የፍርድ ቤት መር አስማሚነት
ከባህላዊ እና ሃይማኖታዊ የሽምግልና ሥርዓት
#ethiopia | የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ተግባራዊ እያደረገ ያለውን የፍርድ ቤት መር አስማሚነት አሰራር ይበልጥ ለማጎልበት እና የህብረተሰቡን ተሳትፎ ከፍ ለማድረግ የሚያስችል የምክክር መድረክ ከድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽሕፈት ቤት ጋር በመተባበር ተካሄደ።
በውይይቱ ላይ የድሬዳዋ ከተማ የባህል ሽማግሌዎች፣ የአባ ገዳዎች፣ የኡጋዞች እና የሃይማኖት አባቶች ተገኝተዋል።
በመድረኩ ላይ የሃገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች በፍርድ ቤት መር አስማሚነት ሥርዓት ውስጥ በንቃት በመሳተፍ የፍትህ አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
በተለይም ድሬዳዋ የተለያዩ ብሔር ብሔረሰቦችና ሃይማኖቶች መኖሪያ እንደመሆኗ፣ ዘመናዊውን የፍርድ ቤት መር አስማሚነት ከባህላዊ ሽምግልና እና ሃይማኖታዊ እሴቶች ጋር አቀናጅቶ መሄድ አስፈላጊ እንደሆነ ተገልጿል።
በምክክር መድረኩ ላይ የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ፉአድ ኪያር እና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጁሃር ተገኝተዋል።
በቀጣይ ፍርድ ቤቱ ከከተማ አስተዳደሩ ጋር የመግባቢያ ስምምነት በመፈራረም፣ ለዘርፉ አዲስ ለሚቀላቀሉ አስማሚዎች የህግ እና የአሰራር ሥልጠና በመስጠት ወደ ተግባራዊ ትግበራ እንደሚገባ ታውቋል።
#ፍርድቤት #ፍትህ #ሽምግልና #ባህል #ሃይማኖት #ድሬዳዋ #ኢትዮጵያ #legal #mediation #culture #religion #diredawa #ethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
ከባህላዊ እና ሃይማኖታዊ የሽምግልና ሥርዓት
#ethiopia | የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ተግባራዊ እያደረገ ያለውን የፍርድ ቤት መር አስማሚነት አሰራር ይበልጥ ለማጎልበት እና የህብረተሰቡን ተሳትፎ ከፍ ለማድረግ የሚያስችል የምክክር መድረክ ከድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽሕፈት ቤት ጋር በመተባበር ተካሄደ።
በውይይቱ ላይ የድሬዳዋ ከተማ የባህል ሽማግሌዎች፣ የአባ ገዳዎች፣ የኡጋዞች እና የሃይማኖት አባቶች ተገኝተዋል።
በመድረኩ ላይ የሃገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች በፍርድ ቤት መር አስማሚነት ሥርዓት ውስጥ በንቃት በመሳተፍ የፍትህ አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
በተለይም ድሬዳዋ የተለያዩ ብሔር ብሔረሰቦችና ሃይማኖቶች መኖሪያ እንደመሆኗ፣ ዘመናዊውን የፍርድ ቤት መር አስማሚነት ከባህላዊ ሽምግልና እና ሃይማኖታዊ እሴቶች ጋር አቀናጅቶ መሄድ አስፈላጊ እንደሆነ ተገልጿል።
በምክክር መድረኩ ላይ የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ክቡር አቶ ፉአድ ኪያር እና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጁሃር ተገኝተዋል።
በቀጣይ ፍርድ ቤቱ ከከተማ አስተዳደሩ ጋር የመግባቢያ ስምምነት በመፈራረም፣ ለዘርፉ አዲስ ለሚቀላቀሉ አስማሚዎች የህግ እና የአሰራር ሥልጠና በመስጠት ወደ ተግባራዊ ትግበራ እንደሚገባ ታውቋል።
#ፍርድቤት #ፍትህ #ሽምግልና #ባህል #ሃይማኖት #ድሬዳዋ #ኢትዮጵያ #legal #mediation #culture #religion #diredawa #ethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 months ago