8 hours ago
ኢትዮጵያና አይ ኤም ኤፍ (አይኤምኤፍ) የ468 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት ላይ ደረሱ
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) እና የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት በተራዘመው የብድር አቅርቦት ፕሮግራም አምስተኛ ግምገማ ላይ በባለሙያዎች ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን አስታውቀዋል።
ይህ ስምምነት በሚቀጥሉት ሳምንታት በድርጅቱ ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሙሉ በሙሉ ሲጸድቅ፣ ኢትዮጵያ የ468 ሚሊዮን ዶላር ገደማ ተጨማሪ የፋይናንስ ድጋፍ እንድታገኝ ያደርጋታል።
ይህም ሀገሪቱ በ4 ዓመታት ውስጥ ከምታገኘው የ3.4 ቢሊዮን ዶላር አጠቃላይ ድጋፍ ውስጥ እስካሁን የተለቀቀላትን የገንዘብ መጠን ወደ 2.65 ቢሊዮን ዶላር ከፍ የሚያደርገው ሲሆን፣ ስምምነቱ ሊደረስ የተቻለው ከአልቫሮ ፒሪስ የተመራው የድርጅቱ ልዑክ ከሚያዝያ 28 እስከ ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ባደረገው የሁለት ሳምንታት ጉብኝትና ተከታታይ የሥራ ውይይቶች ማጠናቀቂያ ላይ ነው።
በዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት መግለጫ ላይ እንደተመለከተው ፣ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከቀጠናዊ ቀውሶች ጋር ተያይዞ የመጣውን ትልቅ ውጫዊ ጫና በመቋቋም ረገድ ከፍተኛ ጥንካሬ አሳይቷል።
ይሁን እንጂ፣ ዓለም አቀፋዊ አለመረጋጋትና የሸቀጦች ዋጋ መዋዠቅ አሁንም እያደገ በመምጣቱ በኢኮኖሚው የወደፊት ጉዞ ላይ የሚታዩት ስጋቶች መጨመራቸውን አይ ኤም ኤፍ አስጠንቅቋል።
የሀገሪቱን የኢኮኖሚ መረጋጋት በዘላቂነት ለማስቀጠልም ድርጅቱ ለኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ቁልፍ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን የጠቆመ ሲሆን፣ ይህም የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲን አጠናክሮ መቀጠልን፣ የውጭ ምንዛሬ ገበያውን ግልጽነትና አሠራር ይበልጥ ማሻሻልን እንዲሁም የአገር ውስጥ ገቢ አሰባሰብን በማጠናከር የወጪ አያያዝን በጥንቃቄ መምራት አስፈላጊ መሆኑን አሳስቧል።
Seledadotio
Seledadotio
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) እና የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት በተራዘመው የብድር አቅርቦት ፕሮግራም አምስተኛ ግምገማ ላይ በባለሙያዎች ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሳቸውን አስታውቀዋል።
ይህ ስምምነት በሚቀጥሉት ሳምንታት በድርጅቱ ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሙሉ በሙሉ ሲጸድቅ፣ ኢትዮጵያ የ468 ሚሊዮን ዶላር ገደማ ተጨማሪ የፋይናንስ ድጋፍ እንድታገኝ ያደርጋታል።
ይህም ሀገሪቱ በ4 ዓመታት ውስጥ ከምታገኘው የ3.4 ቢሊዮን ዶላር አጠቃላይ ድጋፍ ውስጥ እስካሁን የተለቀቀላትን የገንዘብ መጠን ወደ 2.65 ቢሊዮን ዶላር ከፍ የሚያደርገው ሲሆን፣ ስምምነቱ ሊደረስ የተቻለው ከአልቫሮ ፒሪስ የተመራው የድርጅቱ ልዑክ ከሚያዝያ 28 እስከ ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ባደረገው የሁለት ሳምንታት ጉብኝትና ተከታታይ የሥራ ውይይቶች ማጠናቀቂያ ላይ ነው።
በዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት መግለጫ ላይ እንደተመለከተው ፣ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከቀጠናዊ ቀውሶች ጋር ተያይዞ የመጣውን ትልቅ ውጫዊ ጫና በመቋቋም ረገድ ከፍተኛ ጥንካሬ አሳይቷል።
ይሁን እንጂ፣ ዓለም አቀፋዊ አለመረጋጋትና የሸቀጦች ዋጋ መዋዠቅ አሁንም እያደገ በመምጣቱ በኢኮኖሚው የወደፊት ጉዞ ላይ የሚታዩት ስጋቶች መጨመራቸውን አይ ኤም ኤፍ አስጠንቅቋል።
የሀገሪቱን የኢኮኖሚ መረጋጋት በዘላቂነት ለማስቀጠልም ድርጅቱ ለኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ቁልፍ የፖሊሲ አቅጣጫዎችን የጠቆመ ሲሆን፣ ይህም የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲን አጠናክሮ መቀጠልን፣ የውጭ ምንዛሬ ገበያውን ግልጽነትና አሠራር ይበልጥ ማሻሻልን እንዲሁም የአገር ውስጥ ገቢ አሰባሰብን በማጠናከር የወጪ አያያዝን በጥንቃቄ መምራት አስፈላጊ መሆኑን አሳስቧል።
Seledadotio
Seledadotio
19 hours ago
ይህንን ያውቃሉ❓❓
የሲቪል ምዝገባና ነዋሪዎች አገልግሎት ኤጀንሲ በወረዳ ጽሕፈት ቤቶቹ የሚሰጣቸውን የኩነት (የልደት፣ ጋብቻ፣ ፍቺ፣ ሞትና ጉዲፈቻ) ማስረጃዎችን የማረጋገጥ አገልግሎት ለማግኘት ተገልጋዮች ይዘው መቅረብ የሚገባቸው ቅድመ ሁኔታዎችንና ደጋፊ ሰነዶችን እንደሚከተለው ያሳውቃል።
ለእያንዳንዱ አገልግሎት የሚያስፈልጉ ልዩ ቅድመ ሁኔታዎች
1. የልደት ሰርተፍኬት ለማረጋገጥ
ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች ለሆኑ፦ በወረዳ ደረጃ የተመዘገበ የልደት ማስረጃ
አገልግሎቱ የሚሰጠው ከሁለቱ አንዱ ወላጅ በአካል ሲገኝ ነው (የወላጆች የታደሰ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት ያስፈልጋል)።
ምዝገባው በሞግዚትነት ከሆነ የፍርድ ቤት የሞግዚትነት ውሳኔ ሰነድ መቅረብ አለበት።
ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በላይ ለሆኑ፦ ባለጉዳዩ በአካል መቅረብ አለበት። በአካል መቅረብ ካልቻለ፣ ጉዳዩን የሚገልጽ ልዩ ውክልና ከወካይና ተወካይ የታደሰ መታወቂያ/ፓስፖርት ጋር ማቅረብ ይኖርበታል።
2. የጋብቻ ማስረጃ ለማረጋገጥ
በክፍለ ከተማ ወይም በወረዳ ደረጃ የተመዘገበ የጋብቻ ማስረጃ መያዝ።
ለግልባጭ ወይም ለእርማት አገልግሎት፦ የተጋቢዎች ሁለት ሁለት (2) ጉርድ ፎቶግራፍ።
በውክልና የሚጠየቅ ከሆነ (ለእርማት፣ ዕድሳትና ግልባጭ)፦ ባልና ሚስት ጉዳዩን በግልጽ የሚያሳይ ውክልና፣ የወካዮች እና የተወካይ የታደሰ መታወቂያ/ፓስፖርት ወይም የታደሰ የመኖሪያ ፈቃድ ማቅረብ አለባቸው።
3. የፍቺ ማስረጃ ለማረጋገጥ
በክፍለ ከተማ ወይም በወረዳ ደረጃ የተመዘገበ የፍቺ ማስረጃ
የህግ አስገዳጅነቱ የተረጋገጠ የፍርድ ቤት የፍቺ ውሳኔ ሰነድ መቅረብ አለበት።
4. የጉዲፈቻ ሰርተፍኬት ለማረጋገጥ
በወረዳ የተመዘገበ የጉዲፈቻ ሰርተፍኬት እና የፍርድ ቤት ውሳኔ ሰነድ
ጉዲፈቻ አድራጊዎች የታደሰ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት በመያዝ በአካል መቅረብ አለባቸው።
ጉዳዩ በውክልና ከሆነ፣ይህንኑ የሚያስረዳ ልዩ ውክልና መቅረብ አለበት።
5. የሞት ማስረጃ ለማረጋገጥ
በወረዳ ደረጃ የተመዘገበ የሞት ማስረጃ የማረጋገጥ አገልግሎት ለማግኘት
ከሟች ጋር አብሮ ይኖር የነበረ ሰው፣ እርሱ ከሌለ የሟች የስጋ ወይም የጋብቻ ዘመዶች፣ እነዚህም ከሌሉ የቅርብ ጎረቤት ወይም ስለሟቹ መሞት የሚያውቅ ማንኛውም ሰው የታደሰ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት በማቅረብ ማስመዝገብና ማረጋገጥ ይችላል።
ሟች የውጭ ሀገር ዜጋ ከሆነ ከሆስፒታል የተሰጠ የማሳወቂያ ወረቀት መቅረብ አለበት።
ማሳሰቢያ፡- ለሁሉም ከላይ ለተዘረዘሩት የኩነት አገልግሎቶችን ለማግኘት የሚያስፈልግ ደጋፊ ሰነድ
• የታደሰ ብሔራዊ መታወቂያ / የታደሰ ፓስፖርት / የትውልደ ኢትዮጵያ የውጭ ዜግነት መታወቂያ (የቢጫ ካርድ)።
• ከዝቅተኛው አስተዳደር ጽ/ቤት መደበኛ ነዋሪነቱን የሚገልጽ የድጋፍ ደብዳቤ / የስደተኛነት ማስረጃ / የመኖሪያ ፈቃድ።
• ከሚሰራበት መስሪያ ቤት ባልደረባነቱንና ዜግነቱን የሚገልጽ የድጋፍ ደብዳቤ ከመስሪያ ቤቱ መታወቂያ ጋር / የመከላከያ ሰራዊት ከሆነ የመከላከያ ሰራዊት መታወቂያ መያዝ
• የጠፋ ሰርተፍኬት ግልባጭ ለመውሰድ፦ ከፖሊስ የተሰጠ የጠፋ ሰነድ ማረጋገጫ ማቅረብ ግዴታ ነው።
• ከወረዳ የመጡ ማስረጃዎች፦ ከወረዳው ስለመውጣታቸው የሚገልጽ ማረጋገጫ ደብዳቤ ያስፈልጋቸዋል።
• ከክፍለ ከተማ የመጡ ማስረጃዎች፦ ከሰነዱ በስተጀርባ የማረጋገጫ ማህተም ማረፍ ይኖርበታል።
• ከውጭ ሀገር የሚመጣ ውክልና፦ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና በፌደራል ሰነዶች ምዝገባና ማረጋገጫ ኤጀንሲ መረጋገጥ አለበት።
Seledadotio
Seledadotio
የሲቪል ምዝገባና ነዋሪዎች አገልግሎት ኤጀንሲ በወረዳ ጽሕፈት ቤቶቹ የሚሰጣቸውን የኩነት (የልደት፣ ጋብቻ፣ ፍቺ፣ ሞትና ጉዲፈቻ) ማስረጃዎችን የማረጋገጥ አገልግሎት ለማግኘት ተገልጋዮች ይዘው መቅረብ የሚገባቸው ቅድመ ሁኔታዎችንና ደጋፊ ሰነዶችን እንደሚከተለው ያሳውቃል።
ለእያንዳንዱ አገልግሎት የሚያስፈልጉ ልዩ ቅድመ ሁኔታዎች
1. የልደት ሰርተፍኬት ለማረጋገጥ
ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች ለሆኑ፦ በወረዳ ደረጃ የተመዘገበ የልደት ማስረጃ
አገልግሎቱ የሚሰጠው ከሁለቱ አንዱ ወላጅ በአካል ሲገኝ ነው (የወላጆች የታደሰ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት ያስፈልጋል)።
ምዝገባው በሞግዚትነት ከሆነ የፍርድ ቤት የሞግዚትነት ውሳኔ ሰነድ መቅረብ አለበት።
ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በላይ ለሆኑ፦ ባለጉዳዩ በአካል መቅረብ አለበት። በአካል መቅረብ ካልቻለ፣ ጉዳዩን የሚገልጽ ልዩ ውክልና ከወካይና ተወካይ የታደሰ መታወቂያ/ፓስፖርት ጋር ማቅረብ ይኖርበታል።
2. የጋብቻ ማስረጃ ለማረጋገጥ
በክፍለ ከተማ ወይም በወረዳ ደረጃ የተመዘገበ የጋብቻ ማስረጃ መያዝ።
ለግልባጭ ወይም ለእርማት አገልግሎት፦ የተጋቢዎች ሁለት ሁለት (2) ጉርድ ፎቶግራፍ።
በውክልና የሚጠየቅ ከሆነ (ለእርማት፣ ዕድሳትና ግልባጭ)፦ ባልና ሚስት ጉዳዩን በግልጽ የሚያሳይ ውክልና፣ የወካዮች እና የተወካይ የታደሰ መታወቂያ/ፓስፖርት ወይም የታደሰ የመኖሪያ ፈቃድ ማቅረብ አለባቸው።
3. የፍቺ ማስረጃ ለማረጋገጥ
በክፍለ ከተማ ወይም በወረዳ ደረጃ የተመዘገበ የፍቺ ማስረጃ
የህግ አስገዳጅነቱ የተረጋገጠ የፍርድ ቤት የፍቺ ውሳኔ ሰነድ መቅረብ አለበት።
4. የጉዲፈቻ ሰርተፍኬት ለማረጋገጥ
በወረዳ የተመዘገበ የጉዲፈቻ ሰርተፍኬት እና የፍርድ ቤት ውሳኔ ሰነድ
ጉዲፈቻ አድራጊዎች የታደሰ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት በመያዝ በአካል መቅረብ አለባቸው።
ጉዳዩ በውክልና ከሆነ፣ይህንኑ የሚያስረዳ ልዩ ውክልና መቅረብ አለበት።
5. የሞት ማስረጃ ለማረጋገጥ
በወረዳ ደረጃ የተመዘገበ የሞት ማስረጃ የማረጋገጥ አገልግሎት ለማግኘት
ከሟች ጋር አብሮ ይኖር የነበረ ሰው፣ እርሱ ከሌለ የሟች የስጋ ወይም የጋብቻ ዘመዶች፣ እነዚህም ከሌሉ የቅርብ ጎረቤት ወይም ስለሟቹ መሞት የሚያውቅ ማንኛውም ሰው የታደሰ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት በማቅረብ ማስመዝገብና ማረጋገጥ ይችላል።
ሟች የውጭ ሀገር ዜጋ ከሆነ ከሆስፒታል የተሰጠ የማሳወቂያ ወረቀት መቅረብ አለበት።
ማሳሰቢያ፡- ለሁሉም ከላይ ለተዘረዘሩት የኩነት አገልግሎቶችን ለማግኘት የሚያስፈልግ ደጋፊ ሰነድ
• የታደሰ ብሔራዊ መታወቂያ / የታደሰ ፓስፖርት / የትውልደ ኢትዮጵያ የውጭ ዜግነት መታወቂያ (የቢጫ ካርድ)።
• ከዝቅተኛው አስተዳደር ጽ/ቤት መደበኛ ነዋሪነቱን የሚገልጽ የድጋፍ ደብዳቤ / የስደተኛነት ማስረጃ / የመኖሪያ ፈቃድ።
• ከሚሰራበት መስሪያ ቤት ባልደረባነቱንና ዜግነቱን የሚገልጽ የድጋፍ ደብዳቤ ከመስሪያ ቤቱ መታወቂያ ጋር / የመከላከያ ሰራዊት ከሆነ የመከላከያ ሰራዊት መታወቂያ መያዝ
• የጠፋ ሰርተፍኬት ግልባጭ ለመውሰድ፦ ከፖሊስ የተሰጠ የጠፋ ሰነድ ማረጋገጫ ማቅረብ ግዴታ ነው።
• ከወረዳ የመጡ ማስረጃዎች፦ ከወረዳው ስለመውጣታቸው የሚገልጽ ማረጋገጫ ደብዳቤ ያስፈልጋቸዋል።
• ከክፍለ ከተማ የመጡ ማስረጃዎች፦ ከሰነዱ በስተጀርባ የማረጋገጫ ማህተም ማረፍ ይኖርበታል።
• ከውጭ ሀገር የሚመጣ ውክልና፦ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና በፌደራል ሰነዶች ምዝገባና ማረጋገጫ ኤጀንሲ መረጋገጥ አለበት።
Seledadotio
Seledadotio
20 hours ago
IMF ለኢትዮጵያ የ468 ሚሊዮን ዶላር ተጨማሪ የገንዘብ ድጋፍ የሚያስገኝ የስምምነት ደረጃ ላይ መድረሱን አስታወቀ
የኔታ ሚዲያ
የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) የባለሙያዎች ቡድን እና የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት በ3.4 ቢሊዮን ዶላር የተራዘመ የብድር ማዕቀፍ (ECF) አምስተኛው ክለሳ ላይ ከስምምነት መድረሳቸውን ድርጅቱ አስታወቀ።
ይህ በባለሙያዎች ደረጃ የተደረሰው ስምምነት በIMF ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሲጸድቅ ኢትዮጵያ ወደ 468 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚጠጋ ተጨማሪ ገንዘብ ማግኘት የምትችል ይሆናል።
በአልቫሮ ፒሪስ የተመራው የIMF የባለሙያዎች ቡድን ከአምስተኛው ክለሳ ጋር በተያያዘ ከግንቦት 1 እስከ ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ በአካል ከዚያ በኋላ ደግሞ በበይነ መረብ (ቨርቿል) ውይይት ሲያደርግ ቆይቷል።
የልዑካን ቡድኑ መሪ አልቫሮ ፒሪስ ባወጡት መግለጫ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት አገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳቸውን በተሳካ ሁኔታ መተግበራቸውን መቀጠላቸውን ገልጸዋል።
እ.ኤ.አ እስከ 2026 መጀመሪያ ድረስ የምርት አመላካቾች፣ ወጪ ንግድ፣ የውጭ ምንዛሬ ክምችት እና የመንግሥት ገቢ መሻሻል ማሳየታቸውንና የዋጋ ንረትም መቀነሱን ጠቁመዋል።
ሆኖም በመካከለኛው ምስራቅ የተቀሰቀሰው ጦርነት በንግድ እንቅስቃሴ ላይ መስተጓጎል መፍጠሩን፣ ጊዜያዊ የነዳጅ እጥረት ማስከተሉን እና የገቢ ነዳጅና ማዳበሪያ ዋጋን በከፍተኛ ሁኔታ ማናሩን መግለጫው አመልክቷል።
ይህ ትልቅ ውጫዊ ተጽዕኖ ቢሆንም የኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ አሁንም ጠንካራ መሆኑንና በምርት ዕድገትና በሸማቾች ዋጋ ንረት ላይ ያሳደረው ተጽዕኖ እስካሁን መጠነኛ መሆኑ ተገልጿል።
የIMF መግለጫ በመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት ምክንያት ዓለም አቀፋዊ አለመረጋጋትና የሸቀጦች ዋጋ መዋዠቅ በመጨመሩ፣ በኢኮኖሚው ላይ ሊደቀኑ የሚችሉ ስጋቶች መጨመራቸውን ያስጠነቅቃል። በመሆኑም ለነዚህ አዳዲስ ተግዳሮቶች ብልህ ምላሽ መስጠትና የሀብት አጠቃቀምን በጥንቃቄ መምራት እንደሚያስፈልግ አሳስቧል።
ማክሮ-ኢኮኖሚያዊ መረጋጋትን በዘላቂነት ለማስቀጠል የሚከተሉት መሠረታዊ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ድርጅቱ መክሯል፦
• የገንዘብ ፖሊሲ ማጥበቅ፦ የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲን ማስቀጠል።
• የውጭ ምንዛሬ ገበያ ማሻሻያ፦ የውጭ ምንዛሬ ገበያው ይበልጥ ግልጽና ውጤታማ በሆነ መንገድ እንዲሠራ ማድረግ።
• የአገር ውስጥ ገቢና ወጪ አስተዳደር፦ የአገር ውስጥ ገቢ ማሰባሰብን ማሳደግና የወጪ አስተዳደርን በጥንቃቄ በመምራት የፋይናንስ ዘላቂነትን ማረጋገጥ።
• መዋቅራዊ ማሻሻያዎች፦ የንግድ አካባቢን ማሻሻል፣ የፋይናንስ ዘርፉን ጥንካሬ ማጠናከርና የግል ዘርፉ መር ለሆነ ዕድገት በር መክፈት።
የውጭ ዕዳ ሽግሽግ
የኢትዮጵያን የዕዳ ዘላቂነት ለመመለስ የሚያስችል አጠቃላይ የውጭ ዕዳ ሽግሽግ (treatment) ለማግኘት መልካም ግስጋሴ እየታየ መሆኑን IMF ገልጿል። ከባለሥልጣናት አበዳሪዎች ጋር የሚደረገው የዕዳ መልሶ ማዋቀር ውይይት እንደተጠበቀው እየገፋ ሲሆን ከቦንድ ባለቤቶች ጋር የሚደረገው ድርድርም መቀጠሉ ተጠቅሷል።
የIMF ልዑካን ቡድን በአዲስ አበባ በነበረው ቆይታ ከገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ፣ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶ/ር እዮብ ተካልኝ እና ከሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ እንዲሁም ከግል ዘርፉና ከልማት አጋሮች ተወካዮች ጋር ፍሬያማ ውይይት ማድረጉን በመግለጽ ለተደረገለት ትብብር ምስጋና አቅርቧል።
ይህ አምስተኛው ክለሳ በIMF ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሲጸድቅ ኢትዮጵያ በዚሁ ማዕቀፍ እስካሁን ያገኘችው አጠቃላይ የገንዘብ ድጋፍ ወደ 2.65 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ከፍ ይላል።
የኔታ ሚዲያ
የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) የባለሙያዎች ቡድን እና የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት በ3.4 ቢሊዮን ዶላር የተራዘመ የብድር ማዕቀፍ (ECF) አምስተኛው ክለሳ ላይ ከስምምነት መድረሳቸውን ድርጅቱ አስታወቀ።
ይህ በባለሙያዎች ደረጃ የተደረሰው ስምምነት በIMF ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሲጸድቅ ኢትዮጵያ ወደ 468 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚጠጋ ተጨማሪ ገንዘብ ማግኘት የምትችል ይሆናል።
በአልቫሮ ፒሪስ የተመራው የIMF የባለሙያዎች ቡድን ከአምስተኛው ክለሳ ጋር በተያያዘ ከግንቦት 1 እስከ ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ በአካል ከዚያ በኋላ ደግሞ በበይነ መረብ (ቨርቿል) ውይይት ሲያደርግ ቆይቷል።
የልዑካን ቡድኑ መሪ አልቫሮ ፒሪስ ባወጡት መግለጫ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት አገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳቸውን በተሳካ ሁኔታ መተግበራቸውን መቀጠላቸውን ገልጸዋል።
እ.ኤ.አ እስከ 2026 መጀመሪያ ድረስ የምርት አመላካቾች፣ ወጪ ንግድ፣ የውጭ ምንዛሬ ክምችት እና የመንግሥት ገቢ መሻሻል ማሳየታቸውንና የዋጋ ንረትም መቀነሱን ጠቁመዋል።
ሆኖም በመካከለኛው ምስራቅ የተቀሰቀሰው ጦርነት በንግድ እንቅስቃሴ ላይ መስተጓጎል መፍጠሩን፣ ጊዜያዊ የነዳጅ እጥረት ማስከተሉን እና የገቢ ነዳጅና ማዳበሪያ ዋጋን በከፍተኛ ሁኔታ ማናሩን መግለጫው አመልክቷል።
ይህ ትልቅ ውጫዊ ተጽዕኖ ቢሆንም የኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ አሁንም ጠንካራ መሆኑንና በምርት ዕድገትና በሸማቾች ዋጋ ንረት ላይ ያሳደረው ተጽዕኖ እስካሁን መጠነኛ መሆኑ ተገልጿል።
የIMF መግለጫ በመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት ምክንያት ዓለም አቀፋዊ አለመረጋጋትና የሸቀጦች ዋጋ መዋዠቅ በመጨመሩ፣ በኢኮኖሚው ላይ ሊደቀኑ የሚችሉ ስጋቶች መጨመራቸውን ያስጠነቅቃል። በመሆኑም ለነዚህ አዳዲስ ተግዳሮቶች ብልህ ምላሽ መስጠትና የሀብት አጠቃቀምን በጥንቃቄ መምራት እንደሚያስፈልግ አሳስቧል።
ማክሮ-ኢኮኖሚያዊ መረጋጋትን በዘላቂነት ለማስቀጠል የሚከተሉት መሠረታዊ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ድርጅቱ መክሯል፦
• የገንዘብ ፖሊሲ ማጥበቅ፦ የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲን ማስቀጠል።
• የውጭ ምንዛሬ ገበያ ማሻሻያ፦ የውጭ ምንዛሬ ገበያው ይበልጥ ግልጽና ውጤታማ በሆነ መንገድ እንዲሠራ ማድረግ።
• የአገር ውስጥ ገቢና ወጪ አስተዳደር፦ የአገር ውስጥ ገቢ ማሰባሰብን ማሳደግና የወጪ አስተዳደርን በጥንቃቄ በመምራት የፋይናንስ ዘላቂነትን ማረጋገጥ።
• መዋቅራዊ ማሻሻያዎች፦ የንግድ አካባቢን ማሻሻል፣ የፋይናንስ ዘርፉን ጥንካሬ ማጠናከርና የግል ዘርፉ መር ለሆነ ዕድገት በር መክፈት።
የውጭ ዕዳ ሽግሽግ
የኢትዮጵያን የዕዳ ዘላቂነት ለመመለስ የሚያስችል አጠቃላይ የውጭ ዕዳ ሽግሽግ (treatment) ለማግኘት መልካም ግስጋሴ እየታየ መሆኑን IMF ገልጿል። ከባለሥልጣናት አበዳሪዎች ጋር የሚደረገው የዕዳ መልሶ ማዋቀር ውይይት እንደተጠበቀው እየገፋ ሲሆን ከቦንድ ባለቤቶች ጋር የሚደረገው ድርድርም መቀጠሉ ተጠቅሷል።
የIMF ልዑካን ቡድን በአዲስ አበባ በነበረው ቆይታ ከገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ፣ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶ/ር እዮብ ተካልኝ እና ከሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ እንዲሁም ከግል ዘርፉና ከልማት አጋሮች ተወካዮች ጋር ፍሬያማ ውይይት ማድረጉን በመግለጽ ለተደረገለት ትብብር ምስጋና አቅርቧል።
ይህ አምስተኛው ክለሳ በIMF ሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሲጸድቅ ኢትዮጵያ በዚሁ ማዕቀፍ እስካሁን ያገኘችው አጠቃላይ የገንዘብ ድጋፍ ወደ 2.65 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ከፍ ይላል።
23 hours ago
ሁለተኛው የኢትዮጵያ እና ፊንላንድ የፖለቲካ ምክክር በአዲስ አበባ ተካሄደ
*********************
ሁለተኛው የኢትዮጵያ እና ፊንላንድ የፖለቲካ ምክክር በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ የተካሄደ ሲሆን በምክክሩ በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በንግድ፣ በትምህርት እና በአየር ንብረት ለውጥ ዙሪያ ሰፊ ግምገማ ተደርጓል።
ምክክሩን በጋራ የመሩት አምባሳደር መለስ ዓለም እና የፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምክትል ዋና ጸሐፊ አምባሳደር ኦውቲ ሆሎፓይነን የሁለቱን ሀገራት የቆየ ግንኙነት እና አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት በድጋሚ አረጋግጠዋል።
በዚሁ ወቅት ማብራሪያ የሰጡት አምባሳደር መለስ ዓለም በኢትዮጵያ ስላለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ፣ ስለ 7ኛው አጠቃላይ ምርጫ፣ ስለ ብሔራዊ ምክክር ሂደት እና ስለ ፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት አፈጻጸም ለፊንላንድ ልዑካን ገልጸዋል።
አምባሳደሩ የፊንላንድ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ በፈጠራ፣ በቴክኖሎጂ እና በግብርና ማቀነባበሪያ ዘርፎች እንዲሰማሩ ጥሪ በማቅረብ ንግድን ለማሳደግ የሁለቱ ሀገራት የንግድ ምክር ቤቶች በቅርበት እንዲሠሩ አሳስበዋል።
የፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምክትል ዋና ጸሐፊ አምባሳደር ኦውቲ ሆሎፓይነን በበኩላቸው፣ በአዲስ አበባ እየታየ ያለውን ፈጣን የልማት ለውጥ አድንቀዋል።
አምባሳደሩ ኢትዮጵያ ለሀገራቸው ቁልፍ አጋር መሆኗን ገልጸው፣ ፊንላንድ ለኢትዮጵያ የምታደርገውን ድጋፍ እንደምትቀጥል ተናግረዋል።
በተለይም በዲጂታላይዜሽን፣ በከፍተኛ ትምህርት፣ በሜትሮሎጂ እና በአስተማሪዎች ሥልጠና ዙሪያ የሚደረገው ትብብር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀው፣ መሰል መደበኛ ውይይቶችን አጠናክሮ ለመቀጠል መስማማታቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
#ethiopia #ebc #finland #ethiopiafinlandconsultation #addisababa
*********************
ሁለተኛው የኢትዮጵያ እና ፊንላንድ የፖለቲካ ምክክር በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ የተካሄደ ሲሆን በምክክሩ በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በንግድ፣ በትምህርት እና በአየር ንብረት ለውጥ ዙሪያ ሰፊ ግምገማ ተደርጓል።
ምክክሩን በጋራ የመሩት አምባሳደር መለስ ዓለም እና የፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምክትል ዋና ጸሐፊ አምባሳደር ኦውቲ ሆሎፓይነን የሁለቱን ሀገራት የቆየ ግንኙነት እና አጋርነት ይበልጥ ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት በድጋሚ አረጋግጠዋል።
በዚሁ ወቅት ማብራሪያ የሰጡት አምባሳደር መለስ ዓለም በኢትዮጵያ ስላለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ፣ ስለ 7ኛው አጠቃላይ ምርጫ፣ ስለ ብሔራዊ ምክክር ሂደት እና ስለ ፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት አፈጻጸም ለፊንላንድ ልዑካን ገልጸዋል።
አምባሳደሩ የፊንላንድ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ በፈጠራ፣ በቴክኖሎጂ እና በግብርና ማቀነባበሪያ ዘርፎች እንዲሰማሩ ጥሪ በማቅረብ ንግድን ለማሳደግ የሁለቱ ሀገራት የንግድ ምክር ቤቶች በቅርበት እንዲሠሩ አሳስበዋል።
የፊንላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምክትል ዋና ጸሐፊ አምባሳደር ኦውቲ ሆሎፓይነን በበኩላቸው፣ በአዲስ አበባ እየታየ ያለውን ፈጣን የልማት ለውጥ አድንቀዋል።
አምባሳደሩ ኢትዮጵያ ለሀገራቸው ቁልፍ አጋር መሆኗን ገልጸው፣ ፊንላንድ ለኢትዮጵያ የምታደርገውን ድጋፍ እንደምትቀጥል ተናግረዋል።
በተለይም በዲጂታላይዜሽን፣ በከፍተኛ ትምህርት፣ በሜትሮሎጂ እና በአስተማሪዎች ሥልጠና ዙሪያ የሚደረገው ትብብር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀው፣ መሰል መደበኛ ውይይቶችን አጠናክሮ ለመቀጠል መስማማታቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
#ethiopia #ebc #finland #ethiopiafinlandconsultation #addisababa
Sponsored by
Surafel
23 hours ago
የአቡነ ሀብተ ማርያም ምልጃ እና ረድኤት አይለየን🙏
በነገሥታት ፊት የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት መሰከረ።
በምጽዋትና በስገድት የምትጋደለው እናቱ ዮስቴና ሀብቷን ሁሉ ለድሆች ሰጥታ ለምናኔ ወደ በረኃ ሄደች። በዚያ ያገኘችው ባሕታዊም በመንፈስ ቅዱስ ተገልጦለት ከእርሷ ቅዱስ ፍሬ እንደሚወጣ ነግሮ ወደ ዓለም እንድትመለስ አዘዛት። እርሷም “እግዚአብሔር የወደደው ይሁን” ብላ እያመሰገነች ተመልሰች፡፡ የአባቱ የትውልድ ሀገር የራውዕይ በምትባል ሀገር ሲሆን ከዚህች የተባረከች ሴት ጋር ተጋባ። እርሷም በበጎ ምግባርና ሥራ የተጌጠች፣ በሕግ ተወስና በጾም፣ በጸሎት፣ የምትተጋ ነበረች። ከጥቂት ጊዜያት በኋላም ወንድ ልጅ ወለደች። እንደ ሥርዓቱም ሲጠመቅ የመጽሐፍ ስሙን “ሀብተ ማርያም” አሉት። በሕገ እግዚአብሔር አንጸው አሳደጉት። ወደ ቤተ ክርስቲያንም ሲወስዱት “እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ” የሚለውን ጸሎት ቢሰማ እጅጉን ወደዳት። እርሷንም ይዞ ከቤቱ ሌሊቱን የሚጸልይና የሚጋደል ሆነ።
አንድ ቀን የአባቱ በጎቹን ሲጠብቅ የበግ ጠባቂዎቹን “ዛሬ ዝናም ይዘንማልና እንግባ” አላቸው። እነርሱም “ምን ደመና አለ፤ ቀኑ ብራ ነው” አሉት። እርሱ ግን በጎቹን ይዞ ወደ ቤቱ እንደገባ ኃይለኛ፣ ነፋስና መብረቅ የቀላቀለ ዝናም ዘነመ። በሌላም ጊዜ እንዲሁ አንድ እረኛ የሀብተ ማርያምን በትሩን በጉልበት ነጠቀው። “መልስልኝ” ብሎ በስመ እግዚአብሔር ቢያምለውም እምቢ አለው። በተወው ጊዜ እግዚአብሔር ያን እረኛ በአየር ላይ ሠቅሎ አዋለው። እረኞቹም ሀብተ ማርያምን ሲለምኑት፣ እግዚአብሔር ነውና ስለ ስሙ ብሎ የቀጣው መሐሪው እርሱ ከወደደ ይማረው ሲል ያ እረኛ ተፈታና ወረደ። መጥቶም ከአባታችን እግር ስር ወደቀ፡፡ በኋላም ስሟ እለ አድባር ወደምትባል ገዳም ገብቶ ከአባ መልከ ጼዴቅ እጅ መነኰሶ ታላቅ ተጋድሎ ይጋደል ጀመር። በባሕር መካከልም በመቆም መዝሙረ ዳዊትን ይደግምና ግንባሩም የባሕሩን አሸዋ እስኪነካ 500 ጊዜ ይሰግዳል።
እህልም መቅመስን ትቶ የዱር ቅጠል የሚመገብ ሆነ። ዐርባ ዐርባ፣ ሰማንያ ሰማንያ ቀንም ያከፍላል። በሌሊትም ቁሞ በማደር በቀንም አራቱን ወንጌላት ዘወትር ይጸልያል። ተጋድሎውንም ያየ አምላካችን ተገለጠለት። አባ ሀብተ ማርያምም ከግርማው የተነሣ ደንግጦ በግንባሩ ተደፋ። ጌታችንም እፍ ብሉ አጽናንቶ አሥነሳውና ጽኑዕ ተጋድሎው በሰማያት መጻፉን ነገረው፡፡ ስለ ድንግልናው፣ ስለ ምናኔው፣ ስለ ፍጹም ምንኲስናው፣ አራቱን ወንጌላት አዘውትሮ በማንበቡ፣ ረኃብና ጥምን በመታገሡ፣ በልቡ ቂምንና በቀልን ባለማኖሩ፣ ስለ ንጹሕ የክህነት አገልግሎቱና በንጽሕና ስለሚያሣርገው መሥዋዕቱ ሰባት እጅግ የሚያስደንቁ አክሊላትንም አቀዳጀው። የቅዱስ ማቴዎስንና የቅዱስ ማርቆስን ወንጌል ሲያነብ ከሌሎች ሥውራን አበው ጋር የሚገናኝበትን የብርሃን ሠረገላ ሰጠው፡፡
የቅዱስ ሉቃስንና የቅዱስ ዮሐንስን ወንጌል ሲያነብም ሥጋውን ደሙን ለመቀበል ወደ ኢየሩሳሌም የሚሄድበትን የእሳት ሠረገላ ሰጠውና ቃል ኪዳን ገባለት። መታሰቢያውን ለሚያደርጉና በስሙ ለሚዘክሩ፣ ከእነርሱ ጋር የሚኖርበትን አምስት መቶ የወርቅ አምዶች ያሏትን ቦታ ሰጠሁህ አለው። ቅዱሳን መላእክት ሁሉ እየተደሰቱ አባታችን አቡነ ሐብተ ማርያምን “ወንድማችን ወደማያልቀው ሰማያዊ ደስታ ልንወስድህ መጥተናል” አሉት። ይህንንም በተናገረ ጊዜ ጌታችን በሦስትነቱ ተገልጦ ታየው። በኅዳር 26 ቀን ነፍሱ ከሥጋው በሰላም ተለየች። ቅዱሳን መላእክትም በታላቅ ደስታ እያመሰገኑ አሣረጓት። ገዳማውያን የዓለምን ክብር ንቀው ሔደዋልና ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፡፡ በዓታቸውን እናጽና ገዳማቸውን እንደግፍ የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
በነገሥታት ፊት የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት መሰከረ።
በምጽዋትና በስገድት የምትጋደለው እናቱ ዮስቴና ሀብቷን ሁሉ ለድሆች ሰጥታ ለምናኔ ወደ በረኃ ሄደች። በዚያ ያገኘችው ባሕታዊም በመንፈስ ቅዱስ ተገልጦለት ከእርሷ ቅዱስ ፍሬ እንደሚወጣ ነግሮ ወደ ዓለም እንድትመለስ አዘዛት። እርሷም “እግዚአብሔር የወደደው ይሁን” ብላ እያመሰገነች ተመልሰች፡፡ የአባቱ የትውልድ ሀገር የራውዕይ በምትባል ሀገር ሲሆን ከዚህች የተባረከች ሴት ጋር ተጋባ። እርሷም በበጎ ምግባርና ሥራ የተጌጠች፣ በሕግ ተወስና በጾም፣ በጸሎት፣ የምትተጋ ነበረች። ከጥቂት ጊዜያት በኋላም ወንድ ልጅ ወለደች። እንደ ሥርዓቱም ሲጠመቅ የመጽሐፍ ስሙን “ሀብተ ማርያም” አሉት። በሕገ እግዚአብሔር አንጸው አሳደጉት። ወደ ቤተ ክርስቲያንም ሲወስዱት “እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ” የሚለውን ጸሎት ቢሰማ እጅጉን ወደዳት። እርሷንም ይዞ ከቤቱ ሌሊቱን የሚጸልይና የሚጋደል ሆነ።
አንድ ቀን የአባቱ በጎቹን ሲጠብቅ የበግ ጠባቂዎቹን “ዛሬ ዝናም ይዘንማልና እንግባ” አላቸው። እነርሱም “ምን ደመና አለ፤ ቀኑ ብራ ነው” አሉት። እርሱ ግን በጎቹን ይዞ ወደ ቤቱ እንደገባ ኃይለኛ፣ ነፋስና መብረቅ የቀላቀለ ዝናም ዘነመ። በሌላም ጊዜ እንዲሁ አንድ እረኛ የሀብተ ማርያምን በትሩን በጉልበት ነጠቀው። “መልስልኝ” ብሎ በስመ እግዚአብሔር ቢያምለውም እምቢ አለው። በተወው ጊዜ እግዚአብሔር ያን እረኛ በአየር ላይ ሠቅሎ አዋለው። እረኞቹም ሀብተ ማርያምን ሲለምኑት፣ እግዚአብሔር ነውና ስለ ስሙ ብሎ የቀጣው መሐሪው እርሱ ከወደደ ይማረው ሲል ያ እረኛ ተፈታና ወረደ። መጥቶም ከአባታችን እግር ስር ወደቀ፡፡ በኋላም ስሟ እለ አድባር ወደምትባል ገዳም ገብቶ ከአባ መልከ ጼዴቅ እጅ መነኰሶ ታላቅ ተጋድሎ ይጋደል ጀመር። በባሕር መካከልም በመቆም መዝሙረ ዳዊትን ይደግምና ግንባሩም የባሕሩን አሸዋ እስኪነካ 500 ጊዜ ይሰግዳል።
እህልም መቅመስን ትቶ የዱር ቅጠል የሚመገብ ሆነ። ዐርባ ዐርባ፣ ሰማንያ ሰማንያ ቀንም ያከፍላል። በሌሊትም ቁሞ በማደር በቀንም አራቱን ወንጌላት ዘወትር ይጸልያል። ተጋድሎውንም ያየ አምላካችን ተገለጠለት። አባ ሀብተ ማርያምም ከግርማው የተነሣ ደንግጦ በግንባሩ ተደፋ። ጌታችንም እፍ ብሉ አጽናንቶ አሥነሳውና ጽኑዕ ተጋድሎው በሰማያት መጻፉን ነገረው፡፡ ስለ ድንግልናው፣ ስለ ምናኔው፣ ስለ ፍጹም ምንኲስናው፣ አራቱን ወንጌላት አዘውትሮ በማንበቡ፣ ረኃብና ጥምን በመታገሡ፣ በልቡ ቂምንና በቀልን ባለማኖሩ፣ ስለ ንጹሕ የክህነት አገልግሎቱና በንጽሕና ስለሚያሣርገው መሥዋዕቱ ሰባት እጅግ የሚያስደንቁ አክሊላትንም አቀዳጀው። የቅዱስ ማቴዎስንና የቅዱስ ማርቆስን ወንጌል ሲያነብ ከሌሎች ሥውራን አበው ጋር የሚገናኝበትን የብርሃን ሠረገላ ሰጠው፡፡
የቅዱስ ሉቃስንና የቅዱስ ዮሐንስን ወንጌል ሲያነብም ሥጋውን ደሙን ለመቀበል ወደ ኢየሩሳሌም የሚሄድበትን የእሳት ሠረገላ ሰጠውና ቃል ኪዳን ገባለት። መታሰቢያውን ለሚያደርጉና በስሙ ለሚዘክሩ፣ ከእነርሱ ጋር የሚኖርበትን አምስት መቶ የወርቅ አምዶች ያሏትን ቦታ ሰጠሁህ አለው። ቅዱሳን መላእክት ሁሉ እየተደሰቱ አባታችን አቡነ ሐብተ ማርያምን “ወንድማችን ወደማያልቀው ሰማያዊ ደስታ ልንወስድህ መጥተናል” አሉት። ይህንንም በተናገረ ጊዜ ጌታችን በሦስትነቱ ተገልጦ ታየው። በኅዳር 26 ቀን ነፍሱ ከሥጋው በሰላም ተለየች። ቅዱሳን መላእክትም በታላቅ ደስታ እያመሰገኑ አሣረጓት። ገዳማውያን የዓለምን ክብር ንቀው ሔደዋልና ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፡፡ በዓታቸውን እናጽና ገዳማቸውን እንደግፍ የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
1 day ago
ጅቡቲ በዳመርጆግ የነዳጅ ማከማቻ ግንባታ ላይ የኢትዮጵያን ድጋፍና ተሳትፎ እየጠበቀች መሆኑን ገለጸች
የጅቡቲ ወደቦች እና ነፃ ቀጠናዎች ባለስልጣን በሀገሪቱ ደቡብ ምስራቅ በኩል በሚገኘው አዲሱ የዳመርጆግ ፈሳሽ ጭነት ወደብ ላይ የነዳጅ ማከማቻ ዴፖ ግንባታ ለመጀመር በበጀት ዓመቱ መጀመሪያ ላይ የኢትዮጵያን ተሳትፎና የገንዘብ ድጋፍ እየጠበቀ መሆኑን አስታውቋል።
የባለስልጣኑ ሰብሳቢ አቡበከር ኦማር ሀዲ ለካፒታል እንደገለፁት ፣ ዘመናዊው የነዳጅ ወደብ ወደ ስራ እንዲገባ የነዳጅ ማራገፊያ ዴፖ ግንባታ ይቀረዋል።
ለዚህም ባለስልጣኑ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ጋር ድርድር እያደረገ ሲሆን፣ ተቋሙ ሐምሌ 1 ቀን በሚጀምረው አዲስ የበጀት አመት በጀት አፀድቆ ለስራው እንደሚመጣ ይጠበቃል ሲሉ ነው የገለፁት።
Seledadotio
Seledadotio
የጅቡቲ ወደቦች እና ነፃ ቀጠናዎች ባለስልጣን በሀገሪቱ ደቡብ ምስራቅ በኩል በሚገኘው አዲሱ የዳመርጆግ ፈሳሽ ጭነት ወደብ ላይ የነዳጅ ማከማቻ ዴፖ ግንባታ ለመጀመር በበጀት ዓመቱ መጀመሪያ ላይ የኢትዮጵያን ተሳትፎና የገንዘብ ድጋፍ እየጠበቀ መሆኑን አስታውቋል።
የባለስልጣኑ ሰብሳቢ አቡበከር ኦማር ሀዲ ለካፒታል እንደገለፁት ፣ ዘመናዊው የነዳጅ ወደብ ወደ ስራ እንዲገባ የነዳጅ ማራገፊያ ዴፖ ግንባታ ይቀረዋል።
ለዚህም ባለስልጣኑ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ጋር ድርድር እያደረገ ሲሆን፣ ተቋሙ ሐምሌ 1 ቀን በሚጀምረው አዲስ የበጀት አመት በጀት አፀድቆ ለስራው እንደሚመጣ ይጠበቃል ሲሉ ነው የገለፁት።
Seledadotio
Seledadotio
1 day ago
የአቡነ ሀብተ ማርያም ምልጃ እና ረድኤት አይለየን🙏
በነገሥታት ፊት የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት መሰከረ።
የአባቱ የትውልድ ሀገር የራውዕይ በምትባል ሀገር ሲሆን ሀብቷን ሁሉ ለድሆች ሰጥታ ለምናኔ ገዳም ስትገባ የተቀደሰ ልጅ እንደምትወልድ ተነግሯት የተመለሰችው እናቱ ዮስቲና ትባላለች። ልጅም ሲወልዱ የመጽሐፍ ስሙን “ሀብተ ማርያም” አሉት። በሕገ እግዚአብሔርም አንጸው አሳደጉት።
በቤተ ክርስቲያንም የሰማውን “እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ” የምትል ጸሎት እጅጉን ቢወዳት ሌሊቱን ሙሉ በቤቱ እየጸለያት የሚጋደል ሆነ። አንድ ቀን የአባቱ በጎቹን ሲጠብቅ ጓደኞቹን “ዝናም ይዘንማልና ወደቤት እንግባ” አላቸው። ቃሉን ሊሰሙት ባይወዱ በጎቹን ይዞ ወደ ቤቱ እንደገባ፣ ነፋስና መብረቅ የቀላቀለ ኃይለኛ ዝናም ዘነመ። ገና በአዳጊነት እድሜውም ብዙ ተአምራት ያደርግ ነበር፡፡
በኋላም ስሟ እለ አድባር ወደምትባል ገዳም ገብቶ ከአባ መልከ ጼዴቅ እጅ መነኰሶ ታላቅ ተጋድሎ ይጋደል ጀመር። በባሕር መካከልም በመቆም መዝሙረ ዳዊትን ይደግምና ግንባሩም የባሕሩን አሸዋ እስኪነካ 500 ጊዜ ይሰግዳል። እህልም መቅመስን ትቶ የዱር ቅጠል የሚመገብ ሆነ። ዐርባ ዐርባ፣ ሰማንያ ሰማንያ ቀንም ያከፍላል። በሌሊትም ቁሞ በማደር በቀንም አራቱን ወንጌላት ዘወትር ይጸልያል። ተጋድሎውንም ያየ ጌታችን ተገለጠለት። አቡነ ሀብተ ማርያምም ከግርማው የተነሣ ደንግጦ በግንባሩ ተደፋ። ጌታችንም እፍ ብሉ አጽናንቶ አሥነሳውና ጽኑዕ ተጋድሎው በሰማያት መጻፉን ነገረው፡፡
ስለ ድንግልናው፣ ስለ ምናኔው፣ ስለ ፍጹም ምንኲስናው፣ አራቱን ወንጌላት አዘውትሮ ስለማንበቡ፣ ስለተጋድሎው፣ ስለ ንጹሕ የክህነት አገልግሎቱና በንጽሕና ስለሚያሣርገው መሥዋዕቱ ሰባት እጅግ የሚያስደንቁ አክሊላትንም አቀዳጀው። ከሥውራን አበው ጋር የሚገናኝበትንና ሥጋውን ደሙን ለመቀበል ወደ ኢየሩሳሌም የሚሄድበትን የብርሃን ሠረገላም ሰጠው፣ መታሰቢያውን የሚያደርጉትን እንደሚምርለትም፣ ቃል ኪዳን ገባለት። በኅዳር 26 ቀን ነፍሱ ከሥጋው ስትለይም ቅዱሳን መላእክትም በታላቅ ደስታ አሣረጓት። ገዳማውያን የዓለምን ክብር ንቀው ሔደዋልና ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፤ ገዳማቸውን እንደግፍ ከበረከታቸውም እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
በነገሥታት ፊት የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት መሰከረ።
የአባቱ የትውልድ ሀገር የራውዕይ በምትባል ሀገር ሲሆን ሀብቷን ሁሉ ለድሆች ሰጥታ ለምናኔ ገዳም ስትገባ የተቀደሰ ልጅ እንደምትወልድ ተነግሯት የተመለሰችው እናቱ ዮስቲና ትባላለች። ልጅም ሲወልዱ የመጽሐፍ ስሙን “ሀብተ ማርያም” አሉት። በሕገ እግዚአብሔርም አንጸው አሳደጉት።
በቤተ ክርስቲያንም የሰማውን “እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ” የምትል ጸሎት እጅጉን ቢወዳት ሌሊቱን ሙሉ በቤቱ እየጸለያት የሚጋደል ሆነ። አንድ ቀን የአባቱ በጎቹን ሲጠብቅ ጓደኞቹን “ዝናም ይዘንማልና ወደቤት እንግባ” አላቸው። ቃሉን ሊሰሙት ባይወዱ በጎቹን ይዞ ወደ ቤቱ እንደገባ፣ ነፋስና መብረቅ የቀላቀለ ኃይለኛ ዝናም ዘነመ። ገና በአዳጊነት እድሜውም ብዙ ተአምራት ያደርግ ነበር፡፡
በኋላም ስሟ እለ አድባር ወደምትባል ገዳም ገብቶ ከአባ መልከ ጼዴቅ እጅ መነኰሶ ታላቅ ተጋድሎ ይጋደል ጀመር። በባሕር መካከልም በመቆም መዝሙረ ዳዊትን ይደግምና ግንባሩም የባሕሩን አሸዋ እስኪነካ 500 ጊዜ ይሰግዳል። እህልም መቅመስን ትቶ የዱር ቅጠል የሚመገብ ሆነ። ዐርባ ዐርባ፣ ሰማንያ ሰማንያ ቀንም ያከፍላል። በሌሊትም ቁሞ በማደር በቀንም አራቱን ወንጌላት ዘወትር ይጸልያል። ተጋድሎውንም ያየ ጌታችን ተገለጠለት። አቡነ ሀብተ ማርያምም ከግርማው የተነሣ ደንግጦ በግንባሩ ተደፋ። ጌታችንም እፍ ብሉ አጽናንቶ አሥነሳውና ጽኑዕ ተጋድሎው በሰማያት መጻፉን ነገረው፡፡
ስለ ድንግልናው፣ ስለ ምናኔው፣ ስለ ፍጹም ምንኲስናው፣ አራቱን ወንጌላት አዘውትሮ ስለማንበቡ፣ ስለተጋድሎው፣ ስለ ንጹሕ የክህነት አገልግሎቱና በንጽሕና ስለሚያሣርገው መሥዋዕቱ ሰባት እጅግ የሚያስደንቁ አክሊላትንም አቀዳጀው። ከሥውራን አበው ጋር የሚገናኝበትንና ሥጋውን ደሙን ለመቀበል ወደ ኢየሩሳሌም የሚሄድበትን የብርሃን ሠረገላም ሰጠው፣ መታሰቢያውን የሚያደርጉትን እንደሚምርለትም፣ ቃል ኪዳን ገባለት። በኅዳር 26 ቀን ነፍሱ ከሥጋው ስትለይም ቅዱሳን መላእክትም በታላቅ ደስታ አሣረጓት። ገዳማውያን የዓለምን ክብር ንቀው ሔደዋልና ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፤ ገዳማቸውን እንደግፍ ከበረከታቸውም እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
1 day ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የሪፐብሊካን ፓርቲው የአሜሪካ ምክር ቤት አባል ቶማስ ማሲ መንግስታቸው ለእስራኤል እያደረገ ያለውን የገንዘብ ድጋፍ አጥብቀው የተቹ ሲሆን፣ በፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና በእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ መካከል ተፈጥሯል የተባለውን የከረረ የቃላት ልውውጥ "ባዶ ወሬ ነው" ሲሉ አጣጥለውታል።
ህግ አውጭው በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት ጽሁፍ፣ "ሁሉ ነገር ወሬ ነው። ለእስራኤል የሚሰጠውን የውጭ እርዳታ ለአንድ ወር ብቻ ብታቋርጡት ጎረቤቶቻቸውን በቦምብ መደብደብ ያቆማሉ። ያኔ ፈጣን ሰላም ይመጣል፣ የሆርሙዝ ስትሬት (የባህር በር) ክፍት ይሆናል፣ እንዲሁም የነዳጅ ዋጋ በአንድ ጋሎን 2 ዶላር ይቀንሳል" ብለዋል።
አክለውም "እስራኤል ከአሜሪካ ግብር ከፋዮች ከፍተኛውን የእርዳታ ገንዘብ የምትቀበል ሀገር ሆና ቆይታለች፤ አሁንም ያንኑ በመቀጠል ላይ ትገኛለች" ሲሉ የሀገራቸውን የውጭ ፖሊሲ አጥብቀው ተችተዋል።
ህግ አውጭው በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት ጽሁፍ፣ "ሁሉ ነገር ወሬ ነው። ለእስራኤል የሚሰጠውን የውጭ እርዳታ ለአንድ ወር ብቻ ብታቋርጡት ጎረቤቶቻቸውን በቦምብ መደብደብ ያቆማሉ። ያኔ ፈጣን ሰላም ይመጣል፣ የሆርሙዝ ስትሬት (የባህር በር) ክፍት ይሆናል፣ እንዲሁም የነዳጅ ዋጋ በአንድ ጋሎን 2 ዶላር ይቀንሳል" ብለዋል።
አክለውም "እስራኤል ከአሜሪካ ግብር ከፋዮች ከፍተኛውን የእርዳታ ገንዘብ የምትቀበል ሀገር ሆና ቆይታለች፤ አሁንም ያንኑ በመቀጠል ላይ ትገኛለች" ሲሉ የሀገራቸውን የውጭ ፖሊሲ አጥብቀው ተችተዋል።
2 days ago
በአዲስ አበባ ስታዲየም :
የዊ ሻምፒዮንስ ( We Champions 2026 )
የስፖርት ፌስቲቫል እየተሰናዳ ነው
#ethiopia | የአርሰናል እግር ኳስ ክለብ ከ22 ዓመታት ረጅም የጥበቃ ጊዜ በኋላ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ማሸነፉን አስመልክቶ፣ ይህንን ታሪካዊ ድል ለማክበር የተሰናዳውና በሀገራችን የመጀመሪያው ግዙፍ የስፖርት መድረክ የሆነው የዊ ሻምፒዮንስ 2026 ( We Champions 2026 ) የእግር ኳስ ፌስቲቫል በመጪው ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ስታዲየም በታላቅ ድምቀት እንደሚከናወን ተጠቁሟል።
በጎርደን ኢንተርቴይመንት አዘጋጅነት ለሚቀርበው ለዚህ ትልቅ ሁነት አዋሽ ባንክ በአፕክስ ኖብል ፕሮግራሙ አማካኝነት ዋነኛ ስፖንሰር በመሆን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል።
ይህ ልዩ መርሃ ግብር የስፖርቱን ፍቅር፣ ታማኝነትን፣ ባህልን፣ መዝናኛንና ስፖርታዊ እሴቶችን በአንድ ላይ በማስተሳሰር ከ30 ሺህ በላይ የእግር ኳስ አፍቃሪያንን፣ የዓለም አቀፍ ስፖርት ተዋናዮችንና እውቅ ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ ላይ የሚሰበስብ ሀገራዊ ፋይዳ ያለው የደስታ መግለጫ እንደሚሆን ይጠበቃል።
ዝግጅቱ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ በበለጠ ለማስተዋወቅ መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ሲሆን፣ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ የስፖርት መገናኛ ብዙኃንንና የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎችን ትኩረት በመሳብ የሀገሪቱን የቱሪዝም ፍሰት፣ የባህል ገጽታ እንዲሁም ትላልቅ ዓለም አቀፍ ኩነቶችን የማስተናገድ ብቃት በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳድግ ታምኖበታል።
በዕለቱ ከሚታደሙት የክብር እንግዶች መካከል የቀድሞው የአርሰናልና የቱኒዥያ ብሔራዊ ቡድን ተከላካይ ራዲ ጃይዲ የሚገኝበት ሲሆን፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ተደራሽነትና ተፅዕኖ ካላቸው የእግር ኳስ ሚዲያ አንዱ የሆነው የኤኤፍቲቪ መስራቾችና ተወካዮችም በዝግጅቱ ላይ ለመሳተፍ ወደ አዲስ አበባ እንደሚመጡ መረጋገጡን በመግለጫው ላይ አስታውቀዋል።
ወደ ስታዲየም ለመግባት የሚያስችሉ የትኬት ሽያጮችን አስመልክቶ አዘጋጆቹ በሰጡት ማብራሪያ፣ መግቢያ ትኬቶችን ማግኘት የሚቻለው በአዋሽ ባንክ የአፕክስ ኖብል ፕሮግራም በኩል ብቻ መሆኑን ገልጸዋል።
የመዝናኛ ክፍሉን ይበልጥ ማራኪና ድምቅ ለማድረግ ከአስር በላይ ታዋቂና ወጣት የሙዚቃ አርቲስቶች የተጋበዙ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል ታደለ ሮባ፣ ልጅ ሚካኤል (ፋፍ)፣ ሳሚ ዳን፣ አስማማው እሸቱ፣ ራሄል ጌቱ፣ ሮማን ማይክ፣ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ሚካ ያኖ፣ አማኑኤል የማነ፣ አዲስ ሙላት፣ እዩ ፀጋ እና ኩሉ ሱሌ ይገኙበታል።
የአዲስ አበባ ስታዲየም ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ ለታዳሚዎች ክፍት የሚሆን በመሆኑ፣ ተመልካቾች በጊዜ በመገኘት ቦታቸውን እንዲይዙ አዘጋጆቹ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
#wechampions2026 #arsenal #awashbank #apexnoble #gordonentertainment #aftv #radhijaidi #footballfestival #ethiopiantourism #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
የዊ ሻምፒዮንስ ( We Champions 2026 )
የስፖርት ፌስቲቫል እየተሰናዳ ነው
#ethiopia | የአርሰናል እግር ኳስ ክለብ ከ22 ዓመታት ረጅም የጥበቃ ጊዜ በኋላ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ማሸነፉን አስመልክቶ፣ ይህንን ታሪካዊ ድል ለማክበር የተሰናዳውና በሀገራችን የመጀመሪያው ግዙፍ የስፖርት መድረክ የሆነው የዊ ሻምፒዮንስ 2026 ( We Champions 2026 ) የእግር ኳስ ፌስቲቫል በመጪው ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ስታዲየም በታላቅ ድምቀት እንደሚከናወን ተጠቁሟል።
በጎርደን ኢንተርቴይመንት አዘጋጅነት ለሚቀርበው ለዚህ ትልቅ ሁነት አዋሽ ባንክ በአፕክስ ኖብል ፕሮግራሙ አማካኝነት ዋነኛ ስፖንሰር በመሆን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል።
ይህ ልዩ መርሃ ግብር የስፖርቱን ፍቅር፣ ታማኝነትን፣ ባህልን፣ መዝናኛንና ስፖርታዊ እሴቶችን በአንድ ላይ በማስተሳሰር ከ30 ሺህ በላይ የእግር ኳስ አፍቃሪያንን፣ የዓለም አቀፍ ስፖርት ተዋናዮችንና እውቅ ባለሙያዎችን በአንድ መድረክ ላይ የሚሰበስብ ሀገራዊ ፋይዳ ያለው የደስታ መግለጫ እንደሚሆን ይጠበቃል።
ዝግጅቱ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ በበለጠ ለማስተዋወቅ መልካም አጋጣሚን የሚፈጥር ሲሆን፣ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ የስፖርት መገናኛ ብዙኃንንና የዲጂታል ይዘት ፈጣሪዎችን ትኩረት በመሳብ የሀገሪቱን የቱሪዝም ፍሰት፣ የባህል ገጽታ እንዲሁም ትላልቅ ዓለም አቀፍ ኩነቶችን የማስተናገድ ብቃት በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሳድግ ታምኖበታል።
በዕለቱ ከሚታደሙት የክብር እንግዶች መካከል የቀድሞው የአርሰናልና የቱኒዥያ ብሔራዊ ቡድን ተከላካይ ራዲ ጃይዲ የሚገኝበት ሲሆን፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ተደራሽነትና ተፅዕኖ ካላቸው የእግር ኳስ ሚዲያ አንዱ የሆነው የኤኤፍቲቪ መስራቾችና ተወካዮችም በዝግጅቱ ላይ ለመሳተፍ ወደ አዲስ አበባ እንደሚመጡ መረጋገጡን በመግለጫው ላይ አስታውቀዋል።
ወደ ስታዲየም ለመግባት የሚያስችሉ የትኬት ሽያጮችን አስመልክቶ አዘጋጆቹ በሰጡት ማብራሪያ፣ መግቢያ ትኬቶችን ማግኘት የሚቻለው በአዋሽ ባንክ የአፕክስ ኖብል ፕሮግራም በኩል ብቻ መሆኑን ገልጸዋል።
የመዝናኛ ክፍሉን ይበልጥ ማራኪና ድምቅ ለማድረግ ከአስር በላይ ታዋቂና ወጣት የሙዚቃ አርቲስቶች የተጋበዙ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል ታደለ ሮባ፣ ልጅ ሚካኤል (ፋፍ)፣ ሳሚ ዳን፣ አስማማው እሸቱ፣ ራሄል ጌቱ፣ ሮማን ማይክ፣ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ሚካ ያኖ፣ አማኑኤል የማነ፣ አዲስ ሙላት፣ እዩ ፀጋ እና ኩሉ ሱሌ ይገኙበታል።
የአዲስ አበባ ስታዲየም ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ ለታዳሚዎች ክፍት የሚሆን በመሆኑ፣ ተመልካቾች በጊዜ በመገኘት ቦታቸውን እንዲይዙ አዘጋጆቹ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
#wechampions2026 #arsenal #awashbank #apexnoble #gordonentertainment #aftv #radhijaidi #footballfestival #ethiopiantourism #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 days ago
የንግድ ድንበሮችን በመሻገር የአፍሪካን ገበያ ይቆጣጠሩ!
የኢትዮጵያን የቢዝነስ መሪዎች፣ ሥራ አስኪያጆች እና ባለሀብቶች ከሩዋንዳ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሾች ጋር የሚያገናኘው ታላቁ የኢትዮጵያ - ሩዋንዳ ቢዝነስ ፎረም 2026 ምዝገባ ጀምሯል። ይህ የ4 ቀናት የቢዝነስ ጉዞ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድ ልውውጥ ለማሳደግ እና አዲስ የኢንቨስትመንት አድማስ ለመክፈት ታስቦ የተዘጋጀ ልዩ መድረክ ነው።
በፎረሙ ላይ በመሳተፍዎ ምን ያተርፋሉ?
• 🤝 አስቀድመው የተመቻቹ እና ያተኮሩ የB2B (የንግድ ለንግድ) ስብሰባዎች
• 🎯 ከታዋቂ ባለሀብቶች እና ዋና የንግድ ውሳኔ ሰጪዎች ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት
• 📈 ወደ ሩዋንዳ ገበያ በምቾት ለመግባት የሚያስችል ስትራቴጂካዊ ድጋፍ እና የተግባር የመስክ ምልከታ (Site Visits)
•በዛውም በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ የሩዋንዳ ኤግዚቢሽን ላይ ይሳተፋሉ
ዋና ዋና የትኩረት ዘርፎች፦
ግብርና ማቀነባበሪያ (Agro-Processing) | ሪል ስቴት እና ኮንስትራክሽን | ቱሪዝም እና ሆስፒታሊቲ | አይሲቲ እና ኢኖቬሽን | ማኑፋክቸሪንግ (ማምረቻ ዘርፍ)
📅 ቀን፦ hamele 21-24፣ 2018 ዓ.ም (july 28–31, 2026)
📍 ቦታ፦ ኪጋሊ ፣ ሩዋንዳ (Kigali, Rwanda)
⏱️ ቆይታ፦ 4 ቀናት የንግድ ተልዕኮ
የመቀመጫዎች ብዛት በጣም ውስን ስለሆነ አሁኑኑ ይመዝገቡ! 📞 ስልክ ቁጥር፦ +251 911874859/0913174052
📧 ኢሜይል፦ infoalohavistaevents.com
🌐 ድረ-ገጽ፦ www.alohavistaevents.com
በኢትዮጵያ የፌዴራል ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኤምባሲ (ኪጋሊ) እና በሩዋንዳ ልማት ቦርድ (RDB) ትብብር የተዘጋጀ።
የኢትዮጵያን የቢዝነስ መሪዎች፣ ሥራ አስኪያጆች እና ባለሀብቶች ከሩዋንዳ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሾች ጋር የሚያገናኘው ታላቁ የኢትዮጵያ - ሩዋንዳ ቢዝነስ ፎረም 2026 ምዝገባ ጀምሯል። ይህ የ4 ቀናት የቢዝነስ ጉዞ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድ ልውውጥ ለማሳደግ እና አዲስ የኢንቨስትመንት አድማስ ለመክፈት ታስቦ የተዘጋጀ ልዩ መድረክ ነው።
በፎረሙ ላይ በመሳተፍዎ ምን ያተርፋሉ?
• 🤝 አስቀድመው የተመቻቹ እና ያተኮሩ የB2B (የንግድ ለንግድ) ስብሰባዎች
• 🎯 ከታዋቂ ባለሀብቶች እና ዋና የንግድ ውሳኔ ሰጪዎች ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት
• 📈 ወደ ሩዋንዳ ገበያ በምቾት ለመግባት የሚያስችል ስትራቴጂካዊ ድጋፍ እና የተግባር የመስክ ምልከታ (Site Visits)
•በዛውም በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ የሩዋንዳ ኤግዚቢሽን ላይ ይሳተፋሉ
ዋና ዋና የትኩረት ዘርፎች፦
ግብርና ማቀነባበሪያ (Agro-Processing) | ሪል ስቴት እና ኮንስትራክሽን | ቱሪዝም እና ሆስፒታሊቲ | አይሲቲ እና ኢኖቬሽን | ማኑፋክቸሪንግ (ማምረቻ ዘርፍ)
📅 ቀን፦ hamele 21-24፣ 2018 ዓ.ም (july 28–31, 2026)
📍 ቦታ፦ ኪጋሊ ፣ ሩዋንዳ (Kigali, Rwanda)
⏱️ ቆይታ፦ 4 ቀናት የንግድ ተልዕኮ
የመቀመጫዎች ብዛት በጣም ውስን ስለሆነ አሁኑኑ ይመዝገቡ! 📞 ስልክ ቁጥር፦ +251 911874859/0913174052
📧 ኢሜይል፦ infoalohavistaevents.com
🌐 ድረ-ገጽ፦ www.alohavistaevents.com
በኢትዮጵያ የፌዴራል ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኤምባሲ (ኪጋሊ) እና በሩዋንዳ ልማት ቦርድ (RDB) ትብብር የተዘጋጀ።
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በአሁኑ ወቅት ወደ ሩብ (25 በመቶ) የሚጠጋው የኢትዮጵያ መሬት ለጉዳት እና ለመራቆት መዳረጉን አንድ አዲስ የጥናት ሪፖርት አመለከተ። ይህንን ችግር ለመቅረፍ ማህበረሰቡን ያሳተፉ እና አነስተኛ ወጪ የሚጠይቁ መፍትሔዎች ተስፋ ሰጪ ውጤት እያሳዩ መሆኑ ተገልጿል።
ከ25 ዓመታት በላይ ልምድ ባላቸው ከፍተኛ ተመራማሪ ወልዴ መኩሪያ የቀረበው ይህ ጽሁፍ እንደሚያመለክተው፣ መሬቱ ሰብል የማብቀል፣ ዕፅዋትን የመሸከም እና ውሃ የመያዝ ጥራቱን እያጣ ይገኛል። ለዚህ ችግር በዋነኛነት የደን መጨፍጨፍ፣ ከመጠን በላይ መጠቀም እና ደካማ የመሬት አያያዝ የመሳሰሉ የሰው ሰራሽ ጫናዎች በምክንያትነት ይጠቀሳሉ። በተጨማሪም ከባድ ዝናብ የሚያስከትለው የአፈር መሸርሸር እና የአየር ንብረት መለዋወጥ የመሳሰሉ ተፈጥሯዊ ምክንያቶች ከፍተኛ አስተዋጽኦ አላቸው። የዚህ መዘዝ የግብርና ምርታማነትን ከመቀነስ ባለፈ፣ የከርሰ ምድር ውሃ መጠን እንዲቀንስ እና የተከማቸ ካርበን ወደ አየር በመለቀቅ የአየር ንብረት ለውጥን እንዲያባብስ አድርጓል።
ጥናቱ ሁለት ተፈጥሮን መሠረት ያደረጉ አነስተኛ ወጪ የሚጠይቁ መፍትሔዎችን በአማራጭነት አቅርቧል። የመጀመሪያው የተጎዱ መሬቶችን አጥሮ ከሰው እና ከእንስሳት ንክኪ ነፃ ማድረግ ሲሆን፣ ይህም መሬቱ በአምስት ዓመታት አጭር ጊዜ ውስጥ በተፈጥሮው እራሱን መልሶ እንዲያድን ያስችለዋል። ይህ አሰራር የአፈር መሸርሸርን የሚቀንስ፣ የካርበን ክምችትን በመጨመር ብዝሃ ሕይወትን የሚያጎለብት እና ማህበረሰቡን ከድርቅ እና ከጎርፍ የሚጠብቅ ነው። በሰሜን ኢትዮጵያ ትግራይ ክልል በተደረገ ጥናት፣ ለ20 ዓመታት በታጠሩ መሬቶች ላይ ከፍተኛ የካርበን ክምችት መጨመሩ ተረጋግጧል።
ሁለተኛው መፍትሔ የጎርፍ መፋሰሻዎችን እና ስምጥ ሸለቆዎችን መልሶ ማልማት ነው። በደቡብ ኢትዮጵያ በተደረገ ሙከራ፣ ጥልቅ የጎርፍ መፋሰሻዎችን በአካባቢው በሚገኙ አፈር፣ ድንጋይ፣ ሣር እና ዛፎች በመጠቀም በአነስተኛ ወጪ መሙላት ተችሏል። በውሃ መፋሰሻዎቹ ላይ የውሃውን ፍጥነት የሚቀንሱ ትናንሽ ግድቦችን መስራት ሌላኛው ውጤታማ ዘዴ መሆኑ ታይቷል። ይህ አሰራር ውድ የሆኑ ማሽነሪዎችን የማይጠይቅ ሲሆን፣ አብዛኛው ስራ በዶማ እና በሜንጫ ብቻ የሚሰራ በመሆኑ አንድ ሄክታር መሬት ለማልማት ከ600 እስከ 800 የአሜሪካ ዶላር ብቻ ወጪ ይጠይቃል።
በኢትዮጵያ ውስጥ 90 በመቶ የሚሆነውን የሀገሪቱን ሰብል የሚያመርቱ ከ15 ሚሊዮን በላይ አነስተኛ አርሶ አደሮች ይገኛሉ። መሬትን መልሶ የማልማቱ ስራ ውጤታማ የሚሆነው ማህበረሰቡ በጋራ ሲያቅድ፣ አካላዊ ስራውን ሲሰራ እና የረጅም ጊዜ ቁርጠኝነት ሲኖረው ብቻ መሆኑን የጥናቱ ውጤት አረጋግጧል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2011 በገባችው ቃል መሠረት እስከ 2030 ድረስ 7 ሚሊዮን ሄክታር የተጎዳ መሬት መልሶ ለማልማት አቅዳ እስካሁን 4.2 ሚሊዮን ሄክታር ማልማት ችላለች። በተጨማሪም እንደ ሀገራዊ የአየር ንብረት ስትራቴጂ አካል ተጨማሪ 15 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ለማልማት ቃል መግባቷን ሪፖርቱ አትቷል። ትክክለኛ ፖሊሲዎች እና ተከታታይ የፋይናንስ ድጋፍ ካለ እነዚህ አካሄዶች መሬትን ከመታደግ ባለፈ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም ትልቅ አቅም እንደሚፈጥሩ ተመላክቷል።
ከ25 ዓመታት በላይ ልምድ ባላቸው ከፍተኛ ተመራማሪ ወልዴ መኩሪያ የቀረበው ይህ ጽሁፍ እንደሚያመለክተው፣ መሬቱ ሰብል የማብቀል፣ ዕፅዋትን የመሸከም እና ውሃ የመያዝ ጥራቱን እያጣ ይገኛል። ለዚህ ችግር በዋነኛነት የደን መጨፍጨፍ፣ ከመጠን በላይ መጠቀም እና ደካማ የመሬት አያያዝ የመሳሰሉ የሰው ሰራሽ ጫናዎች በምክንያትነት ይጠቀሳሉ። በተጨማሪም ከባድ ዝናብ የሚያስከትለው የአፈር መሸርሸር እና የአየር ንብረት መለዋወጥ የመሳሰሉ ተፈጥሯዊ ምክንያቶች ከፍተኛ አስተዋጽኦ አላቸው። የዚህ መዘዝ የግብርና ምርታማነትን ከመቀነስ ባለፈ፣ የከርሰ ምድር ውሃ መጠን እንዲቀንስ እና የተከማቸ ካርበን ወደ አየር በመለቀቅ የአየር ንብረት ለውጥን እንዲያባብስ አድርጓል።
ጥናቱ ሁለት ተፈጥሮን መሠረት ያደረጉ አነስተኛ ወጪ የሚጠይቁ መፍትሔዎችን በአማራጭነት አቅርቧል። የመጀመሪያው የተጎዱ መሬቶችን አጥሮ ከሰው እና ከእንስሳት ንክኪ ነፃ ማድረግ ሲሆን፣ ይህም መሬቱ በአምስት ዓመታት አጭር ጊዜ ውስጥ በተፈጥሮው እራሱን መልሶ እንዲያድን ያስችለዋል። ይህ አሰራር የአፈር መሸርሸርን የሚቀንስ፣ የካርበን ክምችትን በመጨመር ብዝሃ ሕይወትን የሚያጎለብት እና ማህበረሰቡን ከድርቅ እና ከጎርፍ የሚጠብቅ ነው። በሰሜን ኢትዮጵያ ትግራይ ክልል በተደረገ ጥናት፣ ለ20 ዓመታት በታጠሩ መሬቶች ላይ ከፍተኛ የካርበን ክምችት መጨመሩ ተረጋግጧል።
ሁለተኛው መፍትሔ የጎርፍ መፋሰሻዎችን እና ስምጥ ሸለቆዎችን መልሶ ማልማት ነው። በደቡብ ኢትዮጵያ በተደረገ ሙከራ፣ ጥልቅ የጎርፍ መፋሰሻዎችን በአካባቢው በሚገኙ አፈር፣ ድንጋይ፣ ሣር እና ዛፎች በመጠቀም በአነስተኛ ወጪ መሙላት ተችሏል። በውሃ መፋሰሻዎቹ ላይ የውሃውን ፍጥነት የሚቀንሱ ትናንሽ ግድቦችን መስራት ሌላኛው ውጤታማ ዘዴ መሆኑ ታይቷል። ይህ አሰራር ውድ የሆኑ ማሽነሪዎችን የማይጠይቅ ሲሆን፣ አብዛኛው ስራ በዶማ እና በሜንጫ ብቻ የሚሰራ በመሆኑ አንድ ሄክታር መሬት ለማልማት ከ600 እስከ 800 የአሜሪካ ዶላር ብቻ ወጪ ይጠይቃል።
በኢትዮጵያ ውስጥ 90 በመቶ የሚሆነውን የሀገሪቱን ሰብል የሚያመርቱ ከ15 ሚሊዮን በላይ አነስተኛ አርሶ አደሮች ይገኛሉ። መሬትን መልሶ የማልማቱ ስራ ውጤታማ የሚሆነው ማህበረሰቡ በጋራ ሲያቅድ፣ አካላዊ ስራውን ሲሰራ እና የረጅም ጊዜ ቁርጠኝነት ሲኖረው ብቻ መሆኑን የጥናቱ ውጤት አረጋግጧል።
በሀገር አቀፍ ደረጃ ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ. በ2011 በገባችው ቃል መሠረት እስከ 2030 ድረስ 7 ሚሊዮን ሄክታር የተጎዳ መሬት መልሶ ለማልማት አቅዳ እስካሁን 4.2 ሚሊዮን ሄክታር ማልማት ችላለች። በተጨማሪም እንደ ሀገራዊ የአየር ንብረት ስትራቴጂ አካል ተጨማሪ 15 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ለማልማት ቃል መግባቷን ሪፖርቱ አትቷል። ትክክለኛ ፖሊሲዎች እና ተከታታይ የፋይናንስ ድጋፍ ካለ እነዚህ አካሄዶች መሬትን ከመታደግ ባለፈ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም ትልቅ አቅም እንደሚፈጥሩ ተመላክቷል።
Sponsored by
Surafel
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የሱማሊያ አለም አቀፍ አጋሮች መንግስትና ተቃዋሚዎች በምርጫ ዙሪያ ንግግራቸውን እንዲቀጥሉ አሳሰቡ፡፡ በሱማሊያ ውስጥ የተፈጠረውን ፖለቲካዊ ውጥረት ተከትሎ አለም አቀፍ አጋሮች የፌዴራል መንግስቱና ተቃዋሚ ፓርቲዎች ውይይታቸውን በመቀጠል የምርጫ ፍኖተ ካርታ እንዲያወጡ አሳሰቡ፡፡
ዩናይትድ ኪንግደም፣ የተመድ የሽግግር ተልእኮ ለሱማሊያ፣ የአውሮፓ ህብረት፣ ስዊድን፣ ስዊዘርላንድና ኖርዌይ ዛሬ ባወጡት የጋራ መግለጫ ‹‹በዚህ ወሳኝ ፖለቲካዊ ወቅት የሱማሊያ መሪዎች ለአገራቸው ብሄራዊ ጥቅም ቅድሚያ ሊሰጡ ይገባል›› ብለዋል፡፡ ጨምረውም ‹‹ሁሉም አካላት በተቻለ ፍጥነት ውይይታቸውን ቀጥለው ለሱማሊያ ህዝብ ጥቅም ሲሉ በምርጫ ፍኖተ ካርታ ላይ ስምምነት ላይ እንዲደርሱ ጥሪያችንን እናቀርባለን›› ያለው መግለጫቸው ሁሉም ውጥረትን ከሚያባብስ ድርጊት እንዲቆጠቡም አሳስቧል፡፡
በሱማሊያዊያን በሚመራው ውይይት ላይ ድጋፍ እንዲሰጡ ከተጠየቁ ለማገዝ ዝግጁ መሆናቸውንም ገልጿል፡፡ ይህ መግለጫ ሊወጣ የቻለው የሱማሊያ ፌዴራል መንግስትና ተቃዋሚ ፓርቲዎች በህገ መንግስት ለውጥና ፖለቲካዊ ሽግግር ዙሪያ ያደረጉት ውይይት ያለ ስምምነት መበተኑን ተከትሎ ነው፡፡
ዩናይትድ ኪንግደም፣ የተመድ የሽግግር ተልእኮ ለሱማሊያ፣ የአውሮፓ ህብረት፣ ስዊድን፣ ስዊዘርላንድና ኖርዌይ ዛሬ ባወጡት የጋራ መግለጫ ‹‹በዚህ ወሳኝ ፖለቲካዊ ወቅት የሱማሊያ መሪዎች ለአገራቸው ብሄራዊ ጥቅም ቅድሚያ ሊሰጡ ይገባል›› ብለዋል፡፡ ጨምረውም ‹‹ሁሉም አካላት በተቻለ ፍጥነት ውይይታቸውን ቀጥለው ለሱማሊያ ህዝብ ጥቅም ሲሉ በምርጫ ፍኖተ ካርታ ላይ ስምምነት ላይ እንዲደርሱ ጥሪያችንን እናቀርባለን›› ያለው መግለጫቸው ሁሉም ውጥረትን ከሚያባብስ ድርጊት እንዲቆጠቡም አሳስቧል፡፡
በሱማሊያዊያን በሚመራው ውይይት ላይ ድጋፍ እንዲሰጡ ከተጠየቁ ለማገዝ ዝግጁ መሆናቸውንም ገልጿል፡፡ ይህ መግለጫ ሊወጣ የቻለው የሱማሊያ ፌዴራል መንግስትና ተቃዋሚ ፓርቲዎች በህገ መንግስት ለውጥና ፖለቲካዊ ሽግግር ዙሪያ ያደረጉት ውይይት ያለ ስምምነት መበተኑን ተከትሎ ነው፡፡
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኒውዮርክ ገዥ ካቲ ሆቹል የእስራኤሉ ቀኝ ዘመም የገንዘብ ሚኒስትር ቤዛሌል ስሞትሪች እሁድ ዕለት በኒውዮርክ በተካሄደው ዓመታዊ የእስራኤል የድጋፍ ሰልፍ ላይ መሳተፋቸውን “በጽኑ አውግዘዋል”።
ገዥዋ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው (ኤክስ) ላይ ባሰፈሩት መልዕክት፣ “ቤዛሌል ስሞትሪች አክራሪ ቀኝ ዘመም ሲሆኑ፣ የጥላቻ እና ከፋፋይ ንግግራቸው እኛ በኒውዮርክ አጥብቀን ከምንይዛቸው እና ከምናከብራቸው እሴቶች ጋር ፈጽሞ የሚጻረር ነው” ሲሉ ተችተዋል።
አክለውም፣ “የትናንቱ ሰልፍ የአይሁዳውያን ኩራት፣ ማህበረሰብ እና አንድነት የተከበረበት ነበር። የእርሱን ተሳትፎ ግን በጽኑ አወግዛለሁ” በማለት ጠንካራ አቋማቸውን አንጸባርቀዋል።
በተያያዘ ዜና፣ የኒውዮርክ ከተማ ከንቲባ ዞህራን ማምዳኒ በዘንድሮው ዓመታዊ ሰልፍ ላይ ላለመሳተፍ መወሰናቸው ተገልጿል። ይህ እርምጃቸው በዝግጅቱ የ61 ዓመታት ታሪክ ውስጥ በሰልፉ ላይ ላለመሳተፍ የወሰኑ የመጀመሪያው የከተማዋ መሪ ያደርጋቸዋል።
ገዥዋ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው (ኤክስ) ላይ ባሰፈሩት መልዕክት፣ “ቤዛሌል ስሞትሪች አክራሪ ቀኝ ዘመም ሲሆኑ፣ የጥላቻ እና ከፋፋይ ንግግራቸው እኛ በኒውዮርክ አጥብቀን ከምንይዛቸው እና ከምናከብራቸው እሴቶች ጋር ፈጽሞ የሚጻረር ነው” ሲሉ ተችተዋል።
አክለውም፣ “የትናንቱ ሰልፍ የአይሁዳውያን ኩራት፣ ማህበረሰብ እና አንድነት የተከበረበት ነበር። የእርሱን ተሳትፎ ግን በጽኑ አወግዛለሁ” በማለት ጠንካራ አቋማቸውን አንጸባርቀዋል።
በተያያዘ ዜና፣ የኒውዮርክ ከተማ ከንቲባ ዞህራን ማምዳኒ በዘንድሮው ዓመታዊ ሰልፍ ላይ ላለመሳተፍ መወሰናቸው ተገልጿል። ይህ እርምጃቸው በዝግጅቱ የ61 ዓመታት ታሪክ ውስጥ በሰልፉ ላይ ላለመሳተፍ የወሰኑ የመጀመሪያው የከተማዋ መሪ ያደርጋቸዋል።
3 days ago
የጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ምልጃ እና ረድኤት አይለየን🙏
በተወለዱ በሦስተኛው ቀን ከእናታቸው ዕቅፍ ወርደው “አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ” በማለት ሥላሴን አመስግነዋል፡፡
አባታቸው ጸጋ ዘአብና እናታቸው እግዚእ ኃረያ ፍሥሐ ጽዮን ብለው ሰየሟቸው፡፡ በአንድ ወቅት ታዳጊው ፍሥሐ ጽዮን ወደ ጫካ ለአደን በሔዱበት ጌታችን ተገልጦ ጸጋ መንፈስ ቅዱን አሳደረባቸው፡፡ ለሐዋርያዊ አገልግሎት ለስብከተ ወንጌል እንደሚልካቸውም አስረዳቸው፡፡ በተወለዱ በ15 ዓመታቸው መዓርገ ዲቊናን፣ በ22 ዓመታቸው ደግሞ መዓርገ ቅስናን ከግብጻዊው ጳጳስ አባ ቄርሎስ ተቀብለዋል፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም ስማቸውም ተክለ ሃይማኖት እንደሚባል፣ ትርጓሜውም ተክለ አብ፣ ተክለ ወልድ፣ ተክለ መንፈስ ቅዱስ ማለት እንደሆነ አበሠራቸው፡፡
ወላጆቻቸው ካረፉ በኋላም ንብረታቸውን ሁሉ ለቤተ ክርስቲያንና ለነዳያን ሰጥተው ቤታቸውን ትተው ወንጌልን ለማስተማር ወጡ፡፡ በደብረ ዳሞ ገዳም ለ12 ዓመታት ተቀምጠው ሲወርዱ ገመዱ ቢበጠስ ስድስት ክንፍ አውጥተው በረዋል፡፡ በመላው ኢትዮጵያ እየተዘዋወሩ ወንጌልን በመስበክና ተአምራትን በማድረግ በርካታ አሕዛብን አጥምቀዋል፤ አብያተ ክርስቲያናትንም አሳንጸዋል፡፡ በደብረ ሊባኖስ ገዳም አስቦ ዋሻ በዙሪያቸው ስምንት ጦሮች ተክለው እጆቻቸውን በትእምርተ መስቀል በመዘርጋት የክርስቶስን ሕማምና ሞት በማሰብ ሌሊትና ቀን ያለ ማቋረጥ በጾምና በጸሎት ሲጋደሉ፤ ከመቆም ብዛት አንድ እግራቸው ተሰብሯል፡፡
ጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ በኋላም ለሰባት ዓመታት በአንድ እግራቸው ቆመው ለሰው ዘር ሁሉ ድኅነትን ለምነዋል፡፡ ከዚህ ዓለም ድካም በሚያርፉበት ቀንም ጌታችን ከእናቱ ከቅዱሳን መላእክት፣ ከወዳጆቹ ጋር መጥቶ የምሕረት ቃል ኪዳን ሰጥቷቸዋል፡፡ ዐጽማቸው የፈለሰበት ዕለትም ግንቦት 12 ነው፡፡
የጻድቁን ቃል ኪዳን ያመኑ ገዳማውያን እንደሳቸው ሁሉ ዓለምን ንቀው በተጋድሎ ይኖራሉና ከበረከታቸው እንድንሳተፍ ገዳማቸውን እየደገፍን በዓታቸውን እያጸናን ከበረከታቸው እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
በተወለዱ በሦስተኛው ቀን ከእናታቸው ዕቅፍ ወርደው “አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ” በማለት ሥላሴን አመስግነዋል፡፡
አባታቸው ጸጋ ዘአብና እናታቸው እግዚእ ኃረያ ፍሥሐ ጽዮን ብለው ሰየሟቸው፡፡ በአንድ ወቅት ታዳጊው ፍሥሐ ጽዮን ወደ ጫካ ለአደን በሔዱበት ጌታችን ተገልጦ ጸጋ መንፈስ ቅዱን አሳደረባቸው፡፡ ለሐዋርያዊ አገልግሎት ለስብከተ ወንጌል እንደሚልካቸውም አስረዳቸው፡፡ በተወለዱ በ15 ዓመታቸው መዓርገ ዲቊናን፣ በ22 ዓመታቸው ደግሞ መዓርገ ቅስናን ከግብጻዊው ጳጳስ አባ ቄርሎስ ተቀብለዋል፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም ስማቸውም ተክለ ሃይማኖት እንደሚባል፣ ትርጓሜውም ተክለ አብ፣ ተክለ ወልድ፣ ተክለ መንፈስ ቅዱስ ማለት እንደሆነ አበሠራቸው፡፡
ወላጆቻቸው ካረፉ በኋላም ንብረታቸውን ሁሉ ለቤተ ክርስቲያንና ለነዳያን ሰጥተው ቤታቸውን ትተው ወንጌልን ለማስተማር ወጡ፡፡ በደብረ ዳሞ ገዳም ለ12 ዓመታት ተቀምጠው ሲወርዱ ገመዱ ቢበጠስ ስድስት ክንፍ አውጥተው በረዋል፡፡ በመላው ኢትዮጵያ እየተዘዋወሩ ወንጌልን በመስበክና ተአምራትን በማድረግ በርካታ አሕዛብን አጥምቀዋል፤ አብያተ ክርስቲያናትንም አሳንጸዋል፡፡ በደብረ ሊባኖስ ገዳም አስቦ ዋሻ በዙሪያቸው ስምንት ጦሮች ተክለው እጆቻቸውን በትእምርተ መስቀል በመዘርጋት የክርስቶስን ሕማምና ሞት በማሰብ ሌሊትና ቀን ያለ ማቋረጥ በጾምና በጸሎት ሲጋደሉ፤ ከመቆም ብዛት አንድ እግራቸው ተሰብሯል፡፡
ጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ በኋላም ለሰባት ዓመታት በአንድ እግራቸው ቆመው ለሰው ዘር ሁሉ ድኅነትን ለምነዋል፡፡ ከዚህ ዓለም ድካም በሚያርፉበት ቀንም ጌታችን ከእናቱ ከቅዱሳን መላእክት፣ ከወዳጆቹ ጋር መጥቶ የምሕረት ቃል ኪዳን ሰጥቷቸዋል፡፡ ዐጽማቸው የፈለሰበት ዕለትም ግንቦት 12 ነው፡፡
የጻድቁን ቃል ኪዳን ያመኑ ገዳማውያን እንደሳቸው ሁሉ ዓለምን ንቀው በተጋድሎ ይኖራሉና ከበረከታቸው እንድንሳተፍ ገዳማቸውን እየደገፍን በዓታቸውን እያጸናን ከበረከታቸው እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
3 days ago
ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል፤ ያንጊዜም ይጾማሉ🙏
የጾመ ሐዋርያት የጊዜ ቀመር ሥሌት በዓለ ጰራቅሊጦስ እንደ ገባ ባለው የመጀመሪያው ሰኞ ይውላል፡፡ ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ሥጋዌው ደቀ መዛሙርቱን ይህን ጾም እንደሚጾሙት ተናግሮ እንደነበር መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል፡፡ በማቴዎስ 9÷14 እንደተጻፈው በዚያን ጊዜ የዮሐንስ ደቀ መዛሙርት ወደ እርሱ ቀርበው። እኛና ፈሪሳውያን፥ ብዙ እንጾማለን፣ ደቀ መዛሙርትህስ ለምን አይጾሙም? አሉት፡፡ ኢየሱስም ደቀ መዛሙርቱ ይህንን በጠየቁት ጊዜ “የሙሽራው ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ አይችሉም፤ ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል፤ ያንጊዜም ይጾማሉ” በመለት መለሰላቸው፡፡ እኔ ሳለሁ አይጾሙም ማለቱ እርሱ ካልሞተና ካላረገ፤ መንፈስ ቅዱስንም ካልላከላቸው በመንፈስ ቅዱስ ባልታደሰ ሰውነት ጾመው ድል መንሳት ስለማይቻላቸው ነው፡፡
ስለዚህም ቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ ስለሁለት ዓላማ ይህን ጾም የአገልግሎታቸው መጀመሪያ አድርገውታል፡፡ አንደኛው ስለተሰጣቸው ጸጋ መንፈስ ቅዱስ አምላካቸውን ለማመስገን ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በዓለሙ ሁሉ ዞረው ለሚሰብኩት ወንጌል ራሳቸውን ለማዘጋጀት ነው፡፡ ይህን ጾም የምንጾመው ሐዋርያት ጾመው ጸልየው ድል ያደረጉትን ዓለም እኛም የምናሸንፍበት ኃይል እንዲሰጠን፣ ለቅዱሳን ሐዋርያት የተለመነ አምላክ ቅዱስ እግዚአብሔር እንዲለመነን ለመማጸን ነው፡፡ ይህ ጾም በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን እድሜው ከሰባት ዓመት በላይ የሆነ ኦርቶዲክሳዊ ሁሉ እንዲጾመው በአዋጅ ከታዘዙ አጽዋማት አንዱ ነው፡፡ የሐዋርያትን ጾም አንዳንዶች “የቀሳውስት ጾም” ሲሉት ይሰማል፡፡
አንዳንድ ላለመጾም የሚፈልጉ ወገኖች “የሐዋርያት” የሚለውን ቃል ብቻ በመውሰድ ጥንት ይህንን ጾም ሐዋርያት እንጂ ሕዝቡ አልጾመውም፤ ስለዚህ ዛሬ ደግሞ በሐዋርያት እግር የተተኩ ካህናት ስለሆኑ ጾሙም የእነርሱ ብቻ ሊሆን ይገባል ሲሉ ይደመጣሉ፡፡ በፍትሐ ነገስት አንቀጽ 15፡ 586 ግን ይህን ጾም አንዱ ካንዱ ሳይለይ ዕድሜው ከሰባት ዓመት በላይ የሆነ ሁሉ እንዲጾም ቤተ ክርስቲያን አውጃለች፡፡ እኛም እነርሱን ተከትለን፣ በእነርሱ ሥርዓት በመመራት፣ በሐዋርያት ላይ ያደረው የመንፈስ ቅዱስ ጸጋና ሀብት በእኛም ላይ እንዲያድርብን በየዓመቱ ጾመ ሐዋርያትን እንጾማለን፡፡ ዘመናቸውን በጸሎትና በጾም የሚያሳልፉት ገዳማውያንም ይህን ጾም በመጾም ታላቅ በረከት ያገኛሉ፡፡ ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና የበረከታቸው ተሳታፊ እንሆናለን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
የጾመ ሐዋርያት የጊዜ ቀመር ሥሌት በዓለ ጰራቅሊጦስ እንደ ገባ ባለው የመጀመሪያው ሰኞ ይውላል፡፡ ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ሥጋዌው ደቀ መዛሙርቱን ይህን ጾም እንደሚጾሙት ተናግሮ እንደነበር መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል፡፡ በማቴዎስ 9÷14 እንደተጻፈው በዚያን ጊዜ የዮሐንስ ደቀ መዛሙርት ወደ እርሱ ቀርበው። እኛና ፈሪሳውያን፥ ብዙ እንጾማለን፣ ደቀ መዛሙርትህስ ለምን አይጾሙም? አሉት፡፡ ኢየሱስም ደቀ መዛሙርቱ ይህንን በጠየቁት ጊዜ “የሙሽራው ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ አይችሉም፤ ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወራት ይመጣል፤ ያንጊዜም ይጾማሉ” በመለት መለሰላቸው፡፡ እኔ ሳለሁ አይጾሙም ማለቱ እርሱ ካልሞተና ካላረገ፤ መንፈስ ቅዱስንም ካልላከላቸው በመንፈስ ቅዱስ ባልታደሰ ሰውነት ጾመው ድል መንሳት ስለማይቻላቸው ነው፡፡
ስለዚህም ቅዱሳን ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ ስለሁለት ዓላማ ይህን ጾም የአገልግሎታቸው መጀመሪያ አድርገውታል፡፡ አንደኛው ስለተሰጣቸው ጸጋ መንፈስ ቅዱስ አምላካቸውን ለማመስገን ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በዓለሙ ሁሉ ዞረው ለሚሰብኩት ወንጌል ራሳቸውን ለማዘጋጀት ነው፡፡ ይህን ጾም የምንጾመው ሐዋርያት ጾመው ጸልየው ድል ያደረጉትን ዓለም እኛም የምናሸንፍበት ኃይል እንዲሰጠን፣ ለቅዱሳን ሐዋርያት የተለመነ አምላክ ቅዱስ እግዚአብሔር እንዲለመነን ለመማጸን ነው፡፡ ይህ ጾም በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን እድሜው ከሰባት ዓመት በላይ የሆነ ኦርቶዲክሳዊ ሁሉ እንዲጾመው በአዋጅ ከታዘዙ አጽዋማት አንዱ ነው፡፡ የሐዋርያትን ጾም አንዳንዶች “የቀሳውስት ጾም” ሲሉት ይሰማል፡፡
አንዳንድ ላለመጾም የሚፈልጉ ወገኖች “የሐዋርያት” የሚለውን ቃል ብቻ በመውሰድ ጥንት ይህንን ጾም ሐዋርያት እንጂ ሕዝቡ አልጾመውም፤ ስለዚህ ዛሬ ደግሞ በሐዋርያት እግር የተተኩ ካህናት ስለሆኑ ጾሙም የእነርሱ ብቻ ሊሆን ይገባል ሲሉ ይደመጣሉ፡፡ በፍትሐ ነገስት አንቀጽ 15፡ 586 ግን ይህን ጾም አንዱ ካንዱ ሳይለይ ዕድሜው ከሰባት ዓመት በላይ የሆነ ሁሉ እንዲጾም ቤተ ክርስቲያን አውጃለች፡፡ እኛም እነርሱን ተከትለን፣ በእነርሱ ሥርዓት በመመራት፣ በሐዋርያት ላይ ያደረው የመንፈስ ቅዱስ ጸጋና ሀብት በእኛም ላይ እንዲያድርብን በየዓመቱ ጾመ ሐዋርያትን እንጾማለን፡፡ ዘመናቸውን በጸሎትና በጾም የሚያሳልፉት ገዳማውያንም ይህን ጾም በመጾም ታላቅ በረከት ያገኛሉ፡፡ ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና የበረከታቸው ተሳታፊ እንሆናለን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
4 days ago
ነገ ድምፅ ለመስጠት ሲሄዱ እነዚህን አይዘንጉ፡-
1. በሁሉም ጣቢያዎች ድምፅ መስጠት የሚጀመረው ከጠዋቱ 12፡00 ጀምሮ መሆኑን፤
2. እስከ ምሽቱ 12፡00 የምርጫ ጣቢያ ክፍት ስለሚሆን ጊዜ አለኝ በሚል እንዳይዘናጉ፤
3. ማንነትዎን የሚገልጽ መታወቂያና የመራጮች መታወቂያ ካርድዎን ይዘዋል?
4. ለምርጫ የተመዘገቡበት ጣቢያ ነው የሄዱት? ከሆነ ሰልፍ ይያዙ፤ ካልሆነ ካርድ ወዳወጡበት ይሂዱ፤
5. ስምዎ በመራጮች መዝገብ ላይ ሰፍሯል? መዝገብ ሹሙ ያይልዎታል፤
6. ቀድመው ድምፅ አልሰጡም? ከሰጡ ሌላው መብቱን እንዲጠቀም የምርጫ ጣቢያውን ለቅቀው ይውጡ፤ ድምጽ ከሰጡ በኋላ መሄድ ይገባዎታል፤ ድምፅ ያልሰጡ ከሆነ ግን የምርጫ ወረቀት ወስደው ጣትዎን የመራጭነት ምልክት ቀለም ተቀብተው በምስጢር የሚወክልዎን ይምረጡ፤
7. ድጋፍ የሚያስፈልግዎ ከሆነ መብቱ በሕግ ያልተገደበ ረዳት ይዘው መግባት ይችላሉ፤
8. ቅድሚያ የሚሰጣቸው ወገኖች ካሉ (አካል ጉዳተኞች፣ አረጋውያን፣ ነፍሰ ጡር እናቶች፣ ሕፃናትን የያዙ ወላጆች ) ቅድሚያ እንስጥ፤
ድምጽዎን ለሀገርዎ!
1. በሁሉም ጣቢያዎች ድምፅ መስጠት የሚጀመረው ከጠዋቱ 12፡00 ጀምሮ መሆኑን፤
2. እስከ ምሽቱ 12፡00 የምርጫ ጣቢያ ክፍት ስለሚሆን ጊዜ አለኝ በሚል እንዳይዘናጉ፤
3. ማንነትዎን የሚገልጽ መታወቂያና የመራጮች መታወቂያ ካርድዎን ይዘዋል?
4. ለምርጫ የተመዘገቡበት ጣቢያ ነው የሄዱት? ከሆነ ሰልፍ ይያዙ፤ ካልሆነ ካርድ ወዳወጡበት ይሂዱ፤
5. ስምዎ በመራጮች መዝገብ ላይ ሰፍሯል? መዝገብ ሹሙ ያይልዎታል፤
6. ቀድመው ድምፅ አልሰጡም? ከሰጡ ሌላው መብቱን እንዲጠቀም የምርጫ ጣቢያውን ለቅቀው ይውጡ፤ ድምጽ ከሰጡ በኋላ መሄድ ይገባዎታል፤ ድምፅ ያልሰጡ ከሆነ ግን የምርጫ ወረቀት ወስደው ጣትዎን የመራጭነት ምልክት ቀለም ተቀብተው በምስጢር የሚወክልዎን ይምረጡ፤
7. ድጋፍ የሚያስፈልግዎ ከሆነ መብቱ በሕግ ያልተገደበ ረዳት ይዘው መግባት ይችላሉ፤
8. ቅድሚያ የሚሰጣቸው ወገኖች ካሉ (አካል ጉዳተኞች፣ አረጋውያን፣ ነፍሰ ጡር እናቶች፣ ሕፃናትን የያዙ ወላጆች ) ቅድሚያ እንስጥ፤
ድምጽዎን ለሀገርዎ!
Sponsored by
Surafel
4 days ago
ለወጣቶች እና የሚዲያ ተቋማት በስደት አስተዳደር ዙሪያ የሚዲያ ንቅናቄን ለማጠናከር የስትራቴጂክ አጋርነት ውይይት ተካሄደ።
ውይይቱ በህገወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ አተኩረው በሚሰሩት ሲግማ ኢስት አፍሪካ እና ስዊት ላይፍ ፎር ኦል Sweet Life for All Charity Organization የተሰናዳ መሆኑ ተጠቁሟል ።
ተቋማቱ "ይመለከተኛል" ሲሉ ከዚህ ቀደም አብረው መስራታቸውን በመጥቀስ በመድረኩ እኤአ 2025–2026 ዓ.ም የ“Digital Voices, Real Impact” ዘመቻ የተገኙ ውጤቶች፣ የስደት ጉዳይ ላይ የሚዲያ ሚና፣ የወጣቶች አቅም ግንባታ፣ የሰው ዝውውር እና የህገ-ወጥ ስደት መከላከል እንዲሁም በምስራቅ አፍሪካ ያለው የተቀናጀ ክልላዊ ምላሽ ላይ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል።
ከሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚንስትር ተወክለው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት አቶ ደረጀ ተግይበሉ "እንደዚህ ያሉ መድረኮችን ለማገዝ መረጃዎችን በማቅረብ ፣ ግንዛቤን ከመፍጠር አንፃር እንዲህ ያለው ምክክር እና ስትራቴጂክ አጋርነት አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል።"
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ቢሮ የፍልሰት ትብብር ጥምረት ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ዬሀንስ ብርሀኑ መከላከል ፣ከለላ እና ጥበቃ ቅንጅታዊ አሰራር ፣ የህግ ተጠያቂነት፣ በጋራ መስራት ላይ ስራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አሳስበዋል ።
በዘርፉ የረጅም አመት የስራ ልምድ ያላቸው የውዲንዳድ ሀላፊ እና የምስራቅ አፍሪካ ስትራቴጂክ ተወካይ የሆኑት አቶ ኤፍሬም ሽፈራው ሀገራዊ ምላሹ እንዳለ ሆኖ ቀጠናዊ ጉዳይ ላይም አብሮ መስራት አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል ።
የ Sweet Life for All Charity Organization መስራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አንተነህ ተስፋዬ በንግግራቸው፣ “ዲጂታል ሚዲያ የማህበረሰብ ንቅናቄ መፍጠሪያ እና የወጣቶች ድምፅ ማጉሊያ ኃይለኛ መሳሪያ ነው በማለት በተለይ በፍልሰት እና በህገወጥ ሰው ዝውውር ጉዳዮች ላይ የተቀናጀ የሚዲያ ተሳትፎ ወሳኝ ነው” ብለዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ SIGMA EAST AFRICA CHARITABLE ORGANIZATION FOUNDER AND
CEO የሲግማ ኢስት አፍሪካ መስራች እና ስራ አስኪያጅ በፍልሰት ዙሪያ ሀገራዊና ቀጠናዊ ምላሾች ላይ አብሮ መስራቱ በከፍተኛ ትኩረት የመፍትሔ አቅጣጫዎችን ማመላከቱ ተገቢ መሆኑን አንስተዋል ።
በውይይቱ ውስጥ የስደት አስተዳደር፣ የተመላሽ ዜጎች ድጋፍ፣ የወጣቶች ስራ ፈጠራ፣ የሚዲያ ተሳትፎ እና የህገወጥ የሰው ዝውውር ግንዛቤ ማስፋፊያ ላይ በባለሙያዎች የተመራ ውይይት ተካሂዷል።
ሲግማ ኢስት አፍሪካ እና ስዊት ላይፍ ፎር ኦል የተሰኙት ግብረ ሰናይ ድርጅቶች የምስረታ እድሜያቸው አጭር ቢሆኑም በእቅድ እና በተግባራዊ አፈፃፀማቸው ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ መሆናቸውም ተገልጿል ።
በዛሬው ውይይት ሀገራችን ኢትዮጵያ በሰዎች ዝውውር እያደረገችው ስላለ እንቅስቃሴ እና ስለመጣ ለውጥ የተነሳ ሲሆን ተቋማቱ ከአጋር አካላት ጋር የሰሩትን በቀጣይም በተለያዩ ሀገራት በተለይም በአረቡ አለም በችግር ውስጥ ለሚገኙ ዜጎቻችን ድምፅ ለመሆን ንቅናቄም ለመጀመር ከስምምነት ተደርሷል።
ዝግጅቱ በአዲስ አበባ ማግኖሊያ ሆቴል የተካሄደ ሲሆን ከመንግስት ተቋማት የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ፣
ሴቶችና ማኀበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፋይናስ ቢሮ ፣ ከሚዲያ ተቋማት፣ ከሲቪል ማህበራት፣ ከወጣቶች አደረጃጀት እና ከአለም አቀፍ አጋሮች የተውጣጡ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል።
ይህንንም አላማ ከግብ ለማድረስ አምስት ተቋማት የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል ።
በስተመጨረሻም ሁለቱ ተቋማት ላስመዘገቡት ውጤት በሥራ እንቅስቃሴያቸው ደጋፊ ለነበሩ ተቋማትና ግለሰቦች የምስጋና እና የእውቅና ሰርተፍኬት አበርክተዋል።
ውይይቱ በህገወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ አተኩረው በሚሰሩት ሲግማ ኢስት አፍሪካ እና ስዊት ላይፍ ፎር ኦል Sweet Life for All Charity Organization የተሰናዳ መሆኑ ተጠቁሟል ።
ተቋማቱ "ይመለከተኛል" ሲሉ ከዚህ ቀደም አብረው መስራታቸውን በመጥቀስ በመድረኩ እኤአ 2025–2026 ዓ.ም የ“Digital Voices, Real Impact” ዘመቻ የተገኙ ውጤቶች፣ የስደት ጉዳይ ላይ የሚዲያ ሚና፣ የወጣቶች አቅም ግንባታ፣ የሰው ዝውውር እና የህገ-ወጥ ስደት መከላከል እንዲሁም በምስራቅ አፍሪካ ያለው የተቀናጀ ክልላዊ ምላሽ ላይ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል።
ከሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚንስትር ተወክለው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት አቶ ደረጀ ተግይበሉ "እንደዚህ ያሉ መድረኮችን ለማገዝ መረጃዎችን በማቅረብ ፣ ግንዛቤን ከመፍጠር አንፃር እንዲህ ያለው ምክክር እና ስትራቴጂክ አጋርነት አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል።"
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍትህ ቢሮ የፍልሰት ትብብር ጥምረት ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ዬሀንስ ብርሀኑ መከላከል ፣ከለላ እና ጥበቃ ቅንጅታዊ አሰራር ፣ የህግ ተጠያቂነት፣ በጋራ መስራት ላይ ስራዎች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ አሳስበዋል ።
በዘርፉ የረጅም አመት የስራ ልምድ ያላቸው የውዲንዳድ ሀላፊ እና የምስራቅ አፍሪካ ስትራቴጂክ ተወካይ የሆኑት አቶ ኤፍሬም ሽፈራው ሀገራዊ ምላሹ እንዳለ ሆኖ ቀጠናዊ ጉዳይ ላይም አብሮ መስራት አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል ።
የ Sweet Life for All Charity Organization መስራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አንተነህ ተስፋዬ በንግግራቸው፣ “ዲጂታል ሚዲያ የማህበረሰብ ንቅናቄ መፍጠሪያ እና የወጣቶች ድምፅ ማጉሊያ ኃይለኛ መሳሪያ ነው በማለት በተለይ በፍልሰት እና በህገወጥ ሰው ዝውውር ጉዳዮች ላይ የተቀናጀ የሚዲያ ተሳትፎ ወሳኝ ነው” ብለዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ SIGMA EAST AFRICA CHARITABLE ORGANIZATION FOUNDER AND
CEO የሲግማ ኢስት አፍሪካ መስራች እና ስራ አስኪያጅ በፍልሰት ዙሪያ ሀገራዊና ቀጠናዊ ምላሾች ላይ አብሮ መስራቱ በከፍተኛ ትኩረት የመፍትሔ አቅጣጫዎችን ማመላከቱ ተገቢ መሆኑን አንስተዋል ።
በውይይቱ ውስጥ የስደት አስተዳደር፣ የተመላሽ ዜጎች ድጋፍ፣ የወጣቶች ስራ ፈጠራ፣ የሚዲያ ተሳትፎ እና የህገወጥ የሰው ዝውውር ግንዛቤ ማስፋፊያ ላይ በባለሙያዎች የተመራ ውይይት ተካሂዷል።
ሲግማ ኢስት አፍሪካ እና ስዊት ላይፍ ፎር ኦል የተሰኙት ግብረ ሰናይ ድርጅቶች የምስረታ እድሜያቸው አጭር ቢሆኑም በእቅድ እና በተግባራዊ አፈፃፀማቸው ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ መሆናቸውም ተገልጿል ።
በዛሬው ውይይት ሀገራችን ኢትዮጵያ በሰዎች ዝውውር እያደረገችው ስላለ እንቅስቃሴ እና ስለመጣ ለውጥ የተነሳ ሲሆን ተቋማቱ ከአጋር አካላት ጋር የሰሩትን በቀጣይም በተለያዩ ሀገራት በተለይም በአረቡ አለም በችግር ውስጥ ለሚገኙ ዜጎቻችን ድምፅ ለመሆን ንቅናቄም ለመጀመር ከስምምነት ተደርሷል።
ዝግጅቱ በአዲስ አበባ ማግኖሊያ ሆቴል የተካሄደ ሲሆን ከመንግስት ተቋማት የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ፣
ሴቶችና ማኀበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፋይናስ ቢሮ ፣ ከሚዲያ ተቋማት፣ ከሲቪል ማህበራት፣ ከወጣቶች አደረጃጀት እና ከአለም አቀፍ አጋሮች የተውጣጡ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል።
ይህንንም አላማ ከግብ ለማድረስ አምስት ተቋማት የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል ።
በስተመጨረሻም ሁለቱ ተቋማት ላስመዘገቡት ውጤት በሥራ እንቅስቃሴያቸው ደጋፊ ለነበሩ ተቋማትና ግለሰቦች የምስጋና እና የእውቅና ሰርተፍኬት አበርክተዋል።
4 days ago
ፈተናውን ወደ መልካም አጋጣሚ የቀየረው የልዩ ህክምና ክሊኒክ፤ በዘመናዊ ህንጻና ግብዓቶች ስራ እንደገና ጀመረ
በከተማዋ በተካሄደው የኮሪደር ልማት ምክንያት አገልግሎት ሲሰጥበት የነበረው ህንጻ የፈረሰበት የልዩ ህክምና ክሊኒክ፣ አቅሙንና የህክምና መገልገያ መሳሪያዎቹን በከፍተኛ ደረጃ በማዘመን በአዲስ መልክ ተመርቆ ስራ ጀመረ።
ክሊኒኩ በአሁኑ ወቅት አገልግሎቱን በስፋት መቀጠል የጀመረው በየካ ክፍለ ከተማ፣ ታቦት ማደሪያ እግር ኳስ ሜዳ አጠገብ ባስገነባው ባለ 22 ክፍል ዘመናዊ ህንጻ ላይ መሆኑ ታውቋል።
የተቋሙ መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ዳዊት አማረ በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ እንደገለጹት፤ ክሊኒኩ የገጠመውን ፈተና ወደ መልካም አጋጣሚ በመቀየር በይዘቱም ሆነ በህክምና መገልገያ መሳሪያዎች እራሱን በከፍተኛ ደረጃ ማዘመን ችሏል።
ተቋሙ በተለይም በውስጥ ደዌ እና በሳንባ ስፔሻሊስት (Pulmonology) የህክምና ዘርፎች ላይ ትኩረት አድርጎ ጥራት ያለው አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን፣ ለድንገተኛና ለአስቸኳይ ህክምና ፈላጊዎችም ቀልጣፋ አደረጃጀት ማዘጋጀቱን ገልጸዋል።
"ጤና የእያንዳንዱ ሰው መሰረታዊ መብት ነው" ያሉት ዶክተር ዳዊት፤ ባለፉት ስድስት ዓመታት በርካታ ታካሚዎችን በታማኝነት ሲያገለግሉ መቆየታቸውንና አሁንም ማህበረሰቡን በተሻለ ጥራትና ምቾት ለማገልገል ዝግጁ መሆናቸውን አብራርተዋል።
አዲሱ ህንፃ የህክምና ተቋም ሊያሟላቸው የሚገቡ መስፈርቶችን ሙሉ በሙሉ ያሟላ ከመሆኑም በላይ፣ ህፃናትን ጨምሮ ማንኛውንም ታካሚ በተገቢው ሁኔታ ለማስተናገድ የሚያስችሉ ባለሙያዎችና ዘመናዊ ግብዓቶች ተጠናቀውለታል። ተቋሙ በኮሪደር ልማት ምክንያት ቢፈርስም፣ ላለፉት 14 ዓመታት አገልግሎት ሲሰጥበት በነበረው በዚሁ አካባቢ ለታካሚዎች ምቹ በሆነ ስፍራ ላይ በላቀ አደረጃጀት ዳግም ስራ መጀመሩ ተገልጿል።
ይህ የልዩ ህክምና ክሊኒክ ለ56 የህክምና ባለሙያዎች የስራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 23 የሚሆኑ ስፔሻሊስት እና ሰብ-ስፔሻሊስት ዶክተሮችን በማሳተፍ ላይ ይገኛል። በጥናት ማጠቃለያውም ላይ ክሊኒኩ ባለፉት ዓመታት አብረዋቸው ለቆሙ ታካሚዎች እና በአስቸጋሪ ወቅቶች ስራው ሳይስተጓጎል ድጋፍ ላደረጉ ባልደረቦቹ ከፍተኛ ምስጋና አቅርቧል።
በከተማዋ በተካሄደው የኮሪደር ልማት ምክንያት አገልግሎት ሲሰጥበት የነበረው ህንጻ የፈረሰበት የልዩ ህክምና ክሊኒክ፣ አቅሙንና የህክምና መገልገያ መሳሪያዎቹን በከፍተኛ ደረጃ በማዘመን በአዲስ መልክ ተመርቆ ስራ ጀመረ።
ክሊኒኩ በአሁኑ ወቅት አገልግሎቱን በስፋት መቀጠል የጀመረው በየካ ክፍለ ከተማ፣ ታቦት ማደሪያ እግር ኳስ ሜዳ አጠገብ ባስገነባው ባለ 22 ክፍል ዘመናዊ ህንጻ ላይ መሆኑ ታውቋል።
የተቋሙ መስራችና ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ዳዊት አማረ በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ እንደገለጹት፤ ክሊኒኩ የገጠመውን ፈተና ወደ መልካም አጋጣሚ በመቀየር በይዘቱም ሆነ በህክምና መገልገያ መሳሪያዎች እራሱን በከፍተኛ ደረጃ ማዘመን ችሏል።
ተቋሙ በተለይም በውስጥ ደዌ እና በሳንባ ስፔሻሊስት (Pulmonology) የህክምና ዘርፎች ላይ ትኩረት አድርጎ ጥራት ያለው አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን፣ ለድንገተኛና ለአስቸኳይ ህክምና ፈላጊዎችም ቀልጣፋ አደረጃጀት ማዘጋጀቱን ገልጸዋል።
"ጤና የእያንዳንዱ ሰው መሰረታዊ መብት ነው" ያሉት ዶክተር ዳዊት፤ ባለፉት ስድስት ዓመታት በርካታ ታካሚዎችን በታማኝነት ሲያገለግሉ መቆየታቸውንና አሁንም ማህበረሰቡን በተሻለ ጥራትና ምቾት ለማገልገል ዝግጁ መሆናቸውን አብራርተዋል።
አዲሱ ህንፃ የህክምና ተቋም ሊያሟላቸው የሚገቡ መስፈርቶችን ሙሉ በሙሉ ያሟላ ከመሆኑም በላይ፣ ህፃናትን ጨምሮ ማንኛውንም ታካሚ በተገቢው ሁኔታ ለማስተናገድ የሚያስችሉ ባለሙያዎችና ዘመናዊ ግብዓቶች ተጠናቀውለታል። ተቋሙ በኮሪደር ልማት ምክንያት ቢፈርስም፣ ላለፉት 14 ዓመታት አገልግሎት ሲሰጥበት በነበረው በዚሁ አካባቢ ለታካሚዎች ምቹ በሆነ ስፍራ ላይ በላቀ አደረጃጀት ዳግም ስራ መጀመሩ ተገልጿል።
ይህ የልዩ ህክምና ክሊኒክ ለ56 የህክምና ባለሙያዎች የስራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 23 የሚሆኑ ስፔሻሊስት እና ሰብ-ስፔሻሊስት ዶክተሮችን በማሳተፍ ላይ ይገኛል። በጥናት ማጠቃለያውም ላይ ክሊኒኩ ባለፉት ዓመታት አብረዋቸው ለቆሙ ታካሚዎች እና በአስቸጋሪ ወቅቶች ስራው ሳይስተጓጎል ድጋፍ ላደረጉ ባልደረቦቹ ከፍተኛ ምስጋና አቅርቧል።
4 days ago
ቅዱስ ጊዮርጊስ ከክፉ ነገር ሁሉ ይከልለን፤ ምልጃው እና ረድኤቱም አይለየን🙏
ይህን ከሃዲ እስካሳፍረው ድረስ ነፍሴን አትውሰዳት
አባቱን ገና በልጅነቱ ቢሞትበትም ሌላ ክርስቲያናዊ መስፍን ወስዶ በጦር ኃይል አሰልጠኖ አሳድጎታል፡፡ የስሙ ትርጓሜ “ኮከብ ብሩህ፣ ፀሐይ” ማለት ነው፡፡ ፍልስጤም ውስጥ ልዩ ስሟ “ልዳ” በምትባል ቦታ በ277 ዓ.ም ጥር 20 ተወለደ ታላቁ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ፡፡ ያሳደገው መስፍን ሲሞትም ኀዘኑን ጨርሶ ወደ ቤሩት ከተማ ሄደ፡፡ በዚያም የሚመለክና ሴት ልጆቻቸውን የሚገብሩለትን ደራጎን ገድሎ ሕዝቡን ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር መለሳቸው፡፡ የአባቱን ሹመት ለማግኘት ወደ ፋርስም ሲሔድ ንጉሱ ዱድያኖስ ከሰባ ነገሥታት ጋር ጣዖታት ሲያመልኩ ቢያገኛቸው በፊታቸው የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት መሰከረ፡፡ ሰማዕቱ ከመኳንንት ወገን መሆኑን የተረዳው ዱዲያኖስ አጵሎንን ብታመልክ እሾምሃለው አለው፡፡
ቅዱስ ጊዮርጊስም “አምላኬ ኢየሱስ ክርስቶስን ላንተ ሹመት ስል አልክደውም” አለው፡፡ ዱድያኖስም እጅግ ተቆጥቶ ብዙ አሠቃቂ መከራዎችን አደረሰበት፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም ግን ጌታችንን “ይህን ከሃዲ እስካሳፍረው ድረስ ነፍሴን አትውሰዳት” በማለት ለመነው፡፡ እግዚአብሔርም ጽናትን ሰጥቶታል፡፡ የደረሱበት እጅግ አሠቃቂ መከራዎች የሰው ኅሊና ሊያስባቸው እንኳን የማይችላቸው ናቸው፡፡ በእንጨት ላይ ሰቅለው ሥጋውን በመቃን አስፈተተው፣ ረጃጅም ችንካሮች ያሉበት የብረት ጫማ አጫምተው ሂድ አሉት፡፡ ጌታችንም ቅዱስ ሚካኤልን ልኮለት ፈውሶታል፡፡ ሰውነቱን በመጋዝ አስተልትሎ ጨው ሲነሰንስበት ሥጋው መሬት ላይ ወደቀ፡፡
በሰባ ችንካሮች አስቸንክሮ፣ በእሳት አስተኩሶ፣ አናቱን በመዶሻ አስቀጥቅጦ፣ በሆዱ ላይ የደንጊያ ምሰሶ አሳስሮ እንዲያንከባልሉት አደረገ፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመንፈቀ ሌሊት በእጁ ዳስሶ ፈወሰው፤ ኃይልና ብርታትንም ሰጠው፡፡ በመከራው ብዛት ሦስት ጊዜ ሲሞት ጌታችን ሦስት ጊዜ ከሞት አስነሣው፡፡ ለሰባት ዓመታት ከተጋደለ በኋላም ሚያዝያ 23 በሰይፍ አንገቱን ተመቶ ሲሞት ሰባውን ነገስታት አጥፍቷቸዋል፡፡ ዓለምን የናቁ ገዳማውያን ይህን አብነት አድርገው ይጸናሉ በገድልም ይተጋሉ፡፡ እኛም ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና የበረከታቸው ተሳታፊ እንሆናለን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
ይህን ከሃዲ እስካሳፍረው ድረስ ነፍሴን አትውሰዳት
አባቱን ገና በልጅነቱ ቢሞትበትም ሌላ ክርስቲያናዊ መስፍን ወስዶ በጦር ኃይል አሰልጠኖ አሳድጎታል፡፡ የስሙ ትርጓሜ “ኮከብ ብሩህ፣ ፀሐይ” ማለት ነው፡፡ ፍልስጤም ውስጥ ልዩ ስሟ “ልዳ” በምትባል ቦታ በ277 ዓ.ም ጥር 20 ተወለደ ታላቁ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ፡፡ ያሳደገው መስፍን ሲሞትም ኀዘኑን ጨርሶ ወደ ቤሩት ከተማ ሄደ፡፡ በዚያም የሚመለክና ሴት ልጆቻቸውን የሚገብሩለትን ደራጎን ገድሎ ሕዝቡን ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር መለሳቸው፡፡ የአባቱን ሹመት ለማግኘት ወደ ፋርስም ሲሔድ ንጉሱ ዱድያኖስ ከሰባ ነገሥታት ጋር ጣዖታት ሲያመልኩ ቢያገኛቸው በፊታቸው የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት መሰከረ፡፡ ሰማዕቱ ከመኳንንት ወገን መሆኑን የተረዳው ዱዲያኖስ አጵሎንን ብታመልክ እሾምሃለው አለው፡፡
ቅዱስ ጊዮርጊስም “አምላኬ ኢየሱስ ክርስቶስን ላንተ ሹመት ስል አልክደውም” አለው፡፡ ዱድያኖስም እጅግ ተቆጥቶ ብዙ አሠቃቂ መከራዎችን አደረሰበት፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም ግን ጌታችንን “ይህን ከሃዲ እስካሳፍረው ድረስ ነፍሴን አትውሰዳት” በማለት ለመነው፡፡ እግዚአብሔርም ጽናትን ሰጥቶታል፡፡ የደረሱበት እጅግ አሠቃቂ መከራዎች የሰው ኅሊና ሊያስባቸው እንኳን የማይችላቸው ናቸው፡፡ በእንጨት ላይ ሰቅለው ሥጋውን በመቃን አስፈተተው፣ ረጃጅም ችንካሮች ያሉበት የብረት ጫማ አጫምተው ሂድ አሉት፡፡ ጌታችንም ቅዱስ ሚካኤልን ልኮለት ፈውሶታል፡፡ ሰውነቱን በመጋዝ አስተልትሎ ጨው ሲነሰንስበት ሥጋው መሬት ላይ ወደቀ፡፡
በሰባ ችንካሮች አስቸንክሮ፣ በእሳት አስተኩሶ፣ አናቱን በመዶሻ አስቀጥቅጦ፣ በሆዱ ላይ የደንጊያ ምሰሶ አሳስሮ እንዲያንከባልሉት አደረገ፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመንፈቀ ሌሊት በእጁ ዳስሶ ፈወሰው፤ ኃይልና ብርታትንም ሰጠው፡፡ በመከራው ብዛት ሦስት ጊዜ ሲሞት ጌታችን ሦስት ጊዜ ከሞት አስነሣው፡፡ ለሰባት ዓመታት ከተጋደለ በኋላም ሚያዝያ 23 በሰይፍ አንገቱን ተመቶ ሲሞት ሰባውን ነገስታት አጥፍቷቸዋል፡፡ ዓለምን የናቁ ገዳማውያን ይህን አብነት አድርገው ይጸናሉ በገድልም ይተጋሉ፡፡ እኛም ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና የበረከታቸው ተሳታፊ እንሆናለን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
4 days ago
የየካ ክፍለ ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት በበጀት ዓመቱ ...
#ethiopia | የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የየካ ክፍለ ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ አስር ወራት ውስጥ ፍትሐዊ የገቢ አሰባሰብ ሥርዓትን በመከተል ካቀደው ዕቅድ በላይ 105 በመቶ ማሳካት መቻሉን ገልጿል።
የቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ የታክስ ጉዳዮች ዘርፍ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ወይዘሮ መሰረት መንግስቱ እንደተናገሩት በበጀት ዓመቱ አስር ወራት ውስጥ 5 ነጥብ 45 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ የነበረ ቢሆንም የተከናወነው ተግባር ግን 5 ነጥብ 74 ቢሊየን ብር ለማሰባሰብ አስችሏል።
ይህ አፈጻጸም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ2 ነጥብ 43 ቢሊየን ብር ወይም የ74 በመቶ የገቢ ዕድገት ያሳየ መሆኑን ምክትል ሥራ አስኪያጇ አስረድተዋል።
ለዚህ ስኬታማ ውጤት መገኘት ዋናው ምክንያት የጽሕፈት ቤቱ አመራሮች ለዕቅዱ መሳካት ያሳዩት ቁርጠኝነት መሆኑንና ሠራተኞችን በአንድ ዓላማ ሥር በማስተባበር ሌት ተቀን በቅንጅት እንዲሠሩ ማስቻላቸው እንደሆነ ተገልጿል።
ከዚህ በተጨማሪም ዕለታዊ የሥራ እንቅስቃሴዎችን በቅርብ መከታተል፣ አፈጻጸሞችን መገምገምና የሚታዩ ክፍተቶችን በወቅቱ ማረም የሚያስችል የተደራጀ የክትትልና የድጋፍ ሥርዓት መዘርጋቱ ለውጤታማነቱ ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷል።
ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ የታክስ ሕግን ፍትሐዊ በሆነ መንገድ ለማስከበር ትኩረት ሰጥቶ የሠራ ሲሆን ለግብር ከፋዮች ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት በተደረገው ጥረትም አበረታች ለውጦች መመዝገባቸው ተመልክቷል።
#ethiopia | የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የየካ ክፍለ ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ አስር ወራት ውስጥ ፍትሐዊ የገቢ አሰባሰብ ሥርዓትን በመከተል ካቀደው ዕቅድ በላይ 105 በመቶ ማሳካት መቻሉን ገልጿል።
የቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ የታክስ ጉዳዮች ዘርፍ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ወይዘሮ መሰረት መንግስቱ እንደተናገሩት በበጀት ዓመቱ አስር ወራት ውስጥ 5 ነጥብ 45 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ የነበረ ቢሆንም የተከናወነው ተግባር ግን 5 ነጥብ 74 ቢሊየን ብር ለማሰባሰብ አስችሏል።
ይህ አፈጻጸም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ2 ነጥብ 43 ቢሊየን ብር ወይም የ74 በመቶ የገቢ ዕድገት ያሳየ መሆኑን ምክትል ሥራ አስኪያጇ አስረድተዋል።
ለዚህ ስኬታማ ውጤት መገኘት ዋናው ምክንያት የጽሕፈት ቤቱ አመራሮች ለዕቅዱ መሳካት ያሳዩት ቁርጠኝነት መሆኑንና ሠራተኞችን በአንድ ዓላማ ሥር በማስተባበር ሌት ተቀን በቅንጅት እንዲሠሩ ማስቻላቸው እንደሆነ ተገልጿል።
ከዚህ በተጨማሪም ዕለታዊ የሥራ እንቅስቃሴዎችን በቅርብ መከታተል፣ አፈጻጸሞችን መገምገምና የሚታዩ ክፍተቶችን በወቅቱ ማረም የሚያስችል የተደራጀ የክትትልና የድጋፍ ሥርዓት መዘርጋቱ ለውጤታማነቱ ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷል።
ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ የታክስ ሕግን ፍትሐዊ በሆነ መንገድ ለማስከበር ትኩረት ሰጥቶ የሠራ ሲሆን ለግብር ከፋዮች ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት በተደረገው ጥረትም አበረታች ለውጦች መመዝገባቸው ተመልክቷል።
4 days ago
የየካ ክፍለ ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት በበጀት ዓመቱ ...
#ethiopia | የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የየካ ክፍለ ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ አስር ወራት ውስጥ ፍትሐዊ የገቢ አሰባሰብ ሥርዓትን በመከተል ካቀደው ዕቅድ በላይ 105 በመቶ ማሳካት መቻሉን ገልጿል።
የቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ የታክስ ጉዳዮች ዘርፍ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ወይዘሮ መሰረት መንግስቱ እንደተናገሩት በበጀት ዓመቱ አስር ወራት ውስጥ 5 ነጥብ 45 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ የነበረ ቢሆንም የተከናወነው ተግባር ግን 5 ነጥብ 74 ቢሊየን ብር ለማሰባሰብ አስችሏል።
ይህ አፈጻጸም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ2 ነጥብ 43 ቢሊየን ብር ወይም የ74 በመቶ የገቢ ዕድገት ያሳየ መሆኑን ምክትል ሥራ አስኪያጇ አስረድተዋል።
ለዚህ ስኬታማ ውጤት መገኘት ዋናው ምክንያት የጽሕፈት ቤቱ አመራሮች ለዕቅዱ መሳካት ያሳዩት ቁርጠኝነት መሆኑንና ሠራተኞችን በአንድ ዓላማ ሥር በማስተባበር ሌት ተቀን በቅንጅት እንዲሠሩ ማስቻላቸው እንደሆነ ተገልጿል።
ከዚህ በተጨማሪም ዕለታዊ የሥራ እንቅስቃሴዎችን በቅርብ መከታተል፣ አፈጻጸሞችን መገምገምና የሚታዩ ክፍተቶችን በወቅቱ ማረም የሚያስችል የተደራጀ የክትትልና የድጋፍ ሥርዓት መዘርጋቱ ለውጤታማነቱ ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷል።
ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ የታክስ ሕግን ፍትሐዊ በሆነ መንገድ ለማስከበር ትኩረት ሰጥቶ የሠራ ሲሆን ለግብር ከፋዮች ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት በተደረገው ጥረትም አበረታች ለውጦች መመዝገባቸው ተመልክቷል።
#የአዲስአበባገቢዎች #የካክፍለከተማ #ገቢአሰባሰብ #ታክስ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የየካ ክፍለ ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ አስር ወራት ውስጥ ፍትሐዊ የገቢ አሰባሰብ ሥርዓትን በመከተል ካቀደው ዕቅድ በላይ 105 በመቶ ማሳካት መቻሉን ገልጿል።
የቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ የታክስ ጉዳዮች ዘርፍ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ወይዘሮ መሰረት መንግስቱ እንደተናገሩት በበጀት ዓመቱ አስር ወራት ውስጥ 5 ነጥብ 45 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ የነበረ ቢሆንም የተከናወነው ተግባር ግን 5 ነጥብ 74 ቢሊየን ብር ለማሰባሰብ አስችሏል።
ይህ አፈጻጸም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ2 ነጥብ 43 ቢሊየን ብር ወይም የ74 በመቶ የገቢ ዕድገት ያሳየ መሆኑን ምክትል ሥራ አስኪያጇ አስረድተዋል።
ለዚህ ስኬታማ ውጤት መገኘት ዋናው ምክንያት የጽሕፈት ቤቱ አመራሮች ለዕቅዱ መሳካት ያሳዩት ቁርጠኝነት መሆኑንና ሠራተኞችን በአንድ ዓላማ ሥር በማስተባበር ሌት ተቀን በቅንጅት እንዲሠሩ ማስቻላቸው እንደሆነ ተገልጿል።
ከዚህ በተጨማሪም ዕለታዊ የሥራ እንቅስቃሴዎችን በቅርብ መከታተል፣ አፈጻጸሞችን መገምገምና የሚታዩ ክፍተቶችን በወቅቱ ማረም የሚያስችል የተደራጀ የክትትልና የድጋፍ ሥርዓት መዘርጋቱ ለውጤታማነቱ ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷል።
ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ የታክስ ሕግን ፍትሐዊ በሆነ መንገድ ለማስከበር ትኩረት ሰጥቶ የሠራ ሲሆን ለግብር ከፋዮች ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት በተደረገው ጥረትም አበረታች ለውጦች መመዝገባቸው ተመልክቷል።
#የአዲስአበባገቢዎች #የካክፍለከተማ #ገቢአሰባሰብ #ታክስ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
4 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) ዛሬ ምሽት በተካሄደው የምዕራቡ ዞን የፍጻሜ ማጣሪያ ሰባተኛ እና ወሳኝ ጨዋታ.. ሳን አንቶኒዮ ስፐርስ ኦክላሆማ ሲቲ ታንደርን 111 ለ 103 በሆነ ውጤት በማሸነፍ አጓጊውን ተከታታይ ፍልሚያ በድል አጠናቋል። ይህ የሁለቱ ወጣት እና ሀያል የቅርጫት ኳስ ቡድኖች ግጥሚያ፣ የብሔራዊ የቅርጫት ኳስ ማህበሩን የወደፊት እጣ ፈንታ ማን ይቆጣጠራል ለሚለው ጥያቄ ምላሽ የሰጠ ድንቅ መድረክ ነበር። አሸናፊው ስፐርስ በመጪው ረቡዕ ከኒው ዮርክ ኒክስ ጋር ታላቁን የፍጻሜ ጨዋታ ይጀምራል።
በአንጻሩ ለቀጣዮቹ አመታት የሊጉ የበላይ ይሆናል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረው ታንደር፣ ከዚህ ሽንፈት አገግሞ እንዴት ሊሻሻል እንደሚችል በቁጭት የሚያስብበት ጊዜ ላይ ደርሷል።
ይህ እጅግ ተጠባቂ ጨዋታ በዋናነት "ሻይ ጊልጀስ-አሌክሳንደር ከ ቪክቶር ዌምባንያማ" ወይም የሊጉ ኮከብ ተጫዋች ከአመቱ ምርጥ ተከላካይ ጋር የሚያደርጉት ፍልሚያ ተብሎ ተሰይሞ ነበር። ነገር ግን ዌምባንያማ አምስተኛ ጥፋቱን ሰርቶ በቅጣት ወንበር ላይ በተቀመጠበት ወሳኝ ሰዓት፣ የስፐርስ ተቀያሪ ግዙፍ ተጫዋች የሆነው ሉክ ኮርኔት ያደረገው ድንቅ የኳስ መግታት (ብሎክ) የጨዋታውን ሚዛን ሙሉ በሙሉ ወደ ሳን አንቶኒዮ አዘንብሎታል
ምንም እንኳን ዌምባንያማ አምስተኛ ጥፋቱን ሰርቶ ለመውጣት ቢገደድም፣ 22 ነጥቦችን እና 7 የተመለሱ ኳሶችን በማስቆጠር ስፐርስን በግንባር ቀደምትነት መርቷል። በሌላ በኩል ሻይ ጊልጀስ-አሌክሳንደር 35 ነጥቦችን እና 9 ኳሶችን አመቻችቶ በማቀበል የነበረበትን ከፍተኛ ጫና ለመወጣት አስደናቂ ጥረት አድርጓል።
የታንደር ሌሎች ቁልፍ ኳስ አቀጣጣዮች የሆኑት ጃለን ዊሊያምስ እና አጃይ ሚቼል በጉዳት ምክንያት ከሜዳ መራቃቸው፣ በሻይ ጊልጀስ-አሌክሳንደር ላይ እጅግ ከፍተኛ ጫና ፈጥሮበታል። ቡድኑን ወደ ፍጻሜው ለማድረስ የማይቻለውን ሁሉ ቢሞክርም፣ በዙሪያው ከነበሩት ሌሎች ተጫዋቾች በቂ ድጋፍ ማግኘት አልቻለም።
የታንደር ተቀያሪ ተጫዋቾች በተለይም ጄይሊን ዊሊያምስ 11 ነጥብ፣ 10 የተመለሱ ኳሶች እና 4 ኳሶችን በማቀበል ጥሩ ቢንቀሳቀስም፤ ቼት ሆልምግሬን ግን እጅግ ደካማ አቋም አሳይቷል። ሆልምግሬን ከሞከራቸው ሁለት ኳሶች አንዱን ብቻ በማስቆጠር 4 ነጥብ ይዞ የወጣ ሲሆን፣ ከመጀመሪያው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በኋላ ወደ ቀለበት ምንም አይነት ሙከራ አላደረገም። ዌምባንያማ በቅዳሜውም ሆነ በአጠቃላይ ተከታታይ ጨዋታዎች ላይ ሆልምግሬንን ሙሉ በሙሉ ከጨዋታ ውጪ አድርጎታል።
አሁን ሳን አንቶኒዮ ስፐርስ በሊጉ ታሪክ ምርጥ የሚባለውን የ14 ተከታታይ ጨዋታዎች የማሸነፍ ጉዞ እያደረገ ከሚገኘው ኒው ዮርክ ኒክስ ጋር በፍጻሜው ይፋለማል። ዕድሜያቸው 25 እና ከዚያ በታች የሆኑ አምስት ወጣት ተጫዋቾችን የሚያሰልፈው ስፐርስ፣ ሀያሉን ታንደርን ሊያሸንፍ ይችላል ብሎ መጠበቅ ለብዙዎች አዳጋች ነበር። አሁን ግን ተጠራጣሪዎች ሁሉ ተሳስተው የወጣቶቹ ስብስብ ታሪክ ጽፏል!
በአንጻሩ ለቀጣዮቹ አመታት የሊጉ የበላይ ይሆናል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረው ታንደር፣ ከዚህ ሽንፈት አገግሞ እንዴት ሊሻሻል እንደሚችል በቁጭት የሚያስብበት ጊዜ ላይ ደርሷል።
ይህ እጅግ ተጠባቂ ጨዋታ በዋናነት "ሻይ ጊልጀስ-አሌክሳንደር ከ ቪክቶር ዌምባንያማ" ወይም የሊጉ ኮከብ ተጫዋች ከአመቱ ምርጥ ተከላካይ ጋር የሚያደርጉት ፍልሚያ ተብሎ ተሰይሞ ነበር። ነገር ግን ዌምባንያማ አምስተኛ ጥፋቱን ሰርቶ በቅጣት ወንበር ላይ በተቀመጠበት ወሳኝ ሰዓት፣ የስፐርስ ተቀያሪ ግዙፍ ተጫዋች የሆነው ሉክ ኮርኔት ያደረገው ድንቅ የኳስ መግታት (ብሎክ) የጨዋታውን ሚዛን ሙሉ በሙሉ ወደ ሳን አንቶኒዮ አዘንብሎታል
ምንም እንኳን ዌምባንያማ አምስተኛ ጥፋቱን ሰርቶ ለመውጣት ቢገደድም፣ 22 ነጥቦችን እና 7 የተመለሱ ኳሶችን በማስቆጠር ስፐርስን በግንባር ቀደምትነት መርቷል። በሌላ በኩል ሻይ ጊልጀስ-አሌክሳንደር 35 ነጥቦችን እና 9 ኳሶችን አመቻችቶ በማቀበል የነበረበትን ከፍተኛ ጫና ለመወጣት አስደናቂ ጥረት አድርጓል።
የታንደር ሌሎች ቁልፍ ኳስ አቀጣጣዮች የሆኑት ጃለን ዊሊያምስ እና አጃይ ሚቼል በጉዳት ምክንያት ከሜዳ መራቃቸው፣ በሻይ ጊልጀስ-አሌክሳንደር ላይ እጅግ ከፍተኛ ጫና ፈጥሮበታል። ቡድኑን ወደ ፍጻሜው ለማድረስ የማይቻለውን ሁሉ ቢሞክርም፣ በዙሪያው ከነበሩት ሌሎች ተጫዋቾች በቂ ድጋፍ ማግኘት አልቻለም።
የታንደር ተቀያሪ ተጫዋቾች በተለይም ጄይሊን ዊሊያምስ 11 ነጥብ፣ 10 የተመለሱ ኳሶች እና 4 ኳሶችን በማቀበል ጥሩ ቢንቀሳቀስም፤ ቼት ሆልምግሬን ግን እጅግ ደካማ አቋም አሳይቷል። ሆልምግሬን ከሞከራቸው ሁለት ኳሶች አንዱን ብቻ በማስቆጠር 4 ነጥብ ይዞ የወጣ ሲሆን፣ ከመጀመሪያው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በኋላ ወደ ቀለበት ምንም አይነት ሙከራ አላደረገም። ዌምባንያማ በቅዳሜውም ሆነ በአጠቃላይ ተከታታይ ጨዋታዎች ላይ ሆልምግሬንን ሙሉ በሙሉ ከጨዋታ ውጪ አድርጎታል።
አሁን ሳን አንቶኒዮ ስፐርስ በሊጉ ታሪክ ምርጥ የሚባለውን የ14 ተከታታይ ጨዋታዎች የማሸነፍ ጉዞ እያደረገ ከሚገኘው ኒው ዮርክ ኒክስ ጋር በፍጻሜው ይፋለማል። ዕድሜያቸው 25 እና ከዚያ በታች የሆኑ አምስት ወጣት ተጫዋቾችን የሚያሰልፈው ስፐርስ፣ ሀያሉን ታንደርን ሊያሸንፍ ይችላል ብሎ መጠበቅ ለብዙዎች አዳጋች ነበር። አሁን ግን ተጠራጣሪዎች ሁሉ ተሳስተው የወጣቶቹ ስብስብ ታሪክ ጽፏል!
8 days ago
ጤና ሚኒስቴር ከጣሊያን ሀገር የመጡ በጎ ፈቃደኛ ሐኪሞች ላከናወኑት የሕፃናት ነጻ የልብ ቀዶ ሕክምና ምስጋናና ዕውቅና ሰጠ
የጤና ሚኒስቴር በኸርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ አማካይነት ከጣልያን ሀገር የመጡ በጎ ፈቃደኛ ባለሙያዎች፣ ከኢትዮ ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል የሕክምና ባለሙያዎች ጋር በመቀናጀት 80 የልብ ሕሙማን ሕፃናት በሁለት ጊዜ ምልልስ
በ15 ቀናት ጊዜያት ውስጥ የነጻ ቀዶ ሕክምና አገልግሎት
በመስጠታቸው የምስጋናና የእውቅና ሠርተፊኬት ሰጠ።
ትላንት ግንቦት 18/2018 ዓ.ም በአራዳ ፓርክ በተከናወነው መርሐግብር ባለሙያዎቹ አገልግሎቱን የሰጡት በሁለት ዙር ተልእኮ መኾኑ የተጠቀሰ ሲሆን 48 ሕፃናት በአዲስ አበባ ኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታል፣ 9 ሕፃናት በጂግጂጋ እንዲሁም 23 ሕፃናት በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል (በጎንደር ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰጠ) የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መኾናቸው ተነግሯል።
በመርሐግብሩ ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስቴር ሚንስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ለተሰጠው አገልግሎት በጤና ሚኒስቴር፣ በራሳቸው ስምና ከሁሉም በላይ በዚህ ሕክምና ተጠቃሚ በሆነው ማህበረሰብ ስም ላቅ ያለ ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን ይህ መልካም ተግባር ቀጣይነት እንዲኖረው የአደራ መልዕክት አስተላልፈዋል። በቀጣይም ለሚከናወኑ መሰል ተግባራት ጤና ሚኒስቴርም አስፈላጊውን ድጋፍ የሚያደርግ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ለዚህ ዓላማ መሳካት አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት በተለይም ለኸርት ቱ ኸርት ችልድረን ኤይድ በገንዘብ እና በቴክኒክ ላበረከተው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ይህ የበጎ ፈቃድ አገልግከሎት በ45 ቀናት ለ175 ሕፃናት የልብ ቀዶ ሕክምና ለመስጠት በጤና ሚኒስቴር፣ በኸርት ቱ ኸርት ችልድረንስ ኤይድ እና በተለያዩ የመንግስትና የግል ተቋማት መካከል የተደረገ ስምምነት አካል ነው።
አቶ ብርሃን ተድላ የኸርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ በበኩላቸው የጤና ሚኒስቴር የተከናወነውን የበጎ ተግባር ትልቅ ዋጋ መስጠቱ ሌሎችም ተመሳሳይ ተልእኮዎች በአርአያነት የሚታይ መሆኑን ጠቅሰዋል። ኽርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ በገባው ቃል መሰረት ስራዎቹ በአጭር ጊዜያት እንደሚያጠናቅቅም አቶ ብርሃን ተናግረዋል።
በአጠቃላይ ለስራው የስምምነቱ አካል የኾኑ የመንግስት፣ የግል ሆስፒታሎችና የጤና ተቋማት ያበረከቱት አስተዋጽኦ እጅግ ከፍተኛ መኾኑን በማስታወስ የስራው አጠቃላይ ሪፖርት እኤአ ጁን 10 ከተጠናቀቀ በኋላ ሌላ የምስጋና መርሐግብር እንደሚኖር ዶ/ር አስቻለው ወርቁ የጤና ሚኒስቴር አማካሪ አረጋግጠዋል።
የጤና ሚኒስቴር በኸርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ አማካይነት ከጣልያን ሀገር የመጡ በጎ ፈቃደኛ ባለሙያዎች፣ ከኢትዮ ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል የሕክምና ባለሙያዎች ጋር በመቀናጀት 80 የልብ ሕሙማን ሕፃናት በሁለት ጊዜ ምልልስ
በ15 ቀናት ጊዜያት ውስጥ የነጻ ቀዶ ሕክምና አገልግሎት
በመስጠታቸው የምስጋናና የእውቅና ሠርተፊኬት ሰጠ።
ትላንት ግንቦት 18/2018 ዓ.ም በአራዳ ፓርክ በተከናወነው መርሐግብር ባለሙያዎቹ አገልግሎቱን የሰጡት በሁለት ዙር ተልእኮ መኾኑ የተጠቀሰ ሲሆን 48 ሕፃናት በአዲስ አበባ ኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታል፣ 9 ሕፃናት በጂግጂጋ እንዲሁም 23 ሕፃናት በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል (በጎንደር ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰጠ) የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መኾናቸው ተነግሯል።
በመርሐግብሩ ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስቴር ሚንስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ለተሰጠው አገልግሎት በጤና ሚኒስቴር፣ በራሳቸው ስምና ከሁሉም በላይ በዚህ ሕክምና ተጠቃሚ በሆነው ማህበረሰብ ስም ላቅ ያለ ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን ይህ መልካም ተግባር ቀጣይነት እንዲኖረው የአደራ መልዕክት አስተላልፈዋል። በቀጣይም ለሚከናወኑ መሰል ተግባራት ጤና ሚኒስቴርም አስፈላጊውን ድጋፍ የሚያደርግ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ለዚህ ዓላማ መሳካት አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት በተለይም ለኸርት ቱ ኸርት ችልድረን ኤይድ በገንዘብ እና በቴክኒክ ላበረከተው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ይህ የበጎ ፈቃድ አገልግከሎት በ45 ቀናት ለ175 ሕፃናት የልብ ቀዶ ሕክምና ለመስጠት በጤና ሚኒስቴር፣ በኸርት ቱ ኸርት ችልድረንስ ኤይድ እና በተለያዩ የመንግስትና የግል ተቋማት መካከል የተደረገ ስምምነት አካል ነው።
አቶ ብርሃን ተድላ የኸርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ በበኩላቸው የጤና ሚኒስቴር የተከናወነውን የበጎ ተግባር ትልቅ ዋጋ መስጠቱ ሌሎችም ተመሳሳይ ተልእኮዎች በአርአያነት የሚታይ መሆኑን ጠቅሰዋል። ኽርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ በገባው ቃል መሰረት ስራዎቹ በአጭር ጊዜያት እንደሚያጠናቅቅም አቶ ብርሃን ተናግረዋል።
በአጠቃላይ ለስራው የስምምነቱ አካል የኾኑ የመንግስት፣ የግል ሆስፒታሎችና የጤና ተቋማት ያበረከቱት አስተዋጽኦ እጅግ ከፍተኛ መኾኑን በማስታወስ የስራው አጠቃላይ ሪፖርት እኤአ ጁን 10 ከተጠናቀቀ በኋላ ሌላ የምስጋና መርሐግብር እንደሚኖር ዶ/ር አስቻለው ወርቁ የጤና ሚኒስቴር አማካሪ አረጋግጠዋል።
Sponsored by
Surafel
8 days ago
ጤና ሚኒስቴር ከጣሊያን ሀገር የመጡ በጎ ፈቃደኛ ሐኪሞች ላከናወኑት የሕፃናት ነጻ የልብ ቀዶ ሕክምና ምስጋናና ዕውቅና ሰጠ
#ethiopia | የጤና ሚኒስቴር በኸርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ አማካይነት ከጣልያን ሀገር የመጡ በጎ ፈቃደኛ ባለሙያዎች፣ ከኢትዮ ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል የሕክምና ባለሙያዎች ጋር በመቀናጀት 80 የልብ ሕሙማን ሕፃናት በሁለት ጊዜ ምልልስ በ15 ቀናት ጊዜያት ውስጥ የነጻ ቀዶ ሕክምና አገልግሎት በመስጠታቸው የምስጋናና የእውቅና ሠርተፊኬት ሰጠ።
ትላንት ግንቦት 18/2018 ዓ.ም በአራዳ ፓርክ በተከናወነው መርሐግብር ባለሙያዎቹ አገልግሎቱን የሰጡት በሁለት ዙር ተልእኮ መኾኑ የተጠቀሰ ሲሆን 48 ሕፃናት በአዲስ አበባ ኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታል፣ 9 ሕፃናት በጂግጂጋ እንዲሁም 23 ሕፃናት በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል (በጎንደር ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰጠ) የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መኾናቸው ተነግሯል።
በመርሐግብሩ ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስቴር ሚንስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ለተሰጠው አገልግሎት በጤና ሚኒስቴር፣ በራሳቸው ስምና ከሁሉም በላይ በዚህ ሕክምና ተጠቃሚ በሆነው ማህበረሰብ ስም ላቅ ያለ ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን ይህ መልካም ተግባር ቀጣይነት እንዲኖረው የአደራ መልዕክት አስተላልፈዋል። በቀጣይም ለሚከናወኑ መሰል ተግባራት ጤና ሚኒስቴርም አስፈላጊውን ድጋፍ የሚያደርግ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ለዚህ ዓላማ መሳካት አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት በተለይም ለኸርት ቱ ኸርት ችልድረን ኤይድ በገንዘብ እና በቴክኒክ ላበረከተው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ይህ የበጎ ፈቃድ አገልግከሎት በ45 ቀናት ለ175 ሕፃናት የልብ ቀዶ ሕክምና ለመስጠት በጤና ሚኒስቴር፣ በኸርት ቱ ኸርት ችልድረንስ ኤይድ እና በተለያዩ የመንግስትና የግል ተቋማት መካከል የተደረገ ስምምነት አካል ነው።
አቶ ብርሃን ተድላ የኸርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ በበኩላቸው የጤና ሚኒስቴር የተከናወነውን የበጎ ተግባር ትልቅ ዋጋ መስጠቱ ሌሎችም ተመሳሳይ ተልእኮዎች በአርአያነት የሚታይ መሆኑን ጠቅሰዋል። ኽርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ በገባው ቃል መሰረት ስራዎቹ በአጭር ጊዜያት እንደሚያጠናቅቅም አቶ ብርሃን ተናግረዋል።
በአጠቃላይ ለስራው የስምምነቱ አካል የኾኑ የመንግስት፣ የግል ሆስፒታሎችና የጤና ተቋማት ያበረከቱት አስተዋጽኦ እጅግ ከፍተኛ መኾኑን በማስታወስ የስራው አጠቃላይ ሪፖርት እኤአ ጁን 10 ከተጠናቀቀ በኋላ ሌላ የምስጋና መርሐግብር እንደሚኖር ዶ/ር አስቻለው ወርቁ የጤና ሚኒስቴር አማካሪ አረጋግጠዋል።
#ethiopia | የጤና ሚኒስቴር በኸርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ አማካይነት ከጣልያን ሀገር የመጡ በጎ ፈቃደኛ ባለሙያዎች፣ ከኢትዮ ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል የሕክምና ባለሙያዎች ጋር በመቀናጀት 80 የልብ ሕሙማን ሕፃናት በሁለት ጊዜ ምልልስ በ15 ቀናት ጊዜያት ውስጥ የነጻ ቀዶ ሕክምና አገልግሎት በመስጠታቸው የምስጋናና የእውቅና ሠርተፊኬት ሰጠ።
ትላንት ግንቦት 18/2018 ዓ.ም በአራዳ ፓርክ በተከናወነው መርሐግብር ባለሙያዎቹ አገልግሎቱን የሰጡት በሁለት ዙር ተልእኮ መኾኑ የተጠቀሰ ሲሆን 48 ሕፃናት በአዲስ አበባ ኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታል፣ 9 ሕፃናት በጂግጂጋ እንዲሁም 23 ሕፃናት በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል (በጎንደር ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰጠ) የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መኾናቸው ተነግሯል።
በመርሐግብሩ ላይ የተገኙት የጤና ሚኒስቴር ሚንስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ለተሰጠው አገልግሎት በጤና ሚኒስቴር፣ በራሳቸው ስምና ከሁሉም በላይ በዚህ ሕክምና ተጠቃሚ በሆነው ማህበረሰብ ስም ላቅ ያለ ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን ይህ መልካም ተግባር ቀጣይነት እንዲኖረው የአደራ መልዕክት አስተላልፈዋል። በቀጣይም ለሚከናወኑ መሰል ተግባራት ጤና ሚኒስቴርም አስፈላጊውን ድጋፍ የሚያደርግ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ለዚህ ዓላማ መሳካት አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት በተለይም ለኸርት ቱ ኸርት ችልድረን ኤይድ በገንዘብ እና በቴክኒክ ላበረከተው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ይህ የበጎ ፈቃድ አገልግከሎት በ45 ቀናት ለ175 ሕፃናት የልብ ቀዶ ሕክምና ለመስጠት በጤና ሚኒስቴር፣ በኸርት ቱ ኸርት ችልድረንስ ኤይድ እና በተለያዩ የመንግስትና የግል ተቋማት መካከል የተደረገ ስምምነት አካል ነው።
አቶ ብርሃን ተድላ የኸርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ በበኩላቸው የጤና ሚኒስቴር የተከናወነውን የበጎ ተግባር ትልቅ ዋጋ መስጠቱ ሌሎችም ተመሳሳይ ተልእኮዎች በአርአያነት የሚታይ መሆኑን ጠቅሰዋል። ኽርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ በገባው ቃል መሰረት ስራዎቹ በአጭር ጊዜያት እንደሚያጠናቅቅም አቶ ብርሃን ተናግረዋል።
በአጠቃላይ ለስራው የስምምነቱ አካል የኾኑ የመንግስት፣ የግል ሆስፒታሎችና የጤና ተቋማት ያበረከቱት አስተዋጽኦ እጅግ ከፍተኛ መኾኑን በማስታወስ የስራው አጠቃላይ ሪፖርት እኤአ ጁን 10 ከተጠናቀቀ በኋላ ሌላ የምስጋና መርሐግብር እንደሚኖር ዶ/ር አስቻለው ወርቁ የጤና ሚኒስቴር አማካሪ አረጋግጠዋል።
8 days ago
ቀኝ አዝማች በኩረ ምዕመናን ትዛዙ ኮሬ የኢትዮጵያን ባህል፣ ቱሪዝምና በጎ አድራጎት በማስፋፋት የሚታወቁ ታዋቂ ኢንተርፕረነር፣ የባህል አምባሳደር እና ሀገር በቀል ሽማግሌ ናቸው። በተለይም በኢትዮጵያ የመጀመሪያዎቹን እና ግዙፍ የባህል ምግብ ቤቶች አንዱ የሆነውን ዮድ አቢሲኒያ (Yod Abyssinia) ባህላዊ ምግብ ቤት በመመስረታቸው በሰፊው ይታወቃሉ።
ስለ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ ዋና ዋና መረጃዎች
የዮድ አቢሲኒያ መስራችና ባለቤት በ1996 ዓ.ም.
(እ.ኤ.አ. በ2003) ዮድ አቢሲኒያ ባህላዊ ምግብ ቤትን መስርተዋል።
ምግብ ቤቱ የኢትዮጵያን ብሔር ብሔረሰቦች ባህላዊ ምግቦች፣ ሙዚቃዎች እና ውዝዋዜዎች ለአገር ውስጥና ለውጭ አገር ዜጎች በማስተዋወቅ ረገድ ትልቅ ሚና አለው።
እንደ የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ያሉ በርካታ የዓለም መሪዎችን እና የውጭ አገር ዲፕሎማቶችን በምግብ ቤታቸው አስተናግደዋል።
❸ማኅበራዊ አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ማኅበራዊ አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ለተለያዩ የሃይማኖት ተቋማት እና ችግረኛ ወገኖች ከፍተኛ ድጋፍ በማድረግ ይታወቃሉ።
በበጎ አድራጎት ሥራዎቻቸው ምክንያት በ2016 ዓ.ም የፊላንትሮፒ (የበጎ አድራጎት) ሽልማት አሸናፊ ሆነዋል።
በማኅበረሰቡ ውስጥ ሰላምን ለማስፈንና እርቅ ለማውረድ እንደ ትልቅ የሀገር ሽማግሌ ሆነው ያገለግላሉ።
በጎ ተግባራት እና ማህበራዊ ሀላፊነት በመወጣት አርዓያነት ያለዉን ተግባራት በመስራት ይታወቃል።
የዓመቱን 360 ቀናት ለኢትዮጵያ ሀገራቸዉ እንዲሁም 4 ቀናት ለበጎ አድራጎት ተግባራት ሲውል ፤ 365 ኛውን ቀን ደግሞ ዕድገት እንደሚያስተዋዉቅ የሚያምኑት የድርጅቱ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ ናቸዉ።
የዮድ አቢሲኒያ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ እንዲሁም ድርጅታቸዉ 'ዮድ አቢሲኒያ'ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር፣ ለሜሪጆይ ኢትዮጵያ ፣ ለቶራ የህፃናት ማሳደጊያ ፣ ለሰሊሆም የአእምሮ ህሙማን መርጃ ፣ ለየወደቁትን እናንሳ የአረጋውያን መርጃ ማህበር ለሌሎችም በማገዝና በመርዳት ማህበራዊ ኃላፊነትን በመወጣት በጎ ስምና አርዓያነትን በተግባር ለማሳየት ችሏል።ወደፊትም ይበልጥ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
❹እዉቅናና ሽልማት
➢የዓመቱ በጎ ሰዉ ሽልማትና እዉቅና
ጳጉሜ 3 ቀን 2016 ዓ.ም ለ12ኛ ጊዜ በተካሄደዉ የዓመቱ በጎ ሰዉ ሽልማትና እዉቅና በቅርስ ባህል እና ቱሪዝም ዘርፍ ዮድ አቢሲኒያ፡የባሕል ምግብ አዳራሽ ተሸልሟል።
የኢትዮጵያን ባህላዊ ምግቦችን ፤ ውዝዋዜዎችን እና ባህላዊ እሴቶችን ለቱሪስቶች እና ማህበረሰቡ የሚያቀርብ ተቋም ሲሆን የኢትዮጵያን እሴቶችን በማስተዋወቅ ረገድ ያስቀመጠው ደማቅ አሻራ ከፍ ያለ ነዉ።
ዮድ አቢሲኒያ ባህል ባንድ
ለቱሪስቶች የአገራችንን ብሔር ብሔረሰቦች ሙዚቃዎች ዉዝዋዜን በማሳየት ቱባ ባህላችንን ሳይበረዝና ሳይከለስ ያሳያል።
➢ የቱሪዝም አዋርድ
የአዲስ አበባ ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ሐምሌ 6/2016ዓ.ም በአድዋ መታሰብያ ሙዚየም ባካሄደው የኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ትራንስፎርሜሽን ምክር ቤት ምስረታና 1ኛ መደበኛ ጉባኤ ለከተማችን የቱሪዝም ልማትና እድገት የላቀ አስተዋጽኦ ላደረጉ የቱሪዝም ተቋማትና አካላት የቱሪዝም አዋርድ ከተሰጡት መካከል አንዱ ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ ነዉ።
የቱሪዝም ተቋማቱ በሚሰጡት የአገልግሎት ጥራት ባላቸው የቱሪዝም ፈጠራ ስራ እንዲሁም የቱሪስት አያያዝና የመሳሰሉት መስፈርቶችን መነሻ በማድረግ ከዘርፉ 1ኛ በመዉጣት ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ፣የቱሪዝም አዋርድ ተሸልሟል።
➢"የ8ኛዉ የአርአያ ሰው ሽልማት"
ተቀማጭነቱን በሀገረ አሜሪካ ዳላስ ቴክሳስ ያደረገው ዓድዋ የባህልና የታሪክ ኅብረት ለትርፍ ያልተቋቋመ ግብረ ሰናይ ድርጅት ሲሆን በዋናነትም ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን አርአያ የሚሆን ሥራ ለሚሠሩ ግለሰቦችና ተቋማት"የአርአያ ሰው ሽልማት" በሚል ዕውቅና ይሰጣል፡፡
ለ8ኛ ግዜ በአዲስ አበባ ዮድ አቢሲኒያ የባህል አዳራሽ ሰኔ 13 ቀን 2016 ዓ.ም በተመሳሳይ መልኩ ለሀገር ባለውለታዎች በተለይም በባህል ልማት፣ በተፈጥሮ ጥበቃ፣ በቱሪዝም እና ቅርስ እንዲሁም በታሪክ መስኮች ለሀገራቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱ ግለሰቦችና ተቋማት ሽልማት ከተሰጣቸው መካከል ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ አንዱ ነዉ።
ዓለም አቀፍ እውቅና
የኢትዮጵያን ባህልና ቱሪዝም በዓለም አቀፍ ደረጃ በማስተዋወቃቸው “የባህልና ቱሪዝም አምባሳደር” የሚል ክብር ተሰጥቷቸዋል።
በቅርቡ (እ.ኤ.አ በ2025) በአሜሪካ ሲያትል በተካሄደው የ42ኛው የኢትዮጵያውያን የስፖርትና ባህል ፌስቲቫል (ESFNA) ላይ ለሀገራቸው ላበረከቱት የላቀ አስተዋፅኦ ልዩ የክብር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
❺ዋና ዋና ቅርንጫፎችና አድራሻዎች
ዮድ አቢሲኒያ በአዲስ አበባ በተለያዩ ቁልፍ ቦታዎች ቅርንጫፎችን ከፍቶ ይገኛል፦
ቦሌ ቅርንጫፍ (ዋናው)፦ ቦሌ መድኃኔዓለም አካባቢ፣ ከብራስ ሆስፒታል ከፍ ብሎ የሚገኝ የነበረ ሲሆን አሁን ቀድሞ ከነበረበት በ100 ሜትር ገባ ብሎ ኬኬር ህንፃ አጠገብ ይገኛል።ለቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቅርብ በመሆኑ ለቱሪስቶች ተመራጭ ነው።
ፒያሳ (ቴዎድሮስ አደባባይ) ቅርንጫፍ፦ በቅርቡ በዲል ፕላዛ ፊት ለፊት የተከፈተ አዲስና ዘመናዊ የባህል አዳራሽ፣ የስፖርት ባር (Sport Bar) እና የባዛር ማዕከል ነው።
ዮድ አቢሲኒያ ኢንተርናሽናል ሆቴል፦ ሰዓሊተ ምህረት አደባባይ ከፍ ብሎ፣ ወደ ወሰን በሚወስደው መንገድ ማዕድን ሚኒስቴር አጠገብ የሚገኝ ዘመናዊ ሆቴል ነው።
❻የ"ዮድ" መሪ ቃል በተግባር
የድርጅቱ መሪ ቃል የሃገራችን ኢትዮጵያን ”ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ ” የሚል ነው ባለፉት 22 ዓመታት የኢትዮጵያን ባህልና መስተንግዶን ጨምሮ ሲያስተዋውቅ ኖሯል ፡፡ ለዚህም አስተዋፅኦው ”የኢትዮጵያ የባህልና የቱሪዝም አምባሳደር” የሚል ዕውቅና ከመንግስት ተሰጥቶታል ፡፡
“ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ” በሚል መርህ ከመላው ዓለም ወደ ሃገራችን ለመጡ እንግዶች የባህል ምግብና መጠጦች መስተንግዶ በመስጠት ፣ የብሔር ብሄረሰቦችን ሙዚቃዎችና ውዝዋዜዎች በማቅረብ ፣ የሀገራችንን የታሪክ የባህልና የቱሪዝም ሃብቶችና ቅርሶቻችንን በማስተዋወቅ የኢትዮጵያን መልካም ገፅታ በመገንባት ብዙ በመስራት ”የኢትዮጵያ የባህል እና የቱሪዝም አምባሳደር” የሚል እውቅናን ለማግኘት ችሏል፡፡
"ዮድ"
ዮድ ብሂል የማነ እግዚአብሔር ገብረት ኃይለ
በእግዚአብሔር ቀኝ ያለ እሱ ኃያልና
ጽኑዕ የሆነ ነው ማለት በሌላ መልኩ"ዮድ" ማለት በጉራጌ ቋንቋ "መመስከር ወይም መናገር" ማለት ነዉ።
ከ1996ዓ.ምማለትምላለፉት 22 ዓመታት በተለያዩ ወቅቶች ወደ ሀገራችን የመጡ በርካታ የሀገራት መሪዎችን ፣ ዲፕሎማቶችን ፣ የዓለም ታላላቅ ሰዎችን፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ፣ ታዋቂ ሰዎች ፣ ባለሀብቶች ፣ አትሌቶች ፣ አርቲስቶች የሚዲያ ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎችም በሺዎች የሚቆጠሩ ቱሪስቶችንና ኢትዮጵያዊያን እንግዶችን ተቀብሎ በፍቅርና በአክብሮት ሲያስተናግድ የቆየው ዮድ አቢሲኒያ በቀጣይም በሀገራችን ለሚከናወኑ ታላላቅ ሁነቶች ሙሉ አገልግሎት ለመስጠት ከወትሮው በተለዬ አኳኋን መዘጋጀቱ ተስተዉሏል።በ500 ብር ካፒታል እና በአነስተኛ የስራ ጅምር በጥረት የተገነባ ካምፓኒ በበርካታ ፈተናዎች ዉስጥ አልፎ ዛሬ በርካታ ቁጥር ላላቸዉ ወገኖቻችን የስራ ዕድል መፍጠር የቻለ ግዙፍ ኩባንያ ለመሆን በቅቷል።
"የሃገራችን ኢትዮጵያን ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ ”ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ
ዘጋቢ ጋዜጠኛ ሲሳይ መንግስቴ
ስለ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ ዋና ዋና መረጃዎች
የዮድ አቢሲኒያ መስራችና ባለቤት በ1996 ዓ.ም.
(እ.ኤ.አ. በ2003) ዮድ አቢሲኒያ ባህላዊ ምግብ ቤትን መስርተዋል።
ምግብ ቤቱ የኢትዮጵያን ብሔር ብሔረሰቦች ባህላዊ ምግቦች፣ ሙዚቃዎች እና ውዝዋዜዎች ለአገር ውስጥና ለውጭ አገር ዜጎች በማስተዋወቅ ረገድ ትልቅ ሚና አለው።
እንደ የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ያሉ በርካታ የዓለም መሪዎችን እና የውጭ አገር ዲፕሎማቶችን በምግብ ቤታቸው አስተናግደዋል።
❸ማኅበራዊ አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ማኅበራዊ አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ለተለያዩ የሃይማኖት ተቋማት እና ችግረኛ ወገኖች ከፍተኛ ድጋፍ በማድረግ ይታወቃሉ።
በበጎ አድራጎት ሥራዎቻቸው ምክንያት በ2016 ዓ.ም የፊላንትሮፒ (የበጎ አድራጎት) ሽልማት አሸናፊ ሆነዋል።
በማኅበረሰቡ ውስጥ ሰላምን ለማስፈንና እርቅ ለማውረድ እንደ ትልቅ የሀገር ሽማግሌ ሆነው ያገለግላሉ።
በጎ ተግባራት እና ማህበራዊ ሀላፊነት በመወጣት አርዓያነት ያለዉን ተግባራት በመስራት ይታወቃል።
የዓመቱን 360 ቀናት ለኢትዮጵያ ሀገራቸዉ እንዲሁም 4 ቀናት ለበጎ አድራጎት ተግባራት ሲውል ፤ 365 ኛውን ቀን ደግሞ ዕድገት እንደሚያስተዋዉቅ የሚያምኑት የድርጅቱ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ ናቸዉ።
የዮድ አቢሲኒያ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ እንዲሁም ድርጅታቸዉ 'ዮድ አቢሲኒያ'ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር፣ ለሜሪጆይ ኢትዮጵያ ፣ ለቶራ የህፃናት ማሳደጊያ ፣ ለሰሊሆም የአእምሮ ህሙማን መርጃ ፣ ለየወደቁትን እናንሳ የአረጋውያን መርጃ ማህበር ለሌሎችም በማገዝና በመርዳት ማህበራዊ ኃላፊነትን በመወጣት በጎ ስምና አርዓያነትን በተግባር ለማሳየት ችሏል።ወደፊትም ይበልጥ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
❹እዉቅናና ሽልማት
➢የዓመቱ በጎ ሰዉ ሽልማትና እዉቅና
ጳጉሜ 3 ቀን 2016 ዓ.ም ለ12ኛ ጊዜ በተካሄደዉ የዓመቱ በጎ ሰዉ ሽልማትና እዉቅና በቅርስ ባህል እና ቱሪዝም ዘርፍ ዮድ አቢሲኒያ፡የባሕል ምግብ አዳራሽ ተሸልሟል።
የኢትዮጵያን ባህላዊ ምግቦችን ፤ ውዝዋዜዎችን እና ባህላዊ እሴቶችን ለቱሪስቶች እና ማህበረሰቡ የሚያቀርብ ተቋም ሲሆን የኢትዮጵያን እሴቶችን በማስተዋወቅ ረገድ ያስቀመጠው ደማቅ አሻራ ከፍ ያለ ነዉ።
ዮድ አቢሲኒያ ባህል ባንድ
ለቱሪስቶች የአገራችንን ብሔር ብሔረሰቦች ሙዚቃዎች ዉዝዋዜን በማሳየት ቱባ ባህላችንን ሳይበረዝና ሳይከለስ ያሳያል።
➢ የቱሪዝም አዋርድ
የአዲስ አበባ ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ሐምሌ 6/2016ዓ.ም በአድዋ መታሰብያ ሙዚየም ባካሄደው የኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ትራንስፎርሜሽን ምክር ቤት ምስረታና 1ኛ መደበኛ ጉባኤ ለከተማችን የቱሪዝም ልማትና እድገት የላቀ አስተዋጽኦ ላደረጉ የቱሪዝም ተቋማትና አካላት የቱሪዝም አዋርድ ከተሰጡት መካከል አንዱ ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ ነዉ።
የቱሪዝም ተቋማቱ በሚሰጡት የአገልግሎት ጥራት ባላቸው የቱሪዝም ፈጠራ ስራ እንዲሁም የቱሪስት አያያዝና የመሳሰሉት መስፈርቶችን መነሻ በማድረግ ከዘርፉ 1ኛ በመዉጣት ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ፣የቱሪዝም አዋርድ ተሸልሟል።
➢"የ8ኛዉ የአርአያ ሰው ሽልማት"
ተቀማጭነቱን በሀገረ አሜሪካ ዳላስ ቴክሳስ ያደረገው ዓድዋ የባህልና የታሪክ ኅብረት ለትርፍ ያልተቋቋመ ግብረ ሰናይ ድርጅት ሲሆን በዋናነትም ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን አርአያ የሚሆን ሥራ ለሚሠሩ ግለሰቦችና ተቋማት"የአርአያ ሰው ሽልማት" በሚል ዕውቅና ይሰጣል፡፡
ለ8ኛ ግዜ በአዲስ አበባ ዮድ አቢሲኒያ የባህል አዳራሽ ሰኔ 13 ቀን 2016 ዓ.ም በተመሳሳይ መልኩ ለሀገር ባለውለታዎች በተለይም በባህል ልማት፣ በተፈጥሮ ጥበቃ፣ በቱሪዝም እና ቅርስ እንዲሁም በታሪክ መስኮች ለሀገራቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱ ግለሰቦችና ተቋማት ሽልማት ከተሰጣቸው መካከል ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ አንዱ ነዉ።
ዓለም አቀፍ እውቅና
የኢትዮጵያን ባህልና ቱሪዝም በዓለም አቀፍ ደረጃ በማስተዋወቃቸው “የባህልና ቱሪዝም አምባሳደር” የሚል ክብር ተሰጥቷቸዋል።
በቅርቡ (እ.ኤ.አ በ2025) በአሜሪካ ሲያትል በተካሄደው የ42ኛው የኢትዮጵያውያን የስፖርትና ባህል ፌስቲቫል (ESFNA) ላይ ለሀገራቸው ላበረከቱት የላቀ አስተዋፅኦ ልዩ የክብር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
❺ዋና ዋና ቅርንጫፎችና አድራሻዎች
ዮድ አቢሲኒያ በአዲስ አበባ በተለያዩ ቁልፍ ቦታዎች ቅርንጫፎችን ከፍቶ ይገኛል፦
ቦሌ ቅርንጫፍ (ዋናው)፦ ቦሌ መድኃኔዓለም አካባቢ፣ ከብራስ ሆስፒታል ከፍ ብሎ የሚገኝ የነበረ ሲሆን አሁን ቀድሞ ከነበረበት በ100 ሜትር ገባ ብሎ ኬኬር ህንፃ አጠገብ ይገኛል።ለቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቅርብ በመሆኑ ለቱሪስቶች ተመራጭ ነው።
ፒያሳ (ቴዎድሮስ አደባባይ) ቅርንጫፍ፦ በቅርቡ በዲል ፕላዛ ፊት ለፊት የተከፈተ አዲስና ዘመናዊ የባህል አዳራሽ፣ የስፖርት ባር (Sport Bar) እና የባዛር ማዕከል ነው።
ዮድ አቢሲኒያ ኢንተርናሽናል ሆቴል፦ ሰዓሊተ ምህረት አደባባይ ከፍ ብሎ፣ ወደ ወሰን በሚወስደው መንገድ ማዕድን ሚኒስቴር አጠገብ የሚገኝ ዘመናዊ ሆቴል ነው።
❻የ"ዮድ" መሪ ቃል በተግባር
የድርጅቱ መሪ ቃል የሃገራችን ኢትዮጵያን ”ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ ” የሚል ነው ባለፉት 22 ዓመታት የኢትዮጵያን ባህልና መስተንግዶን ጨምሮ ሲያስተዋውቅ ኖሯል ፡፡ ለዚህም አስተዋፅኦው ”የኢትዮጵያ የባህልና የቱሪዝም አምባሳደር” የሚል ዕውቅና ከመንግስት ተሰጥቶታል ፡፡
“ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ” በሚል መርህ ከመላው ዓለም ወደ ሃገራችን ለመጡ እንግዶች የባህል ምግብና መጠጦች መስተንግዶ በመስጠት ፣ የብሔር ብሄረሰቦችን ሙዚቃዎችና ውዝዋዜዎች በማቅረብ ፣ የሀገራችንን የታሪክ የባህልና የቱሪዝም ሃብቶችና ቅርሶቻችንን በማስተዋወቅ የኢትዮጵያን መልካም ገፅታ በመገንባት ብዙ በመስራት ”የኢትዮጵያ የባህል እና የቱሪዝም አምባሳደር” የሚል እውቅናን ለማግኘት ችሏል፡፡
"ዮድ"
ዮድ ብሂል የማነ እግዚአብሔር ገብረት ኃይለ
በእግዚአብሔር ቀኝ ያለ እሱ ኃያልና
ጽኑዕ የሆነ ነው ማለት በሌላ መልኩ"ዮድ" ማለት በጉራጌ ቋንቋ "መመስከር ወይም መናገር" ማለት ነዉ።
ከ1996ዓ.ምማለትምላለፉት 22 ዓመታት በተለያዩ ወቅቶች ወደ ሀገራችን የመጡ በርካታ የሀገራት መሪዎችን ፣ ዲፕሎማቶችን ፣ የዓለም ታላላቅ ሰዎችን፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ፣ ታዋቂ ሰዎች ፣ ባለሀብቶች ፣ አትሌቶች ፣ አርቲስቶች የሚዲያ ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎችም በሺዎች የሚቆጠሩ ቱሪስቶችንና ኢትዮጵያዊያን እንግዶችን ተቀብሎ በፍቅርና በአክብሮት ሲያስተናግድ የቆየው ዮድ አቢሲኒያ በቀጣይም በሀገራችን ለሚከናወኑ ታላላቅ ሁነቶች ሙሉ አገልግሎት ለመስጠት ከወትሮው በተለዬ አኳኋን መዘጋጀቱ ተስተዉሏል።በ500 ብር ካፒታል እና በአነስተኛ የስራ ጅምር በጥረት የተገነባ ካምፓኒ በበርካታ ፈተናዎች ዉስጥ አልፎ ዛሬ በርካታ ቁጥር ላላቸዉ ወገኖቻችን የስራ ዕድል መፍጠር የቻለ ግዙፍ ኩባንያ ለመሆን በቅቷል።
"የሃገራችን ኢትዮጵያን ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ ”ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ
ዘጋቢ ጋዜጠኛ ሲሳይ መንግስቴ
8 days ago
ከ6ሺ በላይ ለሚሆኑ የአዕምሮ ህሙማን ወደ ማህበረሰቡ እንዲቀላቀሉ የሚያግዝ ህክምና ተሰጠ
ይህ የህክምና ዓይነት በአእምሮ ጤና አውድ ውስጥ የተሃድሶ ህክምና የሚባል ሲሆን የአእምሮ ህመም ያለባቸው ሰዎች በህብረተሰቡ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ተሳታፊ እንዲሆኑና ጥራት ያለው ሕይወት እንዲመሩ የሚረዳ የህክምና እና ድጋፍ ሂደት ነው።
በዚህም የአማኑኤል አዕምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለ6ሺህ334 ዜጎች የተሀድሶ የህክምና አገልግሎት መስጠቱን የሆስፒታሉ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ አብዩ የኔአለም ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል።
ህክምናው ታካሚው የዕለት ከዕለት ተግባራቱን በራሱ እንዲያከናውን የሚረዳ ራስን መንከባከብ ፣ ንፅህናን መጠበቅ እና ከሰዎች ጋር እንዴት መግባባትና ጤናማ ግንኙነት መፍጠር እንደሚቻል የሚሰጥ ነው።
በተጨማሪም የስነልቦና እና ማህበራዊ ድጋፍ የሙያ እና ስራ ስልጠና እንዲሁም ከሆስፒታል የወጡ ታካሚዎች በቀጥታ ወደ ማህበረሰቡ ከመቀላቀላቸው በፊት የቅርብ ክትትል የሚደረግባቸው ጊዜያዊ ማቆያዎችን ማመቻቸትን ይጨምራል።
ታካሚው በተቻለ መጠን በሌሎች ላይ ጥገኝነቱ እንዲቀንስ ፣ያለ አድልዎና ማግለል በቤተሰብና በሰፈር ውስጥ እንዲይኖር የሚያስችል ሲሆን ህመሙ ተመልሶ እንዳይቀሰቀስ ራሱን እንዲጠብቅ ይረዳል ሲሉ አቶ አብዩ የኔአለም ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
ይህ የህክምና ዓይነት በአእምሮ ጤና አውድ ውስጥ የተሃድሶ ህክምና የሚባል ሲሆን የአእምሮ ህመም ያለባቸው ሰዎች በህብረተሰቡ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ተሳታፊ እንዲሆኑና ጥራት ያለው ሕይወት እንዲመሩ የሚረዳ የህክምና እና ድጋፍ ሂደት ነው።
በዚህም የአማኑኤል አዕምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለ6ሺህ334 ዜጎች የተሀድሶ የህክምና አገልግሎት መስጠቱን የሆስፒታሉ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ አብዩ የኔአለም ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል።
ህክምናው ታካሚው የዕለት ከዕለት ተግባራቱን በራሱ እንዲያከናውን የሚረዳ ራስን መንከባከብ ፣ ንፅህናን መጠበቅ እና ከሰዎች ጋር እንዴት መግባባትና ጤናማ ግንኙነት መፍጠር እንደሚቻል የሚሰጥ ነው።
በተጨማሪም የስነልቦና እና ማህበራዊ ድጋፍ የሙያ እና ስራ ስልጠና እንዲሁም ከሆስፒታል የወጡ ታካሚዎች በቀጥታ ወደ ማህበረሰቡ ከመቀላቀላቸው በፊት የቅርብ ክትትል የሚደረግባቸው ጊዜያዊ ማቆያዎችን ማመቻቸትን ይጨምራል።
ታካሚው በተቻለ መጠን በሌሎች ላይ ጥገኝነቱ እንዲቀንስ ፣ያለ አድልዎና ማግለል በቤተሰብና በሰፈር ውስጥ እንዲይኖር የሚያስችል ሲሆን ህመሙ ተመልሶ እንዳይቀሰቀስ ራሱን እንዲጠብቅ ይረዳል ሲሉ አቶ አብዩ የኔአለም ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
8 days ago
ተለያይቻለሁ !!!
ውድ ወዳጆቼ…
ከዛሬ ዘጠኝ ወራት በፊት ከቻናል ዋን የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር የጣቢያው “Creative Director” በመሆን የሥራ ውል ማሰሬንና ሥራ መጀመሬን በማህበራዊ ሚዲያ መግለጼ ይታወሳል።
ሥራ ከጀመርኩበት ቅጽበት ጀምሮ ጣቢያው የቅዳሜ ሾው ያልነበረው በመሆኑ “ቅዳሜኛ” የተሰኘ የመዝናኛና መረጃ (Magazine Format Infotainment Weekly Show) ፕሮግራም ሙሉ በሙሉ በመፍጠርና በማዘጋጀት ላለፉት 6 ወራት በአየር ላይ ቆይቷል። በአጭር ጊዜም ከተመልካቾች ዘንድ እውቅናና ተወዳጅነት ማግኘት ችሏል።
“ቅዳሜኛ” የ3 ሰዓት ቆይታ ያለው ሲሆን በዚህ ቆይታው ውስጥ “ቁራሌው”፣ “ከመወሰንዎ በፊት”፣ “ወጌሻ”፣ “ቢሆንስ”፣ “ቻሌንጅ አንድ”፣ “ሸርሸር”፣ “ለማጅ”፣ “ጨዋታ አንድ”፣ “በላተኞቹ” እና “አቃቂር” የተሰኙ አስተማሪና አዝናኝ ይዘቶችን በመፍጠርና በማዘጋጀት ሰርቻለሁ። እንዲሁም በበዓላት ወቅት የተላለፉ የበዓል ሪያሊቲ ሾዎችንም በመፍጠርና በማዘጋጀት ተሳትፌያለሁ።
ከዚህ በተጨማሪም ለሜንስትሪም ሚዲያው አዲስ የሆኑ ነገር ግን ተሰጥኦ ያላቸው ፕሮግራም አቅራቢዎች አቅማቸውን እንዲያወጡ እድል ከመስጠት ባለፈ፣ ሙያው የሚጠይቀውን ሥነ ምግባር ተከትለው በኃላፊነት እንዲሠሩ ድጋፍና ክትትል ለማድረግ ሞክሬያለሁ።
ሲቀጥል…
አሁን ከዘጠኝ ወራት ቆይታ በኋላ ከጣቢያው ጋር የነበረኝን ውል ማቋረጤን እየገለጽኩ፣ በነበረን የሥራ ጊዜ በትጋትና በመረዳዳት አብረውኝ ለነበሩ የ“ቅዳሜኛ” ሾው አባላት፣ የተቋሙ ካሜራማኖችና ኤዲተሮች ላሳያችሁኝ አክብሮትና ቀናነት ከልብ እያመሰገንኩ ወደፊትም መልካም የሥራ ጊዜ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።
እንዲሁም በጣቢያው ላይ ይተላለፉ የነበሩ ፕሮግራሞችን በመከታተል በተለያየ መንገድ ጠቃሚ አስተያየቶችን ትሰጡኝ የነበራችሁ ወዳጆቼንም በተለይ ማመስገን እወዳለሁ።
አክባሪያችሁ
ሳምሶን ከበደ
Film writer & director | producer|creative director | host
ውድ ወዳጆቼ…
ከዛሬ ዘጠኝ ወራት በፊት ከቻናል ዋን የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር የጣቢያው “Creative Director” በመሆን የሥራ ውል ማሰሬንና ሥራ መጀመሬን በማህበራዊ ሚዲያ መግለጼ ይታወሳል።
ሥራ ከጀመርኩበት ቅጽበት ጀምሮ ጣቢያው የቅዳሜ ሾው ያልነበረው በመሆኑ “ቅዳሜኛ” የተሰኘ የመዝናኛና መረጃ (Magazine Format Infotainment Weekly Show) ፕሮግራም ሙሉ በሙሉ በመፍጠርና በማዘጋጀት ላለፉት 6 ወራት በአየር ላይ ቆይቷል። በአጭር ጊዜም ከተመልካቾች ዘንድ እውቅናና ተወዳጅነት ማግኘት ችሏል።
“ቅዳሜኛ” የ3 ሰዓት ቆይታ ያለው ሲሆን በዚህ ቆይታው ውስጥ “ቁራሌው”፣ “ከመወሰንዎ በፊት”፣ “ወጌሻ”፣ “ቢሆንስ”፣ “ቻሌንጅ አንድ”፣ “ሸርሸር”፣ “ለማጅ”፣ “ጨዋታ አንድ”፣ “በላተኞቹ” እና “አቃቂር” የተሰኙ አስተማሪና አዝናኝ ይዘቶችን በመፍጠርና በማዘጋጀት ሰርቻለሁ። እንዲሁም በበዓላት ወቅት የተላለፉ የበዓል ሪያሊቲ ሾዎችንም በመፍጠርና በማዘጋጀት ተሳትፌያለሁ።
ከዚህ በተጨማሪም ለሜንስትሪም ሚዲያው አዲስ የሆኑ ነገር ግን ተሰጥኦ ያላቸው ፕሮግራም አቅራቢዎች አቅማቸውን እንዲያወጡ እድል ከመስጠት ባለፈ፣ ሙያው የሚጠይቀውን ሥነ ምግባር ተከትለው በኃላፊነት እንዲሠሩ ድጋፍና ክትትል ለማድረግ ሞክሬያለሁ።
ሲቀጥል…
አሁን ከዘጠኝ ወራት ቆይታ በኋላ ከጣቢያው ጋር የነበረኝን ውል ማቋረጤን እየገለጽኩ፣ በነበረን የሥራ ጊዜ በትጋትና በመረዳዳት አብረውኝ ለነበሩ የ“ቅዳሜኛ” ሾው አባላት፣ የተቋሙ ካሜራማኖችና ኤዲተሮች ላሳያችሁኝ አክብሮትና ቀናነት ከልብ እያመሰገንኩ ወደፊትም መልካም የሥራ ጊዜ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።
እንዲሁም በጣቢያው ላይ ይተላለፉ የነበሩ ፕሮግራሞችን በመከታተል በተለያየ መንገድ ጠቃሚ አስተያየቶችን ትሰጡኝ የነበራችሁ ወዳጆቼንም በተለይ ማመስገን እወዳለሁ።
አክባሪያችሁ
ሳምሶን ከበደ
Film writer & director | producer|creative director | host
8 days ago
ሐበሻ ቢራ በብራንድ አፍሪካ የኢትዮጵያ እጅግ ተወዳጁ የቢራ ብራንድ ተብሎ ተሸለመ
#ethiopia | በአፍሪካ ሕብረት እና በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ድጋፍ በሚካሄደው የብራንድ አፍሪካ ዓመታዊ የብራንድ ደረጃ አሰጣጥ፣ ሐበሻ ቢራ በተጠቃሚዎች እና በደንበኞች ድምፅ በተካሄደ ምርጫ “የኢትዮጵያ እጅግ ተወዳጁ የቢራ ብራንድ” በመሆን ከአፍሪካ 100 ምርጥ ብራንዶች መካከል ተ።
ይህ እውቅና በቀጥታ ከተጠቃሚዎች ምርጫ የተገኘ በመሆኑ ለሐበሻ ቢራ ልዩ ትርጉም ያለው ሽልማት ሆኗል። ሐበሻ ቢራ በዘመናት የኢትዮጵያን ባህል፣ ታሪክ እና መገለጫዎች እያከበረና እያነሳ የቆየ ሲሆን፣ ይህ ሽልማትም ለጥራት፣ ለማንነት እና ለኢትዮጵያዊነት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ ሆኗል።
በእያንዳንዱ የሐበሻ ቢራ ጠርሙስ ውስጥ የሚንፀባረቀው የጥራት ደረጃ፣ ኢትዮጵያዊ ኩራት እና ማንነት መሆኑን ይህ እውቅና በድጋሚ አረጋግጧል።
ሐበሻ ቢራ ይህን ክብር ለሰጡት በየቀኑ በምርቱ ላይ እምነት አድርገው የደገፉትን ደንበኞቹን ፣ አጋሮቹን እንዲሁም በሙሉ ብራንድ አፍሪካ ከልብ አመስግኗል።
#habeshabeer #brandafrica #ethiopianbrand #localproducts #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በአፍሪካ ሕብረት እና በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ድጋፍ በሚካሄደው የብራንድ አፍሪካ ዓመታዊ የብራንድ ደረጃ አሰጣጥ፣ ሐበሻ ቢራ በተጠቃሚዎች እና በደንበኞች ድምፅ በተካሄደ ምርጫ “የኢትዮጵያ እጅግ ተወዳጁ የቢራ ብራንድ” በመሆን ከአፍሪካ 100 ምርጥ ብራንዶች መካከል ተ።
ይህ እውቅና በቀጥታ ከተጠቃሚዎች ምርጫ የተገኘ በመሆኑ ለሐበሻ ቢራ ልዩ ትርጉም ያለው ሽልማት ሆኗል። ሐበሻ ቢራ በዘመናት የኢትዮጵያን ባህል፣ ታሪክ እና መገለጫዎች እያከበረና እያነሳ የቆየ ሲሆን፣ ይህ ሽልማትም ለጥራት፣ ለማንነት እና ለኢትዮጵያዊነት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ ሆኗል።
በእያንዳንዱ የሐበሻ ቢራ ጠርሙስ ውስጥ የሚንፀባረቀው የጥራት ደረጃ፣ ኢትዮጵያዊ ኩራት እና ማንነት መሆኑን ይህ እውቅና በድጋሚ አረጋግጧል።
ሐበሻ ቢራ ይህን ክብር ለሰጡት በየቀኑ በምርቱ ላይ እምነት አድርገው የደገፉትን ደንበኞቹን ፣ አጋሮቹን እንዲሁም በሙሉ ብራንድ አፍሪካ ከልብ አመስግኗል።
#habeshabeer #brandafrica #ethiopianbrand #localproducts #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
8 days ago
ከቻናል ዋን ቴሌቪዥን ጋር የነበረኝ የሥራ ስምምነት ተቋርጧል
ለክቡራን የሥራ አጋሮቼ፤ ወዳጆቼ በሙሉ፣
#ethiopia | ከዘጠኝ ወራት በፊት ከቻናል ዋን የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር በፈጠራ ዳይሬክተርነት (Creative Director) ለመሥራት ተስማምቼ ወደ ሥራ መግባቴን በዚህ ገጼ ማጋራቴ ይታወሳል።
ወደ ተቋሙ ከመጣሁበት ጊዜ ጀምሮ የነበረውን ክፍተት በመሙላት፣ ጣቢያው ቀደም ሲል ያልነበረውን የቅዳሜ መዝናኛ ፕሮግራም አዲስ መልክ አስይዤ ለመቅረጽ ተንቀሳቅሻለሁ።
በዚህም መሠረት መረጃና መዝናኛን ያቀናጀውን የቅዳሜኛ ሳምንታዊ ፕሮግራም ሙሉ በሙሉ በመቅረጽና በማዘጋጀት ላለፉት ስድስት ወራት በአየር ላይ እንዲቆይ አድርጌያለሁ። ፕሮግራሙም በአጭር ጊዜ ውስጥ ሰፊ የተመልካች ድጋፍና ተወዳጅነትን ማትረፍ ችሏል።
በየሳምንቱ ለሦስት ሰዓታት በሚተላለፈው በዚህ ፕሮግራም ውስጥ እንደ ቁራሌው፣ ከመወሰንዎ በፊት፣ ወጌሻ፣ ቢሆንስ፣ ቻሌንጅ አንድ፣ ሸርሸር፣ ለማጅ፣ ጨዋታ አንድ፣ በላተኞቹ እና አቃቂር ያሉ አዝናኝና አስተማሪ ዓምዶችን በመፍጠር ሰርቻለሁ።
ከነዚህም በተጨማሪ በበዓላት ወቅት ለአየር የበቁ ልዩ ልዩ የሪአሊቲ ሾው ፕሮግራሞችን በማዘጋጀትና በማስተባበር ተሳትፎ አድርጌያለሁ።
ከይዘት ዝግጅቱ ባለፈ፣ ለቴሌቪዥን ሚዲያ አዲስ የሆኑ ነገር ግን ከፍተኛ ክህሎት ያላቸው ወጣቶች ብቃታቸውን የሚያሳዩበትን ዕድል አመቻችቻለሁ።
እነዚህ አቅራቢዎች የሙያውን ሥነ ምግባር ጠብቀው በኃላፊነት ስሜት እንዲሠሩም የበኩሌን የሙያ ድጋፍና ክትትል አድርጌላቸዋለሁ።
አሁን ግን ከዘጠኝ ወራት የሥራ ቆይታ በኋላ ከጣቢያው ጋር የነበረኝን የሥራ ውል ማቋረጤን ለመግለጽ እወዳለሁ። በነበረን ቆይታ በትጋትና በጋራ ስሜት አብረውኝ ለሠሩት የቅዳሜኛ ፕሮግራም አባላት፣ ለካሜራ ባለሙያዎችና ለኤዲተሮች ላሳዩኝ ወንድማዊ አክብሮትና ቀናነት ከልብ የመነጨ ምስጋናዬን አቀርባለሁ።
ለወደፊቱም መልካም የሥራ ዘመን እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።
በመጨረሻም፣ በጣቢያው ላይ የሚተላለፉ ሥራዎቼን በመከታተል ገንቢና ጠቃሚ አስተያየቶችን ስትለግሱኝ ለነበራችሁ ውድ ተመልካቾቼና ወዳጆቼ ሁልጊዜም ከፍ ያለ ምስጋና አለኝ።
አክባሪያችሁ፣
ሳምሶን ከበደ
የፊልም ደራሲ፣ ዳይሬክተር፣ ፕሮዲውሰር እና አቅራቢ
#channelone #samsonkebede #kedamegna #media #tvshow #entertainment #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
ለክቡራን የሥራ አጋሮቼ፤ ወዳጆቼ በሙሉ፣
#ethiopia | ከዘጠኝ ወራት በፊት ከቻናል ዋን የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር በፈጠራ ዳይሬክተርነት (Creative Director) ለመሥራት ተስማምቼ ወደ ሥራ መግባቴን በዚህ ገጼ ማጋራቴ ይታወሳል።
ወደ ተቋሙ ከመጣሁበት ጊዜ ጀምሮ የነበረውን ክፍተት በመሙላት፣ ጣቢያው ቀደም ሲል ያልነበረውን የቅዳሜ መዝናኛ ፕሮግራም አዲስ መልክ አስይዤ ለመቅረጽ ተንቀሳቅሻለሁ።
በዚህም መሠረት መረጃና መዝናኛን ያቀናጀውን የቅዳሜኛ ሳምንታዊ ፕሮግራም ሙሉ በሙሉ በመቅረጽና በማዘጋጀት ላለፉት ስድስት ወራት በአየር ላይ እንዲቆይ አድርጌያለሁ። ፕሮግራሙም በአጭር ጊዜ ውስጥ ሰፊ የተመልካች ድጋፍና ተወዳጅነትን ማትረፍ ችሏል።
በየሳምንቱ ለሦስት ሰዓታት በሚተላለፈው በዚህ ፕሮግራም ውስጥ እንደ ቁራሌው፣ ከመወሰንዎ በፊት፣ ወጌሻ፣ ቢሆንስ፣ ቻሌንጅ አንድ፣ ሸርሸር፣ ለማጅ፣ ጨዋታ አንድ፣ በላተኞቹ እና አቃቂር ያሉ አዝናኝና አስተማሪ ዓምዶችን በመፍጠር ሰርቻለሁ።
ከነዚህም በተጨማሪ በበዓላት ወቅት ለአየር የበቁ ልዩ ልዩ የሪአሊቲ ሾው ፕሮግራሞችን በማዘጋጀትና በማስተባበር ተሳትፎ አድርጌያለሁ።
ከይዘት ዝግጅቱ ባለፈ፣ ለቴሌቪዥን ሚዲያ አዲስ የሆኑ ነገር ግን ከፍተኛ ክህሎት ያላቸው ወጣቶች ብቃታቸውን የሚያሳዩበትን ዕድል አመቻችቻለሁ።
እነዚህ አቅራቢዎች የሙያውን ሥነ ምግባር ጠብቀው በኃላፊነት ስሜት እንዲሠሩም የበኩሌን የሙያ ድጋፍና ክትትል አድርጌላቸዋለሁ።
አሁን ግን ከዘጠኝ ወራት የሥራ ቆይታ በኋላ ከጣቢያው ጋር የነበረኝን የሥራ ውል ማቋረጤን ለመግለጽ እወዳለሁ። በነበረን ቆይታ በትጋትና በጋራ ስሜት አብረውኝ ለሠሩት የቅዳሜኛ ፕሮግራም አባላት፣ ለካሜራ ባለሙያዎችና ለኤዲተሮች ላሳዩኝ ወንድማዊ አክብሮትና ቀናነት ከልብ የመነጨ ምስጋናዬን አቀርባለሁ።
ለወደፊቱም መልካም የሥራ ዘመን እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።
በመጨረሻም፣ በጣቢያው ላይ የሚተላለፉ ሥራዎቼን በመከታተል ገንቢና ጠቃሚ አስተያየቶችን ስትለግሱኝ ለነበራችሁ ውድ ተመልካቾቼና ወዳጆቼ ሁልጊዜም ከፍ ያለ ምስጋና አለኝ።
አክባሪያችሁ፣
ሳምሶን ከበደ
የፊልም ደራሲ፣ ዳይሬክተር፣ ፕሮዲውሰር እና አቅራቢ
#channelone #samsonkebede #kedamegna #media #tvshow #entertainment #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Sponsored by
Surafel
8 days ago
እንኳን ለቅዱስ ገብርኤል ወርሃዊ በዓል አደረሳችሁ፤ አደረሰን🙏
ቅዱስ ገብርኤል የልባችሁን መልካም መሻት ይሙላላችሁ!!!
ነቢዩ ዳንኤል የመላእክት አለቃ የቅዱስ ገብርኤልን አስፈሪ ግርማ በተመለከተ ጊዜ “ዐይኖቼንም አነሣሁ “እነሆም በፍታ የለበሰውን ጥሩም የአፌዝን ወርቅ በወገቡ ላይ የታጠቀውን ሰው አየሁ፡፡ አካሉም እንደ ቢረሌ ይመስል ነበር፤ ፊቱም እንደ መብረቅ አምሳያ ነበረ፤ ዐይኖቹም እንደሚንበለበል ፋና፣ ክንዶቹና እግሮቹም እንደ ጋለ ናስ፣ የቃሉም ድምፅ እንደ ብዙ ሕዝብ ድምፅ ነበረ፡፡ ይህንም ታላቅ ራእይ አየሁ፤ ኀይልም አልቀረልኝም፤ ክብሬም ወደ ውርደት ተለወጠብኝ ኀይልም አጣሁ፡፡ የቃሉንም ድምፅ ሰማሁ፤ የቃሉን ድምፅ በሰማሁ ጊዜ ደንግጬ በምደር ላይ በግምባሬ ተደፋሁ” አለ፡፡ በዳንኤል 10÷5-9 የተገለጸው የዚህ መልአክ ግርማ የአምላክን ግርማ ይመስላል፡፡ ቅዱስ ገብርኤል የስሙ ትርጓሜ “አምላክ ወሰብእ” ሰውና አምላክ ማለት ሲሆን ከዋነኞቹ የመላዕክት አለቆች አንዱ ነው፡፡
ነቢዩ ኢሳይያስ በምዕራፍ 14÷16 በሰማያት የሳጥናኤል ትዕቢትና ውድቀት ምን እንደሚመስል ሲጽፍልን “አንተ በንጋት የሚወጣ አጥቢያ ኮከብ ሆይ እንዴት ከሰማይ ወደቅህ! ወደ አሕዛብ መልእክትን የላክ አንተ ሆይ እንዴት እስከ ምድር ድረስ ተቀጠቀጥህ! አንተም በልብህ ወደ ሰማይ ዐርጋለሁ ዙፋኔንም ከእግዚአብሔር ከዋክብት በላይ ከፍ ከፍ አደረጋለሁ፤ በልዑልም እመሰላለሁ አልህ፡፡ ዛሬ ግን ወደ ሲኦል ትወድቃለህ፤ ወደ ምደር ጥልቅም ትወርዳለህ” ይለናል፡፡ ቅዱስ ገብርኤል በቅድስና ሕይወት ለተጋውና በገዢዎች ዘንድ የእግዚአብሔር ቅዱስ መንፈስ ያደረበት ሰው ተብሎ ለተመሰገነው ለነቢዩ ዳንኤል ማስተዋልንና ጥበብን የሰጠ፣ እግዚአብሔር አምላክ የሰው ልጆችን ከሰይጣንና ከሞት ባርነት ነጻ ሊያወጣቸው ሰው እንደሚሆንና ሰማይንና ምድርን አሳልፎ በቅዱሳን ላይ ነግሦ እንደሚኖር በምሳሌ ገልጾ ያስተማረው መልአክ ነው፡፡
ቅዱስ ገብርኤል ቅዱሳንን ለእግዚአብሔር በመገዛታቸው ምክንያት ከአላውያን ገዢዎች ከሚደርስባቸው መከራም የሚታደጋቸው መልአክም ነው፡፡ ሦስቱ ሕጻናት አናንያ አዛርያና ሚሳኤል ለጣኦት አንሰግድም ባሉ ጊዜ በንጉሥ ናብከደነፆር ወደ እቶን እሳት ሲጣሉ እስራታቸውን ፈቶ፣ እሳቱን እንደ ውኃ አቀዝቅዞ ያዳናቸው ቅዱስ ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ ቅዱስ ቂርቆስንና እናቱ ቅድስት ኢየሉጣንም ከእሳት ያወጣ እርሱ ነው፡፡ የቅዱስ ገብርኤል ምልጃና ጸሎት ይጠብቀን፡፡ ዛሬም ይህን አማላጅነቱንና ፈጣን ተራዳኢነቱን ያመኑ ገዳማውያ አባቶች በጸሎታቸው ይጠሩታል እርሱም ይራዳቸዋል፡፡ እኛም ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና የበረከታቸው ተሳታፊ እንሆናለን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
ቅዱስ ገብርኤል የልባችሁን መልካም መሻት ይሙላላችሁ!!!
ነቢዩ ዳንኤል የመላእክት አለቃ የቅዱስ ገብርኤልን አስፈሪ ግርማ በተመለከተ ጊዜ “ዐይኖቼንም አነሣሁ “እነሆም በፍታ የለበሰውን ጥሩም የአፌዝን ወርቅ በወገቡ ላይ የታጠቀውን ሰው አየሁ፡፡ አካሉም እንደ ቢረሌ ይመስል ነበር፤ ፊቱም እንደ መብረቅ አምሳያ ነበረ፤ ዐይኖቹም እንደሚንበለበል ፋና፣ ክንዶቹና እግሮቹም እንደ ጋለ ናስ፣ የቃሉም ድምፅ እንደ ብዙ ሕዝብ ድምፅ ነበረ፡፡ ይህንም ታላቅ ራእይ አየሁ፤ ኀይልም አልቀረልኝም፤ ክብሬም ወደ ውርደት ተለወጠብኝ ኀይልም አጣሁ፡፡ የቃሉንም ድምፅ ሰማሁ፤ የቃሉን ድምፅ በሰማሁ ጊዜ ደንግጬ በምደር ላይ በግምባሬ ተደፋሁ” አለ፡፡ በዳንኤል 10÷5-9 የተገለጸው የዚህ መልአክ ግርማ የአምላክን ግርማ ይመስላል፡፡ ቅዱስ ገብርኤል የስሙ ትርጓሜ “አምላክ ወሰብእ” ሰውና አምላክ ማለት ሲሆን ከዋነኞቹ የመላዕክት አለቆች አንዱ ነው፡፡
ነቢዩ ኢሳይያስ በምዕራፍ 14÷16 በሰማያት የሳጥናኤል ትዕቢትና ውድቀት ምን እንደሚመስል ሲጽፍልን “አንተ በንጋት የሚወጣ አጥቢያ ኮከብ ሆይ እንዴት ከሰማይ ወደቅህ! ወደ አሕዛብ መልእክትን የላክ አንተ ሆይ እንዴት እስከ ምድር ድረስ ተቀጠቀጥህ! አንተም በልብህ ወደ ሰማይ ዐርጋለሁ ዙፋኔንም ከእግዚአብሔር ከዋክብት በላይ ከፍ ከፍ አደረጋለሁ፤ በልዑልም እመሰላለሁ አልህ፡፡ ዛሬ ግን ወደ ሲኦል ትወድቃለህ፤ ወደ ምደር ጥልቅም ትወርዳለህ” ይለናል፡፡ ቅዱስ ገብርኤል በቅድስና ሕይወት ለተጋውና በገዢዎች ዘንድ የእግዚአብሔር ቅዱስ መንፈስ ያደረበት ሰው ተብሎ ለተመሰገነው ለነቢዩ ዳንኤል ማስተዋልንና ጥበብን የሰጠ፣ እግዚአብሔር አምላክ የሰው ልጆችን ከሰይጣንና ከሞት ባርነት ነጻ ሊያወጣቸው ሰው እንደሚሆንና ሰማይንና ምድርን አሳልፎ በቅዱሳን ላይ ነግሦ እንደሚኖር በምሳሌ ገልጾ ያስተማረው መልአክ ነው፡፡
ቅዱስ ገብርኤል ቅዱሳንን ለእግዚአብሔር በመገዛታቸው ምክንያት ከአላውያን ገዢዎች ከሚደርስባቸው መከራም የሚታደጋቸው መልአክም ነው፡፡ ሦስቱ ሕጻናት አናንያ አዛርያና ሚሳኤል ለጣኦት አንሰግድም ባሉ ጊዜ በንጉሥ ናብከደነፆር ወደ እቶን እሳት ሲጣሉ እስራታቸውን ፈቶ፣ እሳቱን እንደ ውኃ አቀዝቅዞ ያዳናቸው ቅዱስ ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ ቅዱስ ቂርቆስንና እናቱ ቅድስት ኢየሉጣንም ከእሳት ያወጣ እርሱ ነው፡፡ የቅዱስ ገብርኤል ምልጃና ጸሎት ይጠብቀን፡፡ ዛሬም ይህን አማላጅነቱንና ፈጣን ተራዳኢነቱን ያመኑ ገዳማውያ አባቶች በጸሎታቸው ይጠሩታል እርሱም ይራዳቸዋል፡፡ እኛም ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና የበረከታቸው ተሳታፊ እንሆናለን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444