2 months ago
Yederaw Support:
አምስቱ ድምፅ አልባ ገዳዮች
#ethiopia | ምንም አይነት የህመም ስሜት ወይም ምልክት ሳያሳዩ በውስጣችን ለዓመታት በመደበቅ ድንገተኛ እና አደገኛ የጤና እክል ስለሚያደርሱ አምስት አደገኛ በሽታዎች (ድምፅ አልባ ገዳዮች)ን እንሆ
1. የደም ግፊት (Hypertension)
ይህ የጤና እክል በህክምናው ዓለም ቀዳሚው ድምፅ አልባ ገዳይ በመባል ይታወቃል። የደም ግፊት ምንም አይነት ምልክት ሳያሳይ የደም ቧንቧዎችን እያጠበበ እና እየጎዳ ለአስርት ዓመታት በሰውነታችን ውስጥ ሊቆይ ይችላል። በሽታው ስር እየሰደደ ሲሄድም ለድንገተኛ የጭንቅላት ውስጥ ደም መፍሰስ (ስትሮክ) እና ለልብ ድካም ይዳርጋል።
ይህንን ለመከላከል ጨው የበዛባቸውን ምግቦች ከአመጋገብ ውስጥ ማስወገድ፣ መደበኛ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ እንዲሁም ውጥረትና ጭንቀትን መቀነስ ይመከራል።
2. ከፍተኛ ኮሌስትሮል እና የደም ስር መጥበብ (Atherosclerosis) በደማችን ውስጥ ያለው ከመጠን ያለፈ ስብ (ኮሌስትሮል) የደም ስሮችን ቀስ በቀስ በመዝጋት የደም ቧንቧዎች ለዓመታት እንዲጠቡ ያደርጋል። እነዚህ የደም ቧንቧዎች ሙሉ በሙሉ ተዘግተው ድንገተኛ የልብ ድካም ወይም የጭንቅላት ውስጥ ደም መፍሰስ አደጋ እስከሚያደርሱ ድረስ ምንም አይነት ምልክት ላያሳዩ ይችላሉ።
ስብ የበዛባቸው እና የተቀነባበሩ ምግቦች፣ ከመጠን በላይ ውፍረት፣ ማጨስ፣ አልኮል ማብዛት እንዲሁም የዘር ውርስ ተጠቃሽ ናቸው።
3. ስር የሰደደ የኩላሊት በሽታ (Chronic Kidney Disease)
የዚህ በሽታ አስከፊነቱ ኩላሊት ከ90 በመቶ በላይ ሥራዋን እስክታቆም ድረስ ምንም ምልክት አለማሳየቱ ነው። አንድ ሰው በሽታው ገብቶበት ሰውነቱ ማበጥ ከጀመረ በኋላ ወደ ህክምና ተቋም ቢሄድ ለህክምና ጊዜው እንደረፈደ ሊቆጠር ይችላል።
አይነት 2 የስኳር በሽታ፣ የደም ግፊት፣ ውፍረት፣ ማጨስ፣ የኩላሊት ኢንፌክሽን ወይም ጠጠር፣ የሽንት ፊኛ መዘጋት፣ የህመም ማስታገሻዎችን አብዝቶ መውሰድ እና በቂ ውሃ አለመጠጣት ችግሩን ያፋጥኑታል።
4. አይነት 2 የስኳር በሽታ (Type 2 Diabetes)
ይህ በሽታ ጸጥ ብሎ በመቆየት አብዛኛውን ጊዜ ምልክቱ የሚታወቀው እይታችንን ስናጣ ወይም ከባድ የነርቭ ጉዳት ሲደርስብን ነው።
* እንዴት ይከሰታል? ከፍተኛ ስኳር እና የተቀነባበረ ካርቦሀይድሬት ያለው ምግብ አብዝቶ መጠቀም ጣፊያችን ኢንሱሊን ቶሎ ቶሎ እንድታመነጭ ያስገድዳታል፤ በዚህም ሴሎች ኢንሱሊኑን በመላመድ በሽታው ይከሰታል። በተጨማሪም የአካል ብቃት እንቅስቃሴ አለማድረግ ጡንቻዎቻችን ግሉኮስን እንዳያቃጥሉ በማድረግ ስኳር በደማችን ውስጥ ለረጅም ሰዓት ቆይቶ የደም ቧንቧዎችን እንዲጎዳ ያደርጋል።
5. የጉበት ስብ (Fatty Liver)
በመጨረሻም የምንመለከተው የጉበት ላይ ስብ ክምችትን ነው። ጉበት ህመም ተቀባይ ነርቮች (Pain Receptors) ስለሌሉት፣ ከመጠን በላይ ስብ በውስጡ ሲጠራቀም ምንም አይነት የህመም ስሜት አይሰማንም። ሆኖም ግን ጉበታችን በዝምታ ለረጅም ጊዜ እየተጎዳ ቆይቶ በመጨረሻም 'ሲርሆሲስ' (Cirrhosis) ለተባለ የጉበት ሥራ ማቆም ችግር ይዳርጋል።
ከመጠን በላይ ውፍረት፣ አልኮል አብዝቶ መጠጣት እንዲሁም የስኳር እና የከፍተኛ ኮሌስትሮል ህመሞች በበሽታው የመያዝ እድልን በእጅጉ ከፍ ያደርጋሉ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #አራዳFM #ዜና_ጤና #ጤና #ድምፅ_አልባ_ገዳዮች #የደም_ግፊት #ስኳር_በሽታ #ኩላሊት #የጉበት_ስብ #ኮሌስትሮል #silentkillers #healthnewsethiopia
"ለሚጥል በሽታ መቆጣጠሪያ የሚያገለግለው ፌንቶይን ታብሌት የጥራት ችግር አለበት" - የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት|
#ethiopia | የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የባሕር ዳር ቅርንጫፍ ሜዲካመን ባዮቴክ ሊሚትድ በተባለ ኩባንያ የተመሠረተ ለሚጥል በሽታ (Epilepsy) መቆጣጠሪያ የሚያገለግለውን የፌንቶይን 100 ሚሊ ግራም (Phenytoin 100 mg) ታብሌት መድኃኒት የጥራት ችግር ስላለበት ከጤና ተቋማት በአስቸኳይ እንዲሰበሰብ በደብዳቤ ማዘዙን ታውቋል።
የቅርንጫፍ መሥራያ ቤቱ ለሁሉም የጤና ተቋማት በጻፈው ደብዳቤ ላይ እንደገለጸው በአምራቹ የተመረቱት የዚህ መድኃኒት ባቾች በሙሉ የጥራት ደረጃውን ባለማሟላታቸው ተመላሽ እንዲያደርጉ ማሳሰቢያ ሰጥቷል።
ይኹን እንጅ መድኃኒቱን ያልመለሱ ተቋማት ያላቸውን ቀሪ መጠን በደብዳቤ ገልጸው እስከ መጋቢት 18 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ እንዲመልሱ ጥብቅ ማሳሰቢያ ቢሰጥም አንዳንድ የጤና ተቋማት መድኃኒቱን አለመመለሳቸውን አገልግሎቱ አሳውቋል።
ይህንን ትዕዛዝ ተላልፈው መድኃኒቱን ተመላሽ የማያደርጉ ተቋማት ለሚከሰት የጤና መታወክ ሙሉ ኃላፊነቱን እንደሚወስዱ አሳስቧል።
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት በመረጃው በጠቀሰው ባች የተመረተው ምርት ከ19ኙም የመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎቶች እንዲሰበሰቡ ነው ያዘዘው።
ዜጎች ለሚጥል በሽታ መድኃኒት ሲጠቀሙ በጤና ባለሙያ የታዘዘላቸው እና ጥራቱ የተረጋገጠ መኾኑን እንዲያረጋግጡ ይመክራል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #nbc #tablet #addis #warning #new
አምስቱ ድምፅ አልባ ገዳዮች
#ethiopia | ምንም አይነት የህመም ስሜት ወይም ምልክት ሳያሳዩ በውስጣችን ለዓመታት በመደበቅ ድንገተኛ እና አደገኛ የጤና እክል ስለሚያደርሱ አምስት አደገኛ በሽታዎች (ድምፅ አልባ ገዳዮች)ን እንሆ
1. የደም ግፊት (Hypertension)
ይህ የጤና እክል በህክምናው ዓለም ቀዳሚው ድምፅ አልባ ገዳይ በመባል ይታወቃል። የደም ግፊት ምንም አይነት ምልክት ሳያሳይ የደም ቧንቧዎችን እያጠበበ እና እየጎዳ ለአስርት ዓመታት በሰውነታችን ውስጥ ሊቆይ ይችላል። በሽታው ስር እየሰደደ ሲሄድም ለድንገተኛ የጭንቅላት ውስጥ ደም መፍሰስ (ስትሮክ) እና ለልብ ድካም ይዳርጋል።
ይህንን ለመከላከል ጨው የበዛባቸውን ምግቦች ከአመጋገብ ውስጥ ማስወገድ፣ መደበኛ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ እንዲሁም ውጥረትና ጭንቀትን መቀነስ ይመከራል።
2. ከፍተኛ ኮሌስትሮል እና የደም ስር መጥበብ (Atherosclerosis) በደማችን ውስጥ ያለው ከመጠን ያለፈ ስብ (ኮሌስትሮል) የደም ስሮችን ቀስ በቀስ በመዝጋት የደም ቧንቧዎች ለዓመታት እንዲጠቡ ያደርጋል። እነዚህ የደም ቧንቧዎች ሙሉ በሙሉ ተዘግተው ድንገተኛ የልብ ድካም ወይም የጭንቅላት ውስጥ ደም መፍሰስ አደጋ እስከሚያደርሱ ድረስ ምንም አይነት ምልክት ላያሳዩ ይችላሉ።
ስብ የበዛባቸው እና የተቀነባበሩ ምግቦች፣ ከመጠን በላይ ውፍረት፣ ማጨስ፣ አልኮል ማብዛት እንዲሁም የዘር ውርስ ተጠቃሽ ናቸው።
3. ስር የሰደደ የኩላሊት በሽታ (Chronic Kidney Disease)
የዚህ በሽታ አስከፊነቱ ኩላሊት ከ90 በመቶ በላይ ሥራዋን እስክታቆም ድረስ ምንም ምልክት አለማሳየቱ ነው። አንድ ሰው በሽታው ገብቶበት ሰውነቱ ማበጥ ከጀመረ በኋላ ወደ ህክምና ተቋም ቢሄድ ለህክምና ጊዜው እንደረፈደ ሊቆጠር ይችላል።
አይነት 2 የስኳር በሽታ፣ የደም ግፊት፣ ውፍረት፣ ማጨስ፣ የኩላሊት ኢንፌክሽን ወይም ጠጠር፣ የሽንት ፊኛ መዘጋት፣ የህመም ማስታገሻዎችን አብዝቶ መውሰድ እና በቂ ውሃ አለመጠጣት ችግሩን ያፋጥኑታል።
4. አይነት 2 የስኳር በሽታ (Type 2 Diabetes)
ይህ በሽታ ጸጥ ብሎ በመቆየት አብዛኛውን ጊዜ ምልክቱ የሚታወቀው እይታችንን ስናጣ ወይም ከባድ የነርቭ ጉዳት ሲደርስብን ነው።
* እንዴት ይከሰታል? ከፍተኛ ስኳር እና የተቀነባበረ ካርቦሀይድሬት ያለው ምግብ አብዝቶ መጠቀም ጣፊያችን ኢንሱሊን ቶሎ ቶሎ እንድታመነጭ ያስገድዳታል፤ በዚህም ሴሎች ኢንሱሊኑን በመላመድ በሽታው ይከሰታል። በተጨማሪም የአካል ብቃት እንቅስቃሴ አለማድረግ ጡንቻዎቻችን ግሉኮስን እንዳያቃጥሉ በማድረግ ስኳር በደማችን ውስጥ ለረጅም ሰዓት ቆይቶ የደም ቧንቧዎችን እንዲጎዳ ያደርጋል።
5. የጉበት ስብ (Fatty Liver)
በመጨረሻም የምንመለከተው የጉበት ላይ ስብ ክምችትን ነው። ጉበት ህመም ተቀባይ ነርቮች (Pain Receptors) ስለሌሉት፣ ከመጠን በላይ ስብ በውስጡ ሲጠራቀም ምንም አይነት የህመም ስሜት አይሰማንም። ሆኖም ግን ጉበታችን በዝምታ ለረጅም ጊዜ እየተጎዳ ቆይቶ በመጨረሻም 'ሲርሆሲስ' (Cirrhosis) ለተባለ የጉበት ሥራ ማቆም ችግር ይዳርጋል።
ከመጠን በላይ ውፍረት፣ አልኮል አብዝቶ መጠጣት እንዲሁም የስኳር እና የከፍተኛ ኮሌስትሮል ህመሞች በበሽታው የመያዝ እድልን በእጅጉ ከፍ ያደርጋሉ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #አራዳFM #ዜና_ጤና #ጤና #ድምፅ_አልባ_ገዳዮች #የደም_ግፊት #ስኳር_በሽታ #ኩላሊት #የጉበት_ስብ #ኮሌስትሮል #silentkillers #healthnewsethiopia
"ለሚጥል በሽታ መቆጣጠሪያ የሚያገለግለው ፌንቶይን ታብሌት የጥራት ችግር አለበት" - የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት|
#ethiopia | የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የባሕር ዳር ቅርንጫፍ ሜዲካመን ባዮቴክ ሊሚትድ በተባለ ኩባንያ የተመሠረተ ለሚጥል በሽታ (Epilepsy) መቆጣጠሪያ የሚያገለግለውን የፌንቶይን 100 ሚሊ ግራም (Phenytoin 100 mg) ታብሌት መድኃኒት የጥራት ችግር ስላለበት ከጤና ተቋማት በአስቸኳይ እንዲሰበሰብ በደብዳቤ ማዘዙን ታውቋል።
የቅርንጫፍ መሥራያ ቤቱ ለሁሉም የጤና ተቋማት በጻፈው ደብዳቤ ላይ እንደገለጸው በአምራቹ የተመረቱት የዚህ መድኃኒት ባቾች በሙሉ የጥራት ደረጃውን ባለማሟላታቸው ተመላሽ እንዲያደርጉ ማሳሰቢያ ሰጥቷል።
ይኹን እንጅ መድኃኒቱን ያልመለሱ ተቋማት ያላቸውን ቀሪ መጠን በደብዳቤ ገልጸው እስከ መጋቢት 18 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ እንዲመልሱ ጥብቅ ማሳሰቢያ ቢሰጥም አንዳንድ የጤና ተቋማት መድኃኒቱን አለመመለሳቸውን አገልግሎቱ አሳውቋል።
ይህንን ትዕዛዝ ተላልፈው መድኃኒቱን ተመላሽ የማያደርጉ ተቋማት ለሚከሰት የጤና መታወክ ሙሉ ኃላፊነቱን እንደሚወስዱ አሳስቧል።
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት በመረጃው በጠቀሰው ባች የተመረተው ምርት ከ19ኙም የመድኃኒት አቅራቢ አገልግሎቶች እንዲሰበሰቡ ነው ያዘዘው።
ዜጎች ለሚጥል በሽታ መድኃኒት ሲጠቀሙ በጤና ባለሙያ የታዘዘላቸው እና ጥራቱ የተረጋገጠ መኾኑን እንዲያረጋግጡ ይመክራል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #nbc #tablet #addis #warning #new
3 months ago
🚨 አስቸኳይ የጥቆማ ጥሪ 🚨
በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ፣ በሚሊኒየም አዳራሽ አቅራቢያ የሚገኘው አዶርሰም ሕንፃ (Adorsom Building) 2ኛ ፎቅ ላይ የሚገኝ ቢሮ ተዘርፏል። እነዚህ በምስሉ ላይ የምታዩዋቸው የአድዋን ድል ቀን በድፍረት ንብረት ዘርፈው ተሰውረዋል።
⚠️ የተዘረፉ ንብረቶች፦
ከፍተኛ ዋጋ ያላቸው ላፕቶፕ ኮምፒውተሮች
ታብሌቶች (Tablets)p
ፕሮፌሽናል የፎቶና የቪዲዮ ካሜራዎች
የተለያዩ የስልክ መሣሪያዎች
🔍 የሌቦቹ ሁኔታ፦
ሌቦቹ የቢሮውን የደህንነት ካሜራ (Footage) ለማጥፋትና መረጃ ለመሰወር ቢሞክሩም፣ በሌሎች የሕንፃው መቆጣጠሪያ ካሜራዎች ላይ ማንነታቸው በግልጽ ሊታወቅ ችሏል።
🙏 የዜግነት ግዴታዎን ይወጡ!
እነዚህን ግለሰቦች የምታውቁ፣ ያያችሁ ወይም በተመሳሳይ ሁኔታ ዝርፊያ የተፈጸመባችሁ ወገኖች ጥቆማ በማድረግ እንድትተባበሩ ጥሪ ቀርቧል።
✅ ለጥቆማው ተገቢው ወሮታ ይከፈላል!
ጥቆማ ለማድረስ፦
📍 ቦሌ አደይ አበባ ፖሊስ ጣቢያ በአካል በመቅረብ ወይም
📞 በስልክ ቁጥሮች፦ 0988188890 ወይም 0907247454 ይደውሉ።
የሌቦቹን ፎቶ በማየትና ይህን መረጃ ሼር (Share) በማድረግ ወንጀለኞቹ ለሕግ እንዲቀርቡ ይተባበሩ! ወንጀልን በጋራ እንከላከል!
በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ፣ በሚሊኒየም አዳራሽ አቅራቢያ የሚገኘው አዶርሰም ሕንፃ (Adorsom Building) 2ኛ ፎቅ ላይ የሚገኝ ቢሮ ተዘርፏል። እነዚህ በምስሉ ላይ የምታዩዋቸው የአድዋን ድል ቀን በድፍረት ንብረት ዘርፈው ተሰውረዋል።
⚠️ የተዘረፉ ንብረቶች፦
ከፍተኛ ዋጋ ያላቸው ላፕቶፕ ኮምፒውተሮች
ታብሌቶች (Tablets)p
ፕሮፌሽናል የፎቶና የቪዲዮ ካሜራዎች
የተለያዩ የስልክ መሣሪያዎች
🔍 የሌቦቹ ሁኔታ፦
ሌቦቹ የቢሮውን የደህንነት ካሜራ (Footage) ለማጥፋትና መረጃ ለመሰወር ቢሞክሩም፣ በሌሎች የሕንፃው መቆጣጠሪያ ካሜራዎች ላይ ማንነታቸው በግልጽ ሊታወቅ ችሏል።
🙏 የዜግነት ግዴታዎን ይወጡ!
እነዚህን ግለሰቦች የምታውቁ፣ ያያችሁ ወይም በተመሳሳይ ሁኔታ ዝርፊያ የተፈጸመባችሁ ወገኖች ጥቆማ በማድረግ እንድትተባበሩ ጥሪ ቀርቧል።
✅ ለጥቆማው ተገቢው ወሮታ ይከፈላል!
ጥቆማ ለማድረስ፦
📍 ቦሌ አደይ አበባ ፖሊስ ጣቢያ በአካል በመቅረብ ወይም
📞 በስልክ ቁጥሮች፦ 0988188890 ወይም 0907247454 ይደውሉ።
የሌቦቹን ፎቶ በማየትና ይህን መረጃ ሼር (Share) በማድረግ ወንጀለኞቹ ለሕግ እንዲቀርቡ ይተባበሩ! ወንጀልን በጋራ እንከላከል!
Comments