1 month ago
u12ebu1208u120du12e9u1290u1275 u12a2u1275u12eeu1335u12ebu1295 u121bu120du1260u1235
https://youtu.be/gdbqDMzND... #pmabiyahmed #parliament #ethiopia #greenlegacy ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"ExternalUrl","__isEntity":"ExternalUrl","url":"https://l.facebook.com/l.p...
ያለልዩነት ኢትዮጵያን ማልበስ
https://youtu.be/gdbqDMzND... #pmabiyahmed #parliament #ethiopia #greenlegacy
6 months ago
ለሊቨርፑል ደጋፊዎች ትልቅ ነገር
#ethiopia | የርገን ክሎፕ ከሊቨርፑል ጋር የነበራቸው ቁርኝት ምን ያህል ጥልቅ እንደሆነ የሚያሳይ አዲስ ሚስጥር በወኪላቸው ማርክ ኮሲክ አማካኝነት ይፋ ሆኗል። እንደ ወኪሉ ገለጻ፣ ክሎፕ አንፊልድን ከለቀቁ በኋላ ማንችስተር ዩናይትድ እና ቼልሲ አሰልጣኙን ለመቅጠር ጥያቄ አቅርበውላቸው ነበር።
የክሎፕ "አይ" ለታሪካዊ ተቀናቃኞች
ምንም እንኳን ሁለቱ የለንደን እና የማንችስተር ግዙፍ ክለቦች የርገን ክሎፕን ወደ ስታምፎርድ ብሪጅ ወይም ኦልድ ትራፎርድ ለመውሰድ ቢሞክሩም፣ የጀርመናዊው አሰልጣኝ ምላሽ ግን የማያወላውል ነበር።
"የርገን በእንግሊዝ ውስጥ ከሊቨርፑል ውጪ ሌላ ክለብን በጭራሽ እንደማያሰለጥን ግልጽ አድርጓል" - ማርክ ኮሲክ (የክሎፕ ወኪል)
ታማኝነት ከገንዘብ በላይ
ይህ ውሳኔ ክሎፕ ለሊቨርፑል ደጋፊዎች ያላቸውን ልዩ ክብር እና የገቡትን ቃል ጠባቂነት የሚያሳይ ነው። ምንም እንኳን ከክለቡ ቢለዩም፣ ከሊቨርፑል ጋር ያላቸውን ታሪክ የሚያበላሽ ወይም ደጋፊዎቻቸውን የሚያስከፋ እርምጃ ለመውሰድ ፍቃደኛ አልሆኑም።
ይህ ዜና በተለይ በዩናይትድ እና በቼልሲ ደጋፊዎች ዘንድ "ምን አልባት ቢመጡስ?" የሚል ተስፋ ለነበራቸው ትልቅ መርዶ ሆኗል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #jurgenklopp #liverpoolfc #mufc #cfc #premierleague #footballnews #klopp #ethiosports #lfcfamily
#ethiopia | የርገን ክሎፕ ከሊቨርፑል ጋር የነበራቸው ቁርኝት ምን ያህል ጥልቅ እንደሆነ የሚያሳይ አዲስ ሚስጥር በወኪላቸው ማርክ ኮሲክ አማካኝነት ይፋ ሆኗል። እንደ ወኪሉ ገለጻ፣ ክሎፕ አንፊልድን ከለቀቁ በኋላ ማንችስተር ዩናይትድ እና ቼልሲ አሰልጣኙን ለመቅጠር ጥያቄ አቅርበውላቸው ነበር።
የክሎፕ "አይ" ለታሪካዊ ተቀናቃኞች
ምንም እንኳን ሁለቱ የለንደን እና የማንችስተር ግዙፍ ክለቦች የርገን ክሎፕን ወደ ስታምፎርድ ብሪጅ ወይም ኦልድ ትራፎርድ ለመውሰድ ቢሞክሩም፣ የጀርመናዊው አሰልጣኝ ምላሽ ግን የማያወላውል ነበር።
"የርገን በእንግሊዝ ውስጥ ከሊቨርፑል ውጪ ሌላ ክለብን በጭራሽ እንደማያሰለጥን ግልጽ አድርጓል" - ማርክ ኮሲክ (የክሎፕ ወኪል)
ታማኝነት ከገንዘብ በላይ
ይህ ውሳኔ ክሎፕ ለሊቨርፑል ደጋፊዎች ያላቸውን ልዩ ክብር እና የገቡትን ቃል ጠባቂነት የሚያሳይ ነው። ምንም እንኳን ከክለቡ ቢለዩም፣ ከሊቨርፑል ጋር ያላቸውን ታሪክ የሚያበላሽ ወይም ደጋፊዎቻቸውን የሚያስከፋ እርምጃ ለመውሰድ ፍቃደኛ አልሆኑም።
ይህ ዜና በተለይ በዩናይትድ እና በቼልሲ ደጋፊዎች ዘንድ "ምን አልባት ቢመጡስ?" የሚል ተስፋ ለነበራቸው ትልቅ መርዶ ሆኗል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #jurgenklopp #liverpoolfc #mufc #cfc #premierleague #footballnews #klopp #ethiosports #lfcfamily
7 months ago
ቼልሲ አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካን ከኃላፊነት አነሳ
#ethiopia | የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ ጣሊያናዊውን አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካን ከኃላፊነታቸው ማሰናበቱን በይፋ አስታወቀ።
ክለቡ ባወጣው መግለጫ አሰልጣኙ በቆይታቸው ላከናወኑት ስራና ላስመዘገቡት ውጤት ምስጋናውን አቅርቧል። በተለይም ማሬስካ በክለቡ የቅርብ ጊዜ ታሪክ ውስጥ ያሳኳቸው የዋንጫ ስኬቶች ምንጊዜም ሲታወሱ እንደሚኖሩ ክለቡ ገልጿል።
የአሰልጣኙ የቼልሲ ቆይታ በቁጥር፡🔎
አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ በስታምፎርድ ብሪጅ በነበራቸው ቆይታ ያስመዘገቡት አሃዛዊ መረጃዎች የሚከተሉት ናቸው፦
* ጠቅላላ ጨዋታዎች፡ 92
* ድል ያደረጉባቸው፡ 55
* ያሳኳቸው ዋንጫዎች፡ 2
ቼልሲ በመግለጫው ማጠቃለያ ላይ "ለአሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ ለወደፊት ህይወታቸው መልካሙን እንመኛለን" በማለት ስንብቱን አጽድቋል።
ክለቡ የአሰልጣኙን ስንብት ተከትሎ በጊዜያዊነት ወይም በቋሚነት ክለቡን የሚረከብ አሰልጣኝ እስካሁን በይፋ የገለጸው ነገር የለም።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#chelseafc #enzomaresca #premierleague #footballnews #cfc #sacked #breakingnews
#ethiopia | የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ ጣሊያናዊውን አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካን ከኃላፊነታቸው ማሰናበቱን በይፋ አስታወቀ።
ክለቡ ባወጣው መግለጫ አሰልጣኙ በቆይታቸው ላከናወኑት ስራና ላስመዘገቡት ውጤት ምስጋናውን አቅርቧል። በተለይም ማሬስካ በክለቡ የቅርብ ጊዜ ታሪክ ውስጥ ያሳኳቸው የዋንጫ ስኬቶች ምንጊዜም ሲታወሱ እንደሚኖሩ ክለቡ ገልጿል።
የአሰልጣኙ የቼልሲ ቆይታ በቁጥር፡🔎
አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ በስታምፎርድ ብሪጅ በነበራቸው ቆይታ ያስመዘገቡት አሃዛዊ መረጃዎች የሚከተሉት ናቸው፦
* ጠቅላላ ጨዋታዎች፡ 92
* ድል ያደረጉባቸው፡ 55
* ያሳኳቸው ዋንጫዎች፡ 2
ቼልሲ በመግለጫው ማጠቃለያ ላይ "ለአሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ ለወደፊት ህይወታቸው መልካሙን እንመኛለን" በማለት ስንብቱን አጽድቋል።
ክለቡ የአሰልጣኙን ስንብት ተከትሎ በጊዜያዊነት ወይም በቋሚነት ክለቡን የሚረከብ አሰልጣኝ እስካሁን በይፋ የገለጸው ነገር የለም።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#chelseafc #enzomaresca #premierleague #footballnews #cfc #sacked #breakingnews
11 months ago
💥 ጳጉሜን 2 የደም ጨረቃ በኢትዮጵያ ሊታይ ነው
✍️ ከመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ (መነበብ የሚገባው ወቅታዊ)
💥 ታላቅ ክብር ባላት በ13ኛ ወራችን በጳጒሜን 2/ 2017 ዓ.ም. እሑድ ማታ የኢትዮጵያ ሕዝቦች በሙሉ በዐይናቸው ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ ወይም ታላቅ የደም ጨረቃን ያያሉ፡፡
💥 ከ6 ዓመታት በፊት በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ እና በዶክተር ጌትነት ፈለቀ በተዘጋጀው አንድሮሜዳ መጽሐፍ ገጽ 193 ላይ የሠኔ 14/ 2012 ዓ.ም. ላይ በኢትዮጵያ በላስታ ላሊበላ ስለሚከሰተው ቀለበታማ የፀሓይ ግርዶሽ እና ጳጉሜን 2/ 2017 ዓ.ም. በኢትዮጵያ በሙሉ ስለሚታየው የሙሉ ጨረቃ ግርዶሽ (የጨረቃ ደም መስሎ መታየት) ላይ አስቀድሞ እንደተገለጸ ይታወቃል፡፡
💥 በዓመት ውስጥ 13 ሙሉ ጨረቃዎች ይታያሉ፡፡ ሌሎቹ ሀገራት 13ኛ ወራቸውን በማጥፋታቸው በ12 ወራት ውስጥ 13ኛ ሙሉ ጨረቃ ይከሰትባቸዋል፡፡ የኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ግን ትክክለኛዋን የጳጉሜን 13ኛ ወራትን በመያዙ 13 የዓመቱ ሙሉ ጨረቃዎችን በአንድ ዓመት ውስጥ እናያለን፡፡
💥 ታላቅ የዘመን ቀመርን፣ አስደናቂ ፊደላትን፣ የራሳችን ዜማ፣ ድንቆች ባህሎችን፣ ድንቅ መልክአ ምድርን አስተባብራ የያዘችውን ታላቋን ኢትዮጵያ ለመውረርና በራሳቸው ማንነት ለመቀየር ሮማውያን አህጉር አቋርጠው ቢመጡም በብዙ መሥዋዕትነት በ1888 ዓ.ም. በዐድዋ ላይ አባቶቻችን እናቶቻችን ዋጋ ከፍለው ድል በመንሣት ሙሉ ክብራችንን አስጠብቀውልን ታሪክን በወርቅ ቀለም ጽፈው ለመላው ጥቁር ሕዝቦች አብሪ ብርሃን ኾነው የዘመን ቀመራችን ወደ ሮማ ሳያፈልሱ በክብር ዐልፈዋል፡፡
💥 አኹንም በዚኽች ድንቅ የጳጒሜን ወር አፍሪካውያን፣ አውስትራሊያ፣ በእስያ ያሉ የጨረቃ ግርዶሽን በማየት ምሽታቸውን ያሳልፋሉ፡፡
💥 በመኾንም ውድ ኢትጵያውያን ጳጉሜን 2 ምሽታችኹን ከጨረቃ ግርዶሽ ጋር በማድረግ በሕይወታችኍ የማትረሱትን የደም ጨረቃን በዐይናችኍ በማየት ድንቅ ምሽት እንድታደርጉ መልእክቴን በማስተላለፍ በተለይ ደመና በአካባቢያችኍ ከሌለ በግልጽ የሚታይ ሲኾን በዚኽ 13ኛ የሙሉ ጨረቃ ዕለት የሚከሰተውን የሰማይ መርሐ ግብር ለመከታተል እንድትችሉ ሰዓቱን ከዚኽ በታች አስቀምጬላችኋለኊ፡፡
👉 ከምሽቱ 12፡21 (6:21 PM) - ደማቋ ሙሉዋ ጨረቃ በምሥራቅ አድማስ መውጣት ትጀምራለች፡፡
👉 ከምሽቱ 12፡28 (6፡28 PM) መሬት ጨረቃን መከለል ስትዠምር ድብዝዙ ግርዶሽ መታየት ይጀምራል፡፡
👉 ከምሽቱ 1፡27 (7:27 PM) ከፊል ግርዶሹ ይጀምራል፡፡
👉 ከምሽቱ 2፡30 ላይ (8፡30 PM) ተጠባቂው ሙሉው የጨረቃ ግርዶሽ ዠምሮ ጨረቃ ደም የምትመስልበት ሰዓት ይኾናል፡፡
👉 ከምሽቱ 3፡11 (9:11 PM) ላይ ጨረቃ በጥላው ማእከል የምትኾንበት ደም መምሰሏ የሚጨምርበት ሰዓት ይኾናል፡፡
👉 ከምሽቱ 3፡52 (9:52 PM) ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ (ደም መምሰሏ) ማብቂያ ይኾናል፡፡
👉 በመጨረሻዋ 13 ወራችን በርኅወተ ሰማይ በጳጉሜን 2 የዚኽ የሙሉ ጨረቃ ግርዶሽ መታየቱ እና የጨረቃ ደም መምሰል ያለው ሳይንሳዊ፣ ኢትጵያዊ ዕውቀት፣ ሃይማኖታዊ፣ ምልክትና መጻኢ ጉዳይ ዙሪያ በዶክተር ሮዳስ ታደሰ እና በዶክተር ጌትነት ፈለቀ፣ በመምህር መስፍን ሰሎሞን የቀረበውን ሰፊና ጥልቅ ትንተና ለማየትና ለማድመጥ በዚኽ ሊንክ ከፍተው ይመልከቱ፡፡
https://youtu.be/OoiU6WHxs...
👉 በመኾኑም ይኽነን ቪዲዮና ጽሑፍ ለኹሉም ሼር በማድረግ በዕለቱ ያለውን ክስተት በመላ ኢትዮጵያ ስለሚታይ ኹሉም ኢትዮጵያውን ከቤታቸው ወጥተው በሰዓቱ ክስተቱን እንዲመለከቱና ጨረቃ ደም መስላ ስትታይ እንዳይደናገጡ መልእክቴን አስተላልፋለኍ፡፡
💥 እኔ ከሥራ ባልደረቦቼ እና ከጓደኞቼ ጋር የማይረሳ በዕለቱ ታላቅ የምሽት መርሐ ግብር የምናደርግ ሲኾን እናንተም ከቤተሰቦቻችኊ፣ ከጓደኞቻችኍ ጋር ክስተቱን በማየት እንድታሳልፉ ምክሬን በማቅረብ የደም ጨረቃን (ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽን) በዐይን ማየት ምንም የሚያስከትለው የጤንነት ችግር ስለሌለው ምንም አሳሳቢ ነገር ስለሌለ በተጠቀሰው ሰዓት ባላችኹበት አካባቢ ደመና ከሌለ በሚገባ ማየት ትችላላችኍ፡፡
💥 በዕለቱም ካላችኹበት ቦታ የማስታወሻ ፎቶዎችን በመነሣት በሶሻል ሚዲያዎች እንድታጋሩን በማሳሰብ መጪው 2018 ዓ.ም. ለኹላችኹም የበረከት፣ የምሕረት፣ የከፍታ እንዲኾንላችኍ ከአኹኑ እመኛለኍ፡፡
መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
(ነሐሴ 24/ 2017 ዓ.ም.)
✍️ ከመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ (መነበብ የሚገባው ወቅታዊ)
💥 ታላቅ ክብር ባላት በ13ኛ ወራችን በጳጒሜን 2/ 2017 ዓ.ም. እሑድ ማታ የኢትዮጵያ ሕዝቦች በሙሉ በዐይናቸው ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ ወይም ታላቅ የደም ጨረቃን ያያሉ፡፡
💥 ከ6 ዓመታት በፊት በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ እና በዶክተር ጌትነት ፈለቀ በተዘጋጀው አንድሮሜዳ መጽሐፍ ገጽ 193 ላይ የሠኔ 14/ 2012 ዓ.ም. ላይ በኢትዮጵያ በላስታ ላሊበላ ስለሚከሰተው ቀለበታማ የፀሓይ ግርዶሽ እና ጳጉሜን 2/ 2017 ዓ.ም. በኢትዮጵያ በሙሉ ስለሚታየው የሙሉ ጨረቃ ግርዶሽ (የጨረቃ ደም መስሎ መታየት) ላይ አስቀድሞ እንደተገለጸ ይታወቃል፡፡
💥 በዓመት ውስጥ 13 ሙሉ ጨረቃዎች ይታያሉ፡፡ ሌሎቹ ሀገራት 13ኛ ወራቸውን በማጥፋታቸው በ12 ወራት ውስጥ 13ኛ ሙሉ ጨረቃ ይከሰትባቸዋል፡፡ የኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠር ግን ትክክለኛዋን የጳጉሜን 13ኛ ወራትን በመያዙ 13 የዓመቱ ሙሉ ጨረቃዎችን በአንድ ዓመት ውስጥ እናያለን፡፡
💥 ታላቅ የዘመን ቀመርን፣ አስደናቂ ፊደላትን፣ የራሳችን ዜማ፣ ድንቆች ባህሎችን፣ ድንቅ መልክአ ምድርን አስተባብራ የያዘችውን ታላቋን ኢትዮጵያ ለመውረርና በራሳቸው ማንነት ለመቀየር ሮማውያን አህጉር አቋርጠው ቢመጡም በብዙ መሥዋዕትነት በ1888 ዓ.ም. በዐድዋ ላይ አባቶቻችን እናቶቻችን ዋጋ ከፍለው ድል በመንሣት ሙሉ ክብራችንን አስጠብቀውልን ታሪክን በወርቅ ቀለም ጽፈው ለመላው ጥቁር ሕዝቦች አብሪ ብርሃን ኾነው የዘመን ቀመራችን ወደ ሮማ ሳያፈልሱ በክብር ዐልፈዋል፡፡
💥 አኹንም በዚኽች ድንቅ የጳጒሜን ወር አፍሪካውያን፣ አውስትራሊያ፣ በእስያ ያሉ የጨረቃ ግርዶሽን በማየት ምሽታቸውን ያሳልፋሉ፡፡
💥 በመኾንም ውድ ኢትጵያውያን ጳጉሜን 2 ምሽታችኹን ከጨረቃ ግርዶሽ ጋር በማድረግ በሕይወታችኍ የማትረሱትን የደም ጨረቃን በዐይናችኍ በማየት ድንቅ ምሽት እንድታደርጉ መልእክቴን በማስተላለፍ በተለይ ደመና በአካባቢያችኍ ከሌለ በግልጽ የሚታይ ሲኾን በዚኽ 13ኛ የሙሉ ጨረቃ ዕለት የሚከሰተውን የሰማይ መርሐ ግብር ለመከታተል እንድትችሉ ሰዓቱን ከዚኽ በታች አስቀምጬላችኋለኊ፡፡
👉 ከምሽቱ 12፡21 (6:21 PM) - ደማቋ ሙሉዋ ጨረቃ በምሥራቅ አድማስ መውጣት ትጀምራለች፡፡
👉 ከምሽቱ 12፡28 (6፡28 PM) መሬት ጨረቃን መከለል ስትዠምር ድብዝዙ ግርዶሽ መታየት ይጀምራል፡፡
👉 ከምሽቱ 1፡27 (7:27 PM) ከፊል ግርዶሹ ይጀምራል፡፡
👉 ከምሽቱ 2፡30 ላይ (8፡30 PM) ተጠባቂው ሙሉው የጨረቃ ግርዶሽ ዠምሮ ጨረቃ ደም የምትመስልበት ሰዓት ይኾናል፡፡
👉 ከምሽቱ 3፡11 (9:11 PM) ላይ ጨረቃ በጥላው ማእከል የምትኾንበት ደም መምሰሏ የሚጨምርበት ሰዓት ይኾናል፡፡
👉 ከምሽቱ 3፡52 (9:52 PM) ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽ (ደም መምሰሏ) ማብቂያ ይኾናል፡፡
👉 በመጨረሻዋ 13 ወራችን በርኅወተ ሰማይ በጳጉሜን 2 የዚኽ የሙሉ ጨረቃ ግርዶሽ መታየቱ እና የጨረቃ ደም መምሰል ያለው ሳይንሳዊ፣ ኢትጵያዊ ዕውቀት፣ ሃይማኖታዊ፣ ምልክትና መጻኢ ጉዳይ ዙሪያ በዶክተር ሮዳስ ታደሰ እና በዶክተር ጌትነት ፈለቀ፣ በመምህር መስፍን ሰሎሞን የቀረበውን ሰፊና ጥልቅ ትንተና ለማየትና ለማድመጥ በዚኽ ሊንክ ከፍተው ይመልከቱ፡፡
https://youtu.be/OoiU6WHxs...
👉 በመኾኑም ይኽነን ቪዲዮና ጽሑፍ ለኹሉም ሼር በማድረግ በዕለቱ ያለውን ክስተት በመላ ኢትዮጵያ ስለሚታይ ኹሉም ኢትዮጵያውን ከቤታቸው ወጥተው በሰዓቱ ክስተቱን እንዲመለከቱና ጨረቃ ደም መስላ ስትታይ እንዳይደናገጡ መልእክቴን አስተላልፋለኍ፡፡
💥 እኔ ከሥራ ባልደረቦቼ እና ከጓደኞቼ ጋር የማይረሳ በዕለቱ ታላቅ የምሽት መርሐ ግብር የምናደርግ ሲኾን እናንተም ከቤተሰቦቻችኊ፣ ከጓደኞቻችኍ ጋር ክስተቱን በማየት እንድታሳልፉ ምክሬን በማቅረብ የደም ጨረቃን (ሙሉ የጨረቃ ግርዶሽን) በዐይን ማየት ምንም የሚያስከትለው የጤንነት ችግር ስለሌለው ምንም አሳሳቢ ነገር ስለሌለ በተጠቀሰው ሰዓት ባላችኹበት አካባቢ ደመና ከሌለ በሚገባ ማየት ትችላላችኍ፡፡
💥 በዕለቱም ካላችኹበት ቦታ የማስታወሻ ፎቶዎችን በመነሣት በሶሻል ሚዲያዎች እንድታጋሩን በማሳሰብ መጪው 2018 ዓ.ም. ለኹላችኹም የበረከት፣ የምሕረት፣ የከፍታ እንዲኾንላችኍ ከአኹኑ እመኛለኍ፡፡
መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ
(ነሐሴ 24/ 2017 ዓ.ም.)
Sponsored by
Surafel
Comments