጥተው ወንጀል ቢፈጽሙም ከህግ እንደማያመልጡ የገለፀው የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ህብረተሰቡ ወንጀል እንዳይፈፀምበት ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግ ለፀጥታ አካላት ጥቆማ ከመስጠት ጀምሮ የሚያደርገውን ትብብር አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪውን አቅርቧል።
ዳዊት በላቸው የተባለው ተከሳሽ ከዚህ ቀደም የቅሚያ ወንጀሉን የፈፀመው በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ልዩ ቦታው አረንጓዴ ሰፈር ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ሰኔ 7 ቀን 2014 ዓ/ም ነበር።
ግለሰቡ የዋጋ ግምቱ 25 ሺህ ብር የሚያወጣ ሳምሰንግ M 32 ሞባይል ከግል ተበዳይ ላይ ቀምቶ ለማምለጥ ሲሞክር በፖሊስ አባላትና በህብረተሰቡ ትብብር እጅ ከፈንጅ ተይዞ አስፈላጊውን ምርመራ ከተጣራበት በኋላ አቃቤ ህግ ክስ መስርቶበት ጉዳዩን የተመለከተው የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ቀራንዮ ምድብ ወንጀል ችሎት በ3 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ አስተላልፎበት በማረሚያ ቤት መቆየቱን በክፍለ ከተማው ፖሊስ ዋና መምሪያ የቤተል አካባቢ ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል።
የ3 አመት የእስር ጊዜውን ጨርሶ ከማረሚያ ቤት የወጣውና ያልታረመው ይህ ግለሰብ በወጣ በ3ኛው ቀን በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ቤተል አካባቢ ከሚገኝ አንድ አፖርታማ ገብቶ 19 ሺህ ብር የሚገመቱ የተለያዩ ጫማዎችን ሰርቆ ለማምለጥ ሲሞክር ስራ ላይ በነበሩ የወንጀል መከላከል የፖሊስ አባላትና በህብረተሰቡ ትብብር እጅ ከፈንጅ መያዙን የቤተል አካባቢ ፖሊስ መምሪያ ገልጿል።
የተሰረቁት ንብረቶች በኤግዚቢት ተይዘው በግለሰቡ ላይ አስፈላጊው ምርመራ ከተጣራበት በኋላ አቃቤ ህግ ክስ መስርቶበታል፤ ጉዳዩን የተመለከተው የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ቀራንዮ ምድብ ፈጣን ወንጀል ችሎት ተከሳሹን ያስተምራል ሌሎች ወንጀል ፈፃሚዎችን ያስጠነቅቃል በማለት ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ/ም በዋለው ችሎት በፈፀመው ደጋጋሚ የወንጀል ድርጊት በ4 አመት ከ5 ወር ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ እንዳስተላለፈበት ፖሊስ ጠቅሷል፡፡
አብዛኛው ወንጀል ፈፃሚ በማረሚያ ቤት የእስር ቆይታው በጥሩ ስነ ምግባር ታርሞና ታንፆ ወደ ማህበረሰቡ ቢቀላቀልም አንዳንድ የእጅ አመል ያለባቸው ግለሰቦች ደግሞ ከማረሚያ ቤት ወጥተው ወንጀል ቢፈጽሙም ከህግ እንደማያመልጡ የገለፀው የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ህብረተሰቡ ወንጀል እንዳይፈፀምበት ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግ ለፀጥታ አካላት ጥቆማ ከመስጠት ጀምሮ የሚያደርገውን ትብብር አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪውን አቅርቧል።
2 months ago
የ3 ዓመት ፍርድ ውሳኔውን ጨርሶ ከማረሚያ ቤት በወጣ በ3ኛው ቀን የስርቆት ወንጀል የፈፀመው ግለሰብ በፅኑ እስራት ተቀጣ።
ዳዊት በላቸው የተባለው ተከሳሽ ከዚህ ቀደም የቅሚያ ወንጀሉን የፈፀመው በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ልዩ ቦታው አረንጓዴ ሰፈር ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ሰኔ 7 ቀን 2014 ዓ/ም ነበር።
ግለሰቡ የዋጋ ግምቱ 25 ሺህ ብር የሚያወጣ ሳምሰንግ M 32 ሞባይል ከግል ተበዳይ ላይ ቀምቶ ለማምለጥ ሲሞክር በፖሊስ አባላትና በህብረተሰቡ ትብብር እጅ ከፈንጅ ተይዞ አስፈላጊውን ምርመራ ከተጣራበት በኋላ አቃቤ ህግ ክስ መስርቶበት ጉዳዩን የተመለከተው የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ቀራንዮ ምድብ ወንጀል ችሎት በ3 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ አስተላልፎበት በማረሚያ ቤት መቆየቱን በክፍለ ከተማው ፖሊስ ዋና መምሪያ የቤተል አካባቢ ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል።
የ3 አመት የእስር ጊዜውን ጨርሶ ከማረሚያ ቤት የወጣውና ያልታረመው ይህ ግለሰብ በወጣ በ3ኛው ቀን በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ቤተል አካባቢ ከሚገኝ አንድ አፖርታማ ገብቶ 19 ሺህ ብር የሚገመቱ የተለያዩ ጫማዎችን ሰርቆ ለማምለጥ ሲሞክር ስራ ላይ በነበሩ የወንጀል መከላከል የፖሊስ አባላትና በህብረተሰቡ ትብብር እጅ ከፈንጅ መያዙን የቤተል አካባቢ ፖሊስ መምሪያ ገልጿል።
የተሰረቁት ንብረቶች በኤግዚቢት ተይዘው በግለሰቡ ላይ አስፈላጊው ምርመራ ከተጣራበት በኋላ አቃቤ ህግ ክስ መስርቶበታል፤ ጉዳዩን የተመለከተው የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ቀራንዮ ምድብ ፈጣን ወንጀል ችሎት ተከሳሹን ያስተምራል ሌሎች ወንጀል ፈፃሚዎችን ያስጠነቅቃል በማለት ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ/ም በዋለው ችሎት በፈፀመው ደጋጋሚ የወንጀል ድርጊት በ4 አመት ከ5 ወር ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ እንዳስተላለፈበት ፖሊስ ጠቅሷል፡፡
አብዛኛው ወንጀል ፈፃሚ በማረሚያ ቤት የእስር ቆይታው በጥሩ ስነ ምግባር ታርሞና ታንፆ ወደ ማህበረሰቡ ቢቀላቀልም አንዳንድ የእጅ አመል ያለባቸው ግለሰቦች ደግሞ ከማረሚያ ቤት ወጥተው ወንጀል ቢፈጽሙም ከህግ እንደማያመልጡ የገለፀው የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ህብረተሰቡ ወንጀል እንዳይፈፀምበት ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግ ለፀጥታ አካላት ጥቆማ ከመስጠት ጀምሮ የሚያደርገውን ትብብር አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪውን አቅርቧል።
*
ዳዊት በላቸው የተባለው ተከሳሽ ከዚህ ቀደም የቅሚያ ወንጀሉን የፈፀመው በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ልዩ ቦታው አረንጓዴ ሰፈር ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ሰኔ 7 ቀን 2014 ዓ/ም ነበር።
ግለሰቡ የዋጋ ግምቱ 25 ሺህ ብር የሚያወጣ ሳምሰንግ M 32 ሞባይል ከግል ተበዳይ ላይ ቀምቶ ለማምለጥ ሲሞክር በፖሊስ አባላትና በህብረተሰቡ ትብብር እጅ ከፈንጅ ተይዞ አስፈላጊውን ምርመራ ከተጣራበት በኋላ አቃቤ ህግ ክስ መስርቶበት ጉዳዩን የተመለከተው የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ቀራንዮ ምድብ ወንጀል ችሎት በ3 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ አስተላልፎበት በማረሚያ ቤት መቆየቱን በክፍለ ከተማው ፖሊስ ዋና መምሪያ የቤተል አካባቢ ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል።
የ3 አመት የእስር ጊዜውን ጨርሶ ከማረሚያ ቤት የወጣውና ያልታረመው ይህ ግለሰብ በወጣ በ3ኛው ቀን በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ቤተል አካባቢ ከሚገኝ አንድ አፖርታማ ገብቶ 19 ሺህ ብር የሚገመቱ የተለያዩ ጫማዎችን ሰርቆ ለማምለጥ ሲሞክር ስራ ላይ በነበሩ የወንጀል መከላከል የፖሊስ አባላትና በህብረተሰቡ ትብብር እጅ ከፈንጅ መያዙን የቤተል አካባቢ ፖሊስ መምሪያ ገልጿል።
የተሰረቁት ንብረቶች በኤግዚቢት ተይዘው በግለሰቡ ላይ አስፈላጊው ምርመራ ከተጣራበት በኋላ አቃቤ ህግ ክስ መስርቶበታል፤ ጉዳዩን የተመለከተው የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ቀራንዮ ምድብ ፈጣን ወንጀል ችሎት ተከሳሹን ያስተምራል ሌሎች ወንጀል ፈፃሚዎችን ያስጠነቅቃል በማለት ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ/ም በዋለው ችሎት በፈፀመው ደጋጋሚ የወንጀል ድርጊት በ4 አመት ከ5 ወር ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ እንዳስተላለፈበት ፖሊስ ጠቅሷል፡፡
አብዛኛው ወንጀል ፈፃሚ በማረሚያ ቤት የእስር ቆይታው በጥሩ ስነ ምግባር ታርሞና ታንፆ ወደ ማህበረሰቡ ቢቀላቀልም አንዳንድ የእጅ አመል ያለባቸው ግለሰቦች ደግሞ ከማረሚያ ቤት ወጥተው ወንጀል ቢፈጽሙም ከህግ እንደማያመልጡ የገለፀው የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ህብረተሰቡ ወንጀል እንዳይፈፀምበት ተገቢውን ጥንቃቄ በማድረግ ለፀጥታ አካላት ጥቆማ ከመስጠት ጀምሮ የሚያደርገውን ትብብር አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪውን አቅርቧል።
*
2 months ago
በሳውላ ከተማ የ8ተኛ ክፍል ፈተና ለሰው ሊፈተኑ የገቡ መምህርና ተማሪ በፖሊስ ተያዙ
በሣውላ ከተማ ኩስቲ ቁጥር አንድ ትምህርት ቤት የ8ኛ ክፍል ፈተና ለተማሪ ሊፈተን ከተማሪ ጋር ተመሳስሎ የገባ መምህርና ተማሪው በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን የከተማው ፖሊስ ጽህፈት ቤት ገለፀ
ተማሪን ወክሎ ከመምህር ስነ ምግባር ባፈነገጠ ተግባር ተሳተፈ የተባለው ከቡልቂ ከተማ ሙሉ ፩ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመጣው መምህር እስራኤል አሰፋ የማንዴላ ርቀት ትምህርት ቤት ተማሪ የሆነው አብነት እንዳለን ክልላዊ ፈተና ሊፈትን ሲል በተደረገ የኮማንድ ፖስት ክትትል በቁጥጥር ስር ሊውሉ መቻላቸውን የገለጹት የከተማው ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ያዕቆብ በተላ ናቸው።
ፈተናውን ከኩረጃና ስርቆት የፀዳ ለማድረግ በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት የኮማንድ ፖስት አባላቱ ድርጊቱን በማጋለጥ ለፖሊስ ጥቆማ በመስጠታቸው ሊፈተን የገባው መምህርና ፈተናውን አሳልፎ ከሰጠው ተማሪ ጋር በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስረድተዋል።
የሣውላ ከተማ ፓሊስ አዛዥ ተወካይ ምክትል ኢንስፔክተር ሞገስ ሞኔ በበኩላቸው ተማሪውንና መምህሩን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን ጠቁመው በማዕከሉ እየተሰጠ ያለው ፈተና ፍጹም ሠላማዊ እና በተረጋጋ መንገድ መቀጠሉን ተናግረዋል።
በፖሊስ በቁጥጥር ስር የዋሉ ተጠርጣሪዎችን ምርመራ በአስቸኳይ አጣርቶ በአቃቤ በኩል ለፍርድ ቤት አቅርቦ ለማስወሰን እየሠራ መሆኑንም ምክትል ኢንስፔክተር ሞገስ ሞኔ ገልጸዋል።
Seledadotio
Seledadotio
በሣውላ ከተማ ኩስቲ ቁጥር አንድ ትምህርት ቤት የ8ኛ ክፍል ፈተና ለተማሪ ሊፈተን ከተማሪ ጋር ተመሳስሎ የገባ መምህርና ተማሪው በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን የከተማው ፖሊስ ጽህፈት ቤት ገለፀ
ተማሪን ወክሎ ከመምህር ስነ ምግባር ባፈነገጠ ተግባር ተሳተፈ የተባለው ከቡልቂ ከተማ ሙሉ ፩ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመጣው መምህር እስራኤል አሰፋ የማንዴላ ርቀት ትምህርት ቤት ተማሪ የሆነው አብነት እንዳለን ክልላዊ ፈተና ሊፈትን ሲል በተደረገ የኮማንድ ፖስት ክትትል በቁጥጥር ስር ሊውሉ መቻላቸውን የገለጹት የከተማው ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ያዕቆብ በተላ ናቸው።
ፈተናውን ከኩረጃና ስርቆት የፀዳ ለማድረግ በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት የኮማንድ ፖስት አባላቱ ድርጊቱን በማጋለጥ ለፖሊስ ጥቆማ በመስጠታቸው ሊፈተን የገባው መምህርና ፈተናውን አሳልፎ ከሰጠው ተማሪ ጋር በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስረድተዋል።
የሣውላ ከተማ ፓሊስ አዛዥ ተወካይ ምክትል ኢንስፔክተር ሞገስ ሞኔ በበኩላቸው ተማሪውንና መምህሩን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን ጠቁመው በማዕከሉ እየተሰጠ ያለው ፈተና ፍጹም ሠላማዊ እና በተረጋጋ መንገድ መቀጠሉን ተናግረዋል።
በፖሊስ በቁጥጥር ስር የዋሉ ተጠርጣሪዎችን ምርመራ በአስቸኳይ አጣርቶ በአቃቤ በኩል ለፍርድ ቤት አቅርቦ ለማስወሰን እየሠራ መሆኑንም ምክትል ኢንስፔክተር ሞገስ ሞኔ ገልጸዋል።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
2 months ago
በሣውላ ከተማ የ8ኛ ክፍል ፈተና ለተማሪ ሊፈተን የገባ መምህርና ተማሪው በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋሉ ።
በሣውላ ከተማ ኩስቲ ቁጥር አንድ ትምህርት ቤት የ8ኛ ክፍል ፈተና ለተማሪ ሊፈተን ከተማሪ ጋር ተመሳስሎ የገባ መምህርና ተማሪው በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን የከተማው ፖሊስ ጽህፈት ቤት ገለፀ
ተማሪን ወክሎ ከመምህር ስነ ምግባር ባፈነገጠ ተግባር ተሳተፈ የተባለው ከቡልቂ ከተማ ሙሉ ፩ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመጣው መምህር እስራኤል አሰፋ የማንዴላ ርቀት ትምህርት ቤት ተማሪ የሆነው አብነት እንዳለን ክልላዊ ፈተና ሊፈትን ሲል በተደረገ የኮማንድ ፖስት ክትትል በቁጥጥር ስር ሊውሉ መቻላቸውን የገለጹት የከተማው ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ያዕቆብ በተላ ናቸው።
ፈተናውን ከኩረጃና ስርቆት የፀዳ ለማድረግ በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት የኮማንድ ፖስት አባላቱ ድርጊቱን በማጋለጥ ለፖሊስ ጥቆማ በመስጠታቸው ሊፈተን የገባው መምህርና ፈተናውን አሳልፎ ከሰጠው ተማሪ ጋር በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስረድተዋል።
የሣውላ ከተማ ፓሊስ አዛዥ ተወካይ ምክትል ኢንስፔክተር ሞገስ ሞኔ በበኩላቸው ተማሪውንና መምህሩን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን ጠቁመው በማዕከሉ እየተሰጠ ያለው ፈተና ፍጹም ሠላማዊ እና በተረጋጋ መንገድ መቀጠሉን ተናግረዋል።
በፖሊስ በቁጥጥር ስር የዋሉ ተጠርጣሪዎችን ምርመራ በአስቸኳይ አጣርቶ በአቃቤ በኩል ለፍርድ ቤት አቅርቦ ለማስወሰን እየሠራ መሆኑንም ምክትል ኢንስፔክተር ሞገስ ሞኔ ገልጸዋል።
ምንጭ ሣውላ ከተማ መንግሥት ኮሙኒኬሽን
በሣውላ ከተማ ኩስቲ ቁጥር አንድ ትምህርት ቤት የ8ኛ ክፍል ፈተና ለተማሪ ሊፈተን ከተማሪ ጋር ተመሳስሎ የገባ መምህርና ተማሪው በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን የከተማው ፖሊስ ጽህፈት ቤት ገለፀ
ተማሪን ወክሎ ከመምህር ስነ ምግባር ባፈነገጠ ተግባር ተሳተፈ የተባለው ከቡልቂ ከተማ ሙሉ ፩ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የመጣው መምህር እስራኤል አሰፋ የማንዴላ ርቀት ትምህርት ቤት ተማሪ የሆነው አብነት እንዳለን ክልላዊ ፈተና ሊፈትን ሲል በተደረገ የኮማንድ ፖስት ክትትል በቁጥጥር ስር ሊውሉ መቻላቸውን የገለጹት የከተማው ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ያዕቆብ በተላ ናቸው።
ፈተናውን ከኩረጃና ስርቆት የፀዳ ለማድረግ በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት የኮማንድ ፖስት አባላቱ ድርጊቱን በማጋለጥ ለፖሊስ ጥቆማ በመስጠታቸው ሊፈተን የገባው መምህርና ፈተናውን አሳልፎ ከሰጠው ተማሪ ጋር በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስረድተዋል።
የሣውላ ከተማ ፓሊስ አዛዥ ተወካይ ምክትል ኢንስፔክተር ሞገስ ሞኔ በበኩላቸው ተማሪውንና መምህሩን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን ጠቁመው በማዕከሉ እየተሰጠ ያለው ፈተና ፍጹም ሠላማዊ እና በተረጋጋ መንገድ መቀጠሉን ተናግረዋል።
በፖሊስ በቁጥጥር ስር የዋሉ ተጠርጣሪዎችን ምርመራ በአስቸኳይ አጣርቶ በአቃቤ በኩል ለፍርድ ቤት አቅርቦ ለማስወሰን እየሠራ መሆኑንም ምክትል ኢንስፔክተር ሞገስ ሞኔ ገልጸዋል።
ምንጭ ሣውላ ከተማ መንግሥት ኮሙኒኬሽን
2 months ago
የአማራ ወጣቶች እንዲታገሉ አቶ አረጋ ከበደ ጥሪ አቀረቡ‼️
የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት አረጋ ከበደ ለአማራ ወጣቶች የትግል ጥሪ አቀረቡ፡፡ ‹‹አመራሮቹን ሄዳችሁ ታገሏቸው›› ሲሉ ተደምጠዋል፡፡
አረጋ ይህን ያሉት “ባህር ዳርን ወደ ላቀ ከፍታ ለመውሰድ የወጣቶች ሚና የማይተካ ነው” በሚሉ መሪ ቃላት ከባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ወጣቶች ጋር በተወያዩበት ወቅት ነው።
ከተማን ለነዋሪዎቿ ምቾት አልባ የሚያደርገው የአስተዳደር ብልሽት መሆኑን የጠቀሱት ርዕሰ መስተዳደሩ፣ አመራሩ በቀላሉ የሚገኝ፣ ቀላልና ውሳኔ መስጠት የሚችል መሆን እንዳለበት አጽንኦት የሰጡ ሲሆን በተለይም በሕዝብና በሀገር ላይ የሚፈጸሙ የሌብነት ድርጊቶችን ወጣቱ በግንባር ቀደምትነት ሊታገላቸው ይገባል ብለዋል።
“ሌብነት ውስጥ የመሬት ስርቆት፣ የግብር ስርቆት፣ የኮንትራት ስርቆት ውስጥ የሚገባ፣ ግን መስረቅ ሳያንስ የሚመራውን ደሃ ሕዝብ የጎሪጥ የሚያይ አመራር ላይ በጽናት መታገል ያስፈልጋል።” ሲሉ የባህር ዳር ወጣቶች በተሰበሰቡበት መልዕክት አስተላልፈዋል።
Seledadotio
Seledadotio
የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት አረጋ ከበደ ለአማራ ወጣቶች የትግል ጥሪ አቀረቡ፡፡ ‹‹አመራሮቹን ሄዳችሁ ታገሏቸው›› ሲሉ ተደምጠዋል፡፡
አረጋ ይህን ያሉት “ባህር ዳርን ወደ ላቀ ከፍታ ለመውሰድ የወጣቶች ሚና የማይተካ ነው” በሚሉ መሪ ቃላት ከባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ወጣቶች ጋር በተወያዩበት ወቅት ነው።
ከተማን ለነዋሪዎቿ ምቾት አልባ የሚያደርገው የአስተዳደር ብልሽት መሆኑን የጠቀሱት ርዕሰ መስተዳደሩ፣ አመራሩ በቀላሉ የሚገኝ፣ ቀላልና ውሳኔ መስጠት የሚችል መሆን እንዳለበት አጽንኦት የሰጡ ሲሆን በተለይም በሕዝብና በሀገር ላይ የሚፈጸሙ የሌብነት ድርጊቶችን ወጣቱ በግንባር ቀደምትነት ሊታገላቸው ይገባል ብለዋል።
“ሌብነት ውስጥ የመሬት ስርቆት፣ የግብር ስርቆት፣ የኮንትራት ስርቆት ውስጥ የሚገባ፣ ግን መስረቅ ሳያንስ የሚመራውን ደሃ ሕዝብ የጎሪጥ የሚያይ አመራር ላይ በጽናት መታገል ያስፈልጋል።” ሲሉ የባህር ዳር ወጣቶች በተሰበሰቡበት መልዕክት አስተላልፈዋል።
Seledadotio
Seledadotio
2 months ago
በቡድን በመደራጀትና ጨለማን ተገን በማድረግ የመሰረተ ልማት አውታሮች ላይ የስርቆት ወንጀል የፈፀሙ 5 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ።
የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው በልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 6 ራሺያ ካምፕ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው።
ተጠርጣሪዎቹ ጨለማን እንደምቹ አጋጣሚ በመጠቀም ከሌሊቱ 7 ሠዓት አካባቢ ለቴሌኮም አገልግሎት የሚውል ከመሬት ስር የተዘረጋ ኬብል በተለያዩ መቁረጫዎች በመቆራረጥ ይዘው ከአካባቢው ሊሰወሩ ሲሞክሩ በስራ ላይ በነበሩ የፖሊስ አባላትና የአካባቢ ጥበቃዎች ትብብር ከነ ኤግዚቢቱ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው መሆኑን በልደታ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ የመከኒሳ አካባቢ ፖሊስ መምሪያ ገልጿል።
ፖሊስ በተጠርጣሪዎቹ ላይ ተገቢውን ምርመራ የማስፋት ተግባር እያከናወነ መሆኑን ገልጾ በቀጣይ ክስ እንደሚያስመሠርትም ጠቁሟል።
በመሰረተ ልማት ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች ሀገርን ለከፍተኛ ኪሳራ የሚዳርግ ተግባር በመሆኑ ህብረተሰቡ መሰል የወንጀል ድርጊቶችን ሲመለከት እንደተለመደው በአካባቢው ለሚገኝ የጸጥታ ኃይል ጥቆማ መስጠት እንዳለበት የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ መልእክቱን አስተላልፏል።
Addis Ababa police
የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው በልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 6 ራሺያ ካምፕ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው።
ተጠርጣሪዎቹ ጨለማን እንደምቹ አጋጣሚ በመጠቀም ከሌሊቱ 7 ሠዓት አካባቢ ለቴሌኮም አገልግሎት የሚውል ከመሬት ስር የተዘረጋ ኬብል በተለያዩ መቁረጫዎች በመቆራረጥ ይዘው ከአካባቢው ሊሰወሩ ሲሞክሩ በስራ ላይ በነበሩ የፖሊስ አባላትና የአካባቢ ጥበቃዎች ትብብር ከነ ኤግዚቢቱ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው መሆኑን በልደታ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ የመከኒሳ አካባቢ ፖሊስ መምሪያ ገልጿል።
ፖሊስ በተጠርጣሪዎቹ ላይ ተገቢውን ምርመራ የማስፋት ተግባር እያከናወነ መሆኑን ገልጾ በቀጣይ ክስ እንደሚያስመሠርትም ጠቁሟል።
በመሰረተ ልማት ላይ የሚፈፀሙ ወንጀሎች ሀገርን ለከፍተኛ ኪሳራ የሚዳርግ ተግባር በመሆኑ ህብረተሰቡ መሰል የወንጀል ድርጊቶችን ሲመለከት እንደተለመደው በአካባቢው ለሚገኝ የጸጥታ ኃይል ጥቆማ መስጠት እንዳለበት የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ መልእክቱን አስተላልፏል።
Addis Ababa police
2 months ago
ናይጄሪያ ዜጎቿን ከደቡብ አፍሪካ እያስወጣች ነው
#ethiopia | በደቡብ አፍሪካ ፀረ-ስደተኛ ስሜቶች እያደጉ መምጣታቸውን ተከትሎ፣ ናይጄሪያ የተወሰኑ ዜጎቿን ወደ ሀገራቸው እየመለሰች ያለች አራተኛዋ የአፍሪካ ሀገር ሆናለች።
ሐሙስ ጠዋት ከጆሀንስበርግ የተነሳችና 268 ናይጄሪያውያንን የጫነች አውሮፕላን ሌጎስ ገብታለች። እነዚህ ተጓዦች በደቡብ አፍሪካ የሚገኘው የናይጄሪያ ቆንስላ ጽሕፈት ቤት ወደ ሀገራቸው ለመመለስ ከተመዘገቡት ወደ 1,000 ገደማ ሰዎች መካከል የተወሰኑት ናቸው።
አንዳንድ የቅስቀሳ ዘመቻ አድራጊዎች ሰነድ የሌላቸው ስደተኞች ሀገሪቱን ለቀው እንዲወጡ ካስቀመጡት የሰኔ 30 የጊዜ ገደብ ቀደም ብለው ጋና፣ ዚምባብዌ እና ማላዊ ዜጎቻቸውን የማስወጣት ሥራ አከናውነዋል።
በጆሀንስበርግ ዋና ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ፣ ከናይጄሪያውያን ተጓዦች አንዱ የሆነው ጀስቲን ከ1998 ጀምሮ በደቡብ አፍሪካ እንደኖረ ለቢቢሲ አፍሪካ ተናግሯል።
"እየወጣሁ ያለሁት እዚህ በሰጡን ቅድመ ሁኔታዎች ምክንያት ነው። እስከ ሰኔ 30 ድረስ ወይም ከዚያ በፊት መውጣት እንዳለብን እየነገሩን ነው። በተጨማሪም ሰዎችን፣ ወንድሞቻችንን እየተገደሉ ነው እና እኔ እዚህ ደኅንነት አይሰማኝም" ሲል ጀስቲን ተናግሯል።
ጀስቲን እርሱ ራሱ ቀደም ሲል የጥቃቱ ኢላማ ሆኖ እንደነበር ለቢቢሲ ገልጿል።
"በቅርቡ በአንድ ታክሲ ውስጥ ጥቃት ሰነዘሩብኝ። እኔም ዕቃዎቼን ጥዬ ሮጥኩ፤ ስልኬንና ሁሉንም ነገሬን ትቼ ነው ያመለጥኩት።"
"የተለያዩ ስሞችን እየሰጡ ይሰድቡናል፣ 'ይህችን ሀገር ለቃችሁ መውጣት አለባችሁ' ይሉናል። ልንለምናቸው ስንሞክር ደግሞ ማዋረድና መሳደብ ጀመሩ።"ብሏል፡፡
እሑድ ዕለት ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ ለተቃውሞ ሰልፎቹ ምላሽ ለመስጠት በቴሌቪዥን ባደረጉት ንግግር፣ ሕገ-ወጥ ስደትን ለመቆጣጠር የሚረዱ አዳዲስ ጠንካራ እርምጃዎችን ይፋ አድርገዋል።
እነዚህም እርምጃዎች ሰነድ የሌላቸውን ሠራተኞች የሚቀጥሩ አሰሪዎችን ማሰር፣ የስደት (የማባረር) ሂደቱን ለማፋጠን ልዩ ፍርድ ቤቶችን ማቋቋም እና የማንነት ስርቆትን ለመከላከል በሀገሪቱ ውስጥ የሚገኙትን ሁሉንም ሰዎች ባዮሜትሪክ (የአካል መገለጫ) መረጃ ቋት ማደራጀትን ያካትታሉ።
በተጨማሪም ፕሬዝዳንቱ ደቡብ አፍሪካውያን በሀገሪቱ ውስጥ በሕገ-ወጥ መንገድ ይኖራሉ ብለው የጠረጠሯቸውን ሰዎች ኢላማ በማድረግ ሕግን በገዛ እጃቸው እንዳይተረጉሙ አስጠንቅቀዋል ሲል የኢትዮ ኤፍ ኤም ዘገባ አስታውሷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | በደቡብ አፍሪካ ፀረ-ስደተኛ ስሜቶች እያደጉ መምጣታቸውን ተከትሎ፣ ናይጄሪያ የተወሰኑ ዜጎቿን ወደ ሀገራቸው እየመለሰች ያለች አራተኛዋ የአፍሪካ ሀገር ሆናለች።
ሐሙስ ጠዋት ከጆሀንስበርግ የተነሳችና 268 ናይጄሪያውያንን የጫነች አውሮፕላን ሌጎስ ገብታለች። እነዚህ ተጓዦች በደቡብ አፍሪካ የሚገኘው የናይጄሪያ ቆንስላ ጽሕፈት ቤት ወደ ሀገራቸው ለመመለስ ከተመዘገቡት ወደ 1,000 ገደማ ሰዎች መካከል የተወሰኑት ናቸው።
አንዳንድ የቅስቀሳ ዘመቻ አድራጊዎች ሰነድ የሌላቸው ስደተኞች ሀገሪቱን ለቀው እንዲወጡ ካስቀመጡት የሰኔ 30 የጊዜ ገደብ ቀደም ብለው ጋና፣ ዚምባብዌ እና ማላዊ ዜጎቻቸውን የማስወጣት ሥራ አከናውነዋል።
በጆሀንስበርግ ዋና ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ፣ ከናይጄሪያውያን ተጓዦች አንዱ የሆነው ጀስቲን ከ1998 ጀምሮ በደቡብ አፍሪካ እንደኖረ ለቢቢሲ አፍሪካ ተናግሯል።
"እየወጣሁ ያለሁት እዚህ በሰጡን ቅድመ ሁኔታዎች ምክንያት ነው። እስከ ሰኔ 30 ድረስ ወይም ከዚያ በፊት መውጣት እንዳለብን እየነገሩን ነው። በተጨማሪም ሰዎችን፣ ወንድሞቻችንን እየተገደሉ ነው እና እኔ እዚህ ደኅንነት አይሰማኝም" ሲል ጀስቲን ተናግሯል።
ጀስቲን እርሱ ራሱ ቀደም ሲል የጥቃቱ ኢላማ ሆኖ እንደነበር ለቢቢሲ ገልጿል።
"በቅርቡ በአንድ ታክሲ ውስጥ ጥቃት ሰነዘሩብኝ። እኔም ዕቃዎቼን ጥዬ ሮጥኩ፤ ስልኬንና ሁሉንም ነገሬን ትቼ ነው ያመለጥኩት።"
"የተለያዩ ስሞችን እየሰጡ ይሰድቡናል፣ 'ይህችን ሀገር ለቃችሁ መውጣት አለባችሁ' ይሉናል። ልንለምናቸው ስንሞክር ደግሞ ማዋረድና መሳደብ ጀመሩ።"ብሏል፡፡
እሑድ ዕለት ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ ለተቃውሞ ሰልፎቹ ምላሽ ለመስጠት በቴሌቪዥን ባደረጉት ንግግር፣ ሕገ-ወጥ ስደትን ለመቆጣጠር የሚረዱ አዳዲስ ጠንካራ እርምጃዎችን ይፋ አድርገዋል።
እነዚህም እርምጃዎች ሰነድ የሌላቸውን ሠራተኞች የሚቀጥሩ አሰሪዎችን ማሰር፣ የስደት (የማባረር) ሂደቱን ለማፋጠን ልዩ ፍርድ ቤቶችን ማቋቋም እና የማንነት ስርቆትን ለመከላከል በሀገሪቱ ውስጥ የሚገኙትን ሁሉንም ሰዎች ባዮሜትሪክ (የአካል መገለጫ) መረጃ ቋት ማደራጀትን ያካትታሉ።
በተጨማሪም ፕሬዝዳንቱ ደቡብ አፍሪካውያን በሀገሪቱ ውስጥ በሕገ-ወጥ መንገድ ይኖራሉ ብለው የጠረጠሯቸውን ሰዎች ኢላማ በማድረግ ሕግን በገዛ እጃቸው እንዳይተረጉሙ አስጠንቅቀዋል ሲል የኢትዮ ኤፍ ኤም ዘገባ አስታውሷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
Sponsored by
Surafel
2 months ago
አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ በአዲስ አበባ ከተማ መሰጠት ተጀመረ
#ethiopia | ETH የሚል ዓለም አቀፋዊ ኮድ የያዘዉ አዲሱ ሰሌዳ በአዲስ አበባ ሰሌዳ ለመዉሰድ ተመዝግበው እየተጠባበቁ ባሉ አዲስ ተሽከርካሪዎች ላይ ከሰኔ 4 ጀምሮ ተግባራዊ መደረግ መጀመሩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአሽከርካሪ እና ተሽከርካሪ ቁጥጥር ባለስልጣን አስታውቋል ።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዘገየ በላይነህ አዲሱ ሰሌዳ ሀገራዊ ይዘት ያለዉ ፣ ፎርጂድ የማይሰራ ፣የሀብት ብክነትን የሚቀነስ ፣ለህግ ማስከበር የሚመች ፣ስርቆትንና ህገወጥ ዝዉዉርን ለመከላከል የሚረዳ መሆኑን መናገራቸዉን ብስራት ሬዲዮ ሠምቷል።
የመጀመሪያዉ ሰሌዳ ባለስልጣኑ ካሉት 11 ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቶች አንዱ በሆነዉ የየካ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት መሰጠቱ ተገልጿል ።
በብዙሃን ትራንስፓርት እና የግል ተሽከርካሪዎች የሰሌዳ ዋጋዉ ላይ ልዩነት እንደሚኖረዉ በትራንስፖርትና ሎጂስቲክ ሚኒስቴር የትራንስፖርት አገልግሎት ዘርፍ ቁጥጥር አማካሪ አቶ አሰፋ ሀዲስ ተናግረዋል ።
አዲሱ ሰሌዳ ተሽከርካሪዉ እስኪወገድ ድረስ የሚያገለግል መሆኑን የገለፀዉ ባለስልጣኑ ከ800 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎች መኖራቸዉንና ሰሌዳዉ ተወስዶ መቼ ይጠናቀቃል የሚለዉ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሚወሰን መሆኑን ገልጿል ።
በአዲስ አበባ ከተማ የተወሰነ ከተሄደበት በኃላ በክልሎችም የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክ ሚኒስቴር በሚያስቀምጣቸው የጊዜ እቅድ ሰሌዳዉን የመቀየር ሂደቱ እንደሚተገበር ተገልጿል ያለው ብስራት ኤፍ ኤም ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | ETH የሚል ዓለም አቀፋዊ ኮድ የያዘዉ አዲሱ ሰሌዳ በአዲስ አበባ ሰሌዳ ለመዉሰድ ተመዝግበው እየተጠባበቁ ባሉ አዲስ ተሽከርካሪዎች ላይ ከሰኔ 4 ጀምሮ ተግባራዊ መደረግ መጀመሩ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአሽከርካሪ እና ተሽከርካሪ ቁጥጥር ባለስልጣን አስታውቋል ።
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዘገየ በላይነህ አዲሱ ሰሌዳ ሀገራዊ ይዘት ያለዉ ፣ ፎርጂድ የማይሰራ ፣የሀብት ብክነትን የሚቀነስ ፣ለህግ ማስከበር የሚመች ፣ስርቆትንና ህገወጥ ዝዉዉርን ለመከላከል የሚረዳ መሆኑን መናገራቸዉን ብስራት ሬዲዮ ሠምቷል።
የመጀመሪያዉ ሰሌዳ ባለስልጣኑ ካሉት 11 ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቶች አንዱ በሆነዉ የየካ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት መሰጠቱ ተገልጿል ።
በብዙሃን ትራንስፓርት እና የግል ተሽከርካሪዎች የሰሌዳ ዋጋዉ ላይ ልዩነት እንደሚኖረዉ በትራንስፖርትና ሎጂስቲክ ሚኒስቴር የትራንስፖርት አገልግሎት ዘርፍ ቁጥጥር አማካሪ አቶ አሰፋ ሀዲስ ተናግረዋል ።
አዲሱ ሰሌዳ ተሽከርካሪዉ እስኪወገድ ድረስ የሚያገለግል መሆኑን የገለፀዉ ባለስልጣኑ ከ800 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎች መኖራቸዉንና ሰሌዳዉ ተወስዶ መቼ ይጠናቀቃል የሚለዉ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሚወሰን መሆኑን ገልጿል ።
በአዲስ አበባ ከተማ የተወሰነ ከተሄደበት በኃላ በክልሎችም የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክ ሚኒስቴር በሚያስቀምጣቸው የጊዜ እቅድ ሰሌዳዉን የመቀየር ሂደቱ እንደሚተገበር ተገልጿል ያለው ብስራት ኤፍ ኤም ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
2 months ago
7ኛው ብሔራዊ ምርጫ ሀገራዊ መግባባት ሊያመጣ አይችልም ሲል ኦፌኮ ገለጸ፤ ሁሉን አቀፍ ውይይት እንዲደረግም ጥሪ አቀረበ
የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የተካሄደውን 7ኛውን ሀገር አቀፍ ምርጫ በተመለከተ ባወጣው ይፋዊ መግለጫ፣ ሂደቱ በከፍተኛ መዋቅራዊ ግድፈቶች የተሞላና በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን የመምረጥ መብት የነፈገ በመሆኑ ለሀገሪቱ ዘላቂ ሰላምና ዲሞክራሲያዊ አስተዳደር ሊያመጣ አይችልም ሲል በጽኑ ተቃወመ።
ፓርቲው ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ፣ ምርጫው ከመካሄዱ በፊት ተቃዋሚ ኃይሎች ያቀረቧቸው እንደ ግጭቶች በአስቸኳይ መቆም፣ የፖለቲካ እስረኞች መፈታት፣ የሚዲያና ሲቪል ማህበረሰብ አፋኝ ህጎች መሰረዝና ገለልተኛ የምርጫ ቦርድ መቋቋም የመሳሰሉ መሰረታዊ ቅድመ ሁኔታዎች በመንግስት በኩል ቸል መባላቸውን ገልጿል።
በዚህም ምክንያት ሂደቱ "ለይስሙላ የተደረገ የፖለቲካ ድራማ" ነው ያለው ኦፌኮ፣ ሕጉን ለማክበር ሲል ብቻ በጥቂት እጩዎች እጅግ የተገደበ ተምሳሌታዊ ተሳትፎ ማድረጉን አስታውቋል።
በኦሮሚያ እና በአማራ ክልሎች ባሉ አውዳሚ ጦርነቶች ምክንያት በሰፊው የገጠርና የከተማ ዳርቻዎች ምርጫ ማካሄድ ባለመቻሉ ሂደቱ በከፍተኛ ወታደራዊ ጥበቃ ስር ባሉ ዋና ዋና ከተሞች ብቻ መገደቡንና በትግራይ ክልል ደግሞ ሙሉ በሙሉ አለመካሄዱን ፓርቲው ጠቅሷል።
ምርጫ በተካሄደባቸው አካባቢዎችም ቢሆን፦
* የምርጫ አስፈፃሚዎች ግልጽ አድሎአዊነት መታየቱ፣
* በመራጮች ላይ ማስፈራራትና በተቃዋሚ ተወካዮች ላይ ትንኮሳና ከጣቢያ የማስወጣት ተግባር መፈጸሙ፣
* የሀገር ውስጥ ታዛቢዎች ስልታዊ በሆነ መንገድ መከልከላቸው፣ ሂደቱን ታማኝነት ያጣ እንዳደረገው ገልጿል።
የዓለም አቀፍ ታዛቢዎችን ሚና በተመለከተም ኦፌኮ ጠንካራ ትችት ሰንዝሯል።
የአፍሪካ ህብረት እና የኢጋድ ልዑካን ከ52 ሺህ በላይ የምርጫ ጣቢያዎች ውስጥ ደህንነታቸው በተጠበቁ 208 (0.4%) ጣቢያዎች ላይ ብቻ ተሰማርተው ያወጡትን "ሰላማዊና ግልጽነት" ሪፖርት የምርጫ ዕለት ቱሪዝም ሲል አጣጥሎታል።
የአውሮፓ ህብረት (EU) በበኩሉ በምድር ላይ ታዛቢ ሳይመድብ በርቀት የሰጠውን በጎ መግለጫ የዲፕሎማሲ ማባበያ" (Diplomatic appeasement) እና አምባገነናዊነትን የሚያጸና ነው ብሎታል።
በማግለልና በመዋቅራዊ ስርቆት የተከናወነ ምርጫ የሀገሪቱን ጥልቅ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራት ሊጠግን እንዲሁም ለገዥው ፓርቲ ዓለም አቀፍ አመኔታ ሊያስገኝ አይችልም ያለው ኦፌኮ፣ ብቸኛው አዋጭ መንገድ በአሁኑ ወቅት ከመንግስት ጋር በጦርነት ላይ ያሉ ታጣቂ ኃይሎችንና ሁሉንም የፖለቲካ ወገኖች ያካተተ እውነተኛና ሁሉን አቀፍ የፖለቲካ ውይይትማድረግ ብቻ ነው ብሏል።
በማጠቃለያውም ፓርቲው ሶስት ዋና ዋና አስቸኳይ ጥሪዎችን አቅርቧል፦
1. ለመንግስት፦
ልዩነቶችን በኃይል የመፍታት ስልት እንደማይሰራ ተገንዝቦ፣ ግጭቶች በዓለም አቀፍ ክትትል በአስቸኳይ እንዲቆሙ፣ የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱና ለሀገራዊ ውይይት ምቹ ሁኔታ እንዲፈጥር
2. ለኢትዮጵያ ሕዝቦች፦
መሰረታዊ ችግሮች በዚህ ምርጫ እንደማይፈቱ በመረዳት፣ ለእውነተኛ ራስን በራስ ማስተዳደርና ሕብረ-ብሔራዊ ፌዴራሊዝም በሚደረገው ሰላማዊ ትግል ላይ እንዲጸኑ
3. ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ
ሂደቱ ነፃና ፍትሃዊ እንዳልነበር አውቆ፣ መንግስት ሐቀኛና ሁሉን አቀፍ ሀገራዊ ውይይት እንዲያካሂድ ትርጉም ያለው ጫና እንዲያሳድር ጠይቋል።
ኦፌኮ ዴሞክራሲያዊትና ሰላማዊት ፌዴራል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ትግሉን በቁርጠኝነት እንደሚቀጥል በመግለጫው ማብቂያ ላይ አስታውቋል።
የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የተካሄደውን 7ኛውን ሀገር አቀፍ ምርጫ በተመለከተ ባወጣው ይፋዊ መግለጫ፣ ሂደቱ በከፍተኛ መዋቅራዊ ግድፈቶች የተሞላና በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን የመምረጥ መብት የነፈገ በመሆኑ ለሀገሪቱ ዘላቂ ሰላምና ዲሞክራሲያዊ አስተዳደር ሊያመጣ አይችልም ሲል በጽኑ ተቃወመ።
ፓርቲው ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ፣ ምርጫው ከመካሄዱ በፊት ተቃዋሚ ኃይሎች ያቀረቧቸው እንደ ግጭቶች በአስቸኳይ መቆም፣ የፖለቲካ እስረኞች መፈታት፣ የሚዲያና ሲቪል ማህበረሰብ አፋኝ ህጎች መሰረዝና ገለልተኛ የምርጫ ቦርድ መቋቋም የመሳሰሉ መሰረታዊ ቅድመ ሁኔታዎች በመንግስት በኩል ቸል መባላቸውን ገልጿል።
በዚህም ምክንያት ሂደቱ "ለይስሙላ የተደረገ የፖለቲካ ድራማ" ነው ያለው ኦፌኮ፣ ሕጉን ለማክበር ሲል ብቻ በጥቂት እጩዎች እጅግ የተገደበ ተምሳሌታዊ ተሳትፎ ማድረጉን አስታውቋል።
በኦሮሚያ እና በአማራ ክልሎች ባሉ አውዳሚ ጦርነቶች ምክንያት በሰፊው የገጠርና የከተማ ዳርቻዎች ምርጫ ማካሄድ ባለመቻሉ ሂደቱ በከፍተኛ ወታደራዊ ጥበቃ ስር ባሉ ዋና ዋና ከተሞች ብቻ መገደቡንና በትግራይ ክልል ደግሞ ሙሉ በሙሉ አለመካሄዱን ፓርቲው ጠቅሷል።
ምርጫ በተካሄደባቸው አካባቢዎችም ቢሆን፦
* የምርጫ አስፈፃሚዎች ግልጽ አድሎአዊነት መታየቱ፣
* በመራጮች ላይ ማስፈራራትና በተቃዋሚ ተወካዮች ላይ ትንኮሳና ከጣቢያ የማስወጣት ተግባር መፈጸሙ፣
* የሀገር ውስጥ ታዛቢዎች ስልታዊ በሆነ መንገድ መከልከላቸው፣ ሂደቱን ታማኝነት ያጣ እንዳደረገው ገልጿል።
የዓለም አቀፍ ታዛቢዎችን ሚና በተመለከተም ኦፌኮ ጠንካራ ትችት ሰንዝሯል።
የአፍሪካ ህብረት እና የኢጋድ ልዑካን ከ52 ሺህ በላይ የምርጫ ጣቢያዎች ውስጥ ደህንነታቸው በተጠበቁ 208 (0.4%) ጣቢያዎች ላይ ብቻ ተሰማርተው ያወጡትን "ሰላማዊና ግልጽነት" ሪፖርት የምርጫ ዕለት ቱሪዝም ሲል አጣጥሎታል።
የአውሮፓ ህብረት (EU) በበኩሉ በምድር ላይ ታዛቢ ሳይመድብ በርቀት የሰጠውን በጎ መግለጫ የዲፕሎማሲ ማባበያ" (Diplomatic appeasement) እና አምባገነናዊነትን የሚያጸና ነው ብሎታል።
በማግለልና በመዋቅራዊ ስርቆት የተከናወነ ምርጫ የሀገሪቱን ጥልቅ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ስብራት ሊጠግን እንዲሁም ለገዥው ፓርቲ ዓለም አቀፍ አመኔታ ሊያስገኝ አይችልም ያለው ኦፌኮ፣ ብቸኛው አዋጭ መንገድ በአሁኑ ወቅት ከመንግስት ጋር በጦርነት ላይ ያሉ ታጣቂ ኃይሎችንና ሁሉንም የፖለቲካ ወገኖች ያካተተ እውነተኛና ሁሉን አቀፍ የፖለቲካ ውይይትማድረግ ብቻ ነው ብሏል።
በማጠቃለያውም ፓርቲው ሶስት ዋና ዋና አስቸኳይ ጥሪዎችን አቅርቧል፦
1. ለመንግስት፦
ልዩነቶችን በኃይል የመፍታት ስልት እንደማይሰራ ተገንዝቦ፣ ግጭቶች በዓለም አቀፍ ክትትል በአስቸኳይ እንዲቆሙ፣ የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱና ለሀገራዊ ውይይት ምቹ ሁኔታ እንዲፈጥር
2. ለኢትዮጵያ ሕዝቦች፦
መሰረታዊ ችግሮች በዚህ ምርጫ እንደማይፈቱ በመረዳት፣ ለእውነተኛ ራስን በራስ ማስተዳደርና ሕብረ-ብሔራዊ ፌዴራሊዝም በሚደረገው ሰላማዊ ትግል ላይ እንዲጸኑ
3. ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ
ሂደቱ ነፃና ፍትሃዊ እንዳልነበር አውቆ፣ መንግስት ሐቀኛና ሁሉን አቀፍ ሀገራዊ ውይይት እንዲያካሂድ ትርጉም ያለው ጫና እንዲያሳድር ጠይቋል።
ኦፌኮ ዴሞክራሲያዊትና ሰላማዊት ፌዴራል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ትግሉን በቁርጠኝነት እንደሚቀጥል በመግለጫው ማብቂያ ላይ አስታውቋል።
Comments