2 days ago
የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ።
በአማራ ክልል የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ሆኗል።
ከሰኔ 3-5/2018 ዓ.ም የተሰጠውን የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና 173,699 ተማሪዎች ውስደው ነበር።
ፈተናውን ከወሰዱት ተማሪዎች መካከልም 135,003 (77.72%) ተማሪዎች 50% እና በላይ ውጤት አስመዝግበዋል።
ተማሪዎችም ውጤታቸውን https://amhara.ministry.et... የሚለውን አድራሻ በመፃፍ ፤ በሚመጣው ቅጽ ላይ የተማሪ መለያ ቁጥር (Registration Number) እና ስም በአማርኛ በማስገባት ፤ ዉጤት ይመልከቱ (Check your result) የሚለውን ቁልፍ በመጫን ማየት ይችላሉ፡፡
በተጨማሪም emacs_ministry_result_qmt_bot ላይ መመልከት ይችላሉ።
ተማሪዎች ማንኛውም ከውጤት ጋር የተያያዘ ቅሬታ ካላቸው https://amhara.ministry.et... ላይ በመግባት ቅሬታቸው ማቅረብ እንደሚችሉ የክልሉ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።
2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ ይደረጋል ተብሏል።
tikvahethiopia
በአማራ ክልል የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ሆኗል።
ከሰኔ 3-5/2018 ዓ.ም የተሰጠውን የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና 173,699 ተማሪዎች ውስደው ነበር።
ፈተናውን ከወሰዱት ተማሪዎች መካከልም 135,003 (77.72%) ተማሪዎች 50% እና በላይ ውጤት አስመዝግበዋል።
ተማሪዎችም ውጤታቸውን https://amhara.ministry.et... የሚለውን አድራሻ በመፃፍ ፤ በሚመጣው ቅጽ ላይ የተማሪ መለያ ቁጥር (Registration Number) እና ስም በአማርኛ በማስገባት ፤ ዉጤት ይመልከቱ (Check your result) የሚለውን ቁልፍ በመጫን ማየት ይችላሉ፡፡
በተጨማሪም emacs_ministry_result_qmt_bot ላይ መመልከት ይችላሉ።
ተማሪዎች ማንኛውም ከውጤት ጋር የተያያዘ ቅሬታ ካላቸው https://amhara.ministry.et... ላይ በመግባት ቅሬታቸው ማቅረብ እንደሚችሉ የክልሉ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።
2018 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ ይደረጋል ተብሏል።
tikvahethiopia
11 days ago
በሽብር ወንጀል የተከሰሱት እነ አቶ ክርስቲያን ታደለ እና 52 ተከሳሾች የተከሰሱበትን ክስ ይከላከሉ ወይስ በነጻ ይሰናበቱ የሚለው ጉዳይ ላይ ብይን ሳይሰጥበት በድጋሚ ተራዘመ።
በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙት የቀድሞ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል አቶ ክርስቲያን ታደለ፣ የቀድሞ የአማራ ክልል ምክር ቤት አባል አቶ ዮሐንስ ቧያለው እንዲሁም ዶ/ር ካሳ ተሻገር፣ ዶ/ር ጫኔ ከበደን ጨምሮ በድምሩ 52 ተከሳሾች የፍርድ ውሳኔ ሳያገኙ ላለፉት ሦስት ዓመታት ገደማ በእስር ላይ ይገኛሉ።
ክሱ የተመሠረተው መጋቢት 2016 ዓ.ም ሲሆን፣ ጉዳዩ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሕገ መንግሥትና ፀረ-ሽብር ወንጀሎች ችሎት እየታየ ይገኛል።
ተከሳሾቹ በተለያዩ ወቅቶች ካለባቸው የጤና ችግር ጋር በተያያዘ፣ ከቤተሰብ ጥየቃ፣ ከሰብአዊ መብት ሁኔታ፣ እና ሌሎችም ደረሰብን በማለት በሚያቀርቧቸው ቅሬታዎች ዙሪያ ችሎቱ የተለያዩ ቀጠሮዎችን በመስጠት ጉዳያቸውን ሲመለከት የቆየ በመሆኑ የተከሰሱበትን ዋናው የክስ መዝገብን የማየት ሂደት በተለዋጭ ቀጠሮዎች ከ 4 ጊዜ በላይ ሲራዘም ቆይቷል።
በዋናው የሽብር ክስ መዝገብ ላይ ብይን ለመስጠት ቀደም ሲል ለሐምሌ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ቀጠሮ ተይዞ የነበረ ቢሆንም፣ ችሎቱ ጉዳዩን በተጨማሪ ዝግጅት አጠቃሎ ለማቅረብ ለዛሬ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ለተለዋጭ ቀጠሮ አስተላልፎት ነበር።
ችሎቱ ዛሬ የሚሰጠው ብይን ተከሳሾቹ የተከሰሱበትን ክስ ይከላከሉ ወይስ የነጻ ይሰናበቱ የሚለውን ጥያቄ የሚመልስ እንደሚሆን ቢጠበቅም በድጋሚ በተለዋጭ ቀጠሮ ለ ጥቅምት 6/2019 ዓም በመስጠት ውሳኔውን አራዝሞታል።
ፍርድ ቤቱ ብይኑን ማጠናቀቁን ገልጾ ነበር፤ ይሁን እንጂ የተወሰኑ ተከሳሾች በችሎት ባለመገኘታቸው ብይኑን ለንባብ ማቅረብ እንደማይችል በመግለጽ ንባቡን አላደረገም።
በዛሬው ችሎት ፍርድ ቤቱ ያሰማዋል ተብሎ ሲጠበቅ ከነበረው ብይን በተጨማሪ ከተከሳሾቹ አንዱ ከሆኑት ከዶ/ር ካሳ ተሻገር እና ከጋዜጠኛ ቴዎድሮስ ስልክ ቁጥር ጋር በተያያዘ ቁጥራቸውን ሌላ ሰው እየተጠቀመበት መሆኑን በመግለጽ ከእዚህ ቀደም በችሎቱ ያቀረቡትን ቅሬታ በተመለከተ ኢትዮ ቴሌኮም ለችሎቱ ይሰጠዋል ተብሎ የሚጠበቀውን ምላሽ የመስማት ጉዳይ ነበር።
ከዶ/ር ካሳ ተሻገር እና ከጋዜጠኛ ቴዎድሮስ ስልክ ቁጥሮች ጋር በተያያዘ ኢትዮ ቴሌኮም የላከውን ምላሽ ችሎቱ በንባብ አሰምቶታል።
በምላሹ መሠረት፣ የሁለቱ ተከሳሾች ስልክ ቁጥሮች ለረዥም ጊዜ ከአገልግሎት ውጭ በመቆየታቸው በኩባንያው አሠራር መሠረት ጊዜው አልፎበት (expire አድርጎ) ለሌሎች አዳዲስ ተጠቃሚዎች መዘዋወራቸውን ኢትዮ ቴሌኮም አረጋግጧል።
በዋናው ጉዳይ ላይ የሚጠበቀው ብይን ተከሳሾቹ አቃቤ ሕግ ባቀረበባቸው ማስረጃ ላይ ተመስርተው ክሱን ሊከላከሉ ይገባል ወይስ አቃቤ ሕግ ክሱን በበቂ ማስረጃ ስላላስረዳ በነጻ ሊሰናበቱ ይገባል የሚለውን ጥያቄ የሚመልስ ነው።
የተከሳሾች ጠበቃ የሆኑት አቶ ሰለሞን ገዛኸኝ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል "ተከሳሾቹ ከእዚህ ቀደም በችሎት ውሎዎች ላይ አቃቤ ሕግ ካቀረባቸው የድምጽ፣ የጽሑፍ እና የፎረንሲክ ማስረጃዎች ጋር በተያያዘ አስተያየታቸውን ማቅረባቸውን"ገልጸዋል።
ፍርድ ቤቱ የተከሳሾችን ይህን አስተያየት እና አቃቤ ሕግ ያቀረበውን ማስረጃ መርምሮ፣ ማስረጃው ክሱን በበቂ ሁኔታ የሚያስረዳ ሆኖ ካገኘው ተከሳሾቹ እንዲከላከሉ፣ ካላገኘውም ተከሳሾቹ ያለ ተጨማሪ ክርክር በነጻ እንዲሰናበቱ ብይን የሚሰጥበት ይሆናል ተብሎ ይጠበቅ ነበር ብለውናል።
ይሁን እንጂ ፍርድ ቤቱ የተከሳሾችን ሙሉ ተገኝነት መሠረት በማድረግ ብይኑን ወደ ጥቅምት 6 ቀን 2019 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቶ ችሎቱን ዘግቷል።
የበጀት ዓመቱ መጠናቀቁን ተከትሎ የዳኝነት አገልግሎት ክብደትና ውስብስብነት ከግምት ውስጥ በማስገባት የፌዴራል የመጀመሪያ፣ ከፍተኛና ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች በየአመቱ ከነሐሴ 1 እስከ መስከረም 30 ለ2 ወራት በከፊል ዝግ ሆነው የሚቆዩ መሆኑ ይታወቃል።
tikvahethiopia
በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙት የቀድሞ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል አቶ ክርስቲያን ታደለ፣ የቀድሞ የአማራ ክልል ምክር ቤት አባል አቶ ዮሐንስ ቧያለው እንዲሁም ዶ/ር ካሳ ተሻገር፣ ዶ/ር ጫኔ ከበደን ጨምሮ በድምሩ 52 ተከሳሾች የፍርድ ውሳኔ ሳያገኙ ላለፉት ሦስት ዓመታት ገደማ በእስር ላይ ይገኛሉ።
ክሱ የተመሠረተው መጋቢት 2016 ዓ.ም ሲሆን፣ ጉዳዩ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሕገ መንግሥትና ፀረ-ሽብር ወንጀሎች ችሎት እየታየ ይገኛል።
ተከሳሾቹ በተለያዩ ወቅቶች ካለባቸው የጤና ችግር ጋር በተያያዘ፣ ከቤተሰብ ጥየቃ፣ ከሰብአዊ መብት ሁኔታ፣ እና ሌሎችም ደረሰብን በማለት በሚያቀርቧቸው ቅሬታዎች ዙሪያ ችሎቱ የተለያዩ ቀጠሮዎችን በመስጠት ጉዳያቸውን ሲመለከት የቆየ በመሆኑ የተከሰሱበትን ዋናው የክስ መዝገብን የማየት ሂደት በተለዋጭ ቀጠሮዎች ከ 4 ጊዜ በላይ ሲራዘም ቆይቷል።
በዋናው የሽብር ክስ መዝገብ ላይ ብይን ለመስጠት ቀደም ሲል ለሐምሌ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ቀጠሮ ተይዞ የነበረ ቢሆንም፣ ችሎቱ ጉዳዩን በተጨማሪ ዝግጅት አጠቃሎ ለማቅረብ ለዛሬ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ለተለዋጭ ቀጠሮ አስተላልፎት ነበር።
ችሎቱ ዛሬ የሚሰጠው ብይን ተከሳሾቹ የተከሰሱበትን ክስ ይከላከሉ ወይስ የነጻ ይሰናበቱ የሚለውን ጥያቄ የሚመልስ እንደሚሆን ቢጠበቅም በድጋሚ በተለዋጭ ቀጠሮ ለ ጥቅምት 6/2019 ዓም በመስጠት ውሳኔውን አራዝሞታል።
ፍርድ ቤቱ ብይኑን ማጠናቀቁን ገልጾ ነበር፤ ይሁን እንጂ የተወሰኑ ተከሳሾች በችሎት ባለመገኘታቸው ብይኑን ለንባብ ማቅረብ እንደማይችል በመግለጽ ንባቡን አላደረገም።
በዛሬው ችሎት ፍርድ ቤቱ ያሰማዋል ተብሎ ሲጠበቅ ከነበረው ብይን በተጨማሪ ከተከሳሾቹ አንዱ ከሆኑት ከዶ/ር ካሳ ተሻገር እና ከጋዜጠኛ ቴዎድሮስ ስልክ ቁጥር ጋር በተያያዘ ቁጥራቸውን ሌላ ሰው እየተጠቀመበት መሆኑን በመግለጽ ከእዚህ ቀደም በችሎቱ ያቀረቡትን ቅሬታ በተመለከተ ኢትዮ ቴሌኮም ለችሎቱ ይሰጠዋል ተብሎ የሚጠበቀውን ምላሽ የመስማት ጉዳይ ነበር።
ከዶ/ር ካሳ ተሻገር እና ከጋዜጠኛ ቴዎድሮስ ስልክ ቁጥሮች ጋር በተያያዘ ኢትዮ ቴሌኮም የላከውን ምላሽ ችሎቱ በንባብ አሰምቶታል።
በምላሹ መሠረት፣ የሁለቱ ተከሳሾች ስልክ ቁጥሮች ለረዥም ጊዜ ከአገልግሎት ውጭ በመቆየታቸው በኩባንያው አሠራር መሠረት ጊዜው አልፎበት (expire አድርጎ) ለሌሎች አዳዲስ ተጠቃሚዎች መዘዋወራቸውን ኢትዮ ቴሌኮም አረጋግጧል።
በዋናው ጉዳይ ላይ የሚጠበቀው ብይን ተከሳሾቹ አቃቤ ሕግ ባቀረበባቸው ማስረጃ ላይ ተመስርተው ክሱን ሊከላከሉ ይገባል ወይስ አቃቤ ሕግ ክሱን በበቂ ማስረጃ ስላላስረዳ በነጻ ሊሰናበቱ ይገባል የሚለውን ጥያቄ የሚመልስ ነው።
የተከሳሾች ጠበቃ የሆኑት አቶ ሰለሞን ገዛኸኝ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል "ተከሳሾቹ ከእዚህ ቀደም በችሎት ውሎዎች ላይ አቃቤ ሕግ ካቀረባቸው የድምጽ፣ የጽሑፍ እና የፎረንሲክ ማስረጃዎች ጋር በተያያዘ አስተያየታቸውን ማቅረባቸውን"ገልጸዋል።
ፍርድ ቤቱ የተከሳሾችን ይህን አስተያየት እና አቃቤ ሕግ ያቀረበውን ማስረጃ መርምሮ፣ ማስረጃው ክሱን በበቂ ሁኔታ የሚያስረዳ ሆኖ ካገኘው ተከሳሾቹ እንዲከላከሉ፣ ካላገኘውም ተከሳሾቹ ያለ ተጨማሪ ክርክር በነጻ እንዲሰናበቱ ብይን የሚሰጥበት ይሆናል ተብሎ ይጠበቅ ነበር ብለውናል።
ይሁን እንጂ ፍርድ ቤቱ የተከሳሾችን ሙሉ ተገኝነት መሠረት በማድረግ ብይኑን ወደ ጥቅምት 6 ቀን 2019 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቶ ችሎቱን ዘግቷል።
የበጀት ዓመቱ መጠናቀቁን ተከትሎ የዳኝነት አገልግሎት ክብደትና ውስብስብነት ከግምት ውስጥ በማስገባት የፌዴራል የመጀመሪያ፣ ከፍተኛና ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች በየአመቱ ከነሐሴ 1 እስከ መስከረም 30 ለ2 ወራት በከፊል ዝግ ሆነው የሚቆዩ መሆኑ ይታወቃል።
tikvahethiopia
25 days ago
" ህጋዊው የውል ማሻሻያ ለ2 ዓመታት ይቆያል " - ቢሮው
በአዲስ አበባ የ2019 በጀት ዓመት የቤት ኪራይ ዓመታዊ የጭማሪ ጣሪያ 11.5 በመቶ ሆኖ እንዲጸድቅ መደረጉ ይታወሳል።
ከዚህ ተመን በላይ መጨመር በጥብቅ የተከለከለ ሲሆን ህጋዊው የውል ማሻሻያም ለ2 ዓመታት ይቆያል ሲል የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ አሳውቋል።
ከህጋዊ አሰራር ውጪ የሚደረጉ "የመንደር ውሎች" የተከለከሉ ሲሆን ውል በማያድሱና ህግ በሚተላለፉ አካላት ላይ ቅጣት ይጣላል።
የውል እድሳት ጊዜያቸው አልፎ አከራይም ተከራይም አብረው ኖረው እድሳት ሳይፈጽሙ እስከ 2 ወር ከቆዩ የ1 ወር የቤት ኪራይ ቅጣት ይጣልባቸዋል።
ውል ሳያድሱ 3 ወር እና ከዚያ በላይ የቆዩ የ2 ወር የቤት ኪራይ ቅጣት ይከፍላሉ።
አዲስ ተከራይ አስገብተው ውል ያላደሱ እና ያላስመዘገቡ የ1 ወር የቤት ኪራይ ይቀጣሉ።
በጥቆማ ወይም በክትትል ውል ያላደሱ ወይም ያላስመዘገቡ መሆናቸው ከተረጋገጠ ደግሞ ከ1 እስከ 3 ወር የሚደርስ የኪራይ መጠን ቅጣት እንደሚጣልባቸው ቢሮው አሳውቋል።
የቤት ኪራይ የውል እድሳት በክፍለ ከተማ፣ በወረዳ ጽህፈት ቤቶች ወይም በ"መሶብ" ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫዎች ማከናወን ይቻላል ተብሏል።
tikvahethiopia
በአዲስ አበባ የ2019 በጀት ዓመት የቤት ኪራይ ዓመታዊ የጭማሪ ጣሪያ 11.5 በመቶ ሆኖ እንዲጸድቅ መደረጉ ይታወሳል።
ከዚህ ተመን በላይ መጨመር በጥብቅ የተከለከለ ሲሆን ህጋዊው የውል ማሻሻያም ለ2 ዓመታት ይቆያል ሲል የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ አሳውቋል።
ከህጋዊ አሰራር ውጪ የሚደረጉ "የመንደር ውሎች" የተከለከሉ ሲሆን ውል በማያድሱና ህግ በሚተላለፉ አካላት ላይ ቅጣት ይጣላል።
የውል እድሳት ጊዜያቸው አልፎ አከራይም ተከራይም አብረው ኖረው እድሳት ሳይፈጽሙ እስከ 2 ወር ከቆዩ የ1 ወር የቤት ኪራይ ቅጣት ይጣልባቸዋል።
ውል ሳያድሱ 3 ወር እና ከዚያ በላይ የቆዩ የ2 ወር የቤት ኪራይ ቅጣት ይከፍላሉ።
አዲስ ተከራይ አስገብተው ውል ያላደሱ እና ያላስመዘገቡ የ1 ወር የቤት ኪራይ ይቀጣሉ።
በጥቆማ ወይም በክትትል ውል ያላደሱ ወይም ያላስመዘገቡ መሆናቸው ከተረጋገጠ ደግሞ ከ1 እስከ 3 ወር የሚደርስ የኪራይ መጠን ቅጣት እንደሚጣልባቸው ቢሮው አሳውቋል።
የቤት ኪራይ የውል እድሳት በክፍለ ከተማ፣ በወረዳ ጽህፈት ቤቶች ወይም በ"መሶብ" ዲጂታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫዎች ማከናወን ይቻላል ተብሏል።
tikvahethiopia
1 month ago
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሐምሌ 8/2018 ዓ/ም ለሚጀመረው ሀገራዊ ጉባዔ ለምክክር የቀረጻቸውን 8 አጀንዳዎች ይፋ አድርጓል።
ምክክር የሚደረግባቸው 8 የተመረጡ አጀንዳዎች የትኞቹ ናቸው ?
1) አጀንዳ ቁጥር 1 የሀገር ግንባታ ጉዳይ፣
2) አጀንዳ ቁጥር 2 የፖለቲካ ስርዓት፣ የመንግስት አደረጃጀትና ቅርጽ፣
3) አጀንዳ ቁጥር 3 የፌዴራል ከተሞች፥ አዲስ አበባና ድሬዳዋ
4) አጀንዳ ቁጥር 4 የሃይማኖት ጉዳዮች፣
5) አጀንዳ ቁጥር 5 የተቋማት ግንባታ የሕግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች፣
6) አጀንዳ ቁጥር 6 ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች፣ የአርሶ አደሮች እና የአርብቶ አደሮች ጉዳይ፣
7) አጀንዳ ቁጥር 7 ሙስና እና መልካም አስተዳደር
8) አጀንዳ ቁጥር 8 ሰላም ግንባታ
አጀንዳዎቹ በተለያዩ ክልሎች ከ200 ሺሕ በላይ ሰዎችን በማመካከር የተገኙ መሆናቸውን የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ ተናግረዋል።tikvah
Seledadotio
Seledadotio
ምክክር የሚደረግባቸው 8 የተመረጡ አጀንዳዎች የትኞቹ ናቸው ?
1) አጀንዳ ቁጥር 1 የሀገር ግንባታ ጉዳይ፣
2) አጀንዳ ቁጥር 2 የፖለቲካ ስርዓት፣ የመንግስት አደረጃጀትና ቅርጽ፣
3) አጀንዳ ቁጥር 3 የፌዴራል ከተሞች፥ አዲስ አበባና ድሬዳዋ
4) አጀንዳ ቁጥር 4 የሃይማኖት ጉዳዮች፣
5) አጀንዳ ቁጥር 5 የተቋማት ግንባታ የሕግ የበላይነትና ሰብዓዊ መብቶች፣
6) አጀንዳ ቁጥር 6 ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች፣ የአርሶ አደሮች እና የአርብቶ አደሮች ጉዳይ፣
7) አጀንዳ ቁጥር 7 ሙስና እና መልካም አስተዳደር
8) አጀንዳ ቁጥር 8 ሰላም ግንባታ
አጀንዳዎቹ በተለያዩ ክልሎች ከ200 ሺሕ በላይ ሰዎችን በማመካከር የተገኙ መሆናቸውን የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ ተናግረዋል።tikvah
Seledadotio
Seledadotio
2 months ago
የታክስ ተመላሽ ክፍያ በጊዜ ገደቡ ካልተፈጸመ ባለሥልጣኑ ለከፋዩ ወለዱን ጨምሮ እንዲከፍል የሚያስገድድ መመሪያ ወጥቷል።
የገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ ተመላሽ አሰጣጥ ሥርዓትን ግልጽነትና ተጠያቂነት ባለው መልኩ ለመምራት ያስችላል ያለውን "የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመላሽ የሚደረግበትን ሁኔታ ለመወሰን የወጣ መመሪያ ቁጥር 1132/2018" አውጥቷል።
ይህ አዲስ መመሪያ የወጣው ቀደም ሲል የነበረው የታክስ አዋጅ ተሽሮ በአዲሱ የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ቁጥር 1341/2016 መተካቱን ተከትሎ ሲሆን፣ ዋና ዓላማውም የታክስ ተመላሽ አገልግሎትን የታክስ ከፋዮችን የስጋት ደረጃ መሠረት ባደረገ መልኩ ዘመናዊ ለማድረግ ነው።
መመሪያው የታክስ ተመላሽ ጥያቄ የሚያቀርቡ ከፋዮችን በሦስት ዋና ዋና የስጋት ደረጃዎች የሚከፍል ሲሆን፣ ይህም የኦዲትና የማጣራት ሥራው በታማኝ ከፋዮች ላይ የሚፈጥረውን እንግልት ለመቀነስ ያለመ ነው ይላል።
በዚህም መሠረት ዝቅተኛ የስጋት ደረጃ ያላቸው ከፋዮች ሰፊ ኦዲት ሳይደረግባቸው በተፋጠነ ሁኔታ ተመላሽ የሚያገኙበት ሥርዓት ሲዘረጋ፣ መካከለኛና ከፍተኛ የስጋት ደረጃ ላይ የሚገኙ ከፋዮች ደግሞ እንደሁኔታው ዝርዝርና ጥብቅ የሰነድ ማጣራት እንዲሁም የኦዲት ምርመራ ይደረግባቸዋል።
ይህም በመንግሥት ገቢ ላይ ሊፈጠር የሚችለውን አሉታዊ ተፅዕኖ ለመከላከልና ተገቢው የታክስ ተመላሽ ለትክክለኛው ከፋይ መድረሱን ለማረጋገጥ ይረዳል ይላል።
በመመሪያው ዝርዝር አፈጻጸም መሠረት፣ በዜሮ የማስከፈያ ልክ ምርቶቻቸውን ወደ ውጭ ለሚልኩ አምራቾች፣ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ወርቅ ለሚያቀርቡና ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ የካፒታል ዕቃ ግዥ ለፈጸሙ ከፋዮች ልዩ ትኩረት ሰጥቷል።
በተለይም በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ተመርጠው ወደ ውጭ ላኪነት የተሰማሩ አምራቾች ምርታቸውን ወደ ውጭ ከመላካቸው በፊት በሀገር ውስጥ ለገዟቸው ግብዓቶች የከፈሉት ታክስ በሰባት ቀናት ውስጥ የሚመለስበት "የተፋጠነ የተመላሽ ሥርዓት" ተዘርግቷል።
ሌሎች መደበኛ የተመላሽ ጥያቄዎች ደግሞ አስፈላጊው ማጣራት ተደርጎባቸው በአርባ አምስት ቀናት ውስጥ ውሳኔ እንዲያገኙ በመመሪያው ተደንግጓል።
የታክስ ተመላሽ ጥያቄ የሚያቀርቡ አካላት ሊያሟሏቸው የሚገቡ ጥብቅ ቅድመ ሁኔታዎችም በመመሪያው የተካተቱ ሲሆን ከእነዚህም መካከል ግብይቱ የተፈጸመባቸው ሕጋዊ ኦርጅናል ደረሰኞች፣ የባንክ ክፍያ ማረጋገጫዎችና ሌሎች ተያያዥ ሰነዶች ይገኙበታል።
መመሪያው በተለየ ሁኔታ ካስቀመጣቸው ነጥቦች መካከል፣ ከሐምሌ 1 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ከ50,000 (ሃምሳ ሺህ) ብር በላይ የሆኑ ማናቸውም ግብይቶች በባንክ በኩል ካልተፈጸሙና የጥሬ ገንዘብ ግብይት ገደብን ካላለፉ ለታክስ ተመላሽ ጥያቄ ተቀባይነት እንደማይኖራቸው በግልጽ አስፍሯል።
የታክስ ባለሥልጣኑ (ገቢዎች ሚኒስቴር) ተመላሽ ሊደረግ የሚገባውን ገንዘብ በሕጉ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ሳይከፍል ከዘገየ፣ ለከፋዩ የወለድ ክፍያ የመክፈል ግዴታ የሚኖርበት መሆኑን መመሪያው ያዛል።
ወለዱ የተመላሸ ሒሣብ መከፈል ከነበረበት አግባብነት ካለው ጊዜ መጨረሻ ጀምሮ ተመላሹ ሒሣብ እስከተከፈለ ድረስ ላለው ጊዜ የሚሰላ ሲሆን የወለድ ምጣኔውም በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ ባንኮች የንግድ ብድር የሚሰጡበት ከፍተኛው የወለድ ምጣኔ መሰረት ይሆናል፡፡
ወለዱን ለመክፈል አግባብ ላለው ፍ/ቤት ቀርቦ የተሰጠ ውሳኔ ማስረጃ በማያያዝ ውሳኔው በተሰጠበት በ6 ወራት ጊዜ ውስጥ መቅረብ አለበት፤በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ያልቀረበ ጥያቄ መብቱ እንደተወ እንደሚቆጠር መመሪያው ደንግጓል፡፡
ይህ መመሪያ በፍትህ ሚኒስቴር ተመዝግቦ የጸደቀ መሆኑን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከገቢዎች ሚኒስቴር አረጋግጧል።Via : tikvah
Seledadotio
Seledadotio
የገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ ተመላሽ አሰጣጥ ሥርዓትን ግልጽነትና ተጠያቂነት ባለው መልኩ ለመምራት ያስችላል ያለውን "የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመላሽ የሚደረግበትን ሁኔታ ለመወሰን የወጣ መመሪያ ቁጥር 1132/2018" አውጥቷል።
ይህ አዲስ መመሪያ የወጣው ቀደም ሲል የነበረው የታክስ አዋጅ ተሽሮ በአዲሱ የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ቁጥር 1341/2016 መተካቱን ተከትሎ ሲሆን፣ ዋና ዓላማውም የታክስ ተመላሽ አገልግሎትን የታክስ ከፋዮችን የስጋት ደረጃ መሠረት ባደረገ መልኩ ዘመናዊ ለማድረግ ነው።
መመሪያው የታክስ ተመላሽ ጥያቄ የሚያቀርቡ ከፋዮችን በሦስት ዋና ዋና የስጋት ደረጃዎች የሚከፍል ሲሆን፣ ይህም የኦዲትና የማጣራት ሥራው በታማኝ ከፋዮች ላይ የሚፈጥረውን እንግልት ለመቀነስ ያለመ ነው ይላል።
በዚህም መሠረት ዝቅተኛ የስጋት ደረጃ ያላቸው ከፋዮች ሰፊ ኦዲት ሳይደረግባቸው በተፋጠነ ሁኔታ ተመላሽ የሚያገኙበት ሥርዓት ሲዘረጋ፣ መካከለኛና ከፍተኛ የስጋት ደረጃ ላይ የሚገኙ ከፋዮች ደግሞ እንደሁኔታው ዝርዝርና ጥብቅ የሰነድ ማጣራት እንዲሁም የኦዲት ምርመራ ይደረግባቸዋል።
ይህም በመንግሥት ገቢ ላይ ሊፈጠር የሚችለውን አሉታዊ ተፅዕኖ ለመከላከልና ተገቢው የታክስ ተመላሽ ለትክክለኛው ከፋይ መድረሱን ለማረጋገጥ ይረዳል ይላል።
በመመሪያው ዝርዝር አፈጻጸም መሠረት፣ በዜሮ የማስከፈያ ልክ ምርቶቻቸውን ወደ ውጭ ለሚልኩ አምራቾች፣ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ወርቅ ለሚያቀርቡና ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ የካፒታል ዕቃ ግዥ ለፈጸሙ ከፋዮች ልዩ ትኩረት ሰጥቷል።
በተለይም በኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ተመርጠው ወደ ውጭ ላኪነት የተሰማሩ አምራቾች ምርታቸውን ወደ ውጭ ከመላካቸው በፊት በሀገር ውስጥ ለገዟቸው ግብዓቶች የከፈሉት ታክስ በሰባት ቀናት ውስጥ የሚመለስበት "የተፋጠነ የተመላሽ ሥርዓት" ተዘርግቷል።
ሌሎች መደበኛ የተመላሽ ጥያቄዎች ደግሞ አስፈላጊው ማጣራት ተደርጎባቸው በአርባ አምስት ቀናት ውስጥ ውሳኔ እንዲያገኙ በመመሪያው ተደንግጓል።
የታክስ ተመላሽ ጥያቄ የሚያቀርቡ አካላት ሊያሟሏቸው የሚገቡ ጥብቅ ቅድመ ሁኔታዎችም በመመሪያው የተካተቱ ሲሆን ከእነዚህም መካከል ግብይቱ የተፈጸመባቸው ሕጋዊ ኦርጅናል ደረሰኞች፣ የባንክ ክፍያ ማረጋገጫዎችና ሌሎች ተያያዥ ሰነዶች ይገኙበታል።
መመሪያው በተለየ ሁኔታ ካስቀመጣቸው ነጥቦች መካከል፣ ከሐምሌ 1 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ከ50,000 (ሃምሳ ሺህ) ብር በላይ የሆኑ ማናቸውም ግብይቶች በባንክ በኩል ካልተፈጸሙና የጥሬ ገንዘብ ግብይት ገደብን ካላለፉ ለታክስ ተመላሽ ጥያቄ ተቀባይነት እንደማይኖራቸው በግልጽ አስፍሯል።
የታክስ ባለሥልጣኑ (ገቢዎች ሚኒስቴር) ተመላሽ ሊደረግ የሚገባውን ገንዘብ በሕጉ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ሳይከፍል ከዘገየ፣ ለከፋዩ የወለድ ክፍያ የመክፈል ግዴታ የሚኖርበት መሆኑን መመሪያው ያዛል።
ወለዱ የተመላሸ ሒሣብ መከፈል ከነበረበት አግባብነት ካለው ጊዜ መጨረሻ ጀምሮ ተመላሹ ሒሣብ እስከተከፈለ ድረስ ላለው ጊዜ የሚሰላ ሲሆን የወለድ ምጣኔውም በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ ባንኮች የንግድ ብድር የሚሰጡበት ከፍተኛው የወለድ ምጣኔ መሰረት ይሆናል፡፡
ወለዱን ለመክፈል አግባብ ላለው ፍ/ቤት ቀርቦ የተሰጠ ውሳኔ ማስረጃ በማያያዝ ውሳኔው በተሰጠበት በ6 ወራት ጊዜ ውስጥ መቅረብ አለበት፤በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ያልቀረበ ጥያቄ መብቱ እንደተወ እንደሚቆጠር መመሪያው ደንግጓል፡፡
ይህ መመሪያ በፍትህ ሚኒስቴር ተመዝግቦ የጸደቀ መሆኑን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከገቢዎች ሚኒስቴር አረጋግጧል።Via : tikvah
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
3 months ago
ኢትዮጵያውያን ላይ የተጣለው የአውሮፓ ቪዛ ገደብ በይፋ ተነሳ
አውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጥሎ የነበረው የቪዛ ገደብ በመነሳቱ የሼንገን (Schengen) ቪዛ አሰራር ዳግም ተግባራዊ ሆኗል።
የቪዛ ሂደቱ ወደ ቀድሞው መደበኛ ጊዜ ተመልሷል።
የባለ ብዙ ጊዜ መግቢያ (Multiple-entry) ቪዛዎች ላይ ተጥለው የነበሩ ገደቦች ተነስተው እንደ ቀድሞው በመደበኛ ደንቦች እንዲስተናገዱ ተደርጓል።
tikvahethiopia
አውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያውያን ላይ ጥሎ የነበረው የቪዛ ገደብ በመነሳቱ የሼንገን (Schengen) ቪዛ አሰራር ዳግም ተግባራዊ ሆኗል።
የቪዛ ሂደቱ ወደ ቀድሞው መደበኛ ጊዜ ተመልሷል።
የባለ ብዙ ጊዜ መግቢያ (Multiple-entry) ቪዛዎች ላይ ተጥለው የነበሩ ገደቦች ተነስተው እንደ ቀድሞው በመደበኛ ደንቦች እንዲስተናገዱ ተደርጓል።
tikvahethiopia
3 months ago
ካሴሚሮ ዛሬ ክለቡን ይሰናበታል !
#ethiopia | ብራዚላዊው አማካይ ካሴሚሮ በውድድር አመቱ መጨረሻ ማንችስተር ዩናይትድን እንደሚለቅ ይታወቃል።
ካሴሚሮ ዛሬ በኦልድትራፎርድ ስታዲየም የማንችስተር ዩናይትድ የመጨረሻ ጨዋታውን ያደርጋል።
ይህንንም ተከትሎ ዛሬ በስታዲየሙ ክለቡን በይፋ እንደሚሰናበት ተገልጿል።
“ ማንችስተር ዩናይትድን ለመቀላቀል መወሰኔ የህይወቴ ምርጡ ውሳኔ ነው ደጋፊ ሆኜ እቀጥላለሁ “ ሲል ካሴሚሮ ተናግሯል።
ደጋፊውን “ ከዚህ በፊት አይቼው የማላውቀው ነው “ ያለው ካሴሚሮ ሁልጊዜ ስንሸነፍ በቀጣዩ ጨዋታ የተሻለ ድጋፍ ነው የሚሰጡን አስደናቂ ነው ብሏል።
“ የአምስት አመት ልጄ የማንችስተር ዩናይትድ ደጋፊ ነው የክለቡን ሁሉንም ዜማዎች ያውቃለ ቡድኑ ሲሸነፍ ያለቅሳል “ ካሴሚሮ
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu #tikvah #sport #united
#ethiopia | ብራዚላዊው አማካይ ካሴሚሮ በውድድር አመቱ መጨረሻ ማንችስተር ዩናይትድን እንደሚለቅ ይታወቃል።
ካሴሚሮ ዛሬ በኦልድትራፎርድ ስታዲየም የማንችስተር ዩናይትድ የመጨረሻ ጨዋታውን ያደርጋል።
ይህንንም ተከትሎ ዛሬ በስታዲየሙ ክለቡን በይፋ እንደሚሰናበት ተገልጿል።
“ ማንችስተር ዩናይትድን ለመቀላቀል መወሰኔ የህይወቴ ምርጡ ውሳኔ ነው ደጋፊ ሆኜ እቀጥላለሁ “ ሲል ካሴሚሮ ተናግሯል።
ደጋፊውን “ ከዚህ በፊት አይቼው የማላውቀው ነው “ ያለው ካሴሚሮ ሁልጊዜ ስንሸነፍ በቀጣዩ ጨዋታ የተሻለ ድጋፍ ነው የሚሰጡን አስደናቂ ነው ብሏል።
“ የአምስት አመት ልጄ የማንችስተር ዩናይትድ ደጋፊ ነው የክለቡን ሁሉንም ዜማዎች ያውቃለ ቡድኑ ሲሸነፍ ያለቅሳል “ ካሴሚሮ
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu #tikvah #sport #united
3 months ago
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለሚወስዱ ተፈታኞች
ከመጪው ሰኔ 24/2018 ዓ/ም ጀምሮ የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለሚወስዱ ተፈታኞች የተዘጋጀ የመፈተኛ ክፍል መግቢያ ካርድ (Admission Card) በፈተና አስተዳደር ሲስተም (https://exam.eaes.et/) ከ03/09/2018 ዓ/ም ጀምሮ ለክልል ትምህርት ቢሮ፣ ለዞን ትምህርት መምሪያዎች እና ለትምህርት ቤት ተወካዮች መለቀቁን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
አገልግሎት መ/ቤቱ ፦
1. እያንዳንዱ ተፈታኝ ተማሪ በአድሚሽን ካርዱ ጀርባ ላይ የትምህርት ቤቱን ወይም የወረዳው አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት ማህተም የተደረገበትን አድሚሽን ካርድ ከትምህርት ቤቱ ወስዶ በእጁ መያዝ መያዝ እንዳለበት አሳስቧል።
2. በምዝገባ ወቅት በተፈታኙ ወይም በመዝጋቢው የተከሰተ የትምህርት መስክ ፣ የጾታ ፣ የፎቶ እና መሰል ማስተካከያዎች ካሉ ከግንቦት 30/2018 ዓ.ም በፊት ለትምህርት ቤቱ ማሳወቅና ሂደቱን ጠብቆ መስተካከሉንም ከትምህርት ቤቱ ማረጋገጥ እንደሚገባ ገልጿል።
3. እያንዳንዱ ተፈታኝ አድሚሽን ካርዱን ወደ መፈተኛ ማዕከል ሆነ መፈተኛ ክፍል ለመግባት የሚጠቀምበት በመሆኑ በአግባቡና በጥንቃቄ እንዲይዝ አሳስቧል።
4. ተፈታኞች ፈተና ላይ ከአድሚሽን ካርድ በተጨማሪ የፋይዳ መታወቂያ መያዝ እንደሚጠበቅባቸው ገልጿል።
tikvahethiopia
ከመጪው ሰኔ 24/2018 ዓ/ም ጀምሮ የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለሚወስዱ ተፈታኞች የተዘጋጀ የመፈተኛ ክፍል መግቢያ ካርድ (Admission Card) በፈተና አስተዳደር ሲስተም (https://exam.eaes.et/) ከ03/09/2018 ዓ/ም ጀምሮ ለክልል ትምህርት ቢሮ፣ ለዞን ትምህርት መምሪያዎች እና ለትምህርት ቤት ተወካዮች መለቀቁን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
አገልግሎት መ/ቤቱ ፦
1. እያንዳንዱ ተፈታኝ ተማሪ በአድሚሽን ካርዱ ጀርባ ላይ የትምህርት ቤቱን ወይም የወረዳው አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት ማህተም የተደረገበትን አድሚሽን ካርድ ከትምህርት ቤቱ ወስዶ በእጁ መያዝ መያዝ እንዳለበት አሳስቧል።
2. በምዝገባ ወቅት በተፈታኙ ወይም በመዝጋቢው የተከሰተ የትምህርት መስክ ፣ የጾታ ፣ የፎቶ እና መሰል ማስተካከያዎች ካሉ ከግንቦት 30/2018 ዓ.ም በፊት ለትምህርት ቤቱ ማሳወቅና ሂደቱን ጠብቆ መስተካከሉንም ከትምህርት ቤቱ ማረጋገጥ እንደሚገባ ገልጿል።
3. እያንዳንዱ ተፈታኝ አድሚሽን ካርዱን ወደ መፈተኛ ማዕከል ሆነ መፈተኛ ክፍል ለመግባት የሚጠቀምበት በመሆኑ በአግባቡና በጥንቃቄ እንዲይዝ አሳስቧል።
4. ተፈታኞች ፈተና ላይ ከአድሚሽን ካርድ በተጨማሪ የፋይዳ መታወቂያ መያዝ እንደሚጠበቅባቸው ገልጿል።
tikvahethiopia
3 months ago
በ'ፊንቴክ ኢንቨስትመንት' የማጭበርበር ወንጀል የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች የዋስትና መብታቸው እንዲከበርላቸው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ወሰነ።
ሆኖም ችሎቱ ተጠርጣሪዎች ለዋስትና የሚያቀርቡትን የገንዘብ መጠን ለመወሰን ለሰኞ ግንቦት 3/2018 ዓም ቀነ ቀጠሮ ሰጥቷል።
አቃቢ ህግ በበኩሉ አምስተኛ ተከሳሽ ከሆነው መንሱር ጀማል በቀር የዋስትና መብታቸው ቢከበር እንደማይቃወም ለችሎቱ አሳውቋል።
ችሎቱ በበኩሉ አቃቢ ህግ በአምስተኛ ተከሳሽ መንሱር ጀማል ዋስትና ጉዳይ ላይ አቃቢ ህግ ያለውን ተቃውሞ በጽሁፍ ለግንቦት ሦስት እንዲያቀርብ ትእዛዝ ሰጥቷል።
tikvahethiopia
ሆኖም ችሎቱ ተጠርጣሪዎች ለዋስትና የሚያቀርቡትን የገንዘብ መጠን ለመወሰን ለሰኞ ግንቦት 3/2018 ዓም ቀነ ቀጠሮ ሰጥቷል።
አቃቢ ህግ በበኩሉ አምስተኛ ተከሳሽ ከሆነው መንሱር ጀማል በቀር የዋስትና መብታቸው ቢከበር እንደማይቃወም ለችሎቱ አሳውቋል።
ችሎቱ በበኩሉ አቃቢ ህግ በአምስተኛ ተከሳሽ መንሱር ጀማል ዋስትና ጉዳይ ላይ አቃቢ ህግ ያለውን ተቃውሞ በጽሁፍ ለግንቦት ሦስት እንዲያቀርብ ትእዛዝ ሰጥቷል።
tikvahethiopia
3 months ago
በውጭ የሚኖሩ ዜጎች የፋይዳ መታወቂያ ቁጥርን ከባንክ ሂሳብ ጋር ለማስተሳሰር‼️
የባንክ ሂሳብን ከፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ ቁጥር ጋር በማስተሳሰሩ ሂደት በውጭ ለሚኖሩ ዜጎች የማረጋገጫ ኮድ (OTP) በኢሜል የሚላክበት አሰራር መኖሩን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አሳውቋል።
የፕሮግራሙ የምዝገባ ኦፕሬሽን መሪ አቶ ሄኖክ ጥላሁን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ማብራሪያ፣ ዜጎች መረጃቸውን በኢሜል ጭምር በማስመዝገብ ከርቀት አገልግሎቱን ማግኘት እንደሚችሉ ገልጸዋል።
ብዙዎች የሚጠይቁትን “ ከሀገር ውጭ ያለን ሰዎች የማረጋገጫ ኮድ (OTP) በስልካችን ካልመጣልን ምን እናድርግ ? ” የሚለውን ስጋት በተመለከተ አቶ ሄኖክ ሲመልሱ “ ኢሜል ያላችሁ ሰዎች በፋይዳ ምዝገባቸው ላይ ኢሜላቸውን አብረው እንዲያስመዘግቡ በጣም ነው የምናበረታታው፣ ስልክ ቁጥሩ በተለያየ ምክንያት ቢጠፋ ወይም በኔትወርክ ምክንያት መልዕክት ባይቀበል፣ የማረጋገጫ ኮዱ (OTP) ወዲያውኑ አብሮ ኢሜሉን ላስመዘገበ ሰው ወደ ኢሜሉ ይገባል ” ብለዋል።
እንደ ሃላፊው ገለጻ፣ በአሁኑ ወቅት በርካታ ዜጎች በውጭ ሀገር ሆነው የኢሜል አማራጭን በመጠቀም የባንክ ሂሳባቸውንና የፋይዳ ቁጥራቸውን “ሀርሞናይዝ” እያደረጉ ይገኛሉ።
ይህ አገልግሎት እያንዳንዱ ባንክ ጋር በዲጂታል አማራጮች ስለተተገበረ፣ ተገልጋዮች በኢትዮጵያ ወሰን ውስጥ ብቻ ሳይሆኑ በየትኛውም የዓለም ክፍል ሆነው የባንክ ቅርንጫፍ መሄድ ሳያስፈልጋቸው መስተናገድ እንደሚችሉ ተገልጿል።
ፋይዳ ተመዝግበው ኢሜል ያላስመዘገቡ ካሉም " በፋይዳ የመረጃ ማሻሻያ ስርዓት ላይ መረጃ ማሻሻል እያደረጉ ኢሜላቸውን ቢያስገቡ ለሌላ ጊዜም ሲፈልጉት ይጠቅማቸዋል " ብለዋል።
በውጭ ሀገር የሚኖሩና እስካሁን የፋይዳ መታወቂያ ያልወሰዱ ዜጎችን በተመለከተም ኦፕሬሽን መሪው ማብራሪያ ሰጥተዋል።
አቶ ሄኖክ በአሁኑ ወቅት የፋይዳ ምዝገባ በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች (አቡዳቢና ዱባይ) ብቻ የተጀመረ በመሆኑ፣ በሌሎች ሀገራት ያሉ ዜጎች ባንኮች በሚጠይቋቸው መረጃዎች መሰረት ከዚህ አስገዳጅ ትስስር ለጊዜው ነፃ (Exempt) ሊደረጉ የሚችሉበት አሰራር መዘርጋቱን ጠቁመዋል።
“ ደንበኞቻቸው ውጭ ሀገር ነዋሪ ከሆኑና ሀገር ውስጥ የሌሉ መሆኑን የሚያስረዳ መረጃ ካቀረቡ፣ ከዚህ ትስስር ነፃ እንዲደረጉ ብሔራዊ ባንክ ለእያንዳንዱ ባንክ ሰርኩላር ልኳል ስለዚህ ውጭ ያሉ ሰዎች ስጋት እንዳይገባቸው ” ሲሉ አቶ ሄኖክ አረጋግጠዋል።
ሆኖም ለሚቀጥሉት ስድስት ወራት ትራንዛክሽናቸው እንዳይገደብ የተመቻቸ ቢሆንም፣ ወደ ሀገር ቤት በሚመጡበት ጊዜ ግን ምዝገባውን እንዲያከናውኑ መክረዋል።
አቶ ሄኖክ የብሄራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አገልግሎቱን በውጭ ሀገራት ለማስፋፋት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ጠቁመዋል።
በአሁኑ ወቅት ከ25 በላይ በሚሆኑ ዋና ዋና ከተሞች የባንክ ሂሳብን ከፋይዳ ጋር የማስተሳሰር የጊዜ ገደብ እስከ ግንቦት 6 ቀን መሆኑን ያስታወቁት ኦፕሬሽን መሪው፣ ተገልጋዮች የመጨረሻውን ቀን ጠብቀው ከሚፈጠር መጨናነቅ እንዲቆጠቡ አሳስበዋል።
" ጊዜው ሊያልቅ አንድ ቀን ሲቀረው የሚታየው ሩጫ አላስፈላጊ መጨናነቅንና በሲስተም ላይ ጫናን ያመጣል ዛሬ ይህንን መረጃ የሚሰሙ ሰዎች ጊዜ ሳይወስዱ አሁኑኑ የማስተሳሰር ስራቸውን እንዲያከናውኑ እንጠይቃለን ፣ ሂደቱ አምስት ደቂቃ እንኳን የማይወስድና በጣም ምቹ ነው " ሲሉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
በመረጃዎች መካከል ልዩነት (ለምሳሌ በስም አጻጻፍ ወይም በልደት ቀን) ካለ፣ ተገልጋዮች በፋይዳ የመረጃ ማሻሻያ (Update) ስርአት በመጠቀም በፍጥነት ማስተካከል እንደሚችሉና የማስተሳሰር ሂደቱም በመላ ሀገሪቱ እስከ ሰኔ 30 ቀን ድረስ መጠናቀቅ እንዳለበት አሳስበዋል።
#tikvah
seledadotio
seledadotio
የባንክ ሂሳብን ከፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ ቁጥር ጋር በማስተሳሰሩ ሂደት በውጭ ለሚኖሩ ዜጎች የማረጋገጫ ኮድ (OTP) በኢሜል የሚላክበት አሰራር መኖሩን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አሳውቋል።
የፕሮግራሙ የምዝገባ ኦፕሬሽን መሪ አቶ ሄኖክ ጥላሁን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ማብራሪያ፣ ዜጎች መረጃቸውን በኢሜል ጭምር በማስመዝገብ ከርቀት አገልግሎቱን ማግኘት እንደሚችሉ ገልጸዋል።
ብዙዎች የሚጠይቁትን “ ከሀገር ውጭ ያለን ሰዎች የማረጋገጫ ኮድ (OTP) በስልካችን ካልመጣልን ምን እናድርግ ? ” የሚለውን ስጋት በተመለከተ አቶ ሄኖክ ሲመልሱ “ ኢሜል ያላችሁ ሰዎች በፋይዳ ምዝገባቸው ላይ ኢሜላቸውን አብረው እንዲያስመዘግቡ በጣም ነው የምናበረታታው፣ ስልክ ቁጥሩ በተለያየ ምክንያት ቢጠፋ ወይም በኔትወርክ ምክንያት መልዕክት ባይቀበል፣ የማረጋገጫ ኮዱ (OTP) ወዲያውኑ አብሮ ኢሜሉን ላስመዘገበ ሰው ወደ ኢሜሉ ይገባል ” ብለዋል።
እንደ ሃላፊው ገለጻ፣ በአሁኑ ወቅት በርካታ ዜጎች በውጭ ሀገር ሆነው የኢሜል አማራጭን በመጠቀም የባንክ ሂሳባቸውንና የፋይዳ ቁጥራቸውን “ሀርሞናይዝ” እያደረጉ ይገኛሉ።
ይህ አገልግሎት እያንዳንዱ ባንክ ጋር በዲጂታል አማራጮች ስለተተገበረ፣ ተገልጋዮች በኢትዮጵያ ወሰን ውስጥ ብቻ ሳይሆኑ በየትኛውም የዓለም ክፍል ሆነው የባንክ ቅርንጫፍ መሄድ ሳያስፈልጋቸው መስተናገድ እንደሚችሉ ተገልጿል።
ፋይዳ ተመዝግበው ኢሜል ያላስመዘገቡ ካሉም " በፋይዳ የመረጃ ማሻሻያ ስርዓት ላይ መረጃ ማሻሻል እያደረጉ ኢሜላቸውን ቢያስገቡ ለሌላ ጊዜም ሲፈልጉት ይጠቅማቸዋል " ብለዋል።
በውጭ ሀገር የሚኖሩና እስካሁን የፋይዳ መታወቂያ ያልወሰዱ ዜጎችን በተመለከተም ኦፕሬሽን መሪው ማብራሪያ ሰጥተዋል።
አቶ ሄኖክ በአሁኑ ወቅት የፋይዳ ምዝገባ በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች (አቡዳቢና ዱባይ) ብቻ የተጀመረ በመሆኑ፣ በሌሎች ሀገራት ያሉ ዜጎች ባንኮች በሚጠይቋቸው መረጃዎች መሰረት ከዚህ አስገዳጅ ትስስር ለጊዜው ነፃ (Exempt) ሊደረጉ የሚችሉበት አሰራር መዘርጋቱን ጠቁመዋል።
“ ደንበኞቻቸው ውጭ ሀገር ነዋሪ ከሆኑና ሀገር ውስጥ የሌሉ መሆኑን የሚያስረዳ መረጃ ካቀረቡ፣ ከዚህ ትስስር ነፃ እንዲደረጉ ብሔራዊ ባንክ ለእያንዳንዱ ባንክ ሰርኩላር ልኳል ስለዚህ ውጭ ያሉ ሰዎች ስጋት እንዳይገባቸው ” ሲሉ አቶ ሄኖክ አረጋግጠዋል።
ሆኖም ለሚቀጥሉት ስድስት ወራት ትራንዛክሽናቸው እንዳይገደብ የተመቻቸ ቢሆንም፣ ወደ ሀገር ቤት በሚመጡበት ጊዜ ግን ምዝገባውን እንዲያከናውኑ መክረዋል።
አቶ ሄኖክ የብሄራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አገልግሎቱን በውጭ ሀገራት ለማስፋፋት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ጠቁመዋል።
በአሁኑ ወቅት ከ25 በላይ በሚሆኑ ዋና ዋና ከተሞች የባንክ ሂሳብን ከፋይዳ ጋር የማስተሳሰር የጊዜ ገደብ እስከ ግንቦት 6 ቀን መሆኑን ያስታወቁት ኦፕሬሽን መሪው፣ ተገልጋዮች የመጨረሻውን ቀን ጠብቀው ከሚፈጠር መጨናነቅ እንዲቆጠቡ አሳስበዋል።
" ጊዜው ሊያልቅ አንድ ቀን ሲቀረው የሚታየው ሩጫ አላስፈላጊ መጨናነቅንና በሲስተም ላይ ጫናን ያመጣል ዛሬ ይህንን መረጃ የሚሰሙ ሰዎች ጊዜ ሳይወስዱ አሁኑኑ የማስተሳሰር ስራቸውን እንዲያከናውኑ እንጠይቃለን ፣ ሂደቱ አምስት ደቂቃ እንኳን የማይወስድና በጣም ምቹ ነው " ሲሉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
በመረጃዎች መካከል ልዩነት (ለምሳሌ በስም አጻጻፍ ወይም በልደት ቀን) ካለ፣ ተገልጋዮች በፋይዳ የመረጃ ማሻሻያ (Update) ስርአት በመጠቀም በፍጥነት ማስተካከል እንደሚችሉና የማስተሳሰር ሂደቱም በመላ ሀገሪቱ እስከ ሰኔ 30 ቀን ድረስ መጠናቀቅ እንዳለበት አሳስበዋል።
#tikvah
seledadotio
seledadotio
3 months ago
''አርሰናል ዋንጫውን ማንሳት ይገባዋል" — አርሴን ቬንገር
#ethiopia | የቀድሞው የአርሰናል ዝነኛ አሰልጣኝ አርሴን ቬንገር ክለቡ በሻምፒዮንስ ሊግ መድረክ አዲስ ታሪክ መፃፍ እንደሚችል ያላቸውን ፅኑ እምነት ገልጸዋል።
ቬንገር ለአርሰናል ደጋፊዎች ወሳኝ ምሽት መሆኑን በመጠቆም፣ አሁን ያለው ስብስብ ታላቅ ታሪክ የመስራት አቅም እንዳለው ተናግረዋል። ክለቡ በውድድሩ ካለው የቆየና በህመም የተሞላ ታሪክ አንፃር፣ "ዋንጫው ወደ አርሰናል መሄድ አለበት" ሲሉ አፅንኦት ሰጥተዋል።
አሰልጣኙ አክለውም "ዋንጫው ለአርሰናል ይገባዋል" በማለት ለቀድሞ ክለባቸው ያላቸውን ድጋፍና ለቡድኑ ያላቸውን ከፍተኛ ግምት በይፋ አጋርተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu #tikvah #arsenal #championsleague #arsenewenger #footballnews #gunners #ucl #አርሰናል #ስፖርት #አርሴንቬንገር
#ethiopia | የቀድሞው የአርሰናል ዝነኛ አሰልጣኝ አርሴን ቬንገር ክለቡ በሻምፒዮንስ ሊግ መድረክ አዲስ ታሪክ መፃፍ እንደሚችል ያላቸውን ፅኑ እምነት ገልጸዋል።
ቬንገር ለአርሰናል ደጋፊዎች ወሳኝ ምሽት መሆኑን በመጠቆም፣ አሁን ያለው ስብስብ ታላቅ ታሪክ የመስራት አቅም እንዳለው ተናግረዋል። ክለቡ በውድድሩ ካለው የቆየና በህመም የተሞላ ታሪክ አንፃር፣ "ዋንጫው ወደ አርሰናል መሄድ አለበት" ሲሉ አፅንኦት ሰጥተዋል።
አሰልጣኙ አክለውም "ዋንጫው ለአርሰናል ይገባዋል" በማለት ለቀድሞ ክለባቸው ያላቸውን ድጋፍና ለቡድኑ ያላቸውን ከፍተኛ ግምት በይፋ አጋርተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu #tikvah #arsenal #championsleague #arsenewenger #footballnews #gunners #ucl #አርሰናል #ስፖርት #አርሴንቬንገር
Sponsored by
Surafel
3 months ago
የነዳጅ ዋጋ ጨምሯል
ነጭ ናፍጣ በሊትር 180.46 ብር ገብቷል። ቤንዚንም በሊትር 167.50 ብር ሆኗል።
ከዛሬ ሚያዚያ 26 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምሮ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሪ መደረጉን ማደያዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።
የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ደብዳቤ፣ የዓለም የነዳጅ ዋጋን መሰረት በማድረግ ከሚያዚያ 23 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽት 12:00 ሰዓት ጀምሮ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሬ መደረጉን ያስረዳል።
በደብዳቤው በተገለጸው መሰረት በሊትር፦
- ነጭ ናፍጣ 180.46 ብር
- ቤንዚን 167.50 ብር
- ኬሮሲን 320.66 ብር
- ቀላል ጥቁር ናፍጣ 170.62 ብር
- ከባድ ጥቁር ናፍጣ 167.37 ብር
- የአውሮፕላን ነዳጅ 319.76 ብር ሆኗል።
በተጨማሪም ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ በቅሎ ቤት ፣ ሳሪስ አካባቢ ባሉ ማደያዎች ቅኝት ያደረገ ሲሆን፣ ማደያዎቹ ሽያጭ እያከናወኑ ያሉት በተሻሻለው ዋጋ መሰረት ነው።
የማደያዎቹ ሠራተኞች ቤንዚን 167.50 ብር፣ ነጭ ናፍጣ 180.46 ብር እየሸጡ፣ ሹፌሮችም በዚሁ መሰረት እየቀዱ መሆኑን አረጋግጠዋል።
በነዳጅ ምርቶች ላይ ከአንድ ወር በፊት የዋጋ ጭማሪ ተደርጎ ነበር።
tikvahethiopia
ነጭ ናፍጣ በሊትር 180.46 ብር ገብቷል። ቤንዚንም በሊትር 167.50 ብር ሆኗል።
ከዛሬ ሚያዚያ 26 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምሮ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሪ መደረጉን ማደያዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።
የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ደብዳቤ፣ የዓለም የነዳጅ ዋጋን መሰረት በማድረግ ከሚያዚያ 23 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽት 12:00 ሰዓት ጀምሮ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሬ መደረጉን ያስረዳል።
በደብዳቤው በተገለጸው መሰረት በሊትር፦
- ነጭ ናፍጣ 180.46 ብር
- ቤንዚን 167.50 ብር
- ኬሮሲን 320.66 ብር
- ቀላል ጥቁር ናፍጣ 170.62 ብር
- ከባድ ጥቁር ናፍጣ 167.37 ብር
- የአውሮፕላን ነዳጅ 319.76 ብር ሆኗል።
በተጨማሪም ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ በቅሎ ቤት ፣ ሳሪስ አካባቢ ባሉ ማደያዎች ቅኝት ያደረገ ሲሆን፣ ማደያዎቹ ሽያጭ እያከናወኑ ያሉት በተሻሻለው ዋጋ መሰረት ነው።
የማደያዎቹ ሠራተኞች ቤንዚን 167.50 ብር፣ ነጭ ናፍጣ 180.46 ብር እየሸጡ፣ ሹፌሮችም በዚሁ መሰረት እየቀዱ መሆኑን አረጋግጠዋል።
በነዳጅ ምርቶች ላይ ከአንድ ወር በፊት የዋጋ ጭማሪ ተደርጎ ነበር።
tikvahethiopia
3 months ago
" በአደባባይና በጎዳና ላይ የሚካሄድ የሃይማኖት ስብከት ይቁም " - ጉባኤው
የመቐለ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዛሬ ሰኞ ሚያዝያ 26/2018 በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ በአደባባይና ጎዳና ላይ የሚካሄድ የሃይማኖት ስብከት እንዲቆም አሳስቧል።
ጉባኤው በመቐለ አደባባዮችና ጎዳናዎች ከተለመደው ባፈነገጠ መልኩ በድምፅ ማጉያ የተደገፉ የሃይማኖት ስብከቶች እየታዩ መሆኑን ጠቅሶ፤ ተፈናቃዮች ቀያቸውን ለቀው በስቃይ ባሉበትና ህዝቡ በከባድ ችግር ውስጥ በተዘፈቀበት ሁኔታ በሃይማኖት ሽፋን ሰላም የሚያውኩ አካላት አደብ መግዛት እንዳለባቸው በአፅንኦት ገልጿል።
ህዝብ እና ተሸከርካሪዎች በብዛት በሚንቀሳቀሱባቸው ቦታዎች ከህዝብ ፈቃድ ውጪ በድምፅ ማጉያ የሚካሄድ ስብከት መቆም እንዳለበት አሳስቧል።
በተለያዩ አማኞች መኖሪያና የአምልኮ ቦታዎች ድንጋይ የመወርወር፣ በመጥፎ ቃላት የማንቋሸሽና አካል የማጉደል ተግባራት እንዳሉና ይህን ከጅምሩ ሥርዓት ማስያዝ እንደሚገባ አሳስቧል።
ማንኛውም ሰው በሚከተለው ሃይማኖት ምክንያት ለስድብና አካል ጉዳት መዳረግ ሃይማኖት የሚፃረር ተግባር በመሆኑ አንዱ የሌላውን ክብርና እሴት ከሚጎዳ ስብከት መቆጠብ እንዳለበትና ህዝቡ ካለበት ተደራራቢ ፈተና አንጻር በሃይማኖት ሽፋን ሌላ መከራ መጋበዝ እንደማይገባ መክሯል።
ይህ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ፣ የእስልምና ፣ የካቶሊክና የወንጌላውያን አማኞች በጋራ ያቋቋሙት ነው።
tikvahethiopia
የመቐለ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዛሬ ሰኞ ሚያዝያ 26/2018 በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ በአደባባይና ጎዳና ላይ የሚካሄድ የሃይማኖት ስብከት እንዲቆም አሳስቧል።
ጉባኤው በመቐለ አደባባዮችና ጎዳናዎች ከተለመደው ባፈነገጠ መልኩ በድምፅ ማጉያ የተደገፉ የሃይማኖት ስብከቶች እየታዩ መሆኑን ጠቅሶ፤ ተፈናቃዮች ቀያቸውን ለቀው በስቃይ ባሉበትና ህዝቡ በከባድ ችግር ውስጥ በተዘፈቀበት ሁኔታ በሃይማኖት ሽፋን ሰላም የሚያውኩ አካላት አደብ መግዛት እንዳለባቸው በአፅንኦት ገልጿል።
ህዝብ እና ተሸከርካሪዎች በብዛት በሚንቀሳቀሱባቸው ቦታዎች ከህዝብ ፈቃድ ውጪ በድምፅ ማጉያ የሚካሄድ ስብከት መቆም እንዳለበት አሳስቧል።
በተለያዩ አማኞች መኖሪያና የአምልኮ ቦታዎች ድንጋይ የመወርወር፣ በመጥፎ ቃላት የማንቋሸሽና አካል የማጉደል ተግባራት እንዳሉና ይህን ከጅምሩ ሥርዓት ማስያዝ እንደሚገባ አሳስቧል።
ማንኛውም ሰው በሚከተለው ሃይማኖት ምክንያት ለስድብና አካል ጉዳት መዳረግ ሃይማኖት የሚፃረር ተግባር በመሆኑ አንዱ የሌላውን ክብርና እሴት ከሚጎዳ ስብከት መቆጠብ እንዳለበትና ህዝቡ ካለበት ተደራራቢ ፈተና አንጻር በሃይማኖት ሽፋን ሌላ መከራ መጋበዝ እንደማይገባ መክሯል።
ይህ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ፣ የእስልምና ፣ የካቶሊክና የወንጌላውያን አማኞች በጋራ ያቋቋሙት ነው።
tikvahethiopia
3 months ago
ኃላፊው በተሾሙ በ45 ቀናት ተነሱ።
የትግራይ የመገናኛ ብዙሃን ኤጀንሲ ስራ አስኪያጅ በተሾሙ በ45 ቀናት ውስጥ ከኃላፊነት መነሳታቸው ምንጮች ገለፁ።
ለስራ አስኪያጁ ቅርበት ያላቸው ምንጮች እንደገለፁት የካቲት 30/2018 ዓ/ም የኤጀንሲው ስራ አስኪያጅ ሆኖው የተሸሙት አባዲ ገ/ስላሴ ከሃላፊነታቸው ተነስተዋል።
ሚያዝያ 16/2018 ዓ.ም በፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀ) የተፃፈው ደብዳቤ እንደሚያመለክተው ሃላፊው በሁለት መስመር ፅሁፍ ከሃላፊነታቸው እንዲነሱ ተደርገዋል።
ሃላፊው በተሾሙ በ45 ቀናት ውስጥ ለምን ከሃላፊነት እንደተነሱ በደብዳቤው በግልፅ ባይቀመጥም ስራ አስኪያጁ " ወደ ህወሓት በማዳላት የጊዚያዊ አስተዳደሩ ስራ አደናቅፈዋል " በሚል ምክንያት እንደሆነ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ምንጮች ጠቁመዋል።
ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀ) ሚያዝያ 13/2018 ዓ.ም ለሚድያ የሰጡት መግለጫ በክልሉ መንግስታዊ ሚድያዎች ተዛብቶ መሰራጨቱ በመግለፅና በመወቀስ Landa Report እና ላዛ ትግርኛ ለተባሉ የግል ሚድያዎች ሚያዝያ 14/2018 ዓ.ም ተጨማሪ ማስተካከያና ማብራርያ መስጠታቸው ይታወሳል።
ቴሌቪዥን ጣብያው የፕሮግራሞች ዳይሬክተር ጋዜጠኛ አፈወርቂ ገ/ሂወት የስራ አስኪያጁ ስራ ደርበው እንዲሰሩ ከፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀ) ደብዳቤ እንደደረሳቸው ሰምተናል።
አባዲ ገ/ስላሴ ከጦርነት በፊት እና በኋላ የትግራይ ቴሌቬዥንን ለረጅም ዓመታት የመሩት ተሻለ በቀለ ተክተው መሾማቸው መዘገባችን ይታወሳል።
tikvahethiopia
የትግራይ የመገናኛ ብዙሃን ኤጀንሲ ስራ አስኪያጅ በተሾሙ በ45 ቀናት ውስጥ ከኃላፊነት መነሳታቸው ምንጮች ገለፁ።
ለስራ አስኪያጁ ቅርበት ያላቸው ምንጮች እንደገለፁት የካቲት 30/2018 ዓ/ም የኤጀንሲው ስራ አስኪያጅ ሆኖው የተሸሙት አባዲ ገ/ስላሴ ከሃላፊነታቸው ተነስተዋል።
ሚያዝያ 16/2018 ዓ.ም በፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀ) የተፃፈው ደብዳቤ እንደሚያመለክተው ሃላፊው በሁለት መስመር ፅሁፍ ከሃላፊነታቸው እንዲነሱ ተደርገዋል።
ሃላፊው በተሾሙ በ45 ቀናት ውስጥ ለምን ከሃላፊነት እንደተነሱ በደብዳቤው በግልፅ ባይቀመጥም ስራ አስኪያጁ " ወደ ህወሓት በማዳላት የጊዚያዊ አስተዳደሩ ስራ አደናቅፈዋል " በሚል ምክንያት እንደሆነ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ምንጮች ጠቁመዋል።
ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀ) ሚያዝያ 13/2018 ዓ.ም ለሚድያ የሰጡት መግለጫ በክልሉ መንግስታዊ ሚድያዎች ተዛብቶ መሰራጨቱ በመግለፅና በመወቀስ Landa Report እና ላዛ ትግርኛ ለተባሉ የግል ሚድያዎች ሚያዝያ 14/2018 ዓ.ም ተጨማሪ ማስተካከያና ማብራርያ መስጠታቸው ይታወሳል።
ቴሌቪዥን ጣብያው የፕሮግራሞች ዳይሬክተር ጋዜጠኛ አፈወርቂ ገ/ሂወት የስራ አስኪያጁ ስራ ደርበው እንዲሰሩ ከፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀ) ደብዳቤ እንደደረሳቸው ሰምተናል።
አባዲ ገ/ስላሴ ከጦርነት በፊት እና በኋላ የትግራይ ቴሌቬዥንን ለረጅም ዓመታት የመሩት ተሻለ በቀለ ተክተው መሾማቸው መዘገባችን ይታወሳል።
tikvahethiopia
3 months ago
አቶ ዳዊት ገበየሁ እና አቶ ገደኖ ካዋይታ ተፈረደባቸው።
⚫ ለተፈናቀሉ ወገኖች ድጋፍ እንዲሆን የተለገሰ 6,594 የቤት ክዳን ቆርቆሮ ተሸጦ ለግል ጥቅም ውሏል ፤ 3,702,466.67 ብር ነው ተሽጦ የተበላው።
የኮንሶ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የቀድሞ የኮንሶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የነበሩት አቶ ዳዊት ገበየሁ እና የግብርና መምሪያ የአደጋ ስጋትና ስራ አመራር ኃላፊ የነበሩት አቶ ገደኖ ካዋይታ ላይ የፍርድ ውሳኔ ማሳለፉን የፍርድ ቤቱ ፕሬዚዳንት አቶ ሙሀባ ቀውያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
ግለሰቦቹ " የመንግስትን የሥራ ኃላፊነት በማይመች አኳኋን መምራት እና የሙስና ወንጀል " ጥፋተኛ መሆናቸውን ፍርድ ቤቱ አረጋግጧል ሲሉ ፕሬዚዳንቱ አሳውቀዋል።
ተከሳሾቹ በ2014 ዓ.ም በኮንሶ ዞን ሰገን ዙሪያ ወረዳ በግጭት ምክንያት ለተፈናቀሉ ወገኖች ድጋፍ እንዲሆን ከኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን የተለገሰውን 6,594 የቤት ክዳን ቆርቆሮ ሸጠው ለግል ጥቅማቸው ማዋላቸው በማስረጃ መረጋገጡን አቶ ሙሀባ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል።
ተከሳሾች ለግል ጥቅማቸው ያዋሉት ሀብት ግምቱ ብር 3,702,466.67 (ሶስት ሚሊዮን ሰባት መቶ ሁለት ሺህ አራት መቶ ስልሳ ስልስት ብር ከስልስ ሰባት ሳንቲም) መሆኑን ጠቅሰው ፤ የተገኘው ጥቅምና በህዝብ ላይ የደረሰው ጉዳት እንዲሁም የወንጀሉ ዓላማ ከባድ መሆኑን ፍርድ ቤቱ ግምት ውስጥ ማስገባቱን ገልጸዋል።
እንደ ፕሬዚዳንቱ ገለጻ፣ ፍርድ ቤቱ በመመሪያው መሠረት ተከሳሾቹ እያንዳንዳቸው በ15 ዓመት ጽኑ እስራትና በ50,000 ብር መቀጮ እንዲቀጡ መነሻ ቅጣት ወስኖ ነበር።
ይሁን እንጂ ተከሳሾቹ ፦
- ከዚህ በፊት የወንጀል ሪከርድ የሌላቸው፣
- የቤተሰብ አስተዳዳሪና ለረዥም ጊዜያት ያገለገሉ በመሆናቸው፤
- በተለይ 1ኛ ተከሳሽ "እምርታ" የተሰኘ የበጎ አድራጎት ማህበር መስራችና ስራ አስኪያጅ የነበሩ መሆናቸውን ከግምት ውስጥ በማስገባት ለእያንዳንዳቸው ሦስት የቅጣት ማቅለያዎች መያዛቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አብራርተዋል።
የግራ ቀኙን ክርክር ያደመጠው ፍርድ ቤት የሚከተለውን የመጨረሻ ውሳኔ ማስተላለፉን አቶ ሙሀባ ቀውያ ገልጸዋል።
1ኛ ተከሳሽ አቶ ዳዊት ገበየሁ ፦ በቁጥጥር ስር ከዋሉበት ከሰኔ 25 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ በሚቆጠር በ13 ዓመት ጽኑ እስራትና በብር 20,000 የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ፤
2ኛ ተከሳሽ አቶ ገደኖ ካዋይታ ፦ በቁጥጥር ስር ከዋሉበት ከመስከረም 14 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በሚቆጠር በ13 ዓመት ጽኑ እስራትና በብር 20,000 የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ተወስኗል።
በተጨማሪም ተከሳሾቹ ለግል ጥቅማቸው ያዋሉትን ብር 3,702,466.67 ለመንግስት በጋራ እንዲመልሱ መወሰኑን ፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል።
አቶ ዳዊት ገበየሁ በዚሁ ፍ/ቤት በሌላ የወንጀል መዝገብ የካቲት 12 ቀን 2018 ዓ.ም በ7 ዓመት ጽኑ እስራትና በ5,000 ብር መቀጮ ተፈርዶባቸው የነበረ መሆኑን አቶ ሙሀባ ገልጸው፤ ሁለቱም የወንጀል ቅጣቶች ተደምረው ተከሳሹ በአጠቃላይ በ20 ዓመት ጽኑ እስራትና በ25,000 ብር የገንዘብ መቀጮ የሚቀጡ መሆኑን አስታውቀዋል።
tikvahethiopia
⚫ ለተፈናቀሉ ወገኖች ድጋፍ እንዲሆን የተለገሰ 6,594 የቤት ክዳን ቆርቆሮ ተሸጦ ለግል ጥቅም ውሏል ፤ 3,702,466.67 ብር ነው ተሽጦ የተበላው።
የኮንሶ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የቀድሞ የኮንሶ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የነበሩት አቶ ዳዊት ገበየሁ እና የግብርና መምሪያ የአደጋ ስጋትና ስራ አመራር ኃላፊ የነበሩት አቶ ገደኖ ካዋይታ ላይ የፍርድ ውሳኔ ማሳለፉን የፍርድ ቤቱ ፕሬዚዳንት አቶ ሙሀባ ቀውያ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
ግለሰቦቹ " የመንግስትን የሥራ ኃላፊነት በማይመች አኳኋን መምራት እና የሙስና ወንጀል " ጥፋተኛ መሆናቸውን ፍርድ ቤቱ አረጋግጧል ሲሉ ፕሬዚዳንቱ አሳውቀዋል።
ተከሳሾቹ በ2014 ዓ.ም በኮንሶ ዞን ሰገን ዙሪያ ወረዳ በግጭት ምክንያት ለተፈናቀሉ ወገኖች ድጋፍ እንዲሆን ከኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን የተለገሰውን 6,594 የቤት ክዳን ቆርቆሮ ሸጠው ለግል ጥቅማቸው ማዋላቸው በማስረጃ መረጋገጡን አቶ ሙሀባ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል።
ተከሳሾች ለግል ጥቅማቸው ያዋሉት ሀብት ግምቱ ብር 3,702,466.67 (ሶስት ሚሊዮን ሰባት መቶ ሁለት ሺህ አራት መቶ ስልሳ ስልስት ብር ከስልስ ሰባት ሳንቲም) መሆኑን ጠቅሰው ፤ የተገኘው ጥቅምና በህዝብ ላይ የደረሰው ጉዳት እንዲሁም የወንጀሉ ዓላማ ከባድ መሆኑን ፍርድ ቤቱ ግምት ውስጥ ማስገባቱን ገልጸዋል።
እንደ ፕሬዚዳንቱ ገለጻ፣ ፍርድ ቤቱ በመመሪያው መሠረት ተከሳሾቹ እያንዳንዳቸው በ15 ዓመት ጽኑ እስራትና በ50,000 ብር መቀጮ እንዲቀጡ መነሻ ቅጣት ወስኖ ነበር።
ይሁን እንጂ ተከሳሾቹ ፦
- ከዚህ በፊት የወንጀል ሪከርድ የሌላቸው፣
- የቤተሰብ አስተዳዳሪና ለረዥም ጊዜያት ያገለገሉ በመሆናቸው፤
- በተለይ 1ኛ ተከሳሽ "እምርታ" የተሰኘ የበጎ አድራጎት ማህበር መስራችና ስራ አስኪያጅ የነበሩ መሆናቸውን ከግምት ውስጥ በማስገባት ለእያንዳንዳቸው ሦስት የቅጣት ማቅለያዎች መያዛቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አብራርተዋል።
የግራ ቀኙን ክርክር ያደመጠው ፍርድ ቤት የሚከተለውን የመጨረሻ ውሳኔ ማስተላለፉን አቶ ሙሀባ ቀውያ ገልጸዋል።
1ኛ ተከሳሽ አቶ ዳዊት ገበየሁ ፦ በቁጥጥር ስር ከዋሉበት ከሰኔ 25 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ በሚቆጠር በ13 ዓመት ጽኑ እስራትና በብር 20,000 የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ፤
2ኛ ተከሳሽ አቶ ገደኖ ካዋይታ ፦ በቁጥጥር ስር ከዋሉበት ከመስከረም 14 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በሚቆጠር በ13 ዓመት ጽኑ እስራትና በብር 20,000 የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ተወስኗል።
በተጨማሪም ተከሳሾቹ ለግል ጥቅማቸው ያዋሉትን ብር 3,702,466.67 ለመንግስት በጋራ እንዲመልሱ መወሰኑን ፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል።
አቶ ዳዊት ገበየሁ በዚሁ ፍ/ቤት በሌላ የወንጀል መዝገብ የካቲት 12 ቀን 2018 ዓ.ም በ7 ዓመት ጽኑ እስራትና በ5,000 ብር መቀጮ ተፈርዶባቸው የነበረ መሆኑን አቶ ሙሀባ ገልጸው፤ ሁለቱም የወንጀል ቅጣቶች ተደምረው ተከሳሹ በአጠቃላይ በ20 ዓመት ጽኑ እስራትና በ25,000 ብር የገንዘብ መቀጮ የሚቀጡ መሆኑን አስታውቀዋል።
tikvahethiopia
3 months ago
የ12ኛ ክፍል ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ
#ethiopia | የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሠርተፊኬት (12ኛ ክፍል ፈተና) ከሰኔ 24 እስከ ሃምሌ 17 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቆናል።
በሌላ በኩል ፦
- የሬሜዲያል ፕሮግራም ሀገር አቀፍ ፈተና ከግንቦት 17 እስከ ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ/ም ➡️ ግንቦት 19 ኢድ አልአድሃ
- የቅድመ ምረቃ ትምህርት መውጫ ፈተና ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ/ም
- የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና (NGAT) ከሃምሌ 29 እስከ ሃምሌ 30 ቀን 2018 ዓ/ም
- የመሰረታዊ የንባብና የስሌት ክህሎት ምዘና ጥናትና ምርምር መረጃ መሰብሰብ ከሚያዚያ 26 እስከ ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ/ም ... ይሰጣል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu #tikvah #education #exam #12grade #graduated
#ethiopia | የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሠርተፊኬት (12ኛ ክፍል ፈተና) ከሰኔ 24 እስከ ሃምሌ 17 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቆናል።
በሌላ በኩል ፦
- የሬሜዲያል ፕሮግራም ሀገር አቀፍ ፈተና ከግንቦት 17 እስከ ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ/ም ➡️ ግንቦት 19 ኢድ አልአድሃ
- የቅድመ ምረቃ ትምህርት መውጫ ፈተና ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ/ም
- የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና (NGAT) ከሃምሌ 29 እስከ ሃምሌ 30 ቀን 2018 ዓ/ም
- የመሰረታዊ የንባብና የስሌት ክህሎት ምዘና ጥናትና ምርምር መረጃ መሰብሰብ ከሚያዚያ 26 እስከ ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ/ም ... ይሰጣል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu #tikvah #education #exam #12grade #graduated
3 months ago
የ12ኛ ክፍል ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ።
የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሠርተፊኬት (12ኛ ክፍል ፈተና) ከሰኔ 24 እስከ ሃምሌ 17 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቆናል።
በሌላ በኩል ፦
- የሬሜዲያል ፕሮግራም ሀገር አቀፍ ፈተና ከግንቦት 17 እስከ ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ/ም ➡️ ግንቦት 19 ኢድ አልአድሃ
- የቅድመ ምረቃ ትምህርት መውጫ ፈተና ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ/ም
- የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና (NGAT) ከሃምሌ 29 እስከ ሃምሌ 30 ቀን 2018 ዓ/ም
- የመሰረታዊ የንባብና የስሌት ክህሎት ምዘና ጥናትና ምርምር መረጃ መሰብሰብ ከሚያዚያ 26 እስከ ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ/ም ... ይሰጣል።
tikvahethiopia
የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሠርተፊኬት (12ኛ ክፍል ፈተና) ከሰኔ 24 እስከ ሃምሌ 17 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቆናል።
በሌላ በኩል ፦
- የሬሜዲያል ፕሮግራም ሀገር አቀፍ ፈተና ከግንቦት 17 እስከ ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ/ም ➡️ ግንቦት 19 ኢድ አልአድሃ
- የቅድመ ምረቃ ትምህርት መውጫ ፈተና ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ/ም
- የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና (NGAT) ከሃምሌ 29 እስከ ሃምሌ 30 ቀን 2018 ዓ/ም
- የመሰረታዊ የንባብና የስሌት ክህሎት ምዘና ጥናትና ምርምር መረጃ መሰብሰብ ከሚያዚያ 26 እስከ ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ/ም ... ይሰጣል።
tikvahethiopia
3 months ago
ባሕር ዳር ላይ ሰው ገድሎ የተሰወረው ተጠርጣሪ መቐለ ላይ በትግራይ ክልል ፖሊስ ተያዘ።
በባሕርዳር ከተማ ማህሌት ማሩ የተባለችን እንስት " የአድማ ብተና " አባል በሆነው ተጠርጣሪ ያምራል አለበል አለሙ " ተደፍራ እና ተገድላ ተገኘች " የሚል መረጃ ሲሰራጭ ነበር።
የግድያ ጥቃቱ የደረሰበትን ሁኔታ በተመለከተ፣ ከስፍራው የወጣውና በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጨው አብዛኛው መረጃ፣ ተጠርጣሪው እንስቷ ከምትሰራበት ሆቴል እየተስተናገደ አምሽቶ " አስገድዶ ወደ ሌላ ሆቴል በመውሰድ ከደፈራት በኋላ ገደላት " የሚል ነው።
የወንጀል ድርጊቱ ብዙዎችን ያቆጣ ነው።
የወንጀል ድርጊቱን በመፈጸም የተጠረጠረው ግለሰብ ድርጊቱን ፈጽሞ ከአካባቢው ተሰውሮ ነበር።
ምንም እንኳን የአማራ ክልል ፖሊስ ስለ ግድያው ዝርዝር መረጃ ይፋ ባያደርግም ህዝቡ ያለበትን እንዲጦቅም ጥሪ አቅርቦ ፍለጋ ሲያካሂድ ነበር።
ዛሬ የአማራ ፖሊስ ይፋ ባደረገው መረጃ በነፍስ ግድያ ወንጀል ተጠርጥሮ ሲፈለግ የነበረው ያምራል አለበል አለሙ በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ በቁጥጥር ስር ውሏል።
ፖሊስ " ያምራል አለበል አለሙ የተባለው ተጠርጣሪ ግድያ ፈጽሞ ከአካባቢው በመሰወር ለረጅም ጊዜ ሲፈለግ ቆይቷል " ብሏል።
ለመያዝ ክትትል ሲደረግ ቆይቶ በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ ተሸሽጎ እንደሚገኝ በመረጋገጡ በተደረገ የተቀናጀ ስራ በቁጥጥር ስር ሊውል እንደቻለ አማራ ፖሊስ ገልጿል።
የአማራ ክልል ፖሊስ፣ የትግራይ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ላበረከተው የላቀ አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርቧል።
በሌላ በኩል ቲክቫህ ኢትዮጵያ እንስቷ በምን ሁኔታ ግድያ እንደተፈጸመባት አንድ የአማራ ክልል ፖሊስ አካልን ጠይቆ " ምርመራ ላይ ስለሆነ የሚገልጹት ምርመራ የሚሰሩት ናቸው " ብለዋል።
እስካሁን ባለው ክትትል ስለእንስቷ አሟሟት የተገኘ መረጃ ካለ በድጋሚ እንዲገልጹ ስንጠይቃቸውም፣ " ገና ምርመራ ላይ ያለ ጉዳይ ነው " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
tikvahethiopia
በባሕርዳር ከተማ ማህሌት ማሩ የተባለችን እንስት " የአድማ ብተና " አባል በሆነው ተጠርጣሪ ያምራል አለበል አለሙ " ተደፍራ እና ተገድላ ተገኘች " የሚል መረጃ ሲሰራጭ ነበር።
የግድያ ጥቃቱ የደረሰበትን ሁኔታ በተመለከተ፣ ከስፍራው የወጣውና በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጨው አብዛኛው መረጃ፣ ተጠርጣሪው እንስቷ ከምትሰራበት ሆቴል እየተስተናገደ አምሽቶ " አስገድዶ ወደ ሌላ ሆቴል በመውሰድ ከደፈራት በኋላ ገደላት " የሚል ነው።
የወንጀል ድርጊቱ ብዙዎችን ያቆጣ ነው።
የወንጀል ድርጊቱን በመፈጸም የተጠረጠረው ግለሰብ ድርጊቱን ፈጽሞ ከአካባቢው ተሰውሮ ነበር።
ምንም እንኳን የአማራ ክልል ፖሊስ ስለ ግድያው ዝርዝር መረጃ ይፋ ባያደርግም ህዝቡ ያለበትን እንዲጦቅም ጥሪ አቅርቦ ፍለጋ ሲያካሂድ ነበር።
ዛሬ የአማራ ፖሊስ ይፋ ባደረገው መረጃ በነፍስ ግድያ ወንጀል ተጠርጥሮ ሲፈለግ የነበረው ያምራል አለበል አለሙ በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ በቁጥጥር ስር ውሏል።
ፖሊስ " ያምራል አለበል አለሙ የተባለው ተጠርጣሪ ግድያ ፈጽሞ ከአካባቢው በመሰወር ለረጅም ጊዜ ሲፈለግ ቆይቷል " ብሏል።
ለመያዝ ክትትል ሲደረግ ቆይቶ በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ ተሸሽጎ እንደሚገኝ በመረጋገጡ በተደረገ የተቀናጀ ስራ በቁጥጥር ስር ሊውል እንደቻለ አማራ ፖሊስ ገልጿል።
የአማራ ክልል ፖሊስ፣ የትግራይ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ላበረከተው የላቀ አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርቧል።
በሌላ በኩል ቲክቫህ ኢትዮጵያ እንስቷ በምን ሁኔታ ግድያ እንደተፈጸመባት አንድ የአማራ ክልል ፖሊስ አካልን ጠይቆ " ምርመራ ላይ ስለሆነ የሚገልጹት ምርመራ የሚሰሩት ናቸው " ብለዋል።
እስካሁን ባለው ክትትል ስለእንስቷ አሟሟት የተገኘ መረጃ ካለ በድጋሚ እንዲገልጹ ስንጠይቃቸውም፣ " ገና ምርመራ ላይ ያለ ጉዳይ ነው " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
tikvahethiopia
4 months ago
ኢትዮጵያ የ2027ቱን የዓለም አቀፍ ስፖርት ጋዜጠኞች ማኅበር (AIPS) ጉባኤን ለማስተናገድ ተመረጠች
#ethiopia | የኢትዮጵያ ስፖርት ጋዜጠኞች ማኅበር በ2027 የሚካሄደውን የዓለም አቀፍ ስፖርት ጋዜጠኞች ማኅበር (AIPS) ዓመታዊ ጉባኤን በዝግጅትነት ለመምራት ያቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱ ተነገረ።
ታላቅ ዓለም አቀፍ መድረክ ኢትዮጵያ በስፖርቱ ዓለም ያላትን ስም የምታድስበትና "የስፖርት ቤተሰቡን" በአንድ ጣሪያ ሥር የምታገናኝበት ትልቅ ዕድል ተደርጎ ተወስዷል። በጉባኤው ላይ የሚከተሉት ዋና ዋና ክንውኖች እንደሚጠበቁ ታውቋል፦
ከ100 በላይ አገራ* የተውጣጡ ጋዜጠኞች ተሳትፎ፤ የተለያዩ ዓለም አቀፍ የስፖርት ተቋማት መሪዎች መገኘት፤የዓለም "ምርጥ የስፖርት ጋዜጠኝነት ዓመታዊ የሽልማት ፕሮግራም"፤የወጣት ስፖርት ጋዜጠኞች (AIPS Young Reporters) ሥልጠና ይደረጋል።
ይህ ጉባኤ ከዘገባ ባለፈ ለኢትዮጵያ ስፖርት ዲፕሎማሲ፣ ለኢኮኖሚ መነቃቃትና ለአገራዊ ገጽታ ግንባታ የላቀ ፋይዳ ይኖረዋል ተብሎ ይታመናል። የዓለም ስፖርት ባለሙያዎችና አመራሮች በ2027 በአዲስ አበባ እንደሚሰበሰቡ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #tikvah #ethiopia #aips #sportsjournalism #aips2027 #sportdiplomacy #ኢትዮጵያ #ስፖርትጋዜጠኝነት #አዲስአበባ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ስፖርት ጋዜጠኞች ማኅበር በ2027 የሚካሄደውን የዓለም አቀፍ ስፖርት ጋዜጠኞች ማኅበር (AIPS) ዓመታዊ ጉባኤን በዝግጅትነት ለመምራት ያቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱ ተነገረ።
ታላቅ ዓለም አቀፍ መድረክ ኢትዮጵያ በስፖርቱ ዓለም ያላትን ስም የምታድስበትና "የስፖርት ቤተሰቡን" በአንድ ጣሪያ ሥር የምታገናኝበት ትልቅ ዕድል ተደርጎ ተወስዷል። በጉባኤው ላይ የሚከተሉት ዋና ዋና ክንውኖች እንደሚጠበቁ ታውቋል፦
ከ100 በላይ አገራ* የተውጣጡ ጋዜጠኞች ተሳትፎ፤ የተለያዩ ዓለም አቀፍ የስፖርት ተቋማት መሪዎች መገኘት፤የዓለም "ምርጥ የስፖርት ጋዜጠኝነት ዓመታዊ የሽልማት ፕሮግራም"፤የወጣት ስፖርት ጋዜጠኞች (AIPS Young Reporters) ሥልጠና ይደረጋል።
ይህ ጉባኤ ከዘገባ ባለፈ ለኢትዮጵያ ስፖርት ዲፕሎማሲ፣ ለኢኮኖሚ መነቃቃትና ለአገራዊ ገጽታ ግንባታ የላቀ ፋይዳ ይኖረዋል ተብሎ ይታመናል። የዓለም ስፖርት ባለሙያዎችና አመራሮች በ2027 በአዲስ አበባ እንደሚሰበሰቡ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #tikvah #ethiopia #aips #sportsjournalism #aips2027 #sportdiplomacy #ኢትዮጵያ #ስፖርትጋዜጠኝነት #አዲስአበባ
Sponsored by
Surafel
4 months ago
“መሸነፍ አይገባንም ነበር” - ሚኬል አርቴታ
#ethiopia | ቡድናቸው በኤፌ ካፕ (FA Cup) ከሳውዝሀምፕተን ጋር በነበረው ጨዋታ የደረሰበት ሽንፈት የሚገባው እንዳልነበር በቁጭት ገለጹ።
አሰልጣኙ ከጨዋታው በኋላ በሰጡት አስተያየት፣ ጨዋታውን ለሁለት ጊዜያት ደግመው መመልከታቸውንና ቡድኑ በሜዳ ላይ ካሳየው እንቅስቃሴ አንፃር ሽንፈት የማይገባው እንደነበር አፅንዖት ሰጥተዋል።
አርቴታ አክለውም “ይህ እግርኳስ ነው፤ አንዳንድ ጊዜ ከእኛ ማንነት ጋር በተያያዙ ስህተቶች እንቀጣለን” በማለት፣ ምንም እንኳን ውጤቱ ባይሳካም ሽንፈቱ ከጨዋታው ይዘት ይልቅ በትንንሽ ስህተቶች የመጣ መሆኑን አመልክተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #tikvah #አርሰናል #ሚኬልአርቴታ #ኤፌካፕ #እግርኳስ #የስፖርትዜና #ሳውዝሀምፕተን #arsenal #arteta #facup #footballnews
#ethiopia | ቡድናቸው በኤፌ ካፕ (FA Cup) ከሳውዝሀምፕተን ጋር በነበረው ጨዋታ የደረሰበት ሽንፈት የሚገባው እንዳልነበር በቁጭት ገለጹ።
አሰልጣኙ ከጨዋታው በኋላ በሰጡት አስተያየት፣ ጨዋታውን ለሁለት ጊዜያት ደግመው መመልከታቸውንና ቡድኑ በሜዳ ላይ ካሳየው እንቅስቃሴ አንፃር ሽንፈት የማይገባው እንደነበር አፅንዖት ሰጥተዋል።
አርቴታ አክለውም “ይህ እግርኳስ ነው፤ አንዳንድ ጊዜ ከእኛ ማንነት ጋር በተያያዙ ስህተቶች እንቀጣለን” በማለት፣ ምንም እንኳን ውጤቱ ባይሳካም ሽንፈቱ ከጨዋታው ይዘት ይልቅ በትንንሽ ስህተቶች የመጣ መሆኑን አመልክተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #tikvah #አርሰናል #ሚኬልአርቴታ #ኤፌካፕ #እግርኳስ #የስፖርትዜና #ሳውዝሀምፕተን #arsenal #arteta #facup #footballnews
4 months ago
ምድር ፎቶ ተነሳች
#ethiopia | ናሳ ለአርጤምስ 2 (Artemis II) ተልዕኮ ወደ ጨረቃ የላካቸው አራት ጠፈርተኞች፣ ከምድር 66,000 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ሆነው የቀረጿቸውን እጅግ አስደናቂ እና ጥራት ያላቸውን የምድራችን ምስሎች ይፋ አድርገዋል።
እነዚህ ታሪካዊ ምስሎች የተነሱት የኦርዮን (Orion) መንኮራኩር ወደ ጨረቃ የምታደርገውን ጉዞ በጀመረችበት ወቅት ሲሆን፣ ይህም የሰው ልጅ በ1972 ከተካሄደው የአፖሎ 17 ጉዞ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከምድር ምህዋር ወጥቶ ወደ ጥልቅ ጠፈር የተጓዘበት አጋጣሚ ሆኖ ተመዝግቧል።
ይህ ተልዕኮ በበርካታ ምክንያቶች ታሪካዊና ልዩ ተደርጎ ተወስዷል፦
ተልዕኮው ለመጀመሪያ ጊዜ ሴት እና ጥቁር አሜሪካዊ ጠፈርተኞችን በማካተት የጠፈር ምርምር ታሪክ አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል።
የአርጤምስ 2 ስኬት የሰው ልጅን ዳግም በጨረቃ ላይ ለማሳረፍ ለሚታቀደው የ"አርጤምስ 3" ተልዕኮ ወሳኝ መሠረት የሚጥል ነው።
መንኮራኩሯ ከላከቻቸው ምስሎች ጥራት መረዳት እንደሚቻለው፣ የናሳ የቴክኖሎጂ አቅም ለጥልቅ ህዋ ምርምር ዝግጁ መሆኑን አመላካች ነው።
የአርጤምስ 2 ተልዕኮ የሰው ልጅ የጨረቃን ምህዋር ዙሮ ወደ ምድር በመመለስ፣ ለወደፊቱ የሰው ልጅ የጨረቃና የማርስ ጉዞዎች መንገዱን ክፍት ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#tikvah #getutemesgen #getu #nasa #artemisii #spaceexploration #earthfromspace #moonmission #sciencenews #techethiopia #spacetravel
#ethiopia | ናሳ ለአርጤምስ 2 (Artemis II) ተልዕኮ ወደ ጨረቃ የላካቸው አራት ጠፈርተኞች፣ ከምድር 66,000 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ሆነው የቀረጿቸውን እጅግ አስደናቂ እና ጥራት ያላቸውን የምድራችን ምስሎች ይፋ አድርገዋል።
እነዚህ ታሪካዊ ምስሎች የተነሱት የኦርዮን (Orion) መንኮራኩር ወደ ጨረቃ የምታደርገውን ጉዞ በጀመረችበት ወቅት ሲሆን፣ ይህም የሰው ልጅ በ1972 ከተካሄደው የአፖሎ 17 ጉዞ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከምድር ምህዋር ወጥቶ ወደ ጥልቅ ጠፈር የተጓዘበት አጋጣሚ ሆኖ ተመዝግቧል።
ይህ ተልዕኮ በበርካታ ምክንያቶች ታሪካዊና ልዩ ተደርጎ ተወስዷል፦
ተልዕኮው ለመጀመሪያ ጊዜ ሴት እና ጥቁር አሜሪካዊ ጠፈርተኞችን በማካተት የጠፈር ምርምር ታሪክ አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል።
የአርጤምስ 2 ስኬት የሰው ልጅን ዳግም በጨረቃ ላይ ለማሳረፍ ለሚታቀደው የ"አርጤምስ 3" ተልዕኮ ወሳኝ መሠረት የሚጥል ነው።
መንኮራኩሯ ከላከቻቸው ምስሎች ጥራት መረዳት እንደሚቻለው፣ የናሳ የቴክኖሎጂ አቅም ለጥልቅ ህዋ ምርምር ዝግጁ መሆኑን አመላካች ነው።
የአርጤምስ 2 ተልዕኮ የሰው ልጅ የጨረቃን ምህዋር ዙሮ ወደ ምድር በመመለስ፣ ለወደፊቱ የሰው ልጅ የጨረቃና የማርስ ጉዞዎች መንገዱን ክፍት ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#tikvah #getutemesgen #getu #nasa #artemisii #spaceexploration #earthfromspace #moonmission #sciencenews #techethiopia #spacetravel
4 months ago
የሴኔጋል መንግስት በግብረ ሰዶማዊነት ላይ ጠንካራ እርምጃ የሚወስድ አዲስ ህግ አፀደቀ።
የሴኔጋል ፕሬዝዳንት ባሲሩ ዲዮማዬ ፋዬ በሀገሪቱ ግብረ ሰዶማውያንን በከፍተኛ ሁኔታ የሚቀጣ አዲስ ህግ በፊርማቸው አፅድቀዋል።
ይህ አዲስ ህግ ቀደም ሲል በግብረ ሰዶማዊነት ድርጊት ላይ ተጥሎ የነበረውን ከፍተኛ የእስር ቅጣት ወደ 10 ዓመት ከፍ አድርጎታል።
" ከተፈጥሮ ውጪ የሆኑ ድርጊቶች " ተብለው የተመደቡ የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነቶች ላይ የሚጣለው ቅጣት ከነበረበት 1-5 ዓመት ወደ 5-10 ዓመት ከፍ እንዲል ተደርጓል።
አዲሱ ህግ ከእስር በተጨማሪ ከ2 ሚሊዮን እስከ 10 ሚሊዮን የሴኔጋል ፍራንክ ($3,500 - $17,600) የሚደርስ ከፍተኛ የገንዘብ መቀጮ ደንግጓል። ይህም ቀደም ሲል ከነበረው (1.5 ሚሊዮን ፍራንክ) እጅግ የላቀ ነው።
ግብረ ሰዶማዊነትን የሚያስተዋውቁ ወይም የገንዘብ ድጋፍ የሚያደርጉ ግለሰቦች ከ3 እስከ 7 ዓመት በሚደርስ እስራት እንዲቀጡ ህጉ ይፈቅዳል።
አፀያፊ የተባለውን ይህን ድርጊት የሚያበረታታ ማንኛውም ድርጊት እንደ ወንጀል እንዲታይ ተደርጓል።
ህጉ ያለምንም ማስረጃ ሌላውን ሰው በግብረ ሰዶማዊነት ወንጀል የሚከስ ማንኛውንም አካል በወንጀል እንደሚቀጣ አካቷል።
ይህ ጠንካራ ህግ ፕሬዝዳንት ባሲሩ ዲዮማዬ ፋዬ እና የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኡስማን ሶንኮ በምርጫ ወቅት ለህዝባቸው የገቡትን ቃል የፈጸሙበት ነው ተብሏል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ቮልከር ቱርክ ውሳኔውን " እጅግ አሳሳቢ " ሲሉ የገለጹት ሲሆን ህጉ ሰብአዊ መብቶችን የሚጥስ መሆኑን ተናግረዋል።
በተቃራኒው በሴኔጋል የሚገኙ የሃይማኖት ተቋማት እና ማህበራት ግብረ ሰዶማዊነት "የምዕራባውያን ባህል መጫኛ መሳሪያ ነው" በሚል ጠንካራ ቅጣት እንዲጣል ሲወተውቱ ቆይተዋል ተብሏል።
ከባለፈው የካቲት ወር ጀምሮ በሴኔጋል በርካታ ሰዎች በግብረ ሰዶማዊነት ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ውለዋል።
አዲሱ ህግ ተጠርጣሪዎቹ ላይ የሚጣለውን ቅጣት የበለጠ በማክበድ በሀገሪቱ ያለውን ጥብቅ ቁጥጥር የሚያጠናክር ነው።
በተለይም ድርጊቱ የተፈጸመው ለአካለ መጠን ባልደረሱ ህፃናት ላይ ከሆነ ከፍተኛው ቅጣት እንደሚተገበር ህጉ ይገልጻል።
tikvahethiopia
የሴኔጋል ፕሬዝዳንት ባሲሩ ዲዮማዬ ፋዬ በሀገሪቱ ግብረ ሰዶማውያንን በከፍተኛ ሁኔታ የሚቀጣ አዲስ ህግ በፊርማቸው አፅድቀዋል።
ይህ አዲስ ህግ ቀደም ሲል በግብረ ሰዶማዊነት ድርጊት ላይ ተጥሎ የነበረውን ከፍተኛ የእስር ቅጣት ወደ 10 ዓመት ከፍ አድርጎታል።
" ከተፈጥሮ ውጪ የሆኑ ድርጊቶች " ተብለው የተመደቡ የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነቶች ላይ የሚጣለው ቅጣት ከነበረበት 1-5 ዓመት ወደ 5-10 ዓመት ከፍ እንዲል ተደርጓል።
አዲሱ ህግ ከእስር በተጨማሪ ከ2 ሚሊዮን እስከ 10 ሚሊዮን የሴኔጋል ፍራንክ ($3,500 - $17,600) የሚደርስ ከፍተኛ የገንዘብ መቀጮ ደንግጓል። ይህም ቀደም ሲል ከነበረው (1.5 ሚሊዮን ፍራንክ) እጅግ የላቀ ነው።
ግብረ ሰዶማዊነትን የሚያስተዋውቁ ወይም የገንዘብ ድጋፍ የሚያደርጉ ግለሰቦች ከ3 እስከ 7 ዓመት በሚደርስ እስራት እንዲቀጡ ህጉ ይፈቅዳል።
አፀያፊ የተባለውን ይህን ድርጊት የሚያበረታታ ማንኛውም ድርጊት እንደ ወንጀል እንዲታይ ተደርጓል።
ህጉ ያለምንም ማስረጃ ሌላውን ሰው በግብረ ሰዶማዊነት ወንጀል የሚከስ ማንኛውንም አካል በወንጀል እንደሚቀጣ አካቷል።
ይህ ጠንካራ ህግ ፕሬዝዳንት ባሲሩ ዲዮማዬ ፋዬ እና የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኡስማን ሶንኮ በምርጫ ወቅት ለህዝባቸው የገቡትን ቃል የፈጸሙበት ነው ተብሏል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ቮልከር ቱርክ ውሳኔውን " እጅግ አሳሳቢ " ሲሉ የገለጹት ሲሆን ህጉ ሰብአዊ መብቶችን የሚጥስ መሆኑን ተናግረዋል።
በተቃራኒው በሴኔጋል የሚገኙ የሃይማኖት ተቋማት እና ማህበራት ግብረ ሰዶማዊነት "የምዕራባውያን ባህል መጫኛ መሳሪያ ነው" በሚል ጠንካራ ቅጣት እንዲጣል ሲወተውቱ ቆይተዋል ተብሏል።
ከባለፈው የካቲት ወር ጀምሮ በሴኔጋል በርካታ ሰዎች በግብረ ሰዶማዊነት ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ውለዋል።
አዲሱ ህግ ተጠርጣሪዎቹ ላይ የሚጣለውን ቅጣት የበለጠ በማክበድ በሀገሪቱ ያለውን ጥብቅ ቁጥጥር የሚያጠናክር ነው።
በተለይም ድርጊቱ የተፈጸመው ለአካለ መጠን ባልደረሱ ህፃናት ላይ ከሆነ ከፍተኛው ቅጣት እንደሚተገበር ህጉ ይገልጻል።
tikvahethiopia
4 months ago
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ መካከለኛው ምስራቅ አቋርጧቸው ከነበሩ በረራዎች መካከል የትኞቹን በድጋሚ አስጀመረ ?
በመካከለኛው ምስራቅ በተከሰተው ግጭት ምክንያት በርካታ አየር መንገዶች ወደ ቀጠናው ያደርጉት የነበረውን በረራ በጊዜያዊነት ማቋረጣቸው ይታወቃል።
በሳምንት ከ 100 በላይ ምልልሶችን ያደርግ የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግጭቱ ከተቀሰቀሰበት ጊዜ አንስቶ ወደ መካከለኛው ምስራቅ እና ገልፍ ሃገራት ያደርጋቸው የነበሩ በረራዎችን ካቋረጡ አየር መንገዶች መካከል አንዱ ነው።
ለሳምንታት ተቋረጦ የቆየው በረራ ወደ አንዳንድ የቀጠናው አካባቢዎች በድጋሚ ማስጀመሩን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አሳውቋል።
የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በዛሬው ዕለት ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ማብራሪያ "የመሻሻል ነገሮች በምናይባቸው አካባቢዎች በተወሰነ ደረጃ በረራ እንደገና አስጀምረናል" ብለዋል።
በረራ የጀመረባቸው አካባቢዎች :-
• ዩናይትድ አረብ ኤምሬትስ ውስጥ ዱባይ በቀን አንድ በረራ ፣
• አቡዳቢ በቀን አንድ በረራ ፣
• ሻርጃ በቀን አንድ በረራ
• ሳውዲ አረቢያ (ደማም ከተማ) በቀን አንድ በረራ
• ጆርዳን አማን በቀን አንድ በረራ ናቸው።
ይሁን እንጂ አቶ መስፍን ዶሃ (ኳታር)፣ ባህሬን፣ ኩዌት እንዲሁም ቴላቪቭ እና ቤሩት በረራ እንደተቋረጠባቸው መሆኑን አሳውቀዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በዝርዝር ምን አሉ ?
" እንደሚታወቀው በገልፍ አካባቢ ጦርነት ከተጀመረ አንድ ወር አካባቢ ሆኖታል።
ጦርነቱ ከተጀመረ ጊዜ ጀምሮ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ገልፍ እና መካከለኛው ምስራቅ አገሮች የሚያደርገውን በረራ በተወሰነ ደረጃ ለጊዜው አቋርጧል።
ይህ በመሆኑ ምክንያት ወደ መካከለኛው ምስራቅ እና ገልፍ የሚሄዱ መንገደኞች እያጓጓዝን አይደለም፤ ያ በመንገደኛ ቁጥራችን ላይ የተወሰነ ተፅዕኖ ያሳድራል።
ይሁን እንጂ በሌሎች በምንበርባቸው ዓለም አቀፍ መዳረሻዎቻችን ላይ ያለንን በረራ በማጠናከር ከዚህ ከገልፍ እና መካከለኛው ምስራቅ ያጣነውን መንገደኛ ቁጥር ሌላ ቦታ በመብረር በተወሰነ ደረጃም ቢሆን ለማካካስ ሞክረናል።
በዚህ መንገድ እየቀጠልን ነው፤ ሁኔታውን እየተከታተልን ነው የመሻሻል ነገሮች በምናይባቸው አካባቢዎች በተወሰነ ደረጃ በረራ እንደገና አስጀምረናል ያ እየቀጠለ ነው ያለው።
በረራ ተቋርጦ ከነበረባቸው መካከል አሁን መብረር የጀመርንባቸው ዩናይትድ አረብ ኤምሬትስ ውስጥ ዱባይ በቀን አንድ በረራ እያደረግን ነው፣ አቡዳቢ በቀን አንድ በረራ እያደረግን ነው፣ እንዲሁም ሻርጃ በቀን አንድ በረራ እያደረግን ነው።
በተጨማሪም ሳውዲ አረቢያ ውስጥ ደማም የምትባል ከተማ አቋርጠን ነበር እሱን በረራ ቀጥለናል።
ይሁን እንጂ ዶሃ (ኳታር) ፣ ባህሬን ፣ ኩዌት እንዲሁም ቴላቪቭ እና ቤሩት በረራ እንዳቋረጥን ነው።
እንግዲህ በረራ ስናቋርጥ የበረራ ደህንነትን ትክክለኛ ትንተና አካሂደን ያለውን ሁሉ መረጃ አገናዝበን መብረር ሴፍ (safe) ነው የምንል ሲሆን ብቻ እንበራለን።
በተጨማሪም ጆርዳን አማን አቋርጠን ነበር እሱን ሁለት በረራ ነበረ አሁን በአንድ በረራ ጀምረናል " ብለዋል።
tikvahethiopia
በመካከለኛው ምስራቅ በተከሰተው ግጭት ምክንያት በርካታ አየር መንገዶች ወደ ቀጠናው ያደርጉት የነበረውን በረራ በጊዜያዊነት ማቋረጣቸው ይታወቃል።
በሳምንት ከ 100 በላይ ምልልሶችን ያደርግ የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግጭቱ ከተቀሰቀሰበት ጊዜ አንስቶ ወደ መካከለኛው ምስራቅ እና ገልፍ ሃገራት ያደርጋቸው የነበሩ በረራዎችን ካቋረጡ አየር መንገዶች መካከል አንዱ ነው።
ለሳምንታት ተቋረጦ የቆየው በረራ ወደ አንዳንድ የቀጠናው አካባቢዎች በድጋሚ ማስጀመሩን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አሳውቋል።
የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በዛሬው ዕለት ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ማብራሪያ "የመሻሻል ነገሮች በምናይባቸው አካባቢዎች በተወሰነ ደረጃ በረራ እንደገና አስጀምረናል" ብለዋል።
በረራ የጀመረባቸው አካባቢዎች :-
• ዩናይትድ አረብ ኤምሬትስ ውስጥ ዱባይ በቀን አንድ በረራ ፣
• አቡዳቢ በቀን አንድ በረራ ፣
• ሻርጃ በቀን አንድ በረራ
• ሳውዲ አረቢያ (ደማም ከተማ) በቀን አንድ በረራ
• ጆርዳን አማን በቀን አንድ በረራ ናቸው።
ይሁን እንጂ አቶ መስፍን ዶሃ (ኳታር)፣ ባህሬን፣ ኩዌት እንዲሁም ቴላቪቭ እና ቤሩት በረራ እንደተቋረጠባቸው መሆኑን አሳውቀዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በዝርዝር ምን አሉ ?
" እንደሚታወቀው በገልፍ አካባቢ ጦርነት ከተጀመረ አንድ ወር አካባቢ ሆኖታል።
ጦርነቱ ከተጀመረ ጊዜ ጀምሮ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ገልፍ እና መካከለኛው ምስራቅ አገሮች የሚያደርገውን በረራ በተወሰነ ደረጃ ለጊዜው አቋርጧል።
ይህ በመሆኑ ምክንያት ወደ መካከለኛው ምስራቅ እና ገልፍ የሚሄዱ መንገደኞች እያጓጓዝን አይደለም፤ ያ በመንገደኛ ቁጥራችን ላይ የተወሰነ ተፅዕኖ ያሳድራል።
ይሁን እንጂ በሌሎች በምንበርባቸው ዓለም አቀፍ መዳረሻዎቻችን ላይ ያለንን በረራ በማጠናከር ከዚህ ከገልፍ እና መካከለኛው ምስራቅ ያጣነውን መንገደኛ ቁጥር ሌላ ቦታ በመብረር በተወሰነ ደረጃም ቢሆን ለማካካስ ሞክረናል።
በዚህ መንገድ እየቀጠልን ነው፤ ሁኔታውን እየተከታተልን ነው የመሻሻል ነገሮች በምናይባቸው አካባቢዎች በተወሰነ ደረጃ በረራ እንደገና አስጀምረናል ያ እየቀጠለ ነው ያለው።
በረራ ተቋርጦ ከነበረባቸው መካከል አሁን መብረር የጀመርንባቸው ዩናይትድ አረብ ኤምሬትስ ውስጥ ዱባይ በቀን አንድ በረራ እያደረግን ነው፣ አቡዳቢ በቀን አንድ በረራ እያደረግን ነው፣ እንዲሁም ሻርጃ በቀን አንድ በረራ እያደረግን ነው።
በተጨማሪም ሳውዲ አረቢያ ውስጥ ደማም የምትባል ከተማ አቋርጠን ነበር እሱን በረራ ቀጥለናል።
ይሁን እንጂ ዶሃ (ኳታር) ፣ ባህሬን ፣ ኩዌት እንዲሁም ቴላቪቭ እና ቤሩት በረራ እንዳቋረጥን ነው።
እንግዲህ በረራ ስናቋርጥ የበረራ ደህንነትን ትክክለኛ ትንተና አካሂደን ያለውን ሁሉ መረጃ አገናዝበን መብረር ሴፍ (safe) ነው የምንል ሲሆን ብቻ እንበራለን።
በተጨማሪም ጆርዳን አማን አቋርጠን ነበር እሱን ሁለት በረራ ነበረ አሁን በአንድ በረራ ጀምረናል " ብለዋል።
tikvahethiopia
4 months ago
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የጥራት ችግር ያለበትን ፌኒቶይን (Phenytoin) መድኃኒት በአስቸኳይ እንዲመለስ አዘዘ።
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የባህር ዳር ቅርንጫፍ፣ ሜዲካመን ባዮቴክ ሊሚትድ (Medicamen Biotech limited) በተባለ ኩባንያ የተመረተ የፌኒቶይን 100 ሚሊ ግራም (Phenytoin 100 mg) ታብሌት መድኃኒት የጥራት ችግር ስላለበት ከጤና ተቋማት በአስቸኳይ እንዲሰበሰብ ትዕዛዝ አስተላልፏል።
ቅርንጫፍ መሥሪያ ቤቱ ለሁሉም የጤና ተቋማት በጻፈው ደብዳቤ ላይ እንደገለጸው፣ በአምራቹ የተመረቱት የዚህ መድኃኒት ባቾች (batches) በሙሉ የጥራት ጉድለት የታየባቸው በመሆኑ ተመላሽ እንዲያደርጉ ማሳሰቢያ ሰጥቷል።
ይሁን እንጂ እስካሁን ድረስ አንዳንድ የጤና ተቋማት መድኃኒቱን የመለሱ ቢሆንም፣ አንዳንድ ተቋማት ግን እስካሁን አለመመለሳቸውን አገልግሎቱ ገልጿል።
በመሆኑም መድኃኒቱን ያልመለሱ ተቋማት ያላቸውን ቀሪ መጠን በደብዳቤ ገልጸው እስከ ትላንት ሐምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ እንዲያሳውቁ ጥብቅ ማሳሰቢያ ሰጥቷል።
የመድኃኒት አቅርቦት አገልግሎቱ አክሎም፣ ይህንን ትዕዛዝ ተላልፈው መድኃኒቱን ተመላሽ የማያደርጉ ተቋማት ሙሉ ኃላፊነቱን እንደሚወስዱ አስጠንቅቋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት እንዳረጋገጠው በተጠቀሰው ባች የተመረተው ምርት የጥራት ችግር ያለበት በመሆኑ ከ 19 ኙም የመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች እንዲሰበሰቡ ትዕዛዝ መተላለፉን አረጋግጧል።
የፌኒቶይን (Phenytoin) መድኃኒት አብዛኛውን ጊዜ የሚጥል በሽታን (Epilepsy) ለመቆጣጠርና የሚያገለግል መሆኑ ይታወቃል።via tikvah
seledadotio
seledadotio
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የባህር ዳር ቅርንጫፍ፣ ሜዲካመን ባዮቴክ ሊሚትድ (Medicamen Biotech limited) በተባለ ኩባንያ የተመረተ የፌኒቶይን 100 ሚሊ ግራም (Phenytoin 100 mg) ታብሌት መድኃኒት የጥራት ችግር ስላለበት ከጤና ተቋማት በአስቸኳይ እንዲሰበሰብ ትዕዛዝ አስተላልፏል።
ቅርንጫፍ መሥሪያ ቤቱ ለሁሉም የጤና ተቋማት በጻፈው ደብዳቤ ላይ እንደገለጸው፣ በአምራቹ የተመረቱት የዚህ መድኃኒት ባቾች (batches) በሙሉ የጥራት ጉድለት የታየባቸው በመሆኑ ተመላሽ እንዲያደርጉ ማሳሰቢያ ሰጥቷል።
ይሁን እንጂ እስካሁን ድረስ አንዳንድ የጤና ተቋማት መድኃኒቱን የመለሱ ቢሆንም፣ አንዳንድ ተቋማት ግን እስካሁን አለመመለሳቸውን አገልግሎቱ ገልጿል።
በመሆኑም መድኃኒቱን ያልመለሱ ተቋማት ያላቸውን ቀሪ መጠን በደብዳቤ ገልጸው እስከ ትላንት ሐምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ እንዲያሳውቁ ጥብቅ ማሳሰቢያ ሰጥቷል።
የመድኃኒት አቅርቦት አገልግሎቱ አክሎም፣ ይህንን ትዕዛዝ ተላልፈው መድኃኒቱን ተመላሽ የማያደርጉ ተቋማት ሙሉ ኃላፊነቱን እንደሚወስዱ አስጠንቅቋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት እንዳረጋገጠው በተጠቀሰው ባች የተመረተው ምርት የጥራት ችግር ያለበት በመሆኑ ከ 19 ኙም የመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች እንዲሰበሰቡ ትዕዛዝ መተላለፉን አረጋግጧል።
የፌኒቶይን (Phenytoin) መድኃኒት አብዛኛውን ጊዜ የሚጥል በሽታን (Epilepsy) ለመቆጣጠርና የሚያገለግል መሆኑ ይታወቃል።via tikvah
seledadotio
seledadotio
4 months ago
" ሰባቱ ወዲያው ተገደሉ። አንዱን የሞተ መስሏቸው ጥለውት ሄዱ። አልሞተም ግን እግሩ ከጥቅም ውጭ ሆኗል። ስድስቱ በሰፊ ጉድጓድ በአንድ ቦታ ተቀብረዋል " - የፋብሪካው ሠራተኞች
➡️ " አንድ የከባድ መኪና ሹፌር እና ረዳትም ተገድለው ተገኝተዋል። የሰዎች መታገት የተለመደ ሆኗል። የጸጥታ አካላት አሉ ግን እያዩ እንዳላዩ ነው የሚሆኑት " - ነዋሪ
በኦሮሚያ ክልል፣ ምስራቅ ሸዋ ዞን ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት የመተሐራ ስኳር ፋብሪካ ሠራተኞችን እና ሌሎችን ጨምሮ በሁለት ቀናት ብቻ ዘጠኝ ሰዎች ሲገደሉ፣ ሌሎች መጎዳታቸውን የፋብሪካው ሠራተኞች እና ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
ጉዳዩን ያጣራ አንድ የአካባቢው ነዋሪ በሰጠን ማብራሪያ፣ የፋብሪካው ሠራተኞች በታጣቂዎች የተገደሉት መጋቢት 14 ቀን 2018 ዓ/ም መሆኑን ገልጾ። " አንድ የፋብሪካውን አመራር ለማጥቃት ሂደው ነው ሰባቱን አጃቢዎቹን የገደሏቸው " ብሏል።
ጥቃት አድራሾቹ፣ " መሬታችን ተወስዷል " የሚል ጥያቄ እንዳላቸውም ገልጿል። ጥቃቱ የደረሰው " ጮሬ " በሚባለው የፋብሪካው ካምፕ መሆኑን ያስረዳው ነዋሪው፣ " ሟቾቹ የስኳር ፋብሪካው የጥበቃ ሠራተኞች ናቸው። ታጣቂዎቹ ድንገት መጥተው ተኩስ ፈጽመውባቸው ወዲያው ነው ጫካ የሚገቡት " ሲልም ተናግሯል።
በተያያዘ፣ " ሰባቱ ሰዎች ከመገደላቸው ከአንድ ቀን በፊት መተሐራ እና ወለንጭቲ መካከል የከባድ መኪና ሹፌር እና ረዳትም ተገድለው ተገኝተዋል። በአካባቢው የሰዎች መታገት የተለመደ ሆኗል። የጸጥታ አካላት አሉ ግን እያዩ እንዳላዩ ነው የሚሆኑት " ሲልም ገልጿል።
ሌላኛው ነዋሪ፣ ከ2010 ጀምሮ በየዓመቱ እስከ ዘጠኝ ሰው " የሚገደልበት " ሁኔታ መኖሩን አስረድተው፣ " ህዝቡ ዘላቂ የሆነ መፍትሄ እያገኘ አይደለም " ሲሉ ገልጸዋል።
የሰሞኑን ጎድያ በተመከለተም፣ " በአንድ መኪና ላይ ነው ሰባቱንም የመንግስት ተቀጣሪዎች፤ የስንት ልጆች አባቶችን በአንድ ቀን ገድለውብናል " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ሰሞኑን የተገደሉት የመተሐራ ስኳር ፋብሪካ ሠራተኞች " ትልልቅ ሰዎች ናቸው " ሲሉ ያስረዱ አንድ ጉዳዩን በቅርበት የሚያውቁ የፋብሪካው ሠራተኛ ደግሞ፣ ጥቃቱን " አሳዛኝ " ሲሉ ጠርተውታል።
ሰባቱ ሠራተኞች የተገደሉት አንድ የፋብሪካውን አመራር አጅበው በነበረበት ወቅት መሆኑን ተናግረዋል።
የታጣቁት አካላት የፋብሪካው ሠራተኞች ላይ ተኩስ የከፈቱባቸው " ገና ከፒካፕ መኪና ላይ ሳይወርዱ " መሆኑን፣ በዚህም ሌሎቹ ሲገደሉ አብረው የነበሩት አመራሩ " የውሃ ቦይ ውስጥ ገብተው፣ እየተሳቡ " የተኩሱን ቦታ በመራቅ በህይወት መትረፋቸውን አስረድተዋል።
እኚሁ የፋብሪካው ሠራተኛ፣ ይህ ጥቃት ተፈጽሟል ብሎ ለመናገር እንኳ ከፍተኛ ስጋት እንዳለባቸው ገልጸዋል።
ሌላኛው የፋብሪካው ሠራተኛ በበኩላቸው፣ ግድያው የተፈጸመበት " ጮሬ " በተሰኘው ቦታ አጠገብ መሆኑን ገልጸዋል።
በአጠቃላይ ከሟቾቹ ጋር ዘጠኝ ሰዎች ነበሩ ብለው፣ " ሰባቱ ወዲያው ተገደሉ። አንዱ የሞተ መስሏቸው ጥለውት ሄዱ። አልሞተም ግን እግሩ ከጥቅም ውጭ ሆኗል። አንዱ ደግሞ ተርፏል " ብለዋል። " ስድስቱ በሰፊ ጉድጓድ በአንድ ቦታ ተቀብረዋል " ነው ያሉት።
አዲስ የመጡት የፋብሪካው ሥራ አስኪያጅ ለሟች ቤተሰቦች " በየቤታቸው ሂደው ለእያንዳንዳቸው 150 ሺሕ ብር ሰጥተዋል። 'የተማረ ልጅ ካላቸው በቋሚነት ሥራ እንቀጥራን፣ ካልተማሩ በመደብ 6 የአባታቶቻቸውን ቦታ ይይዛሉ' ሲሉም ቃል ገብተዋል " ሲሉ ተናግረዋል።
ጥቃቱ ከደረሰ በኋላ ያለውን ድባብ ሲያስረዱ ደግሞ፣ ለጊዜው "መከላከያ ገብቷል" ብለዋል።
የአካባቢው ነዋሪ ግን፣ " በአካባቢው የጸጥታ ችግር ተንሰራፍቷል። በሰላም ወጥቶ መግባት በጣም አስቸጋሪ ሆኗል " ሲሉም የሁነቱን አሳሳቢነት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
" ከአንድ ወር በፊት ሁለት ልጆች ታግተው 2 ሚሊዮን ብር ተጠይቆባቸው ነበር። 2 ሚሊዮን ብር ተሰብስቦ አንድ ልጅ ወስዶ ሰጣቸው። በኋላም ለቀቋቸው። ከፍተኛ ድብደባ እና ራሳቸውን እስኪስቱ ድረስ የረሃብ ስቃይ አድርሰውባቸው መንገድ ላይ ነው የጣሏቸው " ሲሉም አስታውሰዋል።
" ገንዘቡን ያደረሰው ልጅ ግን ተገድሏል" በማለት አዝነዋል። ከመተሐራ ስኳር ፋብሪካ ሠራተኞች መካከል አንዱ በበኩላቸው፣ ታጣቂዎቹ "ከአዳማ መተሐራ መንገድ በኃይለኛው እያገቱ ነው፤ ተሳፋሪም መውሰድ ጀምረዋል " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የስኳር ፋብሪካውንም ሆነ ሌሎች የአካባቢውን ኃላፊዎች ለማግኘት ለቀናት ያደረገው ጥረት ለጊዜው ያልተሳካ ሲሆን፣ ጥረቱ ይቀጥላል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#tikvahethiopiafamilyaa
tikvahethiopia
➡️ " አንድ የከባድ መኪና ሹፌር እና ረዳትም ተገድለው ተገኝተዋል። የሰዎች መታገት የተለመደ ሆኗል። የጸጥታ አካላት አሉ ግን እያዩ እንዳላዩ ነው የሚሆኑት " - ነዋሪ
በኦሮሚያ ክልል፣ ምስራቅ ሸዋ ዞን ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት የመተሐራ ስኳር ፋብሪካ ሠራተኞችን እና ሌሎችን ጨምሮ በሁለት ቀናት ብቻ ዘጠኝ ሰዎች ሲገደሉ፣ ሌሎች መጎዳታቸውን የፋብሪካው ሠራተኞች እና ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
ጉዳዩን ያጣራ አንድ የአካባቢው ነዋሪ በሰጠን ማብራሪያ፣ የፋብሪካው ሠራተኞች በታጣቂዎች የተገደሉት መጋቢት 14 ቀን 2018 ዓ/ም መሆኑን ገልጾ። " አንድ የፋብሪካውን አመራር ለማጥቃት ሂደው ነው ሰባቱን አጃቢዎቹን የገደሏቸው " ብሏል።
ጥቃት አድራሾቹ፣ " መሬታችን ተወስዷል " የሚል ጥያቄ እንዳላቸውም ገልጿል። ጥቃቱ የደረሰው " ጮሬ " በሚባለው የፋብሪካው ካምፕ መሆኑን ያስረዳው ነዋሪው፣ " ሟቾቹ የስኳር ፋብሪካው የጥበቃ ሠራተኞች ናቸው። ታጣቂዎቹ ድንገት መጥተው ተኩስ ፈጽመውባቸው ወዲያው ነው ጫካ የሚገቡት " ሲልም ተናግሯል።
በተያያዘ፣ " ሰባቱ ሰዎች ከመገደላቸው ከአንድ ቀን በፊት መተሐራ እና ወለንጭቲ መካከል የከባድ መኪና ሹፌር እና ረዳትም ተገድለው ተገኝተዋል። በአካባቢው የሰዎች መታገት የተለመደ ሆኗል። የጸጥታ አካላት አሉ ግን እያዩ እንዳላዩ ነው የሚሆኑት " ሲልም ገልጿል።
ሌላኛው ነዋሪ፣ ከ2010 ጀምሮ በየዓመቱ እስከ ዘጠኝ ሰው " የሚገደልበት " ሁኔታ መኖሩን አስረድተው፣ " ህዝቡ ዘላቂ የሆነ መፍትሄ እያገኘ አይደለም " ሲሉ ገልጸዋል።
የሰሞኑን ጎድያ በተመከለተም፣ " በአንድ መኪና ላይ ነው ሰባቱንም የመንግስት ተቀጣሪዎች፤ የስንት ልጆች አባቶችን በአንድ ቀን ገድለውብናል " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ሰሞኑን የተገደሉት የመተሐራ ስኳር ፋብሪካ ሠራተኞች " ትልልቅ ሰዎች ናቸው " ሲሉ ያስረዱ አንድ ጉዳዩን በቅርበት የሚያውቁ የፋብሪካው ሠራተኛ ደግሞ፣ ጥቃቱን " አሳዛኝ " ሲሉ ጠርተውታል።
ሰባቱ ሠራተኞች የተገደሉት አንድ የፋብሪካውን አመራር አጅበው በነበረበት ወቅት መሆኑን ተናግረዋል።
የታጣቁት አካላት የፋብሪካው ሠራተኞች ላይ ተኩስ የከፈቱባቸው " ገና ከፒካፕ መኪና ላይ ሳይወርዱ " መሆኑን፣ በዚህም ሌሎቹ ሲገደሉ አብረው የነበሩት አመራሩ " የውሃ ቦይ ውስጥ ገብተው፣ እየተሳቡ " የተኩሱን ቦታ በመራቅ በህይወት መትረፋቸውን አስረድተዋል።
እኚሁ የፋብሪካው ሠራተኛ፣ ይህ ጥቃት ተፈጽሟል ብሎ ለመናገር እንኳ ከፍተኛ ስጋት እንዳለባቸው ገልጸዋል።
ሌላኛው የፋብሪካው ሠራተኛ በበኩላቸው፣ ግድያው የተፈጸመበት " ጮሬ " በተሰኘው ቦታ አጠገብ መሆኑን ገልጸዋል።
በአጠቃላይ ከሟቾቹ ጋር ዘጠኝ ሰዎች ነበሩ ብለው፣ " ሰባቱ ወዲያው ተገደሉ። አንዱ የሞተ መስሏቸው ጥለውት ሄዱ። አልሞተም ግን እግሩ ከጥቅም ውጭ ሆኗል። አንዱ ደግሞ ተርፏል " ብለዋል። " ስድስቱ በሰፊ ጉድጓድ በአንድ ቦታ ተቀብረዋል " ነው ያሉት።
አዲስ የመጡት የፋብሪካው ሥራ አስኪያጅ ለሟች ቤተሰቦች " በየቤታቸው ሂደው ለእያንዳንዳቸው 150 ሺሕ ብር ሰጥተዋል። 'የተማረ ልጅ ካላቸው በቋሚነት ሥራ እንቀጥራን፣ ካልተማሩ በመደብ 6 የአባታቶቻቸውን ቦታ ይይዛሉ' ሲሉም ቃል ገብተዋል " ሲሉ ተናግረዋል።
ጥቃቱ ከደረሰ በኋላ ያለውን ድባብ ሲያስረዱ ደግሞ፣ ለጊዜው "መከላከያ ገብቷል" ብለዋል።
የአካባቢው ነዋሪ ግን፣ " በአካባቢው የጸጥታ ችግር ተንሰራፍቷል። በሰላም ወጥቶ መግባት በጣም አስቸጋሪ ሆኗል " ሲሉም የሁነቱን አሳሳቢነት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
" ከአንድ ወር በፊት ሁለት ልጆች ታግተው 2 ሚሊዮን ብር ተጠይቆባቸው ነበር። 2 ሚሊዮን ብር ተሰብስቦ አንድ ልጅ ወስዶ ሰጣቸው። በኋላም ለቀቋቸው። ከፍተኛ ድብደባ እና ራሳቸውን እስኪስቱ ድረስ የረሃብ ስቃይ አድርሰውባቸው መንገድ ላይ ነው የጣሏቸው " ሲሉም አስታውሰዋል።
" ገንዘቡን ያደረሰው ልጅ ግን ተገድሏል" በማለት አዝነዋል። ከመተሐራ ስኳር ፋብሪካ ሠራተኞች መካከል አንዱ በበኩላቸው፣ ታጣቂዎቹ "ከአዳማ መተሐራ መንገድ በኃይለኛው እያገቱ ነው፤ ተሳፋሪም መውሰድ ጀምረዋል " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የስኳር ፋብሪካውንም ሆነ ሌሎች የአካባቢውን ኃላፊዎች ለማግኘት ለቀናት ያደረገው ጥረት ለጊዜው ያልተሳካ ሲሆን፣ ጥረቱ ይቀጥላል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#tikvahethiopiafamilyaa
tikvahethiopia
4 months ago
" ይህ አይነቱ የወንጀል ድርጊት በአከባቢው ሲፈፀም የመጀመሪያ ነው። የሞት ፍርድ ውሳኔም የመጀመሪያ ነው " - አቶ ነጋልኝ ዓለሙ
በቡርጂ ዞን በውርስ ምክንያት 3 የቤተሰባቸውን አባላትን በጥይት ደብድበው የገደሉ ተከሳሾች በሞት እንዲቀጡ ተወሰነ።
ይህ በአከባቢው የመጀመሪያው የሞት ፍርድ ውሳኔ እንደሆነ ተገልጿል።
የወንጀል ድርጊቱ የተፈጸመው ነሐሴ 16/2017 ዓ/ም ከምሽቱ 2:00 ሰዓት ገደማ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሶያማ ዙሪያ ወረዳ ገራ ቀበሌ መሆኑን በዞን ፍትህ መምሪያ የልዩ ልዩ ወንጀሎች ዘርፍ አስተባባሪ አቶ ነጋልኝ ዓለሙ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
በዚሁ ቀበሌ አቶ ዋቶ ወርቁ የተባሉ አዛውንት ዕድሜያቸው እየገፋ መምጣቱን ተከትሎ በአከባቢው ባህል መሰረት ልጆቻቸውን ጠርተው የመሬት ውርስ ክፍፍል ማድረግ ይጀምራሉ።
ይህ እየሆነ ባለበት በሂደቱ ተቃርኖ የነበራቸው የአዛውንቱ የመጀመሪያ ልጅ እና የልጅ ልጃቸው ሁለቱም የክላሽ ኮቭ መሳሪያ በመታጠቅ በቤተሰብ አባላቱ ላይ ተኩስ መክፈታቸውን አቶ ነጋልኝ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
በጥቃቱ አዛውንቱ አቶ ዋቶ ወርቁን እና ሁለት ልጆቻቸው ወዲያውኑ ሲሞቱ ሁለት የቤተሰብ አባላት ደግሞ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸው ወደ አርባምንጭ ሪፌራል ሆስፒታል መላካቸውን ገልፀዋል።
ፖሊስም ግለሰቦቹን ከነመሳሪያቸው ኤግዚቢትነት በመያዝ ምርመራ ማድረግ ይጀምራል። መዝገቡንም አደራጅቶ ለዞኑ ዐቃቤ ሕግ ያቀርባል።
ዐቃቤ ሕግ መዝገቡን በማደራጀት በሁለቱ ተከሳሾች ላይ በዋና ወንጀል አድራጊነት ፦
• በሶስት የግድያ ወንጀል ክስ በወንጀል ህጉ አንቀጽ 539/1/ሀ መሠረት በከባድ የሰዉ ነብስ ማጥፋት ወንጀል
• ሁለት በህይወት በተረፉ የግል ተበዳዮች ወንጀል ሁለት ክስ በወንጀል ህግ አንቀጽ 27 እና 539/1/ሀ መሠረት ክስ ማቅረቡን አቶ ነጋልኝ አስረድተዋል።
ተከሳሾች ፍርድ ቤት ቀርበው የወንጀል ድርጊቱን ስለመፈፀማቸው ተጠይቀው " አልፈፀምንም " በማለት ክደዉ ተከራክረዋል።
አቃቤ ህግ በሰዉና በሰነድ ማስረጃ አምስቱንም ክስ በሚገባ ያስረዳ ሲሆን ተከሳሾች የቀረበባቸዉን ክስ መከላከል ባለመቻላቸው የቡርጂ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ተከሳሾችን በቀረበባቸው ክሶች ጥፋተኛ ናቸው ብሏል።
የፈፀሙት ወንጀል ጭካኔ የተሞላበትና አስነዋሪ መሆኑ ፤ በአከባቢው ከዚህ ቀደም ተደርጎ የማይታወቅ ፤ ከሁለት በላይ የሆነ የቤተሰብ አባላት ላይ በአንድ ጊዜ የተፈፀመ ግድያ መሆኑን ከግምት ውስጥ ገብቷል።
ፍርድ ቤቱ ሁለቱም ተከሳሾች በሞት እንዲቀጡ ውሳኔ አስተላልፏል።
ይህ አይነቱ የወንጀል ድርጊት በአከባቢው ሲፈፀም የመጀመሪያ ነው ያሉት አቶ ነጋልኝ የሞት ፍርድ ውሳኔም በዞኑ የመጀመሪያ ነው ሲሉ ገልፀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
መጋቢት 18 ቀን 2018 ዓ/ም
tikvahethiopia
በቡርጂ ዞን በውርስ ምክንያት 3 የቤተሰባቸውን አባላትን በጥይት ደብድበው የገደሉ ተከሳሾች በሞት እንዲቀጡ ተወሰነ።
ይህ በአከባቢው የመጀመሪያው የሞት ፍርድ ውሳኔ እንደሆነ ተገልጿል።
የወንጀል ድርጊቱ የተፈጸመው ነሐሴ 16/2017 ዓ/ም ከምሽቱ 2:00 ሰዓት ገደማ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሶያማ ዙሪያ ወረዳ ገራ ቀበሌ መሆኑን በዞን ፍትህ መምሪያ የልዩ ልዩ ወንጀሎች ዘርፍ አስተባባሪ አቶ ነጋልኝ ዓለሙ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
በዚሁ ቀበሌ አቶ ዋቶ ወርቁ የተባሉ አዛውንት ዕድሜያቸው እየገፋ መምጣቱን ተከትሎ በአከባቢው ባህል መሰረት ልጆቻቸውን ጠርተው የመሬት ውርስ ክፍፍል ማድረግ ይጀምራሉ።
ይህ እየሆነ ባለበት በሂደቱ ተቃርኖ የነበራቸው የአዛውንቱ የመጀመሪያ ልጅ እና የልጅ ልጃቸው ሁለቱም የክላሽ ኮቭ መሳሪያ በመታጠቅ በቤተሰብ አባላቱ ላይ ተኩስ መክፈታቸውን አቶ ነጋልኝ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
በጥቃቱ አዛውንቱ አቶ ዋቶ ወርቁን እና ሁለት ልጆቻቸው ወዲያውኑ ሲሞቱ ሁለት የቤተሰብ አባላት ደግሞ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸው ወደ አርባምንጭ ሪፌራል ሆስፒታል መላካቸውን ገልፀዋል።
ፖሊስም ግለሰቦቹን ከነመሳሪያቸው ኤግዚቢትነት በመያዝ ምርመራ ማድረግ ይጀምራል። መዝገቡንም አደራጅቶ ለዞኑ ዐቃቤ ሕግ ያቀርባል።
ዐቃቤ ሕግ መዝገቡን በማደራጀት በሁለቱ ተከሳሾች ላይ በዋና ወንጀል አድራጊነት ፦
• በሶስት የግድያ ወንጀል ክስ በወንጀል ህጉ አንቀጽ 539/1/ሀ መሠረት በከባድ የሰዉ ነብስ ማጥፋት ወንጀል
• ሁለት በህይወት በተረፉ የግል ተበዳዮች ወንጀል ሁለት ክስ በወንጀል ህግ አንቀጽ 27 እና 539/1/ሀ መሠረት ክስ ማቅረቡን አቶ ነጋልኝ አስረድተዋል።
ተከሳሾች ፍርድ ቤት ቀርበው የወንጀል ድርጊቱን ስለመፈፀማቸው ተጠይቀው " አልፈፀምንም " በማለት ክደዉ ተከራክረዋል።
አቃቤ ህግ በሰዉና በሰነድ ማስረጃ አምስቱንም ክስ በሚገባ ያስረዳ ሲሆን ተከሳሾች የቀረበባቸዉን ክስ መከላከል ባለመቻላቸው የቡርጂ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ተከሳሾችን በቀረበባቸው ክሶች ጥፋተኛ ናቸው ብሏል።
የፈፀሙት ወንጀል ጭካኔ የተሞላበትና አስነዋሪ መሆኑ ፤ በአከባቢው ከዚህ ቀደም ተደርጎ የማይታወቅ ፤ ከሁለት በላይ የሆነ የቤተሰብ አባላት ላይ በአንድ ጊዜ የተፈፀመ ግድያ መሆኑን ከግምት ውስጥ ገብቷል።
ፍርድ ቤቱ ሁለቱም ተከሳሾች በሞት እንዲቀጡ ውሳኔ አስተላልፏል።
ይህ አይነቱ የወንጀል ድርጊት በአከባቢው ሲፈፀም የመጀመሪያ ነው ያሉት አቶ ነጋልኝ የሞት ፍርድ ውሳኔም በዞኑ የመጀመሪያ ነው ሲሉ ገልፀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
መጋቢት 18 ቀን 2018 ዓ/ም
tikvahethiopia
4 months ago
የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር በሀገር አቀፍ ደረጃ ወጥነት ያለዉ አዲስ የታርጋ ለውጥ ለማድረግ ሲያከናውን የቆየውን የቅድመ ዝግጅት ስራ አጠናቆ በቅርቡ አዲስ የተሸከርካሪ ሰሌዳ መለያ ቁጥር (ታርጋ) መስጠት እንደሚጀምር አስታወቀ።
የታርጋ መስጠት ስራዉ ከመጀመሩ በፊት ግለሰቦች ወይም ተቋማት የሚፈልጓቸዉን የሰሌዳ ቁጥሮች አጫርቶ ላሸነፉ አካላት ለመስጠት እንደሚፈልግ ገልጿል።
የስርጭት ስራዉ ከመጀመሩ በፊት ግለሰቦች ወይም ተቋማት የሚፈልጉትን ቁጥር በመለየት በሚኒስቴር መስሪያቤቱ 5ኛ ፎቅ በመቅረብ ከ17/07/18 ዓ/ም ጀምሮ ባለዉ አንድ ሳምንት ጊዜ እንዲመዘገቡ ጥሪ አቅርቧል።
tikvahethiopia
የታርጋ መስጠት ስራዉ ከመጀመሩ በፊት ግለሰቦች ወይም ተቋማት የሚፈልጓቸዉን የሰሌዳ ቁጥሮች አጫርቶ ላሸነፉ አካላት ለመስጠት እንደሚፈልግ ገልጿል።
የስርጭት ስራዉ ከመጀመሩ በፊት ግለሰቦች ወይም ተቋማት የሚፈልጉትን ቁጥር በመለየት በሚኒስቴር መስሪያቤቱ 5ኛ ፎቅ በመቅረብ ከ17/07/18 ዓ/ም ጀምሮ ባለዉ አንድ ሳምንት ጊዜ እንዲመዘገቡ ጥሪ አቅርቧል።
tikvahethiopia
4 months ago
#ምርጫ2018
ፓርቲዎች ለመጪው ምርጫ እጩዎቻቸውን እያስተዋወቁ ይገኛሉ።
ገዢው ብልፅግና ፓርቲም ለመጪው ምርጫ የሚወዳደሩ እጩዎችን እያስተዋወቀ ሲሆን ከነዚህም እጩዎች መካከል ጋዜጠኛ ፣ አርቲስት ፣ እንዲሁም አርሶ አደር የሆኑ ይገኙበታል።
በአዲስ አበባ ለምክር ቤት እጩ ሆነው ከቀረቡት መካከል አንደኛው በሙዚቃ አቀናባሪነት የሚታወቀው ካሙዙ ካሳ ነው።
ሙዚቀኛው ፥ ስራው አርቲስት ፣ የትምህርት ደረጃው መካከለኛ ደረጃ ትምህርት እንዲሁም የሚወዳደረው የካ ክፍለ ከተማ መሆኑ ተገልጾ ይፋ ተደርጓል።
ሌላኛዋ የቀድሞ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋዜጠኛዋ ወ/ሮ በሻቱ ቶሎማርያም እዛው የካ ክፍለ ከተማ እጩ ሆና ቀርባለች።
ከዚህ በተጨማሪ አቶ ሹሜ ግዛው የተባሉ አርሶ አደርም በእጩነት ቀርበዋል።
በዚህ ክፍለ ከተማ ሌሎች በፌዴራል ደረጃ፣ በከተማ፣ በክፍለ ከተማ አመራርነት ላይ የሚገኙ እጩዎችም ቀርበዋል።
ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከቀረቡ እጩዎች መካከል ደግሞ ዶ/ር መቅደስ ዳባ ፣ ወ/ሮ አይሻ መሃመድ ፣ ዶ/ር ሌሊሴ ነሜ ይገኙበታል።
መረጃው የየካ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መጋቢት 15 ቀን 2018 ዓ/ም
tikvahethiopia
ፓርቲዎች ለመጪው ምርጫ እጩዎቻቸውን እያስተዋወቁ ይገኛሉ።
ገዢው ብልፅግና ፓርቲም ለመጪው ምርጫ የሚወዳደሩ እጩዎችን እያስተዋወቀ ሲሆን ከነዚህም እጩዎች መካከል ጋዜጠኛ ፣ አርቲስት ፣ እንዲሁም አርሶ አደር የሆኑ ይገኙበታል።
በአዲስ አበባ ለምክር ቤት እጩ ሆነው ከቀረቡት መካከል አንደኛው በሙዚቃ አቀናባሪነት የሚታወቀው ካሙዙ ካሳ ነው።
ሙዚቀኛው ፥ ስራው አርቲስት ፣ የትምህርት ደረጃው መካከለኛ ደረጃ ትምህርት እንዲሁም የሚወዳደረው የካ ክፍለ ከተማ መሆኑ ተገልጾ ይፋ ተደርጓል።
ሌላኛዋ የቀድሞ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋዜጠኛዋ ወ/ሮ በሻቱ ቶሎማርያም እዛው የካ ክፍለ ከተማ እጩ ሆና ቀርባለች።
ከዚህ በተጨማሪ አቶ ሹሜ ግዛው የተባሉ አርሶ አደርም በእጩነት ቀርበዋል።
በዚህ ክፍለ ከተማ ሌሎች በፌዴራል ደረጃ፣ በከተማ፣ በክፍለ ከተማ አመራርነት ላይ የሚገኙ እጩዎችም ቀርበዋል።
ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከቀረቡ እጩዎች መካከል ደግሞ ዶ/ር መቅደስ ዳባ ፣ ወ/ሮ አይሻ መሃመድ ፣ ዶ/ር ሌሊሴ ነሜ ይገኙበታል።
መረጃው የየካ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መጋቢት 15 ቀን 2018 ዓ/ም
tikvahethiopia
Sponsored by
Surafel
5 months ago
" መጋቢት 15/2018 ዓ/ም ከቀኑ 11 ሰዓት 30 ላይ ሲስተሙን እንዘጋለን ፤ ከዚያ በኋላ ማንም መመዝገብ አይችልም " - እሸቱ ከበደ (ዶ/ር)
🗓 የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና መስጫ ትክክለኛ ጊዜው ገና ባይጸድቅም ፈተናው ሰኔ ውስጥ እንደሚሰጥ ተጠቁሟል !
የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ምዝገባ መጋቢት 15 ቀን 2018 ከቀኑ 11 ሰዓት 30 እንደሚጠናቀቅ፣ ያልተመዘገበ እንደማይፈተን በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አሳስቧል።
የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር)፣ ለምዝገባ የተሰጠው የወር ጊዜ መሆኑን ገልጸው፣ " ሁሉም ተሯሩጦ መመዝገብ አለበት፤ ያልተመዘገበ ተማሪ ሳልመዘገብ አምልጦኝ ቢል ምንም ማድረግ አንችልም፤ ቀጣይ አመት ይፈተናል " ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
ወላጆችም ልጆቻቸው መመዝገባቸውን እንዲያረጋግጡ አስገንዝበው፣ " መጋቢት 15/2018 ዓ/ም 11 ሰዓት ተኩል ላይ ሲስተሙን እንዘጋለን፤ ከዚያ በኋላ ማንም መመዝገብ አይችልም " ነው ያሉት።
በጀት ከተመደበ፣ ፈተና አስፈጻሚዎች ከተሰማሩ በኋላ አዲስ ተመዝጋቢ ቢቀርብ ለማስተናገድ እንደሚቸገሩ አስረድተዋል። ትክክለኛ ጊዜው ገና ባይጸድቅም ፈተናው ሰኔ ውስጥ እንደሚሰጥ ጠቁመዋል።
ተመዝጋቢዎች ከ9 እስከ 11 የተማሩበት ውጤት ሊኖራቸው እና አሁን ላይ 12ኛ ክፍል እየተማሩ ሊሆኑ እንደሚገባ ገልጸዋል። ድጋሚ ለሚፈተኑ ደግሞ 750 ብር ክፍያ በመፈጸም ከዚህ በፊት የተፈተኑበትን አድሚሽን ካርድ ማስገባት፣ https://register.eaes.et ላይ መመዝገብ እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ይህም 150 ብሩ ለምዝገባ፣ ለእያንዳንዱ ስድስት ፈተና 100 ብር ተደርጎ ተሰልቶ፣ ተፈታኞች " ቢያንስ ኮስት ሸር " እንዲያደርጉ እና " ከፍዬ ነው " በሚል ለፈተናው ትኩረት እንዲሰጡ ታስቦ የተወሰነ መሆኑን ገልጸዋል።
ተፈታኞች በመረጡበት የፈተና ማእከል መፈተን እንደሚችሉ ያስረዱት እሸቱ (ዶ/ር)፣ " ለምሳሌ አምና አርባምንጭ የተፈተነ ተማሪ፣ ዘንድሮ ወደ አዲስ አበባ መጥቶ ከሆነ ለመፈተን አርባምንጭ መሄድ ሳይጠበቅበት አዲስ አበባ ካሉ ትምህርት ቤት አንዱን መርጦ የግል ተፈታኝ ሆኖ ይፈተናል " ብለዋል።
tikvahethiopia
🗓 የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና መስጫ ትክክለኛ ጊዜው ገና ባይጸድቅም ፈተናው ሰኔ ውስጥ እንደሚሰጥ ተጠቁሟል !
የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ምዝገባ መጋቢት 15 ቀን 2018 ከቀኑ 11 ሰዓት 30 እንደሚጠናቀቅ፣ ያልተመዘገበ እንደማይፈተን በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል አሳስቧል።
የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር)፣ ለምዝገባ የተሰጠው የወር ጊዜ መሆኑን ገልጸው፣ " ሁሉም ተሯሩጦ መመዝገብ አለበት፤ ያልተመዘገበ ተማሪ ሳልመዘገብ አምልጦኝ ቢል ምንም ማድረግ አንችልም፤ ቀጣይ አመት ይፈተናል " ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
ወላጆችም ልጆቻቸው መመዝገባቸውን እንዲያረጋግጡ አስገንዝበው፣ " መጋቢት 15/2018 ዓ/ም 11 ሰዓት ተኩል ላይ ሲስተሙን እንዘጋለን፤ ከዚያ በኋላ ማንም መመዝገብ አይችልም " ነው ያሉት።
በጀት ከተመደበ፣ ፈተና አስፈጻሚዎች ከተሰማሩ በኋላ አዲስ ተመዝጋቢ ቢቀርብ ለማስተናገድ እንደሚቸገሩ አስረድተዋል። ትክክለኛ ጊዜው ገና ባይጸድቅም ፈተናው ሰኔ ውስጥ እንደሚሰጥ ጠቁመዋል።
ተመዝጋቢዎች ከ9 እስከ 11 የተማሩበት ውጤት ሊኖራቸው እና አሁን ላይ 12ኛ ክፍል እየተማሩ ሊሆኑ እንደሚገባ ገልጸዋል። ድጋሚ ለሚፈተኑ ደግሞ 750 ብር ክፍያ በመፈጸም ከዚህ በፊት የተፈተኑበትን አድሚሽን ካርድ ማስገባት፣ https://register.eaes.et ላይ መመዝገብ እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ይህም 150 ብሩ ለምዝገባ፣ ለእያንዳንዱ ስድስት ፈተና 100 ብር ተደርጎ ተሰልቶ፣ ተፈታኞች " ቢያንስ ኮስት ሸር " እንዲያደርጉ እና " ከፍዬ ነው " በሚል ለፈተናው ትኩረት እንዲሰጡ ታስቦ የተወሰነ መሆኑን ገልጸዋል።
ተፈታኞች በመረጡበት የፈተና ማእከል መፈተን እንደሚችሉ ያስረዱት እሸቱ (ዶ/ር)፣ " ለምሳሌ አምና አርባምንጭ የተፈተነ ተማሪ፣ ዘንድሮ ወደ አዲስ አበባ መጥቶ ከሆነ ለመፈተን አርባምንጭ መሄድ ሳይጠበቅበት አዲስ አበባ ካሉ ትምህርት ቤት አንዱን መርጦ የግል ተፈታኝ ሆኖ ይፈተናል " ብለዋል።
tikvahethiopia
5 months ago
" ለግድያ የሚያበቃ ምንም ዓይነት ጥል ሳይኖር የመኖሪያ ቤቱን በር ከውስጥ በመቆለፍ ወላጅ እናቱንና እህቱን በሳንጃ ነው በጭካኔ የገደለው " - ኢንስፔክተር ደሣለኝ ዳመና
ወላጅ እናቱንና እህቱን በዘግናኝ ሁኔታ የገደለው ግለሰብ በሞት እንዲቀጣ ተወሰነ።
አሰቃቂ የወንጀል ድርጊቱ የተፈጸመው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀዲያ ዞን ምዕራብ ባድዋቾ ወረዳ ገርቦ ቀበሌ ነው።
በዚሁ ቀበሌ ወላጅ እናቱንና እህቱን በዘግናኝ ሁኔታ በገደለ ግለሰብ ላይ የሞት ፍርድ ውሳኔ መተላለፉን የሀዲያ ዞን ከፍተኛ ዐቃቤ ሕግና የምዕራብ ባድዋቾ ወረዳ ፖሊስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታውቀዋል።
የምዕራብ ባድዋቾ ወረዳ ፖሊስ የወንጀልና ታክቲክ ጉዳዮች ምርመራ ዘርፍ አስተባባሪ ኢንስፔክተር ደሣለኝ ዳመና ምን አሉ ?
" ተከሳሹ ወጣት ሰንበቶ መንገሻ ይባላል።
ጥር 9 ቀን 2018 ዓ.ም ለግድያ የሚያበቃ ምንም ዓይነት ጥል ሳይኖር የመኖሪያ ቤቱን በር ከውስጥ በመቆለፍ ወላጅ እናቱንና እህቱን በሳንጃ በጭካኔ ገድሏል።
ፖሊስ ባደረገው ማጣራት፣ ወንጀል ፈጻሚው ወላጅ እናቱን በሳንጃ አንገታቸውን፣ ሆዳቸውንና ጀርባቸውን በመውጋት፣ እንዲሁም ጡታቸውን በመቁረጥ ሕይወታቸው እንዲያልፍ አድርጓል።
ይህን ድርጊት አይታ የጮኸችውን ታናሽ እህቱንም በአንገቷ አካባቢ ደጋግሞ በመውጋት ለሞት ዳርጓክ።
ተከሳሹ ቀደም ሲል የመከላከያ አባል ነበር በሕገ-ወጥ መንገድ ከድቶ (ኮብልሎ) የወጣ ነው። " ብለዋል።
የሀዲያ ዞን ሾኔ ምድብ ችሎት ከፍተኛ ዐቃቤ ሕግ አቶ ግዛቸው ታደሴ በበኩላቸው፤ ተከሳሹ ወንጀሉን የፈጸመበትን አኳኋን ከፖሊስ ጋር በመሆን በምርመራ ማጣራታቸውን ገልጸዋል።
ለፍርድ ቤቱም የአስከሬን ምርመራ ማስረጃ፣ ተከሳሹ ለወረዳው ፍርድ ቤት የሰጠው የእምነት ክህደት ቃል እና የሰው ምስክሮችን በማቅረብ ክስ ተመስርቷል።
የክስ መዝገቡን የተመለከተው የሀዲያ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሾኔ ምድብ ችሎት የድርጊቱን አሰቃቂነትና የተከሳሹን የጭካኔ ደረጃ ከግምት ውስጥ በማስገባት ግለሰቡ በሞት እንዲቀጣ በሙሉ ድምፅ ወስኖበታል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
መጋቢት 11 ቀን 2018 ዓ/ም
tikvahethiopia
ወላጅ እናቱንና እህቱን በዘግናኝ ሁኔታ የገደለው ግለሰብ በሞት እንዲቀጣ ተወሰነ።
አሰቃቂ የወንጀል ድርጊቱ የተፈጸመው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሀዲያ ዞን ምዕራብ ባድዋቾ ወረዳ ገርቦ ቀበሌ ነው።
በዚሁ ቀበሌ ወላጅ እናቱንና እህቱን በዘግናኝ ሁኔታ በገደለ ግለሰብ ላይ የሞት ፍርድ ውሳኔ መተላለፉን የሀዲያ ዞን ከፍተኛ ዐቃቤ ሕግና የምዕራብ ባድዋቾ ወረዳ ፖሊስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታውቀዋል።
የምዕራብ ባድዋቾ ወረዳ ፖሊስ የወንጀልና ታክቲክ ጉዳዮች ምርመራ ዘርፍ አስተባባሪ ኢንስፔክተር ደሣለኝ ዳመና ምን አሉ ?
" ተከሳሹ ወጣት ሰንበቶ መንገሻ ይባላል።
ጥር 9 ቀን 2018 ዓ.ም ለግድያ የሚያበቃ ምንም ዓይነት ጥል ሳይኖር የመኖሪያ ቤቱን በር ከውስጥ በመቆለፍ ወላጅ እናቱንና እህቱን በሳንጃ በጭካኔ ገድሏል።
ፖሊስ ባደረገው ማጣራት፣ ወንጀል ፈጻሚው ወላጅ እናቱን በሳንጃ አንገታቸውን፣ ሆዳቸውንና ጀርባቸውን በመውጋት፣ እንዲሁም ጡታቸውን በመቁረጥ ሕይወታቸው እንዲያልፍ አድርጓል።
ይህን ድርጊት አይታ የጮኸችውን ታናሽ እህቱንም በአንገቷ አካባቢ ደጋግሞ በመውጋት ለሞት ዳርጓክ።
ተከሳሹ ቀደም ሲል የመከላከያ አባል ነበር በሕገ-ወጥ መንገድ ከድቶ (ኮብልሎ) የወጣ ነው። " ብለዋል።
የሀዲያ ዞን ሾኔ ምድብ ችሎት ከፍተኛ ዐቃቤ ሕግ አቶ ግዛቸው ታደሴ በበኩላቸው፤ ተከሳሹ ወንጀሉን የፈጸመበትን አኳኋን ከፖሊስ ጋር በመሆን በምርመራ ማጣራታቸውን ገልጸዋል።
ለፍርድ ቤቱም የአስከሬን ምርመራ ማስረጃ፣ ተከሳሹ ለወረዳው ፍርድ ቤት የሰጠው የእምነት ክህደት ቃል እና የሰው ምስክሮችን በማቅረብ ክስ ተመስርቷል።
የክስ መዝገቡን የተመለከተው የሀዲያ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሾኔ ምድብ ችሎት የድርጊቱን አሰቃቂነትና የተከሳሹን የጭካኔ ደረጃ ከግምት ውስጥ በማስገባት ግለሰቡ በሞት እንዲቀጣ በሙሉ ድምፅ ወስኖበታል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
መጋቢት 11 ቀን 2018 ዓ/ም
tikvahethiopia
Comments