Logo
SeledaPost
ከ6ሺ በላይ ለሚሆኑ የአዕምሮ ህሙማን ወደ ማህበረሰቡ እንዲቀላቀሉ የሚያግዝ ህክምና ተሰጠ
 
ይህ የህክምና ዓይነት በአእምሮ ጤና አውድ ውስጥ የተሃድሶ ህክምና የሚባል ሲሆን የአእምሮ ህመም ያለባቸው ሰዎች በህብረተሰቡ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ተሳታፊ እንዲሆኑና ጥራት ያለው ሕይወት እንዲመሩ የሚረዳ የህክምና እና ድጋፍ ሂደት ነው።
 
በዚህም የአማኑኤል አዕምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለ6ሺህ334 ዜጎች የተሀድሶ የህክምና አገልግሎት መስጠቱን የሆስፒታሉ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ አብዩ የኔአለም ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል።
 
ህክምናው  ​ታካሚው የዕለት ከዕለት ተግባራቱን በራሱ እንዲያከናውን የሚረዳ ራስን መንከባከብ ፣ ንፅህናን መጠበቅ እና  ከሰዎች ጋር እንዴት መግባባትና ጤናማ ግንኙነት መፍጠር እንደሚቻል የሚሰጥ ነው።
 
በተጨማሪም የስነልቦና እና ማህበራዊ ድጋፍ  የሙያ እና ስራ ስልጠና እንዲሁም ​ከሆስፒታል የወጡ ታካሚዎች በቀጥታ ወደ ማህበረሰቡ ከመቀላቀላቸው በፊት የቅርብ ክትትል የሚደረግባቸው ጊዜያዊ ማቆያዎችን ማመቻቸትን ይጨምራል።
 
ታካሚው በተቻለ መጠን በሌሎች ላይ ጥገኝነቱ እንዲቀንስ ፣ያለ አድልዎና ማግለል በቤተሰብና በሰፈር ውስጥ እንዲይኖር የሚያስችል ሲሆን ህመሙ ተመልሶ እንዳይቀሰቀስ  ራሱን እንዲጠብቅ ይረዳል ሲሉ አቶ  አብዩ የኔአለም ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።
 
Seledadotio
Seledadotio
8 days ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.