የኢትዮጵያ ኢንተርናሽናል ቴኳንዶ ቡድን በዓለም ሻምፒዮና ላይ ደማቅ ድል አስመዘገበ
#ethiopia | በደቡብ ኮሪያ ጊምቺዮን ከተማ ከሐምሌ 3 እስከ 6 ቀን 2018 ዓ.ም በተካሄደው የዓለም ሻምፒዮና ላይ የተሳተፈው የኢትዮጵያ ኢንተርናሽናል ቴኳንዶ ብሔራዊ ቡድን፣ በአጠቃላይ ዘጠኝ ሜዳሊያዎችን በመሰብሰብ ታሪካዊ ውጤት አስመዝግቧል።
ከ46 አገራት የተውጣጡ ከ2 ሺህ በላይ ስፖርተኞች በተሳተፉበት በዚህ ጠንካራ ውድድር ላይ፣ ለአምስት ወራት ያህል ዝግጅት ሲያደርግ የቆየው የሀገራችን ስብስብ ባሳየው አስደናቂ ብቃት የኢትዮጵያን ስም በዓለም አደባባይ ከፍ ማድረግ ችሏል።
የብሔራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ እና የልዑኩ መሪ ኢንተርናሽናል ኢንስፔክተር ማስተር ኤልያስ ኩመል እንደገለጹት፣ ውድድሩ እጅግ ፈታኝና አድካሚ የነበረ ቢሆንም ካደረጉት ጥልቅ ዝግጅት አንጻር የተጠበቀውን ስኬት ማምጣት ተችሏል።
ቡድኑ በአራት ተወዳዳሪዎች ብቻ በኢንተርናሽናል እና በኮፖት ቴኳንዶ የውድድር ዘርፎች የቀረበ ሲሆን፣ ሁሉም ተሳታፊዎች በየምድባቸው ሜዳሊያ ውስጥ መግባት ችለዋል። በዚህም ቡድኑ ሁለት የወርቅ፣ ሦስት የብር እና አራት የነሐስ ሜዳሊያዎችን በድምሩ ማሸነፍ ችሏል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia #taekwondo #worldchampionship #gimcheon2026 #teamethiopia #ethiopiansports
#ethiopia | በደቡብ ኮሪያ ጊምቺዮን ከተማ ከሐምሌ 3 እስከ 6 ቀን 2018 ዓ.ም በተካሄደው የዓለም ሻምፒዮና ላይ የተሳተፈው የኢትዮጵያ ኢንተርናሽናል ቴኳንዶ ብሔራዊ ቡድን፣ በአጠቃላይ ዘጠኝ ሜዳሊያዎችን በመሰብሰብ ታሪካዊ ውጤት አስመዝግቧል።
ከ46 አገራት የተውጣጡ ከ2 ሺህ በላይ ስፖርተኞች በተሳተፉበት በዚህ ጠንካራ ውድድር ላይ፣ ለአምስት ወራት ያህል ዝግጅት ሲያደርግ የቆየው የሀገራችን ስብስብ ባሳየው አስደናቂ ብቃት የኢትዮጵያን ስም በዓለም አደባባይ ከፍ ማድረግ ችሏል።
የብሔራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ እና የልዑኩ መሪ ኢንተርናሽናል ኢንስፔክተር ማስተር ኤልያስ ኩመል እንደገለጹት፣ ውድድሩ እጅግ ፈታኝና አድካሚ የነበረ ቢሆንም ካደረጉት ጥልቅ ዝግጅት አንጻር የተጠበቀውን ስኬት ማምጣት ተችሏል።
ቡድኑ በአራት ተወዳዳሪዎች ብቻ በኢንተርናሽናል እና በኮፖት ቴኳንዶ የውድድር ዘርፎች የቀረበ ሲሆን፣ ሁሉም ተሳታፊዎች በየምድባቸው ሜዳሊያ ውስጥ መግባት ችለዋል። በዚህም ቡድኑ ሁለት የወርቅ፣ ሦስት የብር እና አራት የነሐስ ሜዳሊያዎችን በድምሩ ማሸነፍ ችሏል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia #taekwondo #worldchampionship #gimcheon2026 #teamethiopia #ethiopiansports
25 days ago