9 months ago
እኔ የተወለድኩበት አካባቢ ያደገ አማርኛዉ ደስ የሚል የገጠሩን ለዛ የተላበሰ አንድ ወጣት ባለሀብት
ጎበዝ ነጋዴ በሰዎች በኩል አስተዋወቁኝ ብሎ ተዋወቀኝ።
ምንያህል ስራዎቼን እንደሚያደንቅና እንሚወደኝ ነግሮኝ የጋብቻ ጥያቄ አቀረበልኝ እኔም ስለ ቀና አመለካከቱ አመስግኜ በጌታ ነህ ወይ ብዬ ስጠይቀዉ አይ ጌታን አልተቀበልኩም አንቺ ጥያቄየን ከተቀበልሽ ጌታን እቀበልልሻለሁ አለኝ🙄
ልጁ ፍፁም የዋህና ቀጥተኛ ሰዉ ነዉ።
እኔም ለኔ ብለህ ሳይሆን ለራስህ ብለህ ተቀበል ብዬ ጌታን የመቀበል ጥቅማ ጥቅሞቹን አስረዳሁ።ከዚያም አንድ የምወደዉ አገልጋይ ጠርቼ እሱ እንዲፀልይለት አደረኩ።
በነጋታዉ ይሄዉ ነጋዴ ደዉሎ ፣እህሳ አለኝ ጌታን ተቀበልኩ በይ አሁን ፍቅራችንን እንጀምር ሲለኝ አሁን መሰረታዊ የመፅሀፍ ቅዱስ ትምህርት ተማር ከዚያ በሗላ ነዉ ደግሞ የጌታ ፈቃድ መሆኑን መወያየትም መፀለይም የሚቻለዉ አሁን ስለምንም ጎዳይ ማዉራት አይፈቀድም ስለዉ
ኧሯ እና ከተማርሁ በሗል እንጃልህ ብትይኝስ ሲለኝ እና በመማርህ የዘለአለም ህይወት አትርፈህ መሄድ ነዉ ምንም አትጎዳም ስለዉ ብዙም አልተዋጠለትም።
ከተወሰነ ቀናት በሗላ የመኪና መሸጫ ቤት ሄዶ ደወለልኛና ነይ አሁኑኑ የ6 ሚሊየን ብር መኪና በስምሽ ገዝቼ ልስጥሽ አለኝ ፣ የምሩን እኔን ለማስደሰትና ለማሳመን አስቦ ነበር።
እኔም ቆጣ ብዬ ምን ለማለት ፈልገህ ነዉ? ይሄ ለኔ ስደብ ነዉ ስለዉ ብስጭት ብሎ ኧረ ይድፋሽ ምኒቱ ናት አያ አለ፣ አዎ ንቀት ነዉ ስለዉ ኧረ እልም ያርግሽ አለኝ።
እንደዚህ ማለቱ በጣም አሳቀኝ፣ ቆጣ ብሎ እኔ ላንቺ ካለኝ ትልቅ አክብሮት እንጅ
ለማንም ልጃገረድ እንኳ ፈፅሞ የማላደርገዉን ነዉ ላንቺ አስቤ ልግዛልሽ ያልኩሽ ሲለኝ የኔ ዋጋኮ ከልጃገረድ ዋጋ እጅግ ይበልጣል ስለዉ እየሳቀ ተይ እንጅ የሁለት ልጆች እናት መሆንሽን አትርሺ እኔ ስላከበርኩሽ ነዉ ልግዛልሽ ያልኩሽ ሲለኝ ፣እኔም በገንዘብ ልታሳምነኝ መሞከርህ ከክብሬ አዉርዶ የሚፈጠፍጠኝ እንጂ የሚያከብረኝ አይደለም አርፈህ የእግዚአብሔርን ቃል ተማር ብዬ ዘጋሁበትና የሩቅ ወዳጆች ሆነን ቀረን።
ወንዶች ሁሉ ራሳችሁን ለፍቅር ወይም ለትዳር ብቁ ለማድረግ ቀዳሚዉ የእግዚአብሔር ቃል ነዉ!
በትዳር ዉስጥ ገንዘብ በጣም አስፈላጊ ነዉ
ነገር ግን ዋና ነገር አይደለም ዋናዉ የእግዚአብሔር ቃል ነዉ!
Sofia shebabaw
ጎበዝ ነጋዴ በሰዎች በኩል አስተዋወቁኝ ብሎ ተዋወቀኝ።
ምንያህል ስራዎቼን እንደሚያደንቅና እንሚወደኝ ነግሮኝ የጋብቻ ጥያቄ አቀረበልኝ እኔም ስለ ቀና አመለካከቱ አመስግኜ በጌታ ነህ ወይ ብዬ ስጠይቀዉ አይ ጌታን አልተቀበልኩም አንቺ ጥያቄየን ከተቀበልሽ ጌታን እቀበልልሻለሁ አለኝ🙄
ልጁ ፍፁም የዋህና ቀጥተኛ ሰዉ ነዉ።
እኔም ለኔ ብለህ ሳይሆን ለራስህ ብለህ ተቀበል ብዬ ጌታን የመቀበል ጥቅማ ጥቅሞቹን አስረዳሁ።ከዚያም አንድ የምወደዉ አገልጋይ ጠርቼ እሱ እንዲፀልይለት አደረኩ።
በነጋታዉ ይሄዉ ነጋዴ ደዉሎ ፣እህሳ አለኝ ጌታን ተቀበልኩ በይ አሁን ፍቅራችንን እንጀምር ሲለኝ አሁን መሰረታዊ የመፅሀፍ ቅዱስ ትምህርት ተማር ከዚያ በሗላ ነዉ ደግሞ የጌታ ፈቃድ መሆኑን መወያየትም መፀለይም የሚቻለዉ አሁን ስለምንም ጎዳይ ማዉራት አይፈቀድም ስለዉ
ኧሯ እና ከተማርሁ በሗል እንጃልህ ብትይኝስ ሲለኝ እና በመማርህ የዘለአለም ህይወት አትርፈህ መሄድ ነዉ ምንም አትጎዳም ስለዉ ብዙም አልተዋጠለትም።
ከተወሰነ ቀናት በሗላ የመኪና መሸጫ ቤት ሄዶ ደወለልኛና ነይ አሁኑኑ የ6 ሚሊየን ብር መኪና በስምሽ ገዝቼ ልስጥሽ አለኝ ፣ የምሩን እኔን ለማስደሰትና ለማሳመን አስቦ ነበር።
እኔም ቆጣ ብዬ ምን ለማለት ፈልገህ ነዉ? ይሄ ለኔ ስደብ ነዉ ስለዉ ብስጭት ብሎ ኧረ ይድፋሽ ምኒቱ ናት አያ አለ፣ አዎ ንቀት ነዉ ስለዉ ኧረ እልም ያርግሽ አለኝ።
እንደዚህ ማለቱ በጣም አሳቀኝ፣ ቆጣ ብሎ እኔ ላንቺ ካለኝ ትልቅ አክብሮት እንጅ
ለማንም ልጃገረድ እንኳ ፈፅሞ የማላደርገዉን ነዉ ላንቺ አስቤ ልግዛልሽ ያልኩሽ ሲለኝ የኔ ዋጋኮ ከልጃገረድ ዋጋ እጅግ ይበልጣል ስለዉ እየሳቀ ተይ እንጅ የሁለት ልጆች እናት መሆንሽን አትርሺ እኔ ስላከበርኩሽ ነዉ ልግዛልሽ ያልኩሽ ሲለኝ ፣እኔም በገንዘብ ልታሳምነኝ መሞከርህ ከክብሬ አዉርዶ የሚፈጠፍጠኝ እንጂ የሚያከብረኝ አይደለም አርፈህ የእግዚአብሔርን ቃል ተማር ብዬ ዘጋሁበትና የሩቅ ወዳጆች ሆነን ቀረን።
ወንዶች ሁሉ ራሳችሁን ለፍቅር ወይም ለትዳር ብቁ ለማድረግ ቀዳሚዉ የእግዚአብሔር ቃል ነዉ!
በትዳር ዉስጥ ገንዘብ በጣም አስፈላጊ ነዉ
ነገር ግን ዋና ነገር አይደለም ዋናዉ የእግዚአብሔር ቃል ነዉ!
Sofia shebabaw
11 months ago
Intervision Song Contest 2025
#ethiopia | የፊታችን መስከረም 10/2018 ዓ.ም በሩስያ ዋና ከተማ ሞስኮ "Intervision Song Contest 2025" (ኢንተርቪዥን ሶንግ ኮንቴስት 2025) የተሰኘ አሜሪካንን ጨምሮ ከ21 በላይ ሃገሮች የሚሳተፉበት ታላቅ የድምፃዊያን ውድድር ይካሄዳል።
ይህን ውድድር የሚያስተባብረው የሩስያ መንግስት ሲሆን ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን አስጀምረውት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ዲሚትሪ ቼርንየሽኮ በበላይነት እንዲቆጣጠሩት ሾመዋቸዋል።
የሩስያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፤ ባህልን ለመጠበቅ እና የብሔራዊ እና የዓለም ባህልን ለማሻሻል የተቋቋመው ("Traditions of Art”)፤ ቻናል ዋን ሩሲያ (Channel One Russia)፤ እና ናሽናል ሚዲያ ግሩፕ (National Media Group) ከአዘጋጁ ጎን ተሰልፈዋል።
ይህንን ታላቅ ውድድር በተባባሪ አዘጋጅነት አብሮ እንዲሰራ ባላገሩ ቲም (Balageru Team) በመመረጡ ከፍተኛ ደስታ ይሰማናል።
ይህንንም ለወሰነው ለሩስያ አዘጋጅ ክፍል ያለንን አድናቆት ስንገልፅ በስራችን የምትኮሩትንና የምታበረታቱንን በመላው አለም የምትኖሩ ኢትዮጵያውያንን ሁሉ በማሰብና ይህ ምርጫ የናንተም እንደሚሆን በመተማመን ነው።
ውድድሩ በእለቱ መስከረም 10/2018 ከምሽቱ 2:00 ሰዓት ጀምሮ በባላገሩ ቴሌቪዥን በቀጥታ ይተላለፋል።
የውድድሩ መስፈርት የሚጠይቀውን ብቻ በመመርኮዝ ነፃነት ሱልጣን "ሃላል" በተሰኘው ዘፈኗ አገራችንን ወክላ ለመጀመርያ ግዜ ስለምትሳተፍ ባላሰለሰ ኢትዮጵያዊ ፍቅር ድጋፋችሁን እንድትሰጧት እንጠይቃለን።
ባላገሩ ምርጥም ሶፊ (ሱልጣን ኑሪ) አገራችንን ወክሎ በዳኝነት እንዲሳተፍ ያደረገ መሆኑን ስንገልፅ ድጋፋችሁ የማንነታችን ዋስትና ቁልፍ ስለሆነ ለምታሳዩን ፍቅር ሁሉ ከወዲሁ በማመስገን ነው።
አብርሃም ወልዴ (ባላገሩ ቲም)
#abrahamwolde #intervision2025 #russia #ethiopia #songcontest #music #sofi #netsanetsultan
#ethiopia | የፊታችን መስከረም 10/2018 ዓ.ም በሩስያ ዋና ከተማ ሞስኮ "Intervision Song Contest 2025" (ኢንተርቪዥን ሶንግ ኮንቴስት 2025) የተሰኘ አሜሪካንን ጨምሮ ከ21 በላይ ሃገሮች የሚሳተፉበት ታላቅ የድምፃዊያን ውድድር ይካሄዳል።
ይህን ውድድር የሚያስተባብረው የሩስያ መንግስት ሲሆን ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን አስጀምረውት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ዲሚትሪ ቼርንየሽኮ በበላይነት እንዲቆጣጠሩት ሾመዋቸዋል።
የሩስያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፤ ባህልን ለመጠበቅ እና የብሔራዊ እና የዓለም ባህልን ለማሻሻል የተቋቋመው ("Traditions of Art”)፤ ቻናል ዋን ሩሲያ (Channel One Russia)፤ እና ናሽናል ሚዲያ ግሩፕ (National Media Group) ከአዘጋጁ ጎን ተሰልፈዋል።
ይህንን ታላቅ ውድድር በተባባሪ አዘጋጅነት አብሮ እንዲሰራ ባላገሩ ቲም (Balageru Team) በመመረጡ ከፍተኛ ደስታ ይሰማናል።
ይህንንም ለወሰነው ለሩስያ አዘጋጅ ክፍል ያለንን አድናቆት ስንገልፅ በስራችን የምትኮሩትንና የምታበረታቱንን በመላው አለም የምትኖሩ ኢትዮጵያውያንን ሁሉ በማሰብና ይህ ምርጫ የናንተም እንደሚሆን በመተማመን ነው።
ውድድሩ በእለቱ መስከረም 10/2018 ከምሽቱ 2:00 ሰዓት ጀምሮ በባላገሩ ቴሌቪዥን በቀጥታ ይተላለፋል።
የውድድሩ መስፈርት የሚጠይቀውን ብቻ በመመርኮዝ ነፃነት ሱልጣን "ሃላል" በተሰኘው ዘፈኗ አገራችንን ወክላ ለመጀመርያ ግዜ ስለምትሳተፍ ባላሰለሰ ኢትዮጵያዊ ፍቅር ድጋፋችሁን እንድትሰጧት እንጠይቃለን።
ባላገሩ ምርጥም ሶፊ (ሱልጣን ኑሪ) አገራችንን ወክሎ በዳኝነት እንዲሳተፍ ያደረገ መሆኑን ስንገልፅ ድጋፋችሁ የማንነታችን ዋስትና ቁልፍ ስለሆነ ለምታሳዩን ፍቅር ሁሉ ከወዲሁ በማመስገን ነው።
አብርሃም ወልዴ (ባላገሩ ቲም)
#abrahamwolde #intervision2025 #russia #ethiopia #songcontest #music #sofi #netsanetsultan
1 year ago
ከኢትዮጵያ ህዝብ ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ጤናማ አመጋገብ የሚያስፈልጉ ምግቦችን ለመግዛት ኢኮኖሚያዊ አቅም የላቸውም ሲል አንድ ሪፖርት አመላከተ
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የዓለም የምግብ ዋስትና እና የተመጣጠነ ምግብ ሁኔታ (SOFI 2025) ሪፖርት የተወሰደ መረጃ እንደሚያሳየው እ.ኤ.አ. በ2024 ከኢትዮጵያ ህዝብ ከግማሽ በላይ የሚሆነው—ከ60 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ጤናማ አመጋገብ የሚያስፈልጉ ምግቦችን ለመግዛት ገቢያቸወው አይፈቅድም ብሏል።
ይህ ቁጥር እ.ኤ.አ. በ2023 ከነበረው 53.4 በመቶ ጋር ሲነጻጸር መጠነኛ ጭማሪ ያሳያል፤ ይህም በዋጋ ንረት እና በኢኮኖሚያዊ ጫናዎች መካከል እየጨመሩ ያሉ ተግዳሮቶችን ያመለክታል።
በ2024 የዓለም የረሃብ መጠን በዓለም ህዝብ ውስጥ ወደ 8.2 በመቶ ዝቅ ብሏል፤ እድገቱ ግን ያልተመጣጠነ ነበር። በአፍሪካ ከ20 በመቶ በላይ የሚሆኑ ሰዎች—307 ሚሊዮን የሚሆኑት—ረሃብ ገጥሟቸዋል፤ ይህም እየተባባሰ የመጣውን ሁኔታ ያንፀባርቃል። የኢትዮጵያ ልምድ ከዚህ የክልላዊ አዝማሚያ ጋር ተመሳሳይ ነው፤ የምግብ ዋጋ ንረት እና መዋቅራዊ ድክመቶች የተመጣጠነ ምግብ የማግኘት ዕድልን ገድበዋል።
የምግብ ዋጋ ንረት በዓለም አቀፍ ደረጃ በ2023 መጀመሪያ ላይ 13.6 በመቶ ደርሶ የነበረ ሲሆን፣ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው አገሮች የዋጋ ንረቱ ከዚህም በላይ ከፍ ያለ ደረጃ ላይ ደርሷል።
እንደ ሪፖርቱ ከሆነ፣ በኢትዮጵያ ጤናማ አመጋገብ ለመመገብ የሚያስፈልገው ወጪ በ2024 በቀን ለአንድ ሰው 4.78 የአሜሪካ ዶላር ደርሷል፤ ይህም ከ2017 ወዲህ የ62 በመቶ ጭማሪ ያሳያል። ይህ ጭማሪ በተለይ በገጠር የሚኖሩ እና ለምግብ ፍላጎታቸው በገበያ ላይ ጥገኛ የሆኑ ቤተሰቦችን በእጅጉ ጎድቷል።
የተባበሩት መንግስታት እ.ኤ.አ. በ2030 በዓለም አቀፍ ደረጃ 512 ሚሊዮን ሰዎች ሥር የሰደደ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ሊገጥማቸው እንደሚችል ይገምታል፤ ከእነዚህ ውስጥ ወደ 60 በመቶ የሚጠጉት በአፍሪካ ውስጥ ይሆናሉ። ይህ ኢትዮጵያ የዘላቂ ልማት ግብ 2ን (ረሃብን ማስወገድ) የማሳካት አቅሟን አደጋ ላይ ይጥላል።
SOFI 2025 በኢትዮጵያ እና በመላው አፍሪካ የምግብ አቅምን እና የመቋቋም አቅምን ለማሻሻል የታለሙ ማህበራዊ ደህንነት መረቦችን፣ አስተማማኝ የዋጋ ንረት መቆጣጠሪያዎችን እና በግብርና እና በመሠረተ ልማት ላይ ስትራቴጂካዊ ኢንቨስትመንቶችን ይመክራል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የዓለም የምግብ ዋስትና እና የተመጣጠነ ምግብ ሁኔታ (SOFI 2025) ሪፖርት የተወሰደ መረጃ እንደሚያሳየው እ.ኤ.አ. በ2024 ከኢትዮጵያ ህዝብ ከግማሽ በላይ የሚሆነው—ከ60 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ጤናማ አመጋገብ የሚያስፈልጉ ምግቦችን ለመግዛት ገቢያቸወው አይፈቅድም ብሏል።
ይህ ቁጥር እ.ኤ.አ. በ2023 ከነበረው 53.4 በመቶ ጋር ሲነጻጸር መጠነኛ ጭማሪ ያሳያል፤ ይህም በዋጋ ንረት እና በኢኮኖሚያዊ ጫናዎች መካከል እየጨመሩ ያሉ ተግዳሮቶችን ያመለክታል።
በ2024 የዓለም የረሃብ መጠን በዓለም ህዝብ ውስጥ ወደ 8.2 በመቶ ዝቅ ብሏል፤ እድገቱ ግን ያልተመጣጠነ ነበር። በአፍሪካ ከ20 በመቶ በላይ የሚሆኑ ሰዎች—307 ሚሊዮን የሚሆኑት—ረሃብ ገጥሟቸዋል፤ ይህም እየተባባሰ የመጣውን ሁኔታ ያንፀባርቃል። የኢትዮጵያ ልምድ ከዚህ የክልላዊ አዝማሚያ ጋር ተመሳሳይ ነው፤ የምግብ ዋጋ ንረት እና መዋቅራዊ ድክመቶች የተመጣጠነ ምግብ የማግኘት ዕድልን ገድበዋል።
የምግብ ዋጋ ንረት በዓለም አቀፍ ደረጃ በ2023 መጀመሪያ ላይ 13.6 በመቶ ደርሶ የነበረ ሲሆን፣ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው አገሮች የዋጋ ንረቱ ከዚህም በላይ ከፍ ያለ ደረጃ ላይ ደርሷል።
እንደ ሪፖርቱ ከሆነ፣ በኢትዮጵያ ጤናማ አመጋገብ ለመመገብ የሚያስፈልገው ወጪ በ2024 በቀን ለአንድ ሰው 4.78 የአሜሪካ ዶላር ደርሷል፤ ይህም ከ2017 ወዲህ የ62 በመቶ ጭማሪ ያሳያል። ይህ ጭማሪ በተለይ በገጠር የሚኖሩ እና ለምግብ ፍላጎታቸው በገበያ ላይ ጥገኛ የሆኑ ቤተሰቦችን በእጅጉ ጎድቷል።
የተባበሩት መንግስታት እ.ኤ.አ. በ2030 በዓለም አቀፍ ደረጃ 512 ሚሊዮን ሰዎች ሥር የሰደደ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ሊገጥማቸው እንደሚችል ይገምታል፤ ከእነዚህ ውስጥ ወደ 60 በመቶ የሚጠጉት በአፍሪካ ውስጥ ይሆናሉ። ይህ ኢትዮጵያ የዘላቂ ልማት ግብ 2ን (ረሃብን ማስወገድ) የማሳካት አቅሟን አደጋ ላይ ይጥላል።
SOFI 2025 በኢትዮጵያ እና በመላው አፍሪካ የምግብ አቅምን እና የመቋቋም አቅምን ለማሻሻል የታለሙ ማህበራዊ ደህንነት መረቦችን፣ አስተማማኝ የዋጋ ንረት መቆጣጠሪያዎችን እና በግብርና እና በመሠረተ ልማት ላይ ስትራቴጂካዊ ኢንቨስትመንቶችን ይመክራል።
Sponsored by
Surafel
Comments