2 months ago
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ያዘጋጀው 18ኛው የመጻሕፍት ኤግዚቢሽን በይፋ መካሄድ ጀመረ
#ethiopia | ታላቅ የዕውቀት እና የባህል መድረክ የሆነው ባለታሪኩ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጀመረው 18ኛው የመጽሐፍት ዓውደ ርዕይ ከሰኔ 1 እስከ ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ በድምቀት መካሄዱን ቀጥሏል።
በዝግጅቱ መክፈቻ ሥነ ሥርዓት ላይ የተገኙት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ባደረጉት ንግግር ተቋሙ ላለፉት አሥር ዓመታት ለንባብ ባህል ማደግና ለመጻሕፍት ስርጭት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ሲሠራ መቆየቱን ጠቁመው፣ የዚህን ዓውደ ርዕይ ቀጣይነት በላቀ ሁኔታ ማስጠበቅና ይበልጥ ተደራሽ ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
በተመሳሳይ የዩኒቨርሲቲው ፕረስ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ዶክተር ደርብ አዶ በበኩላቸው ዝግጅቱ በየጊዜው በይዘቱም ሆነ በተሳታፊዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መምጣቱን በዝርዝር አብራርተዋል።
በዚህ ታላቅ የዕውቀት መድረክ ላይ ከ45 በላይ የሚሆኑ መጽሐፍት አከፋፋዮች፣ ዋና ዋና አሳታሚዎችና ታዋቂ የመጽሐፍት መደብሮች የተሳተፉ ሲሆን፣ በሁሉም የዕውቀት ዘርፎች ከፍተኛ ተፈላጊነት ያላቸው መጻሕፍት ከ20 እስከ 50 በመቶ በሚደርስ ትልቅ ቅናሽ ለጎብኚዎች እየቀረቡ ይገኛሉ።
ከሽያጭና ከግዢ ስምምነቶች ባሻገርም የአዳዲስ መጻሕፍት ምረቃ ሥነ ሥርዓቶች፣ አንጋፋ ደራሲያንና ምሁራን ለወጣቱ ትውልድ ጠቃሚ ተሞክሯቸውን የሚያካፍሉባቸው የውይይት መድረኮች እንዲሁም የሕፃናትን የንባብ ልማድ የሚያበረታቱ ልዩ ልዩ ዝግጅቶች በዓውደ ርዕዩ ቀናት ውስጥ የሚጠበቁ ማራኪ መርሃግብሮች መሆናቸው ታውቋል።
#aaubookfair2018 #ethiopianliterature #readtolead #addisababauniversity #bookfair #ethiopia #ንባብለህይወት #የመጽሐፍትዓውደር #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ታላቅ የዕውቀት እና የባህል መድረክ የሆነው ባለታሪኩ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጀመረው 18ኛው የመጽሐፍት ዓውደ ርዕይ ከሰኔ 1 እስከ ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ በድምቀት መካሄዱን ቀጥሏል።
በዝግጅቱ መክፈቻ ሥነ ሥርዓት ላይ የተገኙት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ባደረጉት ንግግር ተቋሙ ላለፉት አሥር ዓመታት ለንባብ ባህል ማደግና ለመጻሕፍት ስርጭት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ሲሠራ መቆየቱን ጠቁመው፣ የዚህን ዓውደ ርዕይ ቀጣይነት በላቀ ሁኔታ ማስጠበቅና ይበልጥ ተደራሽ ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
በተመሳሳይ የዩኒቨርሲቲው ፕረስ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ዶክተር ደርብ አዶ በበኩላቸው ዝግጅቱ በየጊዜው በይዘቱም ሆነ በተሳታፊዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ መምጣቱን በዝርዝር አብራርተዋል።
በዚህ ታላቅ የዕውቀት መድረክ ላይ ከ45 በላይ የሚሆኑ መጽሐፍት አከፋፋዮች፣ ዋና ዋና አሳታሚዎችና ታዋቂ የመጽሐፍት መደብሮች የተሳተፉ ሲሆን፣ በሁሉም የዕውቀት ዘርፎች ከፍተኛ ተፈላጊነት ያላቸው መጻሕፍት ከ20 እስከ 50 በመቶ በሚደርስ ትልቅ ቅናሽ ለጎብኚዎች እየቀረቡ ይገኛሉ።
ከሽያጭና ከግዢ ስምምነቶች ባሻገርም የአዳዲስ መጻሕፍት ምረቃ ሥነ ሥርዓቶች፣ አንጋፋ ደራሲያንና ምሁራን ለወጣቱ ትውልድ ጠቃሚ ተሞክሯቸውን የሚያካፍሉባቸው የውይይት መድረኮች እንዲሁም የሕፃናትን የንባብ ልማድ የሚያበረታቱ ልዩ ልዩ ዝግጅቶች በዓውደ ርዕዩ ቀናት ውስጥ የሚጠበቁ ማራኪ መርሃግብሮች መሆናቸው ታውቋል።
#aaubookfair2018 #ethiopianliterature #readtolead #addisababauniversity #bookfair #ethiopia #ንባብለህይወት #የመጽሐፍትዓውደር #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
5 months ago
6ኛው ዓመታዊ የሕፃናት ንባብ ጉባኤ በአዲስ አበባ መካሄድ ጀመረ
#ethiopia | በኢትዮጵያ ውስጥ ላለፉት 22 ዓመታት የንባብ ባህልን ለማስፋፋትና ትምህርትን ለመደገፍ ሲሠራ የቆየው ኢትዮጵያ ሪድስ (Ethiopia Reads)፣ ዘንድሮ ለስድስተኛ ጊዜ ያዘጋጀውን ዓመታዊ የሕፃናት ንባብ ጉባኤ በአዲስ አበባ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል።
"የንባብ ችግኝ በቀዳማይ ልጅነት መትከል" በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው ይህ ጉባኤ፣ በሕፃናት የንባብ ዕድገትና በትምህርት ጥራት ዙሪያ ላይ ትኩረት በማድረግ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት የሚከናወን ታላቅ መድረክ ነው።
በዚህ ጉባኤ ላይ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የፖሊሲ አውጪዎች፣ የትምህርት ዘርፍ ተመራማሪዎች፣ መምህራን፣ ደራሲያን፣ የአሳታሚ ድርጅቶች ተወካዮች እንዲሁም ከውጭ አገር የመጡ የዘርፉ ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
መድረኩ በዋናነት በሕፃናት የንባብ ልምድ ላይ ያተኮሩ ጥናታዊ ጽሑፎች የሚቀርቡበት፣ የፓናል ውይይቶች የሚካሄዱበትና ልምድ የሚለዋወጥበት ሰፊ ዕድል የፈጠረ ሲሆን፣ ይህም በዘርፉ ለሚታዩ ችግሮች ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣትና የንባብ ባህልን ከልጅነት ጀምሮ ለማዳበር ከፍተኛ ፋይዳ ይኖረዋል።
ኢትዮጵያ ሪድስ ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ በሁሉም የአገሪቱ ክልሎች ከ70 በላይ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ቤተ-መጻሕፍትን በማቋቋም ከ1.5 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎችና ሕፃናት የንባብ አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ ችሏል።
በተጨማሪም ድርጅቱ ከ"Open Hearts Big Dreams" ጋር በመተባበር "ሬዲ-ሴት-ሪድ" በሚል መጠሪያ የሕፃናት መጻሕፍትን በአሥር አገር በቀል ቋንቋዎች በማዘጋጀትና በማሰራጨት ሕፃናት በትምህርት ቤትም ሆነ በቤታቸው ከወላጆቻቸው ጋር ሆነው እንዲያነቡ ምቹ ሁኔታዎችን ሲፈጥር ቆይቷል።
በአሁኑ ወቅትም ድርጅቱ በደቡብና በኦሮሚያ ክልሎች ትምህርት ቤት መሄድ ለማይችሉ ከ14 ሺህ በላይ ሕፃናት በፈረስና በአህያ በታገዘ ተንቀሳቃሽ የንባብ አገልግሎት መጻሕፍትን እስከ መንደራቸው ድረስ በማድረስ አመርቂ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል።
ይህ የስድስተኛው ዓመታዊ ጉባኤም ድርጅቱ እስካሁን ያከናወናቸውን ተግባራት ከመገምገም ባለፈ፣ ለወደፊቱ የተሻለ የእውቀት ትውልድ ለመቅረጽ የሚያስችሉ ጠቃሚ ግብዓቶችና ምክረ-ሀሳቦች የሚገኙበት እንደሚሆን ታምኖበታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopiareads #childrensliteracy #readingculture #ethiopiaeducation #earlychildhoodeducation #bookfair #literacyconference #readysetread
#ethiopia | በኢትዮጵያ ውስጥ ላለፉት 22 ዓመታት የንባብ ባህልን ለማስፋፋትና ትምህርትን ለመደገፍ ሲሠራ የቆየው ኢትዮጵያ ሪድስ (Ethiopia Reads)፣ ዘንድሮ ለስድስተኛ ጊዜ ያዘጋጀውን ዓመታዊ የሕፃናት ንባብ ጉባኤ በአዲስ አበባ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል።
"የንባብ ችግኝ በቀዳማይ ልጅነት መትከል" በሚል መሪ ቃል የሚካሄደው ይህ ጉባኤ፣ በሕፃናት የንባብ ዕድገትና በትምህርት ጥራት ዙሪያ ላይ ትኩረት በማድረግ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት የሚከናወን ታላቅ መድረክ ነው።
በዚህ ጉባኤ ላይ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የፖሊሲ አውጪዎች፣ የትምህርት ዘርፍ ተመራማሪዎች፣ መምህራን፣ ደራሲያን፣ የአሳታሚ ድርጅቶች ተወካዮች እንዲሁም ከውጭ አገር የመጡ የዘርፉ ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
መድረኩ በዋናነት በሕፃናት የንባብ ልምድ ላይ ያተኮሩ ጥናታዊ ጽሑፎች የሚቀርቡበት፣ የፓናል ውይይቶች የሚካሄዱበትና ልምድ የሚለዋወጥበት ሰፊ ዕድል የፈጠረ ሲሆን፣ ይህም በዘርፉ ለሚታዩ ችግሮች ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣትና የንባብ ባህልን ከልጅነት ጀምሮ ለማዳበር ከፍተኛ ፋይዳ ይኖረዋል።
ኢትዮጵያ ሪድስ ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ በሁሉም የአገሪቱ ክልሎች ከ70 በላይ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ቤተ-መጻሕፍትን በማቋቋም ከ1.5 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎችና ሕፃናት የንባብ አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ ችሏል።
በተጨማሪም ድርጅቱ ከ"Open Hearts Big Dreams" ጋር በመተባበር "ሬዲ-ሴት-ሪድ" በሚል መጠሪያ የሕፃናት መጻሕፍትን በአሥር አገር በቀል ቋንቋዎች በማዘጋጀትና በማሰራጨት ሕፃናት በትምህርት ቤትም ሆነ በቤታቸው ከወላጆቻቸው ጋር ሆነው እንዲያነቡ ምቹ ሁኔታዎችን ሲፈጥር ቆይቷል።
በአሁኑ ወቅትም ድርጅቱ በደቡብና በኦሮሚያ ክልሎች ትምህርት ቤት መሄድ ለማይችሉ ከ14 ሺህ በላይ ሕፃናት በፈረስና በአህያ በታገዘ ተንቀሳቃሽ የንባብ አገልግሎት መጻሕፍትን እስከ መንደራቸው ድረስ በማድረስ አመርቂ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል።
ይህ የስድስተኛው ዓመታዊ ጉባኤም ድርጅቱ እስካሁን ያከናወናቸውን ተግባራት ከመገምገም ባለፈ፣ ለወደፊቱ የተሻለ የእውቀት ትውልድ ለመቅረጽ የሚያስችሉ ጠቃሚ ግብዓቶችና ምክረ-ሀሳቦች የሚገኙበት እንደሚሆን ታምኖበታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopiareads #childrensliteracy #readingculture #ethiopiaeducation #earlychildhoodeducation #bookfair #literacyconference #readysetread
Comments