1 month ago
የነገዋ ታዳጊ ተማሪዎች በቴክኖሎጂ የታገዘ የፈጠራ ስራዎቻቸውን ለእይታ አቀረቡ
#ethiopia | ነገን በቴክኖሎጂ ለመቀየርና የሀገራቸውን ችግሮች በፈጠራ የሳይንስ ጥበብ ለመፍታት ቆርጠው የተነሱ ህጻናትና ታዳጊዎች፣ ማህበረሰባዊ ፋይዳ ያላቸውንና አስደናቂ የሆኑ የሮቦቲክስ ፈጠራ ስራዎቻቸውን ለዕይታ አብቅተዋል።
እነዚህ ታዳጊዎች በዕድሜ ለጋ ቢሆኑም፣ ያቀረቧቸው የፈጠራ ውጤቶች ግን የነገዋን ኢትዮጵያ ብሩህ ተስፋ ፍንትው አድርገው የሚያሳዩ ሆነዋል።
ከተሳታፊዎቹ መካከል የ15 ዓመቷ ታዳጊ ሮዳ ፈታ አንዷ ስትሆን፣ አካል ጉዳተኞችንና የአእምሮ ህመም ያለባቸውን ሰዎች ያለምንም ሰው እገዛ በራሱ ጊዜ መመገብ የሚችል ማሽን ሰርታ ለእይታ አቅርባለች። «ኢትስ ኤ ፊደር» (It's a feeder) የሚል ስያሜ የሰጠችው ይሄው ማሽን፣ የብርሃንና የከለር ሴንሰሮችን በመጠቀም በአንድ ጊዜ እስከ አራት ሰዎችን ማብላት የሚያስችል አቅም አለው ብላለች።
ሆስፒታል ውስጥ የሚገኙ የህክምና ባለሙያ ዘመዷን ለመጠየቅ በምትሄድበት ወቅት የተቸገሩ ሰዎችን አይታ ይሄንን የፈጠራ ስራ ለመስራት መነሳሳቷን የገለጸችው ታዳጊ ሮዳ፣ ማሽኑ ተንቀሳቃሽ እንዲሆን ከስሩ ጎማዎች የተገጠሙለት መሆኑንና ወደፊትም በትምህርቷ ገፍታ በትውልድ ሀገሯ ትልልቅ የቴክኖሎጂ ስራዎችን የመስራት ትልቅ ህልም እንዳላት በልበ ሙሉነት ተናግራለች።
በተመሳሳይ መልኩ ናስናፍ ይስሐቅ እና ኢቫን ዘረይ የተባሉ ታዳጊ ተማሪዎች የሀገራቸውን የቡና ምርት ሂደት ለማቃለል የሚያስችል «ኮፊ ቢን ኮሌክተር» የተሰኘ ዘመናዊ የቡና ፍሬ መልቀሚያ ማሽን ይዘው ቀርበዋል።
የኢትዮጵያ ዋነኛ ችግር ቡና በእጅ መለቀሙ እንደሆነ በመረዳት ችግሩን ለመፍታት መነሳሳታቸውን የገለጹት ታዳጊዎቹ፣ የሰሩት ማሽን በአራት ሞተሮችና በተለያዩ ፕሬዠር ሴንሰሮች የታገዘ ሲሆን፣ ከሰው ጉልበት በተሻለ በ10 እጥፍ ፍጥነት ቡናን ሰብስቦ በተዘጋጀለት ቅርጫት ውስጥ ማስገባት እንደሚችል በተግባር አስረድተዋል።
የስቴም ፎር ኪድስ ፍራንቻይዝ ባለቤትና ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ኤርሚያስ ሰለሞን በበኩላቸው፣ የትምህርት ፕሮግራሙ ዋና ዓላማ ህጻናት እየተጫወቱና እየተደሰቱ ክሬቲቪቲን፣ ኮሙኒኬሽንንና ክሪቲካል ቲንኪንግን እንዲያሳድጉ ማድረግ እንደሆነ ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት በአለም ላይ መደበኛ የሆኑ ስራዎች በሙሉ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስና በማሽን ለርኒንግ እየተተኩ በመሆኑ፣ ልጆችን ከወዲሁ ለዚህ አዲስ ዓለም ማዘጋጀት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ባለፉት ሶስት ዓመታት ተኩል ጊዜ ውስጥ ወደ 5,000 የሚጠጉ ተማሪዎችን ማስተማር መቻላቸውን የገለጹት አቶ ኤርሚያስ፣ ወደፊትም ከኢትዮ ቴሌኮምና ከሳፋሪኮም ጋር በመተባበር ትምህርቱን በኦንላይን በማስፋፋት አቅም ለሌላቸውና በየክፍለ ሀገሩ ለሚገኙ በርካታ የመንግስት ትምህርት ቤት ልጆች ጭምር በስፋት ለማድረስ ከፍተኛ ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ጠቁመው፣ ቴክኖሎጂውን ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት ያለውን የእቃ አቅርቦትና የፖሊሲ ፈተናዎች መንግስት ተረድቶ ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
በጌትነት ተመስገን
📷ከበደ መክብብ
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#stemethiopia #stemforkids # #technologyethiopia #ethiopiangenius #digitaltransformationethiopia
#ethiopia | ነገን በቴክኖሎጂ ለመቀየርና የሀገራቸውን ችግሮች በፈጠራ የሳይንስ ጥበብ ለመፍታት ቆርጠው የተነሱ ህጻናትና ታዳጊዎች፣ ማህበረሰባዊ ፋይዳ ያላቸውንና አስደናቂ የሆኑ የሮቦቲክስ ፈጠራ ስራዎቻቸውን ለዕይታ አብቅተዋል።
እነዚህ ታዳጊዎች በዕድሜ ለጋ ቢሆኑም፣ ያቀረቧቸው የፈጠራ ውጤቶች ግን የነገዋን ኢትዮጵያ ብሩህ ተስፋ ፍንትው አድርገው የሚያሳዩ ሆነዋል።
ከተሳታፊዎቹ መካከል የ15 ዓመቷ ታዳጊ ሮዳ ፈታ አንዷ ስትሆን፣ አካል ጉዳተኞችንና የአእምሮ ህመም ያለባቸውን ሰዎች ያለምንም ሰው እገዛ በራሱ ጊዜ መመገብ የሚችል ማሽን ሰርታ ለእይታ አቅርባለች። «ኢትስ ኤ ፊደር» (It's a feeder) የሚል ስያሜ የሰጠችው ይሄው ማሽን፣ የብርሃንና የከለር ሴንሰሮችን በመጠቀም በአንድ ጊዜ እስከ አራት ሰዎችን ማብላት የሚያስችል አቅም አለው ብላለች።
ሆስፒታል ውስጥ የሚገኙ የህክምና ባለሙያ ዘመዷን ለመጠየቅ በምትሄድበት ወቅት የተቸገሩ ሰዎችን አይታ ይሄንን የፈጠራ ስራ ለመስራት መነሳሳቷን የገለጸችው ታዳጊ ሮዳ፣ ማሽኑ ተንቀሳቃሽ እንዲሆን ከስሩ ጎማዎች የተገጠሙለት መሆኑንና ወደፊትም በትምህርቷ ገፍታ በትውልድ ሀገሯ ትልልቅ የቴክኖሎጂ ስራዎችን የመስራት ትልቅ ህልም እንዳላት በልበ ሙሉነት ተናግራለች።
በተመሳሳይ መልኩ ናስናፍ ይስሐቅ እና ኢቫን ዘረይ የተባሉ ታዳጊ ተማሪዎች የሀገራቸውን የቡና ምርት ሂደት ለማቃለል የሚያስችል «ኮፊ ቢን ኮሌክተር» የተሰኘ ዘመናዊ የቡና ፍሬ መልቀሚያ ማሽን ይዘው ቀርበዋል።
የኢትዮጵያ ዋነኛ ችግር ቡና በእጅ መለቀሙ እንደሆነ በመረዳት ችግሩን ለመፍታት መነሳሳታቸውን የገለጹት ታዳጊዎቹ፣ የሰሩት ማሽን በአራት ሞተሮችና በተለያዩ ፕሬዠር ሴንሰሮች የታገዘ ሲሆን፣ ከሰው ጉልበት በተሻለ በ10 እጥፍ ፍጥነት ቡናን ሰብስቦ በተዘጋጀለት ቅርጫት ውስጥ ማስገባት እንደሚችል በተግባር አስረድተዋል።
የስቴም ፎር ኪድስ ፍራንቻይዝ ባለቤትና ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ኤርሚያስ ሰለሞን በበኩላቸው፣ የትምህርት ፕሮግራሙ ዋና ዓላማ ህጻናት እየተጫወቱና እየተደሰቱ ክሬቲቪቲን፣ ኮሙኒኬሽንንና ክሪቲካል ቲንኪንግን እንዲያሳድጉ ማድረግ እንደሆነ ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት በአለም ላይ መደበኛ የሆኑ ስራዎች በሙሉ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስና በማሽን ለርኒንግ እየተተኩ በመሆኑ፣ ልጆችን ከወዲሁ ለዚህ አዲስ ዓለም ማዘጋጀት እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ባለፉት ሶስት ዓመታት ተኩል ጊዜ ውስጥ ወደ 5,000 የሚጠጉ ተማሪዎችን ማስተማር መቻላቸውን የገለጹት አቶ ኤርሚያስ፣ ወደፊትም ከኢትዮ ቴሌኮምና ከሳፋሪኮም ጋር በመተባበር ትምህርቱን በኦንላይን በማስፋፋት አቅም ለሌላቸውና በየክፍለ ሀገሩ ለሚገኙ በርካታ የመንግስት ትምህርት ቤት ልጆች ጭምር በስፋት ለማድረስ ከፍተኛ ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ጠቁመው፣ ቴክኖሎጂውን ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት ያለውን የእቃ አቅርቦትና የፖሊሲ ፈተናዎች መንግስት ተረድቶ ድጋፍ እንዲያደርግ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
በጌትነት ተመስገን
📷ከበደ መክብብ
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#stemethiopia #stemforkids # #technologyethiopia #ethiopiangenius #digitaltransformationethiopia
4 months ago
አዲስ አበባ የሳይንስና የፈጠራ ማዕከል ለመሆን ተነሳች
#ethiopia | "እውቀት ለችግሮች መፍትሄ ማፍለቅ ነው!" በሚል መሪ ቃል፣ 11ኛው ከተማ አቀፍ የሳይንስ ፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ በአዲስ አበባ በይፋ ተጀምሯል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዛሬው ዕለት አውደ ርዕዩን ሲያስጀምሩ፣ ከተማዋን የፈጠራ ማዕከል ለማድረግ የተያዘው ግብ ውጤት እያሳየ መሆኑን ገልጸዋል።
የውስጥ ተሰጥኦዋቸውን በተግባር ያሳዩ ተማሪዎችና መምህራን።
ተማሪዎች በንድፈ ሀሳብ የተማሩትን እውቀት ወደ ተግባራዊ መፍትሄ እንዲቀይሩ ማበረታታት።
ይህ አስደናቂ የፈጠራ ስራዎች የሚቀርቡበት አውደ ርዕይ ለሁለት ተከታታይ ቀናት ይቆያል።
የከንቲባዋ ጥሪ፦ የጀመሩት የፈጠራ ስራዎች አድገው ለሀገርና ለዓለም የሚተርፉ እንዲሆኑ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ድጋፋቸውን እንዲያጠናክሩ ጥሪ አቅርበዋል።
የአዲስ አበባ ተማሪዎች እንዲህ ባሉ መድረኮች ሲወጡ ማየት ለሀገራችን የቴክኖሎጂ ሽግግር ትልቅ ፋይዳ አለው። ትናንት በንድፈ ሀሳብ የነበረው ዛሬ ወደ ፈጠራ ተቀይሯል። እነዚህ ተማሪዎች ነገ ዓለምን የሚቀይሩ የሳይንስ ባለሙያዎች እንደሚሆኑ አልጠራጠርም!
የነገዋ ኢትዮጵያ በዛሬው ፈጠራ ትገነባለች!
#getu #addisababa #scienceandinnovation #innovationexpo #stemethiopia #adanechabiebie #technologyethiopia #futureleaders #አዲስአበባ #ሳይንስናፈጠራ #የፈጠራስራ #ትምህርት #ጌጡተመስገን #getutemesgen
#ethiopia | "እውቀት ለችግሮች መፍትሄ ማፍለቅ ነው!" በሚል መሪ ቃል፣ 11ኛው ከተማ አቀፍ የሳይንስ ፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ በአዲስ አበባ በይፋ ተጀምሯል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዛሬው ዕለት አውደ ርዕዩን ሲያስጀምሩ፣ ከተማዋን የፈጠራ ማዕከል ለማድረግ የተያዘው ግብ ውጤት እያሳየ መሆኑን ገልጸዋል።
የውስጥ ተሰጥኦዋቸውን በተግባር ያሳዩ ተማሪዎችና መምህራን።
ተማሪዎች በንድፈ ሀሳብ የተማሩትን እውቀት ወደ ተግባራዊ መፍትሄ እንዲቀይሩ ማበረታታት።
ይህ አስደናቂ የፈጠራ ስራዎች የሚቀርቡበት አውደ ርዕይ ለሁለት ተከታታይ ቀናት ይቆያል።
የከንቲባዋ ጥሪ፦ የጀመሩት የፈጠራ ስራዎች አድገው ለሀገርና ለዓለም የሚተርፉ እንዲሆኑ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ድጋፋቸውን እንዲያጠናክሩ ጥሪ አቅርበዋል።
የአዲስ አበባ ተማሪዎች እንዲህ ባሉ መድረኮች ሲወጡ ማየት ለሀገራችን የቴክኖሎጂ ሽግግር ትልቅ ፋይዳ አለው። ትናንት በንድፈ ሀሳብ የነበረው ዛሬ ወደ ፈጠራ ተቀይሯል። እነዚህ ተማሪዎች ነገ ዓለምን የሚቀይሩ የሳይንስ ባለሙያዎች እንደሚሆኑ አልጠራጠርም!
የነገዋ ኢትዮጵያ በዛሬው ፈጠራ ትገነባለች!
#getu #addisababa #scienceandinnovation #innovationexpo #stemethiopia #adanechabiebie #technologyethiopia #futureleaders #አዲስአበባ #ሳይንስናፈጠራ #የፈጠራስራ #ትምህርት #ጌጡተመስገን #getutemesgen
5 months ago
ታዳጊዎችን የሚያሳትፈው "ሮቦቲክስ ለበጎ ዓላማ" ይፋ ተደረገ
📌 አሸናፊዎች ስዊዘርላንድ በሚካሄደው ዓለም አቀፍ ውድድር ይሳተፋሉ!
#ethiopia | በዓለም አቀፉ የቴሌኮሙኒኬሽን ህብረት አዘጋጅነት የሚካሄደውና ዕድሜያቸው ከ10 እስከ 18 ዓመት የሆኑ ታዳጊዎችን የሚያሳትፈው "ሮቦቲክስ ለበጎ ዓላማ" የሮቦቲክስ ሻምፒዮና የ2026 የውድድር ይፋ ተደርጓል።
ይህ ታላቅ ሀገራዊ ንቅናቄ በኤግዚት ሲስተምስ እና ልዩ ዝግጅቶች አስተባባሪነት የሚመራ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ወጣቶች በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) እና በሮቦቲክስ ዘርፍ ያላቸውን ክህሎት ተጠቅመው ዓለም አቀፍ ችግሮችን እንዲፈቱ ዕድል ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ገልጿል።
የዘንድሮው ውድድር ዋና ትኩረቱን በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ውስጥ ወሳኝ በሆነው "የምግብ ዋስትና እና ዘመናዊ ግብርና" ላይ ያደረገ ሲሆን ተማሪዎች ክፍት ምንጭ (Open-source) የሆኑ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ለግብርናው ዘርፍ መፍትሄ የሚሰጡ ሮቦቶችን ዲዛይን የማድረግ፣ የመገንባት እና ፕሮግራም የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል።
ይህም ወጣቶች የንድፈ-ሀሳብ እውቀታቸውን ወደ ተግባራዊ ሀገር በቀል የፈጠራ ስራዎች እንዲቀይሩ ያስችላቸዋል።
በማስጀመሪያ መርሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ሰለሞን ሶካ ባደረጉት ንግግር፣ ይህ ውድድር በኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ውስጥ ያለውን ጉልህ ሚና ገልጸዋል። መንግስት ወጣቶች በቴክኖሎጂ ታግዘው ሀገራዊ ችግሮችን እንዲፈቱ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ያረጋገጡት ሚኒስትር ዴኤታው፣ እንዲህ ያሉ መድረኮች ለሀገር በቀል የፈጠራ ስራዎች መጎልበት ያላቸውን ፋይዳ አጽንኦት ሰጥተውበታል።
የኤግዚት ሲስተምስ ዋና ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ሔለን አቢ በበኩላቸው፣ ይህ ፕሮግራም ኢትዮጵያን ከቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት ወደ መፍትሔ ፈጣሪነት የምትሸጋገርበት ድልድይ መሆኑን ገልጸው፤ ውድድሩ በክልል ማጣሪያዎች፣ በሜንቶርሺፕ እና በቴክኒክ ስልጠናዎች ታጅቦ ዓመቱን ሙሉ የሚቀጥል የፈጠራ ጉዞ እንደሆነ አስረድተዋል።
ሀገራዊ የማጣሪያ ውድድሩ መጋቢት 19 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ በሚገኘው የኢትዮጵያ ሳይንስ ሙዚየም በድምቀት ይካሄዳል።
በጁኒየር እና በሲኒየር ምድቦች አሸናፊ የሚሆኑ ሁለት ምርጥ ቡድኖች በስዊዘርላንድ ጄኔቫ በሚካሄደው "AI for Good Global Summit 2026" ላይ ኢትዮጵያን ወክለው የመሳተፍ ዕድል ያገኛሉ።
ለአሸናፊዎቹ ሙሉ ወጪያቸው የተሸፈነ የጉዞ ትኬት፣ የመግቢያ ፓስ እና ምግብ የሚቀርብላቸው ሲሆን፣ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) እና ከዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ መሪዎች ጋር የመገናኘት ሰፊ ዕድል ይኖራቸዋል ተብላል።
#roboticsforgood #aiforgood #ethiopiatech2026 #youthinnovation #stemethiopia #foodsecurityai #exitsystems #itu #roboticschallenge #futureleaders #digitalethiopialove
📌 አሸናፊዎች ስዊዘርላንድ በሚካሄደው ዓለም አቀፍ ውድድር ይሳተፋሉ!
#ethiopia | በዓለም አቀፉ የቴሌኮሙኒኬሽን ህብረት አዘጋጅነት የሚካሄደውና ዕድሜያቸው ከ10 እስከ 18 ዓመት የሆኑ ታዳጊዎችን የሚያሳትፈው "ሮቦቲክስ ለበጎ ዓላማ" የሮቦቲክስ ሻምፒዮና የ2026 የውድድር ይፋ ተደርጓል።
ይህ ታላቅ ሀገራዊ ንቅናቄ በኤግዚት ሲስተምስ እና ልዩ ዝግጅቶች አስተባባሪነት የሚመራ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ወጣቶች በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) እና በሮቦቲክስ ዘርፍ ያላቸውን ክህሎት ተጠቅመው ዓለም አቀፍ ችግሮችን እንዲፈቱ ዕድል ለመፍጠር ያለመ መሆኑን ገልጿል።
የዘንድሮው ውድድር ዋና ትኩረቱን በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ውስጥ ወሳኝ በሆነው "የምግብ ዋስትና እና ዘመናዊ ግብርና" ላይ ያደረገ ሲሆን ተማሪዎች ክፍት ምንጭ (Open-source) የሆኑ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ለግብርናው ዘርፍ መፍትሄ የሚሰጡ ሮቦቶችን ዲዛይን የማድረግ፣ የመገንባት እና ፕሮግራም የማድረግ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል።
ይህም ወጣቶች የንድፈ-ሀሳብ እውቀታቸውን ወደ ተግባራዊ ሀገር በቀል የፈጠራ ስራዎች እንዲቀይሩ ያስችላቸዋል።
በማስጀመሪያ መርሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ሰለሞን ሶካ ባደረጉት ንግግር፣ ይህ ውድድር በኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ውስጥ ያለውን ጉልህ ሚና ገልጸዋል። መንግስት ወጣቶች በቴክኖሎጂ ታግዘው ሀገራዊ ችግሮችን እንዲፈቱ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ያረጋገጡት ሚኒስትር ዴኤታው፣ እንዲህ ያሉ መድረኮች ለሀገር በቀል የፈጠራ ስራዎች መጎልበት ያላቸውን ፋይዳ አጽንኦት ሰጥተውበታል።
የኤግዚት ሲስተምስ ዋና ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ ሔለን አቢ በበኩላቸው፣ ይህ ፕሮግራም ኢትዮጵያን ከቴክኖሎጂ ተጠቃሚነት ወደ መፍትሔ ፈጣሪነት የምትሸጋገርበት ድልድይ መሆኑን ገልጸው፤ ውድድሩ በክልል ማጣሪያዎች፣ በሜንቶርሺፕ እና በቴክኒክ ስልጠናዎች ታጅቦ ዓመቱን ሙሉ የሚቀጥል የፈጠራ ጉዞ እንደሆነ አስረድተዋል።
ሀገራዊ የማጣሪያ ውድድሩ መጋቢት 19 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ በሚገኘው የኢትዮጵያ ሳይንስ ሙዚየም በድምቀት ይካሄዳል።
በጁኒየር እና በሲኒየር ምድቦች አሸናፊ የሚሆኑ ሁለት ምርጥ ቡድኖች በስዊዘርላንድ ጄኔቫ በሚካሄደው "AI for Good Global Summit 2026" ላይ ኢትዮጵያን ወክለው የመሳተፍ ዕድል ያገኛሉ።
ለአሸናፊዎቹ ሙሉ ወጪያቸው የተሸፈነ የጉዞ ትኬት፣ የመግቢያ ፓስ እና ምግብ የሚቀርብላቸው ሲሆን፣ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት (UN) እና ከዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ መሪዎች ጋር የመገናኘት ሰፊ ዕድል ይኖራቸዋል ተብላል።
#roboticsforgood #aiforgood #ethiopiatech2026 #youthinnovation #stemethiopia #foodsecurityai #exitsystems #itu #roboticschallenge #futureleaders #digitalethiopialove
Comments