15 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የተቀሰቀሰውን ጦርነት ተከትሎ፣ ሞስኮ በሁለቱ ሀገራት መካከል ለሚደረጉ ማናቸውም የሰላም ድርድሮች አስፈላጊውን እገዛ ለማድረግ ዝግጁ መሆኗን የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ምክትል ሚኒስትር ሰርጌይ ራያብኮቭ አስታወቁ።
ምክትል ሚኒስትሩ አክለውም ሩሲያ ድጋፍ ለማድረግ ፍላጎት ቢኖራትም፣ ፍላጎቷን ግን በሁለቱ ወገኖች ላይ በግድ የመጫን እቅድ እንደሌላት በግልጽ ተናግረዋል።
ሰርጌይ ራያብኮቭ ከሀገሪቱ የመንግስት የዜና ወኪል ታስ (TASS) ጋር ባደረጉት ቃለ-ምልልስ፣ "ይህንን ግጭት ለመፍታት ሩሲያ ሊደረግ የሚችለውን ሁሉንም ዓይነት ድጋፍ ለመስጠት ዝግጁ መሆኗን ተፋላሚዎቹ ወገኖች በሚገባ ያውቃሉ። በተመሳሳይ ጊዜ እኛ አገልግሎታችንን በነሱ ላይ በፍጹም ጭነን አናውቅም፤ የመጫንም ፍላጎት የለንም። ነገር ግን ተገቢው ጥያቄ ከቀረበልን የመርጃ እጃችንን እንዘረጋለን" ብለዋል።
ምክትል ሚኒስትሩ ሞስኮ ሁልጊዜም ቢሆን ለችግሮች መፍትሄ የሚገኘው በፖለቲካዊ እና በዲፕሎማሲያዊ መንገዶች ብቻ ነው የሚል ፅኑ እምነት እንዳላት እና አሁንም ለዚህ ቁርጠኛ መሆኗን አፅንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።
ዋሽንግተን እና ቴህራን የድርድር ሂደቱን ለመቀጠል እያደረጉ ያሉትን ሙከራዎች ሩሲያ እንደምትደግፍ የገለጹት ራያብኮቭ፣ በተለይም በአካባቢው መረጋጋት እንዲሰፍን እና ለዘላቂ ሰላም ምቹ ሁኔታዎች እንዲፈጠሩ ለማድረግ የፓኪስታን ወገን እያጫወተ ያለውን ንቁ እና አዎንታዊ ሚና አድንቀዋል።
ምክትል ሚኒስትሩ አክለውም ሩሲያ ድጋፍ ለማድረግ ፍላጎት ቢኖራትም፣ ፍላጎቷን ግን በሁለቱ ወገኖች ላይ በግድ የመጫን እቅድ እንደሌላት በግልጽ ተናግረዋል።
ሰርጌይ ራያብኮቭ ከሀገሪቱ የመንግስት የዜና ወኪል ታስ (TASS) ጋር ባደረጉት ቃለ-ምልልስ፣ "ይህንን ግጭት ለመፍታት ሩሲያ ሊደረግ የሚችለውን ሁሉንም ዓይነት ድጋፍ ለመስጠት ዝግጁ መሆኗን ተፋላሚዎቹ ወገኖች በሚገባ ያውቃሉ። በተመሳሳይ ጊዜ እኛ አገልግሎታችንን በነሱ ላይ በፍጹም ጭነን አናውቅም፤ የመጫንም ፍላጎት የለንም። ነገር ግን ተገቢው ጥያቄ ከቀረበልን የመርጃ እጃችንን እንዘረጋለን" ብለዋል።
ምክትል ሚኒስትሩ ሞስኮ ሁልጊዜም ቢሆን ለችግሮች መፍትሄ የሚገኘው በፖለቲካዊ እና በዲፕሎማሲያዊ መንገዶች ብቻ ነው የሚል ፅኑ እምነት እንዳላት እና አሁንም ለዚህ ቁርጠኛ መሆኗን አፅንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።
ዋሽንግተን እና ቴህራን የድርድር ሂደቱን ለመቀጠል እያደረጉ ያሉትን ሙከራዎች ሩሲያ እንደምትደግፍ የገለጹት ራያብኮቭ፣ በተለይም በአካባቢው መረጋጋት እንዲሰፍን እና ለዘላቂ ሰላም ምቹ ሁኔታዎች እንዲፈጠሩ ለማድረግ የፓኪስታን ወገን እያጫወተ ያለውን ንቁ እና አዎንታዊ ሚና አድንቀዋል።
2 months ago
ሩሲያ ለሽያጭ ቤንዚን ወደ ውጭ ሀገራት አልክም አለች
#ethiopia | የሩሲያ መንግስት ከፊታችን መጋቢት 23 ቀን 2018 ጀምሮ ለሚቀጥሉት ስድስት ወራት የሚቆይ የቤንዚን ኤክስፖርት እገዳ ለመጣል መወሰኑን አስታወቀ። ይህ ውሳኔ በዓለም አቀፍ ደረጃ እየታየ ያለውን የነዳጅ ዋጋ መለዋወጥ ተከትሎ የሀገር ውስጥ ገበያውን ለማረጋጋት የታለመ መሆኑ ተገልጿል።
የሩሲያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አሌክሳንደር ኖቫክ የኢነርጂ ሚኒስቴር እገዳውን የሚጥል ረቂቅ ደንብ እንዲያዘጋጅ ትእዛዝ አስተላልፈዋል። እንደ መንግስታዊው የዜና ወኪል ታስ (TASS) ዘገባ ከሆነ፣ እገዳው እስከ ሐምሌ 24 ቀን 2018 ድረስ የሚቆይ ይሆናል።
ሩሲያ ይህን ጠንከር ያለ እርምጃ እንድትወስድ ካስገደዷት ምክንያቶች መካከል፦
* በመካከለኛው ምስራቅ ባለው ጦርነት ሳቢያ የሚታየውን የነዳጅ ዋጋ መለዋወጥ መቋቋም፣
* የሀገር ውስጥ የነዳጅ አቅርቦትን ማረጋጋት፣
* በሀገር ውስጥ የሚታየውን የዋጋ ንረት መቆጣጠር ዋነኞቹ ናቸው።
ሩሲያ ባለፈው የፈረንጆቹ ዓመት ብቻ ወደ 5 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን የሚጠጋ ቤንዚን ለዓለም ገበያ ያቀረበች ግዙፍ ሀገር በመሆኗ፣ አሁን የጣለችው እገዳ በዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ ላይ ከፍተኛ ጫና ሊፈጥር እንደሚችል የዘርፉ ባለሙያዎች እየገለጹ ይገኛሉ።
በተለይም የነዳጅ ፍላጎት በሚጨምርባቸው ወቅቶች ላይ አቅርቦቱ መቋረጡ የዋጋ ጭማሪን ሊያስከትል ይችላል ተብሎ ተሰግቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #russia #fuelexportban #globalenergy #oilmarket #gasolineprices #economynews #alexandernovak #tass #etbusinessview #ቅዳሜገበያ
#ethiopia | የሩሲያ መንግስት ከፊታችን መጋቢት 23 ቀን 2018 ጀምሮ ለሚቀጥሉት ስድስት ወራት የሚቆይ የቤንዚን ኤክስፖርት እገዳ ለመጣል መወሰኑን አስታወቀ። ይህ ውሳኔ በዓለም አቀፍ ደረጃ እየታየ ያለውን የነዳጅ ዋጋ መለዋወጥ ተከትሎ የሀገር ውስጥ ገበያውን ለማረጋጋት የታለመ መሆኑ ተገልጿል።
የሩሲያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አሌክሳንደር ኖቫክ የኢነርጂ ሚኒስቴር እገዳውን የሚጥል ረቂቅ ደንብ እንዲያዘጋጅ ትእዛዝ አስተላልፈዋል። እንደ መንግስታዊው የዜና ወኪል ታስ (TASS) ዘገባ ከሆነ፣ እገዳው እስከ ሐምሌ 24 ቀን 2018 ድረስ የሚቆይ ይሆናል።
ሩሲያ ይህን ጠንከር ያለ እርምጃ እንድትወስድ ካስገደዷት ምክንያቶች መካከል፦
* በመካከለኛው ምስራቅ ባለው ጦርነት ሳቢያ የሚታየውን የነዳጅ ዋጋ መለዋወጥ መቋቋም፣
* የሀገር ውስጥ የነዳጅ አቅርቦትን ማረጋጋት፣
* በሀገር ውስጥ የሚታየውን የዋጋ ንረት መቆጣጠር ዋነኞቹ ናቸው።
ሩሲያ ባለፈው የፈረንጆቹ ዓመት ብቻ ወደ 5 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን የሚጠጋ ቤንዚን ለዓለም ገበያ ያቀረበች ግዙፍ ሀገር በመሆኗ፣ አሁን የጣለችው እገዳ በዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ ላይ ከፍተኛ ጫና ሊፈጥር እንደሚችል የዘርፉ ባለሙያዎች እየገለጹ ይገኛሉ።
በተለይም የነዳጅ ፍላጎት በሚጨምርባቸው ወቅቶች ላይ አቅርቦቱ መቋረጡ የዋጋ ጭማሪን ሊያስከትል ይችላል ተብሎ ተሰግቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #russia #fuelexportban #globalenergy #oilmarket #gasolineprices #economynews #alexandernovak #tass #etbusinessview #ቅዳሜገበያ
3 months ago
የኢራቅ የታጠቀ ቡድን ካታኢብ ሄዝቦላህ
በአሜሪካ የጦር ሰፈሮች ላይ ጥቃት እንደሚያደርስ አስጠነቀቀ
የኢራቁ ተደማጭነት ያለውና በኢራን የሚደገፈው ካታኢብ ሄዝቦላህ በአሜሪካ የጦር ሰፈሮች ላይ ጥቃት ለመሰንዘር መዘጋጀቱን አስታወቀ።
ቡድኑ ይህንን ማስጠንቀቂያ የሰጠው ዛሬ በደቡብ ኢራቅ በሚገኘው የጁርፍ አል-ሳካር የጦር ሰፈር ላይ የተፈጸመውን የአየር ጥቃት ተከትሎ ነው።
በተሰነዘረው ጥቃት ቢያንስ ሁለት የቡድኑ ተዋጊዎች መገደላቸውንና ሌሎች አምስት መቁሰላቸውን የድርጅቱ ምንጮች አረጋግጠዋል።
የቡድኑ መግለጫ "ለተፈጸመብን ጥቃት ምላሽ ለመስጠት በቅርቡ በአሜሪካ የጦር ሰፈሮች ላይ ጥቃት መጀመራችን አይቀሬ ነው" ሲል ዝቷል ማለቱን TASS ዘግቧል።
በተያያዘ ዜና ሉፍታንሳ ወደ እስራኤልና መካከለኛው ምስራቅ የሚያደርጋቸውን በረራዎች በሙሉ እስከ መጋቢት ወር መጀመሪያ ድረስ ሰርዟል። ሁኔታው ወደ ሰፋ ያለ ቀጠናዊ ጦርነት ሊያመራ እንደሚችል ተሰግቷል።
በአሜሪካ የጦር ሰፈሮች ላይ ጥቃት እንደሚያደርስ አስጠነቀቀ
የኢራቁ ተደማጭነት ያለውና በኢራን የሚደገፈው ካታኢብ ሄዝቦላህ በአሜሪካ የጦር ሰፈሮች ላይ ጥቃት ለመሰንዘር መዘጋጀቱን አስታወቀ።
ቡድኑ ይህንን ማስጠንቀቂያ የሰጠው ዛሬ በደቡብ ኢራቅ በሚገኘው የጁርፍ አል-ሳካር የጦር ሰፈር ላይ የተፈጸመውን የአየር ጥቃት ተከትሎ ነው።
በተሰነዘረው ጥቃት ቢያንስ ሁለት የቡድኑ ተዋጊዎች መገደላቸውንና ሌሎች አምስት መቁሰላቸውን የድርጅቱ ምንጮች አረጋግጠዋል።
የቡድኑ መግለጫ "ለተፈጸመብን ጥቃት ምላሽ ለመስጠት በቅርቡ በአሜሪካ የጦር ሰፈሮች ላይ ጥቃት መጀመራችን አይቀሬ ነው" ሲል ዝቷል ማለቱን TASS ዘግቧል።
በተያያዘ ዜና ሉፍታንሳ ወደ እስራኤልና መካከለኛው ምስራቅ የሚያደርጋቸውን በረራዎች በሙሉ እስከ መጋቢት ወር መጀመሪያ ድረስ ሰርዟል። ሁኔታው ወደ ሰፋ ያለ ቀጠናዊ ጦርነት ሊያመራ እንደሚችል ተሰግቷል።
4 months ago
የቀድሞው የሩሲያ ምክትል የፍትህ ሚኒስትር ሞተው ተገኙ
የቀድሞው የሩሲያ ምክትል የፍትህ ሚኒስትር ሰርጌይ ትሮፒን በሞስኮ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ህይወታቸው አልፎ መገኘቱን የሀገሪቱ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።
አስከሬኑ የተገኘበት ሁኔታ፦ የ70 ዓመቱ ሰርጌይ ትሮፒን አስከሬን የተገኘው በምዕራብ ሞስኮ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው መታጠቢያ ክፍል (Bathroom) ውስጥ ነው።
ምርመራ፦ እስካሁን ባለው መረጃ በሰውነታቸው ላይ ምንም ዓይነት የጥቃት ምልክት እንዳልተገኘ የድንገተኛ አደጋ ባለስልጣናት ገልጸዋል።
የሞት መንስኤ፦ የሞታቸው ትክክለኛ መንስኤ በመጣራት ላይ ቢሆንም፣ የሩሲያ መንግስታዊ የዜና ወኪል (TASS) እንደዘገበው የወንጀል ድርጊት (Foul play) ስለመኖሩ የሚጠቁም ፍንጭ የለም።
ስለ ሰርጌይ ትሮፒን ባጭሩ፦
ሰርጌይ ትሮፒን እ.ኤ.አ. ከ1996 እስከ 1997 ባሉት ዓመታት የሩሲያ ምክትል የፍትህ ሚኒስትር በመሆን ማገልገላቸው ይታወሳል።
የቀድሞው የሩሲያ ምክትል የፍትህ ሚኒስትር ሰርጌይ ትሮፒን በሞስኮ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ህይወታቸው አልፎ መገኘቱን የሀገሪቱ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።
አስከሬኑ የተገኘበት ሁኔታ፦ የ70 ዓመቱ ሰርጌይ ትሮፒን አስከሬን የተገኘው በምዕራብ ሞስኮ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው መታጠቢያ ክፍል (Bathroom) ውስጥ ነው።
ምርመራ፦ እስካሁን ባለው መረጃ በሰውነታቸው ላይ ምንም ዓይነት የጥቃት ምልክት እንዳልተገኘ የድንገተኛ አደጋ ባለስልጣናት ገልጸዋል።
የሞት መንስኤ፦ የሞታቸው ትክክለኛ መንስኤ በመጣራት ላይ ቢሆንም፣ የሩሲያ መንግስታዊ የዜና ወኪል (TASS) እንደዘገበው የወንጀል ድርጊት (Foul play) ስለመኖሩ የሚጠቁም ፍንጭ የለም።
ስለ ሰርጌይ ትሮፒን ባጭሩ፦
ሰርጌይ ትሮፒን እ.ኤ.አ. ከ1996 እስከ 1997 ባሉት ዓመታት የሩሲያ ምክትል የፍትህ ሚኒስትር በመሆን ማገልገላቸው ይታወሳል።
6 months ago
ዊትኮፍ ክሬምሊን ገቡ። ሰአት ወደ ታች መቁጠሩ ተጀምረ
እሳቸውና ጃሬድ ኩሽነር ከፑቲን ጋር በድርድር ላይ ናቸው።
የአሜሪካ ልዩ ልዑክ ስቲቭ ዊትኮፍ የሩሲያና ዩክሬን ጦርነትን ለማቆም ድርድሩን ለማፋጠን ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር እጅግ አስፈላጊ የሆኑ ንግግሮች ለማድረግ ክሬምሊን ገብተዋል።
ከእሳቸው ጋር አብረው ያሉት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት አማች የሆኑት እና በጋዛ ሰላምን በማምጣት ረገድም ቁልፍ ሚና የተጫወቱት ጃሬድ ኩሽነር መሆናቸውን የሩሲያ ሚዲያዎች ዘግበዋል።
ሁለቱ አሜሪካውያን በአውሮፕላን ማረፊያ የተቀበሏቸው የሩሲያ የኢንቨስትመንት ፈንድ ኃላፊ ኪሪል ዲሚትሪየቭ ናቸው፣ ነገር ግን ከሩሲያ በኩል በስብሰባው ላይ የሚገኙት ፑቲን እና አስተርጓሚ ብቻ ናቸው።
የTASS ዘገባ መሰረት የሩሲያ መንግስት ቃል አቀባይ ፔስኮቭ በሰጡት መግለጫ ላይ ሦስቱ ብቻ ንግግር እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል።
ዊትኮፍ በጄኔቫ እና ፍሎሪዳ በተደረጉት የቅርብ ጊዜ ድርድሮች ዙሪያ የተዘጋጀውን የአሜሪካ-ዩክሬን የሥራ ማዕቀፍ የቅርብ ጊዜ እትም ለፑቲን ያቀርባሉ።
ፔስኮቭ በተጨማሪም ሞስኮ ለሰላም ንግግሮች ዝግጁ መሆኗን ገልጸዋል፣ ነገር ግን ግቦቿን ማሳካት እንዳለባት አሳስበዋል።
ዲሚትሪየቭ ዛሬን ለዓለም አስፈላጊ ቀን ነው ሲሉ ጠርተውታል።
“ለዓለም አስፈላጊ ቀን ነው፡ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕን የጋዛ የሰላም ስምምነት ያዘጋጀው ቡድን የትራምፕን የሰላም አጀንዳ በዩክሬን ለማስቀጠል ወደ ሞስኮ ይመጣሉ” ብለዋል።
እሳቸውና ጃሬድ ኩሽነር ከፑቲን ጋር በድርድር ላይ ናቸው።
የአሜሪካ ልዩ ልዑክ ስቲቭ ዊትኮፍ የሩሲያና ዩክሬን ጦርነትን ለማቆም ድርድሩን ለማፋጠን ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር እጅግ አስፈላጊ የሆኑ ንግግሮች ለማድረግ ክሬምሊን ገብተዋል።
ከእሳቸው ጋር አብረው ያሉት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት አማች የሆኑት እና በጋዛ ሰላምን በማምጣት ረገድም ቁልፍ ሚና የተጫወቱት ጃሬድ ኩሽነር መሆናቸውን የሩሲያ ሚዲያዎች ዘግበዋል።
ሁለቱ አሜሪካውያን በአውሮፕላን ማረፊያ የተቀበሏቸው የሩሲያ የኢንቨስትመንት ፈንድ ኃላፊ ኪሪል ዲሚትሪየቭ ናቸው፣ ነገር ግን ከሩሲያ በኩል በስብሰባው ላይ የሚገኙት ፑቲን እና አስተርጓሚ ብቻ ናቸው።
የTASS ዘገባ መሰረት የሩሲያ መንግስት ቃል አቀባይ ፔስኮቭ በሰጡት መግለጫ ላይ ሦስቱ ብቻ ንግግር እንደሚያደርጉ አረጋግጠዋል።
ዊትኮፍ በጄኔቫ እና ፍሎሪዳ በተደረጉት የቅርብ ጊዜ ድርድሮች ዙሪያ የተዘጋጀውን የአሜሪካ-ዩክሬን የሥራ ማዕቀፍ የቅርብ ጊዜ እትም ለፑቲን ያቀርባሉ።
ፔስኮቭ በተጨማሪም ሞስኮ ለሰላም ንግግሮች ዝግጁ መሆኗን ገልጸዋል፣ ነገር ግን ግቦቿን ማሳካት እንዳለባት አሳስበዋል።
ዲሚትሪየቭ ዛሬን ለዓለም አስፈላጊ ቀን ነው ሲሉ ጠርተውታል።
“ለዓለም አስፈላጊ ቀን ነው፡ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕን የጋዛ የሰላም ስምምነት ያዘጋጀው ቡድን የትራምፕን የሰላም አጀንዳ በዩክሬን ለማስቀጠል ወደ ሞስኮ ይመጣሉ” ብለዋል።
6 months ago
ሩሲያ እና ቻይና 200 ቢሊዮን ዶላር የሚገመቱ ከ80 በላይ የጋራ ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን ለመጀመር በዝግጅት ላይ ናቸው ተባለ
በአመት ውስጥ የቻይና የንግድ ሰዎች በሩሲያ ውስጥ 13,000 ኩባንያዎችን በይፋ አስመዝግበዋል።
የሩሲያ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ከዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጋር ያላቸው ግንኙነት ልዩ መልዕክተኛ እና የሩሲያ-ቻይና ወዳጅነት፣ ሰላም እና ልማት ኮሚቴ ተባባሪ ሊቀመንበር የሆኑት ቦሪስ ቲቶቭ ለ TASS እንደተናገሩት፣ ሩሲያ እና ቻይና በጠቅላላ ዋጋቸው 200 ቢሊዮን ዶላር የሚገመቱ ከ80 በላይ የጋራ ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን ለመጀመር በዝግጅት ላይ ናቸው።
ቲቶቭ እንዳብራሩት፣ የሩሲያ መንግሥት የቻይና አጋሮች ከ"ቀጥታ የማስመጣት አቅርቦት" ሞዴል ወደ ሩሲያ ፌዴሬሽን ግዛት ውስጥ ምርትን ወደማስገባት እንዲቀይሩ ለማበረታታት የግብር ማበረታቻዎችን እያስተዋወቀ እንደሆነ ተገልጿል።
ቲቶቭ ለዚህ ትብብር ስኬታማ ምሳሌ እንደ የ Haval እና Moskvich ያሉትን የመኪና ኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶችን እንዲሁም ለቮልጋ መኪና ያለውን እቅድ ጠቅሰዋል።
እሳቸው እንዳሉት፣ በ2025 የቻይና የንግድ ሰዎች በሩሲያ ውስጥ 13,000 ኩባንያዎችን በይፋ አስመዝግበዋል፣ ይህም በሩሲያ ገበያ ውስጥ ከሚንቀሳቀሱት "የምዕራባውያን" ኩባንያዎች ቁጥር "በከፍተኛ ሁኔታ ይበልጣል።"
በአመት ውስጥ የቻይና የንግድ ሰዎች በሩሲያ ውስጥ 13,000 ኩባንያዎችን በይፋ አስመዝግበዋል።
የሩሲያ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ከዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጋር ያላቸው ግንኙነት ልዩ መልዕክተኛ እና የሩሲያ-ቻይና ወዳጅነት፣ ሰላም እና ልማት ኮሚቴ ተባባሪ ሊቀመንበር የሆኑት ቦሪስ ቲቶቭ ለ TASS እንደተናገሩት፣ ሩሲያ እና ቻይና በጠቅላላ ዋጋቸው 200 ቢሊዮን ዶላር የሚገመቱ ከ80 በላይ የጋራ ኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶችን ለመጀመር በዝግጅት ላይ ናቸው።
ቲቶቭ እንዳብራሩት፣ የሩሲያ መንግሥት የቻይና አጋሮች ከ"ቀጥታ የማስመጣት አቅርቦት" ሞዴል ወደ ሩሲያ ፌዴሬሽን ግዛት ውስጥ ምርትን ወደማስገባት እንዲቀይሩ ለማበረታታት የግብር ማበረታቻዎችን እያስተዋወቀ እንደሆነ ተገልጿል።
ቲቶቭ ለዚህ ትብብር ስኬታማ ምሳሌ እንደ የ Haval እና Moskvich ያሉትን የመኪና ኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶችን እንዲሁም ለቮልጋ መኪና ያለውን እቅድ ጠቅሰዋል።
እሳቸው እንዳሉት፣ በ2025 የቻይና የንግድ ሰዎች በሩሲያ ውስጥ 13,000 ኩባንያዎችን በይፋ አስመዝግበዋል፣ ይህም በሩሲያ ገበያ ውስጥ ከሚንቀሳቀሱት "የምዕራባውያን" ኩባንያዎች ቁጥር "በከፍተኛ ሁኔታ ይበልጣል።"
8 months ago
ኢትዮጵያ እና ሩሲያ የኑክሌያር ማብላያ ለመገንባት ተስማምተዋል።
የሩሲያው የዜና ወኪል TASS ን ጠቅሶ አናዶሉ ኤጄንሲ እንደዘገበው ሁለቱ ሀገራት በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን የኑክሌያር ጣቢያ ለመገንባት ተስማምተዋል።
ኑክሌየር የመገንባት ስምምነቱ በሩሲያ የኑክሌር ተቋም ሮሳቶም ዋና ሀላፊ አሌክሲ ሊኻቼቭ እና በኢትዮጵያው ውጭጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ መካከል ተፈርሟል።
በዚህም ኢትዮጵያን የኑክሌያር ጣቢያ ባለቤት የሚያደርጋትን ውል በፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን እና በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ፈቃድ መፈፀሙ ታውቋል።
ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በ 2017 ኑክሌየርን ለሰላማዊ ጥቅም የመገንባት ስምምነትን መፈፀማቸው ለአሁኑ ስምምነት መሰረት መጣሉን አናዶሉ ዘግቧል።
ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድ በህዳሴው ግድብ ምረቃ ላይ ኢትዮጵያ የኑክሌያር ጣቢያ እንደምትገነባ መናገራቸው ይታወቃል።
seledadotio
seledadotio
የሩሲያው የዜና ወኪል TASS ን ጠቅሶ አናዶሉ ኤጄንሲ እንደዘገበው ሁለቱ ሀገራት በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን የኑክሌያር ጣቢያ ለመገንባት ተስማምተዋል።
ኑክሌየር የመገንባት ስምምነቱ በሩሲያ የኑክሌር ተቋም ሮሳቶም ዋና ሀላፊ አሌክሲ ሊኻቼቭ እና በኢትዮጵያው ውጭጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ መካከል ተፈርሟል።
በዚህም ኢትዮጵያን የኑክሌያር ጣቢያ ባለቤት የሚያደርጋትን ውል በፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን እና በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ፈቃድ መፈፀሙ ታውቋል።
ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በ 2017 ኑክሌየርን ለሰላማዊ ጥቅም የመገንባት ስምምነትን መፈፀማቸው ለአሁኑ ስምምነት መሰረት መጣሉን አናዶሉ ዘግቧል።
ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድ በህዳሴው ግድብ ምረቃ ላይ ኢትዮጵያ የኑክሌያር ጣቢያ እንደምትገነባ መናገራቸው ይታወቃል።
seledadotio
seledadotio
Sponsored by
Surafel
9 months ago
ሩሲያ እና ቻይና በአለም ላይ ትልቁን የንግድ ልዉዉጥ ስምምነት ፈፀሙ !
የሩስያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የሳይቤሪያ-2 ፓወር መስመር ዝርጋታ ሁለቱ ሀገራት ስምምነት ከተፈራረሙ በኋላ በሩሲያ እና በቻይና መካከል ያለውን ግንኙነት "ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ከፍተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ" ገልፀዋል ሲል CNN ዘግቧል።
ይህም የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እየተጣለ የሚገኘው የታሪፍ እና ከጊዜ ወደ ጊዜ እያገለሉ የሚሄዱ ፖሊሲዎች በመቃረን የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ እና የአለም አቀፍ ንግድ አካሄድ ለውጥ የሚያመጣ የአለምን ስርዓት የሚቀይር ተብሏል ።
ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት በዓመት 50 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የተፈጥሮ ጋዝን ከምእራብ ሩሲያ ወደ ሰሜናዊ ቻይና በሞንጎሊያ በኩል የሚያጓጉዝ ሲሆን የዩክሬን ጦርነት ከጀመረ በኋላ ሩሲያ ወደ አውሮፓ ከምትልከው የጠፋ ጋዝ ግማሹን ያካክላል ተብሎ ይጠበቃል።
ማክሰኞ ከሰአት በኋላ ፣የሩሲያ የመንግስት ኢነርጂ ኩባንያ ጋዝፕሮም ሞስኮ ለዓመታት ሳትቀበለዉ የቆየችዉ ከአዉሮጳ ጋር ያላትን የንግድ ልዉዉጥ በመግፋት አዲስ የንግድ ልዉዉጥ ያለውን ግዙፍ የሳይቤሪያ-2 ጋዝ ቧንቧ መስመር ለመገንባት ሕጋዊ ስምምነት መፈረሙን አስታውቋል።
ሲ ኤን ኤን እንደዘገበው ይህ ስምምነቱ ፑቲን አውሮፓን በዋና ጋዝ ገዥነት ለመተካት ወደ ቻይና በማዞር ትልቅ ድል ነው። በተጨማሪም የዩኤስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዩክሬን ያለውን ጦርነት ለማስቆም ባደረጉት ጥረት የሩሲያን የሃይል አቅርቦት እንዲቀንሱ ሀገራትን ግፊት በማድረግ ላይ የሚገኙትን የጋራ ተቃውሞ ማሳያ ነው። ሲል ዘግቧል ።
የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማክሰኞ በተደረገው መደበኛ የዜና ኮንፈረንስ ስለ ስምምነቱ ሲጠየቁ ቻይና እና ሩሲያ “ኃይልን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ያለማቋረጥ ተግባራዊ ትብብር አድርገዋል”ብለዋል ።
የጋዝፕሮም ዋና ሥራ አስፈፃሚ አሌክሲ ሚለር እንደተናገሩት ስምምነቱ የ 30 ዓመት የአቅርቦት ስምምነትን ያካተተ ሲሆን የአቅርቦት ዋጋ አውሮፓ ከሚከፍለው ያነሰ ይሆናል ። "በአለም ላይ ትልቁ፣ በጣም ሰፊ እና ከፍተኛ ካፒታል-ተኮር የጋዝ ፕሮጀክት ይሆናል" ሲል ሚለር በ TASS የዜና ወኪል በኩል ተናግሯል ።
ፑቲን ቻይናን በጎበኙበት ወቅት ሁለቱ መሪዎች ከሞንጎሊያው ፕሬዝዳንት ኡክና ክሩልሱክ ጋር በመገናኘት እና በቻይና መሪ ይፋዊ መኖሪያ ቤት ሻይ ሲጠጡ ለሰዓታት አብረው አሳልፈዋል።
የኔታ ቲዩብ ዘጋቢ ፦ ታዴ የማመይ ልጅ
የሩስያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን የሳይቤሪያ-2 ፓወር መስመር ዝርጋታ ሁለቱ ሀገራት ስምምነት ከተፈራረሙ በኋላ በሩሲያ እና በቻይና መካከል ያለውን ግንኙነት "ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ከፍተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ" ገልፀዋል ሲል CNN ዘግቧል።
ይህም የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እየተጣለ የሚገኘው የታሪፍ እና ከጊዜ ወደ ጊዜ እያገለሉ የሚሄዱ ፖሊሲዎች በመቃረን የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ እና የአለም አቀፍ ንግድ አካሄድ ለውጥ የሚያመጣ የአለምን ስርዓት የሚቀይር ተብሏል ።
ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት በዓመት 50 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር የተፈጥሮ ጋዝን ከምእራብ ሩሲያ ወደ ሰሜናዊ ቻይና በሞንጎሊያ በኩል የሚያጓጉዝ ሲሆን የዩክሬን ጦርነት ከጀመረ በኋላ ሩሲያ ወደ አውሮፓ ከምትልከው የጠፋ ጋዝ ግማሹን ያካክላል ተብሎ ይጠበቃል።
ማክሰኞ ከሰአት በኋላ ፣የሩሲያ የመንግስት ኢነርጂ ኩባንያ ጋዝፕሮም ሞስኮ ለዓመታት ሳትቀበለዉ የቆየችዉ ከአዉሮጳ ጋር ያላትን የንግድ ልዉዉጥ በመግፋት አዲስ የንግድ ልዉዉጥ ያለውን ግዙፍ የሳይቤሪያ-2 ጋዝ ቧንቧ መስመር ለመገንባት ሕጋዊ ስምምነት መፈረሙን አስታውቋል።
ሲ ኤን ኤን እንደዘገበው ይህ ስምምነቱ ፑቲን አውሮፓን በዋና ጋዝ ገዥነት ለመተካት ወደ ቻይና በማዞር ትልቅ ድል ነው። በተጨማሪም የዩኤስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዩክሬን ያለውን ጦርነት ለማስቆም ባደረጉት ጥረት የሩሲያን የሃይል አቅርቦት እንዲቀንሱ ሀገራትን ግፊት በማድረግ ላይ የሚገኙትን የጋራ ተቃውሞ ማሳያ ነው። ሲል ዘግቧል ።
የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማክሰኞ በተደረገው መደበኛ የዜና ኮንፈረንስ ስለ ስምምነቱ ሲጠየቁ ቻይና እና ሩሲያ “ኃይልን ጨምሮ በተለያዩ መስኮች ያለማቋረጥ ተግባራዊ ትብብር አድርገዋል”ብለዋል ።
የጋዝፕሮም ዋና ሥራ አስፈፃሚ አሌክሲ ሚለር እንደተናገሩት ስምምነቱ የ 30 ዓመት የአቅርቦት ስምምነትን ያካተተ ሲሆን የአቅርቦት ዋጋ አውሮፓ ከሚከፍለው ያነሰ ይሆናል ። "በአለም ላይ ትልቁ፣ በጣም ሰፊ እና ከፍተኛ ካፒታል-ተኮር የጋዝ ፕሮጀክት ይሆናል" ሲል ሚለር በ TASS የዜና ወኪል በኩል ተናግሯል ።
ፑቲን ቻይናን በጎበኙበት ወቅት ሁለቱ መሪዎች ከሞንጎሊያው ፕሬዝዳንት ኡክና ክሩልሱክ ጋር በመገናኘት እና በቻይና መሪ ይፋዊ መኖሪያ ቤት ሻይ ሲጠጡ ለሰዓታት አብረው አሳልፈዋል።
የኔታ ቲዩብ ዘጋቢ ፦ ታዴ የማመይ ልጅ