9 days ago
እንኳን ደስ አላችሁ፤ እንኳን ደስ አለን!
ኢትዮ ቴሌኮም ባለአክሲዮኖቹ አክሲዮናቸውን በሰነደ ሙዓለ ንዋይ ገበያ መሸጥ፣ መግዛት እና ማስተላለፍ እንደሚችሉ በታላቅ ደስታ ያበስራል!
በዛሬው ዕለት የኩባንያችን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ፤ ኩባንያው አስፈላጊ ሕጋዊ አሠራሮችን በማሟላት ባለአክሲዮኖች በሁለተኛ ገበያ (ESX) አክሲዮኖችን መግዛት፣ መሸጥና ማስተላለፍ እንዲጀምሩ ዝግጁ ማድረጉን በይፋ አብስረዋል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚያችን፤ አንጋፋውን የሀገራችንን ተቋም ወደ አክሲዮን ማኅበር በማዛወር ዜጎችን የጋራ ሀብት ባለቤት ለማድረግ፣ የሀገሪቱን የካፒታል ገበያ ለማጠናከርና የጋራ ዕድገትን ለማፋጠን የተወሰደው እርምጃ ታሪካዊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።
በተለይም ባለፉት ወራት በተከናወነ መጠነ-ሰፊ የማጣራት ሥራ ከ47,377 ባለአክሲዮኖች ውስጥ 45,366ቱ (95.8 በመቶ) ምዝገባቸውን በስኬት ማጠናቀቃቸውን ገልጸዋል። ይህም በገንዘብ ሲሰላ 3.04 ቢሊዮን ብር ዋጋ ያላቸው 10.1 ሚሊዮን አክሲዮኖች ለግብይት ዝግጁ መሆናቸውን ያረጋግጣል ብለዋል።
በሌላ በኩል መረጃ ያልተሟላላቸው 1,646 ባለአክሲዮኖች መረጃቸውን በአፋጣኝ እንዲያሟሉ ጥሪ የቀረበ ሲሆን፤ በአክሲዮን ሽያጩ ለመሳተፍ ብቁ ያልሆኑ 248 የውጭ ዜጎች ክፍያም በአሠራሩ መሠረት ተመላሽ ይደረጋል።
በዕለቱ የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ተዋናዮች በተገኙበት የአክሲዮን ግብይት ማስጀመሪያ የደወል ሥነ ሥርዓት የተከናወነ ሲሆን፣ የመጀመሪያው ግብይትም በሰነደ ሙዓለ ነዋይ ገበያው በይፋ ተከናውኗል። በተጨማሪም ኩባንያችን በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ በይፋ መመዝገቡን በማስመልከት የምስክር ወረቀቱን ዋና ሥራ አስፈጻሚያችን ከኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ነዋይ ገበያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክቡር ዶክተር ጥላሁን እስማኤል ተረክበዋል።
ባለአክሲዮኖች አክሲዮናቸውን ለመሸጥም ሆነ ለመግዛት በመጀመሪያ በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ፈቃድ ከተሰጣቸው አገበያዮች ወይም የኢንቨስትመንት ባንኮች ዘንድ በመቅረብ የንግድ አካውንት መክፈት ይኖርባቸዋል።
በመጪው በጀት ዓመት የፋይናንስ ኦዲቱ እንደተጠናቀቀ በሚጠራው የባለአክሲዮኖች ጠቅላላ ጉባኤ (AGM) ላይ የትርፍ ክፍፍል መጠን ተወስኖ ይፋ ይደረጋል። የባለቤትነት ድርሻቸውን ሂደት ያጠናቀቁ ባለአክሲዮኖች፤ የባለቤትነት መብታቸው ከያዝነው በጀት ዓመት መጀመሪያ ጀምሮ የሚጠበቅላቸው ይሆናል።
ለተጨማሪ መረጃ፦ https://bit.ly/4nROnuL
#ethiotelecom #ecma #capitalmarket #esx #csd
ኢትዮ ቴሌኮም ባለአክሲዮኖቹ አክሲዮናቸውን በሰነደ ሙዓለ ንዋይ ገበያ መሸጥ፣ መግዛት እና ማስተላለፍ እንደሚችሉ በታላቅ ደስታ ያበስራል!
በዛሬው ዕለት የኩባንያችን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ፤ ኩባንያው አስፈላጊ ሕጋዊ አሠራሮችን በማሟላት ባለአክሲዮኖች በሁለተኛ ገበያ (ESX) አክሲዮኖችን መግዛት፣ መሸጥና ማስተላለፍ እንዲጀምሩ ዝግጁ ማድረጉን በይፋ አብስረዋል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚያችን፤ አንጋፋውን የሀገራችንን ተቋም ወደ አክሲዮን ማኅበር በማዛወር ዜጎችን የጋራ ሀብት ባለቤት ለማድረግ፣ የሀገሪቱን የካፒታል ገበያ ለማጠናከርና የጋራ ዕድገትን ለማፋጠን የተወሰደው እርምጃ ታሪካዊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።
በተለይም ባለፉት ወራት በተከናወነ መጠነ-ሰፊ የማጣራት ሥራ ከ47,377 ባለአክሲዮኖች ውስጥ 45,366ቱ (95.8 በመቶ) ምዝገባቸውን በስኬት ማጠናቀቃቸውን ገልጸዋል። ይህም በገንዘብ ሲሰላ 3.04 ቢሊዮን ብር ዋጋ ያላቸው 10.1 ሚሊዮን አክሲዮኖች ለግብይት ዝግጁ መሆናቸውን ያረጋግጣል ብለዋል።
በሌላ በኩል መረጃ ያልተሟላላቸው 1,646 ባለአክሲዮኖች መረጃቸውን በአፋጣኝ እንዲያሟሉ ጥሪ የቀረበ ሲሆን፤ በአክሲዮን ሽያጩ ለመሳተፍ ብቁ ያልሆኑ 248 የውጭ ዜጎች ክፍያም በአሠራሩ መሠረት ተመላሽ ይደረጋል።
በዕለቱ የኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ተዋናዮች በተገኙበት የአክሲዮን ግብይት ማስጀመሪያ የደወል ሥነ ሥርዓት የተከናወነ ሲሆን፣ የመጀመሪያው ግብይትም በሰነደ ሙዓለ ነዋይ ገበያው በይፋ ተከናውኗል። በተጨማሪም ኩባንያችን በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ በይፋ መመዝገቡን በማስመልከት የምስክር ወረቀቱን ዋና ሥራ አስፈጻሚያችን ከኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ነዋይ ገበያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክቡር ዶክተር ጥላሁን እስማኤል ተረክበዋል።
ባለአክሲዮኖች አክሲዮናቸውን ለመሸጥም ሆነ ለመግዛት በመጀመሪያ በኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ፈቃድ ከተሰጣቸው አገበያዮች ወይም የኢንቨስትመንት ባንኮች ዘንድ በመቅረብ የንግድ አካውንት መክፈት ይኖርባቸዋል።
በመጪው በጀት ዓመት የፋይናንስ ኦዲቱ እንደተጠናቀቀ በሚጠራው የባለአክሲዮኖች ጠቅላላ ጉባኤ (AGM) ላይ የትርፍ ክፍፍል መጠን ተወስኖ ይፋ ይደረጋል። የባለቤትነት ድርሻቸውን ሂደት ያጠናቀቁ ባለአክሲዮኖች፤ የባለቤትነት መብታቸው ከያዝነው በጀት ዓመት መጀመሪያ ጀምሮ የሚጠበቅላቸው ይሆናል።
ለተጨማሪ መረጃ፦ https://bit.ly/4nROnuL
#ethiotelecom #ecma #capitalmarket #esx #csd
1 month ago
ላለፉት ስድስት አመታት ልደቷን ምክንያት በማድረግ እርዳታ እያሰባሰበች የልብ ህሙማን ህፃናትን ስታሳክም ቆይታለች። በሺዎች የሚቆጠሩ ህፃናት ከሞት እንዲተርፉ ምክንያት ሆናለች። የብዙ ወላጆች ስቃይ ቀንሷል እንባም ታብሷል። ዛሬ ደግሞ እሷን የምናመሰግንበት ጊዜ ነው። ሊንኩ ከታች አለ። ድምፃችን በክብር የምናበረክትላት ምስጋናችን ነው።
Please vote for Hiwot Tadesse
https://crownofhumanityawa...
Please vote for Hiwot Tadesse
https://crownofhumanityawa...
3 months ago
በአንድ ሳምንት 87.4 ቢሊዮን ብር ተንቀሳቀሰ!
#ethiopia | በኢትዮጵያ የባንኮች መካከል የገንዘብ ግብይት ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ከፍተኛ የገንዘብ ዝውውር ተመዘገበ። የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋይ ገበያ ባወጣው ሳምንታዊ ሪፖርት መሠረት፣ ባሳለፍነው ሳምንት (ከየካቲት 16 እስከ 20 ቀን 2018 ዓ.ም) ብቻ 87.4 ቢሊዮን ብር የሚያወጣ የአንድ ቀን (Overnight) የገንዘብ ልውውጥ ተከናውኗል።
የሳምንቱ ቁልፍ ስኬቶች፦
* አዲስ ክብረ ወሰን፦ በሳምንት ውስጥ የተመዘገበው የ87.4 ቢሊዮን ብር ግብይት፣ በጥር ወር ተመዝግቦ የነበረውን የ53 ቢሊዮን ብር ክብረ ወሰን በከፍተኛ ልዩነት ሰብሮታል።
* የስምምነቶች ብዛት፦ በአምስት የሥራ ቀናት ውስጥ ብቻ 125 የአንድ ቀን ተመላሽ የብድር ስምምነቶች ተፈጽመዋል።
* ወደ 2 ትሪሊዮን፦ አጠቃላይ የተከማቸ የግብይት መጠን 1.96 ትሪሊዮን ብር የደረሰ ሲሆን፣ በሚቀጥለው ሳምንት የ2 ትሪሊዮን ብር ማዕቀፍን እንደሚሻገር ይጠበቃል።
ለምን አደገ?
የዚህ ዕድገት ዋነኛ ምክንያቶች ባንኮች በዘመናዊው የገንዘብ ፖሊሲ ማዕቀፍ ላይ ያላቸው እምነት መጨመር እና የዕለት ተዕለት የገንዘብ ፍላጎታቸውን (Liquidity) ለመሙላት ገበያውን እንደ ቀዳሚ አማራጭ መጠቀም መጀመራቸው ነው። ቀደም ሲል የሰባት ቀን ግብይቶች ይይዙት የነበረው የበላይነት አሁን ወደ አንድ ቀን ግብይት መዞሩ ገበያው ምን ያህል ፈጣንና ቀልጣፋ እየሆነ መምጣቱን ያሳያል።
ጥቅምት 2017 ዓ.ም የተጀመረው ይህ ገበያ፣ በአምስት ወራት ውስጥ ብቻ የግብይት መጠኑን በእጥፍ ማሳደግ መቻሉ ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ መረጋጋት ትልቅ ተስፋን የሰነቀ ሆኗል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ኢትዮጵያ #ባንክ #የገንዘብገበያ #ኢኮኖሚ #ethiopia #banking #economy #esx #financenews
#ethiopia | በኢትዮጵያ የባንኮች መካከል የገንዘብ ግብይት ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ከፍተኛ የገንዘብ ዝውውር ተመዘገበ። የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋይ ገበያ ባወጣው ሳምንታዊ ሪፖርት መሠረት፣ ባሳለፍነው ሳምንት (ከየካቲት 16 እስከ 20 ቀን 2018 ዓ.ም) ብቻ 87.4 ቢሊዮን ብር የሚያወጣ የአንድ ቀን (Overnight) የገንዘብ ልውውጥ ተከናውኗል።
የሳምንቱ ቁልፍ ስኬቶች፦
* አዲስ ክብረ ወሰን፦ በሳምንት ውስጥ የተመዘገበው የ87.4 ቢሊዮን ብር ግብይት፣ በጥር ወር ተመዝግቦ የነበረውን የ53 ቢሊዮን ብር ክብረ ወሰን በከፍተኛ ልዩነት ሰብሮታል።
* የስምምነቶች ብዛት፦ በአምስት የሥራ ቀናት ውስጥ ብቻ 125 የአንድ ቀን ተመላሽ የብድር ስምምነቶች ተፈጽመዋል።
* ወደ 2 ትሪሊዮን፦ አጠቃላይ የተከማቸ የግብይት መጠን 1.96 ትሪሊዮን ብር የደረሰ ሲሆን፣ በሚቀጥለው ሳምንት የ2 ትሪሊዮን ብር ማዕቀፍን እንደሚሻገር ይጠበቃል።
ለምን አደገ?
የዚህ ዕድገት ዋነኛ ምክንያቶች ባንኮች በዘመናዊው የገንዘብ ፖሊሲ ማዕቀፍ ላይ ያላቸው እምነት መጨመር እና የዕለት ተዕለት የገንዘብ ፍላጎታቸውን (Liquidity) ለመሙላት ገበያውን እንደ ቀዳሚ አማራጭ መጠቀም መጀመራቸው ነው። ቀደም ሲል የሰባት ቀን ግብይቶች ይይዙት የነበረው የበላይነት አሁን ወደ አንድ ቀን ግብይት መዞሩ ገበያው ምን ያህል ፈጣንና ቀልጣፋ እየሆነ መምጣቱን ያሳያል።
ጥቅምት 2017 ዓ.ም የተጀመረው ይህ ገበያ፣ በአምስት ወራት ውስጥ ብቻ የግብይት መጠኑን በእጥፍ ማሳደግ መቻሉ ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ መረጋጋት ትልቅ ተስፋን የሰነቀ ሆኗል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ኢትዮጵያ #ባንክ #የገንዘብገበያ #ኢኮኖሚ #ethiopia #banking #economy #esx #financenews
4 months ago
የኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሬ ገበያ ወደ አዲስ ምዕራፍ፡ ባንኮች በዲጂታል መድረክ እርስ በእርስ መገበያየት ጀመሩ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የፋይናንስ ታሪክ የሚቀይር "የባንክ ለባንክ የውጭ ምንዛሬ ግብይት" በዘመናዊ የቴክኖሎጂ ሥርዓት (Automated Trading Platform) መጀመሩን በይፋ አበሰረ።
ይህ አሠራር ባንኮች ያላቸውን ትርፍ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ላለባቸው ባንኮች በገበያ ዋጋ የሚሸጡበት ግልጽ መድረክ ነው።
🌍 የሌሎች ሀገራት ተሞክሮ ምን ያስተምረናል?
ኢትዮጵያ አሁን የጀመረችው ይህ ሥርዓት በዓለም አቀፍ ደረጃ ስኬታማ በሆኑ ሀገራት የተሞከረና ውጤታማነቱ የተረጋገጠ ነው።
ቬትናም : እ.ኤ.አ በ1990ዎቹ መጀመሪያ ላይ ተመሳሳይ የኢንተርባንክ (Interbank) ገበያ በመጀመሯ፣ በሀገሪቱ የነበረውን ጥቁር ገበያ በእጅጉ መቀነስ ችላለች። ይህም የውጭ ኢንቨስተሮች በሀገሪቱ የፋይናንስ ሥርዓት ላይ እምነት እንዲኖራቸው አድርጓል።
ግብፅ : እ.ኤ.አ በ2016 የውጭ ምንዛሬ ተመንን ለገበያ ክፍት ካደረገች በኋላ፣ የባንክ ለባንክ ግብይቱን በማጠናከሯ በባንኮች ውስጥ ያለውን የውጭ ምንዛሬ ፈሳሽነት (Liquidity) በከፍተኛ ደረጃ ማሳደግ ችላለች።
ናይጄሪያ : ምንም እንኳን ተግዳሮቶች ቢገጥሟትም፣ የዲጂታል ግብይት ሥርዓቱን በማዘመኗ የውጭ ምንዛሬ ተመን ግልጽ በሆነ መንገድ በየቀኑ እንዲታወቅና ግምታዊ ግብይት (Speculation) እንዲቀንስ ረድቷታል።
💎 የአዲሱ ሥርዓት ልዩ ባህሪያት
"ሪል ታይም" ግብይት፦ በኢትዮጵያ ሰኩሪቲስ ኤክስቼንጅ (ESX) በኩል የሚመራው ይሄው መድረክ፣ ባንኮች በሰከንዶች ውስጥ የዋጋ ማቅረቢያና ሽያጭ እንዲያከናውኑ ያስችላቸዋል።
የመረጃ እኩልነት፦ ቀደም ሲል የነበረውን "መረጃ ያለው ብቻ ያተርፋል" የሚለውን አሠራር በማስቀረት፣ ሁሉም ባንኮች የገበያውን እንቅስቃሴ በእኩልነት እንዲያዩ ያደርጋል።
ጥብቅ ቁጥጥር፦ ብሔራዊ ባንክ በዳሽቦርዱ በኩል እያንዳንዱን ግብይት በቀጥታ ይከታተላል፤ ይህም ሕገ-ወጥ አሠራሮችንና የዋጋ መዛባትን ይከላከላል።
🎤 የባንኩ ገዥ ዶ/ር እዮብ ተካልኝ ምን አሉ?
"ዛሬ የተጀመረው የቴክኖሎጂ ሥርዓት የፋይናንስ ዘርፋችንን ለማዘመን የወሰድነው ትልቁ እርምጃ ነው። ይህም ግልጽነትን በማስፈን፣ ትክክለኛ የገበያ ዋጋ እንዲወጣ በማድረግ እና ለጠቅላላው ኢኮኖሚ መረጋጋት የጀርባ አጥንት ይሆናል።"
📌 ለምን ይጠቅመናል?
ይህ ሥርዓት ተግባራዊ መሆኑ የውጭ ምንዛሬ በአንድ ባንክ ብቻ ታጥሮ እንዳይቀር ያደርጋል። አንድ ባንክ ምንዛሬ ሲያጥረው ሌላው ካለው እንዲገዛ በማስቻሉ፣ ለገቢ ምርቶች (እንደ መድኃኒትና ነዳጅ) የሚፈለገው የውጭ ምንዛሬ ፍሰት እንዲቀላጠፍ ይረዳል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የፋይናንስ ታሪክ የሚቀይር "የባንክ ለባንክ የውጭ ምንዛሬ ግብይት" በዘመናዊ የቴክኖሎጂ ሥርዓት (Automated Trading Platform) መጀመሩን በይፋ አበሰረ።
ይህ አሠራር ባንኮች ያላቸውን ትርፍ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ላለባቸው ባንኮች በገበያ ዋጋ የሚሸጡበት ግልጽ መድረክ ነው።
🌍 የሌሎች ሀገራት ተሞክሮ ምን ያስተምረናል?
ኢትዮጵያ አሁን የጀመረችው ይህ ሥርዓት በዓለም አቀፍ ደረጃ ስኬታማ በሆኑ ሀገራት የተሞከረና ውጤታማነቱ የተረጋገጠ ነው።
ቬትናም : እ.ኤ.አ በ1990ዎቹ መጀመሪያ ላይ ተመሳሳይ የኢንተርባንክ (Interbank) ገበያ በመጀመሯ፣ በሀገሪቱ የነበረውን ጥቁር ገበያ በእጅጉ መቀነስ ችላለች። ይህም የውጭ ኢንቨስተሮች በሀገሪቱ የፋይናንስ ሥርዓት ላይ እምነት እንዲኖራቸው አድርጓል።
ግብፅ : እ.ኤ.አ በ2016 የውጭ ምንዛሬ ተመንን ለገበያ ክፍት ካደረገች በኋላ፣ የባንክ ለባንክ ግብይቱን በማጠናከሯ በባንኮች ውስጥ ያለውን የውጭ ምንዛሬ ፈሳሽነት (Liquidity) በከፍተኛ ደረጃ ማሳደግ ችላለች።
ናይጄሪያ : ምንም እንኳን ተግዳሮቶች ቢገጥሟትም፣ የዲጂታል ግብይት ሥርዓቱን በማዘመኗ የውጭ ምንዛሬ ተመን ግልጽ በሆነ መንገድ በየቀኑ እንዲታወቅና ግምታዊ ግብይት (Speculation) እንዲቀንስ ረድቷታል።
💎 የአዲሱ ሥርዓት ልዩ ባህሪያት
"ሪል ታይም" ግብይት፦ በኢትዮጵያ ሰኩሪቲስ ኤክስቼንጅ (ESX) በኩል የሚመራው ይሄው መድረክ፣ ባንኮች በሰከንዶች ውስጥ የዋጋ ማቅረቢያና ሽያጭ እንዲያከናውኑ ያስችላቸዋል።
የመረጃ እኩልነት፦ ቀደም ሲል የነበረውን "መረጃ ያለው ብቻ ያተርፋል" የሚለውን አሠራር በማስቀረት፣ ሁሉም ባንኮች የገበያውን እንቅስቃሴ በእኩልነት እንዲያዩ ያደርጋል።
ጥብቅ ቁጥጥር፦ ብሔራዊ ባንክ በዳሽቦርዱ በኩል እያንዳንዱን ግብይት በቀጥታ ይከታተላል፤ ይህም ሕገ-ወጥ አሠራሮችንና የዋጋ መዛባትን ይከላከላል።
🎤 የባንኩ ገዥ ዶ/ር እዮብ ተካልኝ ምን አሉ?
"ዛሬ የተጀመረው የቴክኖሎጂ ሥርዓት የፋይናንስ ዘርፋችንን ለማዘመን የወሰድነው ትልቁ እርምጃ ነው። ይህም ግልጽነትን በማስፈን፣ ትክክለኛ የገበያ ዋጋ እንዲወጣ በማድረግ እና ለጠቅላላው ኢኮኖሚ መረጋጋት የጀርባ አጥንት ይሆናል።"
📌 ለምን ይጠቅመናል?
ይህ ሥርዓት ተግባራዊ መሆኑ የውጭ ምንዛሬ በአንድ ባንክ ብቻ ታጥሮ እንዳይቀር ያደርጋል። አንድ ባንክ ምንዛሬ ሲያጥረው ሌላው ካለው እንዲገዛ በማስቻሉ፣ ለገቢ ምርቶች (እንደ መድኃኒትና ነዳጅ) የሚፈለገው የውጭ ምንዛሬ ፍሰት እንዲቀላጠፍ ይረዳል።
10 months ago
የሀበሻ ቢራ ዋና ባለድርሻ ከአገር ውስጥ ባለአክሲዮኖች ድርሻቸውን በ5,900 ብር ለመግዛት ጥያቄ አቀረበ
የሀበሻ ቢራ ዋና ባለድርሻ የሆነው ባቫሪያ ኦቨርሲዝ ቢሩስ ቢ.ቪ. (BOB) የተባለ የውጭ ኩባንያ፣ ከአገር ውስጥ ባለአክሲዮኖች አክሲዮኖችን በአንድ (1 ሺህ ብር) አክሲዮን 5,900 ብር ለመግዛት ጥያቄ አቀረበ።ይህ ጥያቄ በኩባንያው የኢትዮጵያ ሰነድ መዋዕለ ንዋዮች ገበያ (ESX) ምዝገባ ዙሪያ ውዝግብ በነበረበት ወቅት ይፋ መሆኑን ካፒታል ለመረዳት ችሏል።
አብዛኛውን ድርሻ የያዘው ባቫሪያ ኦቨርሲስ ቢራ ፋብሪካ (BOB) ከአገር ውስጥ ባለአክሲዮኖች ለመግዛት ያቀረበው ይህ ዋጋ፣ ቀደም ሲል በዴሎይት ከተገመተው ዋጋ በ 34% ብልጫ አለው። የኩባንያው መረጃ እንደሚያሳየው፣ የሽያጩ ጊዜ እስከ ነሐሴ 31 ቀን 2025 ድረስ የተራዘመ ነው።
የኢትዮጵያውያን ባለአክሲዮኖች ግን ቅሬታቸውን በማንሳት፣ አነስተኛ ድርሻ ያላቸው ባለሀብቶች ትርፋቸውን ወደ ካፒታል እንዳይቀይሩ ወይም አክሲዮናቸውን በገበያ ላይ እንዳይሸጡ ሲከለከሉ፣ አብዛኛውን ድርሻ የያዘው ባቫሪያ ግን ድርሻውን እንዲያሳድግ ልዩ ዕድል ተሰጥቶታል የሚል ክስ አቅርበዋል።
ባለአክሲዮኖች ይህ እርምጃ ሕጋዊ መሠረት የለውም እና የአገር ውስጥ ባለሀብቶችን ይጎዳል በማለት እየተከራከሩ ነው።የሀበሻ ቢራ የቦርድ ሰብሳቢ ኢንጂነር መስፍን አቢ ቀደም ሲል በሰጡት ምላሽ፣ ባለአክሲዮኖች የ ESX ምዝገባ እስከሚጠናቀቅበት ህዳር 2018 ዓ.ም. ድረስ እንዲጠብቁ ወይም በጠቅላላ ጉባዔ የጸደቀውን የገንዘብ ትርፍ እንዲቀበሉ ሁለት አማራጮች እንደተሰጣቸው ገልፀዋል።
Via Capital
የሀበሻ ቢራ ዋና ባለድርሻ የሆነው ባቫሪያ ኦቨርሲዝ ቢሩስ ቢ.ቪ. (BOB) የተባለ የውጭ ኩባንያ፣ ከአገር ውስጥ ባለአክሲዮኖች አክሲዮኖችን በአንድ (1 ሺህ ብር) አክሲዮን 5,900 ብር ለመግዛት ጥያቄ አቀረበ።ይህ ጥያቄ በኩባንያው የኢትዮጵያ ሰነድ መዋዕለ ንዋዮች ገበያ (ESX) ምዝገባ ዙሪያ ውዝግብ በነበረበት ወቅት ይፋ መሆኑን ካፒታል ለመረዳት ችሏል።
አብዛኛውን ድርሻ የያዘው ባቫሪያ ኦቨርሲስ ቢራ ፋብሪካ (BOB) ከአገር ውስጥ ባለአክሲዮኖች ለመግዛት ያቀረበው ይህ ዋጋ፣ ቀደም ሲል በዴሎይት ከተገመተው ዋጋ በ 34% ብልጫ አለው። የኩባንያው መረጃ እንደሚያሳየው፣ የሽያጩ ጊዜ እስከ ነሐሴ 31 ቀን 2025 ድረስ የተራዘመ ነው።
የኢትዮጵያውያን ባለአክሲዮኖች ግን ቅሬታቸውን በማንሳት፣ አነስተኛ ድርሻ ያላቸው ባለሀብቶች ትርፋቸውን ወደ ካፒታል እንዳይቀይሩ ወይም አክሲዮናቸውን በገበያ ላይ እንዳይሸጡ ሲከለከሉ፣ አብዛኛውን ድርሻ የያዘው ባቫሪያ ግን ድርሻውን እንዲያሳድግ ልዩ ዕድል ተሰጥቶታል የሚል ክስ አቅርበዋል።
ባለአክሲዮኖች ይህ እርምጃ ሕጋዊ መሠረት የለውም እና የአገር ውስጥ ባለሀብቶችን ይጎዳል በማለት እየተከራከሩ ነው።የሀበሻ ቢራ የቦርድ ሰብሳቢ ኢንጂነር መስፍን አቢ ቀደም ሲል በሰጡት ምላሽ፣ ባለአክሲዮኖች የ ESX ምዝገባ እስከሚጠናቀቅበት ህዳር 2018 ዓ.ም. ድረስ እንዲጠብቁ ወይም በጠቅላላ ጉባዔ የጸደቀውን የገንዘብ ትርፍ እንዲቀበሉ ሁለት አማራጮች እንደተሰጣቸው ገልፀዋል።
Via Capital