9 hours ago
ሳይታጠብ እስከ አንድ ወር የሚቆይ አዲስ ቲ-ሸርት ለገበያ ቀረበ
አሜሪካዊው የልብስ ኩባንያ ‘ሄርክሊዮን’ ያለ ምንም እጥበት እስከ አንድ ወር ድረስ መጥፎ ጠረን ሳይይዝ በየቀኑ መልበስ የሚያስችል "HercShirt V5.0" የተሰኘ አዲስ ቲ-ሸርት ለገበያ ማቅረቡን አስታውቋል።
ኩባንያው ለዚህ ፈጠራው መዳብ፣ ብር፣ ዚንክ፣ ወርቅ እና የእሳተ ገሞራ አመድን ጨምሮ ሰባት ልዩ ንጥረ ነገሮችን በጨርቁ ክር ውስጥ ማካተቱ ተገልጿል ።
እነዚህ ንጥረ ነገሮች ባክቴሪያዎችን ያግዳሉ፤ እርጥበትንም በመምጠጥ ልብሱ ምንጊዜም ይዘቱን ጠብቆ እንዲቆይ ያደርጋሉ ተብሏል።
አልፎ አልፎ ብቻ ስለሚታጠብ ከሰባት መደበኛ ቲ-ሸርቶች በላይ ያገለግላል የተባለው ይህ ምርት በ79 ዶላር ይሸጣል።
በተጨማሪም አቅማቸው አነስተኛ ለሆኑ ደንበኞች ለሶስት ቀናት የሚቆይ የ39 ዶላር አማራጭ እና እስከ ሁለት ሳምንት የሚያገለግል መደበኛ ስሪት መዘጋጀቱ ተጠቅሷል።
በቅርቡ በጥቁር ቀለም ሽያጩ የሚጀምረው ይህ ቲ-ሸርት፣ ወደፊት በሌሎች ቀለሞችም ለገበያ ይቀርባል መባሉ ተዘግቧል።
Seledadotio
Seledadotio
አሜሪካዊው የልብስ ኩባንያ ‘ሄርክሊዮን’ ያለ ምንም እጥበት እስከ አንድ ወር ድረስ መጥፎ ጠረን ሳይይዝ በየቀኑ መልበስ የሚያስችል "HercShirt V5.0" የተሰኘ አዲስ ቲ-ሸርት ለገበያ ማቅረቡን አስታውቋል።
ኩባንያው ለዚህ ፈጠራው መዳብ፣ ብር፣ ዚንክ፣ ወርቅ እና የእሳተ ገሞራ አመድን ጨምሮ ሰባት ልዩ ንጥረ ነገሮችን በጨርቁ ክር ውስጥ ማካተቱ ተገልጿል ።
እነዚህ ንጥረ ነገሮች ባክቴሪያዎችን ያግዳሉ፤ እርጥበትንም በመምጠጥ ልብሱ ምንጊዜም ይዘቱን ጠብቆ እንዲቆይ ያደርጋሉ ተብሏል።
አልፎ አልፎ ብቻ ስለሚታጠብ ከሰባት መደበኛ ቲ-ሸርቶች በላይ ያገለግላል የተባለው ይህ ምርት በ79 ዶላር ይሸጣል።
በተጨማሪም አቅማቸው አነስተኛ ለሆኑ ደንበኞች ለሶስት ቀናት የሚቆይ የ39 ዶላር አማራጭ እና እስከ ሁለት ሳምንት የሚያገለግል መደበኛ ስሪት መዘጋጀቱ ተጠቅሷል።
በቅርቡ በጥቁር ቀለም ሽያጩ የሚጀምረው ይህ ቲ-ሸርት፣ ወደፊት በሌሎች ቀለሞችም ለገበያ ይቀርባል መባሉ ተዘግቧል።
Seledadotio
Seledadotio
1 day ago
“ታሪክ በትዝታ ላይ የተጫነ ሸክም አይደለም-የነፍስ መገለጥ እንጂ”
ጋዜጠኛ ዮናስ አየለ እንደጻፈው
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ከአሚኮ ጋር ያደረጉትን ቃለምልልስ አዳምጬ እንደጨረስኩ በቃለ ምልልሱ በርዕሰ ጉዳይ ደረጃ ጎልተው ከወጡ ዋና ዋና ጭብጦች መካከል አንዱ ነገረ ታሪክ እንደሆነ ተሰምቶኛል፡፡ ታሪክ-የሀገር ውስጥና የውጭ፤ የሩቅና የቅርብ ዘመን! ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያንጸባረቁትን ሚዛናዊና አምክኖአዊ የታሪክ እይታና ድምዳሜያቸውን አለማድነቅ ንፉግነት ነው፡፡ የአሥራ ዘጠነኛው ክፍለ ዘመን እንግሊዛዊ የታሪክ ጸሐፊና ፖለቲከኛ ሎርድ አክተን “History is not a burden on the memory but an illumination of the soul” ብሎ ሲጽፍ “ታሪክ የነፍስ መገለጥ እንጂ በትዝታ ላይ የተጫነ ሸክም አይደለም” ማለቱ ነበር፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያነሷቸው የታሪክ አንኳር ጉዳዮች እስከዛሬ ድረስ በሀገራችን የታሪክ አጻጻፍ(Historiography) እና በሕዝባዊ ትርክቶቻችን(በሚዲያዎችን ጭምር) በሚገባቸው ልክ ያልተወሱ፤ ቢወሱም ፈራ ተባ እየተባሉ የሚጠቀሱ፤ አለፍሲልም ባልተገባ የፖለቲካ እይታ ደንቃራ ተደርገው የተወሰዱ የታሪክ ግርዶሽ(eclipse of the history) ሆነው የኖሩ ስብራቶቻችን ነበሩ፡፡ ከነዚህ ቁልፍ ጉዳዮች መካከል ዋነኛዎቹ አንዱ የሕዝቦች ትስስር እና መስተጋብር ታሪክ ሲሆን ሌላኛው በአገረ መንግስት ምሥረታ ውስጥ የሸዋ ጂኦ-ስትራቴጂካዊ ሚናን የተመለከቱት ናቸው፡፡
በመጀመሪያ የአማራና የኦሮሞ ሕዝቦች በኩታ ገጠም ቀዬዎቻቸው እና የታሪክ እድል በፈጠረላቸው የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የባህል አጋጣሚዎች እንደሌሎች ማህበረሰቦች ሁሉ መጋባት መዋለዳቸው፤መተሳሰር መዋሀዳቸው ሀቅ የመሆኑን ያህል የታሪክ ጥናት እና የትርክቶቻችን ማጠንጠኛ አለመሆናቸው ይታወቃል፡፡ ከዚህ በባሰ ሁኔታ ደግሞ በነገሥታቱ መካከል የነበረው የፖለቲካ ጋብቻና የመሪዎቻችን ማህበራዊ መሠረት ጉዳይ ነውር እስኪመስል በእውነታው ልክ ሳይጠናና፣ሳይነገርለት ዘመናት አልፈዋል ፡፡ በሌላ በኩል በሸዋና አካባቢው ለረዥም ዘመን የኖሩ ሕዝቦች በአገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት የተጫወቱት ሚናና የሚጋሩት ቀደምት የሥልጣኔ ባለቤትነት (ታሪክ ሰሪነት-Agency) ግጥምጥሞሽ በሀገር መሪ ደረጃ መወሳታቸው እጅግ ጉልህ ፋይዳ ያለው ጉዳይ ነው ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያነሷቸው የታሪክ እውነታዎች ያለጥርጥር ታሪካችንንና የታሪክ ምልከታችንን ደጋግመን መመርምር እንዳለብን የሚያስገነዝቡና የወገንተኝነት ጥያቄ በሚነሳባቸው ሃይማኖታዊ የታሪክ ምንጮች እንኳን የተቀመጡ ገሃድ እውነታዎች ናቸው፡፡ መመርመር ለሚፈልግ አጥኚ እነዚህ የታሪክ እውነታዎች በየነገሥታቱ ዜና መዋዕሎች (የዐጼ አምደ ጽዮን፣ ዐጼ ሱስንዮስ፣የዐጼ ገላውዲዮስ፣ የዐጼ ሠርጸ ድንግል ወዘተ)፤ የሃይማኖት ሰነዶች፣ የታሪከ ነገሥት ቅጂዎች፣ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩ አውሮፓውያን ተጓዦችና ጸሐፊያን (ፍራንስስኮ አልቫሬዝ፣ ፔድሮ ፔዝ፣ ማኑኤል አልሜዳ፣ ጄሮኒሞ ሎቦ፣ ጀምስ ብሩስ፣ ኮንቲ ሮሲኒ ወዘተ ) መዝግበው በተውልን ሰነዶች ሰፍረው የምናገኛቸው፤ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፉ የኖሩ ቱባ መረጃዎች ናቸው፡፡
ፍራንሲስኮ አልቫሬዝ የተወልን የጽሑፍ ሰነድና ሌሎች ሀገርኛ የቃል መረጃ ምንጮች ዐፄ ልብነድንግል(1498-1532 ዓ.ም.) እንደ መሪ የአማራና የኦሮሞ ብቻ ሳይሆን ምናልባትም የሌሎች ሕዝቦችም ማህበራዊ ዳራ የነበራቸው ንጉሠ ነገሥት እንደሆኑ የሚያስረዱ ሲሆን አልቫሬዝ የንጉሱ የእናት ወንድም የነበሩት አጎታቸው ዶሪ ባህረ ነጋሽ ኦሮሞ እንደነበሩና ባህረ ነጋሽ ዶሪ ሲሞቱ ሥልጣኑ በቀጥታ ወደልጃቸው ቡሎ መሸጋገሩን ጭምር በአይኑ ያየውን ጽፏል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በትኩረት መታየት የሚገባው ጉዳይ ስለዐጼ ልብነ ድንግል የጦር አዛዦች የተነገሩ የቃል መረጃዎች ናቸወ፡፡ ከእነዚህ መካከል የንጉሠ ነገሥቱ ሠራዊት የቦረንትቻ ባሕል ያውቅ እንደነበር በተክለጻዲቅ መኩሪያ መጻፉና ከዐጼ ልብነድንግል የጦር አዛዦች አንዱ የነበረው ቱሉ ደገልሀን በመራው ከኢማም አሕመድ ጋር የተካሄደ ጦርነት የዐጼው ጦር ሲያፈገፍግ ንጉሠ ነገሥቱ “ሁሉም ቢፈራ ቱሉ እንዴት ፈራ? ” ማለታቸው ስለሠራዊታቸው ሥብጥር የሚነግረን ነገር አለ፡፡
ኦቶማን ቱርኮችን እና የዘመኑ ተላላኪዎቻቸውን ለመዋጋት የንጉሠ ነገሥቱ ሠራዊት አንድ አካል ሆነው እስከ ኤርትራ ድረስ ዘምተው ስለነበሩ የኦሮሞ ተዋጊዎች ተጋድሎ የዐጼ ሠርጸድንግል(1542-1590 ዓ.ም.) ዜና መዋእል በግልጽ አስፍሯል፡፡ እነዚህ የኦሮሞና የሌሎች ሕዝቦች ተወላጅ ወታደሮች ትግራይ እንጢጮ አካባቢ ያካሄዱትን አውደ ውጊያ ዜና መዋዕሉ ይተርካል፡፡ ለመንግሥታቸውና ለሀገራቸው እስከባሕር ጠረፍ ድረስ ዘምተው ዋጋ መክፈላቸውም ተመዝግቧል፡፡ የዐጼ ሱስንዮስ(1607-1632 ዓ.ም.) ዜና መዋእል እና በዘመኑ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩ የአውሮፓ(የፖርቱጋል) ተጓዦች የጻፏቸው የመረጃ ምንጮች ንጉሠ ነገሥቱ ግንደበረት፣ሐምቦና አካባቢው ቤታቸው እንደነበር፤ አጎታቸው ለማሞ እንደሚባል፣ ወላጅ እናታቸው(ሐመልማል ወርቅ) የአዛዥ ኩሎ ልጅ የነበረች፤ የዚሁ የሐመልማል ወርቅ ጎሳ ተወላጅ የሆነ ቡኮ የተባለ ኦሮሞና ሠራዊቱ ለአባይ ቅርብ የሆነች ምዕራብ ሸዋ ላይ ዐጼ ሱስንዮስ ሲያገኙት የነበረውን ደስታና የፍቅሩን ጽናት ዜና መዋዕሉ ሳይሰስት ጽፎታል፡፡ ዐጼ ፋሲል(ከ1632 እስከ 1667 ዓ.ም.) አባቱ ሱስንዮስ እናቱ የወሎ ቃሉ ሰው(እቴጌ ሥልጣን ሞገሳ የሚል ስም የተሰጣት) እንደሆነች የታሪክ ምንጮች ያስረዱናል፡፡ በ1620ዎቹ ዓመታት ጀምሮ በኢትዮጵያ ይኖር የነበረው ፖርቱጋላዊ ቄስ ጄሮኒሞ ሎቦ ስለዐጼ ፋሲል እናትና ኦሮሞ ዘመዶቻቸው በአይን ምስክርነት የሚያውቀውን ጽፏል፡፡ የእቴጌ ሥልጣን ሞገሳ አያት ስለብዝሀ ሃይማኖት አስፈላጊነት የነበራቸውን ግልጽ ፖሊሲ ጭምር ሎቦ ዘግቦታል፡፡ የዐጼ በካፋ(1721-1730 ዓ.ም.) እና የዐጼ ኢዮአስ(1747-1761 ዓ.ም.) ጎንደር መቼም ለሕዝቦች ውህደትና ትስስር ጥሩ ማሳያ ነበረች፡፡ የየጁ ኦሮሞ ገዢ የነበረው የአሚቶ ሴት ልጅ ዝነኛዋ ውቢት ልጇ ዐጼ አዮአስ ነበር፡፡ ኢዮአስ ከኦሮሞ አጎቱ ከደጃች ሉቦ ጋር ሥልጣኑን በጎንደር እንዴት እንዳጸና፤ የቤተ መንግሥቱም የሥራ ቋንቋ አፋን ኦሮሞ እንደነበረ የንጉሠ ነገሥቱ ዜና መዋዕልና በጀምስ ብሩስ ቅጽ ሁለት መጽሀፍ የተመዘገቡ የታሪክ መረጃዎች ያስረዱናል፡፡
መነሻውን ወሎ በማድረግ ጎንደር ጸንቶ የኖረው የየጁ ሥርወ መንግሥት(ወረ ሼኮች) መሥራቾች የመርሳው አባ ጌትዬ፣ የልጃቸው ጓንጉል አባ ሴሩ እንዲሁም የልጅ ልጃቸው የራስ አሊ ጓንጉል(አሊ ትልቁ) ታሪክ በኢዮአስ ዜና መዋዕል፣ በጀምስ ብሩስ መጽሐፍና በሌሎች በርካታ ሰነዶች ታሪካቸው ተዘግቧል፡፡ በኋላ ላይ በሽፈራው በቀለ(ፕሮፌሰር) እና ሞላ ትኩዬ የቀረቡ ጥልቅ ጥናቶች ይህን እውነት በዝርዝር ያስረዱናል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው እንደጠቀሱት የእነዚህ መሪዎች የፖለቲካ ጋብቻ ታሪክ የሚያሳየን በሄዱበት አገር ሁሉ የሕዝቦች ትሥሥር እና የፖለቲካ ጋብቻ የኖረ ታሪካችን እና የጉልበታችን ምንጭ እንደነበረ ነው፡፡ በዳግማዊ ዐጼ ቴዎድሮስ ዘመን የተጻፉ የታሪክ ሰነዶች የወሎዋ ገዢ ወርቂቱ ወዳጆ(የማመዶች ሥርወ መንግሥት መሪ የኢማም አሊ አባ ቡላ ባለቤት) ንጉሥ ምኒልክ ከመቅደላ እስር ቤት እንዲያመልጡ ያደረጉ፤ አጃቢ ሠራዊት አሰማርተው ምኒልክን እስከሸዋ የሸኙ እንደነበሩ በዋናነት ከጸሓፌ ትእዛዝ ገብረ ሥላሴ ታሪከ ዘመን ዘ ዳግማዊ ምኒልክ ዜና መዋዕል እና በመቅደላ አምባ እስር ላይ የነበሩ አውሮፓውያን ከጻፏቸው መረጃዎች እንረዳለን፡፡
ሥልጣኔዎቻችን ሁሉ ተደምረን ያሳካናቸው እንደሆነ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው አንስተዋል፡፡ የዐድዋ ዘመቻና ድሉ ለዚህ አንዱ ማሳያ እንደሆነ ተጨባጭ የታሪክ ምንጮች ያስረዱናል፡፡ በ1888 ዓ.ም. ለዓድዋ ዘመቻ ከመላው ኢትዮጵያ የተመመው ሠረዊት ወፍላ ላይ የነበረው ሠልፍ የንጉሠ ነገሥቱ ዜና መዋዕል እንኳን እንዲህ ይገልጸዋል፡፡ “የመኳንንቱ የጦር መሣሪያ፣ወርቁ፣ ጣፋ፣ ብሩ፣ ሙጣው፣ ጫሜው፣ ሎሚታውና ኩፊታው፣ ከሌቻው፣ ወርቅ ለምዱ እንደጸሐይ ሲያበራ ዋለ፡፡” እንደጸሐይ የበራውን ሕብረ ባሕልና ሕብረ ማንነት ትርክቶቻችን በልኩ አጉልተው ያውቃሉ?
ሸዋና አካባቢው(ወሎን ጨምሮ) እንደ አንድ ጂዞ ስትራቴጂ ሥፍራ የሕዝቦች ውህደትና ትስስር መሠረት ሆኖት የመልክዓ ምድር መገኛው ለግብርና እና ለውጭ ንግድ የተመቸ በመሆኑ በኢትዮጵያ አገረ መንግሥት ግንባታ ታሪክ ውስጥ ቁልፍ ቦታ ይዞ መኖሩን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው መግቢያ አስታውሰውናል፡፡ ሸዋና አካባቢው ከመንግሥታት ምስረታ ጋር በተገናኘ ከዘጠነኛው አንስቶ እስካሁን ያለው ረዥም የታሪክ ጉዞ በርግጥም ሊነገር፣ ሊተነተን የአደባባይ ትርክት አካል ሊደረግ የሚገባው እውነት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሸዋ ሡልጣኔት ምስረታ( እ.አ..አ.896 ዓ.ም.) እስከ ዓድዋ ድል(1888 ዓ.ም.) ሥላወሷቸው የአርጎባ(የወላስማ/ወሊ አስማ ሥርወ መንግሥት)፣ የአማራ(ሰለሞናዊ ሥርወ መንግሥት)፣ ኦሮሞ(ቱለማው በተለይ)፣ወርጂ፣ ጉራጌ፣ ጋፋት፣ ወዘተ ሕዝቦች ትስስርም ይሁን የፖለቲካ ጋብቻ የተመለከተ ታሪክ ከበቂ በላይ የታሪክ ማስረጃ ምንጮች ቢኖሩንም በታሪክ ግርዶሹ ምክንያት የወል ትርክት አካል መሆን አልቻለም፡፡
ኤንሪኮ ቼሩሊ ከሐረር አግኝቶ ያሳተመው በአረብኛ የተጻፈው የሸዋ ሡልጣኔት ዜና መዋዕል እንደሚያመለክተው ሡልጣኔቱን እ.አ.አ. በ896/7 የመሰረቱት የማህዙሚ ጎሳ አባላት ናቸው፡፡ መንግሥታቸውም ከ9ኛው እስከ 13ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ በተከታታይ በገዙ አሥራ አራት ሱልጣኖች እንደጸና የታሪክ መረጃ ምንጮች ያመለክታሉ፡፡ የሸዋ ሙስሊም ሡልጣኔቱ መቀመጫ ከተማ ከአዲስ አበባ በስተሰሜን ምሥራቅ 70 ኪሎ ሜትር ላይ የምትገኝ ወለላ የተባለች ሥፍራ እንደነበረች የጆርጅ ደብሊው ቢ ሀንቲንግፎርድ(1989) ጥናት ያመለክታል፡፡ የማህዙሚ ሥርወ መንግሥት ከመጨረሻዎቹ መሪዎች አንዱ የነበረው ሡልጣን ድልመራህ ወርጂዎች የይኖሩበት በነበረው አካባቢ በ1270ዎቹ በነበረ የርስ በርስ ጦርነት ድል ሳይቀናው ሲቀር ሕይወቱን ለማትረፍ ዐጼ(የአማራ ገዥ?) እንደሄደ ይህው የአረብኛ ዜና መዋእል ያስረዳል፡፡ የማህዙሚዎች የሸዋ ሡልጣኔት የተተካው በዋናነት የአርጎባዎች አገር በሆነው ይፋት(ዊፋት) ላይ በወላስማዎች ነበር፡፡ ወላስማዎች ከአጎራባቾቻው ጋር እየተጋቡ፣ እየተስማሙም እየተጋጩም የይፋት ሡልጣኔትን ከ13ኛው እስከ 15ኛው ክፍለ ዘመን ከሸዋ እስከ ምሥራቃዊ የኢትዮጵያ ጠረፍ እንዳስተዳደሩ ስፍር ቁጥር የሌለው የሰነድ( የኢብን ካልዱን ተማሪ የነበረው አል ማቅሪዚ ጽሑፍ- ኪታብ አል ኢልማም)፣ የአርኪዮሎጂና የቃል መረጃ ምንጮች አሉ፡፡
መነሻውን ሰሜን ሸዋ እና ደቡብ ወሎ ያደረገው የክርስቲያኑ ሰሎሞናዊ ሥርወ መንግሥት በአካባቢው ያሉ ሕዝቦች ተዋህደው ከ13ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በጋራ የመሠረቱት እንደሆነ አያጠያይቅም፡፡ አማራዎች፤ አርጎባዎች፣ ወርጂዎች፣ ጋፋቶች፣ ጉራጌዎች እና ኦሮሞዎች፣ አፋሮች፣ ሐረሪዎች ወዘተ በዚህ የሸዋ መንግሥታት የተጽዕኖ ምህዳር(Orbit) ውስጥ እንደሚገኙ ዜና መዋእሎች፣ የሃይማኖት ሰነዶች፣ የአርኪዮሎጂ ማስረጃዎች ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፉ የኖሩ የቃል መረጃ ምንጮች ያመለክታሉ፡፡ ለምሳሌ ታደሠ ታምራት(ፕሮፌሠር) ከ13ኛው እስከ 16ኛው ክፍለ ዘመን የቤተ ክርስቲያንና መንግሥትን ግንኙነት ታሪክ ባጠኑበት መጽሐፋቸው የገላንና ያያ ሰዎች ሸዋ ውስጥ በ13ኛው ክፍለ ዘመን በኦዳ ዛፍ (ኮቢል የሚባል ዋርካ) ሥር ሃይማኖታዊ ሥርዓት ይፈጽሙ እንደነበር ገድለ አቡነ ቀውስጦስን ጠቅሰው ጽፈዋል(ገጽ 184)፡፡ ሸዋ የባለ ብዙ ማንነት ሕዝቦች ሀገር ከመሆኗ ባሻገር በ16ኛው ክፍለ ዘመን የተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች ላይ መረጃ የተወልን መነኩሴው አባ ባህሪይ እንደገለጸው “ሸዋ የመንግሥት ሀገር ነች” (ገጽ 130)፡፡ በየዘመናቱ ከሸዋ የተነሱ የፖለቲካ ኃይሎች፣ ፈረሰኛ ሠራዊታቸውን ይዘው በሰሜን እስከ ኤርትራ(በዐጼ ሠርጸ ድንግል ዘመን- የኤርትራዋ ባሬንቱ የዚህ የታሪክ ሂደት ውርስ አይደለችም ማለት አይቻልም፡፡) በምሥራቅ እስከ ዘይላ(ከዐጼ አምደጽዮን እስከ ገላውዲዮስ ዘመን)፣ በምዕራብ እስከ ሱዳን ፋዞግሊ(ዐጼ ሱስንዮስ ዘመን) በደቡብ እስከ ሞያሌ ተንቀሳቅሰው በአገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት ውስጥ ቁልፍ ሚና ተጫተዋል፡፡
እነዚህ የሸዋ እና አካባቢው ሕዝቦችና ገዢዎች ትልቁን ንቅናቄያቸውን ያደረጉት ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ዐጼ ምኒልክና ራስ ጎበና ዳጬ የቱለማ ኦሮሞ፤ የሸዋ አማራ እና የሌሎችም ውህድ የሆነ ጦራቸውን አዝምተው ወሎ ወግተው ወረኢሉን የመንሥታቸው መቀመጫ ያደረጉት አርሲ፣ወለጋ፣ከሐረር ከመዝመታቸው በፊት ነበር፡፡ የመጫ ኦሮሞ ተወላጁን የጎጃሙን ንጉስ ተክለሃይማኖት(አዳል ተሰማ) በቱለማው መሪ ራስ ጎበና ዳጪ እምባቦ ላይ ያስገበሩት የጂኦ ፖለቲካዊ እና የሕዝቦች ትስስር እድሎች ጉልበት ፈጥሮላቸው፤ ኃይል አጎናጽፏቸው እንጂ በአጋጣሚ አይደለም፡፡ በርግጥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የፖለቲካችን ደንቃራነት የፈጠረውን የታሪክ ግርዶሽ ያሸነፉ ፋና ወጊ ጥናቾች መውጣት ጀምረዋል፡፡ አንዱ “Invisible Actors: The Oromo and the Creation of Modern Ethiopia(1855-1913)” በሚል ርዕስ በብሪያን ጀምስ ዬትስ(2002) በኤሊኖይስ ዩኒቨርሲቲ ከተጠናው እጅግ ጠቃሚ የዶክትሬት ዲግሪ ማሟያ ጥናት ሲሆን ሌላው የደቻሳ አበበ(ዶ/ር) ጎበና ወታደራዊና ፖለቲካዊ ሕይወት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው የዘመናዊት ኢትዮጵያን እውን መሆን ያለ ምኒልክና ያለ ጎበና እንደማይታሰብ ሲጠቅሱ ይህንን እውነታ ማጉላታቸው ይመስለኛል፡፡
የሕዝቦች ትስስርና የፖለቲካ ጋብቻ በአማራና በኦሮሞ ሕዝብ መስተጋብር ብቻ የታጠረ አልነበረም-ሊሆንም አይችልም፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ባህልና ሥልጣኔ መጋመዱ ረቂቅ ነው፡፡ ከጥንታዊ አክሱም ዘመን ጀምሮ በዝነኞቹ የአክሱም መቃብር ሀውልቶች እና በላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ላይ ከምናገኛቸው የኪነ ሕንጻ ትእምርቶች(Symbols) መካከል የውሸት በሮች (False Doors) እና የውሸት መስኮቶች(False windows) የሙታን መንፈስ(ኤከራ) መመላለሻ እንደሆኑ በጥናት የተረጋገጠ ነው (ቢትራይስ ፕሌይን Annales d'Éthiopie 1965) ፡፡ ይህ የኤከራዎች መመላለስና የመነጋገር ባህል እና እምነት ከደቡባዊ ግብጽ አንስቶ እስከ ሰሜን ኬንያ ድረስ በሚኖሩ የኩሽ ሕዝቦች በሰፊው የሚታወቅ ረዥም ዘመን ያስቆጠረ ልምምድ ነው፡፡
ሌላው በልኩ ያልተጠና እና በትርክቶቻችን ውስጥ ትኩረት ያልተሰጠው በሕዝቦች መካከል ያለ ሥልጣኔ ትስስር ታሪክ የእያንዳዱን የዛግዌ ነገሥታት የሥልጣን ዘመናትን የተመለከተ ነው፡፡ ከታሪክ ነገሥት፣ ከልዩ ልዩ ዜና መዋዕሎች፣ ከፖርቱጋል ተጓዦች(ፓኤዝና አልሜዳ) ከብሪቲሽ ሙዝየም እንዲሁም ከኮንቲ ሮሲኒ የተገኙት ምንጮች የሚረጋግጡት የሁሉም የዛግዌ ዐጼዎች( ከአንድ ሁለቱ በስተቀር) የሥልጣን ዘመን 40፤40 ዓመታት ነበር፡፡ ይህ ጉዳይ በኦሮሞ የገዳ ሥርዓት የአንድ ትውልድ የሥልጣን ዑደት ጋር አንድ አይነት የሆነው በአጋጣሚ ነው ወይስ ዛግዌዎች እና ኦሮሞዎች የኩሽ ሕዝቦች በመሆናቸው ቀዳሚ ከሆነው የጋራ ሥልጣኔያቸው የሚቀዳ የአስተዳደር ሥርዓት ነው? እነዚህስ ሀቆች የወል ትርክቶቻችን መመሆን አለመቻላቸው በፖለቲካ ደንቃራነት የተፈጠረ የታሪክ ግርዶሽ(eclipse of history) እንጂ ሌላ ምን ሊባል ይችላል? በላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትና እና በሸዋ በሚገኘው የአዳዲ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ኪነሕንጻ መካከል ያለው ፍጹም ተመሳሳይነት ምንጩ ምንድነው? ሊጠና፣ ሊነገር ልንማርበት ይገባል፡፡
በርግጥም ታሪካችን ትዝታችን ላይ የተጫነ ሸክም ሳይሆን የነፍስ መገለጥ ነው የሚያሰኘው የሕዝቦች ትሥሥር፣ ውህደት የሥልጣኔ መጋራትና መወራረስ ታሪክ መታወቁ መንፈስን ሃርነት ማውጣቱ ይመስለኛል፡፡
ጋዜጠኛ ዮናስ አየለ እንደጻፈው
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ከአሚኮ ጋር ያደረጉትን ቃለምልልስ አዳምጬ እንደጨረስኩ በቃለ ምልልሱ በርዕሰ ጉዳይ ደረጃ ጎልተው ከወጡ ዋና ዋና ጭብጦች መካከል አንዱ ነገረ ታሪክ እንደሆነ ተሰምቶኛል፡፡ ታሪክ-የሀገር ውስጥና የውጭ፤ የሩቅና የቅርብ ዘመን! ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያንጸባረቁትን ሚዛናዊና አምክኖአዊ የታሪክ እይታና ድምዳሜያቸውን አለማድነቅ ንፉግነት ነው፡፡ የአሥራ ዘጠነኛው ክፍለ ዘመን እንግሊዛዊ የታሪክ ጸሐፊና ፖለቲከኛ ሎርድ አክተን “History is not a burden on the memory but an illumination of the soul” ብሎ ሲጽፍ “ታሪክ የነፍስ መገለጥ እንጂ በትዝታ ላይ የተጫነ ሸክም አይደለም” ማለቱ ነበር፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያነሷቸው የታሪክ አንኳር ጉዳዮች እስከዛሬ ድረስ በሀገራችን የታሪክ አጻጻፍ(Historiography) እና በሕዝባዊ ትርክቶቻችን(በሚዲያዎችን ጭምር) በሚገባቸው ልክ ያልተወሱ፤ ቢወሱም ፈራ ተባ እየተባሉ የሚጠቀሱ፤ አለፍሲልም ባልተገባ የፖለቲካ እይታ ደንቃራ ተደርገው የተወሰዱ የታሪክ ግርዶሽ(eclipse of the history) ሆነው የኖሩ ስብራቶቻችን ነበሩ፡፡ ከነዚህ ቁልፍ ጉዳዮች መካከል ዋነኛዎቹ አንዱ የሕዝቦች ትስስር እና መስተጋብር ታሪክ ሲሆን ሌላኛው በአገረ መንግስት ምሥረታ ውስጥ የሸዋ ጂኦ-ስትራቴጂካዊ ሚናን የተመለከቱት ናቸው፡፡
በመጀመሪያ የአማራና የኦሮሞ ሕዝቦች በኩታ ገጠም ቀዬዎቻቸው እና የታሪክ እድል በፈጠረላቸው የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የባህል አጋጣሚዎች እንደሌሎች ማህበረሰቦች ሁሉ መጋባት መዋለዳቸው፤መተሳሰር መዋሀዳቸው ሀቅ የመሆኑን ያህል የታሪክ ጥናት እና የትርክቶቻችን ማጠንጠኛ አለመሆናቸው ይታወቃል፡፡ ከዚህ በባሰ ሁኔታ ደግሞ በነገሥታቱ መካከል የነበረው የፖለቲካ ጋብቻና የመሪዎቻችን ማህበራዊ መሠረት ጉዳይ ነውር እስኪመስል በእውነታው ልክ ሳይጠናና፣ሳይነገርለት ዘመናት አልፈዋል ፡፡ በሌላ በኩል በሸዋና አካባቢው ለረዥም ዘመን የኖሩ ሕዝቦች በአገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት የተጫወቱት ሚናና የሚጋሩት ቀደምት የሥልጣኔ ባለቤትነት (ታሪክ ሰሪነት-Agency) ግጥምጥሞሽ በሀገር መሪ ደረጃ መወሳታቸው እጅግ ጉልህ ፋይዳ ያለው ጉዳይ ነው ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያነሷቸው የታሪክ እውነታዎች ያለጥርጥር ታሪካችንንና የታሪክ ምልከታችንን ደጋግመን መመርምር እንዳለብን የሚያስገነዝቡና የወገንተኝነት ጥያቄ በሚነሳባቸው ሃይማኖታዊ የታሪክ ምንጮች እንኳን የተቀመጡ ገሃድ እውነታዎች ናቸው፡፡ መመርመር ለሚፈልግ አጥኚ እነዚህ የታሪክ እውነታዎች በየነገሥታቱ ዜና መዋዕሎች (የዐጼ አምደ ጽዮን፣ ዐጼ ሱስንዮስ፣የዐጼ ገላውዲዮስ፣ የዐጼ ሠርጸ ድንግል ወዘተ)፤ የሃይማኖት ሰነዶች፣ የታሪከ ነገሥት ቅጂዎች፣ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩ አውሮፓውያን ተጓዦችና ጸሐፊያን (ፍራንስስኮ አልቫሬዝ፣ ፔድሮ ፔዝ፣ ማኑኤል አልሜዳ፣ ጄሮኒሞ ሎቦ፣ ጀምስ ብሩስ፣ ኮንቲ ሮሲኒ ወዘተ ) መዝግበው በተውልን ሰነዶች ሰፍረው የምናገኛቸው፤ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፉ የኖሩ ቱባ መረጃዎች ናቸው፡፡
ፍራንሲስኮ አልቫሬዝ የተወልን የጽሑፍ ሰነድና ሌሎች ሀገርኛ የቃል መረጃ ምንጮች ዐፄ ልብነድንግል(1498-1532 ዓ.ም.) እንደ መሪ የአማራና የኦሮሞ ብቻ ሳይሆን ምናልባትም የሌሎች ሕዝቦችም ማህበራዊ ዳራ የነበራቸው ንጉሠ ነገሥት እንደሆኑ የሚያስረዱ ሲሆን አልቫሬዝ የንጉሱ የእናት ወንድም የነበሩት አጎታቸው ዶሪ ባህረ ነጋሽ ኦሮሞ እንደነበሩና ባህረ ነጋሽ ዶሪ ሲሞቱ ሥልጣኑ በቀጥታ ወደልጃቸው ቡሎ መሸጋገሩን ጭምር በአይኑ ያየውን ጽፏል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በትኩረት መታየት የሚገባው ጉዳይ ስለዐጼ ልብነ ድንግል የጦር አዛዦች የተነገሩ የቃል መረጃዎች ናቸወ፡፡ ከእነዚህ መካከል የንጉሠ ነገሥቱ ሠራዊት የቦረንትቻ ባሕል ያውቅ እንደነበር በተክለጻዲቅ መኩሪያ መጻፉና ከዐጼ ልብነድንግል የጦር አዛዦች አንዱ የነበረው ቱሉ ደገልሀን በመራው ከኢማም አሕመድ ጋር የተካሄደ ጦርነት የዐጼው ጦር ሲያፈገፍግ ንጉሠ ነገሥቱ “ሁሉም ቢፈራ ቱሉ እንዴት ፈራ? ” ማለታቸው ስለሠራዊታቸው ሥብጥር የሚነግረን ነገር አለ፡፡
ኦቶማን ቱርኮችን እና የዘመኑ ተላላኪዎቻቸውን ለመዋጋት የንጉሠ ነገሥቱ ሠራዊት አንድ አካል ሆነው እስከ ኤርትራ ድረስ ዘምተው ስለነበሩ የኦሮሞ ተዋጊዎች ተጋድሎ የዐጼ ሠርጸድንግል(1542-1590 ዓ.ም.) ዜና መዋእል በግልጽ አስፍሯል፡፡ እነዚህ የኦሮሞና የሌሎች ሕዝቦች ተወላጅ ወታደሮች ትግራይ እንጢጮ አካባቢ ያካሄዱትን አውደ ውጊያ ዜና መዋዕሉ ይተርካል፡፡ ለመንግሥታቸውና ለሀገራቸው እስከባሕር ጠረፍ ድረስ ዘምተው ዋጋ መክፈላቸውም ተመዝግቧል፡፡ የዐጼ ሱስንዮስ(1607-1632 ዓ.ም.) ዜና መዋእል እና በዘመኑ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩ የአውሮፓ(የፖርቱጋል) ተጓዦች የጻፏቸው የመረጃ ምንጮች ንጉሠ ነገሥቱ ግንደበረት፣ሐምቦና አካባቢው ቤታቸው እንደነበር፤ አጎታቸው ለማሞ እንደሚባል፣ ወላጅ እናታቸው(ሐመልማል ወርቅ) የአዛዥ ኩሎ ልጅ የነበረች፤ የዚሁ የሐመልማል ወርቅ ጎሳ ተወላጅ የሆነ ቡኮ የተባለ ኦሮሞና ሠራዊቱ ለአባይ ቅርብ የሆነች ምዕራብ ሸዋ ላይ ዐጼ ሱስንዮስ ሲያገኙት የነበረውን ደስታና የፍቅሩን ጽናት ዜና መዋዕሉ ሳይሰስት ጽፎታል፡፡ ዐጼ ፋሲል(ከ1632 እስከ 1667 ዓ.ም.) አባቱ ሱስንዮስ እናቱ የወሎ ቃሉ ሰው(እቴጌ ሥልጣን ሞገሳ የሚል ስም የተሰጣት) እንደሆነች የታሪክ ምንጮች ያስረዱናል፡፡ በ1620ዎቹ ዓመታት ጀምሮ በኢትዮጵያ ይኖር የነበረው ፖርቱጋላዊ ቄስ ጄሮኒሞ ሎቦ ስለዐጼ ፋሲል እናትና ኦሮሞ ዘመዶቻቸው በአይን ምስክርነት የሚያውቀውን ጽፏል፡፡ የእቴጌ ሥልጣን ሞገሳ አያት ስለብዝሀ ሃይማኖት አስፈላጊነት የነበራቸውን ግልጽ ፖሊሲ ጭምር ሎቦ ዘግቦታል፡፡ የዐጼ በካፋ(1721-1730 ዓ.ም.) እና የዐጼ ኢዮአስ(1747-1761 ዓ.ም.) ጎንደር መቼም ለሕዝቦች ውህደትና ትስስር ጥሩ ማሳያ ነበረች፡፡ የየጁ ኦሮሞ ገዢ የነበረው የአሚቶ ሴት ልጅ ዝነኛዋ ውቢት ልጇ ዐጼ አዮአስ ነበር፡፡ ኢዮአስ ከኦሮሞ አጎቱ ከደጃች ሉቦ ጋር ሥልጣኑን በጎንደር እንዴት እንዳጸና፤ የቤተ መንግሥቱም የሥራ ቋንቋ አፋን ኦሮሞ እንደነበረ የንጉሠ ነገሥቱ ዜና መዋዕልና በጀምስ ብሩስ ቅጽ ሁለት መጽሀፍ የተመዘገቡ የታሪክ መረጃዎች ያስረዱናል፡፡
መነሻውን ወሎ በማድረግ ጎንደር ጸንቶ የኖረው የየጁ ሥርወ መንግሥት(ወረ ሼኮች) መሥራቾች የመርሳው አባ ጌትዬ፣ የልጃቸው ጓንጉል አባ ሴሩ እንዲሁም የልጅ ልጃቸው የራስ አሊ ጓንጉል(አሊ ትልቁ) ታሪክ በኢዮአስ ዜና መዋዕል፣ በጀምስ ብሩስ መጽሐፍና በሌሎች በርካታ ሰነዶች ታሪካቸው ተዘግቧል፡፡ በኋላ ላይ በሽፈራው በቀለ(ፕሮፌሰር) እና ሞላ ትኩዬ የቀረቡ ጥልቅ ጥናቶች ይህን እውነት በዝርዝር ያስረዱናል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው እንደጠቀሱት የእነዚህ መሪዎች የፖለቲካ ጋብቻ ታሪክ የሚያሳየን በሄዱበት አገር ሁሉ የሕዝቦች ትሥሥር እና የፖለቲካ ጋብቻ የኖረ ታሪካችን እና የጉልበታችን ምንጭ እንደነበረ ነው፡፡ በዳግማዊ ዐጼ ቴዎድሮስ ዘመን የተጻፉ የታሪክ ሰነዶች የወሎዋ ገዢ ወርቂቱ ወዳጆ(የማመዶች ሥርወ መንግሥት መሪ የኢማም አሊ አባ ቡላ ባለቤት) ንጉሥ ምኒልክ ከመቅደላ እስር ቤት እንዲያመልጡ ያደረጉ፤ አጃቢ ሠራዊት አሰማርተው ምኒልክን እስከሸዋ የሸኙ እንደነበሩ በዋናነት ከጸሓፌ ትእዛዝ ገብረ ሥላሴ ታሪከ ዘመን ዘ ዳግማዊ ምኒልክ ዜና መዋዕል እና በመቅደላ አምባ እስር ላይ የነበሩ አውሮፓውያን ከጻፏቸው መረጃዎች እንረዳለን፡፡
ሥልጣኔዎቻችን ሁሉ ተደምረን ያሳካናቸው እንደሆነ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው አንስተዋል፡፡ የዐድዋ ዘመቻና ድሉ ለዚህ አንዱ ማሳያ እንደሆነ ተጨባጭ የታሪክ ምንጮች ያስረዱናል፡፡ በ1888 ዓ.ም. ለዓድዋ ዘመቻ ከመላው ኢትዮጵያ የተመመው ሠረዊት ወፍላ ላይ የነበረው ሠልፍ የንጉሠ ነገሥቱ ዜና መዋዕል እንኳን እንዲህ ይገልጸዋል፡፡ “የመኳንንቱ የጦር መሣሪያ፣ወርቁ፣ ጣፋ፣ ብሩ፣ ሙጣው፣ ጫሜው፣ ሎሚታውና ኩፊታው፣ ከሌቻው፣ ወርቅ ለምዱ እንደጸሐይ ሲያበራ ዋለ፡፡” እንደጸሐይ የበራውን ሕብረ ባሕልና ሕብረ ማንነት ትርክቶቻችን በልኩ አጉልተው ያውቃሉ?
ሸዋና አካባቢው(ወሎን ጨምሮ) እንደ አንድ ጂዞ ስትራቴጂ ሥፍራ የሕዝቦች ውህደትና ትስስር መሠረት ሆኖት የመልክዓ ምድር መገኛው ለግብርና እና ለውጭ ንግድ የተመቸ በመሆኑ በኢትዮጵያ አገረ መንግሥት ግንባታ ታሪክ ውስጥ ቁልፍ ቦታ ይዞ መኖሩን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው መግቢያ አስታውሰውናል፡፡ ሸዋና አካባቢው ከመንግሥታት ምስረታ ጋር በተገናኘ ከዘጠነኛው አንስቶ እስካሁን ያለው ረዥም የታሪክ ጉዞ በርግጥም ሊነገር፣ ሊተነተን የአደባባይ ትርክት አካል ሊደረግ የሚገባው እውነት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሸዋ ሡልጣኔት ምስረታ( እ.አ..አ.896 ዓ.ም.) እስከ ዓድዋ ድል(1888 ዓ.ም.) ሥላወሷቸው የአርጎባ(የወላስማ/ወሊ አስማ ሥርወ መንግሥት)፣ የአማራ(ሰለሞናዊ ሥርወ መንግሥት)፣ ኦሮሞ(ቱለማው በተለይ)፣ወርጂ፣ ጉራጌ፣ ጋፋት፣ ወዘተ ሕዝቦች ትስስርም ይሁን የፖለቲካ ጋብቻ የተመለከተ ታሪክ ከበቂ በላይ የታሪክ ማስረጃ ምንጮች ቢኖሩንም በታሪክ ግርዶሹ ምክንያት የወል ትርክት አካል መሆን አልቻለም፡፡
ኤንሪኮ ቼሩሊ ከሐረር አግኝቶ ያሳተመው በአረብኛ የተጻፈው የሸዋ ሡልጣኔት ዜና መዋዕል እንደሚያመለክተው ሡልጣኔቱን እ.አ.አ. በ896/7 የመሰረቱት የማህዙሚ ጎሳ አባላት ናቸው፡፡ መንግሥታቸውም ከ9ኛው እስከ 13ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ በተከታታይ በገዙ አሥራ አራት ሱልጣኖች እንደጸና የታሪክ መረጃ ምንጮች ያመለክታሉ፡፡ የሸዋ ሙስሊም ሡልጣኔቱ መቀመጫ ከተማ ከአዲስ አበባ በስተሰሜን ምሥራቅ 70 ኪሎ ሜትር ላይ የምትገኝ ወለላ የተባለች ሥፍራ እንደነበረች የጆርጅ ደብሊው ቢ ሀንቲንግፎርድ(1989) ጥናት ያመለክታል፡፡ የማህዙሚ ሥርወ መንግሥት ከመጨረሻዎቹ መሪዎች አንዱ የነበረው ሡልጣን ድልመራህ ወርጂዎች የይኖሩበት በነበረው አካባቢ በ1270ዎቹ በነበረ የርስ በርስ ጦርነት ድል ሳይቀናው ሲቀር ሕይወቱን ለማትረፍ ዐጼ(የአማራ ገዥ?) እንደሄደ ይህው የአረብኛ ዜና መዋእል ያስረዳል፡፡ የማህዙሚዎች የሸዋ ሡልጣኔት የተተካው በዋናነት የአርጎባዎች አገር በሆነው ይፋት(ዊፋት) ላይ በወላስማዎች ነበር፡፡ ወላስማዎች ከአጎራባቾቻው ጋር እየተጋቡ፣ እየተስማሙም እየተጋጩም የይፋት ሡልጣኔትን ከ13ኛው እስከ 15ኛው ክፍለ ዘመን ከሸዋ እስከ ምሥራቃዊ የኢትዮጵያ ጠረፍ እንዳስተዳደሩ ስፍር ቁጥር የሌለው የሰነድ( የኢብን ካልዱን ተማሪ የነበረው አል ማቅሪዚ ጽሑፍ- ኪታብ አል ኢልማም)፣ የአርኪዮሎጂና የቃል መረጃ ምንጮች አሉ፡፡
መነሻውን ሰሜን ሸዋ እና ደቡብ ወሎ ያደረገው የክርስቲያኑ ሰሎሞናዊ ሥርወ መንግሥት በአካባቢው ያሉ ሕዝቦች ተዋህደው ከ13ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በጋራ የመሠረቱት እንደሆነ አያጠያይቅም፡፡ አማራዎች፤ አርጎባዎች፣ ወርጂዎች፣ ጋፋቶች፣ ጉራጌዎች እና ኦሮሞዎች፣ አፋሮች፣ ሐረሪዎች ወዘተ በዚህ የሸዋ መንግሥታት የተጽዕኖ ምህዳር(Orbit) ውስጥ እንደሚገኙ ዜና መዋእሎች፣ የሃይማኖት ሰነዶች፣ የአርኪዮሎጂ ማስረጃዎች ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፉ የኖሩ የቃል መረጃ ምንጮች ያመለክታሉ፡፡ ለምሳሌ ታደሠ ታምራት(ፕሮፌሠር) ከ13ኛው እስከ 16ኛው ክፍለ ዘመን የቤተ ክርስቲያንና መንግሥትን ግንኙነት ታሪክ ባጠኑበት መጽሐፋቸው የገላንና ያያ ሰዎች ሸዋ ውስጥ በ13ኛው ክፍለ ዘመን በኦዳ ዛፍ (ኮቢል የሚባል ዋርካ) ሥር ሃይማኖታዊ ሥርዓት ይፈጽሙ እንደነበር ገድለ አቡነ ቀውስጦስን ጠቅሰው ጽፈዋል(ገጽ 184)፡፡ ሸዋ የባለ ብዙ ማንነት ሕዝቦች ሀገር ከመሆኗ ባሻገር በ16ኛው ክፍለ ዘመን የተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች ላይ መረጃ የተወልን መነኩሴው አባ ባህሪይ እንደገለጸው “ሸዋ የመንግሥት ሀገር ነች” (ገጽ 130)፡፡ በየዘመናቱ ከሸዋ የተነሱ የፖለቲካ ኃይሎች፣ ፈረሰኛ ሠራዊታቸውን ይዘው በሰሜን እስከ ኤርትራ(በዐጼ ሠርጸ ድንግል ዘመን- የኤርትራዋ ባሬንቱ የዚህ የታሪክ ሂደት ውርስ አይደለችም ማለት አይቻልም፡፡) በምሥራቅ እስከ ዘይላ(ከዐጼ አምደጽዮን እስከ ገላውዲዮስ ዘመን)፣ በምዕራብ እስከ ሱዳን ፋዞግሊ(ዐጼ ሱስንዮስ ዘመን) በደቡብ እስከ ሞያሌ ተንቀሳቅሰው በአገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት ውስጥ ቁልፍ ሚና ተጫተዋል፡፡
እነዚህ የሸዋ እና አካባቢው ሕዝቦችና ገዢዎች ትልቁን ንቅናቄያቸውን ያደረጉት ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ዐጼ ምኒልክና ራስ ጎበና ዳጬ የቱለማ ኦሮሞ፤ የሸዋ አማራ እና የሌሎችም ውህድ የሆነ ጦራቸውን አዝምተው ወሎ ወግተው ወረኢሉን የመንሥታቸው መቀመጫ ያደረጉት አርሲ፣ወለጋ፣ከሐረር ከመዝመታቸው በፊት ነበር፡፡ የመጫ ኦሮሞ ተወላጁን የጎጃሙን ንጉስ ተክለሃይማኖት(አዳል ተሰማ) በቱለማው መሪ ራስ ጎበና ዳጪ እምባቦ ላይ ያስገበሩት የጂኦ ፖለቲካዊ እና የሕዝቦች ትስስር እድሎች ጉልበት ፈጥሮላቸው፤ ኃይል አጎናጽፏቸው እንጂ በአጋጣሚ አይደለም፡፡ በርግጥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የፖለቲካችን ደንቃራነት የፈጠረውን የታሪክ ግርዶሽ ያሸነፉ ፋና ወጊ ጥናቾች መውጣት ጀምረዋል፡፡ አንዱ “Invisible Actors: The Oromo and the Creation of Modern Ethiopia(1855-1913)” በሚል ርዕስ በብሪያን ጀምስ ዬትስ(2002) በኤሊኖይስ ዩኒቨርሲቲ ከተጠናው እጅግ ጠቃሚ የዶክትሬት ዲግሪ ማሟያ ጥናት ሲሆን ሌላው የደቻሳ አበበ(ዶ/ር) ጎበና ወታደራዊና ፖለቲካዊ ሕይወት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው የዘመናዊት ኢትዮጵያን እውን መሆን ያለ ምኒልክና ያለ ጎበና እንደማይታሰብ ሲጠቅሱ ይህንን እውነታ ማጉላታቸው ይመስለኛል፡፡
የሕዝቦች ትስስርና የፖለቲካ ጋብቻ በአማራና በኦሮሞ ሕዝብ መስተጋብር ብቻ የታጠረ አልነበረም-ሊሆንም አይችልም፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ባህልና ሥልጣኔ መጋመዱ ረቂቅ ነው፡፡ ከጥንታዊ አክሱም ዘመን ጀምሮ በዝነኞቹ የአክሱም መቃብር ሀውልቶች እና በላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ላይ ከምናገኛቸው የኪነ ሕንጻ ትእምርቶች(Symbols) መካከል የውሸት በሮች (False Doors) እና የውሸት መስኮቶች(False windows) የሙታን መንፈስ(ኤከራ) መመላለሻ እንደሆኑ በጥናት የተረጋገጠ ነው (ቢትራይስ ፕሌይን Annales d'Éthiopie 1965) ፡፡ ይህ የኤከራዎች መመላለስና የመነጋገር ባህል እና እምነት ከደቡባዊ ግብጽ አንስቶ እስከ ሰሜን ኬንያ ድረስ በሚኖሩ የኩሽ ሕዝቦች በሰፊው የሚታወቅ ረዥም ዘመን ያስቆጠረ ልምምድ ነው፡፡
ሌላው በልኩ ያልተጠና እና በትርክቶቻችን ውስጥ ትኩረት ያልተሰጠው በሕዝቦች መካከል ያለ ሥልጣኔ ትስስር ታሪክ የእያንዳዱን የዛግዌ ነገሥታት የሥልጣን ዘመናትን የተመለከተ ነው፡፡ ከታሪክ ነገሥት፣ ከልዩ ልዩ ዜና መዋዕሎች፣ ከፖርቱጋል ተጓዦች(ፓኤዝና አልሜዳ) ከብሪቲሽ ሙዝየም እንዲሁም ከኮንቲ ሮሲኒ የተገኙት ምንጮች የሚረጋግጡት የሁሉም የዛግዌ ዐጼዎች( ከአንድ ሁለቱ በስተቀር) የሥልጣን ዘመን 40፤40 ዓመታት ነበር፡፡ ይህ ጉዳይ በኦሮሞ የገዳ ሥርዓት የአንድ ትውልድ የሥልጣን ዑደት ጋር አንድ አይነት የሆነው በአጋጣሚ ነው ወይስ ዛግዌዎች እና ኦሮሞዎች የኩሽ ሕዝቦች በመሆናቸው ቀዳሚ ከሆነው የጋራ ሥልጣኔያቸው የሚቀዳ የአስተዳደር ሥርዓት ነው? እነዚህስ ሀቆች የወል ትርክቶቻችን መመሆን አለመቻላቸው በፖለቲካ ደንቃራነት የተፈጠረ የታሪክ ግርዶሽ(eclipse of history) እንጂ ሌላ ምን ሊባል ይችላል? በላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትና እና በሸዋ በሚገኘው የአዳዲ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ኪነሕንጻ መካከል ያለው ፍጹም ተመሳሳይነት ምንጩ ምንድነው? ሊጠና፣ ሊነገር ልንማርበት ይገባል፡፡
በርግጥም ታሪካችን ትዝታችን ላይ የተጫነ ሸክም ሳይሆን የነፍስ መገለጥ ነው የሚያሰኘው የሕዝቦች ትሥሥር፣ ውህደት የሥልጣኔ መጋራትና መወራረስ ታሪክ መታወቁ መንፈስን ሃርነት ማውጣቱ ይመስለኛል፡፡
2 days ago
ከባንኮክ እስከ ፉኬትና ፓታያ ( በወፍ በረር ... )
* ታይላንድ በዓይኔ ያየኋት፣ በእጄ የነካኋት፣ በልቤ የቀረች የባሕር ነፍስ…!
በገብረማርያም ይርጋ [ የጉዞ ማስታወሻ ]
#ethiopia | እውነተኛ ጉዞ የሚጀምረው ሰው ከራሱ ጋር ሲገናኝ ነው። እውነተኛ ጉዞ አውሮፕላኑ ሲያርፍ አያበቃም፤ ትዝታ በልብ ውስጥ ሲቀጥል እንጂ።
ዓለም አቀፍ የባህልና ጥበባት ልማት ሙያዊ ሽልማቴን ለመቀበል ወደ ደቡብ ምስራቅ እስያዋ እንቁ — ታይላንድ — ስጓዝ፣ አእምሮዬን የሞላው የጉዞው ዓላማ ብቻ ነበር።
ነገር ግን እግሬ የታይላንድን ምድር ሲረግጥ የተቀበለኝ የከተማዋ የሲሚንቶና የአስፋልት ግለት ወይም የዘመናዊነት ጫጫታ አልነበረም፤ ከሩቅ የባሕር ጥልቀት እየነፈሰ በፊቴ ላይ እንደ አሮጌ ወዳጅ ቀስ ብሎ የተራመደው ቀዝቃዛ የባሕር ነፋስ እንጂ።
ደቡባዊቷ እንቁ — ፉኬትና የፓታያ ሞገዶች
በውሃው ላይ የተበተኑት ባህላዊ የረጅም ጅራት (Long-tail) ጀልባዎች፣ የፀሐይ ወርቃማ ብርሃን በውሃው ላይ ሲያርፍ የሚፈጥረው ብልጭታ፣ የሰማዩና የባሕሩ አድማስ ላይ መገናኘት… እነዚህ ሁሉ ተደምረው እንደ ተአምራዊ ሕልም ይታዩ ነበር። በዚያ ቅጽበት እኔ ባሕሩን አልተመለከትኩትም፤ ባሕሩ እኔን በጥልቀቱ እየተመለከተኝ ነበር።
በጄትስኪ (Jet Ski) አየርና ውሃውን ሰንጥቄ ስነጥቅ፣ የነጭ አረፋ መስመር ከኋላዬ እንደ ግጥም ይሰመር ነበር። በወቅቱ የተረዳሁት ነገር ቢኖር—ፍጥነት ሰውን ከምድር አያርቀውም፤ ይልቁንም በውስጡ የተሸሸገውን እውነተኛ ደስታ ቅርብ ያደርገዋል!
የሰማይ ላይ በረራ (Parasailing)፦ገመዱ ተለቆ ሰማይ ሲከፈትልኝ፣ ከላይ ሆኜ ስመለከት ባሕሩ እንደ ታላቅ ሰማያዊ መስታወት ተንጣሎ ታየኝ።
በዚያ ከፍታ ላይ ዓለም ትንሽ ስትሆን፣ ሰውን የሚያስጨንቀው የዕለት ተዕለት ጭነቷም አብሮ ትንሽ ይሆናል። እንደ ልጅ ሆኜ የነፋሱን ሹክሹክታ ብቻ እሰማ ነበር… ወጣሁ፣ ተነጠቅሁ!
በፉኬት ነጭ አሸዋው በእግር ስር ሲለሰልስ፣ ግልጽና ሰማያዊው ውሃ እስከ ጉልበት ሲደርስ፣ ፀሐይ በቆዳ ላይ ወርቃማ ሙቀቷን ስትረጭ ዓለምና ጭንቋ ሙሉ በሙሉ የተረሱ ይመስላሉ።
የባንኮክ ድቅቅ ያለ ውበትና የሌሊት ከዋክብት
ባንኮክ በቀን በገዥና ሻጭ፣ በበዛ እንቅስቃሴና ህይወት ስትደምቅ፤ ሌሊት ደግሞ በምድር ላይ እንደወረዱ ከዋክብት የሚያበሩ መብራቶች ያሏት አስማተኛ ከተማ ትሆናለች። የከተማዋ ሰማይ ጠቀስ ህንፃዎች መብራት በውሃው ላይ ሲሰበር፣ ወርቅና አልማዝ በውሃ ላይ የተበተነ ይመስላል።
በቻኦ ፕራያ (Chao Phraya) ወንዝ ላይ ያለ ምሽት
ከጉዞዬ ሁሉ በላይ በልቤ የተቀረፀው በመርከብ ላይ ያሳለፍኩት ምሽት ነው።
የምስራቃዊው የሙዚቃ ዜማ፣ የሰዎች ወዳጃዊ ሳቅ፣ ጣፋጭ እራት…
በወንዙ ላይ እያለፈች ባለው መርከብ ላይ ሆነን በከተማዋ መብራቶች መካከል ስንሳፈፍ፣ በአንድ ቅጽበት ውስጥ ዓለም በሙሉ የተሰበሰበች ያህል ተሰማኝ።
በዚያ ምሽት አንድ ታላቅ እውነት ተረዳሁ—ደስታ ታላቅና ውስብስብ ነገር አይፈልግም፤ በሙሉ ልብ የሚኖር አንድ ቅጽበት ብቻ ይበቃዋል።
በሻንጣ ያልተያዘ፣ በልብ የተያዘ ሀብት
ታይላንድ ከዚህ በኋላ ከእኔ አትጠፋም፤ በውስጤ ዘላለማዊ ቦታዋን ይዛለች። የፓታያ ነፋስ አሁንም በፊቴ ላይ ይነፍሳል፣ የፉኬት ሞገድ በልቤ ይመታል፣ የባንኮክ የሌሊት መብራት በዓይኔ ላይ ይበራል።
ከዚህ ጉዞ ስመለስ በሻንጣዬ ውስጥ ያሸግኩት ያበደሩኝን ልብስ ብቻ አይደለም፤
የሞገዱን ዘላለማዊ ድምፅ፣ ...
የፀሐይዋን አፍቃሪ ሙቀት፣ ...
የአሸዋውን ልስላሴ፣ ...
የሌሊት መብራቶቿን ብሩህነት፣ ...
እና ...
የልቤን ሙሉ ደስታ ነው።
እውነተኛ ጉዞ አውሮፕላኑ ሲያርፍ አይጨርስም፤ ትዝታው በልባችን ውስጥ መኖር ሲቀጥል እንጂ!
ታይላንድ በዓይኔ ያየኋት፣ በእጄ የነካኋት፣ በልቤ የቀረች የባሕር ነፍስ…!
2 days ago
መልካም ጉዞ...
ተፃፈ በመሐሪ ነጋሽ
(የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ኮሚኒኬሽን )
#ethiopia | ዛሬ ማምሻውን የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ልዑክ ቡድናችንን በከፍተኛ ኩራትና በመልካም ምኞት ወደ አሜሪካ ኦሪገን ሸኝተናል።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አትሌቶቻችን በተሟላ ዝግጅት ወደ ሻምፒዮናው እንዲያቀኑ ሱሉልታ በሚገኘው የጀግናው ኦሊምፒያን አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ሆቴል በማሳረፍ አስፈላጊውን ድጋፍ፣ ክትትልና ዝግጅት ሲያደርግ ቆይቷል።
የቀነኒሳ በቀለ ሆቴልም አትሌቶቻችንን እንደቤተሰቦቹ በመቀበል፣ በፍቅር፣ በአክብሮትና በልዩ እንክብካቤ እስከ ሽኝታቸው ድረስ አግዟቸዋል።
ለዚህ ውድ አስተዋፅኦ ከልብ የመነጨ ምስጋና ተቀበሉ
ዓለም የሚጠብቀው ሻምፒዮና 21ኛው የዓለም ከ20 ዓመት በታች (World Athletics U20 Championships) ሻምፒዮና ....
በአሜሪካ ኦሪገን ግዛት ዩጂን ከተማ በሚገኘው ታሪካዊው ሄይዋርድ ፊልድ ከሐምሌ 29 እስከ ነሐሴ 3 ይካሄዳል።
ከ1,700 በላይ ወጣት አትሌቶች ከ190 የሚጠጉ አገራት በ44 የውድድር ዓይነቶች ላይ ይፎካከራሉ።
ዩጂን ከተማ በግምት 180,000 የሚጠጋ ህዝብ ያላት ብትሆንም፣ በዓለም ላይ "Track Town USA" በሚል ስም የምትታወቅ የአትሌቲክስ ዋና መዲና ናት።
የሻምፒዮናው ትኬቶች በፍጥነት እየተሸጡ እንደሆነ አዘጋጆቹ ገልጸዋል፣ ውድድሩም በብዙ የዓለም አቀፍ የቴሌቪዥን ኔትወርኮች፣ ዲጂታል መድረኮች እና በመቶዎች የሚቆጠሩ የስፖርት ጋዜጠኞች ይሸፈናል። የዚህ ውድድር ቀደምት እትሞች በ140 በላይ አገራት በቴሌቪዥን ተሰራጭተው 16 ሚሊዮን በላይ የተጠራቀመ የቲቪ ተመልካች ደርሰው ነበር።
በ2024 በፔሩ ሊማ በተካሄደው 20ኛው ሻምፒዮና ኢትዮጵያ 6 የወርቅ፣ 1 የብር እና 2 የነሐስ ሜዳሊያዎችን በማሸነፍ በአጠቃላይ 9 ሜዳሊያዎችን በመሰብሰብ በዓለም 2ኛ ደረጃን ማስመዝገቧ ይታወሳል።
ዘንድሮም አትሌቶቻችን በ5000 ሜትር፣ 3000 ሜትር፣ 1500 ሜትር፣ 800 ሜትር፣ 3000 ሜትር መሰናክል፣ 400 ሜትር እና በርምጃ ውድድሮች ላይ የኢትዮጵያን ስም በክብር ለማስጠራት ዝግጁ ናቸው።
ለጀግኖቻችን...
ውድ አትሌቶቻችን!
ከእናንተ ጋር የሚጓዘው የኢትዮጵያ 60 ዓመታትን ያስቆጠረ የድል ታሪክ ነው፤ የአበበ ቢቂላ ጨምሮ
የብዙ ጀግኖች የድል አሻራ ነው።
ኢትዮጵያውያን ልብ ከእናንተ ጋር ነው። በእግራችሁ የምትሮጡት ለራሳችሁ ብቻ ሳይሆን ለሀገራችሁ፣ ለሕዝባችሁ እና ለመጪው ትውልድ ነው።
መልካም ጉዞ!
መልካም ውድድር!
መልካም ዕድል! 🇪🇹❤️
ተፃፈ በመሐሪ ነጋሽ
(የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ኮሚኒኬሽን )
#ethiopia | ዛሬ ማምሻውን የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ልዑክ ቡድናችንን በከፍተኛ ኩራትና በመልካም ምኞት ወደ አሜሪካ ኦሪገን ሸኝተናል።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አትሌቶቻችን በተሟላ ዝግጅት ወደ ሻምፒዮናው እንዲያቀኑ ሱሉልታ በሚገኘው የጀግናው ኦሊምፒያን አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ሆቴል በማሳረፍ አስፈላጊውን ድጋፍ፣ ክትትልና ዝግጅት ሲያደርግ ቆይቷል።
የቀነኒሳ በቀለ ሆቴልም አትሌቶቻችንን እንደቤተሰቦቹ በመቀበል፣ በፍቅር፣ በአክብሮትና በልዩ እንክብካቤ እስከ ሽኝታቸው ድረስ አግዟቸዋል።
ለዚህ ውድ አስተዋፅኦ ከልብ የመነጨ ምስጋና ተቀበሉ
ዓለም የሚጠብቀው ሻምፒዮና 21ኛው የዓለም ከ20 ዓመት በታች (World Athletics U20 Championships) ሻምፒዮና ....
በአሜሪካ ኦሪገን ግዛት ዩጂን ከተማ በሚገኘው ታሪካዊው ሄይዋርድ ፊልድ ከሐምሌ 29 እስከ ነሐሴ 3 ይካሄዳል።
ከ1,700 በላይ ወጣት አትሌቶች ከ190 የሚጠጉ አገራት በ44 የውድድር ዓይነቶች ላይ ይፎካከራሉ።
ዩጂን ከተማ በግምት 180,000 የሚጠጋ ህዝብ ያላት ብትሆንም፣ በዓለም ላይ "Track Town USA" በሚል ስም የምትታወቅ የአትሌቲክስ ዋና መዲና ናት።
የሻምፒዮናው ትኬቶች በፍጥነት እየተሸጡ እንደሆነ አዘጋጆቹ ገልጸዋል፣ ውድድሩም በብዙ የዓለም አቀፍ የቴሌቪዥን ኔትወርኮች፣ ዲጂታል መድረኮች እና በመቶዎች የሚቆጠሩ የስፖርት ጋዜጠኞች ይሸፈናል። የዚህ ውድድር ቀደምት እትሞች በ140 በላይ አገራት በቴሌቪዥን ተሰራጭተው 16 ሚሊዮን በላይ የተጠራቀመ የቲቪ ተመልካች ደርሰው ነበር።
በ2024 በፔሩ ሊማ በተካሄደው 20ኛው ሻምፒዮና ኢትዮጵያ 6 የወርቅ፣ 1 የብር እና 2 የነሐስ ሜዳሊያዎችን በማሸነፍ በአጠቃላይ 9 ሜዳሊያዎችን በመሰብሰብ በዓለም 2ኛ ደረጃን ማስመዝገቧ ይታወሳል።
ዘንድሮም አትሌቶቻችን በ5000 ሜትር፣ 3000 ሜትር፣ 1500 ሜትር፣ 800 ሜትር፣ 3000 ሜትር መሰናክል፣ 400 ሜትር እና በርምጃ ውድድሮች ላይ የኢትዮጵያን ስም በክብር ለማስጠራት ዝግጁ ናቸው።
ለጀግኖቻችን...
ውድ አትሌቶቻችን!
ከእናንተ ጋር የሚጓዘው የኢትዮጵያ 60 ዓመታትን ያስቆጠረ የድል ታሪክ ነው፤ የአበበ ቢቂላ ጨምሮ
የብዙ ጀግኖች የድል አሻራ ነው።
ኢትዮጵያውያን ልብ ከእናንተ ጋር ነው። በእግራችሁ የምትሮጡት ለራሳችሁ ብቻ ሳይሆን ለሀገራችሁ፣ ለሕዝባችሁ እና ለመጪው ትውልድ ነው።
መልካም ጉዞ!
መልካም ውድድር!
መልካም ዕድል! 🇪🇹❤️
2 days ago
የቀድሞው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት እና በአሁኑ ወቅት የጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ አማካሪ የሆኑት አቶ ጌታቸው ረዳ፣ የትግራይ ሰራዊት አመራሮችና አባላት በጥቂት የህወሓት ፖለቲከኞች ተገፋፍተው ክልሉን ዳግም ወደ እልቂት ከመክተት እንዲቆጠቡ አሳሰቡ።
አቶ ጌታቸው በኤክስ ገጻቸው የደብረ ጽዮንን ንግግር አያይዘው ባሰራጩት እጅግ ነቀፋ የበዛበት መልእክት፣ የህወሓት አመራሮች የትግራይን ህዝብ አንድነት በመበተን እንዲሁም በፋኖ፣ በሱዳኑ ጄኔራል አል-ቡርሃን እና በኤርትራ መንግስት (ሻዕቢያ) ላይ ተማምነው ዳግም ጦርነት ለመክፈት የሚያደርጉት ፉከራ የሚያመጣው ለውጥ እንደሌለ ገልጸዋል። በዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል፣ በወይዘሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር (ሞንጆሪኖ) እና በቀድሞው የደህንነት ሹም አቶ ጌታቸው አሰፋ መሪነት፣ በጉልበት "አራት ኪሎ እንመለሳለን" በማለት የሚያልሙትን "ቅዠት" በአስቸኳይ እንዲያቆሙ አስጠንቅቀዋል።
ከፌደራል መንግስቱ ጋር በቅርበት እየሰሩ የሚገኙት አቶ ጌታቸው፣ የትግራይ ሰራዊት ከምንም በላይ የህዝቡን ደህንነት እንዲያስቀድም ጥሪ አቅርበዋል። አቅም እያለ የህዝቡን የህልውና ጥያቄዎች መመለስ የሚቻለው በሰላማዊ መንገድ ብቻ መሆኑን በማስገንዘብ፣ ሰራዊቱ በህይወቱና በአካሉ ላይ እየተቆመረበት ያለውን ኃይል 'ይበቃል' ሊለው እንደሚገባ አሳስበዋል።
በመጨረሻም "በሐውልቲ (የህወሓት ጽህፈት ቤት) የመሸገው የብጥብጥ ቡድን" ሲሉ የጠሯቸው እነዚህ አካላት፣ በፉከራና በውጭ ኃይሎች ድጋፍ ላይ በመተማመን የዲፕሎማሲ በሮችን ከዘጉ በኋላ፣ አሁን መሬት ላይ ያለው እውነት ሲከብዳቸው "ዓለም ይድረስልኝ" እያሉ መጮሃቸው ማመዛዘን የጎደለው የፖለቲካ ኪሳራ መሆኑን በአጽንኦት ተችተዋል።
Seledadotio
Seledadotio
አቶ ጌታቸው በኤክስ ገጻቸው የደብረ ጽዮንን ንግግር አያይዘው ባሰራጩት እጅግ ነቀፋ የበዛበት መልእክት፣ የህወሓት አመራሮች የትግራይን ህዝብ አንድነት በመበተን እንዲሁም በፋኖ፣ በሱዳኑ ጄኔራል አል-ቡርሃን እና በኤርትራ መንግስት (ሻዕቢያ) ላይ ተማምነው ዳግም ጦርነት ለመክፈት የሚያደርጉት ፉከራ የሚያመጣው ለውጥ እንደሌለ ገልጸዋል። በዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል፣ በወይዘሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር (ሞንጆሪኖ) እና በቀድሞው የደህንነት ሹም አቶ ጌታቸው አሰፋ መሪነት፣ በጉልበት "አራት ኪሎ እንመለሳለን" በማለት የሚያልሙትን "ቅዠት" በአስቸኳይ እንዲያቆሙ አስጠንቅቀዋል።
ከፌደራል መንግስቱ ጋር በቅርበት እየሰሩ የሚገኙት አቶ ጌታቸው፣ የትግራይ ሰራዊት ከምንም በላይ የህዝቡን ደህንነት እንዲያስቀድም ጥሪ አቅርበዋል። አቅም እያለ የህዝቡን የህልውና ጥያቄዎች መመለስ የሚቻለው በሰላማዊ መንገድ ብቻ መሆኑን በማስገንዘብ፣ ሰራዊቱ በህይወቱና በአካሉ ላይ እየተቆመረበት ያለውን ኃይል 'ይበቃል' ሊለው እንደሚገባ አሳስበዋል።
በመጨረሻም "በሐውልቲ (የህወሓት ጽህፈት ቤት) የመሸገው የብጥብጥ ቡድን" ሲሉ የጠሯቸው እነዚህ አካላት፣ በፉከራና በውጭ ኃይሎች ድጋፍ ላይ በመተማመን የዲፕሎማሲ በሮችን ከዘጉ በኋላ፣ አሁን መሬት ላይ ያለው እውነት ሲከብዳቸው "ዓለም ይድረስልኝ" እያሉ መጮሃቸው ማመዛዘን የጎደለው የፖለቲካ ኪሳራ መሆኑን በአጽንኦት ተችተዋል።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
3 days ago
የአቡነ ሀብተ ማርያም ምልጃ እና ረድኤት አይለየን🙏
በምጽዋትና በስገድት የምትጋደለው እናቱ ዮስቴና ሀብቷን ሁሉ ለድሆች ሰጥታ ለምናኔ ወደ በረኃ ሄደች።
በዚያ ያገኘችው ባሕታዊም በመንፈስ ቅዱስ ተገልጦለት ከእርሷ ቅዱስ ፍሬ እንደሚወጣ ነግሮ ወደ ዓለም እንድትመለስ አዘዛት። እርሷም “እግዚአብሔር የወደደው ይሁን” ብላ እያመሰገነች ተመልሰች፡፡ የአባቱ የትውልድ ሀገር የራውዕይ በምትባል ሀገር ሲሆን ከዚህች የተባረከች ሴት ጋር ተጋባ። እርሷም በበጎ ምግባርና ሥራ የተጌጠች፣ በሕግ ተወስና በጾም፣ በጸሎት፣ የምትተጋ ነበረች።
ከጥቂት ጊዜያት በኋላም ወንድ ልጅ ወለደች። እንደ ሥርዓቱም ሲጠመቅ የመጽሐፍ ስሙን “ሀብተ ማርያም” አሉት። በሕገ እግዚአብሔር አንጸው አሳደጉት። ወደ ቤተ ክርስቲያንም ሲወስዱት “እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ” የሚለውን ጸሎት ቢሰማ እጅጉን ወደዳት። እርሷንም ይዞ ከቤቱ ሌሊቱን የሚጸልይና የሚጋደል ሆነ።
አንድ ቀን የአባቱ በጎቹን ሲጠብቅ የበግ ጠባቂዎቹን “ዛሬ ዝናም ይዘንማልና እንግባ” አላቸው። እነርሱም “ምን ደመና አለ፤ ቀኑ ብራ ነው” አሉት። እርሱ ግን በጎቹን ይዞ ወደ ቤቱ እንደገባ ኃይለኛ፣ ነፋስና መብረቅ የቀላቀለ ዝናም ዘነመ። በሌላም ጊዜ እንዲሁ አንድ እረኛ የሀብተ ማርያምን በትሩን በጉልበት ነጠቀው። “መልስልኝ” ብሎ በስመ እግዚአብሔር ቢያምለውም እምቢ አለው። በተወው ጊዜ እግዚአብሔር ያን እረኛ በአየር ላይ ሠቅ ሎ አዋለው። እረኞቹም ሀብተ ማርያምን ሲለምኑት፣ እግዚአብሔር ነውና ስለ ስሙ ብሎ የቀጣው መሐሪው እርሱ ከወደደ ይማረው ሲል ያ እረኛ ተፈታና ወረደ። መጥቶም ከአባታችን እግር ስር ወደቀ፡፡ በኋላም ስሟ እለ አድባር ወደምትባል ገዳም ገብቶ ከአባ መልከ ጼዴቅ እጅ መነኰሶ ታላቅ ተጋድሎ ይጋደል ጀመር። በባሕር መካከልም በመቆም መዝሙረ ዳዊትን ይደግምና ግንባሩም የባሕሩን አሸዋ እስኪነካ 500 ጊዜ ይሰግዳል።
እህልም መቅመስን ትቶ የዱር ቅጠል የሚመገብ ሆነ። ዐርባ ዐርባ፣ ሰማንያ ሰማንያ ቀንም ያከፍላል። በሌሊትም ቁሞ በማደር በቀንም አራቱን ወንጌላት ዘወትር ይጸልያል። ተጋድሎውንም ያየ አምላካችን ተገለጠለት። አባ ሀብተ ማርያምም ከግርማው የተነሣ ደንግጦ በግንባሩ ተደፋ። ጌታችንም እፍ ብሉ አጽናንቶ አሥነሳውና ጽኑዕ ተጋድሎው በሰማያት መጻፉን ነገረው፡፡ ስለ ድንግልናው፣ ስለ ምናኔው፣ ስለ ፍጹም ምንኲስናው፣ አራቱን ወንጌላት አዘውትሮ በማንበቡ፣ ረኃብና ጥምን በመታገሡ፣ በልቡ ቂምንና በቀልን ባለማኖሩ፣ ስለ ንጹሕ የክህነት አገልግሎቱና በንጽሕና ስለሚያሣርገው መሥዋዕቱ ሰባት እጅግ የሚያስደንቁ አክሊላትንም አቀዳጀው። የቅዱስ ማቴዎስንና የቅዱስ ማርቆስን ወንጌል ሲያነብ ከሌሎች ሥውራን አበው ጋር የሚገናኝበትን የብርሃን ሠረገላ ሰጠው፡፡
የቅዱስ ሉቃስንና የቅዱስ ዮሐንስን ወንጌል ሲያነብም ሥጋውን ደሙን ለመቀበል ወደ ኢየሩሳሌም የሚሄድበትን የእሳት ሠረገላ ሰጠውና ቃል ኪዳን ገባለት። መታሰቢያውን ለሚያደርጉና በስሙ ለሚዘክሩ፣ ከእነርሱ ጋር የሚኖርበትን አምስት መቶ የወርቅ አምዶች ያሏትን ቦታ ሰጠሁህ አለው። ቅዱሳን መላእክት ሁሉ እየተደሰቱ አባታችን አቡነ ሐብተ ማርያምን “ወንድማችን ወደማያልቀው ሰማያዊ ደስታ ልንወስድህ መጥተናል” አሉት። ይህንንም በተናገረ ጊዜ ጌታችን በሦስትነቱ ተገልጦ ታየው። በኅዳር 26 ቀን ነፍሱ ከሥጋው በሰላም ተለየች።
ቅዱሳን መላእክትም በታላቅ ደስታ እያመሰገኑ አሣረጓት። ገዳማውያን የዓለምን ክብር ንቀው ሔደዋልና ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፡፡ በዓታቸውን እናጽና ገዳማቸውን እንደግፍ የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
በምጽዋትና በስገድት የምትጋደለው እናቱ ዮስቴና ሀብቷን ሁሉ ለድሆች ሰጥታ ለምናኔ ወደ በረኃ ሄደች።
በዚያ ያገኘችው ባሕታዊም በመንፈስ ቅዱስ ተገልጦለት ከእርሷ ቅዱስ ፍሬ እንደሚወጣ ነግሮ ወደ ዓለም እንድትመለስ አዘዛት። እርሷም “እግዚአብሔር የወደደው ይሁን” ብላ እያመሰገነች ተመልሰች፡፡ የአባቱ የትውልድ ሀገር የራውዕይ በምትባል ሀገር ሲሆን ከዚህች የተባረከች ሴት ጋር ተጋባ። እርሷም በበጎ ምግባርና ሥራ የተጌጠች፣ በሕግ ተወስና በጾም፣ በጸሎት፣ የምትተጋ ነበረች።
ከጥቂት ጊዜያት በኋላም ወንድ ልጅ ወለደች። እንደ ሥርዓቱም ሲጠመቅ የመጽሐፍ ስሙን “ሀብተ ማርያም” አሉት። በሕገ እግዚአብሔር አንጸው አሳደጉት። ወደ ቤተ ክርስቲያንም ሲወስዱት “እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ” የሚለውን ጸሎት ቢሰማ እጅጉን ወደዳት። እርሷንም ይዞ ከቤቱ ሌሊቱን የሚጸልይና የሚጋደል ሆነ።
አንድ ቀን የአባቱ በጎቹን ሲጠብቅ የበግ ጠባቂዎቹን “ዛሬ ዝናም ይዘንማልና እንግባ” አላቸው። እነርሱም “ምን ደመና አለ፤ ቀኑ ብራ ነው” አሉት። እርሱ ግን በጎቹን ይዞ ወደ ቤቱ እንደገባ ኃይለኛ፣ ነፋስና መብረቅ የቀላቀለ ዝናም ዘነመ። በሌላም ጊዜ እንዲሁ አንድ እረኛ የሀብተ ማርያምን በትሩን በጉልበት ነጠቀው። “መልስልኝ” ብሎ በስመ እግዚአብሔር ቢያምለውም እምቢ አለው። በተወው ጊዜ እግዚአብሔር ያን እረኛ በአየር ላይ ሠቅ ሎ አዋለው። እረኞቹም ሀብተ ማርያምን ሲለምኑት፣ እግዚአብሔር ነውና ስለ ስሙ ብሎ የቀጣው መሐሪው እርሱ ከወደደ ይማረው ሲል ያ እረኛ ተፈታና ወረደ። መጥቶም ከአባታችን እግር ስር ወደቀ፡፡ በኋላም ስሟ እለ አድባር ወደምትባል ገዳም ገብቶ ከአባ መልከ ጼዴቅ እጅ መነኰሶ ታላቅ ተጋድሎ ይጋደል ጀመር። በባሕር መካከልም በመቆም መዝሙረ ዳዊትን ይደግምና ግንባሩም የባሕሩን አሸዋ እስኪነካ 500 ጊዜ ይሰግዳል።
እህልም መቅመስን ትቶ የዱር ቅጠል የሚመገብ ሆነ። ዐርባ ዐርባ፣ ሰማንያ ሰማንያ ቀንም ያከፍላል። በሌሊትም ቁሞ በማደር በቀንም አራቱን ወንጌላት ዘወትር ይጸልያል። ተጋድሎውንም ያየ አምላካችን ተገለጠለት። አባ ሀብተ ማርያምም ከግርማው የተነሣ ደንግጦ በግንባሩ ተደፋ። ጌታችንም እፍ ብሉ አጽናንቶ አሥነሳውና ጽኑዕ ተጋድሎው በሰማያት መጻፉን ነገረው፡፡ ስለ ድንግልናው፣ ስለ ምናኔው፣ ስለ ፍጹም ምንኲስናው፣ አራቱን ወንጌላት አዘውትሮ በማንበቡ፣ ረኃብና ጥምን በመታገሡ፣ በልቡ ቂምንና በቀልን ባለማኖሩ፣ ስለ ንጹሕ የክህነት አገልግሎቱና በንጽሕና ስለሚያሣርገው መሥዋዕቱ ሰባት እጅግ የሚያስደንቁ አክሊላትንም አቀዳጀው። የቅዱስ ማቴዎስንና የቅዱስ ማርቆስን ወንጌል ሲያነብ ከሌሎች ሥውራን አበው ጋር የሚገናኝበትን የብርሃን ሠረገላ ሰጠው፡፡
የቅዱስ ሉቃስንና የቅዱስ ዮሐንስን ወንጌል ሲያነብም ሥጋውን ደሙን ለመቀበል ወደ ኢየሩሳሌም የሚሄድበትን የእሳት ሠረገላ ሰጠውና ቃል ኪዳን ገባለት። መታሰቢያውን ለሚያደርጉና በስሙ ለሚዘክሩ፣ ከእነርሱ ጋር የሚኖርበትን አምስት መቶ የወርቅ አምዶች ያሏትን ቦታ ሰጠሁህ አለው። ቅዱሳን መላእክት ሁሉ እየተደሰቱ አባታችን አቡነ ሐብተ ማርያምን “ወንድማችን ወደማያልቀው ሰማያዊ ደስታ ልንወስድህ መጥተናል” አሉት። ይህንንም በተናገረ ጊዜ ጌታችን በሦስትነቱ ተገልጦ ታየው። በኅዳር 26 ቀን ነፍሱ ከሥጋው በሰላም ተለየች።
ቅዱሳን መላእክትም በታላቅ ደስታ እያመሰገኑ አሣረጓት። ገዳማውያን የዓለምን ክብር ንቀው ሔደዋልና ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፡፡ በዓታቸውን እናጽና ገዳማቸውን እንደግፍ የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
3 days ago
የአቡነ ሀብተ ማርያም ምልጃ እና ረድኤት አይለየን🙏
በምጽዋትና በስገድት የምትጋደለው እናቱ ዮስቴና ሀብቷን ሁሉ ለድሆች ሰጥታ ለምናኔ ወደ በረኃ ሄደች።
በዚያ ያገኘችው ባሕታዊም በመንፈስ ቅዱስ ተገልጦለት ከእርሷ ቅዱስ ፍሬ እንደሚወጣ ነግሮ ወደ ዓለም እንድትመለስ አዘዛት። እርሷም “እግዚአብሔር የወደደው ይሁን” ብላ እያመሰገነች ተመልሰች፡፡ የአባቱ የትውልድ ሀገር የራውዕይ በምትባል ሀገር ሲሆን ከዚህች የተባረከች ሴት ጋር ተጋባ። እርሷም በበጎ ምግባርና ሥራ የተጌጠች፣ በሕግ ተወስና በጾም፣ በጸሎት፣ የምትተጋ ነበረች።
ከጥቂት ጊዜያት በኋላም ወንድ ልጅ ወለደች። እንደ ሥርዓቱም ሲጠመቅ የመጽሐፍ ስሙን “ሀብተ ማርያም” አሉት። በሕገ እግዚአብሔር አንጸው አሳደጉት። ወደ ቤተ ክርስቲያንም ሲወስዱት “እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ” የሚለውን ጸሎት ቢሰማ እጅጉን ወደዳት። እርሷንም ይዞ ከቤቱ ሌሊቱን የሚጸልይና የሚጋደል ሆነ።
አንድ ቀን የአባቱ በጎቹን ሲጠብቅ የበግ ጠባቂዎቹን “ዛሬ ዝናም ይዘንማልና እንግባ” አላቸው። እነርሱም “ምን ደመና አለ፤ ቀኑ ብራ ነው” አሉት። እርሱ ግን በጎቹን ይዞ ወደ ቤቱ እንደገባ ኃይለኛ፣ ነፋስና መብረቅ የቀላቀለ ዝናም ዘነመ። በሌላም ጊዜ እንዲሁ አንድ እረኛ የሀብተ ማርያምን በትሩን በጉልበት ነጠቀው። “መልስልኝ” ብሎ በስመ እግዚአብሔር ቢያምለውም እምቢ አለው። በተወው ጊዜ እግዚአብሔር ያን እረኛ በአየር ላይ ሠቅሎ አዋለው። እረኞቹም ሀብተ ማርያምን ሲለምኑት፣ እግዚአብሔር ነውና ስለ ስሙ ብሎ የቀጣው መሐሪው እርሱ ከወደደ ይማረው ሲል ያ እረኛ ተፈታና ወረደ። መጥቶም ከአባታችን እግር ስር ወደቀ፡፡ በኋላም ስሟ እለ አድባር ወደምትባል ገዳም ገብቶ ከአባ መልከ ጼዴቅ እጅ መነኰሶ ታላቅ ተጋድሎ ይጋደል ጀመር። በባሕር መካከልም በመቆም መዝሙረ ዳዊትን ይደግምና ግንባሩም የባሕሩን አሸዋ እስኪነካ 500 ጊዜ ይሰግዳል።
እህልም መቅመስን ትቶ የዱር ቅጠል የሚመገብ ሆነ። ዐርባ ዐርባ፣ ሰማንያ ሰማንያ ቀንም ያከፍላል። በሌሊትም ቁሞ በማደር በቀንም አራቱን ወንጌላት ዘወትር ይጸልያል። ተጋድሎውንም ያየ አምላካችን ተገለጠለት። አባ ሀብተ ማርያምም ከግርማው የተነሣ ደንግጦ በግንባሩ ተደፋ። ጌታችንም እፍ ብሉ አጽናንቶ አሥነሳውና ጽኑዕ ተጋድሎው በሰማያት መጻፉን ነገረው፡፡ ስለ ድንግልናው፣ ስለ ምናኔው፣ ስለ ፍጹም ምንኲስናው፣ አራቱን ወንጌላት አዘውትሮ በማንበቡ፣ ረኃብና ጥምን በመታገሡ፣ በልቡ ቂምንና በቀልን ባለማኖሩ፣ ስለ ንጹሕ የክህነት አገልግሎቱና በንጽሕና ስለሚያሣርገው መሥዋዕቱ ሰባት እጅግ የሚያስደንቁ አክሊላትንም አቀዳጀው። የቅዱስ ማቴዎስንና የቅዱስ ማርቆስን ወንጌል ሲያነብ ከሌሎች ሥውራን አበው ጋር የሚገናኝበትን የብርሃን ሠረገላ ሰጠው፡፡
የቅዱስ ሉቃስንና የቅዱስ ዮሐንስን ወንጌል ሲያነብም ሥጋውን ደሙን ለመቀበል ወደ ኢየሩሳሌም የሚሄድበትን የእሳት ሠረገላ ሰጠውና ቃል ኪዳን ገባለት። መታሰቢያውን ለሚያደርጉና በስሙ ለሚዘክሩ፣ ከእነርሱ ጋር የሚኖርበትን አምስት መቶ የወርቅ አምዶች ያሏትን ቦታ ሰጠሁህ አለው። ቅዱሳን መላእክት ሁሉ እየተደሰቱ አባታችን አቡነ ሐብተ ማርያምን “ወንድማችን ወደማያልቀው ሰማያዊ ደስታ ልንወስድህ መጥተናል” አሉት። ይህንንም በተናገረ ጊዜ ጌታችን በሦስትነቱ ተገልጦ ታየው። በኅዳር 26 ቀን ነፍሱ ከሥጋው በሰላም ተለየች።
ቅዱሳን መላእክትም በታላቅ ደስታ እያመሰገኑ አሣረጓት። ገዳማውያን የዓለምን ክብር ንቀው ሔደዋልና ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፡፡ በዓታቸውን እናጽና ገዳማቸውን እንደግፍ የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
በምጽዋትና በስገድት የምትጋደለው እናቱ ዮስቴና ሀብቷን ሁሉ ለድሆች ሰጥታ ለምናኔ ወደ በረኃ ሄደች።
በዚያ ያገኘችው ባሕታዊም በመንፈስ ቅዱስ ተገልጦለት ከእርሷ ቅዱስ ፍሬ እንደሚወጣ ነግሮ ወደ ዓለም እንድትመለስ አዘዛት። እርሷም “እግዚአብሔር የወደደው ይሁን” ብላ እያመሰገነች ተመልሰች፡፡ የአባቱ የትውልድ ሀገር የራውዕይ በምትባል ሀገር ሲሆን ከዚህች የተባረከች ሴት ጋር ተጋባ። እርሷም በበጎ ምግባርና ሥራ የተጌጠች፣ በሕግ ተወስና በጾም፣ በጸሎት፣ የምትተጋ ነበረች።
ከጥቂት ጊዜያት በኋላም ወንድ ልጅ ወለደች። እንደ ሥርዓቱም ሲጠመቅ የመጽሐፍ ስሙን “ሀብተ ማርያም” አሉት። በሕገ እግዚአብሔር አንጸው አሳደጉት። ወደ ቤተ ክርስቲያንም ሲወስዱት “እግዚኦ መሐረነ ክርስቶስ” የሚለውን ጸሎት ቢሰማ እጅጉን ወደዳት። እርሷንም ይዞ ከቤቱ ሌሊቱን የሚጸልይና የሚጋደል ሆነ።
አንድ ቀን የአባቱ በጎቹን ሲጠብቅ የበግ ጠባቂዎቹን “ዛሬ ዝናም ይዘንማልና እንግባ” አላቸው። እነርሱም “ምን ደመና አለ፤ ቀኑ ብራ ነው” አሉት። እርሱ ግን በጎቹን ይዞ ወደ ቤቱ እንደገባ ኃይለኛ፣ ነፋስና መብረቅ የቀላቀለ ዝናም ዘነመ። በሌላም ጊዜ እንዲሁ አንድ እረኛ የሀብተ ማርያምን በትሩን በጉልበት ነጠቀው። “መልስልኝ” ብሎ በስመ እግዚአብሔር ቢያምለውም እምቢ አለው። በተወው ጊዜ እግዚአብሔር ያን እረኛ በአየር ላይ ሠቅሎ አዋለው። እረኞቹም ሀብተ ማርያምን ሲለምኑት፣ እግዚአብሔር ነውና ስለ ስሙ ብሎ የቀጣው መሐሪው እርሱ ከወደደ ይማረው ሲል ያ እረኛ ተፈታና ወረደ። መጥቶም ከአባታችን እግር ስር ወደቀ፡፡ በኋላም ስሟ እለ አድባር ወደምትባል ገዳም ገብቶ ከአባ መልከ ጼዴቅ እጅ መነኰሶ ታላቅ ተጋድሎ ይጋደል ጀመር። በባሕር መካከልም በመቆም መዝሙረ ዳዊትን ይደግምና ግንባሩም የባሕሩን አሸዋ እስኪነካ 500 ጊዜ ይሰግዳል።
እህልም መቅመስን ትቶ የዱር ቅጠል የሚመገብ ሆነ። ዐርባ ዐርባ፣ ሰማንያ ሰማንያ ቀንም ያከፍላል። በሌሊትም ቁሞ በማደር በቀንም አራቱን ወንጌላት ዘወትር ይጸልያል። ተጋድሎውንም ያየ አምላካችን ተገለጠለት። አባ ሀብተ ማርያምም ከግርማው የተነሣ ደንግጦ በግንባሩ ተደፋ። ጌታችንም እፍ ብሉ አጽናንቶ አሥነሳውና ጽኑዕ ተጋድሎው በሰማያት መጻፉን ነገረው፡፡ ስለ ድንግልናው፣ ስለ ምናኔው፣ ስለ ፍጹም ምንኲስናው፣ አራቱን ወንጌላት አዘውትሮ በማንበቡ፣ ረኃብና ጥምን በመታገሡ፣ በልቡ ቂምንና በቀልን ባለማኖሩ፣ ስለ ንጹሕ የክህነት አገልግሎቱና በንጽሕና ስለሚያሣርገው መሥዋዕቱ ሰባት እጅግ የሚያስደንቁ አክሊላትንም አቀዳጀው። የቅዱስ ማቴዎስንና የቅዱስ ማርቆስን ወንጌል ሲያነብ ከሌሎች ሥውራን አበው ጋር የሚገናኝበትን የብርሃን ሠረገላ ሰጠው፡፡
የቅዱስ ሉቃስንና የቅዱስ ዮሐንስን ወንጌል ሲያነብም ሥጋውን ደሙን ለመቀበል ወደ ኢየሩሳሌም የሚሄድበትን የእሳት ሠረገላ ሰጠውና ቃል ኪዳን ገባለት። መታሰቢያውን ለሚያደርጉና በስሙ ለሚዘክሩ፣ ከእነርሱ ጋር የሚኖርበትን አምስት መቶ የወርቅ አምዶች ያሏትን ቦታ ሰጠሁህ አለው። ቅዱሳን መላእክት ሁሉ እየተደሰቱ አባታችን አቡነ ሐብተ ማርያምን “ወንድማችን ወደማያልቀው ሰማያዊ ደስታ ልንወስድህ መጥተናል” አሉት። ይህንንም በተናገረ ጊዜ ጌታችን በሦስትነቱ ተገልጦ ታየው። በኅዳር 26 ቀን ነፍሱ ከሥጋው በሰላም ተለየች።
ቅዱሳን መላእክትም በታላቅ ደስታ እያመሰገኑ አሣረጓት። ገዳማውያን የዓለምን ክብር ንቀው ሔደዋልና ጸሎታቸው ኃይልን ታደርጋለች፡፡ በዓታቸውን እናጽና ገዳማቸውን እንደግፍ የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
3 days ago
የቆማ ፋሲለደስ (ደብረ አንፆኪያ) ቤተክርስቲያን – የታሪክ፣ የእምነትና የቅርስ መዲና
#ethiopia | በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ዞን በእስቴ ወረዳ፣ ከእስቴ ከተማ በ52 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘው የቆማ ፋሲለደስ (ደብረ አንፆኪያ) ቤተክርስቲያን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ታሪክ ውስጥ ከፍተኛ ስፍራ ያላት ጥንታዊ የእምነትና የባህል ማዕከል ናት።
ደብሩ በ1597 ዓ.ም. በእቴጌ ወልደ ሳህላ፣ የአፄ ሱስኒዮስ (ስልጣን ሰገድ) ባለቤት ተመሠረተ። በኋላም አፄ ፋሲለደስ በንግሥናቸው ስምንተኛ ዓመት በእናታቸው አሳሳቢነት ደብሩን በ«ርዕሰ አድባራት ወገዳማት» ማዕረግ በማክበር ከፍተኛ መንፈሳዊ ሥልጣንና ክብር ሰጥተውታል።
ቤተክርስቲያኑ በክብ ቅርጽ የተገነባ ሲሆን፣ በ26 ዓምደ ወርቅ የተደገፈና በቀይ ድንጋይ (ቦዝ) የተሠራ ውብ ሕንፃ ነው። በቅፅሩ ውስጥ የትምህርት ቤት፣ ጉባኤ ቤት፣ እንዲሁም በፋሲል ግንብ አቀማመጥ የተሠራ የዕቃ ቤትና የደወል ማማ ይገኛሉ።
የደብሩ አስተዳደራዊና ሥርዓተ አገልግሎት በ318 ሊቃውንት የተዋቀረ ሲሆን፣ መምህራን፣ ሊቃውንት፣ መርጌታዎች፣ መነኮሳት፣ ደብተራዎችና ሌሎች በርካታ አገልጋዮችን ያካተተ ሥርዓት ነበረው።
ደብሩ በተለይ በ«ቆሜ ፀዋት ዜማ» ይታወቃል። ይህ ዜማ ከቅዱስ ያሬድ የወረሰ ጥንታዊ የቅዳሴ ዜማ መሆኑ ይነገራል። በዮዲትና በአህመድ ግራኝ ዘመን ብዙ ቤተክርስቲያናት በተጎዱበት ወቅትም ይህ የያሬድ ዜማ በደብሩ ሳይቀየር እስከ ዛሬ መጠበቁ የቤተክርስቲያኑ ልዩ መለያ ነው።
የቆማ ፋሲለደስ ቤተክርስቲያን በውስጧ ከወርቅ፣ ከብር፣ ከእብነበረድና ከሌሎች ውድ ማዕድናት የተሠሩ ንዋያተ ቅድሳትን የያዘች ሲሆን፣ ለእስቴ ወረዳ፣ ለአማራ ክልል እና ለመላው ኢትዮጵያ ጠቃሚ የታሪክ፣ የሃይማኖትና የቱሪዝም መዳረሻ ሆና ትገኛለች።
የእስቴ ወረዳ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ጽሕፈት ቤት
#ethiopia | በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ዞን በእስቴ ወረዳ፣ ከእስቴ ከተማ በ52 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘው የቆማ ፋሲለደስ (ደብረ አንፆኪያ) ቤተክርስቲያን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ታሪክ ውስጥ ከፍተኛ ስፍራ ያላት ጥንታዊ የእምነትና የባህል ማዕከል ናት።
ደብሩ በ1597 ዓ.ም. በእቴጌ ወልደ ሳህላ፣ የአፄ ሱስኒዮስ (ስልጣን ሰገድ) ባለቤት ተመሠረተ። በኋላም አፄ ፋሲለደስ በንግሥናቸው ስምንተኛ ዓመት በእናታቸው አሳሳቢነት ደብሩን በ«ርዕሰ አድባራት ወገዳማት» ማዕረግ በማክበር ከፍተኛ መንፈሳዊ ሥልጣንና ክብር ሰጥተውታል።
ቤተክርስቲያኑ በክብ ቅርጽ የተገነባ ሲሆን፣ በ26 ዓምደ ወርቅ የተደገፈና በቀይ ድንጋይ (ቦዝ) የተሠራ ውብ ሕንፃ ነው። በቅፅሩ ውስጥ የትምህርት ቤት፣ ጉባኤ ቤት፣ እንዲሁም በፋሲል ግንብ አቀማመጥ የተሠራ የዕቃ ቤትና የደወል ማማ ይገኛሉ።
የደብሩ አስተዳደራዊና ሥርዓተ አገልግሎት በ318 ሊቃውንት የተዋቀረ ሲሆን፣ መምህራን፣ ሊቃውንት፣ መርጌታዎች፣ መነኮሳት፣ ደብተራዎችና ሌሎች በርካታ አገልጋዮችን ያካተተ ሥርዓት ነበረው።
ደብሩ በተለይ በ«ቆሜ ፀዋት ዜማ» ይታወቃል። ይህ ዜማ ከቅዱስ ያሬድ የወረሰ ጥንታዊ የቅዳሴ ዜማ መሆኑ ይነገራል። በዮዲትና በአህመድ ግራኝ ዘመን ብዙ ቤተክርስቲያናት በተጎዱበት ወቅትም ይህ የያሬድ ዜማ በደብሩ ሳይቀየር እስከ ዛሬ መጠበቁ የቤተክርስቲያኑ ልዩ መለያ ነው።
የቆማ ፋሲለደስ ቤተክርስቲያን በውስጧ ከወርቅ፣ ከብር፣ ከእብነበረድና ከሌሎች ውድ ማዕድናት የተሠሩ ንዋያተ ቅድሳትን የያዘች ሲሆን፣ ለእስቴ ወረዳ፣ ለአማራ ክልል እና ለመላው ኢትዮጵያ ጠቃሚ የታሪክ፣ የሃይማኖትና የቱሪዝም መዳረሻ ሆና ትገኛለች።
የእስቴ ወረዳ ባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ጽሕፈት ቤት
3 days ago
ከወርቅ በእጅጉ ውድ የሆነ አዲስ ማዕድን በሩሲያ ተገኘ? ሳይንቲስቶች ምን አገኙ?
#ethiopia | ሞስኮ – በሩሲያ ሰሜን ምዕራብ በሚገኘው የኮላ (Kola) ባሕረ-ገብ መሬት የኪቢኒ (Khibiny) ተራራ አካባቢ የሚገኘው የኪሮቭስኪ ማዕድን ማውጫ ውስጥ የሩሲያ ተመራማሪዎች ከቀድሞው የአሽክሮፍታይን (Ashcroftine) ቤተሰብ ጋር የተያያዘ አዲስ የማዕድን ዓይነት መለየታቸው በሳይንስ ዓለም ትልቅ ትኩረት ስቧል።
ይህ አዲሱ ማዕድን በጊዜያዊነት “Kola Ashcroftine” በሚል ስያሜ እየተጠራ ሲሆን ከታዋቂው Ashcroftine-(Y) የተለየ ክሪስታል መዋቅር እንዳለው የሳይንሳዊ ጥናቶች ያመለክታሉ።
የሩሲያ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር እንደገለጸው፣ ማዕድኑ የኢትሪየም (Yttrium)፣ ሲሊከን፣ ፖታሲየም፣ ሶዲየም፣ ካልሲየም፣ ማንጋኒዝ እና ፍሎሪንን ጨምሮ በርካታ ንጥረ ነገሮችን የያዘ እጅግ ውስብስብ የሲሊኬት ማዕድን ነው።
በነጠላ ክሪስታል ኤክስሬይ ትንተና የተደረገበት ጥናትም ይህ ዓይነት ክሪስታል በውስጡ የናኖ ቱቦችን (nanotubules) የያዘ ልዩ መዋቅር እንዳለው አረጋግጧል።
በማኅበራዊ ሚዲያ የተሰራጨው "በ1 ሚሊሜትር 145 ዶላር ይሸጣል" ወይም "ከወርቅ በእጅጉ ይበልጣል" የሚለው መረጃ ግን በአሁኑ ጊዜ በታተሙ ሳይንሳዊ ጥናቶች ወይም በዓለም የማዕድን ገበያ መረጃዎች የተረጋገጠ አይደለም።
ባለሙያዎች ይህ ግኝት የሳይንስ እና የማዕድን ጥናት እሴት እንዳለው ቢገልጹም፣ የንግድ ዋጋው ገና በግልጽ መልኩ አልተወሰነም።
የኪቢኒ ተራራ እና የኮላ ባሕረ-ገብ መሬት በዓለም ላይ በብዙ ብርቅዬ ማዕድናት የሚታወቅ ክልል ነው። በዚህ አካባቢ ከመቶዎች በላይ አዳዲስ ማዕድናት ተገኝተዋል፤ ከእነዚህም ብዙዎቹ በሌላ የዓለም ክፍል አይገኙም።
ክልሉ በተለይ በሬር አርዝ (Rare Earth Elements) ማዕድናት ምክንያት ለሳይንስና ለከፍተኛ ቴክኖሎጂ ኢንዱስትሪ ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው።
ባለሙያዎች እንደሚሉት፣ እንዲህ ዓይነት አዲስ ማዕድናት መገኘታቸው የምድር አፈጣጠርን ለመረዳት፣ አዳዲስ ቁሶችን ለማዘጋጀት እና በወደፊት በኤሌክትሮኒክስ፣ በኃይል ቴክኖሎጂና በሌሎች የኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ አዳዲስ አጠቃቀሞችን ለማስገኘት የሚያስችሉ ናቸው።
ሆኖም ይህ ማዕድን በንግድ ደረጃ መመረት ወይም በስፋት መጠቀም ይቻል እንደሆነ ለመወሰን ተጨማሪ የምርምር ሥራዎች እንደሚያስፈልጉ ተገልጿል።
#ethiopia | ሞስኮ – በሩሲያ ሰሜን ምዕራብ በሚገኘው የኮላ (Kola) ባሕረ-ገብ መሬት የኪቢኒ (Khibiny) ተራራ አካባቢ የሚገኘው የኪሮቭስኪ ማዕድን ማውጫ ውስጥ የሩሲያ ተመራማሪዎች ከቀድሞው የአሽክሮፍታይን (Ashcroftine) ቤተሰብ ጋር የተያያዘ አዲስ የማዕድን ዓይነት መለየታቸው በሳይንስ ዓለም ትልቅ ትኩረት ስቧል።
ይህ አዲሱ ማዕድን በጊዜያዊነት “Kola Ashcroftine” በሚል ስያሜ እየተጠራ ሲሆን ከታዋቂው Ashcroftine-(Y) የተለየ ክሪስታል መዋቅር እንዳለው የሳይንሳዊ ጥናቶች ያመለክታሉ።
የሩሲያ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር እንደገለጸው፣ ማዕድኑ የኢትሪየም (Yttrium)፣ ሲሊከን፣ ፖታሲየም፣ ሶዲየም፣ ካልሲየም፣ ማንጋኒዝ እና ፍሎሪንን ጨምሮ በርካታ ንጥረ ነገሮችን የያዘ እጅግ ውስብስብ የሲሊኬት ማዕድን ነው።
በነጠላ ክሪስታል ኤክስሬይ ትንተና የተደረገበት ጥናትም ይህ ዓይነት ክሪስታል በውስጡ የናኖ ቱቦችን (nanotubules) የያዘ ልዩ መዋቅር እንዳለው አረጋግጧል።
በማኅበራዊ ሚዲያ የተሰራጨው "በ1 ሚሊሜትር 145 ዶላር ይሸጣል" ወይም "ከወርቅ በእጅጉ ይበልጣል" የሚለው መረጃ ግን በአሁኑ ጊዜ በታተሙ ሳይንሳዊ ጥናቶች ወይም በዓለም የማዕድን ገበያ መረጃዎች የተረጋገጠ አይደለም።
ባለሙያዎች ይህ ግኝት የሳይንስ እና የማዕድን ጥናት እሴት እንዳለው ቢገልጹም፣ የንግድ ዋጋው ገና በግልጽ መልኩ አልተወሰነም።
የኪቢኒ ተራራ እና የኮላ ባሕረ-ገብ መሬት በዓለም ላይ በብዙ ብርቅዬ ማዕድናት የሚታወቅ ክልል ነው። በዚህ አካባቢ ከመቶዎች በላይ አዳዲስ ማዕድናት ተገኝተዋል፤ ከእነዚህም ብዙዎቹ በሌላ የዓለም ክፍል አይገኙም።
ክልሉ በተለይ በሬር አርዝ (Rare Earth Elements) ማዕድናት ምክንያት ለሳይንስና ለከፍተኛ ቴክኖሎጂ ኢንዱስትሪ ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው።
ባለሙያዎች እንደሚሉት፣ እንዲህ ዓይነት አዲስ ማዕድናት መገኘታቸው የምድር አፈጣጠርን ለመረዳት፣ አዳዲስ ቁሶችን ለማዘጋጀት እና በወደፊት በኤሌክትሮኒክስ፣ በኃይል ቴክኖሎጂና በሌሎች የኢንዱስትሪ ዘርፎች ላይ አዳዲስ አጠቃቀሞችን ለማስገኘት የሚያስችሉ ናቸው።
ሆኖም ይህ ማዕድን በንግድ ደረጃ መመረት ወይም በስፋት መጠቀም ይቻል እንደሆነ ለመወሰን ተጨማሪ የምርምር ሥራዎች እንደሚያስፈልጉ ተገልጿል።
Sponsored by
Surafel
3 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የቻይናው ዚጂን ማይኒንግ (የካናዳውን አላይድ ጎልድን በ4.01 ቢሊዮን ዶላር (5.5 ቢሊዮን የካናዳ ዶላር) ለመግዛት ያደረገው ስምምነት በቻይና እና በኢትዮጵያ መንግስታት ጫና ምክንያት መፍረሱ ተገለጸ።
እ.ኤ.አ. በጥር 2026 የተደረሰው ይህ ስምምነት፣ ዚጂን ማይኒንግ በአላይድ ጎልድ ስር የሚገኙትንና በኮትዲቯር፣ ማሊ እና ኢትዮጵያ (ቤኒሻንጉል ጉሙዝ የሚገኘው የኩርሙክ የወርቅ ማዕድን) ያሉትን ፕሮጀክቶች ሙሉ በሙሉ ጠቅልሎ እንዲገዛ የሚያስችል ነበር። ስምምነቱን የካናዳ እና የአፍሪካ ቀጣናዊ ተቋማት (እንደ ኮሜሳ እና ኤኮዋስ) ቢያጸድቁትም፣ የቻይና ብሔራዊ ልማት እና ማሻሻያ ኮሚሽን (NDRC) የግዢውን ዋጋ እና የማሊን የፖለቲካ አለመረጋጋት በመስጋት ማጽደቅ አልቻለም።
በሌላ በኩል የኢትዮጵያ መንግስት በዚሁ ስምምነት ዙሪያ ከፍተኛ የግብር ጥያቄዎችን ማንሳቱ ለድርድሩ መፍረስ ተጨማሪ ምክንያት ሆኗል። የኢትዮጵያ ገቢዎች ህግ የውጭ ኩባንያዎች የባለቤትነት ለውጥ ሲያደርጉ ከፍተኛ ግብር እንዲከፍሉ ያስገድዳል። በተጨማሪም፣ የኢትዮጵያ መንግስት እንደ ኩርሙክ ያለን ስትራቴጂካዊ የወርቅ ማዕድን በአንድ የቻይና የመንግስት ኩባንያ ስር ብቻ እንዲወድቅ አለመፈለጉ ሌላው ተግዳሮት ነበር።
በእነዚህ ጂኦፖለቲካዊ እና አስተዳደራዊ እንቅፋቶች ምክንያት ሁለቱ ኩባንያዎች ሙሉ ግዥውን ሰርዘዋል። በምትኩ፣ ዚጂን ማይኒንግ 295 ሚሊዮን ዶላር በመክፈል 9.2 በመቶ የአላይድ ጎልድ አክሲዮኖችን (Strategic Equity Stake) ብቻ ለመግዛት ተስማምቷል። ይህ ዜና ከተሰማ በኋላ በቶሮንቶ እና ኒውዮርክ የአክሲዮን ገበያዎች ላይ የአላይድ ጎልድ የአክሲዮን ዋጋ ከ16 በመቶ በላይ አሽቆልቁሏል።
እ.ኤ.አ. በጥር 2026 የተደረሰው ይህ ስምምነት፣ ዚጂን ማይኒንግ በአላይድ ጎልድ ስር የሚገኙትንና በኮትዲቯር፣ ማሊ እና ኢትዮጵያ (ቤኒሻንጉል ጉሙዝ የሚገኘው የኩርሙክ የወርቅ ማዕድን) ያሉትን ፕሮጀክቶች ሙሉ በሙሉ ጠቅልሎ እንዲገዛ የሚያስችል ነበር። ስምምነቱን የካናዳ እና የአፍሪካ ቀጣናዊ ተቋማት (እንደ ኮሜሳ እና ኤኮዋስ) ቢያጸድቁትም፣ የቻይና ብሔራዊ ልማት እና ማሻሻያ ኮሚሽን (NDRC) የግዢውን ዋጋ እና የማሊን የፖለቲካ አለመረጋጋት በመስጋት ማጽደቅ አልቻለም።
በሌላ በኩል የኢትዮጵያ መንግስት በዚሁ ስምምነት ዙሪያ ከፍተኛ የግብር ጥያቄዎችን ማንሳቱ ለድርድሩ መፍረስ ተጨማሪ ምክንያት ሆኗል። የኢትዮጵያ ገቢዎች ህግ የውጭ ኩባንያዎች የባለቤትነት ለውጥ ሲያደርጉ ከፍተኛ ግብር እንዲከፍሉ ያስገድዳል። በተጨማሪም፣ የኢትዮጵያ መንግስት እንደ ኩርሙክ ያለን ስትራቴጂካዊ የወርቅ ማዕድን በአንድ የቻይና የመንግስት ኩባንያ ስር ብቻ እንዲወድቅ አለመፈለጉ ሌላው ተግዳሮት ነበር።
በእነዚህ ጂኦፖለቲካዊ እና አስተዳደራዊ እንቅፋቶች ምክንያት ሁለቱ ኩባንያዎች ሙሉ ግዥውን ሰርዘዋል። በምትኩ፣ ዚጂን ማይኒንግ 295 ሚሊዮን ዶላር በመክፈል 9.2 በመቶ የአላይድ ጎልድ አክሲዮኖችን (Strategic Equity Stake) ብቻ ለመግዛት ተስማምቷል። ይህ ዜና ከተሰማ በኋላ በቶሮንቶ እና ኒውዮርክ የአክሲዮን ገበያዎች ላይ የአላይድ ጎልድ የአክሲዮን ዋጋ ከ16 በመቶ በላይ አሽቆልቁሏል።
5 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የኒውካስሉ ተወዳጅ የቀድሞ አሰልጣኝ ኬቨን ኪጋን ካረፉ ገና አስር ቀናት ብቻ ቢቆጠሩም፣ ክለቡ ሌላ ያልተጠበቀ መርዶ አስተናግዷል፦ የኪጋንን ህልም እውን በማድረግ ክለቡን ለክብር ያበቁት አሰልጣኝ ኤዲ ሃው ከኃላፊነታቸው መልቀቃቸውን ይፋ አድርገዋል።
ከእጅግ አስከፊው የ2025-26 የውድድር ዘመን በኋላ በኃላፊነታቸው ለመቀጠል እና ክለቡን መልሰው ለመገንባት ቃል ገብተው የነበሩት ኤዲ ሃው፣ አዲሱ የፕሪሚየር ሊግ የውድድር ዘመን ሊጀመር ሶስት ሳምንታት ብቻ ሲቀሩት ውሳኔያቸውን ቀልብሰዋል።
ማክሰኞ ምሽት በቅድመ-ውድድር ዝግጅት ኒውካስል ከብሪስቶል ሲቲ ጋር ባደረገው የወዳጅነት ጨዋታ 4-1 በሆነ አሳፋሪ ውጤት መሸነፉ ብዙ ነገሮችን የቀየረ ይመስላል። ከሜዳቸው ውጪ ስታዲየሙን ሞልተው የነበሩት የኒውካስል ደጋፊዎች ያሰሙት የተቃውሞ እና የቁጣ ድምፅ፣ ይህ "ትርጉም አልባ" የሚመስል የወዳጅነት ጨዋታ ትልቅ መዘዝ ይዞ እንደሚመጣ አመላካች ነበር።
በማግስቱ ረቡዕ ጠዋት እንደተሰማው ኤዲ ሃው ኃላፊነታቸውን ለመልቀቅ ወስነዋል። የቅርብ ምንጮች እንደሚያሳዩት ይህ ውሳኔ የቅጽበት የብስጭት ውሳኔ ሳይሆን፣ ከከባዱ የውድድር ዘመን መገባደጃ አንስቶ አሰልጣኙ በውስጣቸው ሲያብሰለስሉት የቆዩት እና ሊሸከሙት ያልቻሉት ከባድ ሸክም ውጤት ነው።
ለኤዲ ሃው፣ ይህ ስንብት እጅግ አስደናቂ ለነበረው የኒውካስል ቆይታቸው የማይመጥን አሳዛኝ ማብቂያ ነው። ከ30 ዓመታት በፊት ኬቨን ኪጋን እጅግ ተቃርበውት የነበረውን፣ ደጋፊውም ለ70 ዓመታት ሲናፍቀው የነበረውን ትልቅ ዋንጫ ወደ ሴንት ጀምስ ፓርክ ያመጡት እርሳቸው ነበሩ።
እ.ኤ.አ በ2021 ክለቡ በፕሪሚየር ሊጉ 19ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጦ ወደ መውረድ አፋፍ በደረሰበት ወቅት ኃላፊነቱን የተረከቡት ሃው፣ ኒውካስልን በሊጉ ማቆየት ብቻ ሳይሆን በሚቀጥለው ዓመት ወደ ቻምፒዮንስ ሊግ መድረክ መልሰውታል። በ2024-25 ደግሞ በካራባኦ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ የሊጉን ሻምፒዮን ሊቨርፑልን በዌምብሌይ አሸንፈው ታሪካዊ ዋንጫ በማንሳት ስማቸውን በኒውካስል ታሪክ በወርቅ ቀለም አጽፈው ነበር።
ይህ የዋንጫ ድል የሳዑዲው የኢንቨስትመንት ፈንድ (PIF) በባለቤትነት ለሚያስተዳድረው እና የፕሪሚየር ሊጉን ዋንጫ ለሚያልመው ኒውካስል እንደ ትልቅ መነሻ መታየት ነበረበት። ሆኖም፣ የ2025ቱ ክረምት የሁሉንም ነገር አቅጣጫ ቀየረው።
በተለይም አሌክሳንደር ኢሳክን በክለቡ ለማቆየት የተደረገው ተስፋ አስቆራጭ እና መራር ትግል፣ በመጨረሻም ስዊድናዊው አጥቂ በብሪታንያ የዝውውር ሪከርድ በዝውውር መስኮቱ መዘጋጃ ዕለት ወደ ሊቨርፑል ማምራቱ ክለቡን ክፉኛ ጎድቶታል። ኒውካስል የኢሳክን ክፍተት ሊተካ የሚችል ተጫዋች ማምጣት አልቻለም። እንደ ሁጎ ኤኪቲኬ፣ ቤንጃሚን ሴስኮ እና ጆአዎ ፔድሮ ያሉ ታላላቅ ኢላማዎቹን ለተቀናቃኝ የፕሪሚየር ሊግ ክለቦች አሳልፎ ሰጠ።
በምትኩ ክለቡ እና ኤዲ ሃው በጋራ ያመጧቸው ኒክ ዎልቴማዴ፣ ዮአን ዊሳ እና አንቶኒ ኤላንጋ አጠቃላይ 180 ሚሊዮን ፓውንድ ($243m) ቢወጣባቸውም፣ ያሳዩት አቋም እና የገጠማቸው የጉዳት ችግር የተከፈለባቸውን ዋጋ ፈጽሞ ሊያጸድቅ አልቻለም። የኤላንጋ እና ዎልቴማዴ ብቃት ሲዋዥቅ፣ አጥቂው ዊሳ በሙሉ የውድድር ዘመኑ በሊጉ ያስቆጠረው አንድ ጎል ብቻ ነበር። በ43 ሚሊዮን ፓውንድ የመጣው ጃኮብ ራምሴይም በቁርጭምጭሚት ጉዳት ሲሰቃይ ጊዜውን አሳልፏል።
የዝውውር ውድቀቱ በሜዳ ላይ ውጤት ቢሸፈን ኖሮ የኤዲ ሃው ጫና ያን ያህል አይከፋም ነበር። ሆኖም የ2025-26 የውድድር ዘመን ለኒውካስል እውነተኛ ቅዠት ሆኖ አለፈ።
በዓመቱ መጀመሪያ ጥሩ አጀማመር ያሳየው ክለቡ፣ ከአዲሱ ዓመት በኋላ ግን የመውረድ ስጋት ወዳለባቸው ቡድኖች ወረደ። ከጥር መጨረሻ አንስቶ እስከ የውድድር ዘመኑ ማብቂያ ድረስ ካደረጋቸው 16 ጨዋታዎች በ10ሩ በመሸነፉ፣ ከ6ኛ ደረጃ ወደ 12ኛ ደረጃ በማሽቆልቆል ደጋፊውን በሀዘን እና በቁጣ ሞላው።
ይባስ ብሎ በኤፍኤ ካፕ እና በካራባኦ ካፕ በማንችስተር ሲቲ በቀላሉ ሲሰናበት፣ በቻምፒዮንስ ሊጉ ደግሞ ባርሴሎና በድምር ውጤት 8-3 በሆነ አሳፋሪ የጎል ናዳ አዋርዶ ከውድድሩ አስወጣው።
የኤዲ ሃው የወደፊት እጣ ፈንታ ጥያቄ ውስጥ የገባው ገና በጊዜ ነበር። በሚያዝያ ወር ኒውካስል በተከታታይ ለሶስተኛ ጊዜ በቦርንማውዝ ከተሸነፈ በኋላ፣ የክለቡ ታሪካዊ ሌጀንድ አላን ሺረር እንዲህ ብሎ ነበር፦ "ለኤዲ ምን ያህል ከባድ ጊዜ እንደሆነ ባውቅም፣ የወደፊት እጣ ፈንታው ምን እንደሚሆን አላውቅም። ዳግም የመዋጋት እና ክለቡን የማንሳት አቅሙ ያለው አይመስለኝም። በሚቀጥለው የውድድር ዘመን ኤዲ ሃው ኒውካስልን ያሰለጥናል ብዬ አላስብም።"
ሺረር እንዳለውም ሆነ ኤዲ ሃው ኒውካስልን ወደ ቀደመ ክብሩ የመመለስ ትልቅ ታሪክ ሰርተው፣ ነገር ግን በኋለኛው አመታቸው በዝውውር ውድቀት እና በሜዳ ላይ አስከፊ ውጤቶች ታጅበው የሴንት ጀምስ ፓርኩን በር ዘግተው ወጥተዋል።
ከእጅግ አስከፊው የ2025-26 የውድድር ዘመን በኋላ በኃላፊነታቸው ለመቀጠል እና ክለቡን መልሰው ለመገንባት ቃል ገብተው የነበሩት ኤዲ ሃው፣ አዲሱ የፕሪሚየር ሊግ የውድድር ዘመን ሊጀመር ሶስት ሳምንታት ብቻ ሲቀሩት ውሳኔያቸውን ቀልብሰዋል።
ማክሰኞ ምሽት በቅድመ-ውድድር ዝግጅት ኒውካስል ከብሪስቶል ሲቲ ጋር ባደረገው የወዳጅነት ጨዋታ 4-1 በሆነ አሳፋሪ ውጤት መሸነፉ ብዙ ነገሮችን የቀየረ ይመስላል። ከሜዳቸው ውጪ ስታዲየሙን ሞልተው የነበሩት የኒውካስል ደጋፊዎች ያሰሙት የተቃውሞ እና የቁጣ ድምፅ፣ ይህ "ትርጉም አልባ" የሚመስል የወዳጅነት ጨዋታ ትልቅ መዘዝ ይዞ እንደሚመጣ አመላካች ነበር።
በማግስቱ ረቡዕ ጠዋት እንደተሰማው ኤዲ ሃው ኃላፊነታቸውን ለመልቀቅ ወስነዋል። የቅርብ ምንጮች እንደሚያሳዩት ይህ ውሳኔ የቅጽበት የብስጭት ውሳኔ ሳይሆን፣ ከከባዱ የውድድር ዘመን መገባደጃ አንስቶ አሰልጣኙ በውስጣቸው ሲያብሰለስሉት የቆዩት እና ሊሸከሙት ያልቻሉት ከባድ ሸክም ውጤት ነው።
ለኤዲ ሃው፣ ይህ ስንብት እጅግ አስደናቂ ለነበረው የኒውካስል ቆይታቸው የማይመጥን አሳዛኝ ማብቂያ ነው። ከ30 ዓመታት በፊት ኬቨን ኪጋን እጅግ ተቃርበውት የነበረውን፣ ደጋፊውም ለ70 ዓመታት ሲናፍቀው የነበረውን ትልቅ ዋንጫ ወደ ሴንት ጀምስ ፓርክ ያመጡት እርሳቸው ነበሩ።
እ.ኤ.አ በ2021 ክለቡ በፕሪሚየር ሊጉ 19ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጦ ወደ መውረድ አፋፍ በደረሰበት ወቅት ኃላፊነቱን የተረከቡት ሃው፣ ኒውካስልን በሊጉ ማቆየት ብቻ ሳይሆን በሚቀጥለው ዓመት ወደ ቻምፒዮንስ ሊግ መድረክ መልሰውታል። በ2024-25 ደግሞ በካራባኦ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ የሊጉን ሻምፒዮን ሊቨርፑልን በዌምብሌይ አሸንፈው ታሪካዊ ዋንጫ በማንሳት ስማቸውን በኒውካስል ታሪክ በወርቅ ቀለም አጽፈው ነበር።
ይህ የዋንጫ ድል የሳዑዲው የኢንቨስትመንት ፈንድ (PIF) በባለቤትነት ለሚያስተዳድረው እና የፕሪሚየር ሊጉን ዋንጫ ለሚያልመው ኒውካስል እንደ ትልቅ መነሻ መታየት ነበረበት። ሆኖም፣ የ2025ቱ ክረምት የሁሉንም ነገር አቅጣጫ ቀየረው።
በተለይም አሌክሳንደር ኢሳክን በክለቡ ለማቆየት የተደረገው ተስፋ አስቆራጭ እና መራር ትግል፣ በመጨረሻም ስዊድናዊው አጥቂ በብሪታንያ የዝውውር ሪከርድ በዝውውር መስኮቱ መዘጋጃ ዕለት ወደ ሊቨርፑል ማምራቱ ክለቡን ክፉኛ ጎድቶታል። ኒውካስል የኢሳክን ክፍተት ሊተካ የሚችል ተጫዋች ማምጣት አልቻለም። እንደ ሁጎ ኤኪቲኬ፣ ቤንጃሚን ሴስኮ እና ጆአዎ ፔድሮ ያሉ ታላላቅ ኢላማዎቹን ለተቀናቃኝ የፕሪሚየር ሊግ ክለቦች አሳልፎ ሰጠ።
በምትኩ ክለቡ እና ኤዲ ሃው በጋራ ያመጧቸው ኒክ ዎልቴማዴ፣ ዮአን ዊሳ እና አንቶኒ ኤላንጋ አጠቃላይ 180 ሚሊዮን ፓውንድ ($243m) ቢወጣባቸውም፣ ያሳዩት አቋም እና የገጠማቸው የጉዳት ችግር የተከፈለባቸውን ዋጋ ፈጽሞ ሊያጸድቅ አልቻለም። የኤላንጋ እና ዎልቴማዴ ብቃት ሲዋዥቅ፣ አጥቂው ዊሳ በሙሉ የውድድር ዘመኑ በሊጉ ያስቆጠረው አንድ ጎል ብቻ ነበር። በ43 ሚሊዮን ፓውንድ የመጣው ጃኮብ ራምሴይም በቁርጭምጭሚት ጉዳት ሲሰቃይ ጊዜውን አሳልፏል።
የዝውውር ውድቀቱ በሜዳ ላይ ውጤት ቢሸፈን ኖሮ የኤዲ ሃው ጫና ያን ያህል አይከፋም ነበር። ሆኖም የ2025-26 የውድድር ዘመን ለኒውካስል እውነተኛ ቅዠት ሆኖ አለፈ።
በዓመቱ መጀመሪያ ጥሩ አጀማመር ያሳየው ክለቡ፣ ከአዲሱ ዓመት በኋላ ግን የመውረድ ስጋት ወዳለባቸው ቡድኖች ወረደ። ከጥር መጨረሻ አንስቶ እስከ የውድድር ዘመኑ ማብቂያ ድረስ ካደረጋቸው 16 ጨዋታዎች በ10ሩ በመሸነፉ፣ ከ6ኛ ደረጃ ወደ 12ኛ ደረጃ በማሽቆልቆል ደጋፊውን በሀዘን እና በቁጣ ሞላው።
ይባስ ብሎ በኤፍኤ ካፕ እና በካራባኦ ካፕ በማንችስተር ሲቲ በቀላሉ ሲሰናበት፣ በቻምፒዮንስ ሊጉ ደግሞ ባርሴሎና በድምር ውጤት 8-3 በሆነ አሳፋሪ የጎል ናዳ አዋርዶ ከውድድሩ አስወጣው።
የኤዲ ሃው የወደፊት እጣ ፈንታ ጥያቄ ውስጥ የገባው ገና በጊዜ ነበር። በሚያዝያ ወር ኒውካስል በተከታታይ ለሶስተኛ ጊዜ በቦርንማውዝ ከተሸነፈ በኋላ፣ የክለቡ ታሪካዊ ሌጀንድ አላን ሺረር እንዲህ ብሎ ነበር፦ "ለኤዲ ምን ያህል ከባድ ጊዜ እንደሆነ ባውቅም፣ የወደፊት እጣ ፈንታው ምን እንደሚሆን አላውቅም። ዳግም የመዋጋት እና ክለቡን የማንሳት አቅሙ ያለው አይመስለኝም። በሚቀጥለው የውድድር ዘመን ኤዲ ሃው ኒውካስልን ያሰለጥናል ብዬ አላስብም።"
ሺረር እንዳለውም ሆነ ኤዲ ሃው ኒውካስልን ወደ ቀደመ ክብሩ የመመለስ ትልቅ ታሪክ ሰርተው፣ ነገር ግን በኋለኛው አመታቸው በዝውውር ውድቀት እና በሜዳ ላይ አስከፊ ውጤቶች ታጅበው የሴንት ጀምስ ፓርኩን በር ዘግተው ወጥተዋል።
5 days ago
ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ ሱዳን ካርቱም ገብተዋል!
የኢጋድ ሊቀመንበሩ ጉዞ የሱዳኑን አስከፊ ጦርነት በድርደር ለመቋጨት ያለመ እንደሆነ ተዘግቧል፡፡ ባሁኑ ወቅት የሱዳን ጦርነት ወደ ኢትዮጵያ ድንበር እየተለጠጠ እና በኢትዮጵያ ካለው የአገር ውስጥ ግጭት ጋር ተያይዞ እየተነሳ መሆኑ ይታወቃል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
የኢጋድ ሊቀመንበሩ ጉዞ የሱዳኑን አስከፊ ጦርነት በድርደር ለመቋጨት ያለመ እንደሆነ ተዘግቧል፡፡ ባሁኑ ወቅት የሱዳን ጦርነት ወደ ኢትዮጵያ ድንበር እየተለጠጠ እና በኢትዮጵያ ካለው የአገር ውስጥ ግጭት ጋር ተያይዞ እየተነሳ መሆኑ ይታወቃል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
5 days ago
የዓለም የወርቅ ፍላጎት 380 ቢሊዮን ዶላር ደረሰ
#ethiopia | የዓለም የወርቅ ገበያ በ2026 ሁለተኛ ሩብ ዓመት ታሪካዊ ምዕራፍ መመዝገቡን የዓለም ወርቅ ምክር ቤት (World Gold Council) አስታውቋል።
በሪፖርቱ መሠረት፣ የወርቅ ፍላጎት በመጠን 1,269 ቶን ላይ የተረጋጋ ሲሆን፣ በከፍተኛ የወርቅ ዋጋ ምክንያት የገበያው ጠቅላላ ዋጋ 380 ቢሊዮን ዶላር በመድረስ አዲስ ታሪካዊ ክብረ ወሰን አስመዝግቧል።
ባለሙያዎች እንደሚገልጹት፣ የወርቅ ዋጋ መጨመር፣ የዓለም አቀፍ ጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች፣ የገንዘብ ገበያ አለመረጋጋት እና ባለሀብቶች ወደ ደህንነት ንብረት (Safe Haven Asset) የሚያደርጉት መሸጋገር የወርቅ ፍላጎትን በእጅጉ አጠናክረዋል።
ሪፖርቱ እንደሚያመለክተው፣ በምዕራብ አፍሪካ ያለው የማዕድን ምርት እድገት ለዓለም የወርቅ አቅርቦት ከፍተኛ አስተዋፅኦ አድርጓል። ቡርኪና ፋሶ 17 በመቶ እና ጋና 8 በመቶ የምርት እድገት በማስመዝገብ የወርቅ ምርት ማሳደግ ችለዋል። ይህም የዓለም የወርቅ አቅርቦትን ለማረጋጋት አስፈላጊ ሚና ተጫውቷል።
በሌላ በኩል የዓለም ማዕከላዊ ባንኮች 289 ቶን የወርቅ ግዥ በመፈጸማቸው የገበያውን ፍላጎት ደግፈዋል። ምንም እንኳን በአንዳንድ አገራት የወርቅ ምርት መቀነስ ቢታይም፣ የዓለም አቀፉ ገበያ በአጠቃላይ ጠንካራ መሆኑን ሪፖርቶች ያመለክታሉ።
በወርቅ ገበያ ላይ የሚታየው የዋጋ ንረት የጌጣጌጥ ፍላጎትን እየቀነሰ ቢሆንም፣ የኢንቨስትመንት ፍላጎት በከፍተኛ ሁኔታ ማደጉን የዓለም ወርቅ ምክር ቤት ገልጿል።
በተለይ የወርቅ ETF ፈንዶች፣ የወርቅ ሳንቲሞች እና የወርቅ አሞሌዎች ላይ የባለሀብቶች ፍላጎት እየጨመረ መሆኑ ተጠቁሟል።
ኢኮኖሚስቶች እንደሚሉት፣ የወርቅ ገበያ በቀጣዮቹ ወራትም በዓለም አቀፍ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎች ተፅዕኖ ስር እንደሚቀጥል ይጠበቃል።
በተለይ የማዕከላዊ ባንኮች የወርቅ ክምችት ማሳደግና ባለሀብቶች ወደ ወርቅ የሚያደርጉት መሸጋገር የዋጋ እንቅስቃሴውን ዋና የሚወስኑ ምክንያቶች እንደሚሆኑ ተገልጿል።
#ethiopia | የዓለም የወርቅ ገበያ በ2026 ሁለተኛ ሩብ ዓመት ታሪካዊ ምዕራፍ መመዝገቡን የዓለም ወርቅ ምክር ቤት (World Gold Council) አስታውቋል።
በሪፖርቱ መሠረት፣ የወርቅ ፍላጎት በመጠን 1,269 ቶን ላይ የተረጋጋ ሲሆን፣ በከፍተኛ የወርቅ ዋጋ ምክንያት የገበያው ጠቅላላ ዋጋ 380 ቢሊዮን ዶላር በመድረስ አዲስ ታሪካዊ ክብረ ወሰን አስመዝግቧል።
ባለሙያዎች እንደሚገልጹት፣ የወርቅ ዋጋ መጨመር፣ የዓለም አቀፍ ጂኦፖለቲካዊ ውጥረቶች፣ የገንዘብ ገበያ አለመረጋጋት እና ባለሀብቶች ወደ ደህንነት ንብረት (Safe Haven Asset) የሚያደርጉት መሸጋገር የወርቅ ፍላጎትን በእጅጉ አጠናክረዋል።
ሪፖርቱ እንደሚያመለክተው፣ በምዕራብ አፍሪካ ያለው የማዕድን ምርት እድገት ለዓለም የወርቅ አቅርቦት ከፍተኛ አስተዋፅኦ አድርጓል። ቡርኪና ፋሶ 17 በመቶ እና ጋና 8 በመቶ የምርት እድገት በማስመዝገብ የወርቅ ምርት ማሳደግ ችለዋል። ይህም የዓለም የወርቅ አቅርቦትን ለማረጋጋት አስፈላጊ ሚና ተጫውቷል።
በሌላ በኩል የዓለም ማዕከላዊ ባንኮች 289 ቶን የወርቅ ግዥ በመፈጸማቸው የገበያውን ፍላጎት ደግፈዋል። ምንም እንኳን በአንዳንድ አገራት የወርቅ ምርት መቀነስ ቢታይም፣ የዓለም አቀፉ ገበያ በአጠቃላይ ጠንካራ መሆኑን ሪፖርቶች ያመለክታሉ።
በወርቅ ገበያ ላይ የሚታየው የዋጋ ንረት የጌጣጌጥ ፍላጎትን እየቀነሰ ቢሆንም፣ የኢንቨስትመንት ፍላጎት በከፍተኛ ሁኔታ ማደጉን የዓለም ወርቅ ምክር ቤት ገልጿል።
በተለይ የወርቅ ETF ፈንዶች፣ የወርቅ ሳንቲሞች እና የወርቅ አሞሌዎች ላይ የባለሀብቶች ፍላጎት እየጨመረ መሆኑ ተጠቁሟል።
ኢኮኖሚስቶች እንደሚሉት፣ የወርቅ ገበያ በቀጣዮቹ ወራትም በዓለም አቀፍ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎች ተፅዕኖ ስር እንደሚቀጥል ይጠበቃል።
በተለይ የማዕከላዊ ባንኮች የወርቅ ክምችት ማሳደግና ባለሀብቶች ወደ ወርቅ የሚያደርጉት መሸጋገር የዋጋ እንቅስቃሴውን ዋና የሚወስኑ ምክንያቶች እንደሚሆኑ ተገልጿል።
Sponsored by
Surafel
5 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) እግር ኳስ አንዳንዴ ከስፖርትነት አልፎ ድንቅ እና ስሜት ቀስቃሽ ታሪኮችን ይጽፋል። የ8 ወር ህጻን እያለ በሀገሩ ሄይቲ በደረሰው እና ከ300 ሺህ በላይ ሰዎችን ህይወት በከፋ ሁኔታ በቀጠፈው አሰቃቂ የመሬት መንቀጥቀጥ ወቅት፣ ከተአምር በተጠጋ ሁኔታ የተረፈው ወጣት፤ ዛሬ በዓለም እግር ኳስ ታላቁን ሰማያዊ እና ነጭ ማሊያ ለብሶ አዲስ ታሪክ ጽፏል።
የ17 ዓመቱ ስቲቨን "ኪኪ" ራሞስ ለአርጀንቲና ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በመሰለፍ፣ በሄይቲ ተወልዶ የታላቋን ደቡብ አሜሪካ ሀገር ማሊያ የለበሰ የመጀመሪያው ተጫዋች መሆን ችሏል!
በታዋቂው የቬሌዝ ሳርስፊልድ አካዳሚ ውስጥ በክንፍ አጥቂነት የሚያበራው ይህ ታዳጊ፣ አርጀንቲና ኢኳዶርን 2ለ1 ባሸነፈችበት ጨዋታ ላይ ለአልቢሴሌስቴዎች የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። በጨዋታው ላይ ድንቅ እንቅስቃሴ በማሳየት እና ሁለት ግቦችን በማስቆጠር ቡድኑን ለድል ያበቃው ኪኪ ራሞስ፣ በዓለም እግር ኳስ ግዙፍ ስም ባላቸው አርጀንቲናውያን ዘንድ ስሙን በወርቅ ቀለም ጽፏል።
በ2009 በፖርት-ኦ-ፕሪንስ ሄይቲ የተወለደው ኪኪ፣ ለአርጀንቲና በማንኛውም የዕድሜ እርከን ብሔራዊ ቡድን ውስጥ የተሰለፈ የመጀመሪያው በሄይቲ የተወለደ ጥቁር ተጫዋች በመሆን አዲስ የኢንተርናሽናል እግር ኳስ ምዕራፍ ከፍቷል።
የኪኪ የህይወት ታሪክ ልክ እንደ አስደናቂ የፊልም ስክሪፕት ነው። እ.ኤ.አ በ2010 በሄይቲ ደርሶ በነበረው አውዳሚ የመሬት መንቀጥቀጥ ወቅት ገና የ8 ወር ህጻን የነበረው ኪኪ፣ በነበረበት የሕፃናት ማደሪያ ጣቢያ ውስጥ ጉዳት ሳይደርስበት ከተረፉት በጣም ጥቂት ህጻናት አንዱ ነበር።
ባዮሎጂካል ወላጆቹ አርጀንቲናውያን ባይሆኑም፣ አንድ ደግ ልብ ያላቸው አርጀንቲናውያን ባልና ሚስት በጉዲፈቻ ወስደው ወደ ቦነስ አይረስ አመጡት። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ህይወቱን ሙሉ በአርጀንቲና ያሳለፈው፣ ቋንቋውን እና ባህሉን ለምዶ ያደገው ኪኪ፣ የሀገሪቱን ዜግነት በመያዝ ለብሔራዊ ቡድኑ የመጫወት ህጋዊ መብትን አግኝቷል።
የኪኪ ራሞስ ታሪክ ይፋ መሆንን ተከትሎ በአርጀንቲናውያን የእግር ኳስ አፍቃሪዎች ዘንድ ከፍተኛ ደስታ እና ኩራት ተፈጥሯል። በጨዋታው ካሳየው ከፍተኛ ተሰጥኦ ባሻገር፣ ከሞት አፍ ወጥቶ ለአርጀንቲና ማሊያ እስከመበቃት ያደረገውን ተአምራዊ ጉዞ የተመለከቱ የስፖርቱ ተከታታዮች፣ "እግር ኳስ ሰዎችን የሚያስተስርር ድንቅ ድልድይ ነው" ሲሉ አድናቆታቸውን ገልጸዋል።
ገና በ17 ዓመቱ በአርጀንቲና እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ ልዩ ቦታ የያዘው ይህ ፈጣን የክንፍ መስመር ተጫዋች፣ በቀጣይ በታላቁ የአርጀንቲና ዋና ብሔራዊ ቡድን ውስጥ የመሰለፍ ህልሙን ያሳካ ይሆን? የዓለም እግር ኳስ አፍቃሪዎች ከወዲሁ የዚህን ድንቅ ወጣት ቀጣይ እርምጃዎች በትልቅ ጉጉት እየተከታተሉ ይገኛሉ።
የ17 ዓመቱ ስቲቨን "ኪኪ" ራሞስ ለአርጀንቲና ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን በመሰለፍ፣ በሄይቲ ተወልዶ የታላቋን ደቡብ አሜሪካ ሀገር ማሊያ የለበሰ የመጀመሪያው ተጫዋች መሆን ችሏል!
በታዋቂው የቬሌዝ ሳርስፊልድ አካዳሚ ውስጥ በክንፍ አጥቂነት የሚያበራው ይህ ታዳጊ፣ አርጀንቲና ኢኳዶርን 2ለ1 ባሸነፈችበት ጨዋታ ላይ ለአልቢሴሌስቴዎች የመጀመሪያ ጨዋታውን አድርጓል። በጨዋታው ላይ ድንቅ እንቅስቃሴ በማሳየት እና ሁለት ግቦችን በማስቆጠር ቡድኑን ለድል ያበቃው ኪኪ ራሞስ፣ በዓለም እግር ኳስ ግዙፍ ስም ባላቸው አርጀንቲናውያን ዘንድ ስሙን በወርቅ ቀለም ጽፏል።
በ2009 በፖርት-ኦ-ፕሪንስ ሄይቲ የተወለደው ኪኪ፣ ለአርጀንቲና በማንኛውም የዕድሜ እርከን ብሔራዊ ቡድን ውስጥ የተሰለፈ የመጀመሪያው በሄይቲ የተወለደ ጥቁር ተጫዋች በመሆን አዲስ የኢንተርናሽናል እግር ኳስ ምዕራፍ ከፍቷል።
የኪኪ የህይወት ታሪክ ልክ እንደ አስደናቂ የፊልም ስክሪፕት ነው። እ.ኤ.አ በ2010 በሄይቲ ደርሶ በነበረው አውዳሚ የመሬት መንቀጥቀጥ ወቅት ገና የ8 ወር ህጻን የነበረው ኪኪ፣ በነበረበት የሕፃናት ማደሪያ ጣቢያ ውስጥ ጉዳት ሳይደርስበት ከተረፉት በጣም ጥቂት ህጻናት አንዱ ነበር።
ባዮሎጂካል ወላጆቹ አርጀንቲናውያን ባይሆኑም፣ አንድ ደግ ልብ ያላቸው አርጀንቲናውያን ባልና ሚስት በጉዲፈቻ ወስደው ወደ ቦነስ አይረስ አመጡት። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ህይወቱን ሙሉ በአርጀንቲና ያሳለፈው፣ ቋንቋውን እና ባህሉን ለምዶ ያደገው ኪኪ፣ የሀገሪቱን ዜግነት በመያዝ ለብሔራዊ ቡድኑ የመጫወት ህጋዊ መብትን አግኝቷል።
የኪኪ ራሞስ ታሪክ ይፋ መሆንን ተከትሎ በአርጀንቲናውያን የእግር ኳስ አፍቃሪዎች ዘንድ ከፍተኛ ደስታ እና ኩራት ተፈጥሯል። በጨዋታው ካሳየው ከፍተኛ ተሰጥኦ ባሻገር፣ ከሞት አፍ ወጥቶ ለአርጀንቲና ማሊያ እስከመበቃት ያደረገውን ተአምራዊ ጉዞ የተመለከቱ የስፖርቱ ተከታታዮች፣ "እግር ኳስ ሰዎችን የሚያስተስርር ድንቅ ድልድይ ነው" ሲሉ አድናቆታቸውን ገልጸዋል።
ገና በ17 ዓመቱ በአርጀንቲና እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ ልዩ ቦታ የያዘው ይህ ፈጣን የክንፍ መስመር ተጫዋች፣ በቀጣይ በታላቁ የአርጀንቲና ዋና ብሔራዊ ቡድን ውስጥ የመሰለፍ ህልሙን ያሳካ ይሆን? የዓለም እግር ኳስ አፍቃሪዎች ከወዲሁ የዚህን ድንቅ ወጣት ቀጣይ እርምጃዎች በትልቅ ጉጉት እየተከታተሉ ይገኛሉ።
6 days ago
ናይጄሪያዊቷ ጉድነስ ንዋቹኩ የኮመንዌልዝ ጨዋታዎች የዲስከስ ሻምፒዮንነቷን አስጠበቀች
#ethiopia | ናይጄሪያዊቷ የፓራ አትሌት ጉድነስ ንዋቹኩ በ2026 የግላስጎው ኮመንዌልዝ ጨዋታዎች በሴቶች የዲስከስ F42–44/F61–64 ውድድር 39.66 ሜትር በመወርወር የወርቅ ሜዳልያ አሸንፋለች።
በዚህ ውጤት የራሷን የዓለም ክብረ ወሰን በማሻሻል የኮመንዌልዝ ጨዋታዎች ሻምፒዮንነቷንም በተሳካ ሁኔታ አስጠብቃለች። አዲሱ 39.66 ሜትር ውርወራ ከቀድሞ የዓለም ክብረ ወሰኗ በላይ ከ3 ሜትር በላይ የተሻለ ነው።
#ethiopia | ናይጄሪያዊቷ የፓራ አትሌት ጉድነስ ንዋቹኩ በ2026 የግላስጎው ኮመንዌልዝ ጨዋታዎች በሴቶች የዲስከስ F42–44/F61–64 ውድድር 39.66 ሜትር በመወርወር የወርቅ ሜዳልያ አሸንፋለች።
በዚህ ውጤት የራሷን የዓለም ክብረ ወሰን በማሻሻል የኮመንዌልዝ ጨዋታዎች ሻምፒዮንነቷንም በተሳካ ሁኔታ አስጠብቃለች። አዲሱ 39.66 ሜትር ውርወራ ከቀድሞ የዓለም ክብረ ወሰኗ በላይ ከ3 ሜትር በላይ የተሻለ ነው።
6 days ago
በርካታ አካባቢዎች መብራት ይቋረጣል‼️
የጥገና ሥራ ምክንያት ነገ በበርካታ አካባቢዎች የመብራት አቅርቦት ይቋረጣል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የጥገና ሥራ ለማከናወን ነገ ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የኃይል አቅርቦት ለተወሰነ ሰዓት እንደሚቋረጥ አስታውቋል።
ከጠዋቱ 4፡00 – 10፡00
• ኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት፣ ችሎት አደባባይ፣ ዘበኛ ሰፈር፣ ሾላ፣ ሰሜን ሆቴል ጫፍ፣ ቀለመወርቅ ት/ቤት፣ ዶሮ ተራ፣ ራስ ደስታ፣ አርበኞች ት/ቤት እና አካባቢያቸው።
• ዕንቁላል ፋብሪካ፣ ሀግቤስ አራት መንታ፣ ጎጃም በረንዳ፣ ጅንአድ፣ አበበች ጎበና፣ ቄጤማ ተራ፣ ፓስተር አደባባይ፣ አቤት ሆስፒታል፣ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን፣ ዳትሰን ሰፈር፣ ሰን ሆቴል እና አካባቢያቸው።
• 3ኛ ፖሊስ ጣቢያ፣ አዲስ አበባ ሜዲካል ኮሌጅ፣ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን፣ አትክልት ተራ፣ ጣሊያን ሰፈር፣ ፒያሳ (በከፊል)፣ ማዘጋጃ ቤት፣ አውቶብስ ተራ እና አካባቢያቸው።
• ማርቆስ መጋዘን፣ ቀጨኔ 8 ቁጥር ማዞሪያ፣ ቀጨኔ 1ኛ፣ 2ኛ እና 3ኛ መንገድ፣ ይመር ውኃ፣ መቀጠያ፣ 19 ታቦት ማደሪያ፣ መታፈሪ ሰፈር፣ ጴጥሮስ ሆስፒታል፣ ሽሮ ሜዳ እና አካባቢያቸው።
ከጠዋቱ 2፡00 – 10፡00
• አያት ለገጣፎ ሰብስቴሽን ፊትለፊት ያሉ ኮንዶሚኒየሞች፣ ክቡርደመና፣ ሰላም ቪሌጅ፣ ጣፎ ገብርኤል፣ ጋሪ ተራ፣ ባጃጅ ተራ እና አካባቢያቸው።
ከጠዋቱ 3፡00 – 10፡30
• ገላን፣ አራብሳ፣ እንጀራ ማምረቻ ፋብሪካ፣ ፕሮጀክት 13 አራብሳ ወታደር ሰፈር፣ ነጋ ቦንገር፣ ጀሶ ፋብሪካ፣ ብሔረፅጌ ቆዳ ፋብሪካ፣ ፓስታና መኮረኒ ፋብሪካ እና አካባቢያቸው።
• አባ ሳሙኤል፣ አቡሴራ፣ ሉግና፣ ዱፍና፣ ደበራ ጢኖ፣ ሻሸመኔ፣ ዱከም፣ በላይነህ ክንዴ፣ በስተቀኝ ያሉ ኢንዱስትሪዎች፣ ካፍ ማደያ እና አካባቢያቸው።
ከጠዋቱ 4፡30 – 11፡00
• መቐለ (ላቺ በከፊል)፣ ሀምዲያ ኢንዱስትሪ ዞን፣ ቀበሌ 03፣ ባህርዳር (አዲስ ዓለም)፣ ኦቪድ፣ ሰማኤታ፣ ሚሊኒየም ት/ቤት እና አካባቢያቸው።
ከጠዋቱ 1፡00 – 6፡00
• ወልዲያ፣ ይምርሃነ ክርስቶስ፣ ቢልባላ፣ ቂርቆስ፣ ሳሬዜና፣ ሶርባ፣ ላሊበላ፣ ገነተ ማርያም፣ ዘሃ፣ ሙቅ ውኃ፣ ተከዜ ገዳሜ፣ ኢርፋ ገለሶቴ እና አካባቢያቸው።
• ቅዱስ አርቢ፣ ዳቦ ከተማ፣ ቡርኮ፣ አይና ሚካኤል፣ ጭሮ፣ ሜኤሶ፣ አሰቦት እና አካባቢያቸው።
በመሆኑም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ደንበኞች የጥገና ሥራው እስኪጠናቀቅ እና የኃይል አቅርቦቱ ወደ መደበኛ ሁኔታው እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንዲጠብቁ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጠይቋል።
Seledadotio
Seledadotio
የጥገና ሥራ ምክንያት ነገ በበርካታ አካባቢዎች የመብራት አቅርቦት ይቋረጣል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የጥገና ሥራ ለማከናወን ነገ ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የኃይል አቅርቦት ለተወሰነ ሰዓት እንደሚቋረጥ አስታውቋል።
ከጠዋቱ 4፡00 – 10፡00
• ኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት፣ ችሎት አደባባይ፣ ዘበኛ ሰፈር፣ ሾላ፣ ሰሜን ሆቴል ጫፍ፣ ቀለመወርቅ ት/ቤት፣ ዶሮ ተራ፣ ራስ ደስታ፣ አርበኞች ት/ቤት እና አካባቢያቸው።
• ዕንቁላል ፋብሪካ፣ ሀግቤስ አራት መንታ፣ ጎጃም በረንዳ፣ ጅንአድ፣ አበበች ጎበና፣ ቄጤማ ተራ፣ ፓስተር አደባባይ፣ አቤት ሆስፒታል፣ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን፣ ዳትሰን ሰፈር፣ ሰን ሆቴል እና አካባቢያቸው።
• 3ኛ ፖሊስ ጣቢያ፣ አዲስ አበባ ሜዲካል ኮሌጅ፣ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን፣ አትክልት ተራ፣ ጣሊያን ሰፈር፣ ፒያሳ (በከፊል)፣ ማዘጋጃ ቤት፣ አውቶብስ ተራ እና አካባቢያቸው።
• ማርቆስ መጋዘን፣ ቀጨኔ 8 ቁጥር ማዞሪያ፣ ቀጨኔ 1ኛ፣ 2ኛ እና 3ኛ መንገድ፣ ይመር ውኃ፣ መቀጠያ፣ 19 ታቦት ማደሪያ፣ መታፈሪ ሰፈር፣ ጴጥሮስ ሆስፒታል፣ ሽሮ ሜዳ እና አካባቢያቸው።
ከጠዋቱ 2፡00 – 10፡00
• አያት ለገጣፎ ሰብስቴሽን ፊትለፊት ያሉ ኮንዶሚኒየሞች፣ ክቡርደመና፣ ሰላም ቪሌጅ፣ ጣፎ ገብርኤል፣ ጋሪ ተራ፣ ባጃጅ ተራ እና አካባቢያቸው።
ከጠዋቱ 3፡00 – 10፡30
• ገላን፣ አራብሳ፣ እንጀራ ማምረቻ ፋብሪካ፣ ፕሮጀክት 13 አራብሳ ወታደር ሰፈር፣ ነጋ ቦንገር፣ ጀሶ ፋብሪካ፣ ብሔረፅጌ ቆዳ ፋብሪካ፣ ፓስታና መኮረኒ ፋብሪካ እና አካባቢያቸው።
• አባ ሳሙኤል፣ አቡሴራ፣ ሉግና፣ ዱፍና፣ ደበራ ጢኖ፣ ሻሸመኔ፣ ዱከም፣ በላይነህ ክንዴ፣ በስተቀኝ ያሉ ኢንዱስትሪዎች፣ ካፍ ማደያ እና አካባቢያቸው።
ከጠዋቱ 4፡30 – 11፡00
• መቐለ (ላቺ በከፊል)፣ ሀምዲያ ኢንዱስትሪ ዞን፣ ቀበሌ 03፣ ባህርዳር (አዲስ ዓለም)፣ ኦቪድ፣ ሰማኤታ፣ ሚሊኒየም ት/ቤት እና አካባቢያቸው።
ከጠዋቱ 1፡00 – 6፡00
• ወልዲያ፣ ይምርሃነ ክርስቶስ፣ ቢልባላ፣ ቂርቆስ፣ ሳሬዜና፣ ሶርባ፣ ላሊበላ፣ ገነተ ማርያም፣ ዘሃ፣ ሙቅ ውኃ፣ ተከዜ ገዳሜ፣ ኢርፋ ገለሶቴ እና አካባቢያቸው።
• ቅዱስ አርቢ፣ ዳቦ ከተማ፣ ቡርኮ፣ አይና ሚካኤል፣ ጭሮ፣ ሜኤሶ፣ አሰቦት እና አካባቢያቸው።
በመሆኑም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ደንበኞች የጥገና ሥራው እስኪጠናቀቅ እና የኃይል አቅርቦቱ ወደ መደበኛ ሁኔታው እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንዲጠብቁ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጠይቋል።
Seledadotio
Seledadotio
6 days ago
የኩርሙክ ወርቅ ማዕድን ሥራውን በነሐሴ ወር ሊጀምር መሆኑ ተገለጸ
👉የቻይናው ግዙፍ ወርቅ አምራች 9 በመቶ ድርሻ ለመውሰድ ተስማምቷል
የካናዳው ማዕድን አምራች ኩባንያ የሆነው አላይድ ጎልድ ኮርፖሬሽን በኢትዮጵያ የሚገኘውን ግዙፉን የኩርሙክ ወርቅ ማዕድን ማውጫ ፕሮጀክት ግንባታ አጠናቆ በመጪው የነሐሴ ወር ውስጥ ሥራ ሊጀምር መሆኑን አስታወቀ። ማዕድን ማውጫው ሥራውን ሲጀምር የመጀመሪያውን ወርቅ ምርት በቅርብ ሳምንታት ውስጥ ለገበያ ያቀርባል ተብሎ ይጠበቃል።
ይህ ወሳኝ መረጃ ይፋ የሆነው ከአላይድ ጎልድ እና ከቻይናው ዚጂን ጎልድ ኢንተርናሽናል ጋር የነበረው የ4 ቢሊዮን ዶላር የመገዛት ስምምነት መሰረዙን ተከትሎ ነው።
እንደሚታወሰው የቻይናው ኩባንያ አላይድ ጎልድን በአክሲዮን ለመግዛት አቅዶ አንዳንድ ቅድመ ሁኔታዎች በመዘግየታቸው የስምምነቱ የመጨረሻ የጊዜ ገደብ ሊከበር እንዳልቻለ አላይድ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ጠቅሷል።
ሆኖም ሁለቱ ኩባንያዎች ሙሉ ግዢውን በመሰረዝ ፋንታ በግንኙነታቸው ለመቀጠል እና አዲስ አጋርነት ለመፍጠር በመስማማታቸው ዚጂን ጎልድ በግምት 295 ሚሊዮን ዶላር ስትራቴጂካዊ ኢንቨስትመንት በአላይድ ጎልድ ላይ አድርጓል።
በዚህ አዲስ የኢንቨስትመንት ስምምነት መሠረት ዚጂን ጎልድ 12.8 ሚሊዮን መደበኛ አክሲዮኖችን የሚገዛ ሲሆን፣ ይህም የኩባንያውን 9.2 በመቶ ድርሻ እንዲይዝ ያስችለዋል።
አላይድ ጎልድ እንዳስታወቀው ከዚህ አጋርነት ከሚገኘው የገንዘብ መጠን ውስጥ ከፍተኛው ድርሻ ለኩባንያው ዕድገት ስትራቴጂ፣ ለአሰራር ማሻሻያ እና በተለይም በኢትዮጵያ የሚገኘውን የኩርሙክ ወርቅ ማዕድን ፕሮጀክት ግንባታ ወደ ምርት ለማሸጋገር ይውላል። ከዚህ በተጨማሪ በ ማሊ የሚገኘውን የሳዲዮላ ማዕድን ማስፋፊያ፣ በኮትዲዕፍዋር ያሉ የምርት ማሳደግ ሥራዎችን እና በሌሎችም አካባቢዎች የሚደረጉ የፍለጋ ሥራዎችን ፋይናንስ ለማድረግ ያገለግላል ብሏል።
የኩርሙክ ወርቅ ማዕድን ማውጫ ሥራውን መጀመር ለኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ ትልቅ ፋይዳ ያለው ሲሆን፣ የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሪ ግኝት ከማሳደግ ባለፈ ለአካባቢው ማህበረሰብ በርካታ የስራ እድሎችን ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል።
#ቅዳሜገበያ #etbusinessview #ethiopia #alliedgoldcorp #mali #cotedivoire #canada #china #zijingold Ministry of Finance - Ethiopia Ministry of Mines - Ethiopia Abiy Ahmed Ali
👉የቻይናው ግዙፍ ወርቅ አምራች 9 በመቶ ድርሻ ለመውሰድ ተስማምቷል
የካናዳው ማዕድን አምራች ኩባንያ የሆነው አላይድ ጎልድ ኮርፖሬሽን በኢትዮጵያ የሚገኘውን ግዙፉን የኩርሙክ ወርቅ ማዕድን ማውጫ ፕሮጀክት ግንባታ አጠናቆ በመጪው የነሐሴ ወር ውስጥ ሥራ ሊጀምር መሆኑን አስታወቀ። ማዕድን ማውጫው ሥራውን ሲጀምር የመጀመሪያውን ወርቅ ምርት በቅርብ ሳምንታት ውስጥ ለገበያ ያቀርባል ተብሎ ይጠበቃል።
ይህ ወሳኝ መረጃ ይፋ የሆነው ከአላይድ ጎልድ እና ከቻይናው ዚጂን ጎልድ ኢንተርናሽናል ጋር የነበረው የ4 ቢሊዮን ዶላር የመገዛት ስምምነት መሰረዙን ተከትሎ ነው።
እንደሚታወሰው የቻይናው ኩባንያ አላይድ ጎልድን በአክሲዮን ለመግዛት አቅዶ አንዳንድ ቅድመ ሁኔታዎች በመዘግየታቸው የስምምነቱ የመጨረሻ የጊዜ ገደብ ሊከበር እንዳልቻለ አላይድ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ጠቅሷል።
ሆኖም ሁለቱ ኩባንያዎች ሙሉ ግዢውን በመሰረዝ ፋንታ በግንኙነታቸው ለመቀጠል እና አዲስ አጋርነት ለመፍጠር በመስማማታቸው ዚጂን ጎልድ በግምት 295 ሚሊዮን ዶላር ስትራቴጂካዊ ኢንቨስትመንት በአላይድ ጎልድ ላይ አድርጓል።
በዚህ አዲስ የኢንቨስትመንት ስምምነት መሠረት ዚጂን ጎልድ 12.8 ሚሊዮን መደበኛ አክሲዮኖችን የሚገዛ ሲሆን፣ ይህም የኩባንያውን 9.2 በመቶ ድርሻ እንዲይዝ ያስችለዋል።
አላይድ ጎልድ እንዳስታወቀው ከዚህ አጋርነት ከሚገኘው የገንዘብ መጠን ውስጥ ከፍተኛው ድርሻ ለኩባንያው ዕድገት ስትራቴጂ፣ ለአሰራር ማሻሻያ እና በተለይም በኢትዮጵያ የሚገኘውን የኩርሙክ ወርቅ ማዕድን ፕሮጀክት ግንባታ ወደ ምርት ለማሸጋገር ይውላል። ከዚህ በተጨማሪ በ ማሊ የሚገኘውን የሳዲዮላ ማዕድን ማስፋፊያ፣ በኮትዲዕፍዋር ያሉ የምርት ማሳደግ ሥራዎችን እና በሌሎችም አካባቢዎች የሚደረጉ የፍለጋ ሥራዎችን ፋይናንስ ለማድረግ ያገለግላል ብሏል።
የኩርሙክ ወርቅ ማዕድን ማውጫ ሥራውን መጀመር ለኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ ትልቅ ፋይዳ ያለው ሲሆን፣ የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሪ ግኝት ከማሳደግ ባለፈ ለአካባቢው ማህበረሰብ በርካታ የስራ እድሎችን ይፈጥራል ተብሎ ይጠበቃል።
#ቅዳሜገበያ #etbusinessview #ethiopia #alliedgoldcorp #mali #cotedivoire #canada #china #zijingold Ministry of Finance - Ethiopia Ministry of Mines - Ethiopia Abiy Ahmed Ali
6 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የካናዳው የማዕድን ኩባንያ አላይድ ጎልድ ኮርፖሬሽን ከቻይናው ዚጂን ጎልድ ጋር አድርጎት የነበረውን አጠቃላይ የአደረጃጀት እና የግዥ ስምምነት ማቋረጡን ዛሬ ጁላይ 29 ቀን 2026 ይፋ አድርጓል። ሆኖም ኩባንያው በምትኩ ዚጂን ጎልድ 295 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ስትራቴጂካዊ ኢንቨስትመንት በኩባንያው ላይ ለማፍሰስ መስማማቱን አስታውቋል።
ይህ ወሳኝ የፋይናንስ ውሳኔ፣ በኢትዮጵያ፣ ማሊ እና ኮትዲቯር ለሚገኙት የኩባንያው የማዕድን ማውጣት ፕሮጀክቶች ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ይጠበቃል።
ሁለቱም ኩባንያዎች ቀደም ሲል የገቡት ስምምነት በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ (እስከ ዛሬ ጁላይ 29፣ 2026) ሊጠናቀቅ እንደማይችል በመገንዘባቸው ስምምነቱን በጋራ ስምምነት ሰርዘውታል። ለዚህም እንደ ዋና ምክንያት የተነሳው፣ እንደዚህ ዓይነት ግዙፍ የድንበር ዘለል የንግድ ዝውውሮች የሚያጋጥማቸው የውጭ ተጽዕኖ እና የሂደት ውስብስብነት መሆኑ ተገልጿል።
ከቀድሞው ስምምነት መቋረጥ ጋር በተጓዳኝ፣ ዚጂን ጎልድ በአላይድ ጎልድ ውስጥ 12.8 ሚሊዮን የተለመዱ አክሲዮኖችን ለመግዛት ተስማምቷል። በዚህም መሰረት እያንዳንዱ አክሲዮን አሁን ካለው የገበያ ዋጋ ብልጫ ባለው 32.55 የካናዳ ዶላር የሚሸጥ ይሆናል። ይህ ኢንቨስትመንት ሲጠናቀቅ ዚጂን ጎልድ የአላይድ ጎልድን 9.2 በመቶ አጠቃላይ ድርሻ የሚይዝ ሲሆን፣ ስምምነቱም በቶሮንቶ TSX እና በኒውዮርክ NYSE የአክሲዮን ገበያዎች ይሁንታን ካገኘ በኋላ በነሐሴ 10፣ 2026 አካባቢ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።
አላይድ ጎልድ ከዚህ ስትራቴጂካዊ ኢንቨስትመንት የሚያገኘውን የተጣራ ገቢ የኩባንያውን የእድገት እቅዶች ለማፋጠን ይጠቀምበታል። ከተዘረዘሩት ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች ውስጥ በኢትዮጵያ የሚገኘው ፕሮጀክት ዋነኛውን ስፍራ ይዟል። ኩባንያው በነሐሴ ወር ስራ ይጀምራል ተብሎ የሚጠበቀውን እና ከጥቂት ሳምንታት በኋላ የመጀመሪያውን ወርቅ ያመርታል ተብሎ የታቀደውን የኩርሙክ ወርቅ ማዕድን ፕሮጀክት ግንባታ ለማጠናቀቅ እና ምርት ለማሳደግ ይሰራል ብሏል።
ከዚህም በተጨማሪ በማሊ የሚገኘውን የሳዲዮላ ማዕድን ማውጫ በደረጃ ለማስፋፋት፣ እንዲሁም በኮትዲቯር ያለውን የምርት መጠን ለማሳደግ እና በአጠቃላይ በኩባንያው ስር ባሉ ቦታዎች አዳዲስ የማዕድን ፍለጋዎችን ለማካሄድ ይህ ገንዘብ ይውላል። ይህ እርምጃ አላይድ ጎልድ ኩባንያ ሙሉ በሙሉ በዚጂን ጎልድ ከመዋጥ አደጋ አምልጦ፣ ራሱን ችሎ በአፍሪካ ውስጥ ግንባር ቀደም የወርቅ አምራች ለመሆን የሚያደርገውን ጉዞ የሚያጠናክር ነው። የዘርፉ ባለሙያዎች ለዘ-ሐበሻ በሰጡት አስተያየት… በተለይም በኢትዮጵያ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለሚገኘው የኩርሙክ ፕሮጀክት፣ ይህ የፋይናንስ ፍሰት ስራውን በተያዘለት እቅድ መሰረት ለማስጀመር ወሳኝ ሚና ይጫወታል ተብሎ ተስፋ ተጥሎበታል።
ይህ ወሳኝ የፋይናንስ ውሳኔ፣ በኢትዮጵያ፣ ማሊ እና ኮትዲቯር ለሚገኙት የኩባንያው የማዕድን ማውጣት ፕሮጀክቶች ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ይጠበቃል።
ሁለቱም ኩባንያዎች ቀደም ሲል የገቡት ስምምነት በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ (እስከ ዛሬ ጁላይ 29፣ 2026) ሊጠናቀቅ እንደማይችል በመገንዘባቸው ስምምነቱን በጋራ ስምምነት ሰርዘውታል። ለዚህም እንደ ዋና ምክንያት የተነሳው፣ እንደዚህ ዓይነት ግዙፍ የድንበር ዘለል የንግድ ዝውውሮች የሚያጋጥማቸው የውጭ ተጽዕኖ እና የሂደት ውስብስብነት መሆኑ ተገልጿል።
ከቀድሞው ስምምነት መቋረጥ ጋር በተጓዳኝ፣ ዚጂን ጎልድ በአላይድ ጎልድ ውስጥ 12.8 ሚሊዮን የተለመዱ አክሲዮኖችን ለመግዛት ተስማምቷል። በዚህም መሰረት እያንዳንዱ አክሲዮን አሁን ካለው የገበያ ዋጋ ብልጫ ባለው 32.55 የካናዳ ዶላር የሚሸጥ ይሆናል። ይህ ኢንቨስትመንት ሲጠናቀቅ ዚጂን ጎልድ የአላይድ ጎልድን 9.2 በመቶ አጠቃላይ ድርሻ የሚይዝ ሲሆን፣ ስምምነቱም በቶሮንቶ TSX እና በኒውዮርክ NYSE የአክሲዮን ገበያዎች ይሁንታን ካገኘ በኋላ በነሐሴ 10፣ 2026 አካባቢ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።
አላይድ ጎልድ ከዚህ ስትራቴጂካዊ ኢንቨስትመንት የሚያገኘውን የተጣራ ገቢ የኩባንያውን የእድገት እቅዶች ለማፋጠን ይጠቀምበታል። ከተዘረዘሩት ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች ውስጥ በኢትዮጵያ የሚገኘው ፕሮጀክት ዋነኛውን ስፍራ ይዟል። ኩባንያው በነሐሴ ወር ስራ ይጀምራል ተብሎ የሚጠበቀውን እና ከጥቂት ሳምንታት በኋላ የመጀመሪያውን ወርቅ ያመርታል ተብሎ የታቀደውን የኩርሙክ ወርቅ ማዕድን ፕሮጀክት ግንባታ ለማጠናቀቅ እና ምርት ለማሳደግ ይሰራል ብሏል።
ከዚህም በተጨማሪ በማሊ የሚገኘውን የሳዲዮላ ማዕድን ማውጫ በደረጃ ለማስፋፋት፣ እንዲሁም በኮትዲቯር ያለውን የምርት መጠን ለማሳደግ እና በአጠቃላይ በኩባንያው ስር ባሉ ቦታዎች አዳዲስ የማዕድን ፍለጋዎችን ለማካሄድ ይህ ገንዘብ ይውላል። ይህ እርምጃ አላይድ ጎልድ ኩባንያ ሙሉ በሙሉ በዚጂን ጎልድ ከመዋጥ አደጋ አምልጦ፣ ራሱን ችሎ በአፍሪካ ውስጥ ግንባር ቀደም የወርቅ አምራች ለመሆን የሚያደርገውን ጉዞ የሚያጠናክር ነው። የዘርፉ ባለሙያዎች ለዘ-ሐበሻ በሰጡት አስተያየት… በተለይም በኢትዮጵያ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ለሚገኘው የኩርሙክ ፕሮጀክት፣ ይህ የፋይናንስ ፍሰት ስራውን በተያዘለት እቅድ መሰረት ለማስጀመር ወሳኝ ሚና ይጫወታል ተብሎ ተስፋ ተጥሎበታል።
6 days ago
የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት
ነገ ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦
✅ከጠዋቱ 4፡00 – 10፡00
👉ኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት፣ ችሎት አደባባይ፣ዘበኛ ሰፈር፣ ሾላ፣ ሰሜን ሆቴል ጫፍ፣ ቀለመወርቅ ት/ቤት፣ ዶሮ ተራ፣ ራስ ደስታ አካባቢ፣ አርበኞች ት/ቤት እና አካባቢው፣
👉ዕንቁላል ፋብሪካ፣ ሀግቤስ አራት መንታ፣ ጎጃም በረንዳ ፣ ጅንአድ፣ አበበች ጎበና፣ ቄጤማ ተራ፣ ፓስተር አደባባይ፣ አቤት ሆስፒታል፣ ቅዱስ ዮሐንስ ቤ/ክ፣ ዳትሰን ሰፈር፣ ሰን ሆቴልእና አካባቢው ፣
👉3ኛ ፖሊስ ጣቢያ፣ አዲስ አበባ ሜዲካል ኮሌጅ፣ተ/ሃይማኖት ቤ/ክ፣ አትክልት ተራ፣ ጣሊያን ሰፈር፣ ፒያሳ በከፊል፣ ማዘጋጃ ቤት፣ አውቶብስ ተራ እና አካባቢው ፣
👉ማርቆስ መጋዘን ፣ ቀጨኔ 8 ቁጥር ማዞሪያ፣ ቀጨኔ 1ኛ፣2ኛ እና 3ኛ መንገድ ፣ ይመር ውኃ ፣ መቀጠያ፣ 19 ታቦት ማደሪያ፣ መታፈሪ ሰፈር፣ ጴጥሮስ ሆስፒታል፣ ሽሮ ሜዳ እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 2፡00 – 10፡00
👉አያት ለገጣፎ ሰብስቴሽን ፊትለፊት ያሉ ኮንዶሚኒየሞች፣ ክቡርደመና፣ ሰላም ቪሌጅ፣ ጣፎ ገብርኤል፣ ጋሪ ተራ፣ ባጃጅ ተራ እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 3፡00 – 10፡30
👉ገላን አካበቢ፣ አራብሳ፣ እንጀራ ማምረቻ ፋብሪካ፣ ፕሮጀክት 13 አራብሳ ወታደር ሰፈር፣ ነጋ ቦንገር ዝቅ ብሎ፣ ጀሶ ፋብሪካ፣ ብሔረፅጌ ቆዳ ፋብሪካ ፣ ፓስታና መኮረኒ እና አካባቢው፣
👉አባ ሳሙኤል፣ አቡሴራ፣ ሉግና ፣ ዱፍና፣ ደበራ ጢኖ፣ ሻሸመኔ፣ ዱከም፣በላይነህ ክንዴ፣ በስተቀኝ ያሉ ኢንዱስትሪዎች፣ ካፍ ማደያ እና አካባቢው ፣
✅ከጠዋቱ 4፡30 – 11፡00
👉መቐለ- መቐለ ላቺ በከፊል፣ ሀምዲያ ኢንዱስትሪ ዞን፣ ቀበሌ 03 ፣ ባህርዳር - አዲስ ዓለም፣ ኦቪድ፣ ሰማኤታ፣ሚሊኒየም ት/ቤት እና አካባቢው ፣
✅ከጠዋቱ 1፡00 – 6፡00
👉ወልዲያ - ይምርሃነ-ክርስቶስ፣ ቢልባላ፣ ቂርቆስ፣ ሳሬዜና፣ ሶርባ፣ ላሊይበላ ከተማ፣ ገነተማርያም፣ ዘሃ፣ ሙቅውኃ፣ ተከዜ ገዳሜ፣ ኢርፋ ገለሶቴ እና አካባቢው ፣
👉ቅዱስ አርቢ፣ ዳቦከተማ፣ ቡርኮ፣ አይና ሚኬል እና አካባቢው፣ጭሮ፣ ሜኤሶ፣ አሰቦት እና አካባቢው የኃይል አቅርቦት ተቋርጦ ይቆያል፡፡
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግሰት እንድትጠብቁን እንጠይቃለን፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
ነገ ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦
✅ከጠዋቱ 4፡00 – 10፡00
👉ኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት፣ ችሎት አደባባይ፣ዘበኛ ሰፈር፣ ሾላ፣ ሰሜን ሆቴል ጫፍ፣ ቀለመወርቅ ት/ቤት፣ ዶሮ ተራ፣ ራስ ደስታ አካባቢ፣ አርበኞች ት/ቤት እና አካባቢው፣
👉ዕንቁላል ፋብሪካ፣ ሀግቤስ አራት መንታ፣ ጎጃም በረንዳ ፣ ጅንአድ፣ አበበች ጎበና፣ ቄጤማ ተራ፣ ፓስተር አደባባይ፣ አቤት ሆስፒታል፣ ቅዱስ ዮሐንስ ቤ/ክ፣ ዳትሰን ሰፈር፣ ሰን ሆቴልእና አካባቢው ፣
👉3ኛ ፖሊስ ጣቢያ፣ አዲስ አበባ ሜዲካል ኮሌጅ፣ተ/ሃይማኖት ቤ/ክ፣ አትክልት ተራ፣ ጣሊያን ሰፈር፣ ፒያሳ በከፊል፣ ማዘጋጃ ቤት፣ አውቶብስ ተራ እና አካባቢው ፣
👉ማርቆስ መጋዘን ፣ ቀጨኔ 8 ቁጥር ማዞሪያ፣ ቀጨኔ 1ኛ፣2ኛ እና 3ኛ መንገድ ፣ ይመር ውኃ ፣ መቀጠያ፣ 19 ታቦት ማደሪያ፣ መታፈሪ ሰፈር፣ ጴጥሮስ ሆስፒታል፣ ሽሮ ሜዳ እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 2፡00 – 10፡00
👉አያት ለገጣፎ ሰብስቴሽን ፊትለፊት ያሉ ኮንዶሚኒየሞች፣ ክቡርደመና፣ ሰላም ቪሌጅ፣ ጣፎ ገብርኤል፣ ጋሪ ተራ፣ ባጃጅ ተራ እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 3፡00 – 10፡30
👉ገላን አካበቢ፣ አራብሳ፣ እንጀራ ማምረቻ ፋብሪካ፣ ፕሮጀክት 13 አራብሳ ወታደር ሰፈር፣ ነጋ ቦንገር ዝቅ ብሎ፣ ጀሶ ፋብሪካ፣ ብሔረፅጌ ቆዳ ፋብሪካ ፣ ፓስታና መኮረኒ እና አካባቢው፣
👉አባ ሳሙኤል፣ አቡሴራ፣ ሉግና ፣ ዱፍና፣ ደበራ ጢኖ፣ ሻሸመኔ፣ ዱከም፣በላይነህ ክንዴ፣ በስተቀኝ ያሉ ኢንዱስትሪዎች፣ ካፍ ማደያ እና አካባቢው ፣
✅ከጠዋቱ 4፡30 – 11፡00
👉መቐለ- መቐለ ላቺ በከፊል፣ ሀምዲያ ኢንዱስትሪ ዞን፣ ቀበሌ 03 ፣ ባህርዳር - አዲስ ዓለም፣ ኦቪድ፣ ሰማኤታ፣ሚሊኒየም ት/ቤት እና አካባቢው ፣
✅ከጠዋቱ 1፡00 – 6፡00
👉ወልዲያ - ይምርሃነ-ክርስቶስ፣ ቢልባላ፣ ቂርቆስ፣ ሳሬዜና፣ ሶርባ፣ ላሊይበላ ከተማ፣ ገነተማርያም፣ ዘሃ፣ ሙቅውኃ፣ ተከዜ ገዳሜ፣ ኢርፋ ገለሶቴ እና አካባቢው ፣
👉ቅዱስ አርቢ፣ ዳቦከተማ፣ ቡርኮ፣ አይና ሚኬል እና አካባቢው፣ጭሮ፣ ሜኤሶ፣ አሰቦት እና አካባቢው የኃይል አቅርቦት ተቋርጦ ይቆያል፡፡
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግሰት እንድትጠብቁን እንጠይቃለን፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
7 days ago
የህዝቡን ሰቆቃ በማብዛትና በሞት አዋጅ የሚቀጥል ሕልውና የለም
******************
በትግራይ ሰማይ ስር፣ ተስፋው በጠመንጃ አፈሙዝ የተጠለፈበት፣ ህልሙ በግዴታ ጦርነት የተቀጨበት ወጣት ሰቆቃ ዛሬም ማብቂያ አላገኘም። እናት ልጇን ለትምህርት እና ለስራ ሳይሆን፣ ለማታውቀው እና ላላመነችበት የጥፋት ጦርነት እየተነጠቀች ባለችበት በዚህ አሳዛኝ ወቅት፣ የትግራይን ህዝብ ብሶት እና የወጣቱን ጩኸት ሊሰማ ያልፈለገው ህገወጥ ቡድን ዛሬም በወጣቱ እድል ላይ መቆመሩንና ነጋዴነቱን ቀጥሏል።
ዛሬ ላይ የትግራይ ወጣት ተስፋው ሲጨልምና ከስራ ፈጠራ ይልቅ ጠመንጃ ተሸከም ሲባል የቡድኑ መሪዎች ወርቅ በኮንትሮባንድ በማውጣት እና በህገወጥ ንግድ ላይ በስፋት ተጠምደዋል።
ከዚህም አልፎ ተራ ዜጎችን በማፈን፣ እንዲሁም እጅግ አሳዛኝ እና ዘግናኝ በሆነ ሁኔታ የትግራይን ህጻናት ለሱዳን ወታደራዊ ግዳጅ በመሸጥ የሰው ልጅ የንግድ ልውውጥ ወንጀል እየፈጸሙ ይገኛሉ። ይህ ድርጊት የቡድኑን ዝቅታና ያለበትን ሞራል ዝቅጠት ብሎም ለህዝቡ ያለውን ንቀት በግልጽ የሚያሳይ ነው።
በወጣቱ ላይ የተቃጣው የጭካኔ አዋጅ
የወጣቱን ጩኸት ማዳመጥ የተሳነው ይህ አፋኝ ቡድን፣ ህዝቡን ከራሱ ጋር ማሰለፍ ሲያቅተው ሰሞኑን ያወጣው የሞት አዋጅ የፋሺዝም እና የጭካኔው ማሳያ ነው።
ወደ ጦርነት ካልገቡ ወጣቶችን እና ዜጎችን እስከመግደል የሚያደርሰው ይህ አዋጅ፣ እጅግ ጸረ-ህዝብ እና ህገ-መንግስታዊነትን የጣሰ ነው። በዚህ በሰለጠነ ዘመን በየትኛውም የዓለም ክፍል ሊታሰብ የማይችል ይህ ጭካኔ የተሞላበት ህግ፣ ቡድኑ በህዝብ ላይ የተጫነ መቅሰፍት እንጂ የህዝብ ወገን አለመሆኑን ያረጋግጣል። የትግራይ ወጣት ህይወት ለቡድኑ መሪዎች የስልጣን እድሜ ማራዘሚያ ርካሽ ማገዶ ሆኖ ቀጥሏል።
ወጣቱ በግድያ እና በእስራት እየማቀቀ ባለበት በዚህ ሰዓት፣ የቡድኑ መሪዎች በሚስጥራዊ ስብሰባዎቻቸው ላይ የውጭ ኃይሎች ተሸክመው አዲስ አበባ እንደሚያስገቧቸው እና ስልጣን ላይ እንደሚያወጧቸው ሲያልሙ ይሰማሉ።
ይህ ከህዝብ የተነጠለ፣ የራሱ አቅም የሌለው እና የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለውጭ ኃይሎች አሳልፎ ለመስጠት የተዘጋጀ ርካሽ ስብስብ፣ የትግራይን ወጣት ሰቆቃ ሊሰማ ቀርቶ ሊረዳውም የሚችል የሞራል ልዕልና የለውም።
የቡድኑን ጸረ-ህዝብ አዋጅ እና የግድያ ዛቻ በመሸሽ፣ በርካታ የትግራይ ወጣቶች ስርዓቱን እያወገዙ ወደተለያዩ አካባቢዎች ለማምለጥ እየሞከሩ ነው። ይህ እርምጃ የወጣቱ እውነተኛ ጩኸት እና የተቃውሞ ድምጽ ነው። ከስርዓቱ ያመለጡ ወጣቶች የሚያስተላልፉት የእውነት ቃል፣ የትግራይ ህዝብ በቡድኑ ላይ ያለውን ምሬት እና የለውጥ ፍላጎት የሚያንጸባርቅ ነው።
በአጠቃላይ፣ የትግራይ ወጣት ከዚህ አቅመ-ቢስ፣ ተላላኪ እና ጨካኝ የሽፍታ ስብስብ ነጻ ወጥቶ ከታላቋ ኢትዮጵያ የልማት እና የሰላም ጉዞ ጋር መቆራኘት ይፈልጋል።
ዛሬም ኢትዮጵያ እንደትናንቱ የውስጥ ባንዳዎችን እና የውጭ ሴረኞችን እኩይ ምኞት እያከሸፈች፣ በልማት ሉዓላዊነቷን ታረጋግጣለች።
የትግራይም ወጣት የዚህ ትልቅ ሀገራዊ ጉዞ ማዕቀፍ አካል በመሆን የሰላም እና የብልጽግናው ተጠቃሚ የሚሆንበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም። የደም ነጋዴው እና ጩኸት አላዳምጥ ያለው ህገወጥ ቡድንም ይህ በህዝብ የመነገድ መንገዱ ማብቂያው ጊዜ ሩቅ አይደለም።
በመሀመድ ፊጣሞ
******************
በትግራይ ሰማይ ስር፣ ተስፋው በጠመንጃ አፈሙዝ የተጠለፈበት፣ ህልሙ በግዴታ ጦርነት የተቀጨበት ወጣት ሰቆቃ ዛሬም ማብቂያ አላገኘም። እናት ልጇን ለትምህርት እና ለስራ ሳይሆን፣ ለማታውቀው እና ላላመነችበት የጥፋት ጦርነት እየተነጠቀች ባለችበት በዚህ አሳዛኝ ወቅት፣ የትግራይን ህዝብ ብሶት እና የወጣቱን ጩኸት ሊሰማ ያልፈለገው ህገወጥ ቡድን ዛሬም በወጣቱ እድል ላይ መቆመሩንና ነጋዴነቱን ቀጥሏል።
ዛሬ ላይ የትግራይ ወጣት ተስፋው ሲጨልምና ከስራ ፈጠራ ይልቅ ጠመንጃ ተሸከም ሲባል የቡድኑ መሪዎች ወርቅ በኮንትሮባንድ በማውጣት እና በህገወጥ ንግድ ላይ በስፋት ተጠምደዋል።
ከዚህም አልፎ ተራ ዜጎችን በማፈን፣ እንዲሁም እጅግ አሳዛኝ እና ዘግናኝ በሆነ ሁኔታ የትግራይን ህጻናት ለሱዳን ወታደራዊ ግዳጅ በመሸጥ የሰው ልጅ የንግድ ልውውጥ ወንጀል እየፈጸሙ ይገኛሉ። ይህ ድርጊት የቡድኑን ዝቅታና ያለበትን ሞራል ዝቅጠት ብሎም ለህዝቡ ያለውን ንቀት በግልጽ የሚያሳይ ነው።
በወጣቱ ላይ የተቃጣው የጭካኔ አዋጅ
የወጣቱን ጩኸት ማዳመጥ የተሳነው ይህ አፋኝ ቡድን፣ ህዝቡን ከራሱ ጋር ማሰለፍ ሲያቅተው ሰሞኑን ያወጣው የሞት አዋጅ የፋሺዝም እና የጭካኔው ማሳያ ነው።
ወደ ጦርነት ካልገቡ ወጣቶችን እና ዜጎችን እስከመግደል የሚያደርሰው ይህ አዋጅ፣ እጅግ ጸረ-ህዝብ እና ህገ-መንግስታዊነትን የጣሰ ነው። በዚህ በሰለጠነ ዘመን በየትኛውም የዓለም ክፍል ሊታሰብ የማይችል ይህ ጭካኔ የተሞላበት ህግ፣ ቡድኑ በህዝብ ላይ የተጫነ መቅሰፍት እንጂ የህዝብ ወገን አለመሆኑን ያረጋግጣል። የትግራይ ወጣት ህይወት ለቡድኑ መሪዎች የስልጣን እድሜ ማራዘሚያ ርካሽ ማገዶ ሆኖ ቀጥሏል።
ወጣቱ በግድያ እና በእስራት እየማቀቀ ባለበት በዚህ ሰዓት፣ የቡድኑ መሪዎች በሚስጥራዊ ስብሰባዎቻቸው ላይ የውጭ ኃይሎች ተሸክመው አዲስ አበባ እንደሚያስገቧቸው እና ስልጣን ላይ እንደሚያወጧቸው ሲያልሙ ይሰማሉ።
ይህ ከህዝብ የተነጠለ፣ የራሱ አቅም የሌለው እና የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለውጭ ኃይሎች አሳልፎ ለመስጠት የተዘጋጀ ርካሽ ስብስብ፣ የትግራይን ወጣት ሰቆቃ ሊሰማ ቀርቶ ሊረዳውም የሚችል የሞራል ልዕልና የለውም።
የቡድኑን ጸረ-ህዝብ አዋጅ እና የግድያ ዛቻ በመሸሽ፣ በርካታ የትግራይ ወጣቶች ስርዓቱን እያወገዙ ወደተለያዩ አካባቢዎች ለማምለጥ እየሞከሩ ነው። ይህ እርምጃ የወጣቱ እውነተኛ ጩኸት እና የተቃውሞ ድምጽ ነው። ከስርዓቱ ያመለጡ ወጣቶች የሚያስተላልፉት የእውነት ቃል፣ የትግራይ ህዝብ በቡድኑ ላይ ያለውን ምሬት እና የለውጥ ፍላጎት የሚያንጸባርቅ ነው።
በአጠቃላይ፣ የትግራይ ወጣት ከዚህ አቅመ-ቢስ፣ ተላላኪ እና ጨካኝ የሽፍታ ስብስብ ነጻ ወጥቶ ከታላቋ ኢትዮጵያ የልማት እና የሰላም ጉዞ ጋር መቆራኘት ይፈልጋል።
ዛሬም ኢትዮጵያ እንደትናንቱ የውስጥ ባንዳዎችን እና የውጭ ሴረኞችን እኩይ ምኞት እያከሸፈች፣ በልማት ሉዓላዊነቷን ታረጋግጣለች።
የትግራይም ወጣት የዚህ ትልቅ ሀገራዊ ጉዞ ማዕቀፍ አካል በመሆን የሰላም እና የብልጽግናው ተጠቃሚ የሚሆንበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም። የደም ነጋዴው እና ጩኸት አላዳምጥ ያለው ህገወጥ ቡድንም ይህ በህዝብ የመነገድ መንገዱ ማብቂያው ጊዜ ሩቅ አይደለም።
በመሀመድ ፊጣሞ
Sponsored by
Surafel
7 days ago
በሆነ በዘመን የቀረውን እኔን የመለሰ አልበም!
የአህመድ ተሸመ (ዲንቢ) “ጊዜ አይሄድም”!
ተስፋዬ እሸቱ (ረ/ፕሮፌሰር)
#ethiopia | መቸም የአህመድ ተሾመ (ዲንቢ) ድንቅ የዜማ ደራሲነት ሰብዕና ለድርድር የሚቀርብ አይደለም፡፡ ለራሱ የሠራቸውን ዘግየት እናድርግና ለሌሎች የሙያ አጋሮቹ ሠርቶላቸው በብዙኋን አድማጮች ዘንድ ሰፊ ተቀባይነትን ያገኙትን የዜማ ድርሰቶቹን እንዘርዝር ብንል ጊዜም ሥፍራም አይበቃንም፡፡
እንደው ከግምታችን በላይ ስለሆነው ስለዲንቢ የላቀ የዜማ ደራሲነት ሰብዕና መሠረታዊ ግንዛቤ ሊያስጨብጠን ቢችል ግን ጥቂቱን ብቻ ከዚህ እንደሚከተለው እዘረዝርላችኋለሁ፡—
ለአሊ ቢራና ሄለን በርሄ - “ሲያዴ”፤ ለፀሀዬ ዮሐንስ - “ማን ልበልሽ”፤ ለማዲንጎ አፈወርቅ - “ላላተርፍ”፤ ለብዙአየሁ ደምሴ - “የህልሜ ንግስት”፤ ለዘቢባ ግርማ - “ገራገር”፤ ለኢሳያስ ታምራት - “እያዳነ ያማል”፤ ለታረቀኝ ሙሉ - “ስሚያቸው”፤ ለሚኪያስ ቸርነት - “ግርማ ሞገሴ”፤ ለሃይማኖት ግርማ - “ከዚራ ቁ-2”፤ ለግርማ ተፈራ - “ልዩ”፤ ለሀመልማል አባተ - “ሀሴት”፤ እና የመሳሰሉቱን የአህመድ ዲንቢን የዜማ ፈጠራዎች ከብዙ በጥቂቱ ማስታወስ ይቻላል፡፡
አንዳንድ ሙዚቃዎች ለጆሮ ብቻ አይሰሩም፤ ለስሜት ይደርሳሉ፤ ዛሬ ተሰርተው ግን ትዝታችንን ይመልሱልናል፡፡
አንዳንድ ዜማዎች፣ በውስጣችን የተከረቸሙ የጊዜ በሮችን ያንኳኳሉ፤ ይከፍታሉምም፡፡ በሮቹ ሲከፈቱ ደግሞ የተዘነጉ ፊቶች፣ የተለየናቸው ጓደኞች፣ የተራመድንባቸውን ጎዳናዎች… ብቻ ምኑ ቅጡ ትላንታችንን እንደ መጽሀፍ ይገልጡልናል፡፡ በሆነ ዘመን የቀረውን ማንነታችንን እንደገና ይመልሱልናል።
አህመድ ተሾመ (ዲንቢ) ከ14 ዓመታት በኋላ በአዲስ አልበሙ ሲመለስ፣ እኔ የሰማሁት የአዳዲስ ዜማዎች ስብስብን አይደለም። አንድ በሆነ ዘመን የነበረ የዜማ ሰዋሰውና በዚሁ ዜማ ምክንያት የተሰፋ፣ የምናፍቀውን ዘመን የመለሰልኝ ያህል ነው የተሰማኝ፡፡
ያ የኔ ዘመን የምለው “ዘጠናዎቹ”ን ነው፡፡
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ሆኜ የገባሁት በ1997 ዓ.ም. ነው። አይ፣ ተማሪነት! እንዴት ያለ ጣፋጭ፣ እንዴት ያለ የማይደገም ዘመን ነበር! ያ ዘመን ለእኔ የወጣትነት ወርቃማ ጠዋት ነበር። ዓለምን እንደ አዲስ ማየት የጀመርኩበት፤ ከተማዋን፣ ሕይወትን፣ ፍቅርን፣ ሐሳብንና ነፃነትን ለመጀመሪያ ጊዜ በሙሉ ልብ ያጣጣምኩበት ዘመን ነበር።
ያ ዘመን ከጓደኞቸ ጋር እንደፈለግን የኖርንበት ዘመን ነበር። በአደባባይ የተከራከርንበት፣ አለምን የጠየቅንበት፣ መንግሥትን ለመጀመሪያ ጊዜ የተቃወምንበት፣ ነፃነትን ያየንበት፣ ዜማን ያጣጣምንበት ወቅት ነበር። ያ ዘመን “ዘጠናዎቹ” ነበር፡፡
ያንን ዘመን ሁሌም እናፍቀዋለሁ፤ ምናልባትም የምናፍቀው ዘመኑን ራሱን አይደለም፤ በዚያ ዘመን ውስጥ የነበርነውን እሱን፣ እሷን፣እኔን፣እኛን ነው። እንደገና እንዲመጣም እመኛለሁ።
ማርሴል ፕሩስት የተባለ ፈረንሳያዊ የልብ ወለድ ጸሀፊና ሀያሲ ጥልቅ የሆነን ትዝታ አስበን ለማስታወስ በምናደርገው ጥረት አይመለስም፤ ነገር ግን የስሜት ሕዋሳችን በሚነካ አንድ ድንገተኛ ልምድ ሊቀሰቀስ ይችላል ይላል፡፡ ሙዚቃም ከእነዚህ የትዝታ ቀስቃሾች መካከል እጅግ ኃይለኛው ሳይሆን አይቀርም።
በዚህ ረገድ እንደ አህመድ ተሾመ ጥንቅቅ ተደርጎ የተሰራ ዜማ የተረሳ ግን ተደበቀ ስሜትን ይቀሰቅሳል፤ የጠፋ የሚመስለውን የዜማ ስልተ ምት ይመልሳል፤ በዘመን ጥላ ሥር ተደብቆ የኖረ ማንነት እንደገና ያነቃቃል።
በ1990ዎቹ የኢትዮጵያ ሙዚቃ የራሱ የሆነ የዜማ ሰዋሰው፣ ቀለምና የአወራረድ ለዛ ነበረው። ያ ዘመን ለእኔ ሙዚቃን ከመስማት ወደ ማዳመጥ የተሸጋገርኩበት ጊዜ ነው። ስለዚህ የዚያ ዘመን ዜማዎች በጆሮዬ ብቻ ተደምጠው አልቀሩም፤ በማንነቴ ውስጥ ህያው ናቸው።
እኔ የሙዚቃ ባለሙያ አይደለሁም፤ ሙዚቃን ግን በልቤ አዳምጠዋለሁ። በእኔ የዜማ አረዳድ፣ የዚያ ዘመን የዜማ አሠራሮች በቀላሉ የሚደገሙ አይደሉም። ምክንያቱም ዜማው የተፈጠረው በድምፅ ብቻ ሳይሆን፣ በዘመኑ መንፈስም ጭምር ነው። ከዚያ በኋላ የመጡት ዘመናት የራሳቸውን የሙዚቃ ቋንቋ ፈጥረዋል።
ያው ዘመን ሲለወጥ የዜማ ሰዋሰውም የሚለወጥ ይመስለኛል፡፡ ይህም የሥነ ጥበብ ተፈጥሯዊ ሂደት ነው፤ ዋናው ጉዳይ ግን በ1990ዎቹና ከዚያ በኋላ በመጡት ዜማዎች መካከል የተቋረጠ ነገር ያለ ይመስለኛል፡፡ መቆራረጡ ለሙዚቃ ባለሙያዎች ትልቅ የጥናት ርዕስ የሚሆንም ነው፡፡
ታዲያ የአህመድ ተሾመ አዲስ አልበም፣ የ1990ዎቹን የዜማ መንፈስ አገኘሁበት፤ የቀድሞውን በቀጥታ ሳይደግም፣ ያንን ለዛ በአዲስ ስልተ ምት የቀነበበ ዜማ ሆኖ አዳመጥኩት። ጉዳዩን ሳይንቲፊካሊ መግለጽ ባልችልም ልቤ ግን አልበሙ በዚያን ጊዜና በዛሬው የሙዚቃ ዘመን መካከል የተዘረጋ የዜማ ድልድይ እንደሆነ ይነግረኛል።
በአጠቃላይ ለእኔ፣ የአህመድ ተሾመ (ዲንቢ) ጊዜ አይሄድም አዲስ አልበም የአዳዲስ ዜማዎች ስብስብ ብቻ አይደለም። ካለፈ ጊዜና ትዝታ ጋር የተደረገ ውይይት ነው፤ ትናንትን ከዛሬ ጋር ያስታረቀ የዜማ ድልድይ ነው፤ በዘጠናዎቹ የቀረውን እኔን የመለሰ አልበም ነው። ይመችሽ ዲንቢ!!
ካላመናችሁኝ ደግሞ ከአዲስ አልበሙ መካከል "ጊዜ አይሄድም"፣"አይሽና"፣ "ይረፍዳል" እና "ህልም ነው" አድመጣችሁ ፍረዱኝ፤ ካጠፋሁ እኔ ሳልሆን ዲንቢ ይቀጣል፡፡
የአህመድ ተሸመ (ዲንቢ) “ጊዜ አይሄድም”!
ተስፋዬ እሸቱ (ረ/ፕሮፌሰር)
#ethiopia | መቸም የአህመድ ተሾመ (ዲንቢ) ድንቅ የዜማ ደራሲነት ሰብዕና ለድርድር የሚቀርብ አይደለም፡፡ ለራሱ የሠራቸውን ዘግየት እናድርግና ለሌሎች የሙያ አጋሮቹ ሠርቶላቸው በብዙኋን አድማጮች ዘንድ ሰፊ ተቀባይነትን ያገኙትን የዜማ ድርሰቶቹን እንዘርዝር ብንል ጊዜም ሥፍራም አይበቃንም፡፡
እንደው ከግምታችን በላይ ስለሆነው ስለዲንቢ የላቀ የዜማ ደራሲነት ሰብዕና መሠረታዊ ግንዛቤ ሊያስጨብጠን ቢችል ግን ጥቂቱን ብቻ ከዚህ እንደሚከተለው እዘረዝርላችኋለሁ፡—
ለአሊ ቢራና ሄለን በርሄ - “ሲያዴ”፤ ለፀሀዬ ዮሐንስ - “ማን ልበልሽ”፤ ለማዲንጎ አፈወርቅ - “ላላተርፍ”፤ ለብዙአየሁ ደምሴ - “የህልሜ ንግስት”፤ ለዘቢባ ግርማ - “ገራገር”፤ ለኢሳያስ ታምራት - “እያዳነ ያማል”፤ ለታረቀኝ ሙሉ - “ስሚያቸው”፤ ለሚኪያስ ቸርነት - “ግርማ ሞገሴ”፤ ለሃይማኖት ግርማ - “ከዚራ ቁ-2”፤ ለግርማ ተፈራ - “ልዩ”፤ ለሀመልማል አባተ - “ሀሴት”፤ እና የመሳሰሉቱን የአህመድ ዲንቢን የዜማ ፈጠራዎች ከብዙ በጥቂቱ ማስታወስ ይቻላል፡፡
አንዳንድ ሙዚቃዎች ለጆሮ ብቻ አይሰሩም፤ ለስሜት ይደርሳሉ፤ ዛሬ ተሰርተው ግን ትዝታችንን ይመልሱልናል፡፡
አንዳንድ ዜማዎች፣ በውስጣችን የተከረቸሙ የጊዜ በሮችን ያንኳኳሉ፤ ይከፍታሉምም፡፡ በሮቹ ሲከፈቱ ደግሞ የተዘነጉ ፊቶች፣ የተለየናቸው ጓደኞች፣ የተራመድንባቸውን ጎዳናዎች… ብቻ ምኑ ቅጡ ትላንታችንን እንደ መጽሀፍ ይገልጡልናል፡፡ በሆነ ዘመን የቀረውን ማንነታችንን እንደገና ይመልሱልናል።
አህመድ ተሾመ (ዲንቢ) ከ14 ዓመታት በኋላ በአዲስ አልበሙ ሲመለስ፣ እኔ የሰማሁት የአዳዲስ ዜማዎች ስብስብን አይደለም። አንድ በሆነ ዘመን የነበረ የዜማ ሰዋሰውና በዚሁ ዜማ ምክንያት የተሰፋ፣ የምናፍቀውን ዘመን የመለሰልኝ ያህል ነው የተሰማኝ፡፡
ያ የኔ ዘመን የምለው “ዘጠናዎቹ”ን ነው፡፡
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ሆኜ የገባሁት በ1997 ዓ.ም. ነው። አይ፣ ተማሪነት! እንዴት ያለ ጣፋጭ፣ እንዴት ያለ የማይደገም ዘመን ነበር! ያ ዘመን ለእኔ የወጣትነት ወርቃማ ጠዋት ነበር። ዓለምን እንደ አዲስ ማየት የጀመርኩበት፤ ከተማዋን፣ ሕይወትን፣ ፍቅርን፣ ሐሳብንና ነፃነትን ለመጀመሪያ ጊዜ በሙሉ ልብ ያጣጣምኩበት ዘመን ነበር።
ያ ዘመን ከጓደኞቸ ጋር እንደፈለግን የኖርንበት ዘመን ነበር። በአደባባይ የተከራከርንበት፣ አለምን የጠየቅንበት፣ መንግሥትን ለመጀመሪያ ጊዜ የተቃወምንበት፣ ነፃነትን ያየንበት፣ ዜማን ያጣጣምንበት ወቅት ነበር። ያ ዘመን “ዘጠናዎቹ” ነበር፡፡
ያንን ዘመን ሁሌም እናፍቀዋለሁ፤ ምናልባትም የምናፍቀው ዘመኑን ራሱን አይደለም፤ በዚያ ዘመን ውስጥ የነበርነውን እሱን፣ እሷን፣እኔን፣እኛን ነው። እንደገና እንዲመጣም እመኛለሁ።
ማርሴል ፕሩስት የተባለ ፈረንሳያዊ የልብ ወለድ ጸሀፊና ሀያሲ ጥልቅ የሆነን ትዝታ አስበን ለማስታወስ በምናደርገው ጥረት አይመለስም፤ ነገር ግን የስሜት ሕዋሳችን በሚነካ አንድ ድንገተኛ ልምድ ሊቀሰቀስ ይችላል ይላል፡፡ ሙዚቃም ከእነዚህ የትዝታ ቀስቃሾች መካከል እጅግ ኃይለኛው ሳይሆን አይቀርም።
በዚህ ረገድ እንደ አህመድ ተሾመ ጥንቅቅ ተደርጎ የተሰራ ዜማ የተረሳ ግን ተደበቀ ስሜትን ይቀሰቅሳል፤ የጠፋ የሚመስለውን የዜማ ስልተ ምት ይመልሳል፤ በዘመን ጥላ ሥር ተደብቆ የኖረ ማንነት እንደገና ያነቃቃል።
በ1990ዎቹ የኢትዮጵያ ሙዚቃ የራሱ የሆነ የዜማ ሰዋሰው፣ ቀለምና የአወራረድ ለዛ ነበረው። ያ ዘመን ለእኔ ሙዚቃን ከመስማት ወደ ማዳመጥ የተሸጋገርኩበት ጊዜ ነው። ስለዚህ የዚያ ዘመን ዜማዎች በጆሮዬ ብቻ ተደምጠው አልቀሩም፤ በማንነቴ ውስጥ ህያው ናቸው።
እኔ የሙዚቃ ባለሙያ አይደለሁም፤ ሙዚቃን ግን በልቤ አዳምጠዋለሁ። በእኔ የዜማ አረዳድ፣ የዚያ ዘመን የዜማ አሠራሮች በቀላሉ የሚደገሙ አይደሉም። ምክንያቱም ዜማው የተፈጠረው በድምፅ ብቻ ሳይሆን፣ በዘመኑ መንፈስም ጭምር ነው። ከዚያ በኋላ የመጡት ዘመናት የራሳቸውን የሙዚቃ ቋንቋ ፈጥረዋል።
ያው ዘመን ሲለወጥ የዜማ ሰዋሰውም የሚለወጥ ይመስለኛል፡፡ ይህም የሥነ ጥበብ ተፈጥሯዊ ሂደት ነው፤ ዋናው ጉዳይ ግን በ1990ዎቹና ከዚያ በኋላ በመጡት ዜማዎች መካከል የተቋረጠ ነገር ያለ ይመስለኛል፡፡ መቆራረጡ ለሙዚቃ ባለሙያዎች ትልቅ የጥናት ርዕስ የሚሆንም ነው፡፡
ታዲያ የአህመድ ተሾመ አዲስ አልበም፣ የ1990ዎቹን የዜማ መንፈስ አገኘሁበት፤ የቀድሞውን በቀጥታ ሳይደግም፣ ያንን ለዛ በአዲስ ስልተ ምት የቀነበበ ዜማ ሆኖ አዳመጥኩት። ጉዳዩን ሳይንቲፊካሊ መግለጽ ባልችልም ልቤ ግን አልበሙ በዚያን ጊዜና በዛሬው የሙዚቃ ዘመን መካከል የተዘረጋ የዜማ ድልድይ እንደሆነ ይነግረኛል።
በአጠቃላይ ለእኔ፣ የአህመድ ተሾመ (ዲንቢ) ጊዜ አይሄድም አዲስ አልበም የአዳዲስ ዜማዎች ስብስብ ብቻ አይደለም። ካለፈ ጊዜና ትዝታ ጋር የተደረገ ውይይት ነው፤ ትናንትን ከዛሬ ጋር ያስታረቀ የዜማ ድልድይ ነው፤ በዘጠናዎቹ የቀረውን እኔን የመለሰ አልበም ነው። ይመችሽ ዲንቢ!!
ካላመናችሁኝ ደግሞ ከአዲስ አልበሙ መካከል "ጊዜ አይሄድም"፣"አይሽና"፣ "ይረፍዳል" እና "ህልም ነው" አድመጣችሁ ፍረዱኝ፤ ካጠፋሁ እኔ ሳልሆን ዲንቢ ይቀጣል፡፡
8 days ago
የአሸናፊዎች አሸናፊ ውጊያ ይደረጋል‼️
ህወሃት የ 1983 ታሪክን እንደግማሁ እያለ ነው።
የሕወሓት ጽህፈት ቤት ሀላፊ ወይዘሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሄር (ሞንጆሪኖ) ከሰሞኑ በአንድ መድረክ ላይ አነጋጋሪ አስተያየት ሰጥተዋል፡፡ አሁን ከተጣመርናቸው ኃይሎች ጋር መዋጋታችን አይቀርም ብለዋል፡፡ የሀላፊዋ ንግግር የጽምዶ ኃይሎችን የትብብር መሰረት የሚያናጋ ነው ተብሏል፡፡
ወይዘሮ ፈትለወርቅ ቃል በቃል የተናገሩ፡-
‹‹ዋናው ነገር ብልፅግናን ለመጣል ፍላጎት ያሳይ እንጂ የትኛውም ስብስብ እርስ በራሱ እሳትና ጭድ ቢሆንም እንኳን አብረን እንሰራለን። ብልፅግናን ከጣልን በኃላ ደግሞ የአሸናፊዎች አሸናፊ ለመለየት ሌላ ዙር ፍልሚያ ይኖረናል።
ለዚህም እየተዘጋጀን ነው፤ ይህ በተለያየ መልክ የተጀመረውን ትብብራችንን ስናየው የተለያየ ፍላጎት ያለን ሃይሎች ሆነን ነው ትብብር እየፈጠርን ያለነው። በአላማ፣ በፕሮግም፣ ወደፊት በረዥም ጊዜ እቅድ ምናምን አንድ ነን ማለት አይደለም። ትብብራችን በዛች በምታገናኘን ነገር ብቻ ነው።
እኛ ከፋኖ የምንለይበት የፖለቲካ አቋም አለን። ከሻዕቢያ ይሁን ከሌሎች የተለያዩ ሃይሎች የምንለያይባቸው መዓት ጉዳዮች አሉ። አንድ የሚያደርገን ግን የብልፅግና ስርዓት የሁላችንም ስጋት ነው የሚለው ነው። ይቺ ብቻ ናት የምታገናኘን።
እንደ ተሞክሮ ልንወስደው የሚገባን ነገር ደግሞ እንኳን አሁን በብዙ ጉዳዮች ልዩነት ካለንና በዓላማ ከማንገናኛቸው የተለያዩ ሃይሎች ጋር የምንፈጥረው ትብብር ይቅርና ኢህአዴግም እኮ ፈርሷል።
ኢህአዴግ እኮ የኦሮሞ፣የአማራ፣የደቡብ ኢትዮጵያ ሃይሎች አራት ድርጅቶች አንድ ላይ ሆነን የፈጠርነውና በፕሮግራም ወይም አላማ አንድ የነበረ ድርጅት ነበር። ግንኙነታችንም ስትራቴጂካዊ ነበር[ታክቲካል አልነበረም] ፣ በተለያየ ቋንቋ የተፃፈች አንዲት ፕሮግራም ነበር የነበረችን።
ግንባር ከመሆናችን ውጭ አንድ ድርጅት ማለት ነበርን፤ በዚህ ደረጃ የነበርን ሰዎች እኮ ተካክደናል[እንኳን ይሄ በዓላማ ከማይመስሉን ሃይሎች ጋር የምንፈጥረው ትብብር ይቅርና]›› ወይዘሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሄር
Via :- Andafta
Seledadotio
Seledadotio
ህወሃት የ 1983 ታሪክን እንደግማሁ እያለ ነው።
የሕወሓት ጽህፈት ቤት ሀላፊ ወይዘሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሄር (ሞንጆሪኖ) ከሰሞኑ በአንድ መድረክ ላይ አነጋጋሪ አስተያየት ሰጥተዋል፡፡ አሁን ከተጣመርናቸው ኃይሎች ጋር መዋጋታችን አይቀርም ብለዋል፡፡ የሀላፊዋ ንግግር የጽምዶ ኃይሎችን የትብብር መሰረት የሚያናጋ ነው ተብሏል፡፡
ወይዘሮ ፈትለወርቅ ቃል በቃል የተናገሩ፡-
‹‹ዋናው ነገር ብልፅግናን ለመጣል ፍላጎት ያሳይ እንጂ የትኛውም ስብስብ እርስ በራሱ እሳትና ጭድ ቢሆንም እንኳን አብረን እንሰራለን። ብልፅግናን ከጣልን በኃላ ደግሞ የአሸናፊዎች አሸናፊ ለመለየት ሌላ ዙር ፍልሚያ ይኖረናል።
ለዚህም እየተዘጋጀን ነው፤ ይህ በተለያየ መልክ የተጀመረውን ትብብራችንን ስናየው የተለያየ ፍላጎት ያለን ሃይሎች ሆነን ነው ትብብር እየፈጠርን ያለነው። በአላማ፣ በፕሮግም፣ ወደፊት በረዥም ጊዜ እቅድ ምናምን አንድ ነን ማለት አይደለም። ትብብራችን በዛች በምታገናኘን ነገር ብቻ ነው።
እኛ ከፋኖ የምንለይበት የፖለቲካ አቋም አለን። ከሻዕቢያ ይሁን ከሌሎች የተለያዩ ሃይሎች የምንለያይባቸው መዓት ጉዳዮች አሉ። አንድ የሚያደርገን ግን የብልፅግና ስርዓት የሁላችንም ስጋት ነው የሚለው ነው። ይቺ ብቻ ናት የምታገናኘን።
እንደ ተሞክሮ ልንወስደው የሚገባን ነገር ደግሞ እንኳን አሁን በብዙ ጉዳዮች ልዩነት ካለንና በዓላማ ከማንገናኛቸው የተለያዩ ሃይሎች ጋር የምንፈጥረው ትብብር ይቅርና ኢህአዴግም እኮ ፈርሷል።
ኢህአዴግ እኮ የኦሮሞ፣የአማራ፣የደቡብ ኢትዮጵያ ሃይሎች አራት ድርጅቶች አንድ ላይ ሆነን የፈጠርነውና በፕሮግራም ወይም አላማ አንድ የነበረ ድርጅት ነበር። ግንኙነታችንም ስትራቴጂካዊ ነበር[ታክቲካል አልነበረም] ፣ በተለያየ ቋንቋ የተፃፈች አንዲት ፕሮግራም ነበር የነበረችን።
ግንባር ከመሆናችን ውጭ አንድ ድርጅት ማለት ነበርን፤ በዚህ ደረጃ የነበርን ሰዎች እኮ ተካክደናል[እንኳን ይሄ በዓላማ ከማይመስሉን ሃይሎች ጋር የምንፈጥረው ትብብር ይቅርና]›› ወይዘሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሄር
Via :- Andafta
Seledadotio
Seledadotio
9 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በጸጥታ እና ጂኦፖለቲካዊ ቀውሶች ምክንያት ከ6 እስከ 7 ዓመታት ገደማ ተጓትቶ የነበረው የኬፊ ጎልድ ኤንድ ኮፐር ኩባንያ 'የቱሉ ካፒ' የወርቅ ማዕድን ፕሮጀክት በመጨረሻም ወደ ግንባታ ምዕራፍ መግባቱ ተገለጸ።
ከአዲስ አበባ 360 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምዕራብ ኢትዮጵያ የሚገኘው ይህ ፕሮጀክት፣ ከ400 ሚሊዮን ዶላር በላይ የፋይናንስ ፓኬጅ የተመደበለት ሲሆን (የኢትዮጵያ መንግስት 20 ሚሊዮን ዶላር በማዋጣት የ17 በመቶ ድርሻ ይዟል)፣ በዓመት 166 ሺህ አውንስ ወርቅ የማምረት አቅም ይኖረዋል። ማዕድን ማውጣቱ ክፍት እና ከመሬት በታች የማውጣት ዘዴዎችን አጣምሮ የሚጠቀም ሲሆን፣ በ2027 መገባደጃ ላይ ስራ ጀምሮ በ2028 ሙሉ የማምረት አቅሙ ላይ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል።
የኩባንያው ስራ አስፈፃሚ ሃሪ አናግኖስታራስ-አዳምስ እንዳሉት፤ ይህ "ስትራቴጂካዊ የኢትዮጵያ ፕሮጀክት" አሁን ላይ 1 በመቶ ብቻ ያለውን የማዕድን ዘርፉን የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) አስተዋፅኦ በቀጣዩ አስርት ዓመት ውስጥ ወደ 10 በመቶ ለማሳደግ ለታለመው የመንግስት ዕቅድ ትልቅ ሚና ይጫወታል።
ይሁን እንጂ ኢትዮጵያ ይህንን እጅግ ከፍተኛ ሆነ የኢኮኖሚ ዕቅድ ለማሳካትና ማዕድን ዘርፉን እንደ አውስትራሊያ ለማሳደግ፣ እንደ ቱሉ ካፒ ፕሮጀክት ያጋጠማቸው ዓይነት የጸጥታ መደፍረስና የዓመታት መጓተት ዳግም እንዳይከሰት አስተማማኝ ሰላም ማረጋገጥ ዋነኛ ፈተናዋ ሆኖ ይቀጥላል። ፕሮጀክቱ ትርፋማነቱ (በተለይ አሁን ባለው የዓለም የወርቅ ዋጋ መጨመር) እጅግ አጓጊ ቢሆንም፣ ቀጣይነቱ የሚወሰነው በመሬት ላይ ባለው ፖለቲካዊ እና የጸጥታ መረጋጋት ላይ መሆኑን ባለሙያዎች ለዘ-ሐበሻ ተናግረዋል።
ከአዲስ አበባ 360 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምዕራብ ኢትዮጵያ የሚገኘው ይህ ፕሮጀክት፣ ከ400 ሚሊዮን ዶላር በላይ የፋይናንስ ፓኬጅ የተመደበለት ሲሆን (የኢትዮጵያ መንግስት 20 ሚሊዮን ዶላር በማዋጣት የ17 በመቶ ድርሻ ይዟል)፣ በዓመት 166 ሺህ አውንስ ወርቅ የማምረት አቅም ይኖረዋል። ማዕድን ማውጣቱ ክፍት እና ከመሬት በታች የማውጣት ዘዴዎችን አጣምሮ የሚጠቀም ሲሆን፣ በ2027 መገባደጃ ላይ ስራ ጀምሮ በ2028 ሙሉ የማምረት አቅሙ ላይ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል።
የኩባንያው ስራ አስፈፃሚ ሃሪ አናግኖስታራስ-አዳምስ እንዳሉት፤ ይህ "ስትራቴጂካዊ የኢትዮጵያ ፕሮጀክት" አሁን ላይ 1 በመቶ ብቻ ያለውን የማዕድን ዘርፉን የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) አስተዋፅኦ በቀጣዩ አስርት ዓመት ውስጥ ወደ 10 በመቶ ለማሳደግ ለታለመው የመንግስት ዕቅድ ትልቅ ሚና ይጫወታል።
ይሁን እንጂ ኢትዮጵያ ይህንን እጅግ ከፍተኛ ሆነ የኢኮኖሚ ዕቅድ ለማሳካትና ማዕድን ዘርፉን እንደ አውስትራሊያ ለማሳደግ፣ እንደ ቱሉ ካፒ ፕሮጀክት ያጋጠማቸው ዓይነት የጸጥታ መደፍረስና የዓመታት መጓተት ዳግም እንዳይከሰት አስተማማኝ ሰላም ማረጋገጥ ዋነኛ ፈተናዋ ሆኖ ይቀጥላል። ፕሮጀክቱ ትርፋማነቱ (በተለይ አሁን ባለው የዓለም የወርቅ ዋጋ መጨመር) እጅግ አጓጊ ቢሆንም፣ ቀጣይነቱ የሚወሰነው በመሬት ላይ ባለው ፖለቲካዊ እና የጸጥታ መረጋጋት ላይ መሆኑን ባለሙያዎች ለዘ-ሐበሻ ተናግረዋል።
9 days ago
✨ የዕለቱ የወርቅ ገበያ ዋጋ በኢትዮጵያ (በ1 ግራም)
24 ካራት ፡ 🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨 (20,896.94 ብር)
22 ካራት ፡ 🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨 (19,141.60 ብር)
21 ካራት ፡ 🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨 (18,284.82 ብር)
24 ካራት ፡ 🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨 (20,896.94 ብር)
22 ካራት ፡ 🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨 (19,141.60 ብር)
21 ካራት ፡ 🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨 (18,284.82 ብር)
9 days ago
እንኳን ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል አደረሳችሁ፤ አደረሰን🙏
ቅዱስ ገብርኤል የልባችሁን መልካም መሻት ይሙላላችሁ!!!
ነቢዩ ዳንኤል የመላእክት አለቃ የቅዱስ ገብርኤልን አስፈሪ ግርማ በተመለከተ ጊዜ “ዐይኖቼንም አነሣሁ “እነሆም በፍታ የለበሰውን ጥሩም የአፌዝን ወርቅ በወገቡ ላይ የታጠቀውን ሰው አየሁ፡፡ አካሉም እንደ ቢረሌ ይመስል ነበር፤ ፊቱም እንደ መብረቅ አምሳያ ነበረ፤ ዐይኖቹም እንደሚንበለበል ፋና፣ ክንዶቹና እግሮቹም እንደ ጋለ ናስ፣ የቃሉም ድምፅ እንደ ብዙ ሕዝብ ድምፅ ነበረ፡፡ ይህንም ታላቅ ራእይ አየሁ፤ ኀይልም አልቀረልኝም፤ ክብሬም ወደ ውርደት ተለወጠብኝ ኀይልም አጣሁ፡፡ የቃሉንም ድምፅ ሰማሁ፤ የቃሉን ድምፅ በሰማሁ ጊዜ ደንግጬ በምደር ላይ በግምባሬ ተደፋሁ” አለ፡፡ በዳንኤል 10÷5-9 የተገለጸው የዚህ መልአክ ግርማ የአምላክን ግርማ ይመስላል፡፡ ቅዱስ ገብርኤል የስሙ ትርጓሜ “አምላክ ወሰብእ” ሰውና አምላክ ማለት ሲሆን ከዋነኞቹ የመላዕክት አለቆች አንዱ ነው፡፡
ነቢዩ ኢሳይያስ በምዕራፍ 14÷16 በሰማያት የሳጥናኤል ትዕቢትና ውድቀት ምን እንደሚመስል ሲጽፍልን “አንተ በንጋት የሚወጣ አጥቢያ ኮከብ ሆይ እንዴት ከሰማይ ወደቅህ! ወደ አሕዛብ መልእክትን የላክ አንተ ሆይ እንዴት እስከ ምድር ድረስ ተቀጠቀጥህ! አንተም በልብህ ወደ ሰማይ ዐርጋለሁ ዙፋኔንም ከእግዚአብሔር ከዋክብት በላይ ከፍ ከፍ አደረጋለሁ፤ በልዑልም እመሰላለሁ አልህ፡፡ ዛሬ ግን ወደ ሲኦል ትወድቃለህ፤ ወደ ምደር ጥልቅም ትወርዳለህ” ይለናል፡፡ ቅዱስ ገብርኤል በቅድስና ሕይወት ለተጋውና በገዢዎች ዘንድ የእግዚአብሔር ቅዱስ መንፈስ ያደረበት ሰው ተብሎ ለተመሰገነው ለነቢዩ ዳንኤል ማስተዋልንና ጥበብን የሰጠ፣ እግዚአብሔር አምላክ የሰው ልጆችን ከሰይጣንና ከሞት ባርነት ነጻ ሊያወጣቸው ሰው እንደሚሆንና ሰማይንና ምድርን አሳልፎ በቅዱሳን ላይ ነግሦ እንደሚኖር በምሳሌ ገልጾ ያስተማረው መልአክ ነው፡፡
ቅዱስ ገብርኤል ቅዱሳንን ለእግዚአብሔር በመገዛታቸው ምክንያት ከአላውያን ገዢዎች ከሚደርስባቸው መከራም የሚታደጋቸው መልአክም ነው፡፡ ሦስቱ ሕጻናት አናንያ አዛርያና ሚሳኤል ለጣኦት አንሰግድም ባሉ ጊዜ በንጉሥ ናብከደነፆር ወደ እቶን እሳት ሲጣሉ እስራታቸውን ፈቶ፣ እሳቱን እንደ ውኃ አቀዝቅዞ ያዳናቸው ቅዱስ ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ ቅዱስ ቂርቆስንና እናቱ ቅድስት ኢየሉጣንም ከእሳት ያወጣ እርሱ ነው፡፡ የቅዱስ ገብርኤል ምልጃና ጸሎት ይጠብቀን፡፡ ዛሬም ይህን አማላጅነቱንና ፈጣን ተራዳኢነቱን ያመኑ ገዳማውያ አባቶች በጸሎታቸው ይጠሩታል እርሱም ይራዳቸዋል፡፡ እኛም ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና የበረከታቸው ተሳታፊ እንሆናለን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
ቅዱስ ገብርኤል የልባችሁን መልካም መሻት ይሙላላችሁ!!!
ነቢዩ ዳንኤል የመላእክት አለቃ የቅዱስ ገብርኤልን አስፈሪ ግርማ በተመለከተ ጊዜ “ዐይኖቼንም አነሣሁ “እነሆም በፍታ የለበሰውን ጥሩም የአፌዝን ወርቅ በወገቡ ላይ የታጠቀውን ሰው አየሁ፡፡ አካሉም እንደ ቢረሌ ይመስል ነበር፤ ፊቱም እንደ መብረቅ አምሳያ ነበረ፤ ዐይኖቹም እንደሚንበለበል ፋና፣ ክንዶቹና እግሮቹም እንደ ጋለ ናስ፣ የቃሉም ድምፅ እንደ ብዙ ሕዝብ ድምፅ ነበረ፡፡ ይህንም ታላቅ ራእይ አየሁ፤ ኀይልም አልቀረልኝም፤ ክብሬም ወደ ውርደት ተለወጠብኝ ኀይልም አጣሁ፡፡ የቃሉንም ድምፅ ሰማሁ፤ የቃሉን ድምፅ በሰማሁ ጊዜ ደንግጬ በምደር ላይ በግምባሬ ተደፋሁ” አለ፡፡ በዳንኤል 10÷5-9 የተገለጸው የዚህ መልአክ ግርማ የአምላክን ግርማ ይመስላል፡፡ ቅዱስ ገብርኤል የስሙ ትርጓሜ “አምላክ ወሰብእ” ሰውና አምላክ ማለት ሲሆን ከዋነኞቹ የመላዕክት አለቆች አንዱ ነው፡፡
ነቢዩ ኢሳይያስ በምዕራፍ 14÷16 በሰማያት የሳጥናኤል ትዕቢትና ውድቀት ምን እንደሚመስል ሲጽፍልን “አንተ በንጋት የሚወጣ አጥቢያ ኮከብ ሆይ እንዴት ከሰማይ ወደቅህ! ወደ አሕዛብ መልእክትን የላክ አንተ ሆይ እንዴት እስከ ምድር ድረስ ተቀጠቀጥህ! አንተም በልብህ ወደ ሰማይ ዐርጋለሁ ዙፋኔንም ከእግዚአብሔር ከዋክብት በላይ ከፍ ከፍ አደረጋለሁ፤ በልዑልም እመሰላለሁ አልህ፡፡ ዛሬ ግን ወደ ሲኦል ትወድቃለህ፤ ወደ ምደር ጥልቅም ትወርዳለህ” ይለናል፡፡ ቅዱስ ገብርኤል በቅድስና ሕይወት ለተጋውና በገዢዎች ዘንድ የእግዚአብሔር ቅዱስ መንፈስ ያደረበት ሰው ተብሎ ለተመሰገነው ለነቢዩ ዳንኤል ማስተዋልንና ጥበብን የሰጠ፣ እግዚአብሔር አምላክ የሰው ልጆችን ከሰይጣንና ከሞት ባርነት ነጻ ሊያወጣቸው ሰው እንደሚሆንና ሰማይንና ምድርን አሳልፎ በቅዱሳን ላይ ነግሦ እንደሚኖር በምሳሌ ገልጾ ያስተማረው መልአክ ነው፡፡
ቅዱስ ገብርኤል ቅዱሳንን ለእግዚአብሔር በመገዛታቸው ምክንያት ከአላውያን ገዢዎች ከሚደርስባቸው መከራም የሚታደጋቸው መልአክም ነው፡፡ ሦስቱ ሕጻናት አናንያ አዛርያና ሚሳኤል ለጣኦት አንሰግድም ባሉ ጊዜ በንጉሥ ናብከደነፆር ወደ እቶን እሳት ሲጣሉ እስራታቸውን ፈቶ፣ እሳቱን እንደ ውኃ አቀዝቅዞ ያዳናቸው ቅዱስ ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ ቅዱስ ቂርቆስንና እናቱ ቅድስት ኢየሉጣንም ከእሳት ያወጣ እርሱ ነው፡፡ የቅዱስ ገብርኤል ምልጃና ጸሎት ይጠብቀን፡፡ ዛሬም ይህን አማላጅነቱንና ፈጣን ተራዳኢነቱን ያመኑ ገዳማውያ አባቶች በጸሎታቸው ይጠሩታል እርሱም ይራዳቸዋል፡፡ እኛም ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና የበረከታቸው ተሳታፊ እንሆናለን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
9 days ago
በቦምባይ አውሮፕላን መጸዳጃ ቤት ውስጥ 12 ኪሎ ግራም ወርቅ ደብቀዋል የተባሉ ሶስት ኢትዮጵያውያን መያዛቸው ተሰማ
በህንድ ሙምባይ የሚገኘው የገቢዎች ደህንነት መመሪያ (DRI) ባለስልጣናት ከአዲስ አበባ በተነሳ አውሮፕላን መጸዳጃ ቤት ውስጥ በግምት 2.1 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣ 12 ኪሎ ግራም ወርቅ በድብቅ ይዘው የገቡ ሶስት የኢትዮጵያ ዜጎችን በቁጥጥር ስር ማዋላቸውን አስታወቁ።
ተጠርጣሪዎቹ አህመድ አብዱራህማን ፣ መሐመድ አብዱራህማን እና ጀሚል ኑሪ መሐመድ የተባሉ ሲሆን ባለፈው ሀሙስ ምሽት አውሮፕላኑ ሙምባይ እንዳረፈ ወዲያውኑ በቁጥጥር ስር ውለዋል ሲል ታይምስ ኦፍ ኢንዲያ ዘግቧል።
ባለስልጣናቱ ቀደም ብለው ባገኙት ጥቆማ መሰረት ፍተሻ ባካሄዱበት ወቅት በተጠርጣሪዎቹ የእጅ ቦርሳ ውስጥ የአውሮፕላኑን ግድግዳዎች መፍቻ መሳሪያዎችን አግኝተዋል።
በተደረገባቸው ጥብቅ ምርመራ፣ ወርቁን በአውሮፕላኑ የኋላ መጸዳጃ ቤት ግድግዳዎች ውስጥ ለመደበቅና በኋላም በአየር መንገድ የጽዳት ሰራተኞች አማካይነት ለማስወጣት ማቀዳቸውን አምነዋል።
ፍተሻውን ተከተሎም 6 የወርቅ ባር ብረቶች ተገኝተዋል።
ተጠርጣሪዎቹ የህንድን ህግ አያውቁም ቢሉም፣ ፍርድ ቤት በቁጥጥር ስር ውለው እንዲቆዩ ብይን አስተላልፎባቸዋል።
Seledadotio
Seledadotio
በህንድ ሙምባይ የሚገኘው የገቢዎች ደህንነት መመሪያ (DRI) ባለስልጣናት ከአዲስ አበባ በተነሳ አውሮፕላን መጸዳጃ ቤት ውስጥ በግምት 2.1 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣ 12 ኪሎ ግራም ወርቅ በድብቅ ይዘው የገቡ ሶስት የኢትዮጵያ ዜጎችን በቁጥጥር ስር ማዋላቸውን አስታወቁ።
ተጠርጣሪዎቹ አህመድ አብዱራህማን ፣ መሐመድ አብዱራህማን እና ጀሚል ኑሪ መሐመድ የተባሉ ሲሆን ባለፈው ሀሙስ ምሽት አውሮፕላኑ ሙምባይ እንዳረፈ ወዲያውኑ በቁጥጥር ስር ውለዋል ሲል ታይምስ ኦፍ ኢንዲያ ዘግቧል።
ባለስልጣናቱ ቀደም ብለው ባገኙት ጥቆማ መሰረት ፍተሻ ባካሄዱበት ወቅት በተጠርጣሪዎቹ የእጅ ቦርሳ ውስጥ የአውሮፕላኑን ግድግዳዎች መፍቻ መሳሪያዎችን አግኝተዋል።
በተደረገባቸው ጥብቅ ምርመራ፣ ወርቁን በአውሮፕላኑ የኋላ መጸዳጃ ቤት ግድግዳዎች ውስጥ ለመደበቅና በኋላም በአየር መንገድ የጽዳት ሰራተኞች አማካይነት ለማስወጣት ማቀዳቸውን አምነዋል።
ፍተሻውን ተከተሎም 6 የወርቅ ባር ብረቶች ተገኝተዋል።
ተጠርጣሪዎቹ የህንድን ህግ አያውቁም ቢሉም፣ ፍርድ ቤት በቁጥጥር ስር ውለው እንዲቆዩ ብይን አስተላልፎባቸዋል።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
11 days ago
ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ግዙፍ የወርቅ ማጣሪያ ፋብሪካ ግንባታ እያጠናቀቀች ነው
#ethiopia | ኢትዮጵያ ጥሬ ወርቅን ወደ ዱባይ በመላክ ለብዙ አስርት ዓመታት ስታካሂድ የቆየችውን አሰራር በማቆም የመጀመሪያውን ግዙፍ ሀገር በቀል የወርቅ ማጣሪያ ፋብሪካ ሥራ ለማስጀመር የመጨረሻ ዝግጅቷን እያጠናቀቀች ይገኛል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት ከእንግዲህ በሀገሪቱ የሚመረተው ማናቸውም ወርቅ ወደ ውጭ አገር ከመላኩ በፊት በሀገር ውስጥ ደረጃቸውን የጠበቁ የወርቅ አሞሌዎች ሆነው መጣራት ይኖርባቸዋል።
ይህ አዲስ አሰራር የሀገሪቱን የኤክስፖርት ገቢ ከፍ የሚያደርግ የውጭ ምንዛሬ ክምችትን የሚያጠናክር እና ሕገ-ወጥ የወርቅ ኮንትሮባንድን በከፍተኛ ደረጃ የሚቀንስ እንደሚሆን ታምኖበታል።
በአሁኑ ወቅት የመጨረሻውን የፍተሻ ምዕራፍ እያጠናቀቀ የሚገኘው ይህ ዘመናዊ ተቋም በበቀጣይ ዓመት ሥራ የሚጀምር ሲሆን እንደ ኩርሙክ የወርቅ ፕሮጀክት ያሉ አበይት የማዕድን ልማቶችን ጨምሮ እያደገ የመጣውን ሀገራዊ የወርቅ ምርት ሙሉ በሙሉ የሚያስተናግድ ይሆናል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | ኢትዮጵያ ጥሬ ወርቅን ወደ ዱባይ በመላክ ለብዙ አስርት ዓመታት ስታካሂድ የቆየችውን አሰራር በማቆም የመጀመሪያውን ግዙፍ ሀገር በቀል የወርቅ ማጣሪያ ፋብሪካ ሥራ ለማስጀመር የመጨረሻ ዝግጅቷን እያጠናቀቀች ይገኛል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት ከእንግዲህ በሀገሪቱ የሚመረተው ማናቸውም ወርቅ ወደ ውጭ አገር ከመላኩ በፊት በሀገር ውስጥ ደረጃቸውን የጠበቁ የወርቅ አሞሌዎች ሆነው መጣራት ይኖርባቸዋል።
ይህ አዲስ አሰራር የሀገሪቱን የኤክስፖርት ገቢ ከፍ የሚያደርግ የውጭ ምንዛሬ ክምችትን የሚያጠናክር እና ሕገ-ወጥ የወርቅ ኮንትሮባንድን በከፍተኛ ደረጃ የሚቀንስ እንደሚሆን ታምኖበታል።
በአሁኑ ወቅት የመጨረሻውን የፍተሻ ምዕራፍ እያጠናቀቀ የሚገኘው ይህ ዘመናዊ ተቋም በበቀጣይ ዓመት ሥራ የሚጀምር ሲሆን እንደ ኩርሙክ የወርቅ ፕሮጀክት ያሉ አበይት የማዕድን ልማቶችን ጨምሮ እያደገ የመጣውን ሀገራዊ የወርቅ ምርት ሙሉ በሙሉ የሚያስተናግድ ይሆናል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
11 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ከተማና አካባቢዋ ያለው የነዳጅ እጥረትና ሕገ-ወጥ ንግድ ከቀን ወደ ቀን እየተባባሰ መምጣቱና በአደባባይ ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ እየተደረገበት መሆኑ ተገለጸ። በአሁኑ ወቅት በከተማዋ አንድ ሊትር ነዳጅ በሕገ-ወጥ መንገድ ከ600 እስከ 700 ብር እየተቸበቸበ እንደሚገኝና ይህም በሕዝቡና በንግዱ ማኅበረሰብ ላይ ከባድ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጫና ማሳደሩ ተጠቁሟል።
በተለይም በክልሉ በወርቅና በሌሎች የማዕድን አምራችነት ዘርፎች የተሰማሩ ወገኖች በነዳጅ እጥረትና በዋጋው ንረት ሳቢያ ሥራቸውን ለማስቀጠል መቸገራቸውን ገልጸዋል። አምራቾቹ ሀብታቸውንና ጉልበታቸውን ፈስሰው ለአገሪቱ ኢኮኖሚ የራሳቸውን አስተዋጽኦ እያበረከቱ ቢቆዩም፣ አሁን ባለው የነዳጅ ኮንትሮባንድና ዋጋ ንረት ምክንያት ከስረው ከሥራ ውጭ ለመሆን መገደዳቸውን ለዘ-ሐበሻ ምሬታቸውን ገልጸዋል።
ነዋሪዎችና የማዕድን አምራቾች እንደሚያስረዱት፣ በከተማዋ በሚገኙ ዋና ዋና ማደያዎች (በተለይም ጎመጁ እና የተባበሩት ማደያዎች) ፊትለፊትና በየተለያዩ ቦታዎች ነዳጅ በግልጽ በኮንትሮባንድ መልክ ሲሸጥ የሕግ የበላይነትን ማስከበር የሚገባቸው አካላት ተገቢውን ቁጥጥርና እርምጃ ከመውሰድ ተቆጥበዋል ሲሉ ይከሳሉ። ድርጊቱ በጸጥታ አካላትና በንግድ ቢሮ በኩል ተገቢውን ክትትል ያጣና በጥቂት ጥቅም ፈላጊዎች የተደራጀ ብልሹ አሠራር ሰለባ የሆነ መሆኑን ተናግረዋል።
በመሆኑም አቤቱታ አቅራቢዎቹ የክልሉ መንግሥት እንዲሁም የሚመለከታቸው የፌዴራል አካላት በአሶሳ ከተማና አካባቢዋ ያለውን የነዳጅ ስርጭት ግልጽነትና ሕጋዊነት እንዲያረጋግጡ፣ በሕገ-ወጥ ነዳጅ ንግድና ሙስና ላይ የተሰማሩ አካላትን በሕግ እንዲጠይቁ እና ለአካባቢው ማዕድን አምራቾችና ነዋሪዎች አስቸኳይ መፍትሔ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል።
በተለይም በክልሉ በወርቅና በሌሎች የማዕድን አምራችነት ዘርፎች የተሰማሩ ወገኖች በነዳጅ እጥረትና በዋጋው ንረት ሳቢያ ሥራቸውን ለማስቀጠል መቸገራቸውን ገልጸዋል። አምራቾቹ ሀብታቸውንና ጉልበታቸውን ፈስሰው ለአገሪቱ ኢኮኖሚ የራሳቸውን አስተዋጽኦ እያበረከቱ ቢቆዩም፣ አሁን ባለው የነዳጅ ኮንትሮባንድና ዋጋ ንረት ምክንያት ከስረው ከሥራ ውጭ ለመሆን መገደዳቸውን ለዘ-ሐበሻ ምሬታቸውን ገልጸዋል።
ነዋሪዎችና የማዕድን አምራቾች እንደሚያስረዱት፣ በከተማዋ በሚገኙ ዋና ዋና ማደያዎች (በተለይም ጎመጁ እና የተባበሩት ማደያዎች) ፊትለፊትና በየተለያዩ ቦታዎች ነዳጅ በግልጽ በኮንትሮባንድ መልክ ሲሸጥ የሕግ የበላይነትን ማስከበር የሚገባቸው አካላት ተገቢውን ቁጥጥርና እርምጃ ከመውሰድ ተቆጥበዋል ሲሉ ይከሳሉ። ድርጊቱ በጸጥታ አካላትና በንግድ ቢሮ በኩል ተገቢውን ክትትል ያጣና በጥቂት ጥቅም ፈላጊዎች የተደራጀ ብልሹ አሠራር ሰለባ የሆነ መሆኑን ተናግረዋል።
በመሆኑም አቤቱታ አቅራቢዎቹ የክልሉ መንግሥት እንዲሁም የሚመለከታቸው የፌዴራል አካላት በአሶሳ ከተማና አካባቢዋ ያለውን የነዳጅ ስርጭት ግልጽነትና ሕጋዊነት እንዲያረጋግጡ፣ በሕገ-ወጥ ነዳጅ ንግድና ሙስና ላይ የተሰማሩ አካላትን በሕግ እንዲጠይቁ እና ለአካባቢው ማዕድን አምራቾችና ነዋሪዎች አስቸኳይ መፍትሔ እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል።
Comments