Logo
Getu Temesgen
ከፍተኛ ባለስልጣናት በአንድ አውቶቡስ እንዲጓዙ ተወሰነ
#ethiopia | በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣው ጦርነት በዓለም አቀፍ የነዳጅ አቅርቦትና ዋጋ ላይ እያሳደረ ያለውን ጫና ተከትሎ፣ ታንዛኒያ የመንግሥትን ወጪ ለመቀነስ ጥብቅ መመሪያ አወጣች።

የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ሳሚያ ሱሉሁ ሀሰን ባለስልጣኖቻቸው ለስራ በሚንቀሳቀሱበት ወቅት በየግል መኪኖቻቸው ከመሄድ ይልቅ በአንድ አውቶቡስ በጋራ እንዲጓዙ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል። ይህ ውሳኔ በጦርነቱ ምክንያት የተከሰተውን የነዳጅ ዋጋ ንረትና የኢኮኖሚ ጫና ለመቋቋም ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

ፕሬዚዳንቷ በሰጡት መመሪያ፣ የዓለም አቀፉ የነዳጅ ቀውስ ታንዛኒያንም እየፈተናት በመሆኑ የመንግሥትን ሀብት በከፍተኛ ዲሲፕሊን መጠቀም ግዴታ መሆኑን አሳስበዋል።
በዚህም መሰረት ባለስልጣናቱ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝቶችም ሆነ ለተለያዩ ስብሰባዎች በሚንቀሳቀሱበት ወቅት በተናጠል መኪና መጠቀም አቁመው በአንድ አውቶቡስ ተሰባስበው እንዲጓዙ ይደረጋል።

ከዚህ ቀደምም መንግሥት ወጪን ለመቆጠብ በሚያደርገው ጥረት፣ የፕሬዚዳንቷን አጀብ ተሽከርካሪዎች ቁጥር እንዲቀነሱ ማድረጉ ይታወሳል።

በአሁኑ ወቅት በታንዛኒያ አንድ ሊትር ቤንዚን በ3 ሺህ 820 የታንዛኒያ ሽልንግ እየተሸጠ የሚገኝ ሲሆን፣ ሀገሪቱ የነዳጅ ምርትን ሙሉ በሙሉ ከውጭ የምታስገባ በመሆኗ ለዓለም አቀፍ የዋጋ መዋዠቅ ተጋላጭ ሆና ትገኛለች።

ይህ የታንዛኒያ እርምጃ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራትም የነዳጅ ቀውሱን ለመቋቋም ተመሳሳይ የቁጠባ እርምጃዎችን ሊከተሉ እንደሚችሉ ማሳያ ተደርጎ ተወስዷል።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #fmc #tanzania #samiasul #fuelcrisis #africanews #economy #fuelprice #tanzanianews

4 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.