Logo
Getu Temesgen
⚽️ በካፍ ቤት ምን እየተካሄደ ነው?
ለኢትዮጵያ ምን ይዞ ይመጣል? 🤔
#ethiopia | ​"ቄሱም ዝም መፅሀፉም ዝም... ኢትዮጵያ፣ ቦትስዋና ወይስ ደቡብ አፍሪካ?"

​ትናንት የተደረገው የካፍ ኤክስኪዩቲቭ ኮሚቴ ስብሰባ ብዙዎችን ግራ አጋብቷል። የ2028 የአፍሪካ ዋንጫ አዘጋጅ ሀገርን ይወስናል ተብሎ ቢጠበቅም፤ ነገሮች ባልተለመደ መልኩ ፀጥ ብለዋል።

​ጋዜጠኛ ዐቢይ ዘላለም እንደዘገበው ዋና ዋና ነጥቦች
እነዚህ ናቸው፡-

1️⃣ የገቢ ጉዳይ:
ስብሰባው በዋናነት ካፍ ከኮትዲቯር በኋላ የ90% የገቢ ጭማሪ ማሳየቱ እና ከ17 ግዙፍ ድርጅቶች ጋር መስራቱ እንደ ስኬት ተወርቶበታል።

2️⃣ ያልተጠበቀው ዜና:
ቦትስዋና ከደቡብ አፍሪካ ጋር በጋራ የ2028 ዋንጫን ለማዘጋጀት ጥያቄ ማቅረቧ ለኢትዮጵያ ያልተጠበቀ ክስተት ሆኗል።

3️⃣ የኢትዮጵያ ተስፋ:
ካፍ የመንግስትን (የጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይን) ከፍተኛ ቁርጠኝነት ቢወድም፤ "እንገነባለን" ከሚል ቃል ይልቅ "የተገነባ" ጋራንቲ ይፈልጋል።

4️⃣ ዲፕሎማሲ:
አቶ ኢሳያስ ጅራ ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ ቢሆንም፤ ኢትዮጵያ እንደ ድሮው (እንደ ይድነቃቸው ተሰማ ዘመን) በካፍ ተፅዕኖ ፈጣሪ አይደለችም።

​ዛሬ ምሽት ምን ይፈጠራል?

በሞሮኮ ሰዓት አቆጣጠር 7:00 (በእኛ ምሽት) ፕሬዝዳንቱ ፓትሪስ ሞትሴፔ ጋዜጣዊ መግለጫ ይሰጣሉ። ውሳኔው ምን ይሆን?
​"መንግስት የጀመረውን ስራ አጠናክሮ ይቀጥል፤ እድሉ ከተገኘ መልካም ካልሆነም ለወደፊቱ መሰረት ይሆናል!"
#ዐቢይ ዘላለም

​#caf #afcon2028 #ethiopia #football #abiyzelalem #patricemotsepe

7 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.