21 days ago
ደም መፍሰስን የሚቀንስ የሌዘር ቀዶ ሕክምና ቴክኖሎጂ በአራዳ የህክምና ማዕከል በይፋ ተጀመረ!
#fastmereja :በአዲስ አበባ ከተማ ለሁለት አስርት ዓመታት የሕክምና አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው የአራዳ ሕክምና ማዕከል (አራዳ ጊዮርጊስ ጠቅላላ ሆስፒታል)፣ 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በዛሬው ዕለት በተለያዩ ኩነቶች አክብሯል።
ማዕከሉ በምስረታ በዓሉ ዕለት በዘርፉ ያለውን የአገልግሎት እጥረት ይቀርፋል የተባለለትን የጆሮ፣ አፍንጫ እና ጉሮሮ (ENT) ከፍተኛ ስፔሻላይዝድ ክሊኒክ በዛሬዉ እለት በይፋ መርቆ አገልግሎት አስጀምሯል።
የማዕከሉ መስራችና ስራ አስኪያጅ አቶ ነጋ ገብረሚካኤል በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደገለጹት፤ ተቋሙ በ1998 ዓ.ም በትንሽ ክሊኒክ ደረጃ ጉዞውን የጀመረ ቢሆንም፣ ባለፉት 20 ዓመታት ውስጥ ከ400 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሕክምና አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ መቻሉን ገልፀዋል።
ተቋሙ ከሕክምናው ጎን ለጎን በጤና ባለሙያዎች ስልጠና ላይ በመሰማራትም እስካሁን ከ3,500 በላይ ነርሶችንና የላቦራቶሪ ባለሙያዎችን አሰልጥኖ ለሀገሪቱ የጤና ዘርፍ ማበርከቱ ተገልጿል።
ዛሬ በይፋ የተመረቀው ከፍተኛ የጆሮ፣ አፍንጫ እና ጉሮሮ (ENT) ስፔሻላይዝድ ክሊኒክ፣ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ይህን ልዩ አገልግሎት ከሚሰጡ ጥቂት (አምስት) ተቋማት አንዱ እንዲሆን አድርጎታል፡፡
ክሊኒኩ በዘርፉ አዲስ የሆነውን የሌዘር ማሽን (Laser Machine) በመጠቀም ደም መፍሰስን የሚቀንስ እና ስቃይ የሌለው ቀዶ ሕክምና መስጠት የጀመረ ሲሆን፣ በተጨማሪም አዲስ ለተወለዱ ሕፃናት የመስማት ችሎታ ምርመራ (Audiology) እና የስፒች ቴራፒ አገልግሎቶችን ያካተተ መሆኑ ተጠቁሟል።
ማዕከሉ የ20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በማስመልከት በርካታ የማኅበራዊ ኃላፊነት ተግባራትን እያከናወነ የሚገኝ ሲሆን በመንግሥት ሆስፒታሎች ረጅም የቀጠሮ ዝርዝር ውስጥ የነበሩ 20 ሕፃናትን በነፃ ቀዶ ጥገና ማድረግ፣ ለአረጋውያን ዘመናዊ የጆሮ ምርመራ (Endoscopy and Audiometry) በነፃ መስጠት፣ እንዲሁም ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሲቪል ሰርቪስ ሠራተኞች ነፃ የ ENT ምርመራ ማከናወን ይገኙበታል።
በተጨማሪም ማዕከሉ በቀጣይ አገልግሎቱን ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል (Digital Health) የመቀየር ራዕይ የሰነቀ ሲሆን ለኩላሊት እጥበት (Dialysis) እና ለካንሰር ሕክምና የሚውል ቦታ ከመንግሥት ጋር በመነጋገር ላይ መሆናቸውንና አገልግሎቶቹን በቅርቡ ለመጀመር ማቀዳቸውን በእለቱ ተገልጿል።
በመጨረሻም ላለፉት 20 ዓመታት በማዕከሉ ነፃ ሕክምና ሲደረግላቸው የቆዩ ታካሚዎች ምስጋናቸዉን ያቀረቡ ሲሆን፣ማዕከሉ ከሕክምና አገልግሎቱ ጎን ለጎን ከዩኤስ ኤይድ (USAID) ጋር በመተባበር በኤች አይ ቪ (HIV) ምርመራና በበጎ አድራጎት ስራዎች ላይ በስፋት ሲሳተፍ መቆየቱ ተገልጿል።
#fastmereja :በአዲስ አበባ ከተማ ለሁለት አስርት ዓመታት የሕክምና አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው የአራዳ ሕክምና ማዕከል (አራዳ ጊዮርጊስ ጠቅላላ ሆስፒታል)፣ 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በዛሬው ዕለት በተለያዩ ኩነቶች አክብሯል።
ማዕከሉ በምስረታ በዓሉ ዕለት በዘርፉ ያለውን የአገልግሎት እጥረት ይቀርፋል የተባለለትን የጆሮ፣ አፍንጫ እና ጉሮሮ (ENT) ከፍተኛ ስፔሻላይዝድ ክሊኒክ በዛሬዉ እለት በይፋ መርቆ አገልግሎት አስጀምሯል።
የማዕከሉ መስራችና ስራ አስኪያጅ አቶ ነጋ ገብረሚካኤል በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደገለጹት፤ ተቋሙ በ1998 ዓ.ም በትንሽ ክሊኒክ ደረጃ ጉዞውን የጀመረ ቢሆንም፣ ባለፉት 20 ዓመታት ውስጥ ከ400 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሕክምና አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ መቻሉን ገልፀዋል።
ተቋሙ ከሕክምናው ጎን ለጎን በጤና ባለሙያዎች ስልጠና ላይ በመሰማራትም እስካሁን ከ3,500 በላይ ነርሶችንና የላቦራቶሪ ባለሙያዎችን አሰልጥኖ ለሀገሪቱ የጤና ዘርፍ ማበርከቱ ተገልጿል።
ዛሬ በይፋ የተመረቀው ከፍተኛ የጆሮ፣ አፍንጫ እና ጉሮሮ (ENT) ስፔሻላይዝድ ክሊኒክ፣ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ይህን ልዩ አገልግሎት ከሚሰጡ ጥቂት (አምስት) ተቋማት አንዱ እንዲሆን አድርጎታል፡፡
ክሊኒኩ በዘርፉ አዲስ የሆነውን የሌዘር ማሽን (Laser Machine) በመጠቀም ደም መፍሰስን የሚቀንስ እና ስቃይ የሌለው ቀዶ ሕክምና መስጠት የጀመረ ሲሆን፣ በተጨማሪም አዲስ ለተወለዱ ሕፃናት የመስማት ችሎታ ምርመራ (Audiology) እና የስፒች ቴራፒ አገልግሎቶችን ያካተተ መሆኑ ተጠቁሟል።
ማዕከሉ የ20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በማስመልከት በርካታ የማኅበራዊ ኃላፊነት ተግባራትን እያከናወነ የሚገኝ ሲሆን በመንግሥት ሆስፒታሎች ረጅም የቀጠሮ ዝርዝር ውስጥ የነበሩ 20 ሕፃናትን በነፃ ቀዶ ጥገና ማድረግ፣ ለአረጋውያን ዘመናዊ የጆሮ ምርመራ (Endoscopy and Audiometry) በነፃ መስጠት፣ እንዲሁም ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሲቪል ሰርቪስ ሠራተኞች ነፃ የ ENT ምርመራ ማከናወን ይገኙበታል።
በተጨማሪም ማዕከሉ በቀጣይ አገልግሎቱን ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል (Digital Health) የመቀየር ራዕይ የሰነቀ ሲሆን ለኩላሊት እጥበት (Dialysis) እና ለካንሰር ሕክምና የሚውል ቦታ ከመንግሥት ጋር በመነጋገር ላይ መሆናቸውንና አገልግሎቶቹን በቅርቡ ለመጀመር ማቀዳቸውን በእለቱ ተገልጿል።
በመጨረሻም ላለፉት 20 ዓመታት በማዕከሉ ነፃ ሕክምና ሲደረግላቸው የቆዩ ታካሚዎች ምስጋናቸዉን ያቀረቡ ሲሆን፣ማዕከሉ ከሕክምና አገልግሎቱ ጎን ለጎን ከዩኤስ ኤይድ (USAID) ጋር በመተባበር በኤች አይ ቪ (HIV) ምርመራና በበጎ አድራጎት ስራዎች ላይ በስፋት ሲሳተፍ መቆየቱ ተገልጿል።
29 days ago
ዛምቢያ የአሜሪካ ጥያቄ ውድቅ አደረገች
#fastmereja I ዛምቢያ ከአሜሪካ የሚቀርብላትን የ2 ቢሊዮን ዶላር የጤና ድጋፍ ስምምነት፣ አገሪቱ ካሏት ስልታዊ የማዕድን ሀብቶች ጋር ለማያያዝ የቀረበውን ቅድመ ሁኔታ ውድቅ ማድረጓን አስታወቀች። የዛምቢያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሙላምቦ ሃይምቤ እንደገለጹት፣ የጤና እና የማዕድን ስምምነቶች ለየብቻቸው ሊደራደሩ ይገባል እንጂ አንዱ ለሌላው ማስገደጃ መሆን የለባቸውም።
በሉሳካ እና በዋሽንግተን መካከል የተፈጠረው ይኸው አለመግባባት፣ የአሜሪካ መንግስት የአምስት ዓመት የጤና ድጋፍ ለማድረግ የዛምቢያን የኮባልት እና የኮፐር ማዕድናት ለአሜሪካ ኩባንያዎች ቅድሚያ እንዲሰጥ መጠየቁን ተከትሎ የመጣ ነው። ዛምቢያ ይህ ጥያቄ የአገሪቱን ሉዓላዊነት የሚጋፋ እና ለዜጎች የግል መረጃ ደህንነት አስጊ የሆኑ ድንጋጌዎችን የያዘ ነው በማለት ተቃውማለች።
አሜሪካ በአሁኑ ወቅት የውጭ ዕርዳታ አሰጣጥ መዋቅሯን በመቀየር፣ እንደ USAID ያሉ ተቋማትን በማፍረስ እና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር የነበራትን ግንኙነት በመቀነስ፣ ከአገራት ጋር በቀጥታ የጥቅም ልውውጥ ላይ ያተኮሩ ስምምነቶችን እያደረገች ትገኛለች። ዛምቢያ ይህንን “የጥቅም ልውውጥ” አካሄድ የተቃወመች የቅርብ ጊዜ የአፍሪካ አገር ስትሆን፣ ከዚህ ቀደም ጋና እና ዚምባብዌ ተመሳሳይ የውሂብ ደህንነት ስጋቶችን በማንሳት የአሜሪካን የጤና ስምምነቶች ውድቅ ማድረጋቸው ይታወሳል።
አገሪቱ በአፍሪካ ሁለተኛዋ ትልቅ የኮፐር አምራች እንደመሆኗ፣ የማዕድን ሀብቷ ለአለም አቀፍ የቴክኖሎጂ እና የኢነርጂ ኢንዱስትሪዎች እጅግ አስፈላጊ መሆኑ የውጥረቱ ዋነኛ መንስኤ ሆኗል። አሜሪካ በበኩሏ ይህ አዲስ አካሄድ አገራት በዕርዳታ ላይ ያላቸውን ጥገኝነት ለመቀነስ እና የአሜሪካን ስልታዊ ጥቅም ለማስከበር ያለመ መሆኑን ትገልጻለች።
#fastmereja I ዛምቢያ ከአሜሪካ የሚቀርብላትን የ2 ቢሊዮን ዶላር የጤና ድጋፍ ስምምነት፣ አገሪቱ ካሏት ስልታዊ የማዕድን ሀብቶች ጋር ለማያያዝ የቀረበውን ቅድመ ሁኔታ ውድቅ ማድረጓን አስታወቀች። የዛምቢያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሙላምቦ ሃይምቤ እንደገለጹት፣ የጤና እና የማዕድን ስምምነቶች ለየብቻቸው ሊደራደሩ ይገባል እንጂ አንዱ ለሌላው ማስገደጃ መሆን የለባቸውም።
በሉሳካ እና በዋሽንግተን መካከል የተፈጠረው ይኸው አለመግባባት፣ የአሜሪካ መንግስት የአምስት ዓመት የጤና ድጋፍ ለማድረግ የዛምቢያን የኮባልት እና የኮፐር ማዕድናት ለአሜሪካ ኩባንያዎች ቅድሚያ እንዲሰጥ መጠየቁን ተከትሎ የመጣ ነው። ዛምቢያ ይህ ጥያቄ የአገሪቱን ሉዓላዊነት የሚጋፋ እና ለዜጎች የግል መረጃ ደህንነት አስጊ የሆኑ ድንጋጌዎችን የያዘ ነው በማለት ተቃውማለች።
አሜሪካ በአሁኑ ወቅት የውጭ ዕርዳታ አሰጣጥ መዋቅሯን በመቀየር፣ እንደ USAID ያሉ ተቋማትን በማፍረስ እና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር የነበራትን ግንኙነት በመቀነስ፣ ከአገራት ጋር በቀጥታ የጥቅም ልውውጥ ላይ ያተኮሩ ስምምነቶችን እያደረገች ትገኛለች። ዛምቢያ ይህንን “የጥቅም ልውውጥ” አካሄድ የተቃወመች የቅርብ ጊዜ የአፍሪካ አገር ስትሆን፣ ከዚህ ቀደም ጋና እና ዚምባብዌ ተመሳሳይ የውሂብ ደህንነት ስጋቶችን በማንሳት የአሜሪካን የጤና ስምምነቶች ውድቅ ማድረጋቸው ይታወሳል።
አገሪቱ በአፍሪካ ሁለተኛዋ ትልቅ የኮፐር አምራች እንደመሆኗ፣ የማዕድን ሀብቷ ለአለም አቀፍ የቴክኖሎጂ እና የኢነርጂ ኢንዱስትሪዎች እጅግ አስፈላጊ መሆኑ የውጥረቱ ዋነኛ መንስኤ ሆኗል። አሜሪካ በበኩሏ ይህ አዲስ አካሄድ አገራት በዕርዳታ ላይ ያላቸውን ጥገኝነት ለመቀነስ እና የአሜሪካን ስልታዊ ጥቅም ለማስከበር ያለመ መሆኑን ትገልጻለች።
1 month ago
አሜሪካ የኢትዮጵያን እርዳታ ልታቆም ነው! የተፈናቃዮች ዕጣ ፈንታ ምን ይሆን? #ethiopia #ethiopianews #humanitariancrisis #usaid #usforeignpolicy
4 months ago
ኬንያ ለውጥ ያመጣል የተባለለትን የኤችአይቪ መከላከያ መድኃኒት በመጋቢት ወር ማሰራጨት ልትጀምር ነው።
ኬንያ በዓመት ሁለት ጊዜ ብቻ በመወሰድ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ /ከ99 በመቶ በላይ/ መከላከያ የሚሰጠውን አዲስ የኤችአይቪ መከላከያ መድኃኒት በመጋቢት ወር ላይ ማሰራጨት ትጀምራለች።
በጊሊያድ ሳይንሰስ ኩባንያ የሚመረተው ሌናካፓቪር የተሰኘው መድኃኒት፣ የኤችአይቪ ቫይረስ የመተላለፍ እድልን ከ99.9 በመቶ በላይ ይቀንሳል።
ኬንያ ከግሎባል ፈንድ ጋር ባደረገችው ስምምነት መሰረት የመጀመሪያውን ዙር 21 ሺህ የመድኃኒት መጠን ተረክባለች።
የጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ አደን ዱዋሌ፤ የመጀመሪያው ምዕራፍ 15 ግዛቶችን በማካተት በመጋቢት ወር መጀመሪያ ላይ ይጀምራል ሲሉ ያስታወቁ ሲሆን፤ ተጨማሪ 12 ሺህ የመድኃኒት መጠኖች እስከ ሚያዝያ ወር ድረስ ይጠበቃሉ ብለዋል።
መድኃኒቱን የማዳረስ ስራው የተጀመረው የአፍሪካ ሀገራት በፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ስር ከሚደረገው የእርዳታ ቅነሳ ጋር እየታገሉ ባሉበት ወቅት ነው።
በዓለም ዙሪያ ከሚኖሩ 40.8 ሚሊየን ኤችአይቪ በደማቸው ውስጥ ካለባቸው ሰዎች መካከል 52 በመቶ የሚሆኑት በምስራቅ እና በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ናቸው።
አሜሪካ 3.7 በመቶ የኤችአይቪ ስርጭት መጠን ላላት ኬንያ ተጨማሪ 25 ሺህ የመድኃኒት መጠኖችን ለመስጠት ቃል ገብታለች።
በታህሳስ ወር ኬንያ ከአሜሪካ ጋር የ2.5 ቢሊየን ዶላር የሁለትዮሽ የጤና ስምምነት ተፈራርማለች፤ ይህም ትራምፕ USAIDን ካፈረሱ በኋላ የተደረገ የመጀመሪያው ስምምነት ነው።
በስምምነቱ መሰረት ዋሽንግተን በአምስት ዓመታት ውስጥ 1.6 ቢሊየን ዶላር የምታቀርብ ሲሆን፤ ኬንያ በበኩሏ 8መቶ50 ሚሊየን ዶላር በማዋጣት ቀስ በቀስ ኃላፊነት ትረከባለች ያለዉ አፍሪካ ኒዉስ ኢንግሊሽ ነዉ።
seledadotio
ኬንያ በዓመት ሁለት ጊዜ ብቻ በመወሰድ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ /ከ99 በመቶ በላይ/ መከላከያ የሚሰጠውን አዲስ የኤችአይቪ መከላከያ መድኃኒት በመጋቢት ወር ላይ ማሰራጨት ትጀምራለች።
በጊሊያድ ሳይንሰስ ኩባንያ የሚመረተው ሌናካፓቪር የተሰኘው መድኃኒት፣ የኤችአይቪ ቫይረስ የመተላለፍ እድልን ከ99.9 በመቶ በላይ ይቀንሳል።
ኬንያ ከግሎባል ፈንድ ጋር ባደረገችው ስምምነት መሰረት የመጀመሪያውን ዙር 21 ሺህ የመድኃኒት መጠን ተረክባለች።
የጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ አደን ዱዋሌ፤ የመጀመሪያው ምዕራፍ 15 ግዛቶችን በማካተት በመጋቢት ወር መጀመሪያ ላይ ይጀምራል ሲሉ ያስታወቁ ሲሆን፤ ተጨማሪ 12 ሺህ የመድኃኒት መጠኖች እስከ ሚያዝያ ወር ድረስ ይጠበቃሉ ብለዋል።
መድኃኒቱን የማዳረስ ስራው የተጀመረው የአፍሪካ ሀገራት በፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ስር ከሚደረገው የእርዳታ ቅነሳ ጋር እየታገሉ ባሉበት ወቅት ነው።
በዓለም ዙሪያ ከሚኖሩ 40.8 ሚሊየን ኤችአይቪ በደማቸው ውስጥ ካለባቸው ሰዎች መካከል 52 በመቶ የሚሆኑት በምስራቅ እና በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ናቸው።
አሜሪካ 3.7 በመቶ የኤችአይቪ ስርጭት መጠን ላላት ኬንያ ተጨማሪ 25 ሺህ የመድኃኒት መጠኖችን ለመስጠት ቃል ገብታለች።
በታህሳስ ወር ኬንያ ከአሜሪካ ጋር የ2.5 ቢሊየን ዶላር የሁለትዮሽ የጤና ስምምነት ተፈራርማለች፤ ይህም ትራምፕ USAIDን ካፈረሱ በኋላ የተደረገ የመጀመሪያው ስምምነት ነው።
በስምምነቱ መሰረት ዋሽንግተን በአምስት ዓመታት ውስጥ 1.6 ቢሊየን ዶላር የምታቀርብ ሲሆን፤ ኬንያ በበኩሏ 8መቶ50 ሚሊየን ዶላር በማዋጣት ቀስ በቀስ ኃላፊነት ትረከባለች ያለዉ አፍሪካ ኒዉስ ኢንግሊሽ ነዉ።
seledadotio
4 months ago
ኬንያ ለውጥ ያመጣል የተባለለትን የኤችአይቪ መከላከያ መድኃኒት በመጋቢት ወር ማሰራጨት ልትጀምር ነው
ኬንያ በዓመት ሁለት ጊዜ ብቻ በመወሰድ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ /ከ99 በመቶ በላይ/ መከላከያ የሚሰጠውን አዲስ የኤችአይቪ መከላከያ መድኃኒት በመጋቢት ወር ላይ ማሰራጨት ትጀምራለች።
በጊሊያድ ሳይንሰስ ኩባንያ የሚመረተው ሌናካፓቪር የተሰኘው መድኃኒት፣ የኤችአይቪ ቫይረስ የመተላለፍ እድልን ከ99.9 በመቶ በላይ ይቀንሳል።
ኬንያ ከግሎባል ፈንድ ጋር ባደረገችው ስምምነት መሰረት የመጀመሪያውን ዙር 21 ሺህ የመድኃኒት መጠን ተረክባለች።
የጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ አደን ዱዋሌ፤ የመጀመሪያው ምዕራፍ 15 ግዛቶችን በማካተት በመጋቢት ወር መጀመሪያ ላይ ይጀምራል ሲሉ ያስታወቁ ሲሆን፤ ተጨማሪ 12 ሺህ የመድኃኒት መጠኖች እስከ ሚያዝያ ወር ድረስ ይጠበቃሉ ብለዋል።
መድኃኒቱን የማዳረስ ስራው የተጀመረው የአፍሪካ ሀገራት በፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ስር ከሚደረገው የእርዳታ ቅነሳ ጋር እየታገሉ ባሉበት ወቅት ነው።
በዓለም ዙሪያ ከሚኖሩ 40.8 ሚሊየን ኤችአይቪ በደማቸው ውስጥ ካለባቸው ሰዎች መካከል 52 በመቶ የሚሆኑት በምስራቅ እና በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ናቸው።
አሜሪካ 3.7 በመቶ የኤችአይቪ ስርጭት መጠን ላላት ኬንያ ተጨማሪ 25 ሺህ የመድኃኒት መጠኖችን ለመስጠት ቃል ገብታለች።
በታህሳስ ወር ኬንያ ከአሜሪካ ጋር የ2.5 ቢሊየን ዶላር የሁለትዮሽ የጤና ስምምነት ተፈራርማለች፤ ይህም ትራምፕ USAIDን ካፈረሱ በኋላ የተደረገ የመጀመሪያው ስምምነት ነው።
በስምምነቱ መሰረት ዋሽንግተን በአምስት ዓመታት ውስጥ 1.6 ቢሊየን ዶላር የምታቀርብ ሲሆን፤ ኬንያ በበኩሏ 8መቶ50 ሚሊየን ዶላር በማዋጣት ቀስ በቀስ ኃላፊነት ትረከባለች ያለዉ አፍሪካ ኒዉስ ኢንግሊሽ ነዉ።
ኬንያ በዓመት ሁለት ጊዜ ብቻ በመወሰድ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ /ከ99 በመቶ በላይ/ መከላከያ የሚሰጠውን አዲስ የኤችአይቪ መከላከያ መድኃኒት በመጋቢት ወር ላይ ማሰራጨት ትጀምራለች።
በጊሊያድ ሳይንሰስ ኩባንያ የሚመረተው ሌናካፓቪር የተሰኘው መድኃኒት፣ የኤችአይቪ ቫይረስ የመተላለፍ እድልን ከ99.9 በመቶ በላይ ይቀንሳል።
ኬንያ ከግሎባል ፈንድ ጋር ባደረገችው ስምምነት መሰረት የመጀመሪያውን ዙር 21 ሺህ የመድኃኒት መጠን ተረክባለች።
የጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ አደን ዱዋሌ፤ የመጀመሪያው ምዕራፍ 15 ግዛቶችን በማካተት በመጋቢት ወር መጀመሪያ ላይ ይጀምራል ሲሉ ያስታወቁ ሲሆን፤ ተጨማሪ 12 ሺህ የመድኃኒት መጠኖች እስከ ሚያዝያ ወር ድረስ ይጠበቃሉ ብለዋል።
መድኃኒቱን የማዳረስ ስራው የተጀመረው የአፍሪካ ሀገራት በፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ስር ከሚደረገው የእርዳታ ቅነሳ ጋር እየታገሉ ባሉበት ወቅት ነው።
በዓለም ዙሪያ ከሚኖሩ 40.8 ሚሊየን ኤችአይቪ በደማቸው ውስጥ ካለባቸው ሰዎች መካከል 52 በመቶ የሚሆኑት በምስራቅ እና በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ናቸው።
አሜሪካ 3.7 በመቶ የኤችአይቪ ስርጭት መጠን ላላት ኬንያ ተጨማሪ 25 ሺህ የመድኃኒት መጠኖችን ለመስጠት ቃል ገብታለች።
በታህሳስ ወር ኬንያ ከአሜሪካ ጋር የ2.5 ቢሊየን ዶላር የሁለትዮሽ የጤና ስምምነት ተፈራርማለች፤ ይህም ትራምፕ USAIDን ካፈረሱ በኋላ የተደረገ የመጀመሪያው ስምምነት ነው።
በስምምነቱ መሰረት ዋሽንግተን በአምስት ዓመታት ውስጥ 1.6 ቢሊየን ዶላር የምታቀርብ ሲሆን፤ ኬንያ በበኩሏ 8መቶ50 ሚሊየን ዶላር በማዋጣት ቀስ በቀስ ኃላፊነት ትረከባለች ያለዉ አፍሪካ ኒዉስ ኢንግሊሽ ነዉ።
5 months ago
🇺🇸 አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ሁመራ ገቡ
#ethiopia | በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ፣ በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ ረፋዱን ሁመራ ከተማ ገብተዋል።
🤝 የደማቅ አቀባበል እና የከፍተኛ አመራሮች መገኘት
አምባሳደሩ ሁመራ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሸተ ደምለው እና ከፍተኛ የዞኑ አመራሮች ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል። ለጉብኝቱ ልዩ ትኩረት የሰጠው ሌላው ክስተት የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ አቶ ጌታቸው ረዳ በአምባሳደሩ አጃቢነት አብረው መገኘታቸው ነው።
🏥 የጉብኝቱ ዋና ዓላማዎች
የአምባሳደር ማሲንጋ ወደ ስትራቴጂካዊቷ የድንበር ከተማ ሁመራ ማቅናት ዋና ዋና ግቦች የሚከተሉት ናቸው፦
* የጤና ተቋማት ምልከታ፦ በሰቲት ሁመራ የሚገኙ የጤና ተቋማትን የመሠረተ ልማት እና የግብዓት አቅርቦት ሁኔታ በአካል ተገኝተው በመመልከት የአሜሪካ መንግስት በዘርፉ የሚያደርገውን ድጋፍ ማጠናከር።
* ሰብአዊ ድጋፍ፦ በአካባቢው የሚገኙ የሰብአዊ ድጋፍ ሥራዎችን ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መወያየት።
* ወቅታዊ ሁኔታ፦ ከዞኑ አመራሮች ጋር በመሆን በአካባቢው ያለውን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ መረዳት።
🔍 ለምን ትኩረት ሳበ?
ይህ ጉብኝት አሜሪካ በኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ የምታደርገውን አጋርነት ከማሳየቱም በላይ፣ በዞኑ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ በቅርብ ለመረዳትና የልማት ሥራዎችን ለማስተናገድ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ተመልክቷል። አምባሳደሩ በአካባቢው ከሚገኙ አመራሮች ጋር የሚያደርጉት ውይይት ለቀጣይ የትብብር ሥራዎች መንገድ እንደሚጠርግ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ሁመራ #አሜሪካ #ዲፕሎማሲ #ወልቃይትጠገዴ #ኤርቪንማሲንጋ #ጌታቸውረዳ #ጤና #ኢትዮጵያ #humera #usaid #ethiopia
#ethiopia | በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ፣ በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ ረፋዱን ሁመራ ከተማ ገብተዋል።
🤝 የደማቅ አቀባበል እና የከፍተኛ አመራሮች መገኘት
አምባሳደሩ ሁመራ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሸተ ደምለው እና ከፍተኛ የዞኑ አመራሮች ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል። ለጉብኝቱ ልዩ ትኩረት የሰጠው ሌላው ክስተት የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ አቶ ጌታቸው ረዳ በአምባሳደሩ አጃቢነት አብረው መገኘታቸው ነው።
🏥 የጉብኝቱ ዋና ዓላማዎች
የአምባሳደር ማሲንጋ ወደ ስትራቴጂካዊቷ የድንበር ከተማ ሁመራ ማቅናት ዋና ዋና ግቦች የሚከተሉት ናቸው፦
* የጤና ተቋማት ምልከታ፦ በሰቲት ሁመራ የሚገኙ የጤና ተቋማትን የመሠረተ ልማት እና የግብዓት አቅርቦት ሁኔታ በአካል ተገኝተው በመመልከት የአሜሪካ መንግስት በዘርፉ የሚያደርገውን ድጋፍ ማጠናከር።
* ሰብአዊ ድጋፍ፦ በአካባቢው የሚገኙ የሰብአዊ ድጋፍ ሥራዎችን ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መወያየት።
* ወቅታዊ ሁኔታ፦ ከዞኑ አመራሮች ጋር በመሆን በአካባቢው ያለውን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ መረዳት።
🔍 ለምን ትኩረት ሳበ?
ይህ ጉብኝት አሜሪካ በኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ የምታደርገውን አጋርነት ከማሳየቱም በላይ፣ በዞኑ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ በቅርብ ለመረዳትና የልማት ሥራዎችን ለማስተናገድ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ተመልክቷል። አምባሳደሩ በአካባቢው ከሚገኙ አመራሮች ጋር የሚያደርጉት ውይይት ለቀጣይ የትብብር ሥራዎች መንገድ እንደሚጠርግ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ሁመራ #አሜሪካ #ዲፕሎማሲ #ወልቃይትጠገዴ #ኤርቪንማሲንጋ #ጌታቸውረዳ #ጤና #ኢትዮጵያ #humera #usaid #ethiopia
5 months ago
⚠️ አሜሪካ ሶማሊያን ዕርዳታ አልሰጥሽም አለቻት
#ethiopia | የዕርዳታ መጋዘን መውደም እና የምግብ ዕርዳታ መዘረፍ ነው ተብሏል አሜሪካ ለሶማሊያ የፌዴራል መንግስት የምታበረክተውን ማንኛውንም ዓይነት ድጋፍ ሙሉ በሙሉ ማቋረጧን በይፋ አስታወቀች። ይህ አስደንጋጭ ውሳኔ የተላለፈው በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነት ወደ ከፋ ደረጃ ሊያሸጋግር የሚችል ክስተት በሶማሊያ መፈጸሙን ተከትሎ ነው።
🚫 ለውሳኔው የተሰጡ ምክንያቶች
የአሜሪካ መንግስት ለዚህ እርምጃው ሁለት ዋና ዋና ምክንያቶችን አስቀምጧል፦
* የመጋዘን መውደም፦ አሜሪካ በገንዘብ የምትረዳው የዓለም የምግብ ፕሮግራም (WFP) መጋዘን በሶማሊያ የፌዴራል መንግስት ባለሥልጣናት መውደሙን ገልጻለች።
* የዕርዳታ እህል መያዝ፦ ለተቸገሩ የሶማሊያ ዜጎች እንዲውል በልገሳ የተላከ 76 ሜትሪክ ቶን የምግብ ዕርዳታ በሕገ-ወጥ መንገድ በቁጥጥር ስር መዋሉን አሜሪካ አረጋግጫለሁ ብላለች።
📉 ሊከተል የሚችል ተጽዕኖ
አሜሪካ ለሶማሊያ የምታደርገው ድጋፍ ከሰብአዊ እርዳታ ባለፈ በጸጥታና በመንግስት ግንባታ ላይ ያተኮረ በመሆኑ፣ ድጋፉ መቋረጡ በሶማሊያ የውስጥ መረጋጋትና በአል-ሸባብ ላይ በሚደረገው ዘመቻ ላይ ከፍተኛ ጥላ ሊያሳርፍ እንደሚችል ተሰግቷል።
የሶማሊያ የፌዴራል መንግስት እስካሁን በጉዳዩ ላይ የሰጠው ይፋዊ ምላሽ የለም።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#አሜሪካ #ሶማሊያ #ሰብአዊእርዳታ #ዓለምየምግብፕሮግራም #wfp #የአፍሪካቀንድ #ፖለቲካ #somalia #usaid #ዜና
#ethiopia | የዕርዳታ መጋዘን መውደም እና የምግብ ዕርዳታ መዘረፍ ነው ተብሏል አሜሪካ ለሶማሊያ የፌዴራል መንግስት የምታበረክተውን ማንኛውንም ዓይነት ድጋፍ ሙሉ በሙሉ ማቋረጧን በይፋ አስታወቀች። ይህ አስደንጋጭ ውሳኔ የተላለፈው በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነት ወደ ከፋ ደረጃ ሊያሸጋግር የሚችል ክስተት በሶማሊያ መፈጸሙን ተከትሎ ነው።
🚫 ለውሳኔው የተሰጡ ምክንያቶች
የአሜሪካ መንግስት ለዚህ እርምጃው ሁለት ዋና ዋና ምክንያቶችን አስቀምጧል፦
* የመጋዘን መውደም፦ አሜሪካ በገንዘብ የምትረዳው የዓለም የምግብ ፕሮግራም (WFP) መጋዘን በሶማሊያ የፌዴራል መንግስት ባለሥልጣናት መውደሙን ገልጻለች።
* የዕርዳታ እህል መያዝ፦ ለተቸገሩ የሶማሊያ ዜጎች እንዲውል በልገሳ የተላከ 76 ሜትሪክ ቶን የምግብ ዕርዳታ በሕገ-ወጥ መንገድ በቁጥጥር ስር መዋሉን አሜሪካ አረጋግጫለሁ ብላለች።
📉 ሊከተል የሚችል ተጽዕኖ
አሜሪካ ለሶማሊያ የምታደርገው ድጋፍ ከሰብአዊ እርዳታ ባለፈ በጸጥታና በመንግስት ግንባታ ላይ ያተኮረ በመሆኑ፣ ድጋፉ መቋረጡ በሶማሊያ የውስጥ መረጋጋትና በአል-ሸባብ ላይ በሚደረገው ዘመቻ ላይ ከፍተኛ ጥላ ሊያሳርፍ እንደሚችል ተሰግቷል።
የሶማሊያ የፌዴራል መንግስት እስካሁን በጉዳዩ ላይ የሰጠው ይፋዊ ምላሽ የለም።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#አሜሪካ #ሶማሊያ #ሰብአዊእርዳታ #ዓለምየምግብፕሮግራም #wfp #የአፍሪካቀንድ #ፖለቲካ #somalia #usaid #ዜና
Sponsored by
Surafel
11 months ago
አሜሪካ ለኢትዮጵያ የምትሰጠው እርዳታ በአዲስ መዋቅር ስር ሆኖ እንደሚቀጥል አስታወቀች
የአሜሪካ ዓለም አቀፍ የልማት ኤጀንሲ (USAID) ቢዘጋም ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር የተፈጸሙ “የሁለትዮሽ የእርዳታ ስምምነቶች” በሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ስር በተዘረጋው አዲስ መዋር እንደሚቀጥሉ የአሜሪካ ኤምባሲ አስታወቀ። ኤምባሲው ዋነኛ ናቸው ያላቸው የሰብአዊ እርዳታ፣ ዓለም አቀፍ ጤና እና የምግብ ዋስትና መርሃ ግብሮች በአዲሱ መዋቅር እንደሚቀጥሉ ዛሬው ባወጣው መግለጫ አረጋግጧል።
አሜሪካ በእነዚህ ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምትሰጠው እርዳታ እንደሚቀጥል ኤምባሲው ማረጋገጫ የሰጠው፤ የሀገሪቱ ተራድኦ ደርጅት የሆነው USAID ባለፈው ምንት በይፋ መዘጋቱን ተከትሎ ነው። ላለፉት 64 ዓመታት በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሰብአዊ እና የልማት እርዳታ ሲያቀርብ የቆየው ይህ ተቋም የተዘጋው፤ የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ድርጅቱን ቀስ በቀስ ሲያዳክመው ከቆየ በኋላ ነው።
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት፤ ድርጅቱ የነበሩትን ኃላፊነቶች ካለፈው ሰኞ ሰኔ 24፤ 2017 ጀምሮ በይፋ ተረክቧል። ሽግግሩ “ድግግሞሽን ለመቀነስ”፣ “ተጠያቂነትን ለማጠናከር” እና የእርዳታ መርሃ ግብሮችን ከዩናይትድ ስቴትስ “የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ እና የብሔራዊ ደህንነት ዓላማዎች ጋር ለማጣጣም የሚያስችል” ሆኖ እንደተቀረጸ የአሜሪካ ኤምባሲ በዛሬው መግለጫ ጠቁሟል።
Seledadotio
Seledadotio
የአሜሪካ ዓለም አቀፍ የልማት ኤጀንሲ (USAID) ቢዘጋም ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር የተፈጸሙ “የሁለትዮሽ የእርዳታ ስምምነቶች” በሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ስር በተዘረጋው አዲስ መዋር እንደሚቀጥሉ የአሜሪካ ኤምባሲ አስታወቀ። ኤምባሲው ዋነኛ ናቸው ያላቸው የሰብአዊ እርዳታ፣ ዓለም አቀፍ ጤና እና የምግብ ዋስትና መርሃ ግብሮች በአዲሱ መዋቅር እንደሚቀጥሉ ዛሬው ባወጣው መግለጫ አረጋግጧል።
አሜሪካ በእነዚህ ዘርፎች ለኢትዮጵያ የምትሰጠው እርዳታ እንደሚቀጥል ኤምባሲው ማረጋገጫ የሰጠው፤ የሀገሪቱ ተራድኦ ደርጅት የሆነው USAID ባለፈው ምንት በይፋ መዘጋቱን ተከትሎ ነው። ላለፉት 64 ዓመታት በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሰብአዊ እና የልማት እርዳታ ሲያቀርብ የቆየው ይህ ተቋም የተዘጋው፤ የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ድርጅቱን ቀስ በቀስ ሲያዳክመው ከቆየ በኋላ ነው።
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት፤ ድርጅቱ የነበሩትን ኃላፊነቶች ካለፈው ሰኞ ሰኔ 24፤ 2017 ጀምሮ በይፋ ተረክቧል። ሽግግሩ “ድግግሞሽን ለመቀነስ”፣ “ተጠያቂነትን ለማጠናከር” እና የእርዳታ መርሃ ግብሮችን ከዩናይትድ ስቴትስ “የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ እና የብሔራዊ ደህንነት ዓላማዎች ጋር ለማጣጣም የሚያስችል” ሆኖ እንደተቀረጸ የአሜሪካ ኤምባሲ በዛሬው መግለጫ ጠቁሟል።
Seledadotio
Seledadotio
11 months ago
"ለኢትዮጵያ የሚሰጠው እርዳታ አይቋረጥም"
#ethiopia | አሜሪካ ለኢትዮጵያና መሰል ሀገራት የምትሰጠውን እርዳታ የምታስተዳድርበት መንገድ ላይ ወሳኝ ለውጥ አድርጋለች። ከሰሞኑ ተግባራዊ መሆን የጀመረው ይህ ለውጥ፣ የአሜሪካ መንግስት የልማት፣ የጤና እና የምግብ ዋስትና ድጋፎችን የሚያቀርብበትን አካሄድ በአዲስ መልክ ያዋቅራል።
ከዚህ ቀደም በአሜሪካ ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት (USAID) ይከናወኑ የነበሩ ቁልፍ ተግባራት፣ አሁን በቀጥታ በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስር እንዲሆኑ ተደርጓል።
ይህም በሁለት የተለያዩ ቢሮዎች የሚሰሩ ተቀራራቢ ስራዎችን ወደ አንድ ማዕከል በማምጣት የተሻለ ቅንጅት ለመፍጠር ያለመ ነው ተብሏል።
ይህ ለውጥ ለኢትዮጵያ የሚሰጠው እርዳታ እንዲቋረጥ ያደርጋል? የሚለውን ጥያቄ "አንዳፍታ" በአዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ የሰጠውን መልስ በመጥቀስ እንደማይቋረጥ በዘገባው አመልክቷል፡፡
ኤምባሲው እንዳረጋገጠው፣ ከአሁኑ የኢትዮጵያ መንግስት ጋር የተደረሱ የእርዳታ ስምምነቶች እንደተጠበቁ ሆነው ይቀጥላሉ። በተለይም ህይወት አድን የሆኑና ወሳኝ ድጋፎች ማለትም፦ የሰብዓዊ እርዳታ፣ የዓለም አቀፍ የጤና ድጋፍ፣ የምግብ ዋስትና ፕሮግራሞች ሳይስተጓጎሉ በአዲሱ መዋቅር ስር ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገልጿል።
በፕሬዚዳንት ትራምፕና በውጭ ጉዳይ ጸሃፊ ሩቢዮ አመራር የተጀመረው ይህ እቅድ፣ በመጨረሻም በዓለም ዙሪያ የሚሰጠው ድጋፍ ግቡን እንዲመታና ህይወት እንዲያድን ለማድረግ ያለመ ስልታዊ እርምጃ ነው ተብሏል፡፡
#addis_admas
#ethiopia | አሜሪካ ለኢትዮጵያና መሰል ሀገራት የምትሰጠውን እርዳታ የምታስተዳድርበት መንገድ ላይ ወሳኝ ለውጥ አድርጋለች። ከሰሞኑ ተግባራዊ መሆን የጀመረው ይህ ለውጥ፣ የአሜሪካ መንግስት የልማት፣ የጤና እና የምግብ ዋስትና ድጋፎችን የሚያቀርብበትን አካሄድ በአዲስ መልክ ያዋቅራል።
ከዚህ ቀደም በአሜሪካ ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት (USAID) ይከናወኑ የነበሩ ቁልፍ ተግባራት፣ አሁን በቀጥታ በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስር እንዲሆኑ ተደርጓል።
ይህም በሁለት የተለያዩ ቢሮዎች የሚሰሩ ተቀራራቢ ስራዎችን ወደ አንድ ማዕከል በማምጣት የተሻለ ቅንጅት ለመፍጠር ያለመ ነው ተብሏል።
ይህ ለውጥ ለኢትዮጵያ የሚሰጠው እርዳታ እንዲቋረጥ ያደርጋል? የሚለውን ጥያቄ "አንዳፍታ" በአዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ የሰጠውን መልስ በመጥቀስ እንደማይቋረጥ በዘገባው አመልክቷል፡፡
ኤምባሲው እንዳረጋገጠው፣ ከአሁኑ የኢትዮጵያ መንግስት ጋር የተደረሱ የእርዳታ ስምምነቶች እንደተጠበቁ ሆነው ይቀጥላሉ። በተለይም ህይወት አድን የሆኑና ወሳኝ ድጋፎች ማለትም፦ የሰብዓዊ እርዳታ፣ የዓለም አቀፍ የጤና ድጋፍ፣ የምግብ ዋስትና ፕሮግራሞች ሳይስተጓጎሉ በአዲሱ መዋቅር ስር ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገልጿል።
በፕሬዚዳንት ትራምፕና በውጭ ጉዳይ ጸሃፊ ሩቢዮ አመራር የተጀመረው ይህ እቅድ፣ በመጨረሻም በዓለም ዙሪያ የሚሰጠው ድጋፍ ግቡን እንዲመታና ህይወት እንዲያድን ለማድረግ ያለመ ስልታዊ እርምጃ ነው ተብሏል፡፡
#addis_admas
11 months ago
በዩ ኤስ ኤይድ መቋረጥ ተጨማሪ 14 ሚሊዮን ሰዎችን ለሞት አጋልጧል ተባለ። #ethiopia የአሜሪካ ተራዲዖ ድርጅት (USAID) ስራውን በቅርቡ ካልጀመረ በ2030 በአለማቀፍ ደረጃ 14 ሚሊዮን ሰዎች እንደሚሞቱ የላንሴት ህክምና ቡድን ይፋ ያደረገው ጥናት ያመለክታል። የትራምፕ አስተዳደር ለዩ ኤስ ኤይድ የሚያደርገውን ድጋፍ በማቋረጥ ድርጅቱ እንዲዘጋ አድርጓል። #thenewdaily #thiqaheth