25 days ago
17ኛው የአውሮፓ ቀን የህፃናት ሩጫ በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ተካሄደ
#ethiopia | ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ከአውሮፓ ህብረት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው 17ኛው የአውሮፓ ቀን የህፃናት ሩጫ ግንቦት 2 ቀን 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ በደመቀ ሁኔታ ተከብሯል።
በዚህ ስፖርታዊ ኩነት ላይ ከ2,000 በላይ ህፃናት ከወላጆቻቸው ጋር በመሆን የተሳተፉ ሲሆን የተለያዩ የመዝናኛ ዝግጅቶችም ቀርበዋል።
ዕድሜያቸው እስከ 14 ዓመት የሆኑ ታዳጊዎች የተሳተፉበት ይህ ውድድር በለጋ ዕድሜያቸው ጤናማ የአኗኗር ዘይቤን እንዲላመዱና ማህበራዊ ግንኙነታቸውን እንዲያጠናክሩ ታስቦ የተዘጋጀ ነው።
ተሳታፊዎቹ እንደ ዕድሜያቸው በምድብ ተከፋፍለው የሜዳ ላይ ፉክክር ያደረጉ ሲሆን ይህም ከ5 እስከ 14 ዓመት ያሉ ህፃናትን ያካተተ ነበር።
የዘንድሮው የሩጫ መርሃ ግብር ከአለም አቀፍ የእናቶች ቀን ጋር መገጣጠሙ ለዝግጅቱ ልዩ ድምቀት የሰጠው ሲሆን ህፃናቱም ለእናቶቻቸው ያላቸውን ፍቅር በልዩ ልዩ ስነ ስርዓቶች ገልጸዋል።
የአውሮፓ ቀን የህፃናት ሩጫ በየዓመቱ የሚዘጋጅ ሲሆን በኢትዮጵያና በአውሮፓ ህብረት መካከል ያለውን ስፖርታዊና ባህላዊ ወዳጅነት ይበልጥ ለማጠናከር ትልቅ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
በመጨረሻም በውድድሩ ለተሳተፉ ህፃናት ሁሉ የእውቅና ሜዳሊያ የተሰጠ ሲሆን አሸናፊ ለሆኑት ደግሞ ልዩ ሽልማቶች ተበርክቶላቸዋል።
ዝግጅቱ በሙዚቃና በተለያዩ ስፖርታዊ ጨዋታዎች ታጅቦ በታላቅ ደስታ ተጠናቅቋል።
#europeday #greatethiopianrun #childrenrun #sport #mothersday #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ከአውሮፓ ህብረት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው 17ኛው የአውሮፓ ቀን የህፃናት ሩጫ ግንቦት 2 ቀን 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ በደመቀ ሁኔታ ተከብሯል።
በዚህ ስፖርታዊ ኩነት ላይ ከ2,000 በላይ ህፃናት ከወላጆቻቸው ጋር በመሆን የተሳተፉ ሲሆን የተለያዩ የመዝናኛ ዝግጅቶችም ቀርበዋል።
ዕድሜያቸው እስከ 14 ዓመት የሆኑ ታዳጊዎች የተሳተፉበት ይህ ውድድር በለጋ ዕድሜያቸው ጤናማ የአኗኗር ዘይቤን እንዲላመዱና ማህበራዊ ግንኙነታቸውን እንዲያጠናክሩ ታስቦ የተዘጋጀ ነው።
ተሳታፊዎቹ እንደ ዕድሜያቸው በምድብ ተከፋፍለው የሜዳ ላይ ፉክክር ያደረጉ ሲሆን ይህም ከ5 እስከ 14 ዓመት ያሉ ህፃናትን ያካተተ ነበር።
የዘንድሮው የሩጫ መርሃ ግብር ከአለም አቀፍ የእናቶች ቀን ጋር መገጣጠሙ ለዝግጅቱ ልዩ ድምቀት የሰጠው ሲሆን ህፃናቱም ለእናቶቻቸው ያላቸውን ፍቅር በልዩ ልዩ ስነ ስርዓቶች ገልጸዋል።
የአውሮፓ ቀን የህፃናት ሩጫ በየዓመቱ የሚዘጋጅ ሲሆን በኢትዮጵያና በአውሮፓ ህብረት መካከል ያለውን ስፖርታዊና ባህላዊ ወዳጅነት ይበልጥ ለማጠናከር ትልቅ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
በመጨረሻም በውድድሩ ለተሳተፉ ህፃናት ሁሉ የእውቅና ሜዳሊያ የተሰጠ ሲሆን አሸናፊ ለሆኑት ደግሞ ልዩ ሽልማቶች ተበርክቶላቸዋል።
ዝግጅቱ በሙዚቃና በተለያዩ ስፖርታዊ ጨዋታዎች ታጅቦ በታላቅ ደስታ ተጠናቅቋል።
#europeday #greatethiopianrun #childrenrun #sport #mothersday #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
25 days ago
ከስኬት ማማው በስተጀርባ ያሉት ብርቱ እናቶች
************************
እናትነት በቃላት የማይገለጽ ጥልቅ ፍቅር ብቻ ሳይሆን፣ የሕይወት መጀመሪያ ትምህርት ቤት እና የማያልቅ የጥንካሬ ምንጭ ነው።
ዛሬ በዓለም አቀፍ ደረጃ በታላቅ የክብር ስፍራ ላይ የምናያቸው ስመ-ጥር ግለሰቦች፣ ለደረሱበት የስኬት ማማ ትልቁን መንገድ የጠረጉላቸው በጸሎትና በጽናት ከጎናቸው የቆሙት እናቶቻቸው መሆናቸውን ታሪካቸው ምስክር ነው።
ለአብነት ያህል "የአፍሪካዋ ቴሬዛ" በመባል የሚታወቁት አበበች ጎበና፣ በረሃብ ለተጎዱ በሺዎች የሚቆጠሩ ሕፃናት እናት ለመሆን የገዛ ትዳራቸውንና ምቾታቸውን መስዋዕት በማድረግ ለሀገር የሚጠቅሙ በርካታ ዜጎችን አፍርተዋል።
በዓለም መድረክ ስማቸው በጉልህ የሚጠቀሱ ታላላቅ አትሌቶች እና በተለያዩ ዘርፎች የተሰማሩ ታዋቂ ሰዎች ለዛሬው ዝናቸውና ክብራቸው መሠረቱ በገጠር ሕይወት ውስጥ በታታሪነትና በሥነ-ምግባር ያሳደጓቸው እናቶቻቸው መሆናቸውን በኩራት ይናገራሉ።
በጥበቡ ዓለምም ብንመለከት፣ ድምፃዊ ሮፍናን በ"ነፀብራቅ" አልበሙ ላይ የእናቱን ምክር አካቶ ያቀረበበት መንገድ፣ የእናቶች ቃል ለስኬት ያለውን ጉልህ ሚና ያሳየበት አጋጣሚ ነው።
ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ኮከብ ክርስቲያኖ ሮናልዶም ቢሆን፣ ለዛሬው ዝናው እናቱ በልጅነቱ የከፈለችው መስዋዕትነት ትልቁን ድርሻ እንደሚይዝ ደጋግሞ ይገልጻል።
ታላቁ የፈጠራ ሰው ቶማስ ኤዲሰን ዓለምን በብርሃን የሞላ ግኝት እንዲያበረክት፣ እናቱ ናንሲ ኤዲሰን በልጃቸው ላይ የነበራቸው ጽኑ እምነት እና በቤት ውስጥ ያስተማሩት ትምህርት መሠረት ሆኖታል።
እነዚህ ጥቂት ምሳሌዎች እንጂ፣ ስማቸው በታሪክ መዝገብ ላይ ባይሰፍርም ለልጆቻቸው ሕልም ሲሉ የራሳቸውን ፍላጎት መስዋዕት ያደረጉ እልፍ እናቶች አሉ።
ከአንድ ስኬታማ የጥበብ ሰው፣ ሳይንቲስት ወይም ባለሙያ በስተጀርባ፤ ዓለም ሁሉ ፊቱን ሲያዞር "ትችላለህ" ብላ ተስፋ የሰጠችና የደከመች ብርቱ እናት ሁሌም ትገኛለች። እናትነት የዓለም ሁሉ ስኬት መነሻ ነችና ሁሌም ልትከበር ይገባታል።
በልዩ እሸቱ
#mothersday #successstories #ethiopia #inspiration
************************
እናትነት በቃላት የማይገለጽ ጥልቅ ፍቅር ብቻ ሳይሆን፣ የሕይወት መጀመሪያ ትምህርት ቤት እና የማያልቅ የጥንካሬ ምንጭ ነው።
ዛሬ በዓለም አቀፍ ደረጃ በታላቅ የክብር ስፍራ ላይ የምናያቸው ስመ-ጥር ግለሰቦች፣ ለደረሱበት የስኬት ማማ ትልቁን መንገድ የጠረጉላቸው በጸሎትና በጽናት ከጎናቸው የቆሙት እናቶቻቸው መሆናቸውን ታሪካቸው ምስክር ነው።
ለአብነት ያህል "የአፍሪካዋ ቴሬዛ" በመባል የሚታወቁት አበበች ጎበና፣ በረሃብ ለተጎዱ በሺዎች የሚቆጠሩ ሕፃናት እናት ለመሆን የገዛ ትዳራቸውንና ምቾታቸውን መስዋዕት በማድረግ ለሀገር የሚጠቅሙ በርካታ ዜጎችን አፍርተዋል።
በዓለም መድረክ ስማቸው በጉልህ የሚጠቀሱ ታላላቅ አትሌቶች እና በተለያዩ ዘርፎች የተሰማሩ ታዋቂ ሰዎች ለዛሬው ዝናቸውና ክብራቸው መሠረቱ በገጠር ሕይወት ውስጥ በታታሪነትና በሥነ-ምግባር ያሳደጓቸው እናቶቻቸው መሆናቸውን በኩራት ይናገራሉ።
በጥበቡ ዓለምም ብንመለከት፣ ድምፃዊ ሮፍናን በ"ነፀብራቅ" አልበሙ ላይ የእናቱን ምክር አካቶ ያቀረበበት መንገድ፣ የእናቶች ቃል ለስኬት ያለውን ጉልህ ሚና ያሳየበት አጋጣሚ ነው።
ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ኮከብ ክርስቲያኖ ሮናልዶም ቢሆን፣ ለዛሬው ዝናው እናቱ በልጅነቱ የከፈለችው መስዋዕትነት ትልቁን ድርሻ እንደሚይዝ ደጋግሞ ይገልጻል።
ታላቁ የፈጠራ ሰው ቶማስ ኤዲሰን ዓለምን በብርሃን የሞላ ግኝት እንዲያበረክት፣ እናቱ ናንሲ ኤዲሰን በልጃቸው ላይ የነበራቸው ጽኑ እምነት እና በቤት ውስጥ ያስተማሩት ትምህርት መሠረት ሆኖታል።
እነዚህ ጥቂት ምሳሌዎች እንጂ፣ ስማቸው በታሪክ መዝገብ ላይ ባይሰፍርም ለልጆቻቸው ሕልም ሲሉ የራሳቸውን ፍላጎት መስዋዕት ያደረጉ እልፍ እናቶች አሉ።
ከአንድ ስኬታማ የጥበብ ሰው፣ ሳይንቲስት ወይም ባለሙያ በስተጀርባ፤ ዓለም ሁሉ ፊቱን ሲያዞር "ትችላለህ" ብላ ተስፋ የሰጠችና የደከመች ብርቱ እናት ሁሌም ትገኛለች። እናትነት የዓለም ሁሉ ስኬት መነሻ ነችና ሁሌም ልትከበር ይገባታል።
በልዩ እሸቱ
#mothersday #successstories #ethiopia #inspiration
25 days ago
25 days ago
25 days ago
25 days ago
Sponsored by
Surafel
25 days ago
25 days ago
25 days ago
25 days ago
Sponsored by
Surafel
25 days ago
25 days ago
25 days ago
25 days ago
25 days ago
26 days ago
እናት! ቃላት የማይገልጿት...
************
ዓለም ብዙ ቋንቋዎች አሏት፤ ነገር ግን በሁሉም ቋንቋዎች ውስጥ ትርጉሙ የማይለወጥና ድምፀቱ የማይቀየር አንድ ጣፋጭ ቃል አለ... 'እናት'!
እናት ማለት ተራ ቃል አይደለም። መዝገበ ቃላት ሊፈቱት የማይችሉት ረቂቅ ትርጉም ነው፤ እናት የሕይወት መጀመሪያ፣ የፍቅር ምንጭ እና የጽናት ተምሳሌት ናት፡፡
ራስን በመርሳት ለሌላ ሰው መኖር የሚችል ማን አለ? የገዛ ህመምን ደብቆ የልጅን ሳቅ መምረጥ፣ የራስን ረሃብ ችላ ብሎ ለልጅ ማብላት... እነዚህ የማይቻሉ የሚመስሉ ነገሮች በሙሉ ለእናቶች ተችለዋል፡፡
እናት ማለት በጨለማ ውስጥ ብርሃን የምትሆን፣ በድካም ውስጥ ብርታት የምትሰጥ፣ እንዲሁም ዓለም ፊቷን በምታዞርበት ሰዓት እጆቿን ዘርግታ የምትቀበል ብቸኛ መጠጊያ ናት።
በየዓመቱ የፈረንጆቹ ግንቦት ወር በገባ በሁለተኛው እሁድ የሚከበረው ዓለም አቀፍ የእናቶች ቀን፣ የእናትነትን ክብር እንዲሁም እናቶች በማኅበረሰቡ ውስጥ ያላቸውን የማይተካ ሚና ለማድነቅና ዕውቅና ለመስጠት የሚከበር ልዩ ቀን ነው፡፡
ይህ ቀን እናቶች ለልጆቻቸው እና ለቤተሰባቸው የሚከፍሉትን መስዋዕትነት የምናስብበትና ምስጋናችንን የምንገልጽበት ግሩም አጋጣሚ ነው፡፡
እስቲ ዛሬ ቆም ብለን ራሳችንን እንጠይቅ... ለዚህች እናት የሚመጥን ምን ምላሽ ሰጠናት? ውድ ስጦታ ላያስፈልጋት ይችላል፤ ነገር ግን መልካም ሰው ሆነን የድካሟን ፍሬ አሳይተናት ይሆን? አንድ "እወድሻለሁ!" የሚል ቃል፣ አንድ የፍቅር እቅፍ፣ ወይም ደግሞ ስለ ህልውናዋ የምናቀርበው ምስጋና ለእርሷ ትልቅ ትርጉም አለው።
እናት ማለት የፍቅር ትርጓሜ፣ የቤታችን ምሰሶ እና ቃላት የማይገልጿት ሕያው የፍቅር ትእምርት ናትና በየቀኑ ልናከብራት ይገባል፡፡
የዘንድሮው ዓለም አቀፍ የእናቶች ቀን ነገ (እሁድ) ይከበራል፡፡ ለመሆኑ ለእናቶቻችን ምን ስጦታ አዘጋጅተናል? ምን ዓይነት የፍቅር ቃልስ ልንነግራቸው ወስነናል? እናቶቻችን የከፈሉልንን ዋጋስ በሚገባ አስበንበታል? እነዚህን ጥያቄዎች ራሳችንን እየጠየቅን የውድ እናቶቻችንን ውለታ ለማሰብ እንዘጋጅ!
መልካም የእናቶች ቀን!
በሄዋን ጌታቸው
#mothersday #happymothersday #unconditionallove #mothersday2026 #loveformom
************
ዓለም ብዙ ቋንቋዎች አሏት፤ ነገር ግን በሁሉም ቋንቋዎች ውስጥ ትርጉሙ የማይለወጥና ድምፀቱ የማይቀየር አንድ ጣፋጭ ቃል አለ... 'እናት'!
እናት ማለት ተራ ቃል አይደለም። መዝገበ ቃላት ሊፈቱት የማይችሉት ረቂቅ ትርጉም ነው፤ እናት የሕይወት መጀመሪያ፣ የፍቅር ምንጭ እና የጽናት ተምሳሌት ናት፡፡
ራስን በመርሳት ለሌላ ሰው መኖር የሚችል ማን አለ? የገዛ ህመምን ደብቆ የልጅን ሳቅ መምረጥ፣ የራስን ረሃብ ችላ ብሎ ለልጅ ማብላት... እነዚህ የማይቻሉ የሚመስሉ ነገሮች በሙሉ ለእናቶች ተችለዋል፡፡
እናት ማለት በጨለማ ውስጥ ብርሃን የምትሆን፣ በድካም ውስጥ ብርታት የምትሰጥ፣ እንዲሁም ዓለም ፊቷን በምታዞርበት ሰዓት እጆቿን ዘርግታ የምትቀበል ብቸኛ መጠጊያ ናት።
በየዓመቱ የፈረንጆቹ ግንቦት ወር በገባ በሁለተኛው እሁድ የሚከበረው ዓለም አቀፍ የእናቶች ቀን፣ የእናትነትን ክብር እንዲሁም እናቶች በማኅበረሰቡ ውስጥ ያላቸውን የማይተካ ሚና ለማድነቅና ዕውቅና ለመስጠት የሚከበር ልዩ ቀን ነው፡፡
ይህ ቀን እናቶች ለልጆቻቸው እና ለቤተሰባቸው የሚከፍሉትን መስዋዕትነት የምናስብበትና ምስጋናችንን የምንገልጽበት ግሩም አጋጣሚ ነው፡፡
እስቲ ዛሬ ቆም ብለን ራሳችንን እንጠይቅ... ለዚህች እናት የሚመጥን ምን ምላሽ ሰጠናት? ውድ ስጦታ ላያስፈልጋት ይችላል፤ ነገር ግን መልካም ሰው ሆነን የድካሟን ፍሬ አሳይተናት ይሆን? አንድ "እወድሻለሁ!" የሚል ቃል፣ አንድ የፍቅር እቅፍ፣ ወይም ደግሞ ስለ ህልውናዋ የምናቀርበው ምስጋና ለእርሷ ትልቅ ትርጉም አለው።
እናት ማለት የፍቅር ትርጓሜ፣ የቤታችን ምሰሶ እና ቃላት የማይገልጿት ሕያው የፍቅር ትእምርት ናትና በየቀኑ ልናከብራት ይገባል፡፡
የዘንድሮው ዓለም አቀፍ የእናቶች ቀን ነገ (እሁድ) ይከበራል፡፡ ለመሆኑ ለእናቶቻችን ምን ስጦታ አዘጋጅተናል? ምን ዓይነት የፍቅር ቃልስ ልንነግራቸው ወስነናል? እናቶቻችን የከፈሉልንን ዋጋስ በሚገባ አስበንበታል? እነዚህን ጥያቄዎች ራሳችንን እየጠየቅን የውድ እናቶቻችንን ውለታ ለማሰብ እንዘጋጅ!
መልካም የእናቶች ቀን!
በሄዋን ጌታቸው
#mothersday #happymothersday #unconditionallove #mothersday2026 #loveformom