2 months ago
ከእግር ኳስ በላይ...
የቮዚንሃ እናት እና የአሜሪካ መንግስት አስገራሚ ውሳኔ
በ2 ቀን ውስጥ ከ50 ሺህ Followers ወደ 12.1 ሚሊዮን Followers የገባው።
የአሜሪካ መንግስት የኬፕ ቨርዱን ኮከብ ግብ ጠባቂ ቮዚንሃን (Vozinha) እናት ወደ አሜሪካ ለማምጣት በይፋ ጥረት እያደረገ ይገኛል!
ቮዚንሃ በዓለም ዋንጫው ላይ ድንቅ ብቃቱን አሳይቶ የነበረ ቢሆንም፣ በቪዛ እጥረት እና በከፍተኛ ክፍያ ምክንያት እናቱ ከጎኑ መሆን አለመቻሏ ይታወሳል። አሁን ግን ይህ ትልቅ ህልሙ እውን ሊሆን ተቃርቧል።
እግር ኳስ ከጨዋታ በላይ ነው። ስለ ቤተሰብ፣ ስለ መስዋዕትነት እና ስለ ፍቅር ጭምር ነው! ይህ ሂደት በተሳካ ሁኔታ ተጠናቆ እናቱ በቅርቡ ከልጇ ጋር እንድትገናኝ ሲጫወት በስታዲየም ውስጥ ሆና እንድታየው የብዙዎች ምኞት ነው።
Seledadotio
Seledadotio
የቮዚንሃ እናት እና የአሜሪካ መንግስት አስገራሚ ውሳኔ
በ2 ቀን ውስጥ ከ50 ሺህ Followers ወደ 12.1 ሚሊዮን Followers የገባው።
የአሜሪካ መንግስት የኬፕ ቨርዱን ኮከብ ግብ ጠባቂ ቮዚንሃን (Vozinha) እናት ወደ አሜሪካ ለማምጣት በይፋ ጥረት እያደረገ ይገኛል!
ቮዚንሃ በዓለም ዋንጫው ላይ ድንቅ ብቃቱን አሳይቶ የነበረ ቢሆንም፣ በቪዛ እጥረት እና በከፍተኛ ክፍያ ምክንያት እናቱ ከጎኑ መሆን አለመቻሏ ይታወሳል። አሁን ግን ይህ ትልቅ ህልሙ እውን ሊሆን ተቃርቧል።
እግር ኳስ ከጨዋታ በላይ ነው። ስለ ቤተሰብ፣ ስለ መስዋዕትነት እና ስለ ፍቅር ጭምር ነው! ይህ ሂደት በተሳካ ሁኔታ ተጠናቆ እናቱ በቅርቡ ከልጇ ጋር እንድትገናኝ ሲጫወት በስታዲየም ውስጥ ሆና እንድታየው የብዙዎች ምኞት ነው።
Seledadotio
Seledadotio
5 months ago
'ሌላ እውነት የለኝም' በቨርጂኒያ ተመረቀ
#ethiopia | የአርቲስት ሜሮን ጌትነት ‘ሌላ እውነት የለኝም’ የግጥም መድበል እጅግ ባማረና የሚገባውን ክብር ባገኘ መልኩ እዚህ ቨርጂኒያ ውስጥ ተመርቋል። ግጥሞቿ በሞያ አጋሮቿ ተነበዋል፣ ሙያዊ ዳሰሳም ተደርጎባቸዋል። የሜሪ ግጥሞች በስሜት ማዕበል ሲያወዛውዙን፣ ሲያስደምሙን፣ ሲያስለቅሱን፣ ሲያስቁን፣ ሲመስጡን አመሹ። ነገሮችን የምታይበት መነጽር አዲስ፣ የምትገልጽበት መንገድ ደግሞ የነፍሳችንን አስኳል የሚነካ ሃይል ያለው አለው።
ላይ ላዩን የሚጋልቡ ሳይሆን ሁለንተንችንን የሚነዝሩ፣ ውስጥ ድረስ ዘልቀው የሚሰሙና ጥያቄ የሚያጭሩ ሃሳቦች ግዘፍ ነስተው፣ ነፍስ ዘርተው ግጥሞቿ ውስጥ ይተነፍሳሉ፤ ይናገራሉ። ጥልቅ፣ መሰረታዊ፣ እናም ደግሞ ልዩ ትርጉም ያላቸው ሃሳብ፣ ምልከታና ሙግቶች ‘ሌላ እውነት የለኝም’ ውስጥ ሞልተዋል። ያልታዩ፣ ያልተስተዋሉና ያልታሰቡ የህይወት አቅጣጫወች በሜሪ ግጥሞች ውስጥ ፍንትው ብለው ተገለጠዋል። እናም ሁላችንም ወደ ውስጥ እንድናይ፣ ከራሳችን ጋ እንወዛገብ ዘንድ በር ይከፍታሉ። ይህን ሁሉ የሚያደርጉት ደግሞ በማያልቀው የሜሪ የቋንቋ ውበት፣ የአጻጻፍ ብቃት እና የፈጠራ ክህሎት ታጅበው፣ ጉዞው በማያልቅበት የምናቧ ጥልቀትና ስፋት ተቃኝተው ነው።
ሜሮን እንደ ሁልጊዜው ሁለገብ ከያኒነቷን ግጥሞቿን እየተወነች አሳየችን።ግጥም መጻፍ ብቻ ሳይሆን ማንበብም ጥርት ያለ ጥበብ መሆኑን አስመሰከረች። ግጥምና ጃዝ ዳግም ተጣመሩ። መድረኩ በትወና፣ በሙዚቃ እና በግጥም ደምቆ አመሸ። ግጥሞቿን አምጣ ወልዳ፣ አሳድጋ፣ አሳትማ፣ አስመርቃ ለወግ ለማዕረግ አበቃች። በምሽቱ ስራውቿን በማቅረብ፣ የራሳቸውን የኪነጥበብ ውጤቶችን በማቋደስ፣ የመጽሐፉን ዳሰሳ በማድረግ ለዝግጅቱ ግብዓት የሆኑት የሞያ አጋሮቿ የድግሱ ድምቀቶች ነበሩ። ለታይታና ደረስ ብሎ ለመመልስ ሳይሆን፣ ሙሉ ዝግጅቱን በሙሉ ልብ ለመቋደስ የታደመው የDMV ነዋሪም ለሜሪና ለስራወቿ አፍቃሪና አክባሪ መሆኑን በተግባር አሳይቶ ምሽቱን ምሉዕ አድርጎታል። ለዝግጅቱ መሳካት ሽር ጉድ ሲሉ የነበሩ አስተባባሪወችና ሁል ጊዜም እንዲህ ያሉ ዝግጅቶችን በመደገፍ የሚታወቁ አጋር ድርጅቶች ከሜሮን ጎን በመቆም የማህበራዊ ሃላፊነታቸውን ተወጥተዋል።
የሜሮን ስብዕና፣ ብቃት፣ ለሞያው ያላት መሰጠት እጅግ ይገርማል፣ ያስደምማል፣ ያስደስታል፣ ያኮራል። ሜሪ ሁሌ ጻፊ። እንኳን ደስ አለሽ።
Via Abebe Feleke
Photo Credit: Eagle Photography Nathnael Damtew
Meron Ghetnet Hiwot Tadesse followers #addisababa #ethiopia #dmv
#ethiopia | የአርቲስት ሜሮን ጌትነት ‘ሌላ እውነት የለኝም’ የግጥም መድበል እጅግ ባማረና የሚገባውን ክብር ባገኘ መልኩ እዚህ ቨርጂኒያ ውስጥ ተመርቋል። ግጥሞቿ በሞያ አጋሮቿ ተነበዋል፣ ሙያዊ ዳሰሳም ተደርጎባቸዋል። የሜሪ ግጥሞች በስሜት ማዕበል ሲያወዛውዙን፣ ሲያስደምሙን፣ ሲያስለቅሱን፣ ሲያስቁን፣ ሲመስጡን አመሹ። ነገሮችን የምታይበት መነጽር አዲስ፣ የምትገልጽበት መንገድ ደግሞ የነፍሳችንን አስኳል የሚነካ ሃይል ያለው አለው።
ላይ ላዩን የሚጋልቡ ሳይሆን ሁለንተንችንን የሚነዝሩ፣ ውስጥ ድረስ ዘልቀው የሚሰሙና ጥያቄ የሚያጭሩ ሃሳቦች ግዘፍ ነስተው፣ ነፍስ ዘርተው ግጥሞቿ ውስጥ ይተነፍሳሉ፤ ይናገራሉ። ጥልቅ፣ መሰረታዊ፣ እናም ደግሞ ልዩ ትርጉም ያላቸው ሃሳብ፣ ምልከታና ሙግቶች ‘ሌላ እውነት የለኝም’ ውስጥ ሞልተዋል። ያልታዩ፣ ያልተስተዋሉና ያልታሰቡ የህይወት አቅጣጫወች በሜሪ ግጥሞች ውስጥ ፍንትው ብለው ተገለጠዋል። እናም ሁላችንም ወደ ውስጥ እንድናይ፣ ከራሳችን ጋ እንወዛገብ ዘንድ በር ይከፍታሉ። ይህን ሁሉ የሚያደርጉት ደግሞ በማያልቀው የሜሪ የቋንቋ ውበት፣ የአጻጻፍ ብቃት እና የፈጠራ ክህሎት ታጅበው፣ ጉዞው በማያልቅበት የምናቧ ጥልቀትና ስፋት ተቃኝተው ነው።
ሜሮን እንደ ሁልጊዜው ሁለገብ ከያኒነቷን ግጥሞቿን እየተወነች አሳየችን።ግጥም መጻፍ ብቻ ሳይሆን ማንበብም ጥርት ያለ ጥበብ መሆኑን አስመሰከረች። ግጥምና ጃዝ ዳግም ተጣመሩ። መድረኩ በትወና፣ በሙዚቃ እና በግጥም ደምቆ አመሸ። ግጥሞቿን አምጣ ወልዳ፣ አሳድጋ፣ አሳትማ፣ አስመርቃ ለወግ ለማዕረግ አበቃች። በምሽቱ ስራውቿን በማቅረብ፣ የራሳቸውን የኪነጥበብ ውጤቶችን በማቋደስ፣ የመጽሐፉን ዳሰሳ በማድረግ ለዝግጅቱ ግብዓት የሆኑት የሞያ አጋሮቿ የድግሱ ድምቀቶች ነበሩ። ለታይታና ደረስ ብሎ ለመመልስ ሳይሆን፣ ሙሉ ዝግጅቱን በሙሉ ልብ ለመቋደስ የታደመው የDMV ነዋሪም ለሜሪና ለስራወቿ አፍቃሪና አክባሪ መሆኑን በተግባር አሳይቶ ምሽቱን ምሉዕ አድርጎታል። ለዝግጅቱ መሳካት ሽር ጉድ ሲሉ የነበሩ አስተባባሪወችና ሁል ጊዜም እንዲህ ያሉ ዝግጅቶችን በመደገፍ የሚታወቁ አጋር ድርጅቶች ከሜሮን ጎን በመቆም የማህበራዊ ሃላፊነታቸውን ተወጥተዋል።
የሜሮን ስብዕና፣ ብቃት፣ ለሞያው ያላት መሰጠት እጅግ ይገርማል፣ ያስደምማል፣ ያስደስታል፣ ያኮራል። ሜሪ ሁሌ ጻፊ። እንኳን ደስ አለሽ።
Via Abebe Feleke
Photo Credit: Eagle Photography Nathnael Damtew
Meron Ghetnet Hiwot Tadesse followers #addisababa #ethiopia #dmv
8 months ago
የአብዛኛውን ሰው ትኩረት ፍለጋ (Public Validation)የማህበረሰብ ስነልቦና መዛነፍ እና ግልብነትን ማስፋፋት...
(የሀብታሙ ደባሱ አዲሱ ሀሳብ)
#ethiopia | ዛሬ በተለየ እይታ ነገረ -ሀሳቤን ለማቅረብ እወዳለሁ በዘመናችን ያለው ፈጣን የቴክኖሎጂ እና የማኅበራዊ መስተጋብር ለውጥ ወጣቱ ትውልድ ትኩረት የሚፈልግባቸውን እና ማንነቱን የሚመዝንባቸውን መመዘኛዎች እየቀየረ ነው።
"የአብዛኛውን ሰው ትኩረት ፍለጋ" (Public Validation) ተብሎ የሚጠራው ይህ ክስተት፣ በተለይ በማኅበራዊ ሚዲያ (Social Media) መድረኮች በሚፈጠረው ተጽዕኖ፣ የአብዛኛው ወጣት ስነልቦናዊ መሠረት እየሆነ መጥቷል።
ይሁንና፣ይህ ፍለጋ ከግል ማንነት ምስረታ አልፎ፣ የማኅበረሰብ ስነልቦናዊ መዛነፍ እና አዋቂና ብልሆችን የመዘንጋት ተለምዷዊ ክስተት እንዲከሰት ምክንያት እየሆነ ነው።በዚህም ወጣቶች ለነገ መሰረታቸው የእውቀት ምንጭ የሆኑ ሥራዎች ላይ ከማተኮር ይልቅ ቅቡልነት ለማግኘት የሚያደርጉት ጥረት እርቃንን ወደ አደባባይ እስከ ማቅርብ ደርሷል ።
ይህን ማህበረሰባዊ ህመም በጊዜ ካላከምነው የመረጃ መተራመስ (Information disorder ) ሊያስከትለው የሚችለው በህፃናት ፣በታዳጊዎች እና በወጣቶች ህይወት ላይ ከፍተኛ ፈተና ነው ። እስኪ ነገሩ በአስታውሎት እንመልከተው :-
🔴 የአብዛኛውን ሰው ትኩረት ፍለጋ (Public Validation) እና የወጣቶች ፈተና:- ዛሬ የወጣቶች የትኩረት ማዕከል ከቤተሰብ እና ከአካባቢው እውነታ ወደ ዲጂታል መድረኮች ተቀይሯል። የ'ላይኮች' (Likes)፣ 'አስተያየቶች' (Comments) እና 'ተከታዮች' (Followers) ቁጥር የግለሰቡን ክብደት፣ ተቀባይነት እና ዋጋ የሚለካበት ዋና መመዘኛ እየሆነ መጥቷል። ማኅበራዊ ሚዲያ ለሚያቀርበው ነገር ፈጣን ምላሽ (ትኩረት) ማግኘት ወጣቶች ከረጅም ጊዜ ልፋትና ትዕግስት ይልቅ ፈጣንና ጊዜያዊ እርካታን እንዲመርጡ ያደርጋል። ( ትምህርት እና ንባብ ሰፊ የአንጎል ሥራ የሚጠይቁ ትግባራትን መሸሽ )
🔴የማይጨበጥ ምስል (Unrealistic self image ):-ወጣቶች ሌሎች ከፍ አድርገው የሚመለከቱትን 'ምርጥ' ማንነታቸውን ለመፍጠርና ለማሳየት ይገደዳሉ።ይህም በውስጣቸው ባለው እውነተኛ ማንነት እና በሚያሳዩት የውጭ ምስል መካከል የስነልቦና ክፍተት እንዲፈጠር ያደርጋል። (ሌላን ሰው ለመምሰል የሚደረግ ጥረት) ከመጠን ያለፈ ውድድር ትኩረት ለማግኘት የሚደረገው ዘለቄታ የሌለው ውድድር ለጭንቀት (Anxiety)፣ ለድብርት (Depression) እና ከማኅበረሰቡ የመገለል ስሜት (Social Isolation) እንዲጨምር ያደርጋል። (ትናንት በተካሄደው የቲክቶክ ሽልማት ያልተሸለሙ ተሳታፊዎች እንደተመለከትኩት ጭንቀት ውስጥ የገቡ ይመስላል )
🔴የማኅበረሰብ ስነልቦናዊ መዛነፍ፦
የአብዛኛውን ሰው ትኩረት ፍለጋ የግለሰቡን ስነልቦና ብቻ ሳይሆን መላውን ማኅበረሰብ የሚነካ መዛነፍ ያስከትላል።የእውነት እና የውሸት መደበላለቅ በሰፊው የብዙኃን ትኩረት የተሰጠው ሐሳብ ወይም መረጃ፣ ትክክለኛነቱ ሳይረጋገጥ በቀላሉ "እውነት" ተብሎ የመወሰድ አዝማሚያ ይጨምራል። የጥራት (Quality) ደረጃ ከብዛት (Quantity) በታች ይሆናል።
🔴የጥልቅ ውይይት መጥፋት:፦ውስብስብ እና ጥልቅ የሆኑ ጉዳዮች በትዊተር (Twitter) ወይም በቲክቶክ (TikTok) በፈጣን ቅብብሎሽ ውስጥ ሲቀርቡ፣ በወጉ የመተንተንና የመወያየት ዕድል ይዘጋል።ጥልቀት የሌለው የገጽታ ግንዛቤ (Superficial Understanding) ይስፋፋል።
🔴የጋራ እሴቶች መናድማኅበራዊ ትኩረት በጊዜያዊ ፋሽን (Trend) እና ስሜታዊ ይዘቶች ላይ ያተኮረ ሲሆን፣ ለዘመናት የቆዩ ማኅበራዊ፣ ባህላዊና የሞራል እሴቶች ቦታ ያጣሉ፤ ነውር የሚባል ነገር እየቀረ ድንቁርና በአደባባይ ቦታ ያገኛል ።
🔴 አዋቂና ብልሆችን የመዘንጋት ተለምዷዊ ክስተት እና ግልብነትን ማስፋፋት ፦ ከላይ በተጠቀሱት ምክንያቶች የተነሳ፣ ወጣቱ ትውልድ ለረጅም ጊዜ በሕይወትና በእውቀት ልምምድ ያካበቱትን አዋቂዎችንና ብልሆችን ምክርና ተሞክሮ ዋጋ የመንሳት እና የመዘንጋት አዝማሚያ እየተስተዋለ ነው።የትውልድ ክፍተት (Generational Gap) መስፋት ፈጣን የዲጂታል ቴክኖሎጂ ለውጦች ወጣቶችን በአዲስ "ቋንቋ" እና "እሴት" እንዲመሩ ያደርጋቸዋል።ይህ ደግሞ ከአዋቂዎች ጋር ያላቸውን የመግባቢያ ድልድይ ያፈርሳል።ሙያዊ የዩኒቨርስቲ እውቀት በሊቃውንት የተመሰከረ ጠልቅ እውቀት እየተረሳ የጨረባ የስብዕና ግንባታ እንደ አዎቂነት እየተወሰደ ነው ።
✍️ እንደ መውጫ⁉️
በመጨረሻም፣ የአብዛኛውን ሰው ትኩረት ፍለጋ የወጣቶችን የጊዜያዊ እርካታ ፍላጎት ሊያረካ ቢችልም፣የዘላቂነት ጥበብን እና ጥልቅ የማኅበረሰብ ትስስርን የሚያሳጣ አደገኛ መንገድ ነው። ሁላችንም እውነተኛ እሴት የሚገኘው ከውስጣዊ ማንነት እና ከተከማቸ የጥበብ ምንጭ እንጂ፣ ከዲጂታል ምላሾች ብዛት አለመሆኑን መገንዘብ ይኖርብናል።ይህንም ለልጆቻችን ምን እንደምናስተምራቸው ቆም ብለን ማሰብ ወይም የማህበረሰብ ንግግር ( community conversation ) የሚስፈልግ ይመስለኛል ።
Ethiopia 🇪🇹
ለበለጠ ወዳጅነት የፃሃፊውን የኤክስ(X) እና የፌስቡክ ገፅ ይከታተሉ :-
🔗የኤክስ(X)ገፅ:-https://x.com/HDebasu?t=eR...
🔗የፌስቡክ:-https://www.facebook.com/s...
መልካም እሁድ 🙏
(የሀብታሙ ደባሱ አዲሱ ሀሳብ)
#ethiopia | ዛሬ በተለየ እይታ ነገረ -ሀሳቤን ለማቅረብ እወዳለሁ በዘመናችን ያለው ፈጣን የቴክኖሎጂ እና የማኅበራዊ መስተጋብር ለውጥ ወጣቱ ትውልድ ትኩረት የሚፈልግባቸውን እና ማንነቱን የሚመዝንባቸውን መመዘኛዎች እየቀየረ ነው።
"የአብዛኛውን ሰው ትኩረት ፍለጋ" (Public Validation) ተብሎ የሚጠራው ይህ ክስተት፣ በተለይ በማኅበራዊ ሚዲያ (Social Media) መድረኮች በሚፈጠረው ተጽዕኖ፣ የአብዛኛው ወጣት ስነልቦናዊ መሠረት እየሆነ መጥቷል።
ይሁንና፣ይህ ፍለጋ ከግል ማንነት ምስረታ አልፎ፣ የማኅበረሰብ ስነልቦናዊ መዛነፍ እና አዋቂና ብልሆችን የመዘንጋት ተለምዷዊ ክስተት እንዲከሰት ምክንያት እየሆነ ነው።በዚህም ወጣቶች ለነገ መሰረታቸው የእውቀት ምንጭ የሆኑ ሥራዎች ላይ ከማተኮር ይልቅ ቅቡልነት ለማግኘት የሚያደርጉት ጥረት እርቃንን ወደ አደባባይ እስከ ማቅርብ ደርሷል ።
ይህን ማህበረሰባዊ ህመም በጊዜ ካላከምነው የመረጃ መተራመስ (Information disorder ) ሊያስከትለው የሚችለው በህፃናት ፣በታዳጊዎች እና በወጣቶች ህይወት ላይ ከፍተኛ ፈተና ነው ። እስኪ ነገሩ በአስታውሎት እንመልከተው :-
🔴 የአብዛኛውን ሰው ትኩረት ፍለጋ (Public Validation) እና የወጣቶች ፈተና:- ዛሬ የወጣቶች የትኩረት ማዕከል ከቤተሰብ እና ከአካባቢው እውነታ ወደ ዲጂታል መድረኮች ተቀይሯል። የ'ላይኮች' (Likes)፣ 'አስተያየቶች' (Comments) እና 'ተከታዮች' (Followers) ቁጥር የግለሰቡን ክብደት፣ ተቀባይነት እና ዋጋ የሚለካበት ዋና መመዘኛ እየሆነ መጥቷል። ማኅበራዊ ሚዲያ ለሚያቀርበው ነገር ፈጣን ምላሽ (ትኩረት) ማግኘት ወጣቶች ከረጅም ጊዜ ልፋትና ትዕግስት ይልቅ ፈጣንና ጊዜያዊ እርካታን እንዲመርጡ ያደርጋል። ( ትምህርት እና ንባብ ሰፊ የአንጎል ሥራ የሚጠይቁ ትግባራትን መሸሽ )
🔴የማይጨበጥ ምስል (Unrealistic self image ):-ወጣቶች ሌሎች ከፍ አድርገው የሚመለከቱትን 'ምርጥ' ማንነታቸውን ለመፍጠርና ለማሳየት ይገደዳሉ።ይህም በውስጣቸው ባለው እውነተኛ ማንነት እና በሚያሳዩት የውጭ ምስል መካከል የስነልቦና ክፍተት እንዲፈጠር ያደርጋል። (ሌላን ሰው ለመምሰል የሚደረግ ጥረት) ከመጠን ያለፈ ውድድር ትኩረት ለማግኘት የሚደረገው ዘለቄታ የሌለው ውድድር ለጭንቀት (Anxiety)፣ ለድብርት (Depression) እና ከማኅበረሰቡ የመገለል ስሜት (Social Isolation) እንዲጨምር ያደርጋል። (ትናንት በተካሄደው የቲክቶክ ሽልማት ያልተሸለሙ ተሳታፊዎች እንደተመለከትኩት ጭንቀት ውስጥ የገቡ ይመስላል )
🔴የማኅበረሰብ ስነልቦናዊ መዛነፍ፦
የአብዛኛውን ሰው ትኩረት ፍለጋ የግለሰቡን ስነልቦና ብቻ ሳይሆን መላውን ማኅበረሰብ የሚነካ መዛነፍ ያስከትላል።የእውነት እና የውሸት መደበላለቅ በሰፊው የብዙኃን ትኩረት የተሰጠው ሐሳብ ወይም መረጃ፣ ትክክለኛነቱ ሳይረጋገጥ በቀላሉ "እውነት" ተብሎ የመወሰድ አዝማሚያ ይጨምራል። የጥራት (Quality) ደረጃ ከብዛት (Quantity) በታች ይሆናል።
🔴የጥልቅ ውይይት መጥፋት:፦ውስብስብ እና ጥልቅ የሆኑ ጉዳዮች በትዊተር (Twitter) ወይም በቲክቶክ (TikTok) በፈጣን ቅብብሎሽ ውስጥ ሲቀርቡ፣ በወጉ የመተንተንና የመወያየት ዕድል ይዘጋል።ጥልቀት የሌለው የገጽታ ግንዛቤ (Superficial Understanding) ይስፋፋል።
🔴የጋራ እሴቶች መናድማኅበራዊ ትኩረት በጊዜያዊ ፋሽን (Trend) እና ስሜታዊ ይዘቶች ላይ ያተኮረ ሲሆን፣ ለዘመናት የቆዩ ማኅበራዊ፣ ባህላዊና የሞራል እሴቶች ቦታ ያጣሉ፤ ነውር የሚባል ነገር እየቀረ ድንቁርና በአደባባይ ቦታ ያገኛል ።
🔴 አዋቂና ብልሆችን የመዘንጋት ተለምዷዊ ክስተት እና ግልብነትን ማስፋፋት ፦ ከላይ በተጠቀሱት ምክንያቶች የተነሳ፣ ወጣቱ ትውልድ ለረጅም ጊዜ በሕይወትና በእውቀት ልምምድ ያካበቱትን አዋቂዎችንና ብልሆችን ምክርና ተሞክሮ ዋጋ የመንሳት እና የመዘንጋት አዝማሚያ እየተስተዋለ ነው።የትውልድ ክፍተት (Generational Gap) መስፋት ፈጣን የዲጂታል ቴክኖሎጂ ለውጦች ወጣቶችን በአዲስ "ቋንቋ" እና "እሴት" እንዲመሩ ያደርጋቸዋል።ይህ ደግሞ ከአዋቂዎች ጋር ያላቸውን የመግባቢያ ድልድይ ያፈርሳል።ሙያዊ የዩኒቨርስቲ እውቀት በሊቃውንት የተመሰከረ ጠልቅ እውቀት እየተረሳ የጨረባ የስብዕና ግንባታ እንደ አዎቂነት እየተወሰደ ነው ።
✍️ እንደ መውጫ⁉️
በመጨረሻም፣ የአብዛኛውን ሰው ትኩረት ፍለጋ የወጣቶችን የጊዜያዊ እርካታ ፍላጎት ሊያረካ ቢችልም፣የዘላቂነት ጥበብን እና ጥልቅ የማኅበረሰብ ትስስርን የሚያሳጣ አደገኛ መንገድ ነው። ሁላችንም እውነተኛ እሴት የሚገኘው ከውስጣዊ ማንነት እና ከተከማቸ የጥበብ ምንጭ እንጂ፣ ከዲጂታል ምላሾች ብዛት አለመሆኑን መገንዘብ ይኖርብናል።ይህንም ለልጆቻችን ምን እንደምናስተምራቸው ቆም ብለን ማሰብ ወይም የማህበረሰብ ንግግር ( community conversation ) የሚስፈልግ ይመስለኛል ።
Ethiopia 🇪🇹
ለበለጠ ወዳጅነት የፃሃፊውን የኤክስ(X) እና የፌስቡክ ገፅ ይከታተሉ :-
🔗የኤክስ(X)ገፅ:-https://x.com/HDebasu?t=eR...
🔗የፌስቡክ:-https://www.facebook.com/s...
መልካም እሁድ 🙏
8 months ago
በሳምንቱ መጨረሻ እንደተለመደው አትሌቶቻችን በተለያዩ ሀገራት በተለያየ ርቀት አሸንፈዋል።
2025 Incheon marathon, South Korea
Men's
1. Gerba Dibaba 2:06:52 🇪🇹
2. Gilbert Kibet 2:06:54 🇰🇪
3. Felix Kibitok 2:06:57 🇰🇪
4. Abdisa Tola 2:08:40 🇪🇹
5. Robert Ngeno 2:09:02 🇰🇪
2025 ETHIOPIAN GREAT RUN 10KM
Men's
1. Yismaw Dillu 28:25 🇪🇹
2. Eyob Simegn 28:28 🇪🇹
3. Dinkalem Ayele 28:29 🇪🇹
4. Beniyam Melak 28:30 🇪🇹
5. Jerata Lensa 28:31 🇪🇹
6. Negesa Dekeba 28:34 🇪🇹
7. Adisu Negash 28:39 🇪🇹
8. Chim'sa Debele 28:40 🇪🇹
9. Zenebe Ayele 28:47 🇪🇹
10. B. Gatahun 28:48 🇪🇹
WOMEN
1. Likina Amebaw 27:25 🇪🇹
2. Sheila Jebet 27:55 🇰🇪
3. V. Gemetto 28:11 🇮🇹
4. Idaira Suarez 28:19 🇪🇸
5. Noshim Kimuge 28:33 🇰🇪
Men
1. Mathew Kipsang 23:10 🇰🇪
2. Rodrigue Kwizera 23:11 🇧🇮
3. Mathew Kipkoech 23:13 🇰🇪
4.T. Ndikumwenayo 23:13 🇪🇸
5. Naibei Kiplimo 23:45 🇰🇪
NBF Fujairah 10km (Émirats arabes unis)
1. Abu Salim Mayanja UGA 28:28, 2. Dagne Demsie ETH 28h30,
3. Feyisa Tadese ETH 28:31,
6.7km Cross Cinque Mulini, Italy
Winner: Yenenesh Shimket 19:11 🇪🇹
Via: Toprun news
#athletics #running #5km #10km #15km #halfmarathon #worldathletics #followers #highlight #ethiorunners #ethiorunnersfan #ethiopianathletics #ethiopianathleticsfederation
✍️
Wondmagegn Getachew Yigezu
2025 Incheon marathon, South Korea
Men's
1. Gerba Dibaba 2:06:52 🇪🇹
2. Gilbert Kibet 2:06:54 🇰🇪
3. Felix Kibitok 2:06:57 🇰🇪
4. Abdisa Tola 2:08:40 🇪🇹
5. Robert Ngeno 2:09:02 🇰🇪
2025 ETHIOPIAN GREAT RUN 10KM
Men's
1. Yismaw Dillu 28:25 🇪🇹
2. Eyob Simegn 28:28 🇪🇹
3. Dinkalem Ayele 28:29 🇪🇹
4. Beniyam Melak 28:30 🇪🇹
5. Jerata Lensa 28:31 🇪🇹
6. Negesa Dekeba 28:34 🇪🇹
7. Adisu Negash 28:39 🇪🇹
8. Chim'sa Debele 28:40 🇪🇹
9. Zenebe Ayele 28:47 🇪🇹
10. B. Gatahun 28:48 🇪🇹
WOMEN
1. Likina Amebaw 27:25 🇪🇹
2. Sheila Jebet 27:55 🇰🇪
3. V. Gemetto 28:11 🇮🇹
4. Idaira Suarez 28:19 🇪🇸
5. Noshim Kimuge 28:33 🇰🇪
Men
1. Mathew Kipsang 23:10 🇰🇪
2. Rodrigue Kwizera 23:11 🇧🇮
3. Mathew Kipkoech 23:13 🇰🇪
4.T. Ndikumwenayo 23:13 🇪🇸
5. Naibei Kiplimo 23:45 🇰🇪
NBF Fujairah 10km (Émirats arabes unis)
1. Abu Salim Mayanja UGA 28:28, 2. Dagne Demsie ETH 28h30,
3. Feyisa Tadese ETH 28:31,
6.7km Cross Cinque Mulini, Italy
Winner: Yenenesh Shimket 19:11 🇪🇹
Via: Toprun news
#athletics #running #5km #10km #15km #halfmarathon #worldathletics #followers #highlight #ethiorunners #ethiorunnersfan #ethiopianathletics #ethiopianathleticsfederation
✍️
Wondmagegn Getachew Yigezu
12 months ago
ሳትማሩ ‘ባለሙያ ነን’ አትበሉ
ገንዘብ ለማግኘት ብላችሁ የወላጆችን ሸክም አታክብዱ
መቼም በጣም ደፋር ሰዎች የሞሉበት ሃገር ላይ ነን ያለነው፡፡ አንድ 'ማህበራዊ ቀዳዳ’ ሲገኝ ለመክበር ስንል በሱ በኩል ‘ያለሳይዛችን’ ለማለፍ ስንታገል ቀዳዳውን የምናሰፋ ሰዎች ነን፡፡
ይህንን ጽሁፍ እንደክፍል ሁለት ውሰዱት፡፡ በክፍል አንድ ላይ እንደነገርኳችሁ ኦቲዝም ለኢትዮጵያውያን ወላጆች በጣም ውድ ችግር ነው፡፡ እንኳን ለወጣል የሃገራቸውን ኦቲዝምን ማህበረሰብ ጫና ለተሸከሙ እንደእንግሊዝ እና አሜሪካ ላሉ መንግስታትም ኦቲዝም በየዓመቱ ቢሊዮን ዶላሮችን የሚያስወጣ ብሄራዊ ችግር ሆኗል፡፡
እንደኛ ባለ መቆም ቀርቶ ዳዴ ማለት ባቃተው ሃገር ላይ ደግሞ የችግሩን ጥነት ማሰብ ራሱ ያደክማል፡፡ በዚህ ውድነት ላይ አላግባብ መነገድ ነው እንግዲህ ዋናው ሃጢአት፡፡
በሃገራችን ከኦቲዝምና ተያያዠ የዐዕምሮ ዕድገት ስርዓት መዛባት ጋር የተያያዙ ማህበራዊ ችግሮች በዝተዋል፡፡ ያንን ተከትሎ ምርመራና ልየታን ጨምሮ የቋንቋና ንግግር ፤ የባህሪ ማረቅ (ABA) ፣ የተግባቦትና የክወና ክህሎትቴራፒ የሚሰጡ ባለሙያዎችን የመጠቀም ፍላጎትም በጣም ጨምሯል፡፡
ከዚህ የፍላጎት ዕድገት ጋር ተያይዞም 'ባለሙያ ነን' የሚሉ ሰዎች እዚህም እዚያም እንደአሸን እየፈሉ ነው፡፡ከነዚህ መካከል ስራውን ለመስራት ትምህርቱም፣ ልምዱም፣ ብቃቱም ያላቸው ባለሙያዎች ቢኖሩም ከነርሱ በእጥፍ የሚበዙት ግን ለዚህ የሚያበቃ ምንም ብቃት የላቸውም፡፡
ቲክቶክ ላይ መድረክ አገኘን ብለው “ኦቲዝምን እንመረምራለን፣ የንግግር ፣ የክዋኔ፣ የተግባቦት፣ የማህበራዊ ክህሎት ቴራፒ እንሰጣለን” እያሉ ራሳቸውን በድፍረት ሲያስተዋውቁ የሚውሉ አሸን ናቸው፡፡ ያንን አይቶ የተጎዳ ልጁን ይዞ የሚጎርፍላቸውን ወላጅ በውድ ዋጋ ቆዳውን እንደበግ ገፍፈው ያለውጤት የሚሸኙና የብዙሃኑን ኪስ የሚያራቁቱ ‘የልምድ አዋላጆች’ በርክተዋል፡፡
በድፍረት የማሰልጠኛ ማኑዋል የሚያዘጋጁ፣ “በኦቲዝም ‘ቴራፒስትነት’ አሰልጥነን ስራ እናስቀጥራለን” የሚል ማስታወቂያ ሰርተው ፣ሰርተፍኬት ሰጥተው የእነዚህን ህጻናትን ዕድሜ በነርሱ የለብለብ ሰልጣኞች እጅ ላይ የሚጥሉ ራስወዳድ ሰዎች ብዙ ናቸው፡፡
ሃሜት አይደለም የማወራው ፣ ምናልባት ይህንን አንብበው የሚሰሩት ስራ ተገቢ አለመሆኑን ቆም ብለው ቢያስቡ እድል ለመስጠት እንጂ አስፈላጊ ሲሆን በስም ልዘረዝራቸው እችላለሁ፡፡
መቼም የትኛውም ቢዝነስ የሚፈጠረው አንድ ችግር ለመፍታትና ገቢ ለማግኘት ነው፡፡ አገልግሎት ፈላጊ ሲኖር አገልግሎት ሰጪ በዚያው መጠን መፈጠሩ የሚበረታታ ነው፡፡ ነገር ግን ለነዚህ ልዩ ፍላጎት ያላቸው ልጆች አገልግሎት እንሰጣለን የሚሉት እውን ባለሙያዎች ናቸወይ?...
እየተሰጠ ያለውና ከፍተኛ ገንዘብ የሚጠየቅበት ‘አገልግሎትስ’ በርግጥም ልጆቹን የሚጠቅም ነወይ? ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል፡፡
እየታዘብኩት "ሳያውቁ የመስራት፣ ሳይማሩ የማስተማር" ጎጂና አደገኛ 'የቢዝነስ መረብ' በጣም የሚያሳስበኝም ለዚህ ነው፡፡
ይህ 'ኦቲዝምን ቢዝነስ የማድረግ' ተግባር ወላጆችን ለአላስፈላጊ ወጪና ልፋት ፣ ወርቃማ የሆነውን የኦቲዝም ልጆችን ለጋ እድሜ ደግሞ ለመሻሻል በማይጠቅማቸው 'መግባት መውጣት' አዙሪት ውስጥ እየከተተ ነው፡፡
በባለሙያ ቢታገዝ ፍሬ ሊገኝበት የሚችለውን ኦቲዝም ለተግባር የማይበቃ ዕውቀት የያዙ “ኦቲዝም ላይ እንሰራለን” የሚሉ ሰዎች ውጤት አልባ እያደረጉት ነው፡፡ የብዙሃን ወላጆችን እና የኦቲዝም ልጆችን ተስፋም እያጠወለጉት ነው፡፡
እዚህ ጋር መንግስትን እጠራለሁ!!
እንዳለመታደል ሆኖ በሃገራችን እንደ ኦቲዝም እና ሌሎች ከዐዕምሮ ዕድገት ስርዓት መዛባት ጋር የተያያዙ ኹኔታዎች ላይ ጥርት ያለ ፖሊሲ፡ መርህ ወይም መመሪያ የለም፡፡ ጤና ሚኒስቴር በዚህ አሳሳቢ ጉዳይ ላይ አንዳችም እንቅስቃሴ ሲያደርግ አይታይም ፡፡
ማን ምርመራ ማካሄድ እንደሚችል ፣ ማን የባህሪ፣ የክዋኔ ፣ የቋንቋና ንግግር፣ የማህበራዊ ተራክቦ ወዘተ ህክምና(ቴራፒ) የመስጠት ብቃት እንዳለው ፣ ማን የኦቲዝም የምግብ ዕቅድ (Diet plan) ማውጣትና ማዘዝ እንደሚችል ወዘተ የሚደነግግ መመሪያ የለም፡፡
በኦቲዝምና ተዛማጅ የዐዕምሮ እድገት ጉዳዮች ላይ ለመስራት ምን ዓይነት ስልጠናና የትምህርት ዝግጅት ፣ የስንት ጊዜ የተግባር ልምምድ እንደሚያስፈልግ የተቀመጠ መመሪያም የለም፡፡
ምርመራና ቴራፒ የሚሰጥባቸው ተቋማት ለዚህ ስራ ማሟላት በሚገባቸው መሰረታዊ ግብዓቶችና መሰረተ ልማቶች ላይም ይህ ነው ተብሎ የተቀመጠ መስፈርትም የለም፡፡ ዝም ብሎ ዴይኬር በሚቋቋምበት መስፈርት ነው የሚፈቀደው፡፡ ከጤና ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ባለው በዚህ ዘርፍ ላይ ለመስራት በርካታ መመዘኛዎች ያስፈልጉ ነበር፡፡
በኦቲዝም ላይ እየሰሩ ላሉ ሃኪሞችም ቢሆን ከጤና ሚኒስቴርም ይሁን ከሌሎች መንግስታዊ አካላት የተሰጠ ፍቃድ ስለመኖሩ እጠራጠራለሁ፡፡ ለቴራፒስቶችም ቢሆን (ቀጥታ ከጤና ኹኔታ ጋር የሚያያዝ ስራ ስለሚሰሩ) የሙያና የስራ ፍቃድ እንደሚያስፈልግ አልታሰበበትም፡፡
በዚህ ሳቢያ ኢትዮጵያ ውስጥ ኦቲዝም ‘እችላለሁ’ ያለ ሁሉ እየተነሳ “ቢዝነስ’ የሚሰራበት ‘ያልተበላ የንግድ ዘርፍ’ (Lucrative Business) እየሆነ መጥቷል፡፡ ይህ ደግሞ በኢትዮጵያ ውስጥ ላሉ ቁጥራቸው ከሚሊዮኖች ለሚበልጥ ከኦቲዝም ጋር ለሚኖሩ ልጆች፣ ወጣቶችና ወላጆቻቸው እጅግ ተስፋ አስቆራጭና አሳሳቢ ተግባር ነው፡፡
ዛሬ ኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲን እና አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን ጨምሮ በሃገር ውስጥና በውጭ ሃገር በልዩ ፍላጎት ትምህርት (Special need Education) እና በንግግርና ቋንቋ ህክምና (Speech-language pathology) ዘርፎች በሁለተኛ ዲግሪ ጭምር ትምህርት ይሰጣል፡፡ የመጀመሪያ ትምህርታቸው ስነልቡና እና ስነዐዕምሮ ላይ የሆኑ የልዩ ፍላጎት ባለሙያዎች ይህንን ትምህርት ሲጨምሩበት ብቃት ያላቸው ባለሙያዎች ይወጣቸዋል ፡፡
ችግሩ ግን አሁን በስራ ላይ ያሉት ‘ቴራፒስቶች’ የት ተምረው ቴራፒስት ሆኑ? ‘የልዩ ፍላጎት ማሰልጠኛ’ ከፈትን የሚሉትስ ምን ያህሉ በዚህ መደበኛ የትምህርትና ስልጠና ሂደት አልፈዋል?" ብለን ብንጠይቅ መልሱ አሳዛኝ ነው፡፡
በየሰፈሩ ‘የንግግር፣ የባህሪ ምናምን ቴራፒ እንሰጣለን’ ብለው ቢሮ የከፈቱ ፣ ከጨነቀው ወላጅ ላይ በሰዓት ከፍተኛ ገንዘብ እየተቀበሉ የሚመዘብሩ ግለሰቦችንስ ማን ፍቃድ ሰጥቷቸው ነው ወደዚህ ስራ የገቡት ? ማንም! ምክንያቱም ፍቃድ ሰጪም ነሺም አካል የለማ!!
የቅድመመደበኛ ወይም አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ሆነው ሳለ ‘የልዩ ፍላጎት አካቶ ትምህርት እንሰጣለን’ በማለት እንደኦቲዝም ያለ ከዐዕምሮ ዕድገት ጋር የተያያዘ ጉዳይ ያላቸውን ህጻናት ከመደበኞቹ ጋር አንድ ላይ አጅለው የሚያስተምሩና የወላጅ ትከሻን የሚያደቅቅ ገንዘብ በየወሩ የሚቀበሉ ትምህርት ቤቶችስ “በምን መለኪያና የቁጥጥር ስርዓት አልፈው ነው ይህንን ‘ንግድ’ የሚያከናውኑት ?” የሚለውም እስካሁን ያልተመለሰ ጥያቄ ሆኖ ቀጥሏል፡፡
ስለዚህ እንደኔ እንደኔ መንግስት በዚህ ማህበራዊ ችግር ውስጥ በአስቸኳይ እጁን ማስገባት አለበት፡፡ የግል አገልግሎት ሰጪዎችን ፍቃድ አሰጣጥና ቁጥጥር ላይ አስገዳጅ መመሪያ ማውጣት አለበት፡፡
ለውሣኔም ለተግባርም መነሻ ስለሚሆን የኦቲዝም ስርጭት መጠን ( prevalence rate) ማሳያ ብሔራዊ መረጃ (National Data) አስጠንቶ ይያዝ ።
ማሰልጠኛዎችን መክፈት አለበት፣ እነዚህ ልጆች አግባብ ያለው አገልግሎት ማግኘት የሚችሉባቸውን ማዕከላት መክፈት በመንግስት ትምህርት ቤቶች ግቢ ውስጥ በተጓዳኝ ዘርፍ ማደራጀት አለበት፡፡
በአጠቃላይ ልጆቹ ዜጎች ናቸውና ከሌሎች ልጆች እኩል የመማርና አገለግሎት የማግኘት መብታቸውን ማስከበር አለበት፡፡ መንግስት ካልገባበት ይህ ልምምድ ሰፍቶ ነገ ወላጅንም፣ ማህበረሰቡንም ሃገርን ዋጋ እንዳያስከፍላት እሰጋለሁ፡፡
በነገራችን ላይ!
ከነዚህ የኦቲዝም ልጆች መካከል እኮ ልዩ IQ የታደሉ እነ ኤይንስታይን አሉ፣ እነሜሲ አሉ፣ እነዳቬንቺ አሉ፣ እነሞዛርት አሉ፣ እነስቲቭ ጆብስ አሉ፣ እነኤሎን መስክ አሉ፣ እነቢል ጌትስ አሉ…. ምቹ ሁኔታ ሲያገኙ አለምን የሚለውጡ ብሩህና ስማርት ልጆች ባሉበት ኦቲዝም ላይ መንግስት ዝምታውን ሊሰብር፡ ትርጉም ያለው እንቅስቃሴም ማድረግ አለበት ባይ ነኝ፡፡
ግድ የላችሁም! ነገ ሃገርን የሚጠቅማት ሰው ከነዚህ መካከል ይወጣል፡፡
Ministry of Education EthiopiaMMinistry of Health,EthiopiaMMayor Office of Addis AbabaAAddis Ababa Education BureauAAddis Ababa Trade Bureauየየሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር Ministry of Women and Social Affairs@followers@highlight
ገንዘብ ለማግኘት ብላችሁ የወላጆችን ሸክም አታክብዱ
መቼም በጣም ደፋር ሰዎች የሞሉበት ሃገር ላይ ነን ያለነው፡፡ አንድ 'ማህበራዊ ቀዳዳ’ ሲገኝ ለመክበር ስንል በሱ በኩል ‘ያለሳይዛችን’ ለማለፍ ስንታገል ቀዳዳውን የምናሰፋ ሰዎች ነን፡፡
ይህንን ጽሁፍ እንደክፍል ሁለት ውሰዱት፡፡ በክፍል አንድ ላይ እንደነገርኳችሁ ኦቲዝም ለኢትዮጵያውያን ወላጆች በጣም ውድ ችግር ነው፡፡ እንኳን ለወጣል የሃገራቸውን ኦቲዝምን ማህበረሰብ ጫና ለተሸከሙ እንደእንግሊዝ እና አሜሪካ ላሉ መንግስታትም ኦቲዝም በየዓመቱ ቢሊዮን ዶላሮችን የሚያስወጣ ብሄራዊ ችግር ሆኗል፡፡
እንደኛ ባለ መቆም ቀርቶ ዳዴ ማለት ባቃተው ሃገር ላይ ደግሞ የችግሩን ጥነት ማሰብ ራሱ ያደክማል፡፡ በዚህ ውድነት ላይ አላግባብ መነገድ ነው እንግዲህ ዋናው ሃጢአት፡፡
በሃገራችን ከኦቲዝምና ተያያዠ የዐዕምሮ ዕድገት ስርዓት መዛባት ጋር የተያያዙ ማህበራዊ ችግሮች በዝተዋል፡፡ ያንን ተከትሎ ምርመራና ልየታን ጨምሮ የቋንቋና ንግግር ፤ የባህሪ ማረቅ (ABA) ፣ የተግባቦትና የክወና ክህሎትቴራፒ የሚሰጡ ባለሙያዎችን የመጠቀም ፍላጎትም በጣም ጨምሯል፡፡
ከዚህ የፍላጎት ዕድገት ጋር ተያይዞም 'ባለሙያ ነን' የሚሉ ሰዎች እዚህም እዚያም እንደአሸን እየፈሉ ነው፡፡ከነዚህ መካከል ስራውን ለመስራት ትምህርቱም፣ ልምዱም፣ ብቃቱም ያላቸው ባለሙያዎች ቢኖሩም ከነርሱ በእጥፍ የሚበዙት ግን ለዚህ የሚያበቃ ምንም ብቃት የላቸውም፡፡
ቲክቶክ ላይ መድረክ አገኘን ብለው “ኦቲዝምን እንመረምራለን፣ የንግግር ፣ የክዋኔ፣ የተግባቦት፣ የማህበራዊ ክህሎት ቴራፒ እንሰጣለን” እያሉ ራሳቸውን በድፍረት ሲያስተዋውቁ የሚውሉ አሸን ናቸው፡፡ ያንን አይቶ የተጎዳ ልጁን ይዞ የሚጎርፍላቸውን ወላጅ በውድ ዋጋ ቆዳውን እንደበግ ገፍፈው ያለውጤት የሚሸኙና የብዙሃኑን ኪስ የሚያራቁቱ ‘የልምድ አዋላጆች’ በርክተዋል፡፡
በድፍረት የማሰልጠኛ ማኑዋል የሚያዘጋጁ፣ “በኦቲዝም ‘ቴራፒስትነት’ አሰልጥነን ስራ እናስቀጥራለን” የሚል ማስታወቂያ ሰርተው ፣ሰርተፍኬት ሰጥተው የእነዚህን ህጻናትን ዕድሜ በነርሱ የለብለብ ሰልጣኞች እጅ ላይ የሚጥሉ ራስወዳድ ሰዎች ብዙ ናቸው፡፡
ሃሜት አይደለም የማወራው ፣ ምናልባት ይህንን አንብበው የሚሰሩት ስራ ተገቢ አለመሆኑን ቆም ብለው ቢያስቡ እድል ለመስጠት እንጂ አስፈላጊ ሲሆን በስም ልዘረዝራቸው እችላለሁ፡፡
መቼም የትኛውም ቢዝነስ የሚፈጠረው አንድ ችግር ለመፍታትና ገቢ ለማግኘት ነው፡፡ አገልግሎት ፈላጊ ሲኖር አገልግሎት ሰጪ በዚያው መጠን መፈጠሩ የሚበረታታ ነው፡፡ ነገር ግን ለነዚህ ልዩ ፍላጎት ያላቸው ልጆች አገልግሎት እንሰጣለን የሚሉት እውን ባለሙያዎች ናቸወይ?...
እየተሰጠ ያለውና ከፍተኛ ገንዘብ የሚጠየቅበት ‘አገልግሎትስ’ በርግጥም ልጆቹን የሚጠቅም ነወይ? ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል፡፡
እየታዘብኩት "ሳያውቁ የመስራት፣ ሳይማሩ የማስተማር" ጎጂና አደገኛ 'የቢዝነስ መረብ' በጣም የሚያሳስበኝም ለዚህ ነው፡፡
ይህ 'ኦቲዝምን ቢዝነስ የማድረግ' ተግባር ወላጆችን ለአላስፈላጊ ወጪና ልፋት ፣ ወርቃማ የሆነውን የኦቲዝም ልጆችን ለጋ እድሜ ደግሞ ለመሻሻል በማይጠቅማቸው 'መግባት መውጣት' አዙሪት ውስጥ እየከተተ ነው፡፡
በባለሙያ ቢታገዝ ፍሬ ሊገኝበት የሚችለውን ኦቲዝም ለተግባር የማይበቃ ዕውቀት የያዙ “ኦቲዝም ላይ እንሰራለን” የሚሉ ሰዎች ውጤት አልባ እያደረጉት ነው፡፡ የብዙሃን ወላጆችን እና የኦቲዝም ልጆችን ተስፋም እያጠወለጉት ነው፡፡
እዚህ ጋር መንግስትን እጠራለሁ!!
እንዳለመታደል ሆኖ በሃገራችን እንደ ኦቲዝም እና ሌሎች ከዐዕምሮ ዕድገት ስርዓት መዛባት ጋር የተያያዙ ኹኔታዎች ላይ ጥርት ያለ ፖሊሲ፡ መርህ ወይም መመሪያ የለም፡፡ ጤና ሚኒስቴር በዚህ አሳሳቢ ጉዳይ ላይ አንዳችም እንቅስቃሴ ሲያደርግ አይታይም ፡፡
ማን ምርመራ ማካሄድ እንደሚችል ፣ ማን የባህሪ፣ የክዋኔ ፣ የቋንቋና ንግግር፣ የማህበራዊ ተራክቦ ወዘተ ህክምና(ቴራፒ) የመስጠት ብቃት እንዳለው ፣ ማን የኦቲዝም የምግብ ዕቅድ (Diet plan) ማውጣትና ማዘዝ እንደሚችል ወዘተ የሚደነግግ መመሪያ የለም፡፡
በኦቲዝምና ተዛማጅ የዐዕምሮ እድገት ጉዳዮች ላይ ለመስራት ምን ዓይነት ስልጠናና የትምህርት ዝግጅት ፣ የስንት ጊዜ የተግባር ልምምድ እንደሚያስፈልግ የተቀመጠ መመሪያም የለም፡፡
ምርመራና ቴራፒ የሚሰጥባቸው ተቋማት ለዚህ ስራ ማሟላት በሚገባቸው መሰረታዊ ግብዓቶችና መሰረተ ልማቶች ላይም ይህ ነው ተብሎ የተቀመጠ መስፈርትም የለም፡፡ ዝም ብሎ ዴይኬር በሚቋቋምበት መስፈርት ነው የሚፈቀደው፡፡ ከጤና ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ባለው በዚህ ዘርፍ ላይ ለመስራት በርካታ መመዘኛዎች ያስፈልጉ ነበር፡፡
በኦቲዝም ላይ እየሰሩ ላሉ ሃኪሞችም ቢሆን ከጤና ሚኒስቴርም ይሁን ከሌሎች መንግስታዊ አካላት የተሰጠ ፍቃድ ስለመኖሩ እጠራጠራለሁ፡፡ ለቴራፒስቶችም ቢሆን (ቀጥታ ከጤና ኹኔታ ጋር የሚያያዝ ስራ ስለሚሰሩ) የሙያና የስራ ፍቃድ እንደሚያስፈልግ አልታሰበበትም፡፡
በዚህ ሳቢያ ኢትዮጵያ ውስጥ ኦቲዝም ‘እችላለሁ’ ያለ ሁሉ እየተነሳ “ቢዝነስ’ የሚሰራበት ‘ያልተበላ የንግድ ዘርፍ’ (Lucrative Business) እየሆነ መጥቷል፡፡ ይህ ደግሞ በኢትዮጵያ ውስጥ ላሉ ቁጥራቸው ከሚሊዮኖች ለሚበልጥ ከኦቲዝም ጋር ለሚኖሩ ልጆች፣ ወጣቶችና ወላጆቻቸው እጅግ ተስፋ አስቆራጭና አሳሳቢ ተግባር ነው፡፡
ዛሬ ኮተቤ ሜትሮፖሊታን ዩኒቨርሲቲን እና አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን ጨምሮ በሃገር ውስጥና በውጭ ሃገር በልዩ ፍላጎት ትምህርት (Special need Education) እና በንግግርና ቋንቋ ህክምና (Speech-language pathology) ዘርፎች በሁለተኛ ዲግሪ ጭምር ትምህርት ይሰጣል፡፡ የመጀመሪያ ትምህርታቸው ስነልቡና እና ስነዐዕምሮ ላይ የሆኑ የልዩ ፍላጎት ባለሙያዎች ይህንን ትምህርት ሲጨምሩበት ብቃት ያላቸው ባለሙያዎች ይወጣቸዋል ፡፡
ችግሩ ግን አሁን በስራ ላይ ያሉት ‘ቴራፒስቶች’ የት ተምረው ቴራፒስት ሆኑ? ‘የልዩ ፍላጎት ማሰልጠኛ’ ከፈትን የሚሉትስ ምን ያህሉ በዚህ መደበኛ የትምህርትና ስልጠና ሂደት አልፈዋል?" ብለን ብንጠይቅ መልሱ አሳዛኝ ነው፡፡
በየሰፈሩ ‘የንግግር፣ የባህሪ ምናምን ቴራፒ እንሰጣለን’ ብለው ቢሮ የከፈቱ ፣ ከጨነቀው ወላጅ ላይ በሰዓት ከፍተኛ ገንዘብ እየተቀበሉ የሚመዘብሩ ግለሰቦችንስ ማን ፍቃድ ሰጥቷቸው ነው ወደዚህ ስራ የገቡት ? ማንም! ምክንያቱም ፍቃድ ሰጪም ነሺም አካል የለማ!!
የቅድመመደበኛ ወይም አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ሆነው ሳለ ‘የልዩ ፍላጎት አካቶ ትምህርት እንሰጣለን’ በማለት እንደኦቲዝም ያለ ከዐዕምሮ ዕድገት ጋር የተያያዘ ጉዳይ ያላቸውን ህጻናት ከመደበኞቹ ጋር አንድ ላይ አጅለው የሚያስተምሩና የወላጅ ትከሻን የሚያደቅቅ ገንዘብ በየወሩ የሚቀበሉ ትምህርት ቤቶችስ “በምን መለኪያና የቁጥጥር ስርዓት አልፈው ነው ይህንን ‘ንግድ’ የሚያከናውኑት ?” የሚለውም እስካሁን ያልተመለሰ ጥያቄ ሆኖ ቀጥሏል፡፡
ስለዚህ እንደኔ እንደኔ መንግስት በዚህ ማህበራዊ ችግር ውስጥ በአስቸኳይ እጁን ማስገባት አለበት፡፡ የግል አገልግሎት ሰጪዎችን ፍቃድ አሰጣጥና ቁጥጥር ላይ አስገዳጅ መመሪያ ማውጣት አለበት፡፡
ለውሣኔም ለተግባርም መነሻ ስለሚሆን የኦቲዝም ስርጭት መጠን ( prevalence rate) ማሳያ ብሔራዊ መረጃ (National Data) አስጠንቶ ይያዝ ።
ማሰልጠኛዎችን መክፈት አለበት፣ እነዚህ ልጆች አግባብ ያለው አገልግሎት ማግኘት የሚችሉባቸውን ማዕከላት መክፈት በመንግስት ትምህርት ቤቶች ግቢ ውስጥ በተጓዳኝ ዘርፍ ማደራጀት አለበት፡፡
በአጠቃላይ ልጆቹ ዜጎች ናቸውና ከሌሎች ልጆች እኩል የመማርና አገለግሎት የማግኘት መብታቸውን ማስከበር አለበት፡፡ መንግስት ካልገባበት ይህ ልምምድ ሰፍቶ ነገ ወላጅንም፣ ማህበረሰቡንም ሃገርን ዋጋ እንዳያስከፍላት እሰጋለሁ፡፡
በነገራችን ላይ!
ከነዚህ የኦቲዝም ልጆች መካከል እኮ ልዩ IQ የታደሉ እነ ኤይንስታይን አሉ፣ እነሜሲ አሉ፣ እነዳቬንቺ አሉ፣ እነሞዛርት አሉ፣ እነስቲቭ ጆብስ አሉ፣ እነኤሎን መስክ አሉ፣ እነቢል ጌትስ አሉ…. ምቹ ሁኔታ ሲያገኙ አለምን የሚለውጡ ብሩህና ስማርት ልጆች ባሉበት ኦቲዝም ላይ መንግስት ዝምታውን ሊሰብር፡ ትርጉም ያለው እንቅስቃሴም ማድረግ አለበት ባይ ነኝ፡፡
ግድ የላችሁም! ነገ ሃገርን የሚጠቅማት ሰው ከነዚህ መካከል ይወጣል፡፡
Ministry of Education EthiopiaMMinistry of Health,EthiopiaMMayor Office of Addis AbabaAAddis Ababa Education BureauAAddis Ababa Trade Bureauየየሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር Ministry of Women and Social Affairs@followers@highlight
Sponsored by
Surafel
Comments