8 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በአሜሪካ ትልቁ የፕሮቴስታንት ቤተ እምነት የሆነው የደቡብ ባፕቲስት ጉባኤ (ሳውዘርን ባፕቲስት ኮንቬንሽን)፣ ሴቶች በፓስተርነት እንዳያገለግሉ በይፋ የሚከለክለውን ሕገ-ደንብ ለማጽደቅ ረቡዕ ዕለት በከፍተኛ ድምፅ ወስኗል። ይህ ውሳኔ በቤተክርስቲያኒቱ ወግ አጥባቂ ምዕመናን ዘንድ ስብከት የወንዶች ብቻ መብትና ኃላፊነት መሆኑን ግልጽ መልእክት ያስተላለፈ ነው።
በፍሎሪዳ ግዛት ኦርላንዶ ከተማ በተካሄደው ዓመታዊ ጉባኤ ላይ ከተገኙት ተወካዮች መካከል 6,028ቱ ማሻሻያውን ሲደግፉ፣ 2,026ቱ ብቻ ተቃውመዋል። ይህ ከሦስት እጅ አንድ የሆነው የድምፅ ልዩነት፣ ሕጉን ለማሳለፍ ከሚጠየቀው የሁለት ሦስተኛ አብላጫ ድምፅ በላይ ሆኖ ተመዝግቧል። ይሁን እንጂ ማሻሻያው በቤተክርስቲያኒቱ ሕገ-መንግሥት ውስጥ በቋሚነት እንዲካተት፣ በሚቀጥለው ዓመት በሚካሄደው ተመሳሳይ ጉባኤ ላይ የሁለት ሦስተኛ ድምፅ ማግኘት ይኖርበታል።
የሕግ ማሻሻያውን ያቀረቡት በኬንታኪ የሚገኘው የነገረ መለኮት ትምህርት ቤት ፕሬዝዳንት አልበርት ሞህለር፣ ውሳኔው ቤተ እምነቱ ያለውን አቋም በእውነት፣ በአንድነት እና በጽኑ እምነት በግልጽ ለማሳየት የተፈጠረ ታሪካዊ አጋጣሚ ነው ብለዋል። "በለዘብተኛ (ሊበራል) እና በመጽሐፍ ቅዱሳዊ ወንጌላውያን መካከል ትልቅ የልዩነት መስመር አለ፤ ይህንንም በዚህ ጉዳይ ላይ በግልጽ ማየት ይቻላል። የለዘብተኛ ቤተ እምነቶች አቅጣጫ ግልጽ ነው" በማለት ተናግረዋል።
በጉባኤው ላይ ለማሻሻያው የተሰማው ብቸኛ የተቃውሞ ድምፅ ከሳውዝ ካሮላይናው ፓስተር ዳግ ማይዝ የመጣ ነበር። ይሁን እንጂ የእሳቸውም ተቃውሞ ሴት ፓስተሮችን ከመደገፍ የመነጨ ሳይሆን፣ ቤተ እምነቱ አስቀድሞ ሴት ፓስተሮችን የሚሾሙ አጥቢያዎችን ከማኅበሩ የሚያስወጣበት አሰራር ስላለው ይህ አዲስ ሕገ-መንግስታዊ ማሻሻያ አያስፈልግም በሚል ነው። ቤተ እምነቱ ከዚህ ቀደም በካሊፎርኒያ የሚገኘውን ታዋቂውን የሳድልባክ ቤተክርስቲያንን ጨምሮ፣ ሴቶች በዋና ፓስተርነት የሚያገለግሉባቸውን አጥቢያዎች ከአባልነት ማገዱ ይታወሳል።
አዲሱ የማሻሻያ ቃል፣ ማንኛውም የጉባኤው አባል የሆነ አጥቢያ አንዲትን ሴት በፓስተርነት፣ በሽማግሌነት ወይም በተለይም ለተሰበሰበው ምዕመን ቃሉን እንድትሰብክ መሾም ወይም ማጽደቅ እንደሌለበት በጥብቅ ያስገድዳል። የቤተ እምነቱ መሪዎች ይህንን ውሳኔያቸውን የፓስተርነትን አገልግሎት ለወንዶች ብቻ ከሚገድቡ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ጋር ያያይዙታል።
በሌላ በኩል ከተለያዩ የባፕቲስት አጥቢያዎች ጋር የሚሠራው የባፕቲስት ሴት አገልጋዮች ማኅበር በውሳኔው በእጅጉ ማዘኑን ገልጿል። ማኅበሩ ባወጣው መግለጫ፣ "በዚህ ድምፅ አሰጣጥ፣ ከውሳኔው ጀርባ ባለው የጥላቻ ቅስቀሳ እና ውሳኔው በሚወክለው ጎጂ የነገረ መለኮት ትርጓሜ ለተጎዱ ሴት አገልጋዮች አጋርነታችንን እንገልጻለን። ሴት አገልጋዮች መከበር እና የእግዚአብሔርን ጥሪ የመከተል ዕድል ሊሰጣቸው ይገባል፤ በዚህ ውሳኔ መሰረታዊ ነጻነታቸውን በመነጠቃቸው ልባችን ተሰብሯል" ብሏል።
ከዚህ ታሪካዊ ውሳኔ ጎን ለጎን፣ ማክሰኞ ዕለት በተካሄደው ምርጫ የፍሎሪዳው ፓስተር ዊሊ ራይስ 58 በመቶ ድምፅ በማግኘት የቤተ እምነቱ አዲሱ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመርጠዋል። ራይስ ይህንን ሴት ፓስተሮችን የሚከለክለውን የሕግ ማሻሻያ በጽኑ ከሚደግፉ እና ቤተ እምነቱ በዘር፣ በጾታ እና በስደተኞች ዙሪያ ከመጠን ያለፈ የነጻነት አመለካከት እያራመደ ነው ብለው ከሚሞግቱ ወግ አጥባቂ መሪዎች መካከል አንዱ መሆናቸው ውሳኔውን ይበልጥ አጠናክሮታል።
በፍሎሪዳ ግዛት ኦርላንዶ ከተማ በተካሄደው ዓመታዊ ጉባኤ ላይ ከተገኙት ተወካዮች መካከል 6,028ቱ ማሻሻያውን ሲደግፉ፣ 2,026ቱ ብቻ ተቃውመዋል። ይህ ከሦስት እጅ አንድ የሆነው የድምፅ ልዩነት፣ ሕጉን ለማሳለፍ ከሚጠየቀው የሁለት ሦስተኛ አብላጫ ድምፅ በላይ ሆኖ ተመዝግቧል። ይሁን እንጂ ማሻሻያው በቤተክርስቲያኒቱ ሕገ-መንግሥት ውስጥ በቋሚነት እንዲካተት፣ በሚቀጥለው ዓመት በሚካሄደው ተመሳሳይ ጉባኤ ላይ የሁለት ሦስተኛ ድምፅ ማግኘት ይኖርበታል።
የሕግ ማሻሻያውን ያቀረቡት በኬንታኪ የሚገኘው የነገረ መለኮት ትምህርት ቤት ፕሬዝዳንት አልበርት ሞህለር፣ ውሳኔው ቤተ እምነቱ ያለውን አቋም በእውነት፣ በአንድነት እና በጽኑ እምነት በግልጽ ለማሳየት የተፈጠረ ታሪካዊ አጋጣሚ ነው ብለዋል። "በለዘብተኛ (ሊበራል) እና በመጽሐፍ ቅዱሳዊ ወንጌላውያን መካከል ትልቅ የልዩነት መስመር አለ፤ ይህንንም በዚህ ጉዳይ ላይ በግልጽ ማየት ይቻላል። የለዘብተኛ ቤተ እምነቶች አቅጣጫ ግልጽ ነው" በማለት ተናግረዋል።
በጉባኤው ላይ ለማሻሻያው የተሰማው ብቸኛ የተቃውሞ ድምፅ ከሳውዝ ካሮላይናው ፓስተር ዳግ ማይዝ የመጣ ነበር። ይሁን እንጂ የእሳቸውም ተቃውሞ ሴት ፓስተሮችን ከመደገፍ የመነጨ ሳይሆን፣ ቤተ እምነቱ አስቀድሞ ሴት ፓስተሮችን የሚሾሙ አጥቢያዎችን ከማኅበሩ የሚያስወጣበት አሰራር ስላለው ይህ አዲስ ሕገ-መንግስታዊ ማሻሻያ አያስፈልግም በሚል ነው። ቤተ እምነቱ ከዚህ ቀደም በካሊፎርኒያ የሚገኘውን ታዋቂውን የሳድልባክ ቤተክርስቲያንን ጨምሮ፣ ሴቶች በዋና ፓስተርነት የሚያገለግሉባቸውን አጥቢያዎች ከአባልነት ማገዱ ይታወሳል።
አዲሱ የማሻሻያ ቃል፣ ማንኛውም የጉባኤው አባል የሆነ አጥቢያ አንዲትን ሴት በፓስተርነት፣ በሽማግሌነት ወይም በተለይም ለተሰበሰበው ምዕመን ቃሉን እንድትሰብክ መሾም ወይም ማጽደቅ እንደሌለበት በጥብቅ ያስገድዳል። የቤተ እምነቱ መሪዎች ይህንን ውሳኔያቸውን የፓስተርነትን አገልግሎት ለወንዶች ብቻ ከሚገድቡ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ጋር ያያይዙታል።
በሌላ በኩል ከተለያዩ የባፕቲስት አጥቢያዎች ጋር የሚሠራው የባፕቲስት ሴት አገልጋዮች ማኅበር በውሳኔው በእጅጉ ማዘኑን ገልጿል። ማኅበሩ ባወጣው መግለጫ፣ "በዚህ ድምፅ አሰጣጥ፣ ከውሳኔው ጀርባ ባለው የጥላቻ ቅስቀሳ እና ውሳኔው በሚወክለው ጎጂ የነገረ መለኮት ትርጓሜ ለተጎዱ ሴት አገልጋዮች አጋርነታችንን እንገልጻለን። ሴት አገልጋዮች መከበር እና የእግዚአብሔርን ጥሪ የመከተል ዕድል ሊሰጣቸው ይገባል፤ በዚህ ውሳኔ መሰረታዊ ነጻነታቸውን በመነጠቃቸው ልባችን ተሰብሯል" ብሏል።
ከዚህ ታሪካዊ ውሳኔ ጎን ለጎን፣ ማክሰኞ ዕለት በተካሄደው ምርጫ የፍሎሪዳው ፓስተር ዊሊ ራይስ 58 በመቶ ድምፅ በማግኘት የቤተ እምነቱ አዲሱ ፕሬዝዳንት ሆነው ተመርጠዋል። ራይስ ይህንን ሴት ፓስተሮችን የሚከለክለውን የሕግ ማሻሻያ በጽኑ ከሚደግፉ እና ቤተ እምነቱ በዘር፣ በጾታ እና በስደተኞች ዙሪያ ከመጠን ያለፈ የነጻነት አመለካከት እያራመደ ነው ብለው ከሚሞግቱ ወግ አጥባቂ መሪዎች መካከል አንዱ መሆናቸው ውሳኔውን ይበልጥ አጠናክሮታል።
11 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዕይታ) የዘማሪ እና ሰባኪ ታዲዮስ ግርማ "የመቅደሱ እምባ" የተሰኘውን መዝሙር ስንሰማ በውስጣችን የሚፈጥረው ስሜት ተራ የዜማ ጥበብ አይደለም፤ ይልቁንም የቆሰለ ልብ ጩኸት፣ የወቅቱ የሀገራችን የፖለቲካ እና የሃይማኖት ቀውስ መስተዋት፣ እንዲሁም ልክ እንደ ቀድሞ ነቢያት በድፍረት የቀረበ የማስጠንቀቂያ ደወል ነው። ይህንን መዝሙር በጥልቀት ስንመለከተው፣ ከሚያስተላልፈው መንፈሳዊ እና ማህበራዊ መልእክት ባሻገር ከቅዱሳት መጻሕፍት ጋር የተቆራኙ በርካታ እውነታዎችን እናገኛለን።
ዘማሪው የሀገሪቱን የደም መፋሰስ እያየ ዝም ማለት አልቻለም። የንጹሃን ደም መፍሰስ ሰማይ እንደደረሰ እና ፈጣሪም ለዚህ ፍርድ እንደሚሰጥ በግልጽ ይሞግታል። የባቢሎኑ ንጉሥ ብልጣሶር በእግዚአብሔር ንዋየ ቅድሳት ሲቀልድ ጣት መጥታ ግድግዳ ላይ እንደጻፈችበት ሁሉ (በትንቢተ ዳንኤል 5፥27 ላይ "ማኔ ቴቄል ፋሬስ" ወይም "ቴቄል፤ በሚዛን ተመዘንክ፥ ቀለህም ተገኘህ" እንደሚለው)፣ የዘመናችንም ገዥዎች በመለኮት ሚዛን ቀልለው መገኘታቸውንና "ዙፋኑን ልቀቅ" የሚል ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው ይነግረናል። በተጨማሪም "እንደ ናቡቴ ደም ያንተም ደም ይፈሳል" በማለት፣ ንጉሥ አክዓብ የንጹሑን የናቡቴን ወይን ቦታ ለመቀማት ብሎ በግፍ ስላስገደለውና ፈጣሪ ውሾች ደሙን እንዲልሱት እንደፈረደበት (በ1ኛ ነገሥት 21፥19 ላይ የተጻፈውን) ታሪክ ያስታውሳል። ይህም "እጆቻችሁ ደም ተሞልተዋል" (ኢሳይያስ 1፥15) እንደሚለው፣ በግፍ ለሚገደሉ ዜጎች እግዚአብሔር ዝም እንደማይል የሚያሳይ የሰላ እና ደፋር መልእክት ነው።
ልብን ክፉኛ የሚነካው የመዝሙሩ ክፍል ዘማሪው የራሱን ቤተክርስቲያን ችግር ሳይሸሽግ በድፍረት የሚያጋልጥበት ነው። ቤተ መቅደስ የሰላም እና የመጠጊያ ስፍራ መሆኑ ቀርቶ የዘር ፖለቲካ ማራመጃ፣ እንዲሁም የጥቅም መገበያያ መሆኑን በብርቱ ያወግዛል። ዘማሪው የሚከተለውን ጠንካራ ስንኝ ሲያሰማ እንሰማለን፦
በዘር በቋንቋ ከፋፍለህ ሰጥተሃል፣
ጳጳሳቱ ተመዝነሃል፣
በዘር በቋንቋ የተሾማችሁ፣
ከመቅደሱ ውጡ ቆብ አውልቃችሁ፣
ስምንተኛው ሺ ደረሰ ህገ ቤተክርስቲያን ተጣሰ፣
የወለደ ልጅ ያለው ጳጳስ ስምንተኛው ሺ ደረሰ።
ይህ ስንኝ የቤተክርስቲያኒቱን ወቅታዊ ፈተናዎች ያለ ምንም ድብቅብቅ በቀጥታ የሚሞግት ነው። የመጀመሪያው ጉዳይ በዘር እና በቋንቋ ላይ የተመሰረተውን የሹመት ቀውስ ይመለከታል። ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ እና አግላይ ያልሆነች ተቋም ሆና ሳለች፣ የፖለቲካ እና የዘር ማከፋፈያ መሆኗን አጥብቆ ይቃወማል። ለዚህ መከፋፈል ተባባሪ የሆኑት እና በዘር የተሾሙት አባቶችም በመንፈሳዊው ሚዛን ቀልለው ስለተገኙ፣ ቆባቸውን አውልቀው ከመቅደሱ መውጣት እንዳለባቸው ያለ ፍርሃት ይሞግታል። ሐዋርያው ጳውሎስ "በክርስቶስ ኢየሱስ ሁላችሁ አንድ ናችሁና... አይሁዳዊ ወይም የግሪክ ሰው የለም" (ገላትያ 3፥28) ብሎ ያፈረሰውን የዘር ግድግዳ፣ አሁን ላይ አባቶች ራሳቸው መልሰው ሲገነቡት ማየት እጅግ ያመዋል።
ሁለተኛው ነጥብ የቤተክርስቲያኒቱ ቀኖና እና ሥርዓት መጣስን ያሳያል። "ህገ ቤተክርስቲያን ተጣሰ የወለደ ልጅ ያለው ጳጳስ" የሚለው ቃል፣ የቤተክርስቲያኒቱን ጥብቅ ህግ መናድ ያሳያል። በኦርቶዶክስ ትውፊት ጳጳስ የሚመረጠው ከምንኩስና ሕይወት በመሆኑ፣ ዓለማዊ ፍላጎቱን የገደለ እና ቤተሰብ የሌለው መሆን አለበት። ነገር ግን ይህ የቅድስና ሥርዓት ተጥሶ ዓለማዊ እና ሥጋዊ ሕይወት ያላቸው ሰዎች ወደዚህ ከፍተኛ የመንፈሳዊ አመራር ሥፍራ መምጣታቸውን በከፍተኛ ኃዘን ይገልጻል።
ሦስተኛው ጉዳይ "ስምንተኛው ሺህ" የሚለው ትንቢታዊ አገላለጽ ነው። ይህ ብሂል በኢትዮጵያዊያን ዘንድ የክፋት መብዛትን፣ የስርዓት መበላሸትን እና የማይታሰብ ድርጊት የሚፈጸምበትን የኃጢአት ዘመን ለመግለጽ የምንጠቀምበት ነው። ዘማሪው በመቅደሱ ውስጥ እንዲህ ያለ የዘር ክፍፍል እና የቀኖና ጥሰት መታየቱ የዘመኑን ክፋት፣ የሥርዓቱን መፍረስ እና የመጨረሻውን የጥፋት ዘመን መቃረብ አመላካች መሆኑን እያስጠነቀቀን ይገኛል።
ከዚህ ሁሉ ትችት እና ማስጠንቀቂያ በኋላ መዝሙሩ ተስፋ ወደ መቁረጥ ሳይሆን ወደ እውነተኛው መፍትሄ ይመራናል። የኢትዮጵያ መፍትሄ ያለው በጉልበት ወይም በጦር መሳሪያ ሳይሆን በንስሐ እና ወደ እግዚአብሔር በመመለስ መሆኑን ያሳስበናል። "እንደ ራሔል የኢትዮጵያ እናት አልቅሳ" ሲል "ድምፅ በራማ ተሰማ፥ ልቅሶና መራራ ዋይታ፤ ራሔል ስለ ልጆችዋ አለቀሰች... መጽናናትንም እንቢ አለች" (ኤርምያስ 31፥15) የሚለውን የነቢዩን ቃል በማስታወስ፣ የሀገሪቱ እናቶች በልጆቻቸው መሞት አንጀታቸው ማረሩን ይገልጻል። በመጨረሻም የኢትዮጵያ ጥንካሬ መንበርከክ መሆኑን በማንሳት፣ "ስሜ የተጠራበት ሕዝቤ ሰውነታቸውን አዋርደው ቢጸልዩ... እኔ ከሰማይ እሰማለሁ፥ ኃጢአታቸውንም ይቅር እላለሁ፥ ምድራቸውንም እፈውሳለሁ" (2ኛ ዜና መዋዕል 7፥14) የሚለውን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል በተግባር እንድናውለው ጥሪ ያደርጋል።
ይህ መዝሙር ለፖለቲከኛውም ሆነ ለሃይማኖት መሪው መስተዋት ነው። "ባለ ማዕተቦች" እና እውነተኛ አማኞች ከስሜታዊነት ወጥተው ስለውድቀታቸው እንዲያስቡ፣ እንዲጸልዩ እና ወደ ፈጣሪያቸው እንዲመለሱ የሚጠይቅ የነፍስ ጥሪ ነው።
ለዘ-ሐበሻ ማርታ ከሚኒሶታ
ዘማሪው የሀገሪቱን የደም መፋሰስ እያየ ዝም ማለት አልቻለም። የንጹሃን ደም መፍሰስ ሰማይ እንደደረሰ እና ፈጣሪም ለዚህ ፍርድ እንደሚሰጥ በግልጽ ይሞግታል። የባቢሎኑ ንጉሥ ብልጣሶር በእግዚአብሔር ንዋየ ቅድሳት ሲቀልድ ጣት መጥታ ግድግዳ ላይ እንደጻፈችበት ሁሉ (በትንቢተ ዳንኤል 5፥27 ላይ "ማኔ ቴቄል ፋሬስ" ወይም "ቴቄል፤ በሚዛን ተመዘንክ፥ ቀለህም ተገኘህ" እንደሚለው)፣ የዘመናችንም ገዥዎች በመለኮት ሚዛን ቀልለው መገኘታቸውንና "ዙፋኑን ልቀቅ" የሚል ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው ይነግረናል። በተጨማሪም "እንደ ናቡቴ ደም ያንተም ደም ይፈሳል" በማለት፣ ንጉሥ አክዓብ የንጹሑን የናቡቴን ወይን ቦታ ለመቀማት ብሎ በግፍ ስላስገደለውና ፈጣሪ ውሾች ደሙን እንዲልሱት እንደፈረደበት (በ1ኛ ነገሥት 21፥19 ላይ የተጻፈውን) ታሪክ ያስታውሳል። ይህም "እጆቻችሁ ደም ተሞልተዋል" (ኢሳይያስ 1፥15) እንደሚለው፣ በግፍ ለሚገደሉ ዜጎች እግዚአብሔር ዝም እንደማይል የሚያሳይ የሰላ እና ደፋር መልእክት ነው።
ልብን ክፉኛ የሚነካው የመዝሙሩ ክፍል ዘማሪው የራሱን ቤተክርስቲያን ችግር ሳይሸሽግ በድፍረት የሚያጋልጥበት ነው። ቤተ መቅደስ የሰላም እና የመጠጊያ ስፍራ መሆኑ ቀርቶ የዘር ፖለቲካ ማራመጃ፣ እንዲሁም የጥቅም መገበያያ መሆኑን በብርቱ ያወግዛል። ዘማሪው የሚከተለውን ጠንካራ ስንኝ ሲያሰማ እንሰማለን፦
በዘር በቋንቋ ከፋፍለህ ሰጥተሃል፣
ጳጳሳቱ ተመዝነሃል፣
በዘር በቋንቋ የተሾማችሁ፣
ከመቅደሱ ውጡ ቆብ አውልቃችሁ፣
ስምንተኛው ሺ ደረሰ ህገ ቤተክርስቲያን ተጣሰ፣
የወለደ ልጅ ያለው ጳጳስ ስምንተኛው ሺ ደረሰ።
ይህ ስንኝ የቤተክርስቲያኒቱን ወቅታዊ ፈተናዎች ያለ ምንም ድብቅብቅ በቀጥታ የሚሞግት ነው። የመጀመሪያው ጉዳይ በዘር እና በቋንቋ ላይ የተመሰረተውን የሹመት ቀውስ ይመለከታል። ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ እና አግላይ ያልሆነች ተቋም ሆና ሳለች፣ የፖለቲካ እና የዘር ማከፋፈያ መሆኗን አጥብቆ ይቃወማል። ለዚህ መከፋፈል ተባባሪ የሆኑት እና በዘር የተሾሙት አባቶችም በመንፈሳዊው ሚዛን ቀልለው ስለተገኙ፣ ቆባቸውን አውልቀው ከመቅደሱ መውጣት እንዳለባቸው ያለ ፍርሃት ይሞግታል። ሐዋርያው ጳውሎስ "በክርስቶስ ኢየሱስ ሁላችሁ አንድ ናችሁና... አይሁዳዊ ወይም የግሪክ ሰው የለም" (ገላትያ 3፥28) ብሎ ያፈረሰውን የዘር ግድግዳ፣ አሁን ላይ አባቶች ራሳቸው መልሰው ሲገነቡት ማየት እጅግ ያመዋል።
ሁለተኛው ነጥብ የቤተክርስቲያኒቱ ቀኖና እና ሥርዓት መጣስን ያሳያል። "ህገ ቤተክርስቲያን ተጣሰ የወለደ ልጅ ያለው ጳጳስ" የሚለው ቃል፣ የቤተክርስቲያኒቱን ጥብቅ ህግ መናድ ያሳያል። በኦርቶዶክስ ትውፊት ጳጳስ የሚመረጠው ከምንኩስና ሕይወት በመሆኑ፣ ዓለማዊ ፍላጎቱን የገደለ እና ቤተሰብ የሌለው መሆን አለበት። ነገር ግን ይህ የቅድስና ሥርዓት ተጥሶ ዓለማዊ እና ሥጋዊ ሕይወት ያላቸው ሰዎች ወደዚህ ከፍተኛ የመንፈሳዊ አመራር ሥፍራ መምጣታቸውን በከፍተኛ ኃዘን ይገልጻል።
ሦስተኛው ጉዳይ "ስምንተኛው ሺህ" የሚለው ትንቢታዊ አገላለጽ ነው። ይህ ብሂል በኢትዮጵያዊያን ዘንድ የክፋት መብዛትን፣ የስርዓት መበላሸትን እና የማይታሰብ ድርጊት የሚፈጸምበትን የኃጢአት ዘመን ለመግለጽ የምንጠቀምበት ነው። ዘማሪው በመቅደሱ ውስጥ እንዲህ ያለ የዘር ክፍፍል እና የቀኖና ጥሰት መታየቱ የዘመኑን ክፋት፣ የሥርዓቱን መፍረስ እና የመጨረሻውን የጥፋት ዘመን መቃረብ አመላካች መሆኑን እያስጠነቀቀን ይገኛል።
ከዚህ ሁሉ ትችት እና ማስጠንቀቂያ በኋላ መዝሙሩ ተስፋ ወደ መቁረጥ ሳይሆን ወደ እውነተኛው መፍትሄ ይመራናል። የኢትዮጵያ መፍትሄ ያለው በጉልበት ወይም በጦር መሳሪያ ሳይሆን በንስሐ እና ወደ እግዚአብሔር በመመለስ መሆኑን ያሳስበናል። "እንደ ራሔል የኢትዮጵያ እናት አልቅሳ" ሲል "ድምፅ በራማ ተሰማ፥ ልቅሶና መራራ ዋይታ፤ ራሔል ስለ ልጆችዋ አለቀሰች... መጽናናትንም እንቢ አለች" (ኤርምያስ 31፥15) የሚለውን የነቢዩን ቃል በማስታወስ፣ የሀገሪቱ እናቶች በልጆቻቸው መሞት አንጀታቸው ማረሩን ይገልጻል። በመጨረሻም የኢትዮጵያ ጥንካሬ መንበርከክ መሆኑን በማንሳት፣ "ስሜ የተጠራበት ሕዝቤ ሰውነታቸውን አዋርደው ቢጸልዩ... እኔ ከሰማይ እሰማለሁ፥ ኃጢአታቸውንም ይቅር እላለሁ፥ ምድራቸውንም እፈውሳለሁ" (2ኛ ዜና መዋዕል 7፥14) የሚለውን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል በተግባር እንድናውለው ጥሪ ያደርጋል።
ይህ መዝሙር ለፖለቲከኛውም ሆነ ለሃይማኖት መሪው መስተዋት ነው። "ባለ ማዕተቦች" እና እውነተኛ አማኞች ከስሜታዊነት ወጥተው ስለውድቀታቸው እንዲያስቡ፣ እንዲጸልዩ እና ወደ ፈጣሪያቸው እንዲመለሱ የሚጠይቅ የነፍስ ጥሪ ነው።
ለዘ-ሐበሻ ማርታ ከሚኒሶታ
11 days ago
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ያዘጋጀው 18ኛው የመጻሕፍት ኤግዚቢሽን በይፋ መካሄድ ጀመረ
#ethiopia | ታላቅ የዕውቀት እና የባህል መድረክ የሆነው ባለታሪኩ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጀመረው 18ኛው የመጽሐፍት ዓውደ ርዕይ ከሰኔ 1 እስከ ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ በድምቀት መካሄዱን ቀጥሏል።
በዝግጅቱ መክፈቻ ሥነ ሥርዓት ላይ የተገኙት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ባደረጉት ንግግር ተቋሙ ላለፉት አሥር ዓመታት ለንባብ ባህል ማደግና ለመጻሕፍት ስርጭት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ሲሠራ መቆየቱን ጠቁመው፣ የዚህን ዓውደ ርዕይ ቀጣይነት በላቀ ሁኔታ ማስጠበቅና ይበልጥ ተደራሽ ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
በተመሳሳይ የዩኒቨርሲቲው ፕረስ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ዶክተር ደርብ አዶ በበኩላቸው ዝግጅቱ በየጊዜው በይዘቱም ሆነ በተሳታፊዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መምጣቱን በዝርዝር አብራርተዋል።
በዚህ ታላቅ የዕውቀት መድረክ ላይ ከ45 በላይ የሚሆኑ መጽሐፍት አከፋፋዮች፣ ዋና ዋና አሳታሚዎችና ታዋቂ የመጽሐፍት መደብሮች የተሳተፉ ሲሆን፣ በሁሉም የዕውቀት ዘርፎች ከፍተኛ ተፈላጊነት ያላቸው መጻሕፍት ከ20 እስከ 50 በመቶ በሚደርስ ትልቅ ቅናሽ ለጎብኚዎች እየቀረቡ ይገኛሉ።
ከሽያጭና ከግዢ ስምምነቶች ባሻገርም የአዳዲስ መጻሕፍት ምረቃ ሥነ ሥርዓቶች፣ አንጋፋ ደራሲያንና ምሁራን ለወጣቱ ትውልድ ጠቃሚ ተሞክሯቸውን የሚያካፍሉባቸው የውይይት መድረኮች እንዲሁም የሕፃናትን የንባብ ልማድ የሚያበረታቱ ልዩ ልዩ ዝግጅቶች በዓውደ ርዕዩ ቀናት ውስጥ የሚጠበቁ ማራኪ መርሃግብሮች መሆናቸው ታውቋል።
#aaubookfair2018 #ethiopianliterature #readtolead #addisababauniversity #bookfair #ethiopia #ንባብለህይወት #የመጽሐፍትዓውደር #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ታላቅ የዕውቀት እና የባህል መድረክ የሆነው ባለታሪኩ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጀመረው 18ኛው የመጽሐፍት ዓውደ ርዕይ ከሰኔ 1 እስከ ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ በድምቀት መካሄዱን ቀጥሏል።
በዝግጅቱ መክፈቻ ሥነ ሥርዓት ላይ የተገኙት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ባደረጉት ንግግር ተቋሙ ላለፉት አሥር ዓመታት ለንባብ ባህል ማደግና ለመጻሕፍት ስርጭት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ሲሠራ መቆየቱን ጠቁመው፣ የዚህን ዓውደ ርዕይ ቀጣይነት በላቀ ሁኔታ ማስጠበቅና ይበልጥ ተደራሽ ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
በተመሳሳይ የዩኒቨርሲቲው ፕረስ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ዶክተር ደርብ አዶ በበኩላቸው ዝግጅቱ በየጊዜው በይዘቱም ሆነ በተሳታፊዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መምጣቱን በዝርዝር አብራርተዋል።
በዚህ ታላቅ የዕውቀት መድረክ ላይ ከ45 በላይ የሚሆኑ መጽሐፍት አከፋፋዮች፣ ዋና ዋና አሳታሚዎችና ታዋቂ የመጽሐፍት መደብሮች የተሳተፉ ሲሆን፣ በሁሉም የዕውቀት ዘርፎች ከፍተኛ ተፈላጊነት ያላቸው መጻሕፍት ከ20 እስከ 50 በመቶ በሚደርስ ትልቅ ቅናሽ ለጎብኚዎች እየቀረቡ ይገኛሉ።
ከሽያጭና ከግዢ ስምምነቶች ባሻገርም የአዳዲስ መጻሕፍት ምረቃ ሥነ ሥርዓቶች፣ አንጋፋ ደራሲያንና ምሁራን ለወጣቱ ትውልድ ጠቃሚ ተሞክሯቸውን የሚያካፍሉባቸው የውይይት መድረኮች እንዲሁም የሕፃናትን የንባብ ልማድ የሚያበረታቱ ልዩ ልዩ ዝግጅቶች በዓውደ ርዕዩ ቀናት ውስጥ የሚጠበቁ ማራኪ መርሃግብሮች መሆናቸው ታውቋል።
#aaubookfair2018 #ethiopianliterature #readtolead #addisababauniversity #bookfair #ethiopia #ንባብለህይወት #የመጽሐፍትዓውደር #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
11 days ago
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 18ኛው የመጽሐፍት ዓውደ ርዕይ ተጀመረ
*******************
ትልቅ የዕውቀት እና የባህል መድረክ የሆነው 18ኛው የመጽሐፍት ዓውደ ርዕይ ከሰኔ 1 እስከ ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ በድምቀት ይካሄዳል።
ዩኒቨርስቲው 10 ዓመታትን በተሻገሩት ጊዜያት ለንባብና ለመፃህፍት ትልቅ ትኩረት በመስጠት እየሰራ መሆኑን የተናገሩት የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ዩኒቨርስቲው የአውደርዕዩን ቀጣይነት ማስጠበቅና ለውጡ የፈጠረውን እድል ተጠቅሞ ይበልጥ ተደራሽ እንዲሆን ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።
በአውደ ርዕዩ ከ45 በላይ መጽሐፍት አከፋፋዮች፣ አሳታሚዎችና የመጽሐፍት መደብሮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
በሁሉም የዕውቀት ዘርፎች ከፍተኛ ተፈላጊነት ያላቸው መጽሐፍት ለጎብኚዎች እንደቀረቡም ተጠቁሟል።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕረስ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ዶ/ር ደርብ አዶ አውደ ርዕዩ ከዘመኑ ጋር እያደገ በስፋትም በተሳታፊዎች ቁጥርም መሻሻሉን ተናግረዋል።
ያነጋገርናቸው መፃህፍት ሻጮችም በአውደርዕዩ ከ20 እስከ 50 በመቶ ቅናሽ በሚሆን ዋጋ መፅሀፍቶችን እየሸጡ እንደሆነ ገልፀውልናል።
የአዳዲስ መጽሐፍት ምረቃ ሥነ ሥርዓቶች፣ ታዋቂና አንጋፋ ደራሲያን ተሞክሯቸውን ለወጣቱ ትውልድ የሚያካፍሉባቸው የውይይት መድረኮች እንዲሁም የሕፃናት የንባብ ማበረታቻ ልዩ ዝግጅቶችም ዓውደርዕዩ በሚቀጥልባቸው ቀናት የሚጠበቁ መርሃግብሮች ናቸው።
በዳዊት ጣሰው
Ethiopian Broadcasting Corporation #አዲስአበባዩኒቨርስቲ #መጽሐፍት #ኢትዮጵያ
*******************
ትልቅ የዕውቀት እና የባህል መድረክ የሆነው 18ኛው የመጽሐፍት ዓውደ ርዕይ ከሰኔ 1 እስከ ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ በድምቀት ይካሄዳል።
ዩኒቨርስቲው 10 ዓመታትን በተሻገሩት ጊዜያት ለንባብና ለመፃህፍት ትልቅ ትኩረት በመስጠት እየሰራ መሆኑን የተናገሩት የዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ዩኒቨርስቲው የአውደርዕዩን ቀጣይነት ማስጠበቅና ለውጡ የፈጠረውን እድል ተጠቅሞ ይበልጥ ተደራሽ እንዲሆን ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።
በአውደ ርዕዩ ከ45 በላይ መጽሐፍት አከፋፋዮች፣ አሳታሚዎችና የመጽሐፍት መደብሮች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
በሁሉም የዕውቀት ዘርፎች ከፍተኛ ተፈላጊነት ያላቸው መጽሐፍት ለጎብኚዎች እንደቀረቡም ተጠቁሟል።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕረስ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ዶ/ር ደርብ አዶ አውደ ርዕዩ ከዘመኑ ጋር እያደገ በስፋትም በተሳታፊዎች ቁጥርም መሻሻሉን ተናግረዋል።
ያነጋገርናቸው መፃህፍት ሻጮችም በአውደርዕዩ ከ20 እስከ 50 በመቶ ቅናሽ በሚሆን ዋጋ መፅሀፍቶችን እየሸጡ እንደሆነ ገልፀውልናል።
የአዳዲስ መጽሐፍት ምረቃ ሥነ ሥርዓቶች፣ ታዋቂና አንጋፋ ደራሲያን ተሞክሯቸውን ለወጣቱ ትውልድ የሚያካፍሉባቸው የውይይት መድረኮች እንዲሁም የሕፃናት የንባብ ማበረታቻ ልዩ ዝግጅቶችም ዓውደርዕዩ በሚቀጥልባቸው ቀናት የሚጠበቁ መርሃግብሮች ናቸው።
በዳዊት ጣሰው
Ethiopian Broadcasting Corporation #አዲስአበባዩኒቨርስቲ #መጽሐፍት #ኢትዮጵያ
Sponsored by
Surafel
16 days ago
የአቡነ ሀብተ ማርያም ምልጃ እና ረድኤት አይለየን🙏
በነገሥታት ፊት የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት መሰከረ።
በምጽዋትና በስገድት የምትጋደለው እናቱ ዮስቴና ሀብቷን ሁሉ ለድሆች ሰጥታ ለምናኔ ወደ በረኃ ሄደች። በዚያ ያገኘችው ባሕታዊም በመንፈስ ቅዱስ ተገልጦለት ከእርሷ ቅዱስ ፍሬ እንደሚወጣ ነግሮ ወደ ዓለም እንድትመለስ አዘዛት። እርሷም “እግዚአብሔር የወደደው ይሁን” ብላ እያመሰገነች ተመልሰች፡፡ የአባቱ የትውልድ ሀገር የራውዕይ በምትባል ሀገር ሲሆን ከዚህች የተባረከች ሴት ጋር ተጋባ። እርሷም በበጎ ምግባርና ሥራ የተጌጠች፣ በሕግ ተወስና በጾም፣ በጸሎት፣ የምትተጋ ነበረች። ከጥቂት ጊዜያት በኋላም ወንድ ልጅ ወለደች። እንደ ሥርዓቱም ሲጠመቅ የመጽሐፍ ስሙን “ሀብተ ማርያም” አሉት። በሕገ እግዚአብሔር አንጸው አሳደጉት። ወደ ቤተ ክርስቲያንም ሲወስዱት “እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ” የሚለውን ጸሎት ቢሰማ እጅጉን ወደዳት። እርሷንም ይዞ ከቤቱ ሌሊቱን የሚጸልይና የሚጋደል ሆነ።
አንድ ቀን የአባቱ በጎቹን ሲጠብቅ የበግ ጠባቂዎቹን “ዛሬ ዝናም ይዘንማልና እንግባ” አላቸው። እነርሱም “ምን ደመና አለ፤ ቀኑ ብራ ነው” አሉት። እርሱ ግን በጎቹን ይዞ ወደ ቤቱ እንደገባ ኃይለኛ፣ ነፋስና መብረቅ የቀላቀለ ዝናም ዘነመ። በሌላም ጊዜ እንዲሁ አንድ እረኛ የሀብተ ማርያምን በትሩን በጉልበት ነጠቀው። “መልስልኝ” ብሎ በስመ እግዚአብሔር ቢያምለውም እምቢ አለው። በተወው ጊዜ እግዚአብሔር ያን እረኛ በአየር ላይ ሠቅሎ አዋለው። እረኞቹም ሀብተ ማርያምን ሲለምኑት፣ እግዚአብሔር ነውና ስለ ስሙ ብሎ የቀጣው መሐሪው እርሱ ከወደደ ይማረው ሲል ያ እረኛ ተፈታና ወረደ። መጥቶም ከአባታችን እግር ስር ወደቀ፡፡ በኋላም ስሟ እለ አድባር ወደምትባል ገዳም ገብቶ ከአባ መልከ ጼዴቅ እጅ መነኰሶ ታላቅ ተጋድሎ ይጋደል ጀመር። በባሕር መካከልም በመቆም መዝሙረ ዳዊትን ይደግምና ግንባሩም የባሕሩን አሸዋ እስኪነካ 500 ጊዜ ይሰግዳል።
እህልም መቅመስን ትቶ የዱር ቅጠል የሚመገብ ሆነ። ዐርባ ዐርባ፣ ሰማንያ ሰማንያ ቀንም ያከፍላል። በሌሊትም ቁሞ በማደር በቀንም አራቱን ወንጌላት ዘወትር ይጸልያል። ተጋድሎውንም ያየ አምላካችን ተገለጠለት። አባ ሀብተ ማርያምም ከግርማው የተነሣ ደንግጦ በግንባሩ ተደፋ። ጌታችንም እፍ ብሉ አጽናንቶ አሥነሳውና ጽኑዕ ተጋድሎው በሰማያት መጻፉን ነገረው፡፡ ስለ ድንግልናው፣ ስለ ምናኔው፣ ስለ ፍጹም ምንኲስናው፣ አራቱን ወንጌላት አዘውትሮ በማንበቡ፣ ረኃብና ጥምን በመታገሡ፣ በልቡ ቂምንና በቀልን ባለማኖሩ፣ ስለ ንጹሕ የክህነት አገልግሎቱና በንጽሕና ስለሚያሣርገው መሥዋዕቱ ሰባት እጅግ የሚያስደንቁ አክሊላትንም አቀዳጀው። የቅዱስ ማቴዎስንና የቅዱስ ማርቆስን ወንጌል ሲያነብ ከሌሎች ሥውራን አበው ጋር የሚገናኝበትን የብርሃን ሠረገላ ሰጠው፡፡
የቅዱስ ሉቃስንና የቅዱስ ዮሐንስን ወንጌል ሲያነብም ሥጋውን ደሙን ለመቀበል ወደ ኢየሩሳሌም የሚሄድበትን የእሳት ሠረገላ ሰጠውና ቃል ኪዳን ገባለት። መታሰቢያውን ለሚያደርጉና በስሙ ለሚዘክሩ፣ ከእነርሱ ጋር የሚኖርበትን አምስት መቶ የወርቅ አምዶች ያሏትን ቦታ ሰጠሁህ አለው። ቅዱሳን መላእክት ሁሉ እየተደሰቱ አባታችን አቡነ ሐብተ ማርያምን “ወንድማችን ወደማያልቀው ሰማያዊ ደስታ ልንወስድህ መጥተናል” አሉት። ይህንንም በተናገረ ጊዜ ጌታችን በሦስትነቱ ተገልጦ ታየው። በኅዳር 26 ቀን ነፍሱ ከሥጋው በሰላም ተለየች። ቅዱሳን መላእክትም በታላቅ ደስታ እያመሰገኑ አሣረጓት። ገዳማውያን የዓለምን ክብር ንቀው ሔደዋልና ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፡፡ በዓታቸውን እናጽና ገዳማቸውን እንደግፍ የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
በነገሥታት ፊት የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት መሰከረ።
በምጽዋትና በስገድት የምትጋደለው እናቱ ዮስቴና ሀብቷን ሁሉ ለድሆች ሰጥታ ለምናኔ ወደ በረኃ ሄደች። በዚያ ያገኘችው ባሕታዊም በመንፈስ ቅዱስ ተገልጦለት ከእርሷ ቅዱስ ፍሬ እንደሚወጣ ነግሮ ወደ ዓለም እንድትመለስ አዘዛት። እርሷም “እግዚአብሔር የወደደው ይሁን” ብላ እያመሰገነች ተመልሰች፡፡ የአባቱ የትውልድ ሀገር የራውዕይ በምትባል ሀገር ሲሆን ከዚህች የተባረከች ሴት ጋር ተጋባ። እርሷም በበጎ ምግባርና ሥራ የተጌጠች፣ በሕግ ተወስና በጾም፣ በጸሎት፣ የምትተጋ ነበረች። ከጥቂት ጊዜያት በኋላም ወንድ ልጅ ወለደች። እንደ ሥርዓቱም ሲጠመቅ የመጽሐፍ ስሙን “ሀብተ ማርያም” አሉት። በሕገ እግዚአብሔር አንጸው አሳደጉት። ወደ ቤተ ክርስቲያንም ሲወስዱት “እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ” የሚለውን ጸሎት ቢሰማ እጅጉን ወደዳት። እርሷንም ይዞ ከቤቱ ሌሊቱን የሚጸልይና የሚጋደል ሆነ።
አንድ ቀን የአባቱ በጎቹን ሲጠብቅ የበግ ጠባቂዎቹን “ዛሬ ዝናም ይዘንማልና እንግባ” አላቸው። እነርሱም “ምን ደመና አለ፤ ቀኑ ብራ ነው” አሉት። እርሱ ግን በጎቹን ይዞ ወደ ቤቱ እንደገባ ኃይለኛ፣ ነፋስና መብረቅ የቀላቀለ ዝናም ዘነመ። በሌላም ጊዜ እንዲሁ አንድ እረኛ የሀብተ ማርያምን በትሩን በጉልበት ነጠቀው። “መልስልኝ” ብሎ በስመ እግዚአብሔር ቢያምለውም እምቢ አለው። በተወው ጊዜ እግዚአብሔር ያን እረኛ በአየር ላይ ሠቅሎ አዋለው። እረኞቹም ሀብተ ማርያምን ሲለምኑት፣ እግዚአብሔር ነውና ስለ ስሙ ብሎ የቀጣው መሐሪው እርሱ ከወደደ ይማረው ሲል ያ እረኛ ተፈታና ወረደ። መጥቶም ከአባታችን እግር ስር ወደቀ፡፡ በኋላም ስሟ እለ አድባር ወደምትባል ገዳም ገብቶ ከአባ መልከ ጼዴቅ እጅ መነኰሶ ታላቅ ተጋድሎ ይጋደል ጀመር። በባሕር መካከልም በመቆም መዝሙረ ዳዊትን ይደግምና ግንባሩም የባሕሩን አሸዋ እስኪነካ 500 ጊዜ ይሰግዳል።
እህልም መቅመስን ትቶ የዱር ቅጠል የሚመገብ ሆነ። ዐርባ ዐርባ፣ ሰማንያ ሰማንያ ቀንም ያከፍላል። በሌሊትም ቁሞ በማደር በቀንም አራቱን ወንጌላት ዘወትር ይጸልያል። ተጋድሎውንም ያየ አምላካችን ተገለጠለት። አባ ሀብተ ማርያምም ከግርማው የተነሣ ደንግጦ በግንባሩ ተደፋ። ጌታችንም እፍ ብሉ አጽናንቶ አሥነሳውና ጽኑዕ ተጋድሎው በሰማያት መጻፉን ነገረው፡፡ ስለ ድንግልናው፣ ስለ ምናኔው፣ ስለ ፍጹም ምንኲስናው፣ አራቱን ወንጌላት አዘውትሮ በማንበቡ፣ ረኃብና ጥምን በመታገሡ፣ በልቡ ቂምንና በቀልን ባለማኖሩ፣ ስለ ንጹሕ የክህነት አገልግሎቱና በንጽሕና ስለሚያሣርገው መሥዋዕቱ ሰባት እጅግ የሚያስደንቁ አክሊላትንም አቀዳጀው። የቅዱስ ማቴዎስንና የቅዱስ ማርቆስን ወንጌል ሲያነብ ከሌሎች ሥውራን አበው ጋር የሚገናኝበትን የብርሃን ሠረገላ ሰጠው፡፡
የቅዱስ ሉቃስንና የቅዱስ ዮሐንስን ወንጌል ሲያነብም ሥጋውን ደሙን ለመቀበል ወደ ኢየሩሳሌም የሚሄድበትን የእሳት ሠረገላ ሰጠውና ቃል ኪዳን ገባለት። መታሰቢያውን ለሚያደርጉና በስሙ ለሚዘክሩ፣ ከእነርሱ ጋር የሚኖርበትን አምስት መቶ የወርቅ አምዶች ያሏትን ቦታ ሰጠሁህ አለው። ቅዱሳን መላእክት ሁሉ እየተደሰቱ አባታችን አቡነ ሐብተ ማርያምን “ወንድማችን ወደማያልቀው ሰማያዊ ደስታ ልንወስድህ መጥተናል” አሉት። ይህንንም በተናገረ ጊዜ ጌታችን በሦስትነቱ ተገልጦ ታየው። በኅዳር 26 ቀን ነፍሱ ከሥጋው በሰላም ተለየች። ቅዱሳን መላእክትም በታላቅ ደስታ እያመሰገኑ አሣረጓት። ገዳማውያን የዓለምን ክብር ንቀው ሔደዋልና ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፡፡ በዓታቸውን እናጽና ገዳማቸውን እንደግፍ የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
16 days ago
የአቡነ ሀብተ ማርያም ምልጃ እና ረድኤት አይለየን🙏
በነገሥታት ፊት የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት መሰከረ።
የአባቱ የትውልድ ሀገር የራውዕይ በምትባል ሀገር ሲሆን ሀብቷን ሁሉ ለድሆች ሰጥታ ለምናኔ ገዳም ስትገባ የተቀደሰ ልጅ እንደምትወልድ ተነግሯት የተመለሰችው እናቱ ዮስቲና ትባላለች። ልጅም ሲወልዱ የመጽሐፍ ስሙን “ሀብተ ማርያም” አሉት። በሕገ እግዚአብሔርም አንጸው አሳደጉት።
በቤተ ክርስቲያንም የሰማውን “እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ” የምትል ጸሎት እጅጉን ቢወዳት ሌሊቱን ሙሉ በቤቱ እየጸለያት የሚጋደል ሆነ። አንድ ቀን የአባቱ በጎቹን ሲጠብቅ ጓደኞቹን “ዝናም ይዘንማልና ወደቤት እንግባ” አላቸው። ቃሉን ሊሰሙት ባይወዱ በጎቹን ይዞ ወደ ቤቱ እንደገባ፣ ነፋስና መብረቅ የቀላቀለ ኃይለኛ ዝናም ዘነመ። ገና በአዳጊነት እድሜውም ብዙ ተአምራት ያደርግ ነበር፡፡
በኋላም ስሟ እለ አድባር ወደምትባል ገዳም ገብቶ ከአባ መልከ ጼዴቅ እጅ መነኰሶ ታላቅ ተጋድሎ ይጋደል ጀመር። በባሕር መካከልም በመቆም መዝሙረ ዳዊትን ይደግምና ግንባሩም የባሕሩን አሸዋ እስኪነካ 500 ጊዜ ይሰግዳል። እህልም መቅመስን ትቶ የዱር ቅጠል የሚመገብ ሆነ። ዐርባ ዐርባ፣ ሰማንያ ሰማንያ ቀንም ያከፍላል። በሌሊትም ቁሞ በማደር በቀንም አራቱን ወንጌላት ዘወትር ይጸልያል። ተጋድሎውንም ያየ ጌታችን ተገለጠለት። አቡነ ሀብተ ማርያምም ከግርማው የተነሣ ደንግጦ በግንባሩ ተደፋ። ጌታችንም እፍ ብሉ አጽናንቶ አሥነሳውና ጽኑዕ ተጋድሎው በሰማያት መጻፉን ነገረው፡፡
ስለ ድንግልናው፣ ስለ ምናኔው፣ ስለ ፍጹም ምንኲስናው፣ አራቱን ወንጌላት አዘውትሮ ስለማንበቡ፣ ስለተጋድሎው፣ ስለ ንጹሕ የክህነት አገልግሎቱና በንጽሕና ስለሚያሣርገው መሥዋዕቱ ሰባት እጅግ የሚያስደንቁ አክሊላትንም አቀዳጀው። ከሥውራን አበው ጋር የሚገናኝበትንና ሥጋውን ደሙን ለመቀበል ወደ ኢየሩሳሌም የሚሄድበትን የብርሃን ሠረገላም ሰጠው፣ መታሰቢያውን የሚያደርጉትን እንደሚምርለትም፣ ቃል ኪዳን ገባለት። በኅዳር 26 ቀን ነፍሱ ከሥጋው ስትለይም ቅዱሳን መላእክትም በታላቅ ደስታ አሣረጓት። ገዳማውያን የዓለምን ክብር ንቀው ሔደዋልና ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፤ ገዳማቸውን እንደግፍ ከበረከታቸውም እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
በነገሥታት ፊት የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት መሰከረ።
የአባቱ የትውልድ ሀገር የራውዕይ በምትባል ሀገር ሲሆን ሀብቷን ሁሉ ለድሆች ሰጥታ ለምናኔ ገዳም ስትገባ የተቀደሰ ልጅ እንደምትወልድ ተነግሯት የተመለሰችው እናቱ ዮስቲና ትባላለች። ልጅም ሲወልዱ የመጽሐፍ ስሙን “ሀብተ ማርያም” አሉት። በሕገ እግዚአብሔርም አንጸው አሳደጉት።
በቤተ ክርስቲያንም የሰማውን “እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ” የምትል ጸሎት እጅጉን ቢወዳት ሌሊቱን ሙሉ በቤቱ እየጸለያት የሚጋደል ሆነ። አንድ ቀን የአባቱ በጎቹን ሲጠብቅ ጓደኞቹን “ዝናም ይዘንማልና ወደቤት እንግባ” አላቸው። ቃሉን ሊሰሙት ባይወዱ በጎቹን ይዞ ወደ ቤቱ እንደገባ፣ ነፋስና መብረቅ የቀላቀለ ኃይለኛ ዝናም ዘነመ። ገና በአዳጊነት እድሜውም ብዙ ተአምራት ያደርግ ነበር፡፡
በኋላም ስሟ እለ አድባር ወደምትባል ገዳም ገብቶ ከአባ መልከ ጼዴቅ እጅ መነኰሶ ታላቅ ተጋድሎ ይጋደል ጀመር። በባሕር መካከልም በመቆም መዝሙረ ዳዊትን ይደግምና ግንባሩም የባሕሩን አሸዋ እስኪነካ 500 ጊዜ ይሰግዳል። እህልም መቅመስን ትቶ የዱር ቅጠል የሚመገብ ሆነ። ዐርባ ዐርባ፣ ሰማንያ ሰማንያ ቀንም ያከፍላል። በሌሊትም ቁሞ በማደር በቀንም አራቱን ወንጌላት ዘወትር ይጸልያል። ተጋድሎውንም ያየ ጌታችን ተገለጠለት። አቡነ ሀብተ ማርያምም ከግርማው የተነሣ ደንግጦ በግንባሩ ተደፋ። ጌታችንም እፍ ብሉ አጽናንቶ አሥነሳውና ጽኑዕ ተጋድሎው በሰማያት መጻፉን ነገረው፡፡
ስለ ድንግልናው፣ ስለ ምናኔው፣ ስለ ፍጹም ምንኲስናው፣ አራቱን ወንጌላት አዘውትሮ ስለማንበቡ፣ ስለተጋድሎው፣ ስለ ንጹሕ የክህነት አገልግሎቱና በንጽሕና ስለሚያሣርገው መሥዋዕቱ ሰባት እጅግ የሚያስደንቁ አክሊላትንም አቀዳጀው። ከሥውራን አበው ጋር የሚገናኝበትንና ሥጋውን ደሙን ለመቀበል ወደ ኢየሩሳሌም የሚሄድበትን የብርሃን ሠረገላም ሰጠው፣ መታሰቢያውን የሚያደርጉትን እንደሚምርለትም፣ ቃል ኪዳን ገባለት። በኅዳር 26 ቀን ነፍሱ ከሥጋው ስትለይም ቅዱሳን መላእክትም በታላቅ ደስታ አሣረጓት። ገዳማውያን የዓለምን ክብር ንቀው ሔደዋልና ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፤ ገዳማቸውን እንደግፍ ከበረከታቸውም እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
16 days ago
(ከተዋሕዶ ወርልድ) የአርሲ ተራሮች ለዘመናት የሰላም፣ የግብርና እና የአብሮነት ምልክት ሆነው ኖረዋል። የጠዋቱ ጸሐይ ሲወጣ የከብቶች ጩኸት፣ የእረኞች ዜማ እና የቤተ ክርስቲያን የደወል ድምፅ ተቀናጅተው መንፈስን የሚያድስ ተስፋን ይሰጡ ነበር። ዛሬ ግን... ዛሬ ከእነዚህ ተራሮች ጀርባ የሚወጣው ጭስ የዕጣን አይደለም፤ የቃጠሎ ነው። ዛሬ የሚሰማው ድምፅ የዝማሬ ሳይሆን የእንባ እና የዋይታ ነው። ከግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሺርካ እና በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳዎች ላይ ያንዣበበው የሞት ጥላ፣ ንጹሐንን በግፍ ቀጥፏል፤ ታሪካዊ መቅደሶችንም ወደ አመድነት ቀይሯል።
ይህ የተዋህዶ ወርልድ ትንታኔ የቁጥሮች ድምር አይደለም፤ የ13 የከበሩ የሰው ልጆች ሕይወት መነጠቅ፣ የ101 ዓመት ታሪክ መቃጠል፣ እና የ280 ዜጎች በባዶ እጅ መሰደድ ታሪክ እንጂ። ይህ፣ ሃይማኖት እና ማንነትን መሠረት አድርጎ የሚፈጸም አክራሪነት የሰውን ልጅ ምን ያህል ወደ አውሬነት እንደሚቀይረው የሚያሳይ የዘመናችን ህያው ማሳያ ነው።
የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያንን እናስበው። ለ101 ዓመታት ሙሉ፣ አባቶች እና እናቶች በደጃፉ ተንበርክከው ፈጣሪያቸውን ተማጽነዋል። በዚያ መቅደስ ውስጥ ስንቱ ተጠምቋል? ስንቱ ተክሊል አስሯል? ስንቱስ በጸሎት ተጽናንቷል? ከአንድ ምዕተ ዓመት በላይ የቆመው ይህ የጸጋ ቤት፣ የበርካታ ትውልዶች የእምነት ማህደር ነበር። ነገር ግን፣ ጥላቻ ታሪክን አያውቅም፤ ክፋት ቅድስናን አይረዳም። በአንድ ጀንበር፣ ያ ሁሉ ታሪክ፣ ያ ሁሉ የእንጨት ጠረንና የዕጣን መዓዛ፣ በጭካኔ እሳት ተበላ።
በሌላ በኩል ደግሞ የካራ ኩፍተና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ዕጣ ፈንታ ሌላ ልብ ሰባሪ ትዕይንት ነበር። ታጣቂዎች መቅደሱን ሲዘርፉ፣ አማኞች የራሳቸውን ሕይወት እና ንብረት ለማዳን አልተጣደፉም። ይልቁንም፣ መኖሪያ ቤታቸው እያዩት በእሳት ሲጋይ፣ የዕድሜ ልክ ጥሪታቸው፣ ከብቶቻቸውና ማሳቸው ሲዘረፍ፣ እነርሱ ግን ከሁሉ የሚያስበልጡትን የቤተ ክርስቲያኑን ጽላት (ታቦት) በደረታቸው አቅፈው በጨለማ ወደማያውቁት ስደት መጓዝን መረጡ።
ይህ ትዕይንት ወደ ኋላ መለስ ብለን የመጽሐፍ ቅዱስን ታሪክ እንድናስታውስ ያደርገናል። እስራኤላውያን ታቦተ ጽዮንን ተሸክመው በበረሃ እንደተጓዙት ሁሉ፣ የአርሲ ምእመናንም አምላካቸውን በደረታቸው አቅፈው መከራውን ተቀበሉ።
ሞት በቁጥር ሲገለጽ ስሜት አይሰጥም፤ ነገር ግን እያንዳንዱ ቁጥር ከጀርባው ቤተሰብ፣ ተስፋ እና ህልም አለው። በአጠቃላይ 13 ንጹሐን ኦርቶዶክሳውያን በግፍ ተገድለዋል።
የ80 ዓመቱን አቶ አማረ በላይነህን እንመልከት። እኚህ አረጋዊ በህይወት ዘመናቸው ስንት መንግስታትን አይተዋል? ስንት የሀገር መከራን አሳልፈዋል? በስተእርጅናቸው ዘመን ክፋት አላርፍ ብሎ አስጨናቂ ሞትን አመጣባቸው። የ70 ዓመት የዕድሜ ባለጸጋ የሆኑት አቶ ደምረው አበራ፣ አቶ ሐይሉ ንጉሴ እና አቶ ሰሙ አባይነህም እንዲሁ የዚህ ጭካኔ ሰለባ ሆነዋል። እነዚህ አባቶች ለሀገር ምርቃት እንጂ መርገም ያልነበሩ፣ በእምነታቸው ጸንተው የኖሩ የሰላም ሰዎች ነበሩ።
እንደነ እሸቴ ዳመና (42 ዓመት) እና አበባየሁ ዳኜ (42 ዓመት) ያሉ የጎልማሳነት ዘመናቸው ላይ የነበሩ አባወራዎች ሲገደሉ፣ ከጀርባቸው ስንት ቤተሰብ በትነው እንደሄዱ ማሰብ ያሳምማል። ገና ለሀገር እና ለወገን ይደርሳሉ የተባሉ ወጣቶችም የዚህ ጽዋ ቀማሾች ሆነዋል። ተሬ ደሴ (የ25 ዓመት ወጣት)፣ ገነነ ጥላሁን እና ሙርቴሳ ጥላሁን በሺርካ ወረዳ ሕልማቸው ተጨናግፎ፣ ደማቸው በመሬት ላይ ፈሷል።
አቶ ንጉሱ ማንደፍሮ፣ አቶ በቀለ ኃ/ሚካኤል፣ ከፈለኝ ልክየለው... እነዚህ ስሞች ዝም ብለው በወረቀት ላይ የሰፈሩ አይደሉም። እነዚህ አባቶች ያሏቸው፣ እናቶች ያሳደጓቸው፣ ልጆች የሚጠብቋቸው ነፍሶች ነበሩ። በሃይማኖታቸው ምክንያት ብቻ በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደሉ።
ይህ ዓይነቱ እምነትን መሠረት ያደረገ መከራ፣ በዓለማችን ታሪክ አዲስ አይደለም። የሰው ልጅ በፈጣሪው በማመኑ ብቻ የተከፈለው ዋጋ ብዙ ነው።
ወደ ሩቅ ጎረቤት ሀገር ግብጽ ስንሄድ የኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ለዘመናት በእምነታቸው ምክንያት ከፍተኛ ዋጋ ሲከፍሉ ኖረዋል። በተለይም እ.ኤ.አ. በ2015 በሊቢያ የባህር ዳርቻ አይ ኤስ በተባለው አሸባሪ ቡድን የታረዱት 21 የግብጽ ኮፕቲክ ክርስቲያኖችን ዓለም መቼም አይረሳም። ቢላዋ በአንገታቸው ላይ ሲያርፍ እንኳን የፈጣሪያቸውን ስም እየጠሩ በድፍረት ሰማዕትነትን ተቀብለዋል። የአርሲዎቹም ሰማዕታት ከዚሁ የጽናት መንገድ የወጡ አይደሉም። ኢትዮጵያውያንም በተመሳሳይ በሊቢያ እንዲሁ።
ወደ ምዕራብ አፍሪካ ስናቀና ደግሞ ናይጄሪያ እናገኛለን። በቦኮሃራም እና በአክራሪ የፉላኒ ታጣቂዎች አማካኝነት በሰሜን እና በመካከለኛው የሀገሪቱ ክፍል በሺዎች የሚቆጠሩ ክርስቲያኖች አብያተ ክርስቲያናቶቻቸው ተቃጥለውባቸው፣ መንደራቸው ወድሞ በግፍ ተጨፍጭፈዋል።
የአርሜንያ የዘር ማጥፋት ታሪክም ሌላው ትልቅ ትምህርት ነው። በ1915 በኦቶማን ኢምፓየር ዘመን፣ ከአንድ ሚሊዮን በላይ አርመናውያን በክርስትና እምነታቸው እና በማንነታቸው ምክንያት ብቻ በግፍ ተጨፍጭፈዋል፣ በበረሃም ተሰደው አልቀዋል። ነገር ግን ዛሬ አርሜንያውያን ከየትኛውም ጊዜ በላይ አብበው፣ እምነታቸውንም አጽንተው ይገኛሉ። ጥይት እና እሳት ስጋን ሊገድል ይችላል፣ እምነትን እና መንፈስን ግን መቼም ሊያጠፋ አይችልም።
ታዋቂው የጥንት ቤተ ክርስቲያን ጸሐፊ ቴርቱሊያን እንዳለው፡-
"የሰማዕታት ደም የቤተ ክርስቲያን ዘር ነው።"
በአርሲ ተራሮች ላይ የፈሰሰው የነ አቶ አማረ፣ የነ ወጣት ተሬ ደሴ ደም በከንቱ አይቀርም። የቤተ ክርስቲያን ታሪክ እንደሚያስተምረን፣ መከራ በበዛ ቁጥር፣ መቅደሶች በነደዱ ቁጥር፣ የእምነት ስር ይበልጥ ይጠልቃል እንጂ አይደርቅም።
በእንደዚህ ዓይነት ጥልቅ ሀዘን እና የሰብአዊነት ውድቀት ውስጥ ስናልፍ፣ የሰው ልጅ ታሪክ ካፈራቸው ታላላቅ መሪዎች እና ፈላስፎች የምንማረው ብዙ ነገር አለ። ጭካኔን በጭካኔ መመለስ የትም አያደርስም።
የሰብአዊ መብት ታጋዩ ማርቲን ሉተር ኪንግ ጁኒየር (የተናገረው ኃያል ቃል በዚህ ጊዜ ትዝ ይለናል፡-
"ጨለማ ጨለማን ሊያባርር አይችልም፤ ይህንን ማድረግ የሚችለው ብርሃን ብቻ ነው። ጥላቻ ጥላቻን ሊያጠፋ አይችልም፤ ይህንን ማድረግ የሚችለው ፍቅር ብቻ ነው።"
በአርሲ የተፈጸመው ድርጊት የጨለማ እና የጥላቻ ፍሬ ነው። ነገር ግን የተፈናቀሉት ምዕመናን ጽላቱን አቅፈው መውጣታቸው፣ ብርሃንን እና ፍቅርን ምርጫቸው እንዳደረጉ ያሳያል።
የሰላም ኖቤል ሽልማት አሸናፊው እና የሆሎኮስት (የአይሁዳውያን ጭፍጨፋ) ተራፊው ኤሊ ዊሰል ስለ ግፍ ዝምታ ሲናገር፡-
"ዝምታ ሁልጊዜም የሚጠቅመው አጥቂውን እንጂ ተጠቂውን አይደለም። ገለልተኝነት የሚረዳው ጨቋኙን እንጂ ተጨቋኙን አይደለም።" ብሎ ነበር።
ስለሆነም የነዚህን ንጹሐን መገደል፣ የ101 ዓመት ታሪካዊ ቅርስ መቃጠል፣ እና የ280 ሰዎች መፈናቀል እንደ ቀላል ዜና አልፈነው ልንሄድ አይገባም። ህመማቸውን ልንጋራ፣ ድምጻቸው ልንሆን ይገባል።
ታላቁ የነጻነት ታጋይ ኔልሰን ማንዴላ ደግሞ ስለ መጽናት እንዲህ ይላሉ፡-
"ትልቁ የህይወት ክብር ያለው ፈጽሞ ባለመውደቅ ውስጥ ሳይሆን፣ በወደቅን ቁጥር ተመልሶ በመነሳት ውስጥ ነው።"
ኦርቶዶክሳውያኑ ዛሬ ቤታቸው ፈርሶ፣ ዘመዶቻቸው ተገድለውባቸው ሜዳ ላይ ወድቀው ሊሆን ይችላል፤ ነገር ግን እምነታቸው እስካለ ድረስ፣ ነገ ከአመዱ ላይ ተመልሰው ይነሳሉ።
በአሰኮ ወረዳ ብቻ ከ280 በላይ የሚሆኑ ዜጎች ተፈናቅለዋል። መፈናቀል ማለት መጓዝ ብቻ አይደለም። መፈናቀል ማለት ትዝታን፣ ልፋትን፣ የልጅነት የቦረቁበትን አፈር፣ እና የዘመዶችን መቃብር ትቶ መሄድ ማለት ነው። እነዚህ ሰዎች አሁን ያሉት ሜዳ ላይ ነው። የለበሱት ልብስ ብቻ ነው ያላቸው። የሌሊቱ ብርድ ሲቆራርጣቸው፣ የጠዋቱ ጸሐይ ሲያቃጥላቸው፣ የልጆቻቸው ርሃብ አንጀታቸውን ሲበላው... ያላቸው ብቸኛ መጽናኛ በደረታቸው ያቀፉት እምነታቸው ብቻ ነው።
"ስለ አንተ ሁልጊዜም ተገድለናል እንደሚታረዱም በጎች ሆነናል" (መዝሙር 43:22)። የአርሲና ሶማሌ ክልል ጅግጅጋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሀዘን መግለጫቸውን የጀመሩት በዚህ የዳዊት መዝሙር ነበር። ይህ ቃል የዛሬን ብቻ ሳይሆን የዘመናትን የክርስቲያኖችን ህይወት የሚገልጽ ነው።
በእርግጥም እንደ በግ ለመታረድ የተሰለፉት እነዚህ ወገኖች ጥፋታቸው ምንድን ነው? ከማንም ጋር ያልተጣሉ፣ የፖለቲካ አጀንዳ የሌላቸው፣ ኑሯቸውን ለማሸነፍ መሬት የሚጭሩ ምስኪን ገበሬዎች ነበሩ። ነገር ግን በአክራሪነት የታወረው አእምሮ ይህንን ሊረዳ አይችልም።
እሳት ሁሉንም ነገር ያወድማል፤ መጽሐፍትን ያቃጥላል፣ ግድግዳን ያፈርሳል፣ ስጋን ያጠፋል። ነገር ግን እሳት እምነትን ሊያቃጥል አይችልም። የ101 ዓመቱ የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ዛሬ በአካላዊ ገጽታው ባይኖርም፣ ያ መቅደስ የሰራው መንፈሳዊ ህንጻ ግን አሁንም በምዕመናኑ ልብ ውስጥ ጸንቶ ይገኛል።
የ13ቱ ሰማዕታት ነፍስ በሰላም ታርፋለች፤ ደማቸው ግን ለትውልድ የሚተላለፍ የጽናት ትምህርት ሆኖ ይኖራል። የተሰደዱት ወገኖቻችን ዛሬ ሜዳ ላይ ቢሆኑም፣ የታሪክ ጌታ የሆነው አምላክ ነገን አዲስ አድርጎ ይሰራላቸዋል። የጥላቻ ኃይሎች በክፋታቸው መቅደሱን አፍርሰውታል፤ ሆኖም እውነተኛዋ ቤተ ክርስቲያን የድንጋይ እና የእንጨት ክምር ሳትሆን፣ ያቺ በስደት መሃልም ጽላቷን አቅፋ የምትጓዘዋ የሰው ልጅ ልብ ናት።
እስከዚያው ግን እንደ አቡነ ኤልሳዕ ጸሎት፤ ፈጣሪ የሞቱትን ነፍስ በመንግሥተ ሰማያት ያሳርፍ፣ የተፈናቀሉትን፣ የተራቡትን እና የተራቆቱትን ደግሞ በምህረት እጁ ይጎብኝ፣ ያጽናናም። ከጭስ እና ከአመድ በስተጀርባ፣ ብርሃን አለና።
ይህ የተዋህዶ ወርልድ ትንታኔ የቁጥሮች ድምር አይደለም፤ የ13 የከበሩ የሰው ልጆች ሕይወት መነጠቅ፣ የ101 ዓመት ታሪክ መቃጠል፣ እና የ280 ዜጎች በባዶ እጅ መሰደድ ታሪክ እንጂ። ይህ፣ ሃይማኖት እና ማንነትን መሠረት አድርጎ የሚፈጸም አክራሪነት የሰውን ልጅ ምን ያህል ወደ አውሬነት እንደሚቀይረው የሚያሳይ የዘመናችን ህያው ማሳያ ነው።
የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያንን እናስበው። ለ101 ዓመታት ሙሉ፣ አባቶች እና እናቶች በደጃፉ ተንበርክከው ፈጣሪያቸውን ተማጽነዋል። በዚያ መቅደስ ውስጥ ስንቱ ተጠምቋል? ስንቱ ተክሊል አስሯል? ስንቱስ በጸሎት ተጽናንቷል? ከአንድ ምዕተ ዓመት በላይ የቆመው ይህ የጸጋ ቤት፣ የበርካታ ትውልዶች የእምነት ማህደር ነበር። ነገር ግን፣ ጥላቻ ታሪክን አያውቅም፤ ክፋት ቅድስናን አይረዳም። በአንድ ጀንበር፣ ያ ሁሉ ታሪክ፣ ያ ሁሉ የእንጨት ጠረንና የዕጣን መዓዛ፣ በጭካኔ እሳት ተበላ።
በሌላ በኩል ደግሞ የካራ ኩፍተና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ዕጣ ፈንታ ሌላ ልብ ሰባሪ ትዕይንት ነበር። ታጣቂዎች መቅደሱን ሲዘርፉ፣ አማኞች የራሳቸውን ሕይወት እና ንብረት ለማዳን አልተጣደፉም። ይልቁንም፣ መኖሪያ ቤታቸው እያዩት በእሳት ሲጋይ፣ የዕድሜ ልክ ጥሪታቸው፣ ከብቶቻቸውና ማሳቸው ሲዘረፍ፣ እነርሱ ግን ከሁሉ የሚያስበልጡትን የቤተ ክርስቲያኑን ጽላት (ታቦት) በደረታቸው አቅፈው በጨለማ ወደማያውቁት ስደት መጓዝን መረጡ።
ይህ ትዕይንት ወደ ኋላ መለስ ብለን የመጽሐፍ ቅዱስን ታሪክ እንድናስታውስ ያደርገናል። እስራኤላውያን ታቦተ ጽዮንን ተሸክመው በበረሃ እንደተጓዙት ሁሉ፣ የአርሲ ምእመናንም አምላካቸውን በደረታቸው አቅፈው መከራውን ተቀበሉ።
ሞት በቁጥር ሲገለጽ ስሜት አይሰጥም፤ ነገር ግን እያንዳንዱ ቁጥር ከጀርባው ቤተሰብ፣ ተስፋ እና ህልም አለው። በአጠቃላይ 13 ንጹሐን ኦርቶዶክሳውያን በግፍ ተገድለዋል።
የ80 ዓመቱን አቶ አማረ በላይነህን እንመልከት። እኚህ አረጋዊ በህይወት ዘመናቸው ስንት መንግስታትን አይተዋል? ስንት የሀገር መከራን አሳልፈዋል? በስተእርጅናቸው ዘመን ክፋት አላርፍ ብሎ አስጨናቂ ሞትን አመጣባቸው። የ70 ዓመት የዕድሜ ባለጸጋ የሆኑት አቶ ደምረው አበራ፣ አቶ ሐይሉ ንጉሴ እና አቶ ሰሙ አባይነህም እንዲሁ የዚህ ጭካኔ ሰለባ ሆነዋል። እነዚህ አባቶች ለሀገር ምርቃት እንጂ መርገም ያልነበሩ፣ በእምነታቸው ጸንተው የኖሩ የሰላም ሰዎች ነበሩ።
እንደነ እሸቴ ዳመና (42 ዓመት) እና አበባየሁ ዳኜ (42 ዓመት) ያሉ የጎልማሳነት ዘመናቸው ላይ የነበሩ አባወራዎች ሲገደሉ፣ ከጀርባቸው ስንት ቤተሰብ በትነው እንደሄዱ ማሰብ ያሳምማል። ገና ለሀገር እና ለወገን ይደርሳሉ የተባሉ ወጣቶችም የዚህ ጽዋ ቀማሾች ሆነዋል። ተሬ ደሴ (የ25 ዓመት ወጣት)፣ ገነነ ጥላሁን እና ሙርቴሳ ጥላሁን በሺርካ ወረዳ ሕልማቸው ተጨናግፎ፣ ደማቸው በመሬት ላይ ፈሷል።
አቶ ንጉሱ ማንደፍሮ፣ አቶ በቀለ ኃ/ሚካኤል፣ ከፈለኝ ልክየለው... እነዚህ ስሞች ዝም ብለው በወረቀት ላይ የሰፈሩ አይደሉም። እነዚህ አባቶች ያሏቸው፣ እናቶች ያሳደጓቸው፣ ልጆች የሚጠብቋቸው ነፍሶች ነበሩ። በሃይማኖታቸው ምክንያት ብቻ በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደሉ።
ይህ ዓይነቱ እምነትን መሠረት ያደረገ መከራ፣ በዓለማችን ታሪክ አዲስ አይደለም። የሰው ልጅ በፈጣሪው በማመኑ ብቻ የተከፈለው ዋጋ ብዙ ነው።
ወደ ሩቅ ጎረቤት ሀገር ግብጽ ስንሄድ የኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ለዘመናት በእምነታቸው ምክንያት ከፍተኛ ዋጋ ሲከፍሉ ኖረዋል። በተለይም እ.ኤ.አ. በ2015 በሊቢያ የባህር ዳርቻ አይ ኤስ በተባለው አሸባሪ ቡድን የታረዱት 21 የግብጽ ኮፕቲክ ክርስቲያኖችን ዓለም መቼም አይረሳም። ቢላዋ በአንገታቸው ላይ ሲያርፍ እንኳን የፈጣሪያቸውን ስም እየጠሩ በድፍረት ሰማዕትነትን ተቀብለዋል። የአርሲዎቹም ሰማዕታት ከዚሁ የጽናት መንገድ የወጡ አይደሉም። ኢትዮጵያውያንም በተመሳሳይ በሊቢያ እንዲሁ።
ወደ ምዕራብ አፍሪካ ስናቀና ደግሞ ናይጄሪያ እናገኛለን። በቦኮሃራም እና በአክራሪ የፉላኒ ታጣቂዎች አማካኝነት በሰሜን እና በመካከለኛው የሀገሪቱ ክፍል በሺዎች የሚቆጠሩ ክርስቲያኖች አብያተ ክርስቲያናቶቻቸው ተቃጥለውባቸው፣ መንደራቸው ወድሞ በግፍ ተጨፍጭፈዋል።
የአርሜንያ የዘር ማጥፋት ታሪክም ሌላው ትልቅ ትምህርት ነው። በ1915 በኦቶማን ኢምፓየር ዘመን፣ ከአንድ ሚሊዮን በላይ አርመናውያን በክርስትና እምነታቸው እና በማንነታቸው ምክንያት ብቻ በግፍ ተጨፍጭፈዋል፣ በበረሃም ተሰደው አልቀዋል። ነገር ግን ዛሬ አርሜንያውያን ከየትኛውም ጊዜ በላይ አብበው፣ እምነታቸውንም አጽንተው ይገኛሉ። ጥይት እና እሳት ስጋን ሊገድል ይችላል፣ እምነትን እና መንፈስን ግን መቼም ሊያጠፋ አይችልም።
ታዋቂው የጥንት ቤተ ክርስቲያን ጸሐፊ ቴርቱሊያን እንዳለው፡-
"የሰማዕታት ደም የቤተ ክርስቲያን ዘር ነው።"
በአርሲ ተራሮች ላይ የፈሰሰው የነ አቶ አማረ፣ የነ ወጣት ተሬ ደሴ ደም በከንቱ አይቀርም። የቤተ ክርስቲያን ታሪክ እንደሚያስተምረን፣ መከራ በበዛ ቁጥር፣ መቅደሶች በነደዱ ቁጥር፣ የእምነት ስር ይበልጥ ይጠልቃል እንጂ አይደርቅም።
በእንደዚህ ዓይነት ጥልቅ ሀዘን እና የሰብአዊነት ውድቀት ውስጥ ስናልፍ፣ የሰው ልጅ ታሪክ ካፈራቸው ታላላቅ መሪዎች እና ፈላስፎች የምንማረው ብዙ ነገር አለ። ጭካኔን በጭካኔ መመለስ የትም አያደርስም።
የሰብአዊ መብት ታጋዩ ማርቲን ሉተር ኪንግ ጁኒየር (የተናገረው ኃያል ቃል በዚህ ጊዜ ትዝ ይለናል፡-
"ጨለማ ጨለማን ሊያባርር አይችልም፤ ይህንን ማድረግ የሚችለው ብርሃን ብቻ ነው። ጥላቻ ጥላቻን ሊያጠፋ አይችልም፤ ይህንን ማድረግ የሚችለው ፍቅር ብቻ ነው።"
በአርሲ የተፈጸመው ድርጊት የጨለማ እና የጥላቻ ፍሬ ነው። ነገር ግን የተፈናቀሉት ምዕመናን ጽላቱን አቅፈው መውጣታቸው፣ ብርሃንን እና ፍቅርን ምርጫቸው እንዳደረጉ ያሳያል።
የሰላም ኖቤል ሽልማት አሸናፊው እና የሆሎኮስት (የአይሁዳውያን ጭፍጨፋ) ተራፊው ኤሊ ዊሰል ስለ ግፍ ዝምታ ሲናገር፡-
"ዝምታ ሁልጊዜም የሚጠቅመው አጥቂውን እንጂ ተጠቂውን አይደለም። ገለልተኝነት የሚረዳው ጨቋኙን እንጂ ተጨቋኙን አይደለም።" ብሎ ነበር።
ስለሆነም የነዚህን ንጹሐን መገደል፣ የ101 ዓመት ታሪካዊ ቅርስ መቃጠል፣ እና የ280 ሰዎች መፈናቀል እንደ ቀላል ዜና አልፈነው ልንሄድ አይገባም። ህመማቸውን ልንጋራ፣ ድምጻቸው ልንሆን ይገባል።
ታላቁ የነጻነት ታጋይ ኔልሰን ማንዴላ ደግሞ ስለ መጽናት እንዲህ ይላሉ፡-
"ትልቁ የህይወት ክብር ያለው ፈጽሞ ባለመውደቅ ውስጥ ሳይሆን፣ በወደቅን ቁጥር ተመልሶ በመነሳት ውስጥ ነው።"
ኦርቶዶክሳውያኑ ዛሬ ቤታቸው ፈርሶ፣ ዘመዶቻቸው ተገድለውባቸው ሜዳ ላይ ወድቀው ሊሆን ይችላል፤ ነገር ግን እምነታቸው እስካለ ድረስ፣ ነገ ከአመዱ ላይ ተመልሰው ይነሳሉ።
በአሰኮ ወረዳ ብቻ ከ280 በላይ የሚሆኑ ዜጎች ተፈናቅለዋል። መፈናቀል ማለት መጓዝ ብቻ አይደለም። መፈናቀል ማለት ትዝታን፣ ልፋትን፣ የልጅነት የቦረቁበትን አፈር፣ እና የዘመዶችን መቃብር ትቶ መሄድ ማለት ነው። እነዚህ ሰዎች አሁን ያሉት ሜዳ ላይ ነው። የለበሱት ልብስ ብቻ ነው ያላቸው። የሌሊቱ ብርድ ሲቆራርጣቸው፣ የጠዋቱ ጸሐይ ሲያቃጥላቸው፣ የልጆቻቸው ርሃብ አንጀታቸውን ሲበላው... ያላቸው ብቸኛ መጽናኛ በደረታቸው ያቀፉት እምነታቸው ብቻ ነው።
"ስለ አንተ ሁልጊዜም ተገድለናል እንደሚታረዱም በጎች ሆነናል" (መዝሙር 43:22)። የአርሲና ሶማሌ ክልል ጅግጅጋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሀዘን መግለጫቸውን የጀመሩት በዚህ የዳዊት መዝሙር ነበር። ይህ ቃል የዛሬን ብቻ ሳይሆን የዘመናትን የክርስቲያኖችን ህይወት የሚገልጽ ነው።
በእርግጥም እንደ በግ ለመታረድ የተሰለፉት እነዚህ ወገኖች ጥፋታቸው ምንድን ነው? ከማንም ጋር ያልተጣሉ፣ የፖለቲካ አጀንዳ የሌላቸው፣ ኑሯቸውን ለማሸነፍ መሬት የሚጭሩ ምስኪን ገበሬዎች ነበሩ። ነገር ግን በአክራሪነት የታወረው አእምሮ ይህንን ሊረዳ አይችልም።
እሳት ሁሉንም ነገር ያወድማል፤ መጽሐፍትን ያቃጥላል፣ ግድግዳን ያፈርሳል፣ ስጋን ያጠፋል። ነገር ግን እሳት እምነትን ሊያቃጥል አይችልም። የ101 ዓመቱ የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ዛሬ በአካላዊ ገጽታው ባይኖርም፣ ያ መቅደስ የሰራው መንፈሳዊ ህንጻ ግን አሁንም በምዕመናኑ ልብ ውስጥ ጸንቶ ይገኛል።
የ13ቱ ሰማዕታት ነፍስ በሰላም ታርፋለች፤ ደማቸው ግን ለትውልድ የሚተላለፍ የጽናት ትምህርት ሆኖ ይኖራል። የተሰደዱት ወገኖቻችን ዛሬ ሜዳ ላይ ቢሆኑም፣ የታሪክ ጌታ የሆነው አምላክ ነገን አዲስ አድርጎ ይሰራላቸዋል። የጥላቻ ኃይሎች በክፋታቸው መቅደሱን አፍርሰውታል፤ ሆኖም እውነተኛዋ ቤተ ክርስቲያን የድንጋይ እና የእንጨት ክምር ሳትሆን፣ ያቺ በስደት መሃልም ጽላቷን አቅፋ የምትጓዘዋ የሰው ልጅ ልብ ናት።
እስከዚያው ግን እንደ አቡነ ኤልሳዕ ጸሎት፤ ፈጣሪ የሞቱትን ነፍስ በመንግሥተ ሰማያት ያሳርፍ፣ የተፈናቀሉትን፣ የተራቡትን እና የተራቆቱትን ደግሞ በምህረት እጁ ይጎብኝ፣ ያጽናናም። ከጭስ እና ከአመድ በስተጀርባ፣ ብርሃን አለና።
26 days ago
"ምስጉን ሰው" የተሰኘው መጽሐፍ በድምቀት ተመረቀ
#ethiopia | የአቶ ታምራት ተመስገንን የሕይወት እና የሥራ ታሪክ የሚተርከው "ምስጉን ሰው" የተሰኘው አዲስ መጽሐፍ ዛሬ ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም በዲ ሊዮፖል ሆቴል በተካሄደ ስነ-ስርዓት በይፋ ተመረቀ።
ሰም እና ወርቅ ሚዲያ እና ኢንተርቴይመንት ባዘጋጀው በዚህ የመጽሐፍ የምረቃ መርሃ-ግብር ላይ የክብር እንግዶች፣ አንጋፋ የሥነ-ጽሑፍ ሰዎች፣ የባለታሪኩ ወዳጆች እና ጥሪ የተደረገላቸው በርካታ እንግዶች ታድመዋል።
መጽሐፉ በጉራጌ ዞን በእንደጋኝ ወረዳ ተወልደው በሊስትሮነትና በሌሎች እጅግ አነስተኛ የጉልበት ሥራዎች ሕይወታቸውን የጀመሩትን የአቶ ታምራት ተመስገንን የትግል ጉዞ በሰፊው ይዳስሳል።
ባለታሪኩ ይህንን ፈታኝ የሕይወት ውጣ ውረድ በፅናት አልፈው ሀገሪቱ ካሏት ታላላቅ የግንባታ ኮንትራክተሮች አንዱ ለመሆን የቻሉ ሲሆን፣ ለበርካታ ዜጎችም የሥራ ዕድል በመፍጠር በሙያቸው እንዲበቁ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸው በምረቃው ላይ ተገልጿል።
አቶ ታምራት ከጠንካራ የሥራ ባህላቸው ባሻገር በማኅበረሰባዊ እና በበጎ አድራጎት ሥራዎቻቸውም በሰፊው እንደሚታወቁ በመጽሐፉ ተብራርቷል።
በችግር የተዘጉ ቤቶችን በመክፈት፣ አቅመ ደካሞችን በመደገፍ እንዲሁም ህሙማንን በማሳከም ኃላፊነታቸውን የተወጡ ምስጉን ሰው ናቸው። በተጨማሪም መንገዶችን፣ ቤተ እምነቶችን፣ የሕክምና ተቋማትን እና ትምህርት ቤቶችን በገንዘባቸውና በሙያቸው በመደገፍና በመገንባት ለአገልግሎት እንዲበቁ አድርገዋል።
ይህ የባለታሪኩን አርዓያነት ያለው ሕይወት አጉልቶ የሚያሳየው "ምስጉን ሰው" የተሰኘው መጽሐፍ፣ በሃያሲና የሥነ-ጽሑፍ መምህር ባዩልኝ አያሌው እንዲሁም በደራሲና ጋዜጠኛ ዘነበ ወላ ተጽፎ ለንባብ የበቃ ነው።
የሕይወት ታሪክ መጽሐፉ በአምስት ዋና ዋና ክፍሎች እና በአርባ ሁለት ምዕራፎች የተዋቀረ ሲሆን፣ በአጠቃላይ በሶስት መቶ ሰማንያ ሁለት ገጾች ተቀነባብሮ ቀርቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia | የአቶ ታምራት ተመስገንን የሕይወት እና የሥራ ታሪክ የሚተርከው "ምስጉን ሰው" የተሰኘው አዲስ መጽሐፍ ዛሬ ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም በዲ ሊዮፖል ሆቴል በተካሄደ ስነ-ስርዓት በይፋ ተመረቀ።
ሰም እና ወርቅ ሚዲያ እና ኢንተርቴይመንት ባዘጋጀው በዚህ የመጽሐፍ የምረቃ መርሃ-ግብር ላይ የክብር እንግዶች፣ አንጋፋ የሥነ-ጽሑፍ ሰዎች፣ የባለታሪኩ ወዳጆች እና ጥሪ የተደረገላቸው በርካታ እንግዶች ታድመዋል።
መጽሐፉ በጉራጌ ዞን በእንደጋኝ ወረዳ ተወልደው በሊስትሮነትና በሌሎች እጅግ አነስተኛ የጉልበት ሥራዎች ሕይወታቸውን የጀመሩትን የአቶ ታምራት ተመስገንን የትግል ጉዞ በሰፊው ይዳስሳል።
ባለታሪኩ ይህንን ፈታኝ የሕይወት ውጣ ውረድ በፅናት አልፈው ሀገሪቱ ካሏት ታላላቅ የግንባታ ኮንትራክተሮች አንዱ ለመሆን የቻሉ ሲሆን፣ ለበርካታ ዜጎችም የሥራ ዕድል በመፍጠር በሙያቸው እንዲበቁ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸው በምረቃው ላይ ተገልጿል።
አቶ ታምራት ከጠንካራ የሥራ ባህላቸው ባሻገር በማኅበረሰባዊ እና በበጎ አድራጎት ሥራዎቻቸውም በሰፊው እንደሚታወቁ በመጽሐፉ ተብራርቷል።
በችግር የተዘጉ ቤቶችን በመክፈት፣ አቅመ ደካሞችን በመደገፍ እንዲሁም ህሙማንን በማሳከም ኃላፊነታቸውን የተወጡ ምስጉን ሰው ናቸው። በተጨማሪም መንገዶችን፣ ቤተ እምነቶችን፣ የሕክምና ተቋማትን እና ትምህርት ቤቶችን በገንዘባቸውና በሙያቸው በመደገፍና በመገንባት ለአገልግሎት እንዲበቁ አድርገዋል።
ይህ የባለታሪኩን አርዓያነት ያለው ሕይወት አጉልቶ የሚያሳየው "ምስጉን ሰው" የተሰኘው መጽሐፍ፣ በሃያሲና የሥነ-ጽሑፍ መምህር ባዩልኝ አያሌው እንዲሁም በደራሲና ጋዜጠኛ ዘነበ ወላ ተጽፎ ለንባብ የበቃ ነው።
የሕይወት ታሪክ መጽሐፉ በአምስት ዋና ዋና ክፍሎች እና በአርባ ሁለት ምዕራፎች የተዋቀረ ሲሆን፣ በአጠቃላይ በሶስት መቶ ሰማንያ ሁለት ገጾች ተቀነባብሮ ቀርቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
29 days ago
Sponsored by
Surafel
1 month ago
መጋቢ ዐቢይ ታደለ “መልክአ-ስብዕና” የተሰኘ መጽሐፋቸውን አስመረቁ።
የኤክሌሺያ ዓለምአቀፍ የወንጌል አማኞች ማኅበር ዋና ዳይሬክተር እና የኪያ ሾው መርሐግብር አዘጋጅ፣ የመጋቢ ዐቢይ ታደለ (ኪያ) “መልክአ-ስብዕና” መጽሐፍ፣ ግንቦት 08/2018 ዓ.ም በቤዛ ዓለምአቀፍ ቤተክርስቲያን ለምረቃ በቅቷል።
በምረቃው ሥነ ሥርዓትም የመጽሐፉ ደራሲ መጋቢ ዐቢይ ታደለ፣ የመጋቢ ዐቢይ ታደለ ባለቤት ወ/ሮ ማክዳ ጌታቸው፣ የቤተክርስቲያን መሪዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች እና የመጋቢ ወዳጆች ተገኝተዋል።
በወንድም የኔነህ መድረክ አጋፋሪነት ቅደም ተከተል የተሰጣቸው የመርሐግብሩ አካላት ጸሎት፣ “የእንኳን ደስ አለህ” መልእክት፣ ዝማሬ፣ የመጽሐፍ ዳሰሳ ያቀረቡ ሲሆን በመጋቢ ዐቢይ ታደለ አወያይነት “መሆን ለተጽዕኖ” የተሰኘ የፓናል ዲስከሽን ተካሂዶ፣ የመጋቢ ዐቢይ ታደለን አገልግሎት የሚያሳይ አጭር ዘጋቢ ፊልም ለተመልካቾች ቀርቧል።
በዛሬው ዕለት የተመረቀው፣ “መልክአ-ስብዕና” የተሰኘው መጽሐፍ፣ በኢትዮጵያ የአመራር እና የስብዕና ግንባታ ታሪክ ውስጥ የራሱን አስተዋጽኦ የሚያበረክት ሲሆን፣ መሪነትን በውስጣዊ ማንነት እና በታማኝነት መሠረት ላይ ለመገንባት የሚያስችሉ አሥራ አንድ መሠረታዊ፣ ምሥጢር አዘል ምዕራፎችን አካትቷል።
በምረቃው የመጽሐፍ ዳሰሳ መርሐግብር እንደተገለጸው መጽሐፉ ለዘመናችን መሪዎች እና አገልጋዮች፣ የመሪነት ስጦታ ላላቸው ወጣቶች እንዲሁም ለተተኪው ትውልድ፣ በቤተክርስቲያን እና ከቤተክርስቲያን ውጪ ላሉ ሁሉ፣ ትልቅ አስተዋጽኦ የሚያበረክት የጊዜው መልእክት ነው።
ለአሥራ አንድ ዓመታት በኪያ ሾው መርሐግብር በክርስቲያን ሚዲያ ላይ ተጽዕኖ የፈጠሩት እና ከዚህ ቀደም “አካላዊ አስተሳሰብ” የተሰኘ መጽሐፍ ወደ አንባቢ ያደረሱት መጋቢ ዐቢይ ታደለ፣ ከ“መልክአ-ስብዕና” የመጽሐፍ ምረቃ በኋላ በሰጡት መግለጫ በቀጣይ ሁለት መጽሐፍትን ወደ አንባቢ እንደሚያደርሱ ገልጸዋል።
የኤክሌሺያ ዓለምአቀፍ የወንጌል አማኞች ማኅበር ዋና ዳይሬክተር እና የኪያ ሾው መርሐግብር አዘጋጅ፣ የመጋቢ ዐቢይ ታደለ (ኪያ) “መልክአ-ስብዕና” መጽሐፍ፣ ግንቦት 08/2018 ዓ.ም በቤዛ ዓለምአቀፍ ቤተክርስቲያን ለምረቃ በቅቷል።
በምረቃው ሥነ ሥርዓትም የመጽሐፉ ደራሲ መጋቢ ዐቢይ ታደለ፣ የመጋቢ ዐቢይ ታደለ ባለቤት ወ/ሮ ማክዳ ጌታቸው፣ የቤተክርስቲያን መሪዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች እና የመጋቢ ወዳጆች ተገኝተዋል።
በወንድም የኔነህ መድረክ አጋፋሪነት ቅደም ተከተል የተሰጣቸው የመርሐግብሩ አካላት ጸሎት፣ “የእንኳን ደስ አለህ” መልእክት፣ ዝማሬ፣ የመጽሐፍ ዳሰሳ ያቀረቡ ሲሆን በመጋቢ ዐቢይ ታደለ አወያይነት “መሆን ለተጽዕኖ” የተሰኘ የፓናል ዲስከሽን ተካሂዶ፣ የመጋቢ ዐቢይ ታደለን አገልግሎት የሚያሳይ አጭር ዘጋቢ ፊልም ለተመልካቾች ቀርቧል።
በዛሬው ዕለት የተመረቀው፣ “መልክአ-ስብዕና” የተሰኘው መጽሐፍ፣ በኢትዮጵያ የአመራር እና የስብዕና ግንባታ ታሪክ ውስጥ የራሱን አስተዋጽኦ የሚያበረክት ሲሆን፣ መሪነትን በውስጣዊ ማንነት እና በታማኝነት መሠረት ላይ ለመገንባት የሚያስችሉ አሥራ አንድ መሠረታዊ፣ ምሥጢር አዘል ምዕራፎችን አካትቷል።
በምረቃው የመጽሐፍ ዳሰሳ መርሐግብር እንደተገለጸው መጽሐፉ ለዘመናችን መሪዎች እና አገልጋዮች፣ የመሪነት ስጦታ ላላቸው ወጣቶች እንዲሁም ለተተኪው ትውልድ፣ በቤተክርስቲያን እና ከቤተክርስቲያን ውጪ ላሉ ሁሉ፣ ትልቅ አስተዋጽኦ የሚያበረክት የጊዜው መልእክት ነው።
ለአሥራ አንድ ዓመታት በኪያ ሾው መርሐግብር በክርስቲያን ሚዲያ ላይ ተጽዕኖ የፈጠሩት እና ከዚህ ቀደም “አካላዊ አስተሳሰብ” የተሰኘ መጽሐፍ ወደ አንባቢ ያደረሱት መጋቢ ዐቢይ ታደለ፣ ከ“መልክአ-ስብዕና” የመጽሐፍ ምረቃ በኋላ በሰጡት መግለጫ በቀጣይ ሁለት መጽሐፍትን ወደ አንባቢ እንደሚያደርሱ ገልጸዋል።
1 month ago
“የአዶ ትዝታዎች” የተሰኘው አዲስ መጽሐፍ በፕሮፌሰር ታሪክ ወልደሚካኤል እና በአቶ ሙሉጌታ ወልደሚካኤል መጪው ቅዳሜ ግንቦት 15 ቀን 2018 ዓ.ም ይመረቃል።
መጽሐፉ፤ የአንድ ቤተሰብን ታሪክ ዋቢ በማድረግ ከጉራጌ ማህበረሰብ ምድር ተነስተው ወደ አዲስ አበባ የተደረጉ ታሪካዊና ትውልድ ተሻጋሪ የህይወት ጉዞዎችን በስፋት የሚዳስስ ነው። በተለይም ውድ አያት ኑሮን ለማሸነፍ የከፈሉትን ከፍተኛ ተጋድሎ፣ ያጋጠሟቸውን አስገራሚ ክስተቶች በሳቅና በትዝታ ታጅቦ በሚያስነብብ መልኩ እንደተከተበ ተገልጿል።
ከዚህም በተጨማሪ የክቡር አባታችን የአቶ ወልደሚካኤል አንዳግቤ እና የውድ እናታችን የወ/ሮ አስካለ ኃብተማርያም ከጉራጌ ዞን እስከ አዲስ አበባ የዘለቀውን አስደናቂ የህይወት ጉዞ፤ ህይወትን ለመለወጥና ቤተሰብን ለመገንባት ያደረጉትን ተጋድሎ፣ ያፈሩትን ሀብትና ያጋጠሟቸውን ውጣ ውረዶች በግልጽ የሚያሳይ መሆኑ ተጠቁሟል።
ይህ መጽሐፍ ፈጣሪ የሰጠንን ችሎታና ማስተዋል ለበጎ ነገር ማዋል እንደምንችል የምንማርበት፣ ከየትኛውም ከባድ ውድቀት መነሳት እንደሚቻል የሚያሳይና የትውልድ ቅብብሎሽን የሚያጸና የታሪክ መዝገብ መሆኑን የደረሰን መረጃ ያመለክታል።
የመጽሐፉ የምረቃ ሥነ-ስርዓት ቅዳሜ ግንቦት 15 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ ከሜክስኮ ወደ መካኒሳ በሚወስደው መንገድ፣ ከሳር ቤት አደባባይ አለፍ ብሎ በስተቀኝ በኩል በሚገኘው የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቲዎሎጂካል ሴሚናሪ (EGST) አዳራሽ በድምቀት እንደሚካሄድ ታውቋል።
በዚህ ታላቅና ታሪካዊ የምረቃ በዓል ላይ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ ወዳጅ ዘመዶችና የመጽሐፍ አፍቃሪያን ተገኝተው የደስታው ተካፋይ እንዲሆኑ አዘጋጆቹ በአክብሮት ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
መጽሐፉ፤ የአንድ ቤተሰብን ታሪክ ዋቢ በማድረግ ከጉራጌ ማህበረሰብ ምድር ተነስተው ወደ አዲስ አበባ የተደረጉ ታሪካዊና ትውልድ ተሻጋሪ የህይወት ጉዞዎችን በስፋት የሚዳስስ ነው። በተለይም ውድ አያት ኑሮን ለማሸነፍ የከፈሉትን ከፍተኛ ተጋድሎ፣ ያጋጠሟቸውን አስገራሚ ክስተቶች በሳቅና በትዝታ ታጅቦ በሚያስነብብ መልኩ እንደተከተበ ተገልጿል።
ከዚህም በተጨማሪ የክቡር አባታችን የአቶ ወልደሚካኤል አንዳግቤ እና የውድ እናታችን የወ/ሮ አስካለ ኃብተማርያም ከጉራጌ ዞን እስከ አዲስ አበባ የዘለቀውን አስደናቂ የህይወት ጉዞ፤ ህይወትን ለመለወጥና ቤተሰብን ለመገንባት ያደረጉትን ተጋድሎ፣ ያፈሩትን ሀብትና ያጋጠሟቸውን ውጣ ውረዶች በግልጽ የሚያሳይ መሆኑ ተጠቁሟል።
ይህ መጽሐፍ ፈጣሪ የሰጠንን ችሎታና ማስተዋል ለበጎ ነገር ማዋል እንደምንችል የምንማርበት፣ ከየትኛውም ከባድ ውድቀት መነሳት እንደሚቻል የሚያሳይና የትውልድ ቅብብሎሽን የሚያጸና የታሪክ መዝገብ መሆኑን የደረሰን መረጃ ያመለክታል።
የመጽሐፉ የምረቃ ሥነ-ስርዓት ቅዳሜ ግንቦት 15 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ ከሜክስኮ ወደ መካኒሳ በሚወስደው መንገድ፣ ከሳር ቤት አደባባይ አለፍ ብሎ በስተቀኝ በኩል በሚገኘው የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቲዎሎጂካል ሴሚናሪ (EGST) አዳራሽ በድምቀት እንደሚካሄድ ታውቋል።
በዚህ ታላቅና ታሪካዊ የምረቃ በዓል ላይ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ ወዳጅ ዘመዶችና የመጽሐፍ አፍቃሪያን ተገኝተው የደስታው ተካፋይ እንዲሆኑ አዘጋጆቹ በአክብሮት ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
1 month ago
የመጽሐፍ ምረቃ ጥሪ
የደራሲ ማቴዎስ ገና (ዶ/ር) አዲስ መጽሐፍ ለምረቃ በቅቷል።
መጽሐፉ ለዘላቂ የፖለቲካ መረጋጋት እና ለማኅበራዊ ህይወት መሻሻል ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ተገልጿል።
የመጽሐፉ ርዕስ
"በረከት እና 'ርገማን በአንድ ብዕር ሲፈተሹ!!
የምረቃው መርሃ-ግብር
ቅዳሜ ግንቦት 15 ቀን 2018 ዓ.ም.
ከጠዋቱ 2፡00 እስከ 6፡30
(በኢትዮጵያ አቆጣጠር)
በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር
ለዘላቂ የፖለቲካ መረጋጋት እና ለማህበራዊ ሕይወት መሻሻል!!
ሁላችሁም በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ እንድትታደሙ ጥሪ ቀርቧል።
ለምረቃው የቀረው 7 ቀናት ብቻ ነው!
#newbook #booklaunch #ethiopia #addisababa #የመጽሐፍምረቃ #ብሔራዊቴአትር #ማቴዎስጌታቸው #በረከትናርገማን
የደራሲ ማቴዎስ ገና (ዶ/ር) አዲስ መጽሐፍ ለምረቃ በቅቷል።
መጽሐፉ ለዘላቂ የፖለቲካ መረጋጋት እና ለማኅበራዊ ህይወት መሻሻል ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ተገልጿል።
የመጽሐፉ ርዕስ
"በረከት እና 'ርገማን በአንድ ብዕር ሲፈተሹ!!
የምረቃው መርሃ-ግብር
ቅዳሜ ግንቦት 15 ቀን 2018 ዓ.ም.
ከጠዋቱ 2፡00 እስከ 6፡30
(በኢትዮጵያ አቆጣጠር)
በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር
ለዘላቂ የፖለቲካ መረጋጋት እና ለማህበራዊ ሕይወት መሻሻል!!
ሁላችሁም በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ እንድትታደሙ ጥሪ ቀርቧል።
ለምረቃው የቀረው 7 ቀናት ብቻ ነው!
#newbook #booklaunch #ethiopia #addisababa #የመጽሐፍምረቃ #ብሔራዊቴአትር #ማቴዎስጌታቸው #በረከትናርገማን
1 month ago
የጋዜጠኛና ደራሲ ስመኝ ግዛው አዲስ መጽሐፍ በቅርቡ ለንባብ ይበቃል
#ethiopia | ለዛ ባላቸው ጽሁፎቿ የምትታወቀው ጋዜጠኛ፣ ገጣሚና ደራሲ ስመኝ ግዛው የእናቴ "ሮሚዮ" እና ሌሎች አጫጭር ታሪኮች የተሰኘ አዲስ መጽሐፏን ለገበያ ልታቀርብ መሆኑን ገልጻለች።
የእናቴ "ሮሚዮ" መጽሐፍ ተራ የሚመስሉ ነገር ግን ጥልቅ ትርጉም ያላቸውን የሕይወት ክስተቶች በረቂቅ አጻጻፍ የሚያስቃኙ 20 አጫጭር ታሪኮችን በውስጡ አካትቷል።
ታሪኮቹ በእውነተኛ የፍቅርና የትዳር ሕይወት ውጣ ውረዶች ላይ የሚያተኩሩ ሲሆን ስሜትን በሚነኩ ግጥሞችም የታጀቡ መሆናቸውን ደራሲዋ አስታውቃለች።
በ 220 ገጾች ተቀንብቦ የቀረበው ይህ ሥራ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና ኮሙኒኬሽን ረዳት ፕሮፌሰር መኩሪያ መካሻ ግምገማ የተደረገበት ሲሆን መጽሐፉ በሳል ይዘትና ልዩ አቀራረብ እንዳለው ምሁሩ ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።
የመጽሐፍ ምርቃቱ ከጥቂት ቀናት በኋላ እንደሚከናወንም ታውቋል።
#የእናቴሮሚዮ #ስመኝግዛው #አዲስመጽሐፍ #ስነጽሁፍ #ኢትዮጵያ #አጫጭርታሪኮች #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ለዛ ባላቸው ጽሁፎቿ የምትታወቀው ጋዜጠኛ፣ ገጣሚና ደራሲ ስመኝ ግዛው የእናቴ "ሮሚዮ" እና ሌሎች አጫጭር ታሪኮች የተሰኘ አዲስ መጽሐፏን ለገበያ ልታቀርብ መሆኑን ገልጻለች።
የእናቴ "ሮሚዮ" መጽሐፍ ተራ የሚመስሉ ነገር ግን ጥልቅ ትርጉም ያላቸውን የሕይወት ክስተቶች በረቂቅ አጻጻፍ የሚያስቃኙ 20 አጫጭር ታሪኮችን በውስጡ አካትቷል።
ታሪኮቹ በእውነተኛ የፍቅርና የትዳር ሕይወት ውጣ ውረዶች ላይ የሚያተኩሩ ሲሆን ስሜትን በሚነኩ ግጥሞችም የታጀቡ መሆናቸውን ደራሲዋ አስታውቃለች።
በ 220 ገጾች ተቀንብቦ የቀረበው ይህ ሥራ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነትና ኮሙኒኬሽን ረዳት ፕሮፌሰር መኩሪያ መካሻ ግምገማ የተደረገበት ሲሆን መጽሐፉ በሳል ይዘትና ልዩ አቀራረብ እንዳለው ምሁሩ ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።
የመጽሐፍ ምርቃቱ ከጥቂት ቀናት በኋላ እንደሚከናወንም ታውቋል።
#የእናቴሮሚዮ #ስመኝግዛው #አዲስመጽሐፍ #ስነጽሁፍ #ኢትዮጵያ #አጫጭርታሪኮች #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
1 month ago
የመጽሐፍ ምረቃ የክብር ጥሪ
"በረከትና 'ርግማን በአንድ ብዕር ሲፈተሹ . . .”
በሃይማኖት፣ በባህል፣ በፖለቲካ፣ በስነ-ልቦና፣ በማህበራዊ ሕይወት እና በሳይንስ እይታዎች መካከል ያለውን ጥልቅ ምስጢር የሚመረምር ድንቅ ስራ!
ደራሲ ማቴዎስ ጌና (ዶክተር) በብዙ ጥረት ያዘጋጁትንና በአይነቱ ልዩ የሆነውን "ነገረ ርግማን ወበረከት" የተሰኘ መጽሐፍ የምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ ተገኝተው የደስታችን ተካፋይ እንዲሆኑ በአክብሮት ተጋብዘዋል።
የምረቃው መርሃ-ግብር፡-
• ቀን፦ ግንቦተት 15 ቀን 2018 ዓ.ም
• ሰዓት፦ ከጧቱ 2:30 - 6:00
• ቦታ፦ ብሔራዊ ቲያትር (ለገሃር አከባቢ/ብሔራዊ ባንክ አጠገብ)
"ጥበብንና እውቀትን በአንድነት እንቋደስ!"
የእርስዎ መገኘት ለጥበብ ጉዟችን ትልቅ ብርታት ነው!
እናመሰግናለን‼
"በረከትና 'ርግማን በአንድ ብዕር ሲፈተሹ . . .”
በሃይማኖት፣ በባህል፣ በፖለቲካ፣ በስነ-ልቦና፣ በማህበራዊ ሕይወት እና በሳይንስ እይታዎች መካከል ያለውን ጥልቅ ምስጢር የሚመረምር ድንቅ ስራ!
ደራሲ ማቴዎስ ጌና (ዶክተር) በብዙ ጥረት ያዘጋጁትንና በአይነቱ ልዩ የሆነውን "ነገረ ርግማን ወበረከት" የተሰኘ መጽሐፍ የምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ ተገኝተው የደስታችን ተካፋይ እንዲሆኑ በአክብሮት ተጋብዘዋል።
የምረቃው መርሃ-ግብር፡-
• ቀን፦ ግንቦተት 15 ቀን 2018 ዓ.ም
• ሰዓት፦ ከጧቱ 2:30 - 6:00
• ቦታ፦ ብሔራዊ ቲያትር (ለገሃር አከባቢ/ብሔራዊ ባንክ አጠገብ)
"ጥበብንና እውቀትን በአንድነት እንቋደስ!"
የእርስዎ መገኘት ለጥበብ ጉዟችን ትልቅ ብርታት ነው!
እናመሰግናለን‼
1 month ago
የአንጋፋው ፖለቲከኛ ሌንጮ ለታን የግማሽ ክፍለ ዘመን ጉዞ የሚዳስስ መጽሐፍ ሊመረቅ ነው።
#fastmereja I አንጋፋው ፖለቲከኛ አቶ ሌንጮ ለታ ላለፉት 50 ዓመታት በኦሮሞ ብሔራዊ የፖለቲካ ትግል ውስጥ የነበራቸውን ሚና እና ያበረከቱትን አስተዋጽኦ የሚያዘክር ልዩ የክብር መርሃ ግብር ግንቦት 2 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስካይ ላይት ሆቴል እንደሚካሄድ ተገለጸ።
በዕለቱ የፖለቲከኛው የሕይወት ታሪክ ላይ የሚያተኩርና በደራሲ ዙፋን ኡርጋ የተሰናዳ "የሌንጮ ለታ የሕይወት ታሪክ" መጽሐፍ በኦሮምኛና በአማርኛ ቋንቋዎች ተዘጋጅቶ ለንባብ እንደሚበቃ የመርሃ ግብሩ አስተባባሪ ኮሚቴ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል።
ይህ መርሃ ግብር በዋናነት ሦስት ዓላማዎችን ያሰነቀ ሲሆን፥ የመጀመሪያው የአቶ ሌንጮ ለታን የትግል ሕይወት ማክበርና ለኦሮሞ የፖለቲካ ትግል ዕድገት የነበራቸውን ፋና ወጊነት ዕውቅና መስጠት ነው።
ሁለተኛው ዓላማ የሌንጮ ለታን ፍልስፍናዊና ፖለቲካዊ ሐሳቦች፣ በተለይም በብሔርተኝነት፣ በሀገራዊ ግንባታ እና በአፍሪካ ቀንድ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ጥልቅ ትንታኔ የሚዳስስ ምሁራዊ መድረክ መፍጠር እንደሆነ ተገልጿል። በሦስተኛ ደረጃ መርሃ ግብሩ የፖለቲካ ትግሉን ሰብዓዊ ገጽታ ለማሳየት ያለመ ሲሆን፣ ይህም የአቶ ሌንጮን ቤተሰባዊ ሕይወትና ከትግሉ ጋር የነበረውን መስተጋብር የሚቃኝ ይሆናል።
በዝግጅቱ ላይ የፎቶ ኤግዚቢሽን፣ የፓናል ውይይት፣ የቤተሰብ አባላት ምስክርነት እና የመጽሐፍ ዳሰሳ የሚቀርብ ሲሆን፥ የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፣ አንጋፋ ታጋዮች፣ ምሁራንና የሀገር ሽማግሌዎች እንደሚታደሙ ይጠበቃል።
#fastmereja I አንጋፋው ፖለቲከኛ አቶ ሌንጮ ለታ ላለፉት 50 ዓመታት በኦሮሞ ብሔራዊ የፖለቲካ ትግል ውስጥ የነበራቸውን ሚና እና ያበረከቱትን አስተዋጽኦ የሚያዘክር ልዩ የክብር መርሃ ግብር ግንቦት 2 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስካይ ላይት ሆቴል እንደሚካሄድ ተገለጸ።
በዕለቱ የፖለቲከኛው የሕይወት ታሪክ ላይ የሚያተኩርና በደራሲ ዙፋን ኡርጋ የተሰናዳ "የሌንጮ ለታ የሕይወት ታሪክ" መጽሐፍ በኦሮምኛና በአማርኛ ቋንቋዎች ተዘጋጅቶ ለንባብ እንደሚበቃ የመርሃ ግብሩ አስተባባሪ ኮሚቴ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል።
ይህ መርሃ ግብር በዋናነት ሦስት ዓላማዎችን ያሰነቀ ሲሆን፥ የመጀመሪያው የአቶ ሌንጮ ለታን የትግል ሕይወት ማክበርና ለኦሮሞ የፖለቲካ ትግል ዕድገት የነበራቸውን ፋና ወጊነት ዕውቅና መስጠት ነው።
ሁለተኛው ዓላማ የሌንጮ ለታን ፍልስፍናዊና ፖለቲካዊ ሐሳቦች፣ በተለይም በብሔርተኝነት፣ በሀገራዊ ግንባታ እና በአፍሪካ ቀንድ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ጥልቅ ትንታኔ የሚዳስስ ምሁራዊ መድረክ መፍጠር እንደሆነ ተገልጿል። በሦስተኛ ደረጃ መርሃ ግብሩ የፖለቲካ ትግሉን ሰብዓዊ ገጽታ ለማሳየት ያለመ ሲሆን፣ ይህም የአቶ ሌንጮን ቤተሰባዊ ሕይወትና ከትግሉ ጋር የነበረውን መስተጋብር የሚቃኝ ይሆናል።
በዝግጅቱ ላይ የፎቶ ኤግዚቢሽን፣ የፓናል ውይይት፣ የቤተሰብ አባላት ምስክርነት እና የመጽሐፍ ዳሰሳ የሚቀርብ ሲሆን፥ የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፣ አንጋፋ ታጋዮች፣ ምሁራንና የሀገር ሽማግሌዎች እንደሚታደሙ ይጠበቃል።
Sponsored by
Surafel
2 months ago
አቡነ ሀብተ ማርያም🙏
በነገሥታት ፊት የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት መሰከረ።
በምጽዋትና በስገድት የምትጋደለው እናቱ ዮስቴና ሀብቷን ሁሉ ለድሆች ሰጥታ ለምናኔ ወደ በረኃ ሄደች። በዚያ ያገኘችው ባሕታዊም በመንፈስ ቅዱስ ተገልጦለት ከእርሷ ቅዱስ ፍሬ እንደሚወጣ ነግሮ ወደ ዓለም እንድትመለስ አዘዛት። እርሷም “እግዚአብሔር የወደደው ይሁን” ብላ እያመሰገነች ተመልሰች፡፡ የአባቱ የትውልድ ሀገር የራውዕይ በምትባል ሀገር ሲሆን ከዚህች የተባረከች ሴት ጋር ተጋባ። እርሷም በበጎ ምግባርና ሥራ የተጌጠች፣ በሕግ ተወስና በጾም፣ በጸሎት፣ የምትተጋ ነበረች። ከጥቂት ጊዜያት በኋላም ወንድ ልጅ ወለደች። እንደ ሥርዓቱም ሲጠመቅ የመጽሐፍ ስሙን “ሀብተ ማርያም” አሉት። በሕገ እግዚአብሔር አንጸው አሳደጉት። ወደ ቤተ ክርስቲያንም ሲወስዱት “እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ” የሚለውን ጸሎት ቢሰማ እጅጉን ወደዳት። እርሷንም ይዞ ከቤቱ ሌሊቱን የሚጸልይና የሚጋደል ሆነ።
አንድ ቀን የአባቱ በጎቹን ሲጠብቅ የበግ ጠባቂዎቹን “ዛሬ ዝናም ይዘንማልና እንግባ” አላቸው። እነርሱም “ምን ደመና አለ፤ ቀኑ ብራ ነው” አሉት። እርሱ ግን በጎቹን ይዞ ወደ ቤቱ እንደገባ ኃይለኛ፣ ነፋስና መብረቅ የቀላቀለ ዝናም ዘነመ። በሌላም ጊዜ እንዲሁ አንድ እረኛ የሀብተ ማርያምን በትሩን በጉልበት ነጠቀው። “መልስልኝ” ብሎ በስመ እግዚአብሔር ቢያምለውም እምቢ አለው። በተወው ጊዜ እግዚአብሔር ያን እረኛ በአየር ላይ ሠቅሎ አዋለው። እረኞቹም ሀብተ ማርያምን ሲለምኑት፣ እግዚአብሔር ነውና ስለ ስሙ ብሎ የቀጣው መሐሪው እርሱ ከወደደ ይማረው ሲል ያ እረኛ ተፈታና ወረደ። መጥቶም ከአባታችን እግር ስር ወደቀ፡፡ በኋላም ስሟ እለ አድባር ወደምትባል ገዳም ገብቶ ከአባ መልከ ጼዴቅ እጅ መነኰሶ ታላቅ ተጋድሎ ይጋደል ጀመር። በባሕር መካከልም በመቆም መዝሙረ ዳዊትን ይደግምና ግንባሩም የባሕሩን አሸዋ እስኪነካ 500 ጊዜ ይሰግዳል።
እህልም መቅመስን ትቶ የዱር ቅጠል የሚመገብ ሆነ። ዐርባ ዐርባ፣ ሰማንያ ሰማንያ ቀንም ያከፍላል። በሌሊትም ቁሞ በማደር በቀንም አራቱን ወንጌላት ዘወትር ይጸልያል። ተጋድሎውንም ያየ አምላካችን ተገለጠለት። አባ ሀብተ ማርያምም ከግርማው የተነሣ ደንግጦ በግንባሩ ተደፋ። ጌታችንም እፍ ብሉ አጽናንቶ አሥነሳውና ጽኑዕ ተጋድሎው በሰማያት መጻፉን ነገረው፡፡ ስለ ድንግልናው፣ ስለ ምናኔው፣ ስለ ፍጹም ምንኲስናው፣ አራቱን ወንጌላት አዘውትሮ በማንበቡ፣ ረኃብና ጥምን በመታገሡ፣ በልቡ ቂምንና በቀልን ባለማኖሩ፣ ስለ ንጹሕ የክህነት አገልግሎቱና በንጽሕና ስለሚያሣርገው መሥዋዕቱ ሰባት እጅግ የሚያስደንቁ አክሊላትንም አቀዳጀው። የቅዱስ ማቴዎስንና የቅዱስ ማርቆስን ወንጌል ሲያነብ ከሌሎች ሥውራን አበው ጋር የሚገናኝበትን የብርሃን ሠረገላ ሰጠው፡፡
የቅዱስ ሉቃስንና የቅዱስ ዮሐንስን ወንጌል ሲያነብም ሥጋውን ደሙን ለመቀበል ወደ ኢየሩሳሌም የሚሄድበትን የእሳት ሠረገላ ሰጠውና ቃል ኪዳን ገባለት። መታሰቢያውን ለሚያደርጉና በስሙ ለሚዘክሩ፣ ከእነርሱ ጋር የሚኖርበትን አምስት መቶ የወርቅ አምዶች ያሏትን ቦታ ሰጠሁህ አለው። ቅዱሳን መላእክት ሁሉ እየተደሰቱ አባታችን አቡነ ሐብተ ማርያምን “ወንድማችን ወደማያልቀው ሰማያዊ ደስታ ልንወስድህ መጥተናል” አሉት። ይህንንም በተናገረ ጊዜ ጌታችን በሦስትነቱ ተገልጦ ታየው። በኅዳር 26 ቀን ነፍሱ ከሥጋው በሰላም ተለየች። ቅዱሳን መላእክትም በታላቅ ደስታ እያመሰገኑ አሣረጓት። ገዳማውያን የዓለምን ክብር ንቀው ሔደዋልና ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፡፡ በዓታቸውን እናጽና ገዳማቸውን እንደግፍ የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
በነገሥታት ፊት የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት መሰከረ።
በምጽዋትና በስገድት የምትጋደለው እናቱ ዮስቴና ሀብቷን ሁሉ ለድሆች ሰጥታ ለምናኔ ወደ በረኃ ሄደች። በዚያ ያገኘችው ባሕታዊም በመንፈስ ቅዱስ ተገልጦለት ከእርሷ ቅዱስ ፍሬ እንደሚወጣ ነግሮ ወደ ዓለም እንድትመለስ አዘዛት። እርሷም “እግዚአብሔር የወደደው ይሁን” ብላ እያመሰገነች ተመልሰች፡፡ የአባቱ የትውልድ ሀገር የራውዕይ በምትባል ሀገር ሲሆን ከዚህች የተባረከች ሴት ጋር ተጋባ። እርሷም በበጎ ምግባርና ሥራ የተጌጠች፣ በሕግ ተወስና በጾም፣ በጸሎት፣ የምትተጋ ነበረች። ከጥቂት ጊዜያት በኋላም ወንድ ልጅ ወለደች። እንደ ሥርዓቱም ሲጠመቅ የመጽሐፍ ስሙን “ሀብተ ማርያም” አሉት። በሕገ እግዚአብሔር አንጸው አሳደጉት። ወደ ቤተ ክርስቲያንም ሲወስዱት “እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ” የሚለውን ጸሎት ቢሰማ እጅጉን ወደዳት። እርሷንም ይዞ ከቤቱ ሌሊቱን የሚጸልይና የሚጋደል ሆነ።
አንድ ቀን የአባቱ በጎቹን ሲጠብቅ የበግ ጠባቂዎቹን “ዛሬ ዝናም ይዘንማልና እንግባ” አላቸው። እነርሱም “ምን ደመና አለ፤ ቀኑ ብራ ነው” አሉት። እርሱ ግን በጎቹን ይዞ ወደ ቤቱ እንደገባ ኃይለኛ፣ ነፋስና መብረቅ የቀላቀለ ዝናም ዘነመ። በሌላም ጊዜ እንዲሁ አንድ እረኛ የሀብተ ማርያምን በትሩን በጉልበት ነጠቀው። “መልስልኝ” ብሎ በስመ እግዚአብሔር ቢያምለውም እምቢ አለው። በተወው ጊዜ እግዚአብሔር ያን እረኛ በአየር ላይ ሠቅሎ አዋለው። እረኞቹም ሀብተ ማርያምን ሲለምኑት፣ እግዚአብሔር ነውና ስለ ስሙ ብሎ የቀጣው መሐሪው እርሱ ከወደደ ይማረው ሲል ያ እረኛ ተፈታና ወረደ። መጥቶም ከአባታችን እግር ስር ወደቀ፡፡ በኋላም ስሟ እለ አድባር ወደምትባል ገዳም ገብቶ ከአባ መልከ ጼዴቅ እጅ መነኰሶ ታላቅ ተጋድሎ ይጋደል ጀመር። በባሕር መካከልም በመቆም መዝሙረ ዳዊትን ይደግምና ግንባሩም የባሕሩን አሸዋ እስኪነካ 500 ጊዜ ይሰግዳል።
እህልም መቅመስን ትቶ የዱር ቅጠል የሚመገብ ሆነ። ዐርባ ዐርባ፣ ሰማንያ ሰማንያ ቀንም ያከፍላል። በሌሊትም ቁሞ በማደር በቀንም አራቱን ወንጌላት ዘወትር ይጸልያል። ተጋድሎውንም ያየ አምላካችን ተገለጠለት። አባ ሀብተ ማርያምም ከግርማው የተነሣ ደንግጦ በግንባሩ ተደፋ። ጌታችንም እፍ ብሉ አጽናንቶ አሥነሳውና ጽኑዕ ተጋድሎው በሰማያት መጻፉን ነገረው፡፡ ስለ ድንግልናው፣ ስለ ምናኔው፣ ስለ ፍጹም ምንኲስናው፣ አራቱን ወንጌላት አዘውትሮ በማንበቡ፣ ረኃብና ጥምን በመታገሡ፣ በልቡ ቂምንና በቀልን ባለማኖሩ፣ ስለ ንጹሕ የክህነት አገልግሎቱና በንጽሕና ስለሚያሣርገው መሥዋዕቱ ሰባት እጅግ የሚያስደንቁ አክሊላትንም አቀዳጀው። የቅዱስ ማቴዎስንና የቅዱስ ማርቆስን ወንጌል ሲያነብ ከሌሎች ሥውራን አበው ጋር የሚገናኝበትን የብርሃን ሠረገላ ሰጠው፡፡
የቅዱስ ሉቃስንና የቅዱስ ዮሐንስን ወንጌል ሲያነብም ሥጋውን ደሙን ለመቀበል ወደ ኢየሩሳሌም የሚሄድበትን የእሳት ሠረገላ ሰጠውና ቃል ኪዳን ገባለት። መታሰቢያውን ለሚያደርጉና በስሙ ለሚዘክሩ፣ ከእነርሱ ጋር የሚኖርበትን አምስት መቶ የወርቅ አምዶች ያሏትን ቦታ ሰጠሁህ አለው። ቅዱሳን መላእክት ሁሉ እየተደሰቱ አባታችን አቡነ ሐብተ ማርያምን “ወንድማችን ወደማያልቀው ሰማያዊ ደስታ ልንወስድህ መጥተናል” አሉት። ይህንንም በተናገረ ጊዜ ጌታችን በሦስትነቱ ተገልጦ ታየው። በኅዳር 26 ቀን ነፍሱ ከሥጋው በሰላም ተለየች። ቅዱሳን መላእክትም በታላቅ ደስታ እያመሰገኑ አሣረጓት። ገዳማውያን የዓለምን ክብር ንቀው ሔደዋልና ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፡፡ በዓታቸውን እናጽና ገዳማቸውን እንደግፍ የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
2 months ago
ክንዶቹና እግሮቹም እንደ ጋለ ናስ፣ ድምጹም እንደ ብዙ ሕዝብ ድምፅ 🙏
ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ገብርኤል ለነቢዩ ዳንኤል ማስተዋልንና ጥበብን የሰጠ፣ እግዚአብሔር አምላክ የሰው ልጆችን ከሰይጣንና ከሞት ባርነት ነጻ ሊያወጣቸው ሰው እንደሚሆን ሰማይንና ምድርን አሳልፎ በቅዱሳን ላይ ነግሦ እንደሚኖር በምሳሌ ገልጾ ያስተማረው መልአክ ነው፡፡ ነቢዩም የቅዱስ ገብርኤልን አስፈሪ ግርማ ሲገልጽ “ዐይኖቼንም አነሣሁ “እነሆም በፍታ የለበሰውን ጥሩም የአፌዝን ወርቅ በወገቡ ላይ የታጠቀውን ሰው አየሁ፡፡ አካሉም እንደ ቢረሌ ይመስል ነበር፤ ፊቱም እንደ መብረቅ አምሳያ ነበረ፤ ዐይኖቹም እንደሚንበለበል ፋና፣ ክንዶቹና እግሮቹም እንደ ጋለ ናስ፣ የቃሉም ድምፅ እንደ ብዙ ሕዝብ ድምፅ ነበረ፡፡ ይህንም ታላቅ ራእይ አየሁ፤ ኀይልም አልቀረልኝም፤ ክብሬም ወደ ውርደት ተለወጠብኝ ኀይልም አጣሁ፡፡ የቃሉንም ድምፅ ሰማሁ፤ የቃሉን ድምፅ በሰማሁ ጊዜ ደንግጬ በምደር ላይ በግምባሬ ተደፋሁ” አለ፡፡
ቅዱስ ገብርኤል የስሙ ትርጓሜ ሰውና አምላክ ማለት ሲሆን ከዋነኞቹ የመላዕክት አለቆች አንዱ ሲሆን አርባብ፣ አጋእዝት ወይም ጌቶች የተባሉትን ነገድ የሚመራ ነው፡፡ ከበታቹም የሚመራቸው ዐሥር ነገደ መላእክት አሉ፡፡ ቅዱሳን መላእክት በቅዱስ ሚካኤል ፊት አውራሪነት የሰው ልጆች ጠላት ዲያብሎስን ተዋግተው ድል ከመንሳታቸው አስቀድሞ እግዚአብሔር መላዕክት ፈጥሮ ተሰወረባቸው፡፡ ይህን ጊዜ ማን ፈጠረን ብለው ግራ ሲጋቡ የመላዕክት አለቃ አድርጎ የፈጠረው ሳጥናኤል እኔ ፈጠርኳችሁ አላቸው፡፡ አንዳንዶች አመኑት፣ አንዳንዶችም ግራ ተጋብተው መወሰን አልቻሉም፡፡ ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ገብርኤል ግን ሳጥናኤልን “አንተ ፈጣሪ ከሆንክ ደግመህ ፈጥረህ አሳየን አለው፡፡ ሳጥናኤልም ቢሞክር አቃተው፡፡ ይህን ጊዜ ቅዱስ ገብርኤል ሳጥናኤልን በመቃወም “አይዞአችሁ ፈጣሪያችን ፈጥሮ አይጥለንምና እስክናውቀው ድረስ በያለንበት እንቁም፡፡” በማለት መላእክትን አረጋጋቸው፡፡
በራእይ 18÷1 “ከዚህ በኋላ ታላቅ ሥልጣን ያለው ሌላ መልአክ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ፤ ከክብሩም የተነሣ ምድር በራች፡፡” ተብሎ እንደተጻፈ ቅዱስ ገብርኤል ብርሃናዊ መልአክ ነው፡፡ ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊትም በመዝሙር 103÷4 “መላእክቱን የእሳት ነበልባል የሚያደርግ” እንዳለው ቅዱስ ገብርኤል ነበልባላዊ መልአክ ነው፡፡ ነቢዩ ሔኖክም 10÷14 “በሠራዊት ሁሉ ላይ የተሾመ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ነው” ይላል፡፡ በተለያዩ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎችም የቅዱስ ገብርኤልን ቁጣ የምንሰማና የምናይ ሲሆን ለምሳሌ ካህኑ ዘካርያስ የመልአኩን ብስራት ባለመቀበሉ ዲዳ ሁኗል፡፡ ዛሬም ይህን አማላጅነቱንና ፈጣን ተራዳኢነቱን ያመኑ ገዳማውያ አባቶች በጸሎታቸው ይጠሩታል እርሱም ፈጥኖ ይራዳቸዋል፡፡ እኛም ገዳማውያንን ስንደግፍ፣ በዓታቸውን ስናጸና፣ የበረከታቸው ተሳታፊ እንሆናለን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957
ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ገብርኤል ለነቢዩ ዳንኤል ማስተዋልንና ጥበብን የሰጠ፣ እግዚአብሔር አምላክ የሰው ልጆችን ከሰይጣንና ከሞት ባርነት ነጻ ሊያወጣቸው ሰው እንደሚሆን ሰማይንና ምድርን አሳልፎ በቅዱሳን ላይ ነግሦ እንደሚኖር በምሳሌ ገልጾ ያስተማረው መልአክ ነው፡፡ ነቢዩም የቅዱስ ገብርኤልን አስፈሪ ግርማ ሲገልጽ “ዐይኖቼንም አነሣሁ “እነሆም በፍታ የለበሰውን ጥሩም የአፌዝን ወርቅ በወገቡ ላይ የታጠቀውን ሰው አየሁ፡፡ አካሉም እንደ ቢረሌ ይመስል ነበር፤ ፊቱም እንደ መብረቅ አምሳያ ነበረ፤ ዐይኖቹም እንደሚንበለበል ፋና፣ ክንዶቹና እግሮቹም እንደ ጋለ ናስ፣ የቃሉም ድምፅ እንደ ብዙ ሕዝብ ድምፅ ነበረ፡፡ ይህንም ታላቅ ራእይ አየሁ፤ ኀይልም አልቀረልኝም፤ ክብሬም ወደ ውርደት ተለወጠብኝ ኀይልም አጣሁ፡፡ የቃሉንም ድምፅ ሰማሁ፤ የቃሉን ድምፅ በሰማሁ ጊዜ ደንግጬ በምደር ላይ በግምባሬ ተደፋሁ” አለ፡፡
ቅዱስ ገብርኤል የስሙ ትርጓሜ ሰውና አምላክ ማለት ሲሆን ከዋነኞቹ የመላዕክት አለቆች አንዱ ሲሆን አርባብ፣ አጋእዝት ወይም ጌቶች የተባሉትን ነገድ የሚመራ ነው፡፡ ከበታቹም የሚመራቸው ዐሥር ነገደ መላእክት አሉ፡፡ ቅዱሳን መላእክት በቅዱስ ሚካኤል ፊት አውራሪነት የሰው ልጆች ጠላት ዲያብሎስን ተዋግተው ድል ከመንሳታቸው አስቀድሞ እግዚአብሔር መላዕክት ፈጥሮ ተሰወረባቸው፡፡ ይህን ጊዜ ማን ፈጠረን ብለው ግራ ሲጋቡ የመላዕክት አለቃ አድርጎ የፈጠረው ሳጥናኤል እኔ ፈጠርኳችሁ አላቸው፡፡ አንዳንዶች አመኑት፣ አንዳንዶችም ግራ ተጋብተው መወሰን አልቻሉም፡፡ ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ገብርኤል ግን ሳጥናኤልን “አንተ ፈጣሪ ከሆንክ ደግመህ ፈጥረህ አሳየን አለው፡፡ ሳጥናኤልም ቢሞክር አቃተው፡፡ ይህን ጊዜ ቅዱስ ገብርኤል ሳጥናኤልን በመቃወም “አይዞአችሁ ፈጣሪያችን ፈጥሮ አይጥለንምና እስክናውቀው ድረስ በያለንበት እንቁም፡፡” በማለት መላእክትን አረጋጋቸው፡፡
በራእይ 18÷1 “ከዚህ በኋላ ታላቅ ሥልጣን ያለው ሌላ መልአክ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ፤ ከክብሩም የተነሣ ምድር በራች፡፡” ተብሎ እንደተጻፈ ቅዱስ ገብርኤል ብርሃናዊ መልአክ ነው፡፡ ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊትም በመዝሙር 103÷4 “መላእክቱን የእሳት ነበልባል የሚያደርግ” እንዳለው ቅዱስ ገብርኤል ነበልባላዊ መልአክ ነው፡፡ ነቢዩ ሔኖክም 10÷14 “በሠራዊት ሁሉ ላይ የተሾመ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ነው” ይላል፡፡ በተለያዩ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎችም የቅዱስ ገብርኤልን ቁጣ የምንሰማና የምናይ ሲሆን ለምሳሌ ካህኑ ዘካርያስ የመልአኩን ብስራት ባለመቀበሉ ዲዳ ሁኗል፡፡ ዛሬም ይህን አማላጅነቱንና ፈጣን ተራዳኢነቱን ያመኑ ገዳማውያ አባቶች በጸሎታቸው ይጠሩታል እርሱም ፈጥኖ ይራዳቸዋል፡፡ እኛም ገዳማውያንን ስንደግፍ፣ በዓታቸውን ስናጸና፣ የበረከታቸው ተሳታፊ እንሆናለን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957
2 months ago
ኮንታ : ኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት በዓል
#ethiopia | በዓሉ በኮንታ ዞን አመያ ደብረ ኤፍራታ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን እና በጪዳ መንበረ ፀሐይ ቅድስት ኪዳነምህረት ቤተክርስቲያን በድምቀት እየተከበረ ይገኛል፡፡
በዓሉ የኢየሱስ ክርስቶስን መከራና ስቅለት በማሰብ በጸሎት፣ በስግደት እንዲሁም የሕመማት ሳምንትን በሚዘክሩ ልዩ ልዩ መንፈሳዊ መርኃ ግብሮች ነው እየተከበረ የሚገኘው።
በዕለቱ ቀኑን የሚያወሱ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች የሚነበቡ ሲሆን፤ በዕለተ ስቅለት የተከናወኑ ተግባራት እየታሰበም የስግደት ስርዓት ይከናወናል።
የ#ኮንታ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት
#ethiopia | በዓሉ በኮንታ ዞን አመያ ደብረ ኤፍራታ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን እና በጪዳ መንበረ ፀሐይ ቅድስት ኪዳነምህረት ቤተክርስቲያን በድምቀት እየተከበረ ይገኛል፡፡
በዓሉ የኢየሱስ ክርስቶስን መከራና ስቅለት በማሰብ በጸሎት፣ በስግደት እንዲሁም የሕመማት ሳምንትን በሚዘክሩ ልዩ ልዩ መንፈሳዊ መርኃ ግብሮች ነው እየተከበረ የሚገኘው።
በዕለቱ ቀኑን የሚያወሱ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች የሚነበቡ ሲሆን፤ በዕለተ ስቅለት የተከናወኑ ተግባራት እየታሰበም የስግደት ስርዓት ይከናወናል።
የ#ኮንታ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት
2 months ago
ሰሙነ ሕማማት ማክሰኞ - የጥያቄና የትምህርት ቀን 🙏
ጌታችን አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱሱ ክርስቶስ በዕለተ ሰኞ ባደረገው አንጽሖተ ቤተመቅደስ ምክንያት፣ ሥልጣንን ለሰው ልጅ የሰጠው ጌታችን፣ ስለ ሥልጣኑ በጸሐፍት ፈሪሳውያን ተጠይቋልና ዕለተ ማክሰኞ የጥያቄ ቀን ይባላል፡፡ ጠያቂዎቹ የካህናት አለቆችና የሕዝብ አለቆች ናቸው፡፡ አንድም በዚህ ዕለት ጌታችን በቤተ መቅደስ ረጅም ትምህርት ስላስተማረ ዕለቱ “የትምህርት ቀን” ይባላል፡፡ ክርስቲያን የሆነ ሁሉ ከሥጋዊ ነገር ርቆ በዚህ ሰሞን የሃይማኖት ትምህርት ሲማር፣ ሲጠይቅ መሰንበት እንደሚገባው ይህ መጽሐፋዊ ሥርዓት ይነግረናል፡፡ በዕለተ ሰኞ የነጋዴዎችን ንብረት መገልበጥና ማባረሩን መነሻ በማድረግ “በማን ሥልጣን እነዚህን ታደርጋለህ?” ሲሉ ጠይቀውታል፡፡ ጌታችን ሲያደርጋቸው የነበሩት ተአምራት፣ ድንቅ ድንቅ ሥራዎችና ትምህርቱ ህዝቡ እንዲከተለው ስላደረገ የካህናት አለቆች በቅናት ከሮማ መንግሥት ባለ ሥልጣናት ጋር ሊያጋጩት የቀየሱት ስልት ነው፡፡
ነጋዴን ማባረርና መደብን ማስለቀቅ መንግሥታዊ ሥራ ነውና ጌታችን በራሴ ሥልጣን ነው ቢላቸው ጸረ መንግሥት ነው በማለት ለሮማ መንግሥት ያሳጡት ነበር፡፡ ጌታችን ግን ለጥያቄያቸው ቀጥተኛ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ “የዮሐንስ ጥምቀት ከየት ነው? ከሰማይ ነው ወይስ ከምድር?” በማለት በጥያቄ መልሶላቸዋል፡፡ እነርሱም “ከሰማይ ነው” ቢሉት “ለምን አላመናችሁበትም?” እንዳይላቸው ሰጉ፡፡ “ከሰው ነው” ቢሉት ደግሞ ሕዝቡ ዮሐንስን እንደ መምህር ይፈሩት፣ እንደ አባት ያከብሩት ነበርና እንዳይጣሏቸው ፈሩ፤ እናም “ከወዴት እንደሆነ አናውቅም” የሚል የተንኮል ምላሽ ሰጡት፡፡ እርሱም “እኔም በማን ሥልጣን እነዚህን እንደማደርግ አልነግራችሁም” አላቸው፡፡ በልቡናቸው የሚያደርጋቸውን ተግባራት ሁሉ በራሱ ሥልጣን እንደሚያደርግ ቢያውቁም በክፋትና በጥርጥሬ ስለተሞሉ ነበር የጠየቁት፡፡
በማቴዎስ ወንጌል 21÷28፣ 25÷46፣ በማርቆስ ወንጌል 12÷12፣ 13÷37፤ በሉቃስ ወንጌል 20÷9፣ 21÷38፣ የሚገኙ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ስለማክሰኞ ዕለት የሚነገሩ ትምህርቶችን ይዘዋል፡፡ ዳግመኛም በዚህ ዕለት በቤተ መቅደስ ረጅም ትምህርት ስላስተማረ የትምህርት ቀን ይባላል፡፡ ይኸውም ከሃይማኖት የራቁትን፣ ከፍቅረ እግዚአብሔር የተለዩትን አስተምሮ ማቅረብ፣ መክሮ መመለስ እንደሚገባን ሲገልጽልን ነው፡፡ ክርስቲያን የሆነ ሁሉ ከሥጋዊ ነገር ርቆ፣ ከዋዛ ፈዛዛ ተጠብቆ የጌታችንን ውለታ፣ ሕማሙን፣ ግረፋትና ስቅለቱን፣ ሞቱንና መከራውን እያሰበ በስግደት ይህን ሳምንት ሊያሳልፈው ይገባል፡፡ ገዳማውያን ይህን ፍቅሩን እያሰቡ በጾምና በጸሎት ይኖራሉ፤ ገዳማቸውን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957
ጌታችን አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱሱ ክርስቶስ በዕለተ ሰኞ ባደረገው አንጽሖተ ቤተመቅደስ ምክንያት፣ ሥልጣንን ለሰው ልጅ የሰጠው ጌታችን፣ ስለ ሥልጣኑ በጸሐፍት ፈሪሳውያን ተጠይቋልና ዕለተ ማክሰኞ የጥያቄ ቀን ይባላል፡፡ ጠያቂዎቹ የካህናት አለቆችና የሕዝብ አለቆች ናቸው፡፡ አንድም በዚህ ዕለት ጌታችን በቤተ መቅደስ ረጅም ትምህርት ስላስተማረ ዕለቱ “የትምህርት ቀን” ይባላል፡፡ ክርስቲያን የሆነ ሁሉ ከሥጋዊ ነገር ርቆ በዚህ ሰሞን የሃይማኖት ትምህርት ሲማር፣ ሲጠይቅ መሰንበት እንደሚገባው ይህ መጽሐፋዊ ሥርዓት ይነግረናል፡፡ በዕለተ ሰኞ የነጋዴዎችን ንብረት መገልበጥና ማባረሩን መነሻ በማድረግ “በማን ሥልጣን እነዚህን ታደርጋለህ?” ሲሉ ጠይቀውታል፡፡ ጌታችን ሲያደርጋቸው የነበሩት ተአምራት፣ ድንቅ ድንቅ ሥራዎችና ትምህርቱ ህዝቡ እንዲከተለው ስላደረገ የካህናት አለቆች በቅናት ከሮማ መንግሥት ባለ ሥልጣናት ጋር ሊያጋጩት የቀየሱት ስልት ነው፡፡
ነጋዴን ማባረርና መደብን ማስለቀቅ መንግሥታዊ ሥራ ነውና ጌታችን በራሴ ሥልጣን ነው ቢላቸው ጸረ መንግሥት ነው በማለት ለሮማ መንግሥት ያሳጡት ነበር፡፡ ጌታችን ግን ለጥያቄያቸው ቀጥተኛ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ “የዮሐንስ ጥምቀት ከየት ነው? ከሰማይ ነው ወይስ ከምድር?” በማለት በጥያቄ መልሶላቸዋል፡፡ እነርሱም “ከሰማይ ነው” ቢሉት “ለምን አላመናችሁበትም?” እንዳይላቸው ሰጉ፡፡ “ከሰው ነው” ቢሉት ደግሞ ሕዝቡ ዮሐንስን እንደ መምህር ይፈሩት፣ እንደ አባት ያከብሩት ነበርና እንዳይጣሏቸው ፈሩ፤ እናም “ከወዴት እንደሆነ አናውቅም” የሚል የተንኮል ምላሽ ሰጡት፡፡ እርሱም “እኔም በማን ሥልጣን እነዚህን እንደማደርግ አልነግራችሁም” አላቸው፡፡ በልቡናቸው የሚያደርጋቸውን ተግባራት ሁሉ በራሱ ሥልጣን እንደሚያደርግ ቢያውቁም በክፋትና በጥርጥሬ ስለተሞሉ ነበር የጠየቁት፡፡
በማቴዎስ ወንጌል 21÷28፣ 25÷46፣ በማርቆስ ወንጌል 12÷12፣ 13÷37፤ በሉቃስ ወንጌል 20÷9፣ 21÷38፣ የሚገኙ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ስለማክሰኞ ዕለት የሚነገሩ ትምህርቶችን ይዘዋል፡፡ ዳግመኛም በዚህ ዕለት በቤተ መቅደስ ረጅም ትምህርት ስላስተማረ የትምህርት ቀን ይባላል፡፡ ይኸውም ከሃይማኖት የራቁትን፣ ከፍቅረ እግዚአብሔር የተለዩትን አስተምሮ ማቅረብ፣ መክሮ መመለስ እንደሚገባን ሲገልጽልን ነው፡፡ ክርስቲያን የሆነ ሁሉ ከሥጋዊ ነገር ርቆ፣ ከዋዛ ፈዛዛ ተጠብቆ የጌታችንን ውለታ፣ ሕማሙን፣ ግረፋትና ስቅለቱን፣ ሞቱንና መከራውን እያሰበ በስግደት ይህን ሳምንት ሊያሳልፈው ይገባል፡፡ ገዳማውያን ይህን ፍቅሩን እያሰቡ በጾምና በጸሎት ይኖራሉ፤ ገዳማቸውን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957
Sponsored by
Surafel
3 months ago
#ዲያብሎስን_ቤት_አሳጣው
አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ
#ዲያብሎስን_ቤት_አሳጣው
የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ።
አዲሱን የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ መጽሐፍ ገበያ ላይ መዋል ምክንያት በማድረግ እነሆ ከመጽሐፉ ጀርባ ለቅምሻ ጋብዘናል።
#ዲያብሎስን_ቤት_አሳጣው
ዲያብሎስ በወንድማችን፣ በጓደኛችን፣ በሚስታችን ወይም በጣም በምንቀርበው ሰው ውስጥ አድሮ ተገቢ ያልሆነ ምክር ቢሰጠን፣ ምክሩን አንቀበል። ይልቁንም ያ ገዳይ ምክር የመጣው ከጠላት እንደሆነ አውቀን ከሰሚው እንራቅ። ዛሬም ቢሆን ሰይጣን የርኅራኄ ጭንብል ለብሶ፣ ወዳጅ መስሎ፣ ከመርዝ የከፋ ጥፋትን በሰዎች ውስጥ ያሰርጋል።
☦️☦️☦️
አንተ የንጉሥ ልጅ ብትሆንና በአባትህ ማዕድ የመቀመጥ ክብር ቢኖርህ፣ ያን ትተህ በወህኒ ቤት ካሉ እስረኞችና ከተፈረደባቸው ሰዎች ጋር በማዕዳቸው ለመካፈል ብትመርጥ፣ አባትህ ይህን ይፈቅድልሃልን? ይልቁንም በታላቅ ኃይል ከዚያ ያስወጣሃል እንጂ። ይህን የሚያደርገው ማዕዱ ስለሚጎዳህ ሳይሆን፣ ያንተን ክብርና የንጉሡን ማዕድ ስለሚያቃልል ነው።
☦️☦️☦️
በዓለም ምን ትሠራለህ? በተሰበረ ማሰሮ ውስጥ ውኃ ለማከማቸት ነውን? አሁን ላለችው ሕይወት በብላሽ ለመድከም ነውን? መቃጠሉ የማይቀርን ድር ለምን ታዳውራለህ? ለምንስ በምድረ በዳ ነፋሳትን ትከተላለህ? ለምንስ በሸለቆ ውስጥ ዓይንህን ጨፍነህ ትቅበዘበዛለህ? እያንዳንዱ ጥበብ ነገር አይደለምን? ይህ ለሁላችንም ግልጽ ነው። እንግዲህ አንተም በሕይወትህ ውስጥ ለምትሠራው ሥራ ዓላማ አሳየኝ። በእውነት አንዳች የለህም።
☦️☦️☦️
ሌቦች ጭቃ፣ ገለባ ወይም እንጨት ባለበት ቤት አይሰርቁም። ይልቁንም ወርቅና ብር ወዳለበት ቤት ዓይናቸውን ይጥላሉ። ሰይጣንም ልክ እንደዚሁ ነው፤ ልዩ ትኩረት የሚሰጠው ለመንፈሳዊ ነገር ቦታ በሚሰጡ ሰዎች ላይ ነው። በጎነት ባለበት ቦታ ወጥመድ ይበዛል፤ ምጽዋትና ዕርዳታ ባለበትም ምቀኝነት አይጠፋም። ነገር ግን ይሄንን ሁሉ የጠላት ተንኮል የምናሸንፍበት አንድ ትልቅ መሣሪያ አለን፤ ይሄ ድንቅ መሳሪያ ምን ይሆን?
#ዲያብሎስን_ቤት_አሳጣው መጽሐፍ መጽሐፍ በገበያ ላይ
በየመጽሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ይገኛሉ።
ሌሎች #የቅዱስ_ዮሐንስ እና #የአቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ አዳዲስ መንፈሳዊ መጽሐፍት በገበያ ላይ
👇🎀👇
👉#መንፈሳዊ_ተጋድሎ መጽሐፍ
👉#ለነፍስ_የሚበጅ_መንገድ መጽሐፍ
👉#የነፍስን_ነገር_ማሰብ መጽሐፍ
👉#ለደከመች_ነፍስ_መመሪያ መጽሐፍ
👉#መንፈሳዊ_ሰው_መሆን መጽሐፍ
👉#ኦርቶዶክሳዊ_ሕይወትን_መኖር መጽሐፍ
👉#ጠይቁ_ይመለስላችኋል መጽሐፍ
👉 #ሰይጣንን_አስርቡት መጽሐፍ
👉 #ሕይወት_እና_ክርስትና መጽሐፍ
👉 #የጽድቅ_መንገድ መጽሐፍ
👉 #የነፍስ_ምግብ መጽሐፍ
👉 #ለነፍስህ_ቤት_ስራላት መጽሐፍ
👉 #እስከማዕዜኑ መጽሐፍ
👉 #ትምህርተ_ሺኖዳ መጽሐፍ
👉 #አቡነሺኖዳ_መልስ_አላቸው መጽሐፍ
👉 #ኦርቶጵያ መጽሐፍ
👉#የተሰቀለው_ንጉሥ መጽሐፍ
👉#the_crucifixion_of_the_king_of_glory (በእንግሊዝኛ)
ሁሉም መጽሐፍት በየመጽሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ይገኛሉ።
📕📕📕
ፌስቡክ ገጽ
👉 https://web.facebook.com/p...
ቲክቶክ-
👉https://www.tiktok.com/@ha...
አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ
#ዲያብሎስን_ቤት_አሳጣው
የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ።
አዲሱን የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ መጽሐፍ ገበያ ላይ መዋል ምክንያት በማድረግ እነሆ ከመጽሐፉ ጀርባ ለቅምሻ ጋብዘናል።
#ዲያብሎስን_ቤት_አሳጣው
ዲያብሎስ በወንድማችን፣ በጓደኛችን፣ በሚስታችን ወይም በጣም በምንቀርበው ሰው ውስጥ አድሮ ተገቢ ያልሆነ ምክር ቢሰጠን፣ ምክሩን አንቀበል። ይልቁንም ያ ገዳይ ምክር የመጣው ከጠላት እንደሆነ አውቀን ከሰሚው እንራቅ። ዛሬም ቢሆን ሰይጣን የርኅራኄ ጭንብል ለብሶ፣ ወዳጅ መስሎ፣ ከመርዝ የከፋ ጥፋትን በሰዎች ውስጥ ያሰርጋል።
☦️☦️☦️
አንተ የንጉሥ ልጅ ብትሆንና በአባትህ ማዕድ የመቀመጥ ክብር ቢኖርህ፣ ያን ትተህ በወህኒ ቤት ካሉ እስረኞችና ከተፈረደባቸው ሰዎች ጋር በማዕዳቸው ለመካፈል ብትመርጥ፣ አባትህ ይህን ይፈቅድልሃልን? ይልቁንም በታላቅ ኃይል ከዚያ ያስወጣሃል እንጂ። ይህን የሚያደርገው ማዕዱ ስለሚጎዳህ ሳይሆን፣ ያንተን ክብርና የንጉሡን ማዕድ ስለሚያቃልል ነው።
☦️☦️☦️
በዓለም ምን ትሠራለህ? በተሰበረ ማሰሮ ውስጥ ውኃ ለማከማቸት ነውን? አሁን ላለችው ሕይወት በብላሽ ለመድከም ነውን? መቃጠሉ የማይቀርን ድር ለምን ታዳውራለህ? ለምንስ በምድረ በዳ ነፋሳትን ትከተላለህ? ለምንስ በሸለቆ ውስጥ ዓይንህን ጨፍነህ ትቅበዘበዛለህ? እያንዳንዱ ጥበብ ነገር አይደለምን? ይህ ለሁላችንም ግልጽ ነው። እንግዲህ አንተም በሕይወትህ ውስጥ ለምትሠራው ሥራ ዓላማ አሳየኝ። በእውነት አንዳች የለህም።
☦️☦️☦️
ሌቦች ጭቃ፣ ገለባ ወይም እንጨት ባለበት ቤት አይሰርቁም። ይልቁንም ወርቅና ብር ወዳለበት ቤት ዓይናቸውን ይጥላሉ። ሰይጣንም ልክ እንደዚሁ ነው፤ ልዩ ትኩረት የሚሰጠው ለመንፈሳዊ ነገር ቦታ በሚሰጡ ሰዎች ላይ ነው። በጎነት ባለበት ቦታ ወጥመድ ይበዛል፤ ምጽዋትና ዕርዳታ ባለበትም ምቀኝነት አይጠፋም። ነገር ግን ይሄንን ሁሉ የጠላት ተንኮል የምናሸንፍበት አንድ ትልቅ መሣሪያ አለን፤ ይሄ ድንቅ መሳሪያ ምን ይሆን?
#ዲያብሎስን_ቤት_አሳጣው መጽሐፍ መጽሐፍ በገበያ ላይ
በየመጽሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ይገኛሉ።
ሌሎች #የቅዱስ_ዮሐንስ እና #የአቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ አዳዲስ መንፈሳዊ መጽሐፍት በገበያ ላይ
👇🎀👇
👉#መንፈሳዊ_ተጋድሎ መጽሐፍ
👉#ለነፍስ_የሚበጅ_መንገድ መጽሐፍ
👉#የነፍስን_ነገር_ማሰብ መጽሐፍ
👉#ለደከመች_ነፍስ_መመሪያ መጽሐፍ
👉#መንፈሳዊ_ሰው_መሆን መጽሐፍ
👉#ኦርቶዶክሳዊ_ሕይወትን_መኖር መጽሐፍ
👉#ጠይቁ_ይመለስላችኋል መጽሐፍ
👉 #ሰይጣንን_አስርቡት መጽሐፍ
👉 #ሕይወት_እና_ክርስትና መጽሐፍ
👉 #የጽድቅ_መንገድ መጽሐፍ
👉 #የነፍስ_ምግብ መጽሐፍ
👉 #ለነፍስህ_ቤት_ስራላት መጽሐፍ
👉 #እስከማዕዜኑ መጽሐፍ
👉 #ትምህርተ_ሺኖዳ መጽሐፍ
👉 #አቡነሺኖዳ_መልስ_አላቸው መጽሐፍ
👉 #ኦርቶጵያ መጽሐፍ
👉#የተሰቀለው_ንጉሥ መጽሐፍ
👉#the_crucifixion_of_the_king_of_glory (በእንግሊዝኛ)
ሁሉም መጽሐፍት በየመጽሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ይገኛሉ።
📕📕📕
ፌስቡክ ገጽ
👉 https://web.facebook.com/p...
ቲክቶክ-
👉https://www.tiktok.com/@ha...
3 months ago
በወላይታ ሶዶ ቅዱስ መጽሐፍን ለንግድ መጠቅለያነት ሲጠቀም የተገኘ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ
በወላይታ ሶዶ ከተማ የመጽሐፍ ቅዱስ ገጾችን በመቅደድ ለብስኩት መጠቅለያነት ሲጠቀም የተገኘ ግለሰብ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለጠ። ድርጊቱ በከተማዋ ነዋሪዎች መካከል ግጭት ለመቀስቀስ የታለመ ቢሆንም፣ ማህበረሰቡ በሰላማዊ መንገድ ለፖሊስ ጥቆማ በመስጠት ያሳየው ጨዋነት ተመስግኗል።
ትላንት መጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ አራዳ ክፍለ ከተማ ልዩ ስሙ ህብረት ቀበሌ ውስጥ አቶ ሽኩር መሃመድ የተባለ በሻይ ቤት ንግድ ስራ የሚተዳደር ግለሰብ፣ የቅዱስ መጽሐፍ ገጾችን በመቅደድ ብስኩት ሲጠቀልልና ሲሸጥ መገኘቱን የከተማው ፖሊስ አስታውቋል። ፖሊስ ከህብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማ መሰረት ግለሰቡን ወዲያውኑ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያካሄደ ይገኛል።
የወላይታ ሶዶ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ባወጣው መግለጫ እንደጠቆመው ግለሰቡ ለዚሁ ድርጊት ፈጻሚነት ህጻን ልጅ ሲጠቀም እንደነበረ ተረጋግጧል። የንግድ ስፍራው በፖሊስ የታሸገ ሲሆን፣ በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ተጨማሪ ፍተሻዎች እየተካሄዱ ነው። ድርጊቱ በሃይማኖቶች መካከል ያለውን የመቻቻል እሴት ለመናድ የታቀደ የሁከት ሙከራ መሆኑ ተገልጿል።
ፖሊስ የከተማው ነዋሪዎች በጉዳዩ ሳይቆጡ በሰላማዊ መንገድ ለህግ የበላይነት በሰጡት ቅድሚያ ምስጋናውን ያቀረበ ሲሆን፣ የምርመራ ውጤቱ እስኪጠናቀቅ ድረስ ማህበረሰቡ በትዕግስት እንዲጠባበቅ አሳስቧል። ማንኛውንም ሁከት ሊፈጥሩ የሚችሉ አካላትን በመከላከል ረገድ ህዝቡ ከጸጥታ አካላት ጋር ያለውን ትብብር አጠናክሮ እንዲቀጥልም መልዕክት ተላልፏል።
የወላይታ ሶዶ ከተማ ፖሊስ መምሪያ
በወላይታ ሶዶ ከተማ የመጽሐፍ ቅዱስ ገጾችን በመቅደድ ለብስኩት መጠቅለያነት ሲጠቀም የተገኘ ግለሰብ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለጠ። ድርጊቱ በከተማዋ ነዋሪዎች መካከል ግጭት ለመቀስቀስ የታለመ ቢሆንም፣ ማህበረሰቡ በሰላማዊ መንገድ ለፖሊስ ጥቆማ በመስጠት ያሳየው ጨዋነት ተመስግኗል።
ትላንት መጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ አራዳ ክፍለ ከተማ ልዩ ስሙ ህብረት ቀበሌ ውስጥ አቶ ሽኩር መሃመድ የተባለ በሻይ ቤት ንግድ ስራ የሚተዳደር ግለሰብ፣ የቅዱስ መጽሐፍ ገጾችን በመቅደድ ብስኩት ሲጠቀልልና ሲሸጥ መገኘቱን የከተማው ፖሊስ አስታውቋል። ፖሊስ ከህብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማ መሰረት ግለሰቡን ወዲያውኑ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያካሄደ ይገኛል።
የወላይታ ሶዶ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ባወጣው መግለጫ እንደጠቆመው ግለሰቡ ለዚሁ ድርጊት ፈጻሚነት ህጻን ልጅ ሲጠቀም እንደነበረ ተረጋግጧል። የንግድ ስፍራው በፖሊስ የታሸገ ሲሆን፣ በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ተጨማሪ ፍተሻዎች እየተካሄዱ ነው። ድርጊቱ በሃይማኖቶች መካከል ያለውን የመቻቻል እሴት ለመናድ የታቀደ የሁከት ሙከራ መሆኑ ተገልጿል።
ፖሊስ የከተማው ነዋሪዎች በጉዳዩ ሳይቆጡ በሰላማዊ መንገድ ለህግ የበላይነት በሰጡት ቅድሚያ ምስጋናውን ያቀረበ ሲሆን፣ የምርመራ ውጤቱ እስኪጠናቀቅ ድረስ ማህበረሰቡ በትዕግስት እንዲጠባበቅ አሳስቧል። ማንኛውንም ሁከት ሊፈጥሩ የሚችሉ አካላትን በመከላከል ረገድ ህዝቡ ከጸጥታ አካላት ጋር ያለውን ትብብር አጠናክሮ እንዲቀጥልም መልዕክት ተላልፏል።
የወላይታ ሶዶ ከተማ ፖሊስ መምሪያ
3 months ago
በወላይታ ሶዶ ቅዱስ መጽሐፍን ለንግድ መጠቅለያነት ሲጠቀም የተገኘ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ
#fastmereja I በወላይታ ሶዶ ከተማ የመጽሐፍ ቅዱስ ገጾችን በመቅደድ ለብስኩት መጠቅለያነት ሲጠቀም የተገኘ ግለሰብ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለጠ። ድርጊቱ በከተማዋ ነዋሪዎች መካከል ግጭት ለመቀስቀስ የታለመ ቢሆንም፣ ማህበረሰቡ በሰላማዊ መንገድ ለፖሊስ ጥቆማ በመስጠት ያሳየው ጨዋነት ተመስግኗል።
ትላንት መጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ አራዳ ክፍለ ከተማ ልዩ ስሙ ህብረት ቀበሌ ውስጥ አቶ ሽኩር መሃመድ የተባለ በሻይ ቤት ንግድ ስራ የሚተዳደር ግለሰብ፣ የቅዱስ መጽሐፍ ገጾችን በመቅደድ ብስኩት ሲጠቀልልና ሲሸጥ መገኘቱን የከተማው ፖሊስ አስታውቋል። ፖሊስ ከህብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማ መሰረት ግለሰቡን ወዲያውኑ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያካሄደ ይገኛል።
የወላይታ ሶዶ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ባወጣው መግለጫ እንደጠቆመው ግለሰቡ ለዚሁ ድርጊት ፈጻሚነት ህጻን ልጅ ሲጠቀም እንደነበረ ተረጋግጧል። የንግድ ስፍራው በፖሊስ የታሸገ ሲሆን፣ በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ተጨማሪ ፍተሻዎች እየተካሄዱ ነው። ድርጊቱ በሃይማኖቶች መካከል ያለውን የመቻቻል እሴት ለመናድ የታቀደ የሁከት ሙከራ መሆኑ ተገልጿል።
ፖሊስ የከተማው ነዋሪዎች በጉዳዩ ሳይቆጡ በሰላማዊ መንገድ ለህግ የበላይነት በሰጡት ቅድሚያ ምስጋናውን ያቀረበ ሲሆን፣ የምርመራ ውጤቱ እስኪጠናቀቅ ድረስ ማህበረሰቡ በትዕግስት እንዲጠባበቅ አሳስቧል። ማንኛውንም ሁከት ሊፈጥሩ የሚችሉ አካላትን በመከላከል ረገድ ህዝቡ ከጸጥታ አካላት ጋር ያለውን ትብብር አጠናክሮ እንዲቀጥልም መልዕክት ተላልፏል።
መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም
ወላይታ ሶዶ፣ ኢትዮጵያ
#fastmereja I በወላይታ ሶዶ ከተማ የመጽሐፍ ቅዱስ ገጾችን በመቅደድ ለብስኩት መጠቅለያነት ሲጠቀም የተገኘ ግለሰብ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለጠ። ድርጊቱ በከተማዋ ነዋሪዎች መካከል ግጭት ለመቀስቀስ የታለመ ቢሆንም፣ ማህበረሰቡ በሰላማዊ መንገድ ለፖሊስ ጥቆማ በመስጠት ያሳየው ጨዋነት ተመስግኗል።
ትላንት መጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ.ም በወላይታ ሶዶ ከተማ አራዳ ክፍለ ከተማ ልዩ ስሙ ህብረት ቀበሌ ውስጥ አቶ ሽኩር መሃመድ የተባለ በሻይ ቤት ንግድ ስራ የሚተዳደር ግለሰብ፣ የቅዱስ መጽሐፍ ገጾችን በመቅደድ ብስኩት ሲጠቀልልና ሲሸጥ መገኘቱን የከተማው ፖሊስ አስታውቋል። ፖሊስ ከህብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማ መሰረት ግለሰቡን ወዲያውኑ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያካሄደ ይገኛል።
የወላይታ ሶዶ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ባወጣው መግለጫ እንደጠቆመው ግለሰቡ ለዚሁ ድርጊት ፈጻሚነት ህጻን ልጅ ሲጠቀም እንደነበረ ተረጋግጧል። የንግድ ስፍራው በፖሊስ የታሸገ ሲሆን፣ በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ተጨማሪ ፍተሻዎች እየተካሄዱ ነው። ድርጊቱ በሃይማኖቶች መካከል ያለውን የመቻቻል እሴት ለመናድ የታቀደ የሁከት ሙከራ መሆኑ ተገልጿል።
ፖሊስ የከተማው ነዋሪዎች በጉዳዩ ሳይቆጡ በሰላማዊ መንገድ ለህግ የበላይነት በሰጡት ቅድሚያ ምስጋናውን ያቀረበ ሲሆን፣ የምርመራ ውጤቱ እስኪጠናቀቅ ድረስ ማህበረሰቡ በትዕግስት እንዲጠባበቅ አሳስቧል። ማንኛውንም ሁከት ሊፈጥሩ የሚችሉ አካላትን በመከላከል ረገድ ህዝቡ ከጸጥታ አካላት ጋር ያለውን ትብብር አጠናክሮ እንዲቀጥልም መልዕክት ተላልፏል።
መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም
ወላይታ ሶዶ፣ ኢትዮጵያ
3 months ago
#ያበቃልህ_ሲመስልህ_እነዚህን_5ቱን_አስብ፦
1. አብርሃም የመቶ ዓመት ሽማግሌ ነበር
👉ግን የብዙ ሕዝብ አባት ሆነ።
2. ሳራ ማሕፀኗ ደርቆ ነበር
👉 ግን በስተርጅናዋ ይስሐቅን ወለደች
3. አላዛር ሞቶ አራት ቀን ሆኖት ነበር
👉 ግን በመቃብር ውስጥ ሕይወት አገኘ
4. ሐና ለብዙ ዓመታት መካን ነበረች
👉ግን ታላቁን ነቢይ ሳሙኤልን አቀፈች
5. ያ መጻጉዕ ለ38 ዓመታት በአልጋ ላይ ነበር
👉 ግን በቃሉ ተፈውሶ ተነሳ።
የአንተ "ዘግይቷል" የእግዚአብሔር "ትክክለኛው ሰዓት" ነው።
#መንፈሳዊ_ተጋድሎ መጽሐፍ
እና #ለነፍስ_የሚበጅ_መንገድ መጽሐፍ
ሁለት አዳዲስ የአቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ መጽሐፍት በገበያ ላይ
የአቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ፣ የቅዱስ ዮሐንስ አዲስ ምርጥ ምርጥ መንፈሳዊ መጽሐፍት በገበያ ላይ
👇🎀👇
👉#በቤት_ውስጥ_ያለች_ቤተክርስቲያን
👉#ኃጢአትን_ማሸነፍ
👉#ለደከመች_ነፍስ_መመሪያ
👉#መንፈሳዊ_ሰው_መሆን
👉#ኦርቶዶክሳዊ_ሕይወትን_መኖር
👉#ጠይቁ_ይመለስላችኋል
👉 #ሰይጣንን_አስርቡት
👉 #ሕይወት_እና_ክርስትና
👉 #የጽድቅ_መንገድ
👉 #የነፍስ_ምግብ
👉 #ለነፍስህ_ቤት_ስራላት
👉 #እስከማዕዜኑ
👉 #ትምህርተ_ሺኖዳ
👉 #አቡነሺኖዳ_መልስ_አላቸው
👉 #ኦርቶጵያ
👉#የተሰቀለው_ንጉሥ
👉#the_crucifixion_of_the_king_of_glory (በእንግሊዝኛ)
ሁሉም መጽሐፍት በየመጽሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ይገኛሉ።
📕📕📕
ፌስቡክ ገጽ
👉 https://web.facebook.com/p...
ቲክቶክ-
👉https://www.tiktok.com/@ha...
1. አብርሃም የመቶ ዓመት ሽማግሌ ነበር
👉ግን የብዙ ሕዝብ አባት ሆነ።
2. ሳራ ማሕፀኗ ደርቆ ነበር
👉 ግን በስተርጅናዋ ይስሐቅን ወለደች
3. አላዛር ሞቶ አራት ቀን ሆኖት ነበር
👉 ግን በመቃብር ውስጥ ሕይወት አገኘ
4. ሐና ለብዙ ዓመታት መካን ነበረች
👉ግን ታላቁን ነቢይ ሳሙኤልን አቀፈች
5. ያ መጻጉዕ ለ38 ዓመታት በአልጋ ላይ ነበር
👉 ግን በቃሉ ተፈውሶ ተነሳ።
የአንተ "ዘግይቷል" የእግዚአብሔር "ትክክለኛው ሰዓት" ነው።
#መንፈሳዊ_ተጋድሎ መጽሐፍ
እና #ለነፍስ_የሚበጅ_መንገድ መጽሐፍ
ሁለት አዳዲስ የአቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ መጽሐፍት በገበያ ላይ
የአቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ፣ የቅዱስ ዮሐንስ አዲስ ምርጥ ምርጥ መንፈሳዊ መጽሐፍት በገበያ ላይ
👇🎀👇
👉#በቤት_ውስጥ_ያለች_ቤተክርስቲያን
👉#ኃጢአትን_ማሸነፍ
👉#ለደከመች_ነፍስ_መመሪያ
👉#መንፈሳዊ_ሰው_መሆን
👉#ኦርቶዶክሳዊ_ሕይወትን_መኖር
👉#ጠይቁ_ይመለስላችኋል
👉 #ሰይጣንን_አስርቡት
👉 #ሕይወት_እና_ክርስትና
👉 #የጽድቅ_መንገድ
👉 #የነፍስ_ምግብ
👉 #ለነፍስህ_ቤት_ስራላት
👉 #እስከማዕዜኑ
👉 #ትምህርተ_ሺኖዳ
👉 #አቡነሺኖዳ_መልስ_አላቸው
👉 #ኦርቶጵያ
👉#የተሰቀለው_ንጉሥ
👉#the_crucifixion_of_the_king_of_glory (በእንግሊዝኛ)
ሁሉም መጽሐፍት በየመጽሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ይገኛሉ።
📕📕📕
ፌስቡክ ገጽ
👉 https://web.facebook.com/p...
ቲክቶክ-
👉https://www.tiktok.com/@ha...
3 months ago
የትንሳኤ በዓል አስመልክቶ የጸሎት መርሐ-ግብር ተዘጋጀ
📌 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ ጸሎት ይደረጋል
#ethiopia | የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት የተመሰረተበትን 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል እና የዘንድሮውን የትንሳኤ በዓል በማስመልከት፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አማኞች የሚሳተፉበት ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ በመጪው እሁድ ሚያዚያ 4 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስቴዲየም እንደሚያካሂድ በዛሬው ዕለት በይፋ አስታውቋል።
ይህ ታላቅ መድረክ ከሃይማኖታዊ ስነ-ሥርዓት ባለፈ፣ መጪው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላምና በታማኝነት እንዲጠናቀቅ "የአደባባይ ጸሎት" የሚደረግበት ልዩ ሀገራዊ መርሃ-ግብር እንደሆነም በሰፊው ተገልጿል።
ህብረቱ በ1968 ዓ.ም በአዳማ ከተማ የመጀመሪያውን ጉባኤ ካካሄደበት ጊዜ አንስቶ ያለፈባቸውን አምስት አስርት ዓመታት ለመዘከር ልዩ ዝግጅቶችን እያከናወነ የሚገኝ ሲሆን፣ የዕለቱ ዝግጅትም የዚህ ታሪካዊ ጉዞና የኢዮቤልዩ በዓል አንድ አካል ተደርጎ ተወስዷል።
የህብረቱ ፕሬዝዳንት ፓስተር ደረጀ ታፈሰ እንደገለጹት፣ ዋናው የኢዮቤልዩ በዓል በሐምሌ ወር የሚከበር ቢሆንም፣ በትንሳኤ በዓል ዕለት የሚከናወነው ጉባኤ የህብረቱን ምስረታ የሚዘክሩ የፎቶግራፍ ኤግዚቢሽኖች እና የታሪክ ምስክርነቶች የሚቀርቡበት ይሆናል።
ፓስተር ደረጀ ቤተክርስቲያን ለሀገር መረጋጋትና ለአንድነት ያላትን ኃላፊነት በይፋ እንደምትወጣ አረጋግጠው፣ በሃይማኖትና በብሔር ስም የሚነሱ የመለያየት አስተምህሮዎችን ህብረቱ በጽኑ እንደሚቃወም ገልጸዋል።
እውነተኛው የወንጌል አስተምህሮ ሰላምና ፍቅር እንጂ መቃቃር እንዳልሆነ በመጠቆም፣ በመጪው ምርጫ ዙሪያ አደባባይ ላይ የሚደረገው ጸሎት ለሀገር ትልቅ ሰላምን የሚያመጣ መሆኑን በንግግራቸው አጽንኦት ሰጥተውበታል።
በተጨማሪም ህብረቱ "ትንሳኤና ሕይወት እኔ ነኝ" የሚለውን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል መሪ በማድረግ፣ በዕለቱ የተቸገሩ ወገኖችን የመርዳትና የማዕድ ማጋራት መርሐ-ግብር አዘጋጅቷል። ይህ ማህበራዊ አገልግሎት ህብረቱ በየዓመቱ በታላላቅ በዓላት የሚያከናውነው ልማድ ሲሆን፣ ዘንድሮም በከፍተኛ ሁኔታ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተነግሯል።
ከማለዳው 12:00 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ስቴዲየም በሚካሄደው በዚህ ታላቅ መርሐ-ግብር ላይ፣ በአዲስ አበባና በዙሪያዋ የሚገኙ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አማኞች ተገኝተው የትንሳኤውን በዓል በጋራ እንዲያከብሩና ስለ ሀገር ሰላም እንዲጸልዩ ጥሪ ተላልፏል።
#ethiopia #easterinethiopia #evangelicalchurchesfellowship #nationalprayer #goldenjubilee #addisababastadium #peaceandunity #resurrectionpower
📌 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ ጸሎት ይደረጋል
#ethiopia | የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት የተመሰረተበትን 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል እና የዘንድሮውን የትንሳኤ በዓል በማስመልከት፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አማኞች የሚሳተፉበት ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ በመጪው እሁድ ሚያዚያ 4 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስቴዲየም እንደሚያካሂድ በዛሬው ዕለት በይፋ አስታውቋል።
ይህ ታላቅ መድረክ ከሃይማኖታዊ ስነ-ሥርዓት ባለፈ፣ መጪው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላምና በታማኝነት እንዲጠናቀቅ "የአደባባይ ጸሎት" የሚደረግበት ልዩ ሀገራዊ መርሃ-ግብር እንደሆነም በሰፊው ተገልጿል።
ህብረቱ በ1968 ዓ.ም በአዳማ ከተማ የመጀመሪያውን ጉባኤ ካካሄደበት ጊዜ አንስቶ ያለፈባቸውን አምስት አስርት ዓመታት ለመዘከር ልዩ ዝግጅቶችን እያከናወነ የሚገኝ ሲሆን፣ የዕለቱ ዝግጅትም የዚህ ታሪካዊ ጉዞና የኢዮቤልዩ በዓል አንድ አካል ተደርጎ ተወስዷል።
የህብረቱ ፕሬዝዳንት ፓስተር ደረጀ ታፈሰ እንደገለጹት፣ ዋናው የኢዮቤልዩ በዓል በሐምሌ ወር የሚከበር ቢሆንም፣ በትንሳኤ በዓል ዕለት የሚከናወነው ጉባኤ የህብረቱን ምስረታ የሚዘክሩ የፎቶግራፍ ኤግዚቢሽኖች እና የታሪክ ምስክርነቶች የሚቀርቡበት ይሆናል።
ፓስተር ደረጀ ቤተክርስቲያን ለሀገር መረጋጋትና ለአንድነት ያላትን ኃላፊነት በይፋ እንደምትወጣ አረጋግጠው፣ በሃይማኖትና በብሔር ስም የሚነሱ የመለያየት አስተምህሮዎችን ህብረቱ በጽኑ እንደሚቃወም ገልጸዋል።
እውነተኛው የወንጌል አስተምህሮ ሰላምና ፍቅር እንጂ መቃቃር እንዳልሆነ በመጠቆም፣ በመጪው ምርጫ ዙሪያ አደባባይ ላይ የሚደረገው ጸሎት ለሀገር ትልቅ ሰላምን የሚያመጣ መሆኑን በንግግራቸው አጽንኦት ሰጥተውበታል።
በተጨማሪም ህብረቱ "ትንሳኤና ሕይወት እኔ ነኝ" የሚለውን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል መሪ በማድረግ፣ በዕለቱ የተቸገሩ ወገኖችን የመርዳትና የማዕድ ማጋራት መርሐ-ግብር አዘጋጅቷል። ይህ ማህበራዊ አገልግሎት ህብረቱ በየዓመቱ በታላላቅ በዓላት የሚያከናውነው ልማድ ሲሆን፣ ዘንድሮም በከፍተኛ ሁኔታ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተነግሯል።
ከማለዳው 12:00 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ስቴዲየም በሚካሄደው በዚህ ታላቅ መርሐ-ግብር ላይ፣ በአዲስ አበባና በዙሪያዋ የሚገኙ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አማኞች ተገኝተው የትንሳኤውን በዓል በጋራ እንዲያከብሩና ስለ ሀገር ሰላም እንዲጸልዩ ጥሪ ተላልፏል።
#ethiopia #easterinethiopia #evangelicalchurchesfellowship #nationalprayer #goldenjubilee #addisababastadium #peaceandunity #resurrectionpower
3 months ago
ሚሊዮኖች የሚሳተፉበት የታላቁ የትንሳኤ በዓል እና የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሀገራዊ ጸሎት መርሐ-ግብር ተዘጋጀ!
#fastmereja I የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት የምስረታውን 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ እና የዘንድሮውን የትንሳኤ በዓል በማስመልከት፣ በመጪው እሁድ በአዲስ አበባ ስቴዲየም ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ እንደሚያካሂድ በዛሬዉ እለት አስታዉቋል።
ይህ በዓል ከሃይማኖታዊ ስነ-ሥርዓት ባለፈ፣ መጪው 7ተኛዉ ሀገራዊ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ ''የአደባባይ ጸሎት" የሚደረግበት መድረክ እንደሆነም ተገልጿል።
የግማሽ ክፍለ ዘመን ጉዞ እና የወርቅ ኢዮቤልዩ ህብረቱ በ1968 ዓ.ም በአዳማ ከተማ የመጀመሪያውን ጉባኤ ካካሄደበት ጊዜ አንስቶ ያለፈባቸውን አምስት አስርት ዓመታት ለመዘከር ልዩ ዝግጅቶችን እያከናወነ ይገኛል፡፡
የህብረቱ ፕሬዝዳንት ፓስተር ደረጀ ታፈሰ እንደገለፁት ዋናው የኢዮቤልዩ በዓል በሐምሌ ወር የሚከበር ቢሆንም፣ የፊታችን ሚያዚያ 4 ቀን 2018 ዓ.ም የሚከበረው የትንሳኤ በዓል የዚህ ታሪካዊ ጉዞ አካል መሆኑን ገልጸዋል።
በዕለቱ የህብረቱን ምስረታ የሚዘክሩ የፎቶግራፍ ኤግዚቢሽኖች እና የታሪክ ምስክርነቶች ለምዕመኑ እንደሚቀርቡ ታውቋል።
ፓስተር ደረጀ "መጪው ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ አደባባይ ላይ ወጥተን ጸሎት እናደርጋለን" ሲሉ የገለጹ ሲሆን፣ ቤተክርስቲያን ለሀገር መረጋጋትና ለአንድነት ያላትን ኃላፊነት በይፋ እንደምትወጣ አረጋግጠዋል።
ፕሬዝዳንቱ አክለውም፣ በሃይማኖትና በብሔር ስም የሚነሱ የጥልና የመለያየት አስተምህሮዎችን ህብረቱ በጽኑ እንደሚቃወም ገልጸው፤ "እውነተኛው የወንጌል አስተምህሮ ሰላምና ፍቅር እንጂ መቃቃር አይደለም'' ብለዋል፡፡
ህብረቱ "ትንሳኤና ሕይወት እኔ ነኝ" የሚለውን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል መሪ በማድረግ፣ በዕለቱ የተቸገሩ ወገኖችን የመርዳትና የማዕድ ማጋራት መርሐ-ግብር አዘጋጅቷል። ይህ ልማድ ህብረቱ በየዓመቱ በታላላቅ በዓላት የሚያከናውነው ማህበራዊ አገልግሎት መሆኑ ተጠቅሷል።
ሚያዚያ 4 ቀን ከማለዳው 12:00 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ስቴዲየም በሚካሄደው በዚህ ታላቅ መርሐ-ግብር ላይ፣ በአዲስ አበባና በዙሪያዋ የሚገኙ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አማኞች እንዲገኙ ጥሪ ተላልፏል።
#fastmereja I የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት የምስረታውን 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ እና የዘንድሮውን የትንሳኤ በዓል በማስመልከት፣ በመጪው እሁድ በአዲስ አበባ ስቴዲየም ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ እንደሚያካሂድ በዛሬዉ እለት አስታዉቋል።
ይህ በዓል ከሃይማኖታዊ ስነ-ሥርዓት ባለፈ፣ መጪው 7ተኛዉ ሀገራዊ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ ''የአደባባይ ጸሎት" የሚደረግበት መድረክ እንደሆነም ተገልጿል።
የግማሽ ክፍለ ዘመን ጉዞ እና የወርቅ ኢዮቤልዩ ህብረቱ በ1968 ዓ.ም በአዳማ ከተማ የመጀመሪያውን ጉባኤ ካካሄደበት ጊዜ አንስቶ ያለፈባቸውን አምስት አስርት ዓመታት ለመዘከር ልዩ ዝግጅቶችን እያከናወነ ይገኛል፡፡
የህብረቱ ፕሬዝዳንት ፓስተር ደረጀ ታፈሰ እንደገለፁት ዋናው የኢዮቤልዩ በዓል በሐምሌ ወር የሚከበር ቢሆንም፣ የፊታችን ሚያዚያ 4 ቀን 2018 ዓ.ም የሚከበረው የትንሳኤ በዓል የዚህ ታሪካዊ ጉዞ አካል መሆኑን ገልጸዋል።
በዕለቱ የህብረቱን ምስረታ የሚዘክሩ የፎቶግራፍ ኤግዚቢሽኖች እና የታሪክ ምስክርነቶች ለምዕመኑ እንደሚቀርቡ ታውቋል።
ፓስተር ደረጀ "መጪው ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ አደባባይ ላይ ወጥተን ጸሎት እናደርጋለን" ሲሉ የገለጹ ሲሆን፣ ቤተክርስቲያን ለሀገር መረጋጋትና ለአንድነት ያላትን ኃላፊነት በይፋ እንደምትወጣ አረጋግጠዋል።
ፕሬዝዳንቱ አክለውም፣ በሃይማኖትና በብሔር ስም የሚነሱ የጥልና የመለያየት አስተምህሮዎችን ህብረቱ በጽኑ እንደሚቃወም ገልጸው፤ "እውነተኛው የወንጌል አስተምህሮ ሰላምና ፍቅር እንጂ መቃቃር አይደለም'' ብለዋል፡፡
ህብረቱ "ትንሳኤና ሕይወት እኔ ነኝ" የሚለውን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል መሪ በማድረግ፣ በዕለቱ የተቸገሩ ወገኖችን የመርዳትና የማዕድ ማጋራት መርሐ-ግብር አዘጋጅቷል። ይህ ልማድ ህብረቱ በየዓመቱ በታላላቅ በዓላት የሚያከናውነው ማህበራዊ አገልግሎት መሆኑ ተጠቅሷል።
ሚያዚያ 4 ቀን ከማለዳው 12:00 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ስቴዲየም በሚካሄደው በዚህ ታላቅ መርሐ-ግብር ላይ፣ በአዲስ አበባና በዙሪያዋ የሚገኙ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አማኞች እንዲገኙ ጥሪ ተላልፏል።
3 months ago
ድምፃዊ አቤል ሙሉጌታ ከዘፈኑ ዓለም ራሱን አሰናበተ
#ethiopia | ታዋቂው ወጣት ድምፃዊ አቤል ሙሉጌታ ከዓለማዊ ሙዚቃ (ዘፈን) ሙሉ በሙሉ መውጣቱንና ወደ ቀድሞ መንፈሳዊ ህይወቱ መመለሱን በይፉ አስታወቀ።
አርቲስቱ ይህንን ውሳኔውን ያስታወቀው በይፋዊው የፌስቡክ ገጹ ሲሆን፣ የዘፈኑን ዓለም "ውስብስብና አጋንንታዊ አሰራር ያለበት" ሲል ገልጾታል።
አቤል ላለፉት ዓመታት በሙዚቃው ዓለም በቆየባቸው ጊዜያት ውስጥ ከፍተኛ ውስጣዊ ትግል ሲያደርግ እንደነበር ገልጿል። በተለይም ከ2005 እስከ 2007 ዓ.ም ድረስ ለሁለት ዓመታት ሙዚቃን አቁሞ እንደነበር አስታውሶ፣ በወቅቱ ወደ ዘፈኑ ዓለም ዳግም መመለሱ ጸጸት እንደፈጠረበት አልሸሸገም።
"ዓለም ውሸት ነው፤ ዝናም ከንቱ ቆሻሻ ነው! የውሸት መልክና የውሸት ፈገግታ ብቻ!" ሲል አቤል አሁን ያለውን አቋም በጽኑ ቃላት ገልጿል።
ድምፃዊው ለውሳኔው መነሻ የሆኑትን የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች (2ኛ ጴጥሮስ 2፥22 እና ዕብራውያን 10፥38) በመጥቀስ፣ ወደ ኋላ ማፈግፈግ አብቅቶለታል ብሏል።
ለዚህም ለውጡ የጸለዩለትን ሁሉ አመስግኗል።
አቤል ሙሉጌታ ከዚህ በኋላ ወደ ዘፈኑ ዓለም ዳግም እንደማይመለስና ህይወቱን ለእግዚአብሔር አሳልፎ መስጠቱን በማረጋገጥ መልዕክቱን አጠቃሏል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | ታዋቂው ወጣት ድምፃዊ አቤል ሙሉጌታ ከዓለማዊ ሙዚቃ (ዘፈን) ሙሉ በሙሉ መውጣቱንና ወደ ቀድሞ መንፈሳዊ ህይወቱ መመለሱን በይፉ አስታወቀ።
አርቲስቱ ይህንን ውሳኔውን ያስታወቀው በይፋዊው የፌስቡክ ገጹ ሲሆን፣ የዘፈኑን ዓለም "ውስብስብና አጋንንታዊ አሰራር ያለበት" ሲል ገልጾታል።
አቤል ላለፉት ዓመታት በሙዚቃው ዓለም በቆየባቸው ጊዜያት ውስጥ ከፍተኛ ውስጣዊ ትግል ሲያደርግ እንደነበር ገልጿል። በተለይም ከ2005 እስከ 2007 ዓ.ም ድረስ ለሁለት ዓመታት ሙዚቃን አቁሞ እንደነበር አስታውሶ፣ በወቅቱ ወደ ዘፈኑ ዓለም ዳግም መመለሱ ጸጸት እንደፈጠረበት አልሸሸገም።
"ዓለም ውሸት ነው፤ ዝናም ከንቱ ቆሻሻ ነው! የውሸት መልክና የውሸት ፈገግታ ብቻ!" ሲል አቤል አሁን ያለውን አቋም በጽኑ ቃላት ገልጿል።
ድምፃዊው ለውሳኔው መነሻ የሆኑትን የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች (2ኛ ጴጥሮስ 2፥22 እና ዕብራውያን 10፥38) በመጥቀስ፣ ወደ ኋላ ማፈግፈግ አብቅቶለታል ብሏል።
ለዚህም ለውጡ የጸለዩለትን ሁሉ አመስግኗል።
አቤል ሙሉጌታ ከዚህ በኋላ ወደ ዘፈኑ ዓለም ዳግም እንደማይመለስና ህይወቱን ለእግዚአብሔር አሳልፎ መስጠቱን በማረጋገጥ መልዕክቱን አጠቃሏል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
Sponsored by
Surafel
3 months ago
ደራሲ ( ሲራክ ወንድሙ )
“ሶምሶሟ” ~ ( የመጽሐፍ ) ምረቃት !
#ethiopia | መንቃት ጉዞ ነው እንጂ መድረሻ አይደለም፣ ማታለያዎችን መግፈፍ የማይመቹ እውነቶችን ፣ መጋፈጥ ብሎም ጥያቄ ከማይቀርብባቸው ፣ የወል እምነቶች የጋራ ግዴለሽነት ባለፈ በሶምሶሟ ብሒል መራመድ እንዳለብን ሥመጥር ደራሲያን የፃፉትን መፅሐፍ በብዙ አንብበናል።
ሆኖም ( መፅሐፍት ) አንድ ከባድ እውነታን በጆሮሯችን ያንሾኳሹኳሉ ብርሃን'ን የሚሹ ሁል- ጊዜ በጥላ ውስጥ በሚቀሩት ዳሩ ይገፋሉ ፤ አዎ መፅሐፍት ልሒቅ ያደርጋሉ።
ከ ( 8 ዓመታት ) በፊት ካልተሳሳትኩኝ “የኦጋዴን ድመቶች” ሲራክ እያነበበ ሳለ ነበር በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ ያየውት።
በእርግጥም የተቀመጠበት ሥፍራ ፤ ኮሽታ የማይሰማበት ማርያም ( ቤተ-ክርስቲያን ) ጀርባ ሚገኘው መቃብር ሥፍራ ላይ ነበር። ያኔ በተመስጦ ( መፅሐፉን ) እያነበበ አየውት።
ይህ ልጅ እንዴት በዚ የለጋነት እድሜው መፅሐፍትን እንዲህ በፍቅር ሊያነብ ቻለ ብዬ እገረም ነበር። በእርግጥም ሲራክ መፅሐፍት ማንበብ ብቻ ሳይሆን ፤ ዳሩ ደርሶልን አስነበበን።
ታላቁ ፈላስፋ ኒቼ በመፅሐፉ ፤ በአንድ ወቅት አንድን ሰው የሚደንሥ ኮከብ ለመውለድ ፤ በውስጡ ትርምስ ሊኖረው ይገባል ብሎ ጽፏል። ትውልዱ ንቁ አንባቢ ሊሆኑ ይገባል።
ትርምስ በዚህ አተያይ ሊወገድ የሚገባው ሥርዓት አልባነት አይደለም ፤ ዳሩ ግን እምቅ አቅም ነው፣ለውጥን የሚፈቅድ ክፍትነት ነው ፤ አይበገሬ የ ( ርዕዮተ- ምሪት ) ማለት ነው።
ሙሉ በሙሉ መኖር ማለት ዳሩ ከትርምስ ዓለም ማምለጥ ሳይሆን በትርምስ ዓለም ውስጥ ትርጉምን እንዴት መቅረጽ እንዳለብን መማር እንደ ሆነ አያሌ ደራሲያን ይስማማሉ።
ደራሲ ( ሲራክ ) መፅሐፍት ፤ በብዛት እንጠብቃለን ካንተ !
ወርኃ ( መጋቢት - 20 ) ነገ ዕለተ እሁድ ( 8 : 00 ) ላይ በከተማችን በ (ሚዛን - አማን) በሳላይሽ - ሆቴል ፈፅሞ አይቀርም ፤ እንግዶችም ይገኛሉ። በክብር ጋበዝናችሁ !
ጌታመሳይ ሙሉጌታ
“ሶምሶሟ” ~ ( የመጽሐፍ ) ምረቃት !
#ethiopia | መንቃት ጉዞ ነው እንጂ መድረሻ አይደለም፣ ማታለያዎችን መግፈፍ የማይመቹ እውነቶችን ፣ መጋፈጥ ብሎም ጥያቄ ከማይቀርብባቸው ፣ የወል እምነቶች የጋራ ግዴለሽነት ባለፈ በሶምሶሟ ብሒል መራመድ እንዳለብን ሥመጥር ደራሲያን የፃፉትን መፅሐፍ በብዙ አንብበናል።
ሆኖም ( መፅሐፍት ) አንድ ከባድ እውነታን በጆሮሯችን ያንሾኳሹኳሉ ብርሃን'ን የሚሹ ሁል- ጊዜ በጥላ ውስጥ በሚቀሩት ዳሩ ይገፋሉ ፤ አዎ መፅሐፍት ልሒቅ ያደርጋሉ።
ከ ( 8 ዓመታት ) በፊት ካልተሳሳትኩኝ “የኦጋዴን ድመቶች” ሲራክ እያነበበ ሳለ ነበር በአካል ለመጀመሪያ ጊዜ ያየውት።
በእርግጥም የተቀመጠበት ሥፍራ ፤ ኮሽታ የማይሰማበት ማርያም ( ቤተ-ክርስቲያን ) ጀርባ ሚገኘው መቃብር ሥፍራ ላይ ነበር። ያኔ በተመስጦ ( መፅሐፉን ) እያነበበ አየውት።
ይህ ልጅ እንዴት በዚ የለጋነት እድሜው መፅሐፍትን እንዲህ በፍቅር ሊያነብ ቻለ ብዬ እገረም ነበር። በእርግጥም ሲራክ መፅሐፍት ማንበብ ብቻ ሳይሆን ፤ ዳሩ ደርሶልን አስነበበን።
ታላቁ ፈላስፋ ኒቼ በመፅሐፉ ፤ በአንድ ወቅት አንድን ሰው የሚደንሥ ኮከብ ለመውለድ ፤ በውስጡ ትርምስ ሊኖረው ይገባል ብሎ ጽፏል። ትውልዱ ንቁ አንባቢ ሊሆኑ ይገባል።
ትርምስ በዚህ አተያይ ሊወገድ የሚገባው ሥርዓት አልባነት አይደለም ፤ ዳሩ ግን እምቅ አቅም ነው፣ለውጥን የሚፈቅድ ክፍትነት ነው ፤ አይበገሬ የ ( ርዕዮተ- ምሪት ) ማለት ነው።
ሙሉ በሙሉ መኖር ማለት ዳሩ ከትርምስ ዓለም ማምለጥ ሳይሆን በትርምስ ዓለም ውስጥ ትርጉምን እንዴት መቅረጽ እንዳለብን መማር እንደ ሆነ አያሌ ደራሲያን ይስማማሉ።
ደራሲ ( ሲራክ ) መፅሐፍት ፤ በብዛት እንጠብቃለን ካንተ !
ወርኃ ( መጋቢት - 20 ) ነገ ዕለተ እሁድ ( 8 : 00 ) ላይ በከተማችን በ (ሚዛን - አማን) በሳላይሽ - ሆቴል ፈፅሞ አይቀርም ፤ እንግዶችም ይገኛሉ። በክብር ጋበዝናችሁ !
ጌታመሳይ ሙሉጌታ
3 months ago
#ሰይጣን_እንዳይገዛህ_ራስህን_ግዛ_5_ዘዴዎች፦
1. ርሐብን ናቀው
ስጋህ ሲራብ መንፈስህ ይበረታል፤ ጾም የነፍስ ጅራፍ ነው።
2. ዝምታን ጌጥ አድርገው
በወሬ ብዛት ጸጋህ ይፈሳል፤ ከንፈርህን ለጉመህ ልብህን ክፈት።
3. ምቾትን አትላመድ
ተድላና ቅንጦት ለነፍስ እንቅልፍ ናቸው፤ ራስህን አስጨንቀው።
4. በትዕግስት እረፍ
መከራ ሲመጣ አትማረር፤ ፈጣሪ አልማዝ እያደረገህ ነው።
5. እንደ ወታደር ሁን
መንፈሳዊ ጉዞ ዘና ማለት የለውም፤ ዘወትር በንቃት ጠብቅ።
#መንፈሳዊ_ተጋድሎ መጽሐፍ
እና #ለነፍስ_የሚበጅ_መንገድ መጽሐፍ
ሁለት አዳዲስ የአቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ መጽሐፍት በገበያ ላይ
የአቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ፣ የቅዱስ ዮሐንስ አዲስ ምርጥ ምርጥ መንፈሳዊ መጽሐፍት በገበያ ላይ
👇🎀👇
👉#በቤት_ውስጥ_ያለች_ቤተክርስቲያን
👉#ኃጢአትን_ማሸነፍ
👉#ለደከመች_ነፍስ_መመሪያ
👉#መንፈሳዊ_ሰው_መሆን
👉#ኦርቶዶክሳዊ_ሕይወትን_መኖር
👉#ጠይቁ_ይመለስላችኋል
👉 #ሰይጣንን_አስርቡት
👉 #ሕይወት_እና_ክርስትና
👉 #የጽድቅ_መንገድ
👉 #የነፍስ_ምግብ
👉 #ለነፍስህ_ቤት_ስራላት
👉 #እስከማዕዜኑ
👉 #ትምህርተ_ሺኖዳ
👉 #አቡነሺኖዳ_መልስ_አላቸው
👉 #ኦርቶጵያ
👉#የተሰቀለው_ንጉሥ
👉#the_crucifixion_of_the_king_of_glory (በእንግሊዝኛ)
ሁሉም መጽሐፍት በየመጽሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ይገኛሉ።
📕📕📕
ፌስቡክ ገጽ
👉 https://web.facebook.com/p...
ቲክቶክ-
👉https://www.tiktok.com/@ha...
1. ርሐብን ናቀው
ስጋህ ሲራብ መንፈስህ ይበረታል፤ ጾም የነፍስ ጅራፍ ነው።
2. ዝምታን ጌጥ አድርገው
በወሬ ብዛት ጸጋህ ይፈሳል፤ ከንፈርህን ለጉመህ ልብህን ክፈት።
3. ምቾትን አትላመድ
ተድላና ቅንጦት ለነፍስ እንቅልፍ ናቸው፤ ራስህን አስጨንቀው።
4. በትዕግስት እረፍ
መከራ ሲመጣ አትማረር፤ ፈጣሪ አልማዝ እያደረገህ ነው።
5. እንደ ወታደር ሁን
መንፈሳዊ ጉዞ ዘና ማለት የለውም፤ ዘወትር በንቃት ጠብቅ።
#መንፈሳዊ_ተጋድሎ መጽሐፍ
እና #ለነፍስ_የሚበጅ_መንገድ መጽሐፍ
ሁለት አዳዲስ የአቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ መጽሐፍት በገበያ ላይ
የአቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ፣ የቅዱስ ዮሐንስ አዲስ ምርጥ ምርጥ መንፈሳዊ መጽሐፍት በገበያ ላይ
👇🎀👇
👉#በቤት_ውስጥ_ያለች_ቤተክርስቲያን
👉#ኃጢአትን_ማሸነፍ
👉#ለደከመች_ነፍስ_መመሪያ
👉#መንፈሳዊ_ሰው_መሆን
👉#ኦርቶዶክሳዊ_ሕይወትን_መኖር
👉#ጠይቁ_ይመለስላችኋል
👉 #ሰይጣንን_አስርቡት
👉 #ሕይወት_እና_ክርስትና
👉 #የጽድቅ_መንገድ
👉 #የነፍስ_ምግብ
👉 #ለነፍስህ_ቤት_ስራላት
👉 #እስከማዕዜኑ
👉 #ትምህርተ_ሺኖዳ
👉 #አቡነሺኖዳ_መልስ_አላቸው
👉 #ኦርቶጵያ
👉#የተሰቀለው_ንጉሥ
👉#the_crucifixion_of_the_king_of_glory (በእንግሊዝኛ)
ሁሉም መጽሐፍት በየመጽሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ይገኛሉ።
📕📕📕
ፌስቡክ ገጽ
👉 https://web.facebook.com/p...
ቲክቶክ-
👉https://www.tiktok.com/@ha...
3 months ago
የቤተክርስቲያን ትምህርት በኦሮሚኛ ቋንቋ በቴክኖሎጂ ታግዞ ሊሰጥ ነው #ethiopia | የመንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ዓምደ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት ከወልዳ ዳንዲ አቦቲ (ማኅበረ ፍኖተ አበው) ጋር በመሆን፣ መሠረታዊ የቤተክርስቲያን ትምህርትን በኦሮሚኛ ቋንቋ በርቀትና በኢ-ለርኒንግ (Online) ለመስጠት ዝግጅቱን ማጠናቀቁን በዛሬው ዕለት በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል።
ትምህርተ ሃይማኖት፣ ሥርዓተ ቤተክርስቲያን፣ ምስጢራተ ቤተክርስቲያን፣ ነገረ ቅዱሳን፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት (ብሉይና ሐዲስ) እና የቤተክርስቲያን ታሪክን ያካተቱ 5 መጻሕፍት በኦሮሚኛ ቋንቋ ተዘጋጅተዋል።
ትምህርቱ በመጽሐፍ (ርቀት) እና በቴክኖሎጂ የታገዘ በይነ-መረብ (ኢ-ለርኒንግ) አማራጮች የቀረበ ሲሆን፣ ማንኛውም ምእመን ባለበት ቦታ ሆኖ በኢንተርኔት መማር ይችላል።
የርቀት ትምህርቱ በአንድ ዓመት የሚጠናቀቅ ሲሆን፣ የኢ-ለርኒንግ ትምህርቱ ደግሞ በተማሪው ፍጥነት እስከ አንድ ዓመት ድረስ ሊጠናቀቅ ይችላል።
መጋቢት 19 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ 7፡00 ሰዓት ጀምሮ በአራት ኪሎ ታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ገዳም መሠረተ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት አዳራሽ ብጹዓን አባቶችና እንግዶች በተገኙበት በደመቀ ሁኔታ ይመረቃል።
ይህ አገልግሎት የቤተክርስቲያንን ትምህርት በቋንቋና በአካባቢ ሳይገደብ ለምእመናን ለማድረስ ትልቅ አቅም የሚፈጥር በመሆኑ፣ በምርቃቱ ዕለት የሚዲያ አካላት፣ ባለሀብቶችና ምእመናን በመገኘት ድጋፋቸውን እንዲያሳዩ ጥሪ ቀርቧል።
#getu #ethiopia #orthodoxtewahedo #oromiffaministry #elearning #distanceeducation #amdehaymanot #woldadandiaboti #gospelexpansion #addisababa #መንፈሳዊትምህርት #ኦሮሚኛ #ኢለርኒንግ #ተዋሕዶ #ቅዱስገብርኤል #ጌጡተመስገን #getutemesgen
ትምህርተ ሃይማኖት፣ ሥርዓተ ቤተክርስቲያን፣ ምስጢራተ ቤተክርስቲያን፣ ነገረ ቅዱሳን፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት (ብሉይና ሐዲስ) እና የቤተክርስቲያን ታሪክን ያካተቱ 5 መጻሕፍት በኦሮሚኛ ቋንቋ ተዘጋጅተዋል።
ትምህርቱ በመጽሐፍ (ርቀት) እና በቴክኖሎጂ የታገዘ በይነ-መረብ (ኢ-ለርኒንግ) አማራጮች የቀረበ ሲሆን፣ ማንኛውም ምእመን ባለበት ቦታ ሆኖ በኢንተርኔት መማር ይችላል።
የርቀት ትምህርቱ በአንድ ዓመት የሚጠናቀቅ ሲሆን፣ የኢ-ለርኒንግ ትምህርቱ ደግሞ በተማሪው ፍጥነት እስከ አንድ ዓመት ድረስ ሊጠናቀቅ ይችላል።
መጋቢት 19 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ 7፡00 ሰዓት ጀምሮ በአራት ኪሎ ታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ገዳም መሠረተ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት አዳራሽ ብጹዓን አባቶችና እንግዶች በተገኙበት በደመቀ ሁኔታ ይመረቃል።
ይህ አገልግሎት የቤተክርስቲያንን ትምህርት በቋንቋና በአካባቢ ሳይገደብ ለምእመናን ለማድረስ ትልቅ አቅም የሚፈጥር በመሆኑ፣ በምርቃቱ ዕለት የሚዲያ አካላት፣ ባለሀብቶችና ምእመናን በመገኘት ድጋፋቸውን እንዲያሳዩ ጥሪ ቀርቧል።
#getu #ethiopia #orthodoxtewahedo #oromiffaministry #elearning #distanceeducation #amdehaymanot #woldadandiaboti #gospelexpansion #addisababa #መንፈሳዊትምህርት #ኦሮሚኛ #ኢለርኒንግ #ተዋሕዶ #ቅዱስገብርኤል #ጌጡተመስገን #getutemesgen
3 months ago
#የሥጋህን_ብቻ_ሳይሆን_የነፍስህንም_ነገር_አስብ !!!
#የነፍስን_ነገር_ማሰብ መጽሐፍ #ለነፍስ_የሚበጅ_መንገድ መጽሐፍ #መንፈሳዊ_ተጋድሎ መጽሐፍ
የብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ ሶስት አዳዲስ መጽሐፍት በገበያ ላይ
#የነፍስን_ነገር_ማሰብ መጽሐፍ
ለሥጋችን ጤንነትና ደህንነት እጅግ ጥንቁቆች ነን። "ይህ ምግብ ያጠነክረኛል፣ ያኛው በሽታ ይከላከልልኛል" እያልን እንመርጣለን። ለምንለብሰው ልብስና ለምንጫማው ጫማ ጥራት የምንጨነቀው፣ ከውጫዊ ጉዳት እንዲጠብቀን ነው። ለጊዜያዊው ሥጋችን እንዲህ ከተጨነቅን፣ በየዕለቱ ከባድ ፈተና ለሚገጥማት ዘላለማዊ ነፍሳችን ምን ያህል አብልጠን መጠንቀቅ ይኖርብን ይሆን?
#ለነፍስ_የሚበጅ_መንገድ መጽሐፍ
በዚህች ዓለም የሕይወት ጉዞ ላይ ብዙ መንገዶች ከፊታችን ተዘርግተዋል። አንዳንዱ ለዐይን የሚያምር ግን ወደ ጥፋት የሚወስድ ነው፤ ሌላው ደግሞ ጠባብና አስቸጋሪ ቢመስልም ወደ ሕይወት የሚያደርስ ነው። ታዲያ በዚህ የመንገድ መጥፋት ዘመን፣ ለዘላለማዊት ነፍሳችን በእርግጥ የሚበጀው የትኛው ነው?
#መንፈሳዊ_ተጋድሎ መጽሐፍ
የሰው ልጅ አእምሮ የእግዚአብሔር ጥበብ ማደሪያ፣ እጹብና ድንቅ የሆነ ስጦታ ነው። በየዕለቱ በአእምሯችን ጓዳ ውስጥ የሚመላለሱት እልፍ አዕላፍ ሀሳቦች የዚህን ተፈጥሮ ልዕልና ይመሰክራሉ። ነገር ግን፣ በዚህ ግራ በተጋባ የቴክኖሎጂ ዘመን፣ ወደ አእምሯችን የሚጎርፉት አብዛኛዎቹ ሀሳቦች እንደ መርዝ የሚናደፉና ነፍስን የሚያቆስሉ ሆነዋል።
ከሕጻናት እስከ አረጋውያን ድረስ፣ በስልክና በኮምፒውተር መስኮት በኩል የሚረጨው የዓለም መንፈስ ግን ፊቱን ቀይሮና ተሽሞንሙኖ ይቀርብላቸዋል።
እነዚህ የጠላት ጦሮች፦
👉ዘመናዊነት እና ሥልጣኔ፣
👉አራዳነት እና ምሁራዊነት፣
👉 ጠያቂነት እና ዓለም አቀፋዊነት...
የሚሉ "የበግ ለምድ የለበሱ ተኩላዎች" ናቸው። ውጫቸው ሲታይ ያማረ፣ ውስጣቸው ግን መንፈሳዊ ማንነትን የሚቦርብር ነው።
ታዲያ በፈተና ማዕበል የሚናወጠው ክርስቲያን፣ ይህንን የመንፈስ ውጊያ እንዴት ድል ይነሳል? እንዴትስ ነው መርዙን ከማር ለይቶ የሚጥለው?
ሶስቱም የብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ አዳዲስ መጽሐፍት በገበያ ላይ ውለዋል።
በየመጽሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ይገኛሉ።
የአቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ፣ የቅዱስ ዮሐንስ አዲስ ምርጥ ምርጥ መንፈሳዊ መጽሐፍት በገበያ ላይ
👇🎀👇
👉#በቤት_ውስጥ_ያለች_ቤተክርስቲያን
👉#ኃጢአትን_ማሸነፍ
👉#ለደከመች_ነፍስ_መመሪያ
👉#መንፈሳዊ_ሰው_መሆን
👉#ኦርቶዶክሳዊ_ሕይወትን_መኖር
👉#ጠይቁ_ይመለስላችኋል
👉 #ሰይጣንን_አስርቡት
👉 #ሕይወት_እና_ክርስትና
👉 #የጽድቅ_መንገድ
👉 #የነፍስ_ምግብ
👉 #ለነፍስህ_ቤት_ስራላት
👉 #እስከማዕዜኑ
👉 #ትምህርተ_ሺኖዳ
👉 #አቡነሺኖዳ_መልስ_አላቸው
👉 #ኦርቶጵያ
👉#የተሰቀለው_ንጉሥ
👉#the_crucifixion_of_the_king_of_glory (በእንግሊዝኛ)
ሁሉም መጽሐፍት በየመጽሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ይገኛሉ።
📕📕📕
ፌስቡክ ገጽ
👉 https://web.facebook.com/p...
ቲክቶክ-
👉https://www.tiktok.com/@ha...
#የነፍስን_ነገር_ማሰብ መጽሐፍ #ለነፍስ_የሚበጅ_መንገድ መጽሐፍ #መንፈሳዊ_ተጋድሎ መጽሐፍ
የብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ ሶስት አዳዲስ መጽሐፍት በገበያ ላይ
#የነፍስን_ነገር_ማሰብ መጽሐፍ
ለሥጋችን ጤንነትና ደህንነት እጅግ ጥንቁቆች ነን። "ይህ ምግብ ያጠነክረኛል፣ ያኛው በሽታ ይከላከልልኛል" እያልን እንመርጣለን። ለምንለብሰው ልብስና ለምንጫማው ጫማ ጥራት የምንጨነቀው፣ ከውጫዊ ጉዳት እንዲጠብቀን ነው። ለጊዜያዊው ሥጋችን እንዲህ ከተጨነቅን፣ በየዕለቱ ከባድ ፈተና ለሚገጥማት ዘላለማዊ ነፍሳችን ምን ያህል አብልጠን መጠንቀቅ ይኖርብን ይሆን?
#ለነፍስ_የሚበጅ_መንገድ መጽሐፍ
በዚህች ዓለም የሕይወት ጉዞ ላይ ብዙ መንገዶች ከፊታችን ተዘርግተዋል። አንዳንዱ ለዐይን የሚያምር ግን ወደ ጥፋት የሚወስድ ነው፤ ሌላው ደግሞ ጠባብና አስቸጋሪ ቢመስልም ወደ ሕይወት የሚያደርስ ነው። ታዲያ በዚህ የመንገድ መጥፋት ዘመን፣ ለዘላለማዊት ነፍሳችን በእርግጥ የሚበጀው የትኛው ነው?
#መንፈሳዊ_ተጋድሎ መጽሐፍ
የሰው ልጅ አእምሮ የእግዚአብሔር ጥበብ ማደሪያ፣ እጹብና ድንቅ የሆነ ስጦታ ነው። በየዕለቱ በአእምሯችን ጓዳ ውስጥ የሚመላለሱት እልፍ አዕላፍ ሀሳቦች የዚህን ተፈጥሮ ልዕልና ይመሰክራሉ። ነገር ግን፣ በዚህ ግራ በተጋባ የቴክኖሎጂ ዘመን፣ ወደ አእምሯችን የሚጎርፉት አብዛኛዎቹ ሀሳቦች እንደ መርዝ የሚናደፉና ነፍስን የሚያቆስሉ ሆነዋል።
ከሕጻናት እስከ አረጋውያን ድረስ፣ በስልክና በኮምፒውተር መስኮት በኩል የሚረጨው የዓለም መንፈስ ግን ፊቱን ቀይሮና ተሽሞንሙኖ ይቀርብላቸዋል።
እነዚህ የጠላት ጦሮች፦
👉ዘመናዊነት እና ሥልጣኔ፣
👉አራዳነት እና ምሁራዊነት፣
👉 ጠያቂነት እና ዓለም አቀፋዊነት...
የሚሉ "የበግ ለምድ የለበሱ ተኩላዎች" ናቸው። ውጫቸው ሲታይ ያማረ፣ ውስጣቸው ግን መንፈሳዊ ማንነትን የሚቦርብር ነው።
ታዲያ በፈተና ማዕበል የሚናወጠው ክርስቲያን፣ ይህንን የመንፈስ ውጊያ እንዴት ድል ይነሳል? እንዴትስ ነው መርዙን ከማር ለይቶ የሚጥለው?
ሶስቱም የብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ አዳዲስ መጽሐፍት በገበያ ላይ ውለዋል።
በየመጽሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ይገኛሉ።
የአቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ፣ የቅዱስ ዮሐንስ አዲስ ምርጥ ምርጥ መንፈሳዊ መጽሐፍት በገበያ ላይ
👇🎀👇
👉#በቤት_ውስጥ_ያለች_ቤተክርስቲያን
👉#ኃጢአትን_ማሸነፍ
👉#ለደከመች_ነፍስ_መመሪያ
👉#መንፈሳዊ_ሰው_መሆን
👉#ኦርቶዶክሳዊ_ሕይወትን_መኖር
👉#ጠይቁ_ይመለስላችኋል
👉 #ሰይጣንን_አስርቡት
👉 #ሕይወት_እና_ክርስትና
👉 #የጽድቅ_መንገድ
👉 #የነፍስ_ምግብ
👉 #ለነፍስህ_ቤት_ስራላት
👉 #እስከማዕዜኑ
👉 #ትምህርተ_ሺኖዳ
👉 #አቡነሺኖዳ_መልስ_አላቸው
👉 #ኦርቶጵያ
👉#የተሰቀለው_ንጉሥ
👉#the_crucifixion_of_the_king_of_glory (በእንግሊዝኛ)
ሁሉም መጽሐፍት በየመጽሐፍት መደብሩና በአዟሪዎች እጅ ይገኛሉ።
📕📕📕
ፌስቡክ ገጽ
👉 https://web.facebook.com/p...
ቲክቶክ-
👉https://www.tiktok.com/@ha...
Comments