3 months ago
አትሌቷ እገዳ ተጣለባት
ኬንያዊቷ ናንሲ ጄላጋት ሜቶ የተከለከለ አቅምን የሚያጎለብት ንጥረ ነገር ተጠቅማ በመገኘቷ ለሁለት ዓመታት ታገደች።
ሰኔ 5 ቀን 2016 ዓ.ም. ናንሲ ጄላጋት ሜቶ በኬንያ ውስጥ ከውድድር ውጭ በተደረገላት የልምምድ ወቅት ምርመራ 'ፉሮሴማይድ' የተባለ የተከለከለ አቅምን የሚያጎለብት ንጥረ ነገር ተገኝቶባታል።
በወቅቱ ዕድሜዋ 38 ዓመት የነበረ ሲሆን፤ እንደ ሌሎች ኤሊት አትሌቶች ሁሉ እሷም በአለም አቀፍ የክትትል ዝርዝር ውስጥ ትገኝ ነበር።
ከሦስት ዓመታት ገደማ በኋላ የአትሌቲክስ ኢንተግሪቲ ዩኒት (AIU) ትናንት በሰጠው መግለጫ የምርመራ ዝርዝር ሂደትን ካብራራ በኋላ ጥፋተኛ ሆና በመገኘቷ የሁለት ዓመት የዕገዳ ቅጣት ሊጥልባት ችሏል።
ምርመራው ከተደረገ ከስድስት ሳምንታት በኋላ ጁን 22 የኬንያ የፀረ-አበረታች ቅመሞች ኤጀንሲ የአትሌቷ ናሙና ተልኮበት ከነበረው በሉዛን ከሚገኘው የዓለም የፀረ-አበረታች ቅመሞች ላቦራቶሪ ውጤቱን ካገኘ በኋላ፤ አትሌቷ የተከለከለ ንጥረ ነገር እንደተገኘባት አሳወቃት።
በመቀጠልም ኃላፊነቱ ወደ አትሌቲክስ ኢንተግሪቲ ዩኒት (AIU) የተዛወረ ሲሆን፤ ተቋሙም ኦገስት 21 የተገኘውን የላቦራቶሪ ውጤት ለሜቶ አሳወቃት። እሷም ውጤቱን ያስተባበለች ሲሆን፤ በደል እንደተፈጸመባትም ተከራክራለች።
በሴፕቴምበር ወር መጨረሻ ላይ ሜቶ "የመጀመሪያው ማሳወቂያ አልደረሰኝም በማለቷ (ምንም እንኳን ማሳወቂያው የተላከው እሷ ራሷ መልዕክት እየላከችበት ባለው የኢሜይል አድራሻ ቢሆንም)፤ AIU ጉዳዩን መልሶ ለኬንያው ADAK መርቶታል። የኬንያ ከፍተኛ ፍርድ ቤትም በጉዳዩ ውስጥ ጣልቃ በመግባቱ ይፋዊ መግለጫው እንዲዘገይ አድርጓል።
እንደ ጋዜጣዊ መግለጫው ከሆነ AIU ለአትሌቷ የቢ (B) ናሙና ምርመራ እንዲደረግላት የመጠየቅና የተገኘውን የላቦራቶሪ ውጤት የሚያረጋግጡ የሰነድ ጥቅሎችን የማግኘት ተጨማሪ ዕድል ሰጥቷታል።
በተጨማሪም አትሌቷ በጉዳዩ ላይ እንዴት መቀጠል እንደምትፈልግ እንድታረጋግጥ፤ የፀረ-አበረታች ቅመሞች ደንብ ጥሰቱንና የቀረበባትን ቅጣት እንድትቀበል፤ ወይም በስፖርት የግልግል ዳኝነት ችሎት ፊት ቀርባ እንድትከራከር ዕድል ተሰጥቷት ነበር።
ማርች 13 ቀን 2026 AIU በአትሌቷ የተፈረመ የደንብ ጥሰቱን አምኖ የመቀበልና ቅጣቱን የመቀበያ ቅጽ ደርሶታል። በዚህም መሰረት የእርሷ እገዳ ከጁላይ 11 ቀን 2024 ጀምሮ ለሁለት ዓመታት የሚቆይ ይሆናል።
አሁን ዕድሜዋ 40 ዓመት የደረሰው ይህች አትሌት በመጪው ክረምት ወደ ውድድር ልትመለስ ትችላለች።
ናንሲ ጄላጋት ሜቶ የ2021 የቫሌንሲያ ማራቶን አሸናፊ እንደነበረች የሚታወስ ነው። በወቅቱ የገባችበት 2:19.31 በርቀቱ የግል ምርጥ ሰዓቷ ሆኖ ተመዝግቦላታል።
ምስጋናው ታደሰ
ኬንያዊቷ ናንሲ ጄላጋት ሜቶ የተከለከለ አቅምን የሚያጎለብት ንጥረ ነገር ተጠቅማ በመገኘቷ ለሁለት ዓመታት ታገደች።
ሰኔ 5 ቀን 2016 ዓ.ም. ናንሲ ጄላጋት ሜቶ በኬንያ ውስጥ ከውድድር ውጭ በተደረገላት የልምምድ ወቅት ምርመራ 'ፉሮሴማይድ' የተባለ የተከለከለ አቅምን የሚያጎለብት ንጥረ ነገር ተገኝቶባታል።
በወቅቱ ዕድሜዋ 38 ዓመት የነበረ ሲሆን፤ እንደ ሌሎች ኤሊት አትሌቶች ሁሉ እሷም በአለም አቀፍ የክትትል ዝርዝር ውስጥ ትገኝ ነበር።
ከሦስት ዓመታት ገደማ በኋላ የአትሌቲክስ ኢንተግሪቲ ዩኒት (AIU) ትናንት በሰጠው መግለጫ የምርመራ ዝርዝር ሂደትን ካብራራ በኋላ ጥፋተኛ ሆና በመገኘቷ የሁለት ዓመት የዕገዳ ቅጣት ሊጥልባት ችሏል።
ምርመራው ከተደረገ ከስድስት ሳምንታት በኋላ ጁን 22 የኬንያ የፀረ-አበረታች ቅመሞች ኤጀንሲ የአትሌቷ ናሙና ተልኮበት ከነበረው በሉዛን ከሚገኘው የዓለም የፀረ-አበረታች ቅመሞች ላቦራቶሪ ውጤቱን ካገኘ በኋላ፤ አትሌቷ የተከለከለ ንጥረ ነገር እንደተገኘባት አሳወቃት።
በመቀጠልም ኃላፊነቱ ወደ አትሌቲክስ ኢንተግሪቲ ዩኒት (AIU) የተዛወረ ሲሆን፤ ተቋሙም ኦገስት 21 የተገኘውን የላቦራቶሪ ውጤት ለሜቶ አሳወቃት። እሷም ውጤቱን ያስተባበለች ሲሆን፤ በደል እንደተፈጸመባትም ተከራክራለች።
በሴፕቴምበር ወር መጨረሻ ላይ ሜቶ "የመጀመሪያው ማሳወቂያ አልደረሰኝም በማለቷ (ምንም እንኳን ማሳወቂያው የተላከው እሷ ራሷ መልዕክት እየላከችበት ባለው የኢሜይል አድራሻ ቢሆንም)፤ AIU ጉዳዩን መልሶ ለኬንያው ADAK መርቶታል። የኬንያ ከፍተኛ ፍርድ ቤትም በጉዳዩ ውስጥ ጣልቃ በመግባቱ ይፋዊ መግለጫው እንዲዘገይ አድርጓል።
እንደ ጋዜጣዊ መግለጫው ከሆነ AIU ለአትሌቷ የቢ (B) ናሙና ምርመራ እንዲደረግላት የመጠየቅና የተገኘውን የላቦራቶሪ ውጤት የሚያረጋግጡ የሰነድ ጥቅሎችን የማግኘት ተጨማሪ ዕድል ሰጥቷታል።
በተጨማሪም አትሌቷ በጉዳዩ ላይ እንዴት መቀጠል እንደምትፈልግ እንድታረጋግጥ፤ የፀረ-አበረታች ቅመሞች ደንብ ጥሰቱንና የቀረበባትን ቅጣት እንድትቀበል፤ ወይም በስፖርት የግልግል ዳኝነት ችሎት ፊት ቀርባ እንድትከራከር ዕድል ተሰጥቷት ነበር።
ማርች 13 ቀን 2026 AIU በአትሌቷ የተፈረመ የደንብ ጥሰቱን አምኖ የመቀበልና ቅጣቱን የመቀበያ ቅጽ ደርሶታል። በዚህም መሰረት የእርሷ እገዳ ከጁላይ 11 ቀን 2024 ጀምሮ ለሁለት ዓመታት የሚቆይ ይሆናል።
አሁን ዕድሜዋ 40 ዓመት የደረሰው ይህች አትሌት በመጪው ክረምት ወደ ውድድር ልትመለስ ትችላለች።
ናንሲ ጄላጋት ሜቶ የ2021 የቫሌንሲያ ማራቶን አሸናፊ እንደነበረች የሚታወስ ነው። በወቅቱ የገባችበት 2:19.31 በርቀቱ የግል ምርጥ ሰዓቷ ሆኖ ተመዝግቦላታል።
ምስጋናው ታደሰ
3 months ago
የቫሌንሲያ ማራቶን አሸናፊዋ ናንሲ ጄላጋት ሜቶ በዶፒንግ ታገደች
#ethiopia | የቀድሞዋ የቫሌንሲያ ማራቶን አሸናፊ ኬንያዊቷ ናንሲ ጄላጋት ሜቶ፣ የተከለከለ አበረታች ንጥረ ነገር (Doping) ተጠቅማ በመገኘቷ የሁለት ዓመት የእገዳ ቅጣት ተጣለባት።
የቅጣቱ ዝርዝር ሁኔታ፦
* የተገኘው ንጥረ ነገር፦ ‘ፉሮሴማይድ’ (Furosemide) የተባለ የአቅም ማጎልበቻ።
* ምርመራው የተደረገበት ወቅት፦ ሰኔ 2016 ዓ.ም. በኬንያ በነበረ የልምምድ ወቅት።
* የእገዳው ጊዜ፦ ከጁላይ 11 ቀን 2024 ጀምሮ ለሁለት ዓመታት የሚቆይ ይሆናል።
ከውጤቱ በስተጀርባ፦
አትሌቷ መጀመሪያ ላይ ጥፋተኛ አይደለሁም ብላ ብትከራከርም፣ የአትሌቲክስ ኢንተግሪቲ ዩኒት (AIU) ባቀረበው ዝርዝር ማስረጃና የላቦራቶሪ ውጤት መሠረት፣ በመጨረሻም ማርች 13 ቀን 2026 ጥፋቷን አምና የቅጣት ቅጹን ፈርማለች።
የ40 ዓመቷ አትሌት ናንሲ ጄላጋት፣ በ2021 የቫሌንሲያ ማራቶንን በ2:19.31 በሆነ የግል ምርጥ ሰዓቷ አሸንፋ እንደነበር ይታወሳል። አትሌቷ ቅጣቷን ጨርሳ በመጪው ክረምት ወደ ውድድር እንደምትመለስ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #nancyjelagat #athleticsnews #dopingban #kenyaathletics #aiu #breakingnews #sportsupdate #marathon #valenciamarathon
#ethiopia | የቀድሞዋ የቫሌንሲያ ማራቶን አሸናፊ ኬንያዊቷ ናንሲ ጄላጋት ሜቶ፣ የተከለከለ አበረታች ንጥረ ነገር (Doping) ተጠቅማ በመገኘቷ የሁለት ዓመት የእገዳ ቅጣት ተጣለባት።
የቅጣቱ ዝርዝር ሁኔታ፦
* የተገኘው ንጥረ ነገር፦ ‘ፉሮሴማይድ’ (Furosemide) የተባለ የአቅም ማጎልበቻ።
* ምርመራው የተደረገበት ወቅት፦ ሰኔ 2016 ዓ.ም. በኬንያ በነበረ የልምምድ ወቅት።
* የእገዳው ጊዜ፦ ከጁላይ 11 ቀን 2024 ጀምሮ ለሁለት ዓመታት የሚቆይ ይሆናል።
ከውጤቱ በስተጀርባ፦
አትሌቷ መጀመሪያ ላይ ጥፋተኛ አይደለሁም ብላ ብትከራከርም፣ የአትሌቲክስ ኢንተግሪቲ ዩኒት (AIU) ባቀረበው ዝርዝር ማስረጃና የላቦራቶሪ ውጤት መሠረት፣ በመጨረሻም ማርች 13 ቀን 2026 ጥፋቷን አምና የቅጣት ቅጹን ፈርማለች።
የ40 ዓመቷ አትሌት ናንሲ ጄላጋት፣ በ2021 የቫሌንሲያ ማራቶንን በ2:19.31 በሆነ የግል ምርጥ ሰዓቷ አሸንፋ እንደነበር ይታወሳል። አትሌቷ ቅጣቷን ጨርሳ በመጪው ክረምት ወደ ውድድር እንደምትመለስ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #nancyjelagat #athleticsnews #dopingban #kenyaathletics #aiu #breakingnews #sportsupdate #marathon #valenciamarathon
6 months ago
ለመመዝገብ ፍላጎት ላላችሁ‼️
በተለያዩ የትምህርት መስኮች ተመርቃችሁ ለመምህርነት ሙያ ማመልከት ለምትፈልጉ
ቀደም ሲል በወጣው መመልመያ መስፈርት መሰረት ለመመዝገብ የምትፈልጉ በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሚሰጡ የትምህርት ዓይነቶችና ተዛማጅ የትምህርት መስኮችን በትምህርት ሚኒስቴር ዌብሳይት ላይ በዚህ ሊንክ https://shorturl.at/ORED9 በመግባት “የትምህርት ዓይነትና ተዛማች የትምህርት መስኮች” የሚለውን download በማድረግ ማግኘት የምትችሉ መሆኑን ገልጸን፤ የ5 ዩኒቨርስቲዎችን የመመዝገቢያ ሊንኮች ማሳወቃችን ይታወሳል፤
ከተገለጹት 5 ዩኒቨርስቲዎች በተጨማሪ በመቀሌ ዩኒቨርስቲ መመዝገብ የሚቻል ሲሆን ለመመዝገብ የምትፈልጉ አመልካቾች በዚህ ሊንክ https://docs.google.com/fo... በመግባት መመዝገብ ትችላላችሁ።
seledadotio
seledadotio
በተለያዩ የትምህርት መስኮች ተመርቃችሁ ለመምህርነት ሙያ ማመልከት ለምትፈልጉ
ቀደም ሲል በወጣው መመልመያ መስፈርት መሰረት ለመመዝገብ የምትፈልጉ በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሚሰጡ የትምህርት ዓይነቶችና ተዛማጅ የትምህርት መስኮችን በትምህርት ሚኒስቴር ዌብሳይት ላይ በዚህ ሊንክ https://shorturl.at/ORED9 በመግባት “የትምህርት ዓይነትና ተዛማች የትምህርት መስኮች” የሚለውን download በማድረግ ማግኘት የምትችሉ መሆኑን ገልጸን፤ የ5 ዩኒቨርስቲዎችን የመመዝገቢያ ሊንኮች ማሳወቃችን ይታወሳል፤
ከተገለጹት 5 ዩኒቨርስቲዎች በተጨማሪ በመቀሌ ዩኒቨርስቲ መመዝገብ የሚቻል ሲሆን ለመመዝገብ የምትፈልጉ አመልካቾች በዚህ ሊንክ https://docs.google.com/fo... በመግባት መመዝገብ ትችላላችሁ።
seledadotio
seledadotio
8 months ago
የአትሌቷ ቅጣትና የሪከርዱ ጉዳይ እንዴት ይሆናል?
(ምስጋናው ታደሰ)
#ethiopia | Hydrochlorothiazide (ሀይድሮክሎራይዝድ) HCTZ የተባለ የተከለከለ አበረታች ንጥረ ነገር መጠቀሟ የተረጋገጠባት ኬንያዊቷ የሴቶች ማራቶን የዓለም ሪከርድ ባለቤት ሩት ቼፕንጌቲች የሶስት ዓመታት እገዳ እንደተጣለባት The Athletics Integrity Unit (AIU) ዛሬ (ሐሙስ) ባወጣው መግለጫ ማስታወቁን ገልጬ ፅፌያለሁ።
ይህንን ተከትሎም የሪከርዱ ጉዳይ እንዴት ይሆናል? ለቀድሞዋ የሪከርዱ ባለቤት ትዕግስት አሰፋ ይመለሳል ወይ? የሚሉ ጥያቄዎች እየተነሱ ይገኛሉ።
እናስ?
እናማ ሪከርዱ ወደ ትዕግስት አይመለስም፤ ከሩት ቼፕንጌቲች ጋር ይቆያል።
እንዴት ይህ ሊሆን ቻለ?
የ31 ዓመቷ ኬንያዊት "ሀይድሮክሎራይዝድ" የተባለውን የተከለከለ ንጥረ ነገር መውሰዷ የተረጋገጠባት ማርች 14/2025 በተደረገላት የደምና የሽንት ምርመራ ነው። በመሆኑም ከዛን ጊዜ አንስቶ ጊዜያዊ እገዳ ተጥሎባት የቆየ ሲሆን በዛሬው ዕለት ደግሞ የሶስት ዓመት እገዳ ተጥሎባታል።
የAIU ዋና ስራ አስፈፃሚ የሆኑት ብሬት ክሎዚዬ ጉዳዩን አስመልክተው በሰጡት አስተያየት እገዳው የሚፀናባት ምርመራው ከተደረገላት ከማርች 2025 ወዲህ መሆኑንና ከዛ በፊት የነበሩት ውጤቶቿ የዓለም ሪከርድን ጨምሮ በእጇ እንደሚቆዩ ማረጋገጫ ሰጥተዋል። ስለዚህ ሪከርዱ ወደ ትዕግስት አሰፋ አይመለስም።
ይሁንና ይሄ እስከ መጨረሻው የሚፀና ውሳኔ ላይሆን ይችላል። ምክንያቱም ይሄኛው ውጤት ይፋ ከሆነ በኋላ AIU ወደኋላ ተመልሶ በአትሌቷ ላይ ተጨማሪ ምርመራዎችን ጀምሯል።
ለምሳሌ በምርመራው ወቅት ቃለ-ምልልስ ሲደረግላት "ባመመኝ ሰዓት ይሄንን ሀይድሮክሎራይዝድ ጨምሮ ሌሎችንም የባህል መድሃኒቶችን የምትሰጠኝ የቤት ሰራተኛዬ ናት" የሚል ቃል ሰጥታለች። በዚህም ሰራተኛዋም ምርመራ እየተደረገባት ነው።
ቼፕንጌቲች "Rosa Associati" በተባለው የአትሌቲክስ ማኔጅመንት ስር ነው የምትወዳደረው። የዚህ ኩባንያ ባለቤት ጣልያናዊው ፌዴሪኮ ሮሳ (በ2ኛው ፎቶ የሚታየው) ነው።
ይህ ሰው ከ30 በላይ ስመጥር ኬንያውያን አትሌቶችን በስሩ የሚያስተዳድር ሲሆን ከዶፒንግ ጋር በተያያዘ ለቅጣት ከሚዳረጉት በርካታ የሀገሪቱ አትሌቶች መካከልም አብዛኛዎቹ በእሱ ስር የሚወዳደሩ ናቸው። የኬንያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከኦገስት 2025 አንስቶ እገዳ ጥሎበታል። ይህንን ተከትሎም እሱም በAIU ምርመራ እየተደረገበት ነው።
ይህም ብቻ ሳይሆን የቼፕንጌቲች የሞባይል ስልክ ላይም ምርመራ እየተደረገ ነው። አትሌቷ መጀመሪያ ላይ ሞባይሏን ላለማስፈተሽ አንገራግራ የነበረ ቢሆንም በኋላ ላይ ግን ተስማምታለች። ከፌዴሪኮ ሮሳ ጋር የተፃፃፈቻቸው መልዕክቶች እና የመድሃኒት ፎቶዎች እየተመረመሩ ነው።
የእነዚህ ምርመራ ገና በሂደት ላይ ነው። ወደ ኋላ ተሂዶ እየተደረገ ባለው ምርመራና የመጨረሻ ውጤት ከዚህ በፊትም ዶፒንግ ትወስድ እንደነበር ከተረጋገጠባት ሪከርዱን ልትነጠቅና ለትዕግስት አሰፋ ሊመለስላት ይችላል።
(ምስጋናው ታደሰ)
#ethiopia | Hydrochlorothiazide (ሀይድሮክሎራይዝድ) HCTZ የተባለ የተከለከለ አበረታች ንጥረ ነገር መጠቀሟ የተረጋገጠባት ኬንያዊቷ የሴቶች ማራቶን የዓለም ሪከርድ ባለቤት ሩት ቼፕንጌቲች የሶስት ዓመታት እገዳ እንደተጣለባት The Athletics Integrity Unit (AIU) ዛሬ (ሐሙስ) ባወጣው መግለጫ ማስታወቁን ገልጬ ፅፌያለሁ።
ይህንን ተከትሎም የሪከርዱ ጉዳይ እንዴት ይሆናል? ለቀድሞዋ የሪከርዱ ባለቤት ትዕግስት አሰፋ ይመለሳል ወይ? የሚሉ ጥያቄዎች እየተነሱ ይገኛሉ።
እናስ?
እናማ ሪከርዱ ወደ ትዕግስት አይመለስም፤ ከሩት ቼፕንጌቲች ጋር ይቆያል።
እንዴት ይህ ሊሆን ቻለ?
የ31 ዓመቷ ኬንያዊት "ሀይድሮክሎራይዝድ" የተባለውን የተከለከለ ንጥረ ነገር መውሰዷ የተረጋገጠባት ማርች 14/2025 በተደረገላት የደምና የሽንት ምርመራ ነው። በመሆኑም ከዛን ጊዜ አንስቶ ጊዜያዊ እገዳ ተጥሎባት የቆየ ሲሆን በዛሬው ዕለት ደግሞ የሶስት ዓመት እገዳ ተጥሎባታል።
የAIU ዋና ስራ አስፈፃሚ የሆኑት ብሬት ክሎዚዬ ጉዳዩን አስመልክተው በሰጡት አስተያየት እገዳው የሚፀናባት ምርመራው ከተደረገላት ከማርች 2025 ወዲህ መሆኑንና ከዛ በፊት የነበሩት ውጤቶቿ የዓለም ሪከርድን ጨምሮ በእጇ እንደሚቆዩ ማረጋገጫ ሰጥተዋል። ስለዚህ ሪከርዱ ወደ ትዕግስት አሰፋ አይመለስም።
ይሁንና ይሄ እስከ መጨረሻው የሚፀና ውሳኔ ላይሆን ይችላል። ምክንያቱም ይሄኛው ውጤት ይፋ ከሆነ በኋላ AIU ወደኋላ ተመልሶ በአትሌቷ ላይ ተጨማሪ ምርመራዎችን ጀምሯል።
ለምሳሌ በምርመራው ወቅት ቃለ-ምልልስ ሲደረግላት "ባመመኝ ሰዓት ይሄንን ሀይድሮክሎራይዝድ ጨምሮ ሌሎችንም የባህል መድሃኒቶችን የምትሰጠኝ የቤት ሰራተኛዬ ናት" የሚል ቃል ሰጥታለች። በዚህም ሰራተኛዋም ምርመራ እየተደረገባት ነው።
ቼፕንጌቲች "Rosa Associati" በተባለው የአትሌቲክስ ማኔጅመንት ስር ነው የምትወዳደረው። የዚህ ኩባንያ ባለቤት ጣልያናዊው ፌዴሪኮ ሮሳ (በ2ኛው ፎቶ የሚታየው) ነው።
ይህ ሰው ከ30 በላይ ስመጥር ኬንያውያን አትሌቶችን በስሩ የሚያስተዳድር ሲሆን ከዶፒንግ ጋር በተያያዘ ለቅጣት ከሚዳረጉት በርካታ የሀገሪቱ አትሌቶች መካከልም አብዛኛዎቹ በእሱ ስር የሚወዳደሩ ናቸው። የኬንያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ከኦገስት 2025 አንስቶ እገዳ ጥሎበታል። ይህንን ተከትሎም እሱም በAIU ምርመራ እየተደረገበት ነው።
ይህም ብቻ ሳይሆን የቼፕንጌቲች የሞባይል ስልክ ላይም ምርመራ እየተደረገ ነው። አትሌቷ መጀመሪያ ላይ ሞባይሏን ላለማስፈተሽ አንገራግራ የነበረ ቢሆንም በኋላ ላይ ግን ተስማምታለች። ከፌዴሪኮ ሮሳ ጋር የተፃፃፈቻቸው መልዕክቶች እና የመድሃኒት ፎቶዎች እየተመረመሩ ነው።
የእነዚህ ምርመራ ገና በሂደት ላይ ነው። ወደ ኋላ ተሂዶ እየተደረገ ባለው ምርመራና የመጨረሻ ውጤት ከዚህ በፊትም ዶፒንግ ትወስድ እንደነበር ከተረጋገጠባት ሪከርዱን ልትነጠቅና ለትዕግስት አሰፋ ሊመለስላት ይችላል።
Sponsored by
Surafel
9 months ago
የኢትዮጵያ ፀረ-አበረታች ቅመሞች ባለስልጣን በድርቤ ወልተጂ ዙሪያ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ፀረ-አበረታች ቅመሞች ባለስልጣን በህግ በተሰጠው ስልጣንና ኃላፊነት መሰረት በስፖርት ውድድር ወቅትና ከውድድር ጊዜ ውጭ የአበረታች ቅመሞች ወይም ዶፒንግ ምርመራ የሚያካሂድ መሆኑ ይታወቃል።
በዚህም መሰረት የምርመራ እቅድ(TDP) በማዘጋጀት እ.ኤ.አ የካቲት 25/2025 ለአትሌት ድርቤ ወልተጅ ከውድድር ጊዜ ውጭ ምርመራ (Out of Competition Test) ለማካሄድ ሙከራ ያደረገ ሲሆን ሳይሳካ ቀርቷል።
ምርመራውም የተደናቀፈው አትሌቷ ፍቃደኛ ሳትሆን በመቅረቷና በምርመራ ባለሞያዎች (Sample Collection Personnel) ላይ ጫና በመደረጉ ምክንያት እንደሆነ መገንዘብ ተችሏል።
ይህንንም መሰረት በማድረግ ጉዳዩን በጥልቀት በማጣራት ነፃና ገለልተኛ በሆነ የዳኝነት አካል (Hearing Panel) እንዲታይ የተደረገ ሲሆን ባለስልጣን መ/ቤቱ ያለውን መረጃና ማስረጃ በማቅረብ በአትሌቷ ላይ አግባብነት ያለው ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ ተከራክሯል፡፡
ይሁን እንጅ የዳኝነት አካሉ ግራ ቀኙን ማለትም አትሌቷንና የኢትዮጵያ ፀረ-አበረታች ቅመሞች ባለስልጣንን በማከራከር በህግ አግባብ ትክክል ነው ብሎ ያመነበትን ውሳኔ ወስኗል፡፡
ባለስልጣን መ/ቤቱም እንደ ከሳሽ አካል በውሳኔው ደስተኛ ባይሆንም በአለም አቀፉ ህግ መሰረት ውሳኔውን በመቀበል ለአትሌቷ እንዲሁም ለአለም አቀፍ ተቋማት አሳውቋል፡፡
ከዚህም በመነሳት የአለም አትሌቲክስ የኢንተግሪቲ ዩኒት (AIU) ጉዳዩን በተለይም የቀረቡትን ሰነዶችና ሌሎችንም መረጃዎች በመመርመር ለአለም አቀፉ የስፖርት ግልግል ፍ/ቤት (CAS) ይግባኝ አቅርቧል፡፡
ከዚህም ጋር ተያይዞ የኢትዮጵያ ፀረ-አበረታች ቅመሞች ባለስልጣን በማንኛውም ደረጃ በሚፈፀሙ የፀረ-አበረታች ቅመሞች የህግ ጥሰት ላይ አስተማሪ የሆነ እርምጃ እንዲወሰድ ለማስቻል በትኩረት የሚሰራ መሆኑን እየገለፅን በአትሌት ድርቤ ወልተጅ ጉዳይ ላይም አግባብነት ያለው ፍትኃዊ ውሳኔ እንዲወሰን አስፈላጊውን ድጋፍና ያላሳለሰ ጥረት ሁሉ የሚያደርግ መሆኑን ያረጋግጣል ያለው ኤ ኤም ኤን ነው፡፡
#ethiopia | የኢትዮጵያ ፀረ-አበረታች ቅመሞች ባለስልጣን በህግ በተሰጠው ስልጣንና ኃላፊነት መሰረት በስፖርት ውድድር ወቅትና ከውድድር ጊዜ ውጭ የአበረታች ቅመሞች ወይም ዶፒንግ ምርመራ የሚያካሂድ መሆኑ ይታወቃል።
በዚህም መሰረት የምርመራ እቅድ(TDP) በማዘጋጀት እ.ኤ.አ የካቲት 25/2025 ለአትሌት ድርቤ ወልተጅ ከውድድር ጊዜ ውጭ ምርመራ (Out of Competition Test) ለማካሄድ ሙከራ ያደረገ ሲሆን ሳይሳካ ቀርቷል።
ምርመራውም የተደናቀፈው አትሌቷ ፍቃደኛ ሳትሆን በመቅረቷና በምርመራ ባለሞያዎች (Sample Collection Personnel) ላይ ጫና በመደረጉ ምክንያት እንደሆነ መገንዘብ ተችሏል።
ይህንንም መሰረት በማድረግ ጉዳዩን በጥልቀት በማጣራት ነፃና ገለልተኛ በሆነ የዳኝነት አካል (Hearing Panel) እንዲታይ የተደረገ ሲሆን ባለስልጣን መ/ቤቱ ያለውን መረጃና ማስረጃ በማቅረብ በአትሌቷ ላይ አግባብነት ያለው ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ ተከራክሯል፡፡
ይሁን እንጅ የዳኝነት አካሉ ግራ ቀኙን ማለትም አትሌቷንና የኢትዮጵያ ፀረ-አበረታች ቅመሞች ባለስልጣንን በማከራከር በህግ አግባብ ትክክል ነው ብሎ ያመነበትን ውሳኔ ወስኗል፡፡
ባለስልጣን መ/ቤቱም እንደ ከሳሽ አካል በውሳኔው ደስተኛ ባይሆንም በአለም አቀፉ ህግ መሰረት ውሳኔውን በመቀበል ለአትሌቷ እንዲሁም ለአለም አቀፍ ተቋማት አሳውቋል፡፡
ከዚህም በመነሳት የአለም አትሌቲክስ የኢንተግሪቲ ዩኒት (AIU) ጉዳዩን በተለይም የቀረቡትን ሰነዶችና ሌሎችንም መረጃዎች በመመርመር ለአለም አቀፉ የስፖርት ግልግል ፍ/ቤት (CAS) ይግባኝ አቅርቧል፡፡
ከዚህም ጋር ተያይዞ የኢትዮጵያ ፀረ-አበረታች ቅመሞች ባለስልጣን በማንኛውም ደረጃ በሚፈፀሙ የፀረ-አበረታች ቅመሞች የህግ ጥሰት ላይ አስተማሪ የሆነ እርምጃ እንዲወሰድ ለማስቻል በትኩረት የሚሰራ መሆኑን እየገለፅን በአትሌት ድርቤ ወልተጅ ጉዳይ ላይም አግባብነት ያለው ፍትኃዊ ውሳኔ እንዲወሰን አስፈላጊውን ድጋፍና ያላሳለሰ ጥረት ሁሉ የሚያደርግ መሆኑን ያረጋግጣል ያለው ኤ ኤም ኤን ነው፡፡
9 months ago
አትሌት ድርቤ ወልተጂ ከውድድሩ ውጪ ሆነች
ኢትዮጵያን በአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ውድድር በ 1500ሜ ለመወከል ተመርጣ የነበረችው አትሌት ድርቤ ወልተጂ ከውድድሩ ውጪ መሆኗ ተገልጿል።
አትትሌቷ ከውድድሩ ውጪ የሆነችው ሊደረግላት የነበረውን የአበረታች ንጥረነገር ምርመራ ለማድረግ ፈቃደኛ ባለመሆኗ መሆኑ ተነግሯል።
አትሌቶች አበረታች ዕፅ መጠቀም አለመጠቀማቸውን የሚቆጣጠረው "The Athletics Integrity Unit (AIU)" የዶፒንግ ምርመራ እንድትሰጥ ቢጠይቃትም ፈቃደኛ አለመሆኗ ተገልጿል።
ይህንንም ተከትሎ " AIU " አትሌቷ ከቶኪዮው የዓለም ሻምፒዮና ውጪ እንድትሆን ለዓለም አቀፉ የስፖርት ጉዳዮች ግልግል ችሎት (Court of Arbitration for Sport (CAS) ክስ አቅርቧል።
የክሱ ውሳኔው በዓለም አቀፉ የስፖርት ጉዳዮች ግልግል ችሎት የታወቀ ሲሆን አትሌት ድርቤ ወልተጂ ከውድድሩ ውጪ መሆኗ ታውቋል።
በርቀቱ ሁለተኛ ምርጥ ሰዓት ባለቤት የሆነችው አትሌቷ ለኢትዮጵያ ሜዳልያ ያስገኛሉ ተብለው ከሚጠበቁ አትሌቶች አንዷ ነበረች።
ምንጭ :- ጋዜጠኛ ብሩክ ተስፋዬ
ኢትዮጵያን በአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ውድድር በ 1500ሜ ለመወከል ተመርጣ የነበረችው አትሌት ድርቤ ወልተጂ ከውድድሩ ውጪ መሆኗ ተገልጿል።
አትትሌቷ ከውድድሩ ውጪ የሆነችው ሊደረግላት የነበረውን የአበረታች ንጥረነገር ምርመራ ለማድረግ ፈቃደኛ ባለመሆኗ መሆኑ ተነግሯል።
አትሌቶች አበረታች ዕፅ መጠቀም አለመጠቀማቸውን የሚቆጣጠረው "The Athletics Integrity Unit (AIU)" የዶፒንግ ምርመራ እንድትሰጥ ቢጠይቃትም ፈቃደኛ አለመሆኗ ተገልጿል።
ይህንንም ተከትሎ " AIU " አትሌቷ ከቶኪዮው የዓለም ሻምፒዮና ውጪ እንድትሆን ለዓለም አቀፉ የስፖርት ጉዳዮች ግልግል ችሎት (Court of Arbitration for Sport (CAS) ክስ አቅርቧል።
የክሱ ውሳኔው በዓለም አቀፉ የስፖርት ጉዳዮች ግልግል ችሎት የታወቀ ሲሆን አትሌት ድርቤ ወልተጂ ከውድድሩ ውጪ መሆኗ ታውቋል።
በርቀቱ ሁለተኛ ምርጥ ሰዓት ባለቤት የሆነችው አትሌቷ ለኢትዮጵያ ሜዳልያ ያስገኛሉ ተብለው ከሚጠበቁ አትሌቶች አንዷ ነበረች።
ምንጭ :- ጋዜጠኛ ብሩክ ተስፋዬ
Comments