Logo
SeledaPost
የህወሓት ወታደራዊ ክንፍ ከፍተኛ መኮንኖች አዲስ አበባ ገቡ

በህወሓት (TPLF) ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች እና በድርጅቱ የፖለቲካ መዋቅር መካከል ያለው ልዩነት ከመቼውም ጊዜ በላይ እየሰፋ መምጣቱን የሚያሳዩ መረጃዎች እየወጡ ነው።

​ይህ እንቅስቃሴ በህወሓት የውስጥ አንድነት ላይ ከፍተኛ ጥያቄ ያስነሳ ሲሆን፤ ድርጅቱ ለዓመታት ሲመካበት የነበረው የወታደራዊ መዋቅር ቁጥጥር እየላላ መምጣቱን ያመላክታል።

​ወደ መዲናዋ አዲስ አበባ ከገቡት ከፍተኛ መኮንኖች መካከል ብሪጋዴር ጀነራል ጉዕሽ ገብረ አንዱ ናቸው።

ጀነራሉ ቀደም ሲል በህወሓት ቁጥጥር ስር ውለው በእስር ላይ የነበሩ ሲሆን፣ በቅርቡ በዋስ ተለቀው ጉዟቸውን ወደ አዲስ አበባ ማድረጋቸው የሁኔታውን ውስብስብነት ያሳያል።

ከእሳቸው ጋርም ኮሎኔል ከበደ ፍቃዱ እና ኮሎኔል ንጉስ ወልደገብርኤል (ወለጋ) የተባሉ መኮንኖች አብረው መግባታቸው ተረጋግጧል።

​እነዚህ መኮንኖች ድርጅቱን "ለግል ወይም ለቡድን ጥቅም ሰራዊቱን እንደ ንብረት ይጠቀማል" በሚል እንደሚከሱ ተሰምቷል።

seledadotio
seledadotio
4 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.