29 days ago
ዓለም አቀፉ የፓርላማ፣ መረጃና ደህንነት ፎረም በአዲስ አበባ መካሄድ ጀመረ
**************
ዓለም አቀፉ የፓርላማ፣ መረጃና ደህንነት ፎረም በአዲስ አበባ ከተማ መካሄድ ጀምሯል። ፎረሙ በአፍሪካ ለሁለተኛ ጊዜ የተካሄደ ሲሆን አዲስ አበባም መድረኩን በማስተናገድ ሁለተኛዋ የአፍሪካ ከተማ ሆናለች።
ለሚቀጥሉት ሁለት ቀናት በሚቆየው በዚህ ጉባኤ ላይ ሽብርተኝነትን መከላከል፣ ቀጣናዊ ፀጥታ እንዲሁም የቴክኖሎጂ አጠቃቀም በዋናነት ትኩረት የተደረገባቸው ጉዳዮች ናቸው።
መድረኩን በንግግር የከፈቱት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ኢትዮጵያ ይህንን ዓለም አቀፍ ፎረም የምታስተናግደው 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ፍትሐዊና ግልጽ በሆነ መልኩ ባካሄደች ማግሥት መሆኑ ልዩ ትርጉም እንዳለው ገልጸዋል።
አፈ ጉባኤው አክለውም፣ በምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና የሚስተዋሉ የፀጥታ ችግሮችን ከጎረቤት ሀገራት ጋር በመተባበርና በቆራጥነት ለመከላከል ሀገራችን ሰፊ ሥራዎችን እያከናወነች እንደምትገኝ ጠቁመዋል።
በቴክኖሎጂው ዘርፍም ኢትዮጵያ አመርቂ ተግባራትን እያከናወነች መሆኑን ያብራሩት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የዲጂታልና የሳይበር ደህንነት ይበልጥ የተጠበቀ እንዲሆን በየጊዜው ከሚፈጠሩ አዳዲስ የቴክኖሎጂ ዕድገቶች ጋር ራስን በማላመድ ረገድ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን ለጉባኤው ተሳታፊዎች አስገንዝበዋል።
በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኢርቪንግ ማሲንጋ በበኩላቸው፣ ይህ ፎረም ሀገራት መረጃዎችን የጋራ በማድረግ የዜጎቻቸውን ደህንነት ለማረጋገጥና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀለኞችን ተከታትሎ ለሕግ ለማቅረብ ትልቅ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸው፣ መሰል ዓለም አቀፍ የደህንነት ትብብሮች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አሳስበዋል።
የፎረሙ ሊቀመንበር ሮበርት ፒትንገር በበኩላቸው፣ ኢትዮጵያ ሽብርተኝነትን፣ ሕገወጥ የሰዎች ዝውውርንና ሌሎች ቀጣናዊ የፀጥታ ስጋቶችን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ውስጥ "እውነተኛ አጋር" መሆኗን በተግባር እያረጋገጠች የምትገኝ ሀገር ናት ሲሉ ገልጸዋል።
በሳደት መሀመድሳኒ
#ethiopianbroadcastingcorporation #parliamentaryintelligencesecurityforum #pisf2026 #securityforumafrica
**************
ዓለም አቀፉ የፓርላማ፣ መረጃና ደህንነት ፎረም በአዲስ አበባ ከተማ መካሄድ ጀምሯል። ፎረሙ በአፍሪካ ለሁለተኛ ጊዜ የተካሄደ ሲሆን አዲስ አበባም መድረኩን በማስተናገድ ሁለተኛዋ የአፍሪካ ከተማ ሆናለች።
ለሚቀጥሉት ሁለት ቀናት በሚቆየው በዚህ ጉባኤ ላይ ሽብርተኝነትን መከላከል፣ ቀጣናዊ ፀጥታ እንዲሁም የቴክኖሎጂ አጠቃቀም በዋናነት ትኩረት የተደረገባቸው ጉዳዮች ናቸው።
መድረኩን በንግግር የከፈቱት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ኢትዮጵያ ይህንን ዓለም አቀፍ ፎረም የምታስተናግደው 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ፍትሐዊና ግልጽ በሆነ መልኩ ባካሄደች ማግሥት መሆኑ ልዩ ትርጉም እንዳለው ገልጸዋል።
አፈ ጉባኤው አክለውም፣ በምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና የሚስተዋሉ የፀጥታ ችግሮችን ከጎረቤት ሀገራት ጋር በመተባበርና በቆራጥነት ለመከላከል ሀገራችን ሰፊ ሥራዎችን እያከናወነች እንደምትገኝ ጠቁመዋል።
በቴክኖሎጂው ዘርፍም ኢትዮጵያ አመርቂ ተግባራትን እያከናወነች መሆኑን ያብራሩት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የዲጂታልና የሳይበር ደህንነት ይበልጥ የተጠበቀ እንዲሆን በየጊዜው ከሚፈጠሩ አዳዲስ የቴክኖሎጂ ዕድገቶች ጋር ራስን በማላመድ ረገድ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን ለጉባኤው ተሳታፊዎች አስገንዝበዋል።
በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኢርቪንግ ማሲንጋ በበኩላቸው፣ ይህ ፎረም ሀገራት መረጃዎችን የጋራ በማድረግ የዜጎቻቸውን ደህንነት ለማረጋገጥና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀለኞችን ተከታትሎ ለሕግ ለማቅረብ ትልቅ ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ገልጸው፣ መሰል ዓለም አቀፍ የደህንነት ትብብሮች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አሳስበዋል።
የፎረሙ ሊቀመንበር ሮበርት ፒትንገር በበኩላቸው፣ ኢትዮጵያ ሽብርተኝነትን፣ ሕገወጥ የሰዎች ዝውውርንና ሌሎች ቀጣናዊ የፀጥታ ስጋቶችን ለመከላከል በሚደረገው ጥረት ውስጥ "እውነተኛ አጋር" መሆኗን በተግባር እያረጋገጠች የምትገኝ ሀገር ናት ሲሉ ገልጸዋል።
በሳደት መሀመድሳኒ
#ethiopianbroadcastingcorporation #parliamentaryintelligencesecurityforum #pisf2026 #securityforumafrica
29 days ago
ዓለም አቀፉ የፓርላማ የመረጃና ደህንነት ፎረም በአዲስ አበባ መካሄድ ጀመረ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዋና ትኩረቱን በፓርላማ አባላት፣ በመረጃ ባለሙያዎችና በመንግሥት ባለስልጣናት መካከል በዓለም አቀፍ የደህንነት ስጋቶች ዙሪያ ትብብር ለማጎልበት ያደረገ ዓለም አቀፉ የፓርላማ የመረጃና ደህንነት ፎረም መካሄድ ጀምሯል።
በፈረንጆቹ 2014 በአሜሪካ ኮንግረስ የቀድሞ አባል ሮበርት ፒቴንገር የተመሰረተው ፎረሙ፤ ዋና ተልዕኮው በሕግ አውጪው አካልና በአስፈፃሚው የመረጃና ደህንነት ተቋማት መካከል ያለውን ክፍተት ማጥበብ ነው።
በፎረሙ በፍጥነት እያደጉ የመጡ ድንበር ዘለል እና የቴክኖሎጂ ስጋቶችን ለመፍታት፣ የቀጣናውና የዓለም አቀፍ ሕግ አውጪዎችና የደህንነት ባለሙያዎች ይመክራሉ።
በዚህም ሕግና ቴክኖሎጂ የሚገናኙባቸውን የደህንነት ተግዳሮቶች መሠረት አድርጎ እንደሚመክር እና በዋናነት የሳይበር ደህንነት፣ ሕገወጥ ፋይናንስና ለሽብርተኝነት የሚውል የገንዘብ ምንጭን መከላከል እና ሕገወጥ የሰዎች ዝውውርን መከላከልን ጨምሮ ሌሎች ተዛማጅ ጉዳዮች ላይ ውይይት ይደረጋል።
በፎረሙ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የፓርላማ መረጃና ደህንነት ፎረም መስራቹ ሮበርት ፒቴንገር፣ የመንግስት ዋና ተጠሪ ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር)፣ የውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር)፣ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቬን ማሲንጋን ጨምሮ ከ43 ሀገራት የተውጣጡ የፓርላማ አባላት እየተሳተፉ ነው።
ፎረሙ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት ይካሄዳል።
በዓለምሰገድ አሳዬ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዋና ትኩረቱን በፓርላማ አባላት፣ በመረጃ ባለሙያዎችና በመንግሥት ባለስልጣናት መካከል በዓለም አቀፍ የደህንነት ስጋቶች ዙሪያ ትብብር ለማጎልበት ያደረገ ዓለም አቀፉ የፓርላማ የመረጃና ደህንነት ፎረም መካሄድ ጀምሯል።
በፈረንጆቹ 2014 በአሜሪካ ኮንግረስ የቀድሞ አባል ሮበርት ፒቴንገር የተመሰረተው ፎረሙ፤ ዋና ተልዕኮው በሕግ አውጪው አካልና በአስፈፃሚው የመረጃና ደህንነት ተቋማት መካከል ያለውን ክፍተት ማጥበብ ነው።
በፎረሙ በፍጥነት እያደጉ የመጡ ድንበር ዘለል እና የቴክኖሎጂ ስጋቶችን ለመፍታት፣ የቀጣናውና የዓለም አቀፍ ሕግ አውጪዎችና የደህንነት ባለሙያዎች ይመክራሉ።
በዚህም ሕግና ቴክኖሎጂ የሚገናኙባቸውን የደህንነት ተግዳሮቶች መሠረት አድርጎ እንደሚመክር እና በዋናነት የሳይበር ደህንነት፣ ሕገወጥ ፋይናንስና ለሽብርተኝነት የሚውል የገንዘብ ምንጭን መከላከል እና ሕገወጥ የሰዎች ዝውውርን መከላከልን ጨምሮ ሌሎች ተዛማጅ ጉዳዮች ላይ ውይይት ይደረጋል።
በፎረሙ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የፓርላማ መረጃና ደህንነት ፎረም መስራቹ ሮበርት ፒቴንገር፣ የመንግስት ዋና ተጠሪ ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር)፣ የውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር)፣ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቬን ማሲንጋን ጨምሮ ከ43 ሀገራት የተውጣጡ የፓርላማ አባላት እየተሳተፉ ነው።
ፎረሙ ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት ይካሄዳል።
በዓለምሰገድ አሳዬ
5 months ago
በኬንያ ታግተው የነበሩ 66 ኢትዮጵያውያን እና 4 ኤርትራውያን በፖሊስ ነጻ ወጡ
#ethiopia | የኬንያ ፖሊስ በናይሮቢ ዳርቻ በሚገኝ አንድ መኖሪያ ቤት ውስጥ በሕገ-ወጥ የሰዎች አጋቾች ታግተው የነበሩ 70 የውጭ ሀገር ዜጎችን ነጻ ማውጣቱን አስታወቀ። እንደ ፖሊስ መግለጫ ከሆነ፣ ነጻ ከወጡት መካከል 66ቱ ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ፣ ቀሪዎቹ 4ቱ ደግሞ ኤርትራውያን ናቸው።
የታጋቾቹ ሁኔታና መዳረሻ
ስደተኞቹ በናይሮቢ አቅራቢያ በሚገኘው ሩዋይ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ በአንድ ቤት ውስጥ ተቆልፎባቸው እንደነበር ፖሊስ በኤክስ (X) ገጹ ባወጣው መረጃ አመልክቷል። ተጎጂዎቹ ለጸጥታ አካላት በሰጡት ቃል፦
* ከሀገራቸው የወጡት በተለያዩ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ምክንያት መሆኑን ገልጸዋል።
* ዋና ዓላማቸው የተሻለ የሥራ ዕድል ፍለጋ ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመጓዝ የነበረ ቢሆንም፣ በመንገድ ላይ በአጋቾቹ እጅ መውደቃቸውን ተናግረዋል።
የፖሊስ እርምጃ
የኬንያ የጸጥታ አካላት በዚህ የወንጀል ተግባር ላይ ተሳትፎ አላቸው የተባሉ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋል ሰፊ ምርመራ እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም በድንበር አካባቢ የሚስተዋሉ ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ተግባራትን ለመከላከል ቁጥጥራቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል።
ይህ ክስተት በምሥራቅ አፍሪካ በኩል ወደ ደቡብ አፍሪካ የሚደረገው ሕገ-ወጥ ስደት አሁንም ለዜጎች ሕይወት አደገኛ መሆኑን በድጋሚ አመልክቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ኬንያ #ስደት #ኢትዮጵያ #ኤርትራ #ናይሮቢ #ሕገወጥ_የሰዎች_ዝውውር #kenya #ethiopia #humantrafficking #nairobi
#ethiopia | የኬንያ ፖሊስ በናይሮቢ ዳርቻ በሚገኝ አንድ መኖሪያ ቤት ውስጥ በሕገ-ወጥ የሰዎች አጋቾች ታግተው የነበሩ 70 የውጭ ሀገር ዜጎችን ነጻ ማውጣቱን አስታወቀ። እንደ ፖሊስ መግለጫ ከሆነ፣ ነጻ ከወጡት መካከል 66ቱ ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ፣ ቀሪዎቹ 4ቱ ደግሞ ኤርትራውያን ናቸው።
የታጋቾቹ ሁኔታና መዳረሻ
ስደተኞቹ በናይሮቢ አቅራቢያ በሚገኘው ሩዋይ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ በአንድ ቤት ውስጥ ተቆልፎባቸው እንደነበር ፖሊስ በኤክስ (X) ገጹ ባወጣው መረጃ አመልክቷል። ተጎጂዎቹ ለጸጥታ አካላት በሰጡት ቃል፦
* ከሀገራቸው የወጡት በተለያዩ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ምክንያት መሆኑን ገልጸዋል።
* ዋና ዓላማቸው የተሻለ የሥራ ዕድል ፍለጋ ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመጓዝ የነበረ ቢሆንም፣ በመንገድ ላይ በአጋቾቹ እጅ መውደቃቸውን ተናግረዋል።
የፖሊስ እርምጃ
የኬንያ የጸጥታ አካላት በዚህ የወንጀል ተግባር ላይ ተሳትፎ አላቸው የተባሉ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋል ሰፊ ምርመራ እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል። በተጨማሪም በድንበር አካባቢ የሚስተዋሉ ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ተግባራትን ለመከላከል ቁጥጥራቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል።
ይህ ክስተት በምሥራቅ አፍሪካ በኩል ወደ ደቡብ አፍሪካ የሚደረገው ሕገ-ወጥ ስደት አሁንም ለዜጎች ሕይወት አደገኛ መሆኑን በድጋሚ አመልክቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ኬንያ #ስደት #ኢትዮጵያ #ኤርትራ #ናይሮቢ #ሕገወጥ_የሰዎች_ዝውውር #kenya #ethiopia #humantrafficking #nairobi
7 months ago
645 ኪሎ ሜትር በተሽከርካሪ ወንበር ስር ተደብቆ የተጓዘው የ10 ዓመት ታዳጊ ሰውነቱ በጉዞው ተዳክሞ ባሰማው ድምፅ በሰላም ከወንበሩ ስር ወጣ
ከደምቢደሎ ተነስቶ ወደ አዲስ አበባ ይጓዝ በነበረ የህዝብ ማመላለሻ አውቶብስ ስር ተደብቆ፣ ከ645 ኪሎ ሜትር በላይ የተጓዘው የ10 ዓመት ታዳጊ በሰላም ተገኝቷል።
ታዳጊው ጉዞውን የጀመረው ከሌሊቱ 10 ሰዓት ደምቢደሎ ላይ ሲሆን፣ ማንም ሳይመለከተው በአውቶብሱ ስር ያሉ የብረት ክፍሎችን ሙጥኝ ብሎ በመያዝ ለአስር ሰዓታት ያህል አደገኛ ጉዞ አድርጓል። ታዳጊው ይህንን ሁሉ ርቀት ያለምንም ጉዳት መጓዙን መረጃዎች ያመለክታሉ።
አውቶብሱ አዲስ አበባ ሊገባ 40 ኪ.ሜ ሲቀረው ሆለታ አካባቢ፣ ከታችኛው የአውቶብሱ ክፍል የሰው የጣር እንግዳ ድምፅ የሰሙ ተሳፋሪዎች ለሾፌሩ ጥቆማ ይሰጣሉ። ተሽከርካሪው ቆሞ በተደረገ ፍተሻም፣ ታዳጊው ከአውቶብሱ እስር ብረት በመያዝ በህይወት ተገኝቷል። ጉዳዩ በአሁኑ ወቅት በአስኮ ፖሊስ ጣቢያ ሪፖርት የተደረገና እየተመረመረ ሲሆን፣ አሽከርካሪዎች ማንኛውንም ጉዞ ከመጀመራቸው በፊት የመኪናቸውን ደህንነትና ስር መፈተሽ እንዳለባቸው ትልቅ ትምህርት የተሰጠበት ሆኗል።
"ታዳጊው በጉዞው ላይ ጉዳት ደርሶበት ቢሆን ኖሮ ሾፌሩ ለከባድ የህግ ተጠያቂነት ይዳረግ ነበር፤ በመሆኑም ቅድመ ጥንቃቄ ወሳኝ ነው" ሲሉ ጉዳዩን የተከታተሉ አካላት ገልጸዋል።የተለያዩ ወንጀሎች ምርመራ አቃቢ ሕግ አብዮት አስፋ ማንኛውም አሽከርካሪ ሆነ ረዳት ተሽከርካሪው ከመንቀሳቀሱ በፊት አስፈላጊውን ፍተሻ ማድረግ የሚገባቸው ሲሆን ታዳጊው ይህን ያህል ኪሎ ሜትር በወንበር ስር ተጉዞ ሲመጣ ጥንቃቄ ያላደረጉ አሽከርካሪና ረዳት በሕገወጥ የሰዎች ዝውውር ና ድንበር የማሻገር ወንጀል ሊከሠሱ እንደሚችሉ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
በምህረት ታደሰ
#ዳጉ_ጆርናል
ከደምቢደሎ ተነስቶ ወደ አዲስ አበባ ይጓዝ በነበረ የህዝብ ማመላለሻ አውቶብስ ስር ተደብቆ፣ ከ645 ኪሎ ሜትር በላይ የተጓዘው የ10 ዓመት ታዳጊ በሰላም ተገኝቷል።
ታዳጊው ጉዞውን የጀመረው ከሌሊቱ 10 ሰዓት ደምቢደሎ ላይ ሲሆን፣ ማንም ሳይመለከተው በአውቶብሱ ስር ያሉ የብረት ክፍሎችን ሙጥኝ ብሎ በመያዝ ለአስር ሰዓታት ያህል አደገኛ ጉዞ አድርጓል። ታዳጊው ይህንን ሁሉ ርቀት ያለምንም ጉዳት መጓዙን መረጃዎች ያመለክታሉ።
አውቶብሱ አዲስ አበባ ሊገባ 40 ኪ.ሜ ሲቀረው ሆለታ አካባቢ፣ ከታችኛው የአውቶብሱ ክፍል የሰው የጣር እንግዳ ድምፅ የሰሙ ተሳፋሪዎች ለሾፌሩ ጥቆማ ይሰጣሉ። ተሽከርካሪው ቆሞ በተደረገ ፍተሻም፣ ታዳጊው ከአውቶብሱ እስር ብረት በመያዝ በህይወት ተገኝቷል። ጉዳዩ በአሁኑ ወቅት በአስኮ ፖሊስ ጣቢያ ሪፖርት የተደረገና እየተመረመረ ሲሆን፣ አሽከርካሪዎች ማንኛውንም ጉዞ ከመጀመራቸው በፊት የመኪናቸውን ደህንነትና ስር መፈተሽ እንዳለባቸው ትልቅ ትምህርት የተሰጠበት ሆኗል።
"ታዳጊው በጉዞው ላይ ጉዳት ደርሶበት ቢሆን ኖሮ ሾፌሩ ለከባድ የህግ ተጠያቂነት ይዳረግ ነበር፤ በመሆኑም ቅድመ ጥንቃቄ ወሳኝ ነው" ሲሉ ጉዳዩን የተከታተሉ አካላት ገልጸዋል።የተለያዩ ወንጀሎች ምርመራ አቃቢ ሕግ አብዮት አስፋ ማንኛውም አሽከርካሪ ሆነ ረዳት ተሽከርካሪው ከመንቀሳቀሱ በፊት አስፈላጊውን ፍተሻ ማድረግ የሚገባቸው ሲሆን ታዳጊው ይህን ያህል ኪሎ ሜትር በወንበር ስር ተጉዞ ሲመጣ ጥንቃቄ ያላደረጉ አሽከርካሪና ረዳት በሕገወጥ የሰዎች ዝውውር ና ድንበር የማሻገር ወንጀል ሊከሠሱ እንደሚችሉ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
በምህረት ታደሰ
#ዳጉ_ጆርናል
Sponsored by
Surafel
1 year ago
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) የሀዘን መግለጫ አወጣ::
በትናንትናው እለት፣ ሐምሌ 27፣ 2017 ዓ.ም. የዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (IMO) በሰጠው መግለጫ፣ በጀልባ ወደ የመን ሲያልፉ የነበሩ
ኢትዮጵያውያን ላይ በደረሰ አደጋ ምክንያት፣ 68 ወገኖቻችን ህይወታቸውን ማጣታቸው ተገልጿል።
ሌሎች 12 ሰዎች በህይወት ቢተርፉም፣ 74 ሰዎች እስካሁን ድረስ እንዳልተገኙ ተነግሯል።
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (#ኢዜማ) በዚህ አሰቃቂ አደጋ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጿል፤ ለሟች ቤተሰቦች፣ ዘመዶች እና ወዳጆች መፅናናትንም ተመኝቷል።
ከዚህ አሳዛኝ ሁኔታ ጋር በተያያዘም ኢዜማ
መንግስት ላይ የሚከተሉትን ጥያቄዎች አቅርቧል፦
1. ለስደት ምክንያት የሚሆኑ ችግሮች ይፈቱ:
* ዜጎች በሀገራቸው ተረጋግተው እንዳይኖሩ የሚያደርጉ ግጭቶችንና የሥራ አጥነትን በቅድሚያ እንዲፈታ።
* የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር፣ ህጋዊ በሆነ መንገድ በውጪ ሀገር መሥራት ለሚፈልጉ ዜጎች፣ ተገቢውን ሥልጠናና የጉዞ እድል አጥጋቢ በሆነ መንገድ እንዲያመቻች።
2. የሕገወጥ የሰዎች ዝውውር ወንጀለኞች ተጠያቂ ይሁኑ:
* መንግስት የሰውን ህይወት የሚያጠፉ ሕገወጥ ደላላዎችን እና አዘዋዋሪዎችን በሕግ እንዲጠይቅ።
በመጨረሻም፣ ኢዜማ የሀገራችን ዜጎች በሀገር ውስጥ ችግሮች ቢኖሩም፣ ከፍተኛ የጉዳት ስጋት ወዳለበት አደገኛ መንገድ ከመጓዝ ይልቅ፣ ደህንነቱ በተጠበቀ እና ሕጋዊ በሆነ መንገድ ብቻ እንዲጓዙ ጥሪ አቅርቧል።
የሟች እህት ወንድሞቻችን ነፍስ ይማር!
Via ኢዜማ
በትናንትናው እለት፣ ሐምሌ 27፣ 2017 ዓ.ም. የዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (IMO) በሰጠው መግለጫ፣ በጀልባ ወደ የመን ሲያልፉ የነበሩ
ኢትዮጵያውያን ላይ በደረሰ አደጋ ምክንያት፣ 68 ወገኖቻችን ህይወታቸውን ማጣታቸው ተገልጿል።
ሌሎች 12 ሰዎች በህይወት ቢተርፉም፣ 74 ሰዎች እስካሁን ድረስ እንዳልተገኙ ተነግሯል።
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (#ኢዜማ) በዚህ አሰቃቂ አደጋ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጿል፤ ለሟች ቤተሰቦች፣ ዘመዶች እና ወዳጆች መፅናናትንም ተመኝቷል።
ከዚህ አሳዛኝ ሁኔታ ጋር በተያያዘም ኢዜማ
መንግስት ላይ የሚከተሉትን ጥያቄዎች አቅርቧል፦
1. ለስደት ምክንያት የሚሆኑ ችግሮች ይፈቱ:
* ዜጎች በሀገራቸው ተረጋግተው እንዳይኖሩ የሚያደርጉ ግጭቶችንና የሥራ አጥነትን በቅድሚያ እንዲፈታ።
* የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር፣ ህጋዊ በሆነ መንገድ በውጪ ሀገር መሥራት ለሚፈልጉ ዜጎች፣ ተገቢውን ሥልጠናና የጉዞ እድል አጥጋቢ በሆነ መንገድ እንዲያመቻች።
2. የሕገወጥ የሰዎች ዝውውር ወንጀለኞች ተጠያቂ ይሁኑ:
* መንግስት የሰውን ህይወት የሚያጠፉ ሕገወጥ ደላላዎችን እና አዘዋዋሪዎችን በሕግ እንዲጠይቅ።
በመጨረሻም፣ ኢዜማ የሀገራችን ዜጎች በሀገር ውስጥ ችግሮች ቢኖሩም፣ ከፍተኛ የጉዳት ስጋት ወዳለበት አደገኛ መንገድ ከመጓዝ ይልቅ፣ ደህንነቱ በተጠበቀ እና ሕጋዊ በሆነ መንገድ ብቻ እንዲጓዙ ጥሪ አቅርቧል።
የሟች እህት ወንድሞቻችን ነፍስ ይማር!
Via ኢዜማ
Comments