1 month ago
የታይዋን ፕሬዝዳንት የአየር ክልል ተዘግቶባቸው የአፍሪካ ጉዛቸውን ተሰረዘ
#ethiopia | የታይዋኑ ፕሬዝዳንት ላይ ቺንግ ቴ ወደ አፍሪካዊቷ ሀገር ኢስዋቲኒ ለማቅናት አቅደው የነበረ ቢሆንም፣ የአየር ክልል ፍቃድ በማጣታቸው ጉዟቸውን ለመሰረዝ ተገደዋል።
ሲሸልስ፣ ሞሪሸስ እና ማዳጋስካር ለፕሬዝዳንቱ በረራ የአየር ክልላቸውን ክፍት ለማድረግ ፍቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል።
የታይዋን ፕሬዝዳንታዊ ፅህፈት ቤት ሃላፊ ፓን ሜንጋን እንደገለጹት፣ ሀገራቱ ቀደም ሲል ፍቃደኝነታቸውን አሳውቀው የነበረ ቢሆንም ከጥቂት ቀናት በኋላ ግን በድንገት ሃሳባቸውን ቀይረዋል።
ታይዋን ለዚህ የአቋም ለውጥ ዋነኛው ምክንያት ከቤጂንግ (ቻይና) የሚመጣ ዲፕሎማሲያዊ ጫና መሆኑን በግልጽ ተናግራለች።
"ቻይና ታይዋንን በዓለም አቀፍ መድረክ በዲፕሎማሲ ለማግለል የምታደርገው ጥረት አካል ነው" — የታይዋን ባለስልጣናት
ፕሬዝዳንት ላይ ቺንግ ቴ ወደ ስፍራው ማቅናት የፈለጉት፣ የታይዋን የቅርብ ወዳጅ የሆኑት የኢስዋቲኒው ንጉሥ ሚስዋቲ 40ኛ ዓመት የንግሥና በዓል ላይ ለመታደም ነበር።
ኢስዋቲኒ በአሁኑ ወቅት ለታይዋን ሙሉ ዲፕሎማሲያዊ እውቅና ከሰጡ 12 የዓለማችን ሀገራት መካከል አንዷ መሆኗ ይታወቃል።
ይህ ክስተት ቻይና የታይዋንን የውጭ ግንኙነት መስመር ለመዝጋት የምታደርገውን ጥብቅ ቁጥጥርና በአፍሪካ ሀገራት ላይ ያላትን የፖለቲካ ተጽዕኖ በድጋሚ ያሳየ ሆኗል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#premiumtimes #taiwan #eswatini #china #africa #diplomacy #thiqaheth
#ethiopia | የታይዋኑ ፕሬዝዳንት ላይ ቺንግ ቴ ወደ አፍሪካዊቷ ሀገር ኢስዋቲኒ ለማቅናት አቅደው የነበረ ቢሆንም፣ የአየር ክልል ፍቃድ በማጣታቸው ጉዟቸውን ለመሰረዝ ተገደዋል።
ሲሸልስ፣ ሞሪሸስ እና ማዳጋስካር ለፕሬዝዳንቱ በረራ የአየር ክልላቸውን ክፍት ለማድረግ ፍቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል።
የታይዋን ፕሬዝዳንታዊ ፅህፈት ቤት ሃላፊ ፓን ሜንጋን እንደገለጹት፣ ሀገራቱ ቀደም ሲል ፍቃደኝነታቸውን አሳውቀው የነበረ ቢሆንም ከጥቂት ቀናት በኋላ ግን በድንገት ሃሳባቸውን ቀይረዋል።
ታይዋን ለዚህ የአቋም ለውጥ ዋነኛው ምክንያት ከቤጂንግ (ቻይና) የሚመጣ ዲፕሎማሲያዊ ጫና መሆኑን በግልጽ ተናግራለች።
"ቻይና ታይዋንን በዓለም አቀፍ መድረክ በዲፕሎማሲ ለማግለል የምታደርገው ጥረት አካል ነው" — የታይዋን ባለስልጣናት
ፕሬዝዳንት ላይ ቺንግ ቴ ወደ ስፍራው ማቅናት የፈለጉት፣ የታይዋን የቅርብ ወዳጅ የሆኑት የኢስዋቲኒው ንጉሥ ሚስዋቲ 40ኛ ዓመት የንግሥና በዓል ላይ ለመታደም ነበር።
ኢስዋቲኒ በአሁኑ ወቅት ለታይዋን ሙሉ ዲፕሎማሲያዊ እውቅና ከሰጡ 12 የዓለማችን ሀገራት መካከል አንዷ መሆኗ ይታወቃል።
ይህ ክስተት ቻይና የታይዋንን የውጭ ግንኙነት መስመር ለመዝጋት የምታደርገውን ጥብቅ ቁጥጥርና በአፍሪካ ሀገራት ላይ ያላትን የፖለቲካ ተጽዕኖ በድጋሚ ያሳየ ሆኗል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#premiumtimes #taiwan #eswatini #china #africa #diplomacy #thiqaheth
2 months ago
የኤርትራ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች በእስዋቲኒ መኮብለላቸው ተሰማ
#ethiopia | የኤርትራ ብሔራዊ ቡድን (ቀይ ባህር ግመሎች) ለዓመታት ከአህጉራዊ ውድድሮች ርቆ ከቆየ በኋላ፣ በቅርቡ ባደረገው የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታ ውጤታማ ሆኖ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ ድልድል መቀላቀሉ የሚታወስ ነው። ሆኖም ይህን ደስታ የሚያደበዝዝ ዜና ከስፍራው እየወጣ ይገኛል።
ከቡድኑ ስብስብ ጋር ወደ እስዋቲኒ ተጉዘው ከነበሩት የሀገር ውስጥ ተጫዋቾች መካከል ሰባቱ (7) መጥፋታቸው ተረጋግጧል።
ቡድኑ የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታውን ባከናወነባት እስዋቲኒ።በስብስቡ ውስጥ ተካተው ከነበሩ 10 የሀገር ውስጥ ተጫዋቾች መካከል 3ቱ ብቻ ወደ ሀገራቸው ሲመለሱ፣ 7ቱ ግን እዛው ቀርተዋል።
ተጫዋቾቹ ብሔራዊ ቡድኑ ረጅም ጊዜ ከቆየበት እገዳ ተላቆ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ እንዲመለስ ትልቅ ግዳጅ ከተወጡ በኋላ ነው የመመለስ ፍቃደኛ ያልሆኑት።
የኤርትራ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች ከዚህ ቀደም በተለያዩ ሀገራት በሚደረጉ ውድድሮች ላይ መሰል ድርጊቶችን ሲፈጽሙ መቆየታቸው የሚታወስ ሲሆን፣ የአሁኑ አጋጣሚ ቡድኑ ወደ ዓለም አቀፍ መድረክ በተመለሰበት ማግስት መከሰቱ ትኩረት ስቧል ያለው ቲክቫህ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #eritrea #redseacamels #afcon2025 #footballnews #eswatini #africacupof Nations #breakingnews #eritreanfootball
#ethiopia | የኤርትራ ብሔራዊ ቡድን (ቀይ ባህር ግመሎች) ለዓመታት ከአህጉራዊ ውድድሮች ርቆ ከቆየ በኋላ፣ በቅርቡ ባደረገው የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታ ውጤታማ ሆኖ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ ድልድል መቀላቀሉ የሚታወስ ነው። ሆኖም ይህን ደስታ የሚያደበዝዝ ዜና ከስፍራው እየወጣ ይገኛል።
ከቡድኑ ስብስብ ጋር ወደ እስዋቲኒ ተጉዘው ከነበሩት የሀገር ውስጥ ተጫዋቾች መካከል ሰባቱ (7) መጥፋታቸው ተረጋግጧል።
ቡድኑ የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታውን ባከናወነባት እስዋቲኒ።በስብስቡ ውስጥ ተካተው ከነበሩ 10 የሀገር ውስጥ ተጫዋቾች መካከል 3ቱ ብቻ ወደ ሀገራቸው ሲመለሱ፣ 7ቱ ግን እዛው ቀርተዋል።
ተጫዋቾቹ ብሔራዊ ቡድኑ ረጅም ጊዜ ከቆየበት እገዳ ተላቆ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ እንዲመለስ ትልቅ ግዳጅ ከተወጡ በኋላ ነው የመመለስ ፍቃደኛ ያልሆኑት።
የኤርትራ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች ከዚህ ቀደም በተለያዩ ሀገራት በሚደረጉ ውድድሮች ላይ መሰል ድርጊቶችን ሲፈጽሙ መቆየታቸው የሚታወስ ሲሆን፣ የአሁኑ አጋጣሚ ቡድኑ ወደ ዓለም አቀፍ መድረክ በተመለሰበት ማግስት መከሰቱ ትኩረት ስቧል ያለው ቲክቫህ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #eritrea #redseacamels #afcon2025 #footballnews #eswatini #africacupof Nations #breakingnews #eritreanfootball