3 months ago
የአንድ ወጣት መታሰቢያ ለብዙዎች ተስፋ ሆነ
📌የኢዮብ ተስፋ ድርጅት የ27 ሚሊዮን ብር የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ
#ethiopia | በድንገተኛ የልብ ሕመም ሕይወቱ ያለፈውን ወጣት ኢዮብ አበባውን ለመዘከር የተቋቋመው “ኢዮብ ተስፋ ለሕጻናትና ለወጣቶች በጎ አድራጎት ድርጅት”፣ በኢትዮጵያ የልብ ሕመም ላለባቸው ሕፃናትና ወጣቶች የሚውሉ የ180 ሺህ ዶላር (ከ27.5 ሚሊዮን ብር በላይ) ግምት ያላቸው የሕክምና ቁሳቁሶችን ለሦስት የጤና ተቋማት አስረከበ።
ድርጅቱ ያሰባሰባቸውን ነፍስ አድን ቁሳቁሶች ለሚከተሉት ተቋማት በስጦታ አበርክቷል፦
-ለጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል
-ለቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም የሕክምና ኮሌጅ
-ለኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕፃናት መርጃ ማዕከል
የድርጅቱ መሥራችና የኢዮብ አባት የሆኑት አቶ አበባው አንበሳው እንደገለጹት፣ ቁሳቁሶቹ የተገኙት ከድርጅቱ ደጋፊዎችና ከታዋቂው የሜድትሮኒክ (Medtronic) ኩባንያ ጋር በተደረገ ትብብር ነው። ድርጅቱ ከተመሠረተባቸው አራት ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ የልብ ሕክምና ዘርፍ ላይ በርትቶ እየሠራ የሚገኝ ሲሆን፣ እስካሁን በልብ ሕሙማን ሕፃናት መርጃ ማዕከል ብቻ የ100 ሕፃናትን ሕክምና በቀጥታ መደገፍ ችሏል።
አቶ አንበሳው "የልጃችንን ሕይወት በድንገት ብናጣም፣ የእሱን ስም ይዘን በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ሕፃናትን ልብ ለመጠገንና ተስፋ ለመስጠት እየሠራን እንገኛለን"ብለዋል።
የሆስፒታሎቹ ኃላፊዎች ድጋፉ ለታካሚዎች የሚሰጠውን አገልግሎት በእጅጉ እንደሚያሳልጥ ገልጸው፣ ለድርጅቱ ላቅ ያለ ምስጋና አቅርበዋል።
ድርጅቱ በቀጣይም መሰል ድጋፎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቆ፣ በየትኛውም የዓለም ክፍል የሚገኙ ግለሰቦችና ተቋማት ለዚህ በጎ ተግባር እጃቸውን እንዲዘረጉ ጥሪውን አስተላልፏል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#ኢዮብተስፋ #የልብሕክምና #በጎአድራጎት #ኢትዮጵያ #eyobtesfa #hearthealthethiopia #charity
📌የኢዮብ ተስፋ ድርጅት የ27 ሚሊዮን ብር የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ
#ethiopia | በድንገተኛ የልብ ሕመም ሕይወቱ ያለፈውን ወጣት ኢዮብ አበባውን ለመዘከር የተቋቋመው “ኢዮብ ተስፋ ለሕጻናትና ለወጣቶች በጎ አድራጎት ድርጅት”፣ በኢትዮጵያ የልብ ሕመም ላለባቸው ሕፃናትና ወጣቶች የሚውሉ የ180 ሺህ ዶላር (ከ27.5 ሚሊዮን ብር በላይ) ግምት ያላቸው የሕክምና ቁሳቁሶችን ለሦስት የጤና ተቋማት አስረከበ።
ድርጅቱ ያሰባሰባቸውን ነፍስ አድን ቁሳቁሶች ለሚከተሉት ተቋማት በስጦታ አበርክቷል፦
-ለጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል
-ለቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም የሕክምና ኮሌጅ
-ለኢትዮጵያ የልብ ሕሙማን ሕፃናት መርጃ ማዕከል
የድርጅቱ መሥራችና የኢዮብ አባት የሆኑት አቶ አበባው አንበሳው እንደገለጹት፣ ቁሳቁሶቹ የተገኙት ከድርጅቱ ደጋፊዎችና ከታዋቂው የሜድትሮኒክ (Medtronic) ኩባንያ ጋር በተደረገ ትብብር ነው። ድርጅቱ ከተመሠረተባቸው አራት ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ የልብ ሕክምና ዘርፍ ላይ በርትቶ እየሠራ የሚገኝ ሲሆን፣ እስካሁን በልብ ሕሙማን ሕፃናት መርጃ ማዕከል ብቻ የ100 ሕፃናትን ሕክምና በቀጥታ መደገፍ ችሏል።
አቶ አንበሳው "የልጃችንን ሕይወት በድንገት ብናጣም፣ የእሱን ስም ይዘን በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ሕፃናትን ልብ ለመጠገንና ተስፋ ለመስጠት እየሠራን እንገኛለን"ብለዋል።
የሆስፒታሎቹ ኃላፊዎች ድጋፉ ለታካሚዎች የሚሰጠውን አገልግሎት በእጅጉ እንደሚያሳልጥ ገልጸው፣ ለድርጅቱ ላቅ ያለ ምስጋና አቅርበዋል።
ድርጅቱ በቀጣይም መሰል ድጋፎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቆ፣ በየትኛውም የዓለም ክፍል የሚገኙ ግለሰቦችና ተቋማት ለዚህ በጎ ተግባር እጃቸውን እንዲዘረጉ ጥሪውን አስተላልፏል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#ኢዮብተስፋ #የልብሕክምና #በጎአድራጎት #ኢትዮጵያ #eyobtesfa #hearthealthethiopia #charity
3 months ago
ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታልን ጎበኙ
የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ክቡር ታዬ አጽቀሥላሴ በኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታል ተገኝተው በኢትዮጵያዊያንና በውጭ ሀገር ስፔሻሊስቶች እየተከናወነ በሚገኘው የልብ ህሙማን ህፃናት የነፃ ቀዶ ጥገና አገልግሎት ተጠቃሚ የሆኑ ህፃናትን ጎብኝተዋል።
ፕሬዝዳንቱ በጉብኝታቸው ወቅት ሆስፒታሉ እያከናወነ ያለውን ዘመናዊ የሕክምና አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራ አድንቀው በኢትዮጵያ የሕክምና ዘርፉ ወደ አዲስ ምዕራፍ መሸጋገሩን ጠቁመዋል።
ለሕክምናው ቡድን አገልግሎት "Heart to Heart Children’s Aid" የተሰኘው ፋውንዴሽን ካሰባሰበው የእርዳታ ገንዘብ እና Ethio-Istanbul General Hospital ባደረገው ሙሉ የሆስፒታል አገልግሎትና የባለሙያዎች አቅርቦት በሚያደርጉት ድጋፍ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ ሲሆን፣ በፕሮፌሰር ሳሻ የሚመራው የጣሊያኑ የ"ፔድሬ ፓዮ" የሕክምና ቡድንም በሥፍራው ተገኝቶ ከኢትዮ ኢስታንቡል ሆስፒታል ባለሙያዎች ጋር በመዋሀድ እየሰጠ ባለው አገልግሎት በ12 ቀናት ውስጥ ብቻ በአዲስ አበባ 58 በጅግጅጋ 16 በድምሩ የ74 ሕፃናት የልብ ቀዶ ጥገና በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።
የሆስፒታሉ መስራችና ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ብርሃን ተድላ እንደገለጹት፣ ኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታል አሁን የተሰሩትን 74 ህፃናት ሳይጨምር ባለፉት ሁለት ዓመታት ለ114 ሕፃናት በብር 120,000,000.00 (አንድ መቶ ሃያ ሚሊዮን ብር) በሚገመት ወጪ ነፃ ሕክምና ሰጥቷል።
ሆስፒታሉ ከተመሰረተ ሦስት ዓመት ቢሆነውም፣ ከ86 በላይ የሰብስፔሻሊስት ዶክተሮችን በመያዝ ውስብስብ የልብ፣ የካንሰር፣ የደም ስር የጭንቅላት የህብለሰረስና የአጥንት ቀዶ ጥገና ህክምናና በሌሎችም አገልግሎቶች ላይ ሰፊ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል።
አቶ ብርሃን አክለውም፣ ሆስፒታሉን ለማቋቋም ያነሳሳቸው በራሳቸው ላይ የደረሰ የሕክምና እንግልትና ዜጎች ለሕክምና ወደ ውጭ ሀገር ሄደው የሚደርስባቸውን የገንዘብ ወጪና የሞራል ጉዳት ለማስቀረት ካላቸው ራዕይ መሆኑን በመግለፅ አገልግሎቱን ከዚህ በተሻለ በስፋት ለመስጠት እንዲያስችላቸው ላቀረቡት የቦታ ጥያቄ መንግስት ትኩረት እንዲሰጥላቸው አሳስበዋል።
ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በንግግራቸው፣ "ያስተማረንን ሕዝብ ማስታወስ ትልቅ በረከት ነው" በማለት በውጭ ሀገር የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች ወደ ሀገራቸው ተመልሰው እንዲያገለግሉ ጥሪ አቅርበዋል።
እንዲህ ያሉ ለትርፍ ብቻ ታስበው ሳይሆን ለመልካም አገልግሎት የተቋቋሙ የላቁ የሕክምና ተቋማት መኖራቸው ዜጎች ወደ ውጭ በመሄድ ከሚያወጡት ከፍተኛ ወጪና ከሚደርስባቸው እንግልት እንደሚታደጋቸውም ገልጸዋል።
በተያያዘም ክቡር ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀስላሴ ለሕክምና ቡድኑ ባስተላለፉት የምስጋና መልእክት፣ በሕፃናቱና በቤተሰቦቻቸው ላይ የታየውን ደስታ "የተስፋ ብርሃን" በማለት ገልጸውታል። በተለይም የሕክምና ቡድኑ ወደ ጅግጅጋ በመጓዝ አገልግሎት መስጠቱ የሁለቱን ሀገራት (ኢትዮጵያና ጣሊያን) ግንኙነት ይበልጥ እንደሚያጠናክር ጠቁመዋል።
በዕለቱ ምስክርነታቸውን የሰጡ ወላጆች፣ የሕክምናውን ወጪ በመሸፈን ልጆቻቸው ማሳከም ባለመቻላቸው ለዓመታት ሲሰቃዩ መቆየታቸውን ገልፀው አሁን ባገኙት ነፃ የልብ ቀዶ ጥገና ልጆቻቸው ዳግም ሕይወት ማግኘታቸውን በደስታና በምርቃት ገልጸዋል።
ይህ የህፃናት ነፃ የልብ ሕክምና አገልግሎት በቀጣይነት ወደ ኦሮሚያ፣ አማራ፥ ትግራይ፣ ሲዳማ፣ ደቡብና ሌሎችም ክልሎች በመጓዝ ቀሪዎቹን ሕፃናት ለማከም ዕቅድ መያዙን አቶ ብርሃን ተድላ ገልፀው ለዚህ ዘመቻ መሳካት ከፍተኛ አስተዋፅኦና ትብብር ላደረጉት ለጤና ሚኒስቴር፣ ለጉምሩክ ኮሚሽን፣ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ለስካይላይት ሆቴል፣ ለኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ቁጥጥር ባለሥልጣንና ለሌሎችም በዘመቻው ለተሳተፉ የህክምና ተቋማት እንዲሁም የገንዘብ ድጋፍ ላደረጉ በጎ አድራጊዎችና ለፋውንዴሽኑ የቦርድ አባላት ከፍተኛ ምስጋና አቅርበዋል። #ኢትዮኢስታንቡልሆስፒታል #የልብሕክምና #በጎአድራጎት #ጤና #ታዬአጽቀሥላሴ #ኢትዮጵያ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ክቡር ታዬ አጽቀሥላሴ በኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታል ተገኝተው በኢትዮጵያዊያንና በውጭ ሀገር ስፔሻሊስቶች እየተከናወነ በሚገኘው የልብ ህሙማን ህፃናት የነፃ ቀዶ ጥገና አገልግሎት ተጠቃሚ የሆኑ ህፃናትን ጎብኝተዋል።
ፕሬዝዳንቱ በጉብኝታቸው ወቅት ሆስፒታሉ እያከናወነ ያለውን ዘመናዊ የሕክምና አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራ አድንቀው በኢትዮጵያ የሕክምና ዘርፉ ወደ አዲስ ምዕራፍ መሸጋገሩን ጠቁመዋል።
ለሕክምናው ቡድን አገልግሎት "Heart to Heart Children’s Aid" የተሰኘው ፋውንዴሽን ካሰባሰበው የእርዳታ ገንዘብ እና Ethio-Istanbul General Hospital ባደረገው ሙሉ የሆስፒታል አገልግሎትና የባለሙያዎች አቅርቦት በሚያደርጉት ድጋፍ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ ሲሆን፣ በፕሮፌሰር ሳሻ የሚመራው የጣሊያኑ የ"ፔድሬ ፓዮ" የሕክምና ቡድንም በሥፍራው ተገኝቶ ከኢትዮ ኢስታንቡል ሆስፒታል ባለሙያዎች ጋር በመዋሀድ እየሰጠ ባለው አገልግሎት በ12 ቀናት ውስጥ ብቻ በአዲስ አበባ 58 በጅግጅጋ 16 በድምሩ የ74 ሕፃናት የልብ ቀዶ ጥገና በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።
የሆስፒታሉ መስራችና ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ብርሃን ተድላ እንደገለጹት፣ ኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታል አሁን የተሰሩትን 74 ህፃናት ሳይጨምር ባለፉት ሁለት ዓመታት ለ114 ሕፃናት በብር 120,000,000.00 (አንድ መቶ ሃያ ሚሊዮን ብር) በሚገመት ወጪ ነፃ ሕክምና ሰጥቷል።
ሆስፒታሉ ከተመሰረተ ሦስት ዓመት ቢሆነውም፣ ከ86 በላይ የሰብስፔሻሊስት ዶክተሮችን በመያዝ ውስብስብ የልብ፣ የካንሰር፣ የደም ስር የጭንቅላት የህብለሰረስና የአጥንት ቀዶ ጥገና ህክምናና በሌሎችም አገልግሎቶች ላይ ሰፊ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል።
አቶ ብርሃን አክለውም፣ ሆስፒታሉን ለማቋቋም ያነሳሳቸው በራሳቸው ላይ የደረሰ የሕክምና እንግልትና ዜጎች ለሕክምና ወደ ውጭ ሀገር ሄደው የሚደርስባቸውን የገንዘብ ወጪና የሞራል ጉዳት ለማስቀረት ካላቸው ራዕይ መሆኑን በመግለፅ አገልግሎቱን ከዚህ በተሻለ በስፋት ለመስጠት እንዲያስችላቸው ላቀረቡት የቦታ ጥያቄ መንግስት ትኩረት እንዲሰጥላቸው አሳስበዋል።
ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በንግግራቸው፣ "ያስተማረንን ሕዝብ ማስታወስ ትልቅ በረከት ነው" በማለት በውጭ ሀገር የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች ወደ ሀገራቸው ተመልሰው እንዲያገለግሉ ጥሪ አቅርበዋል።
እንዲህ ያሉ ለትርፍ ብቻ ታስበው ሳይሆን ለመልካም አገልግሎት የተቋቋሙ የላቁ የሕክምና ተቋማት መኖራቸው ዜጎች ወደ ውጭ በመሄድ ከሚያወጡት ከፍተኛ ወጪና ከሚደርስባቸው እንግልት እንደሚታደጋቸውም ገልጸዋል።
በተያያዘም ክቡር ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀስላሴ ለሕክምና ቡድኑ ባስተላለፉት የምስጋና መልእክት፣ በሕፃናቱና በቤተሰቦቻቸው ላይ የታየውን ደስታ "የተስፋ ብርሃን" በማለት ገልጸውታል። በተለይም የሕክምና ቡድኑ ወደ ጅግጅጋ በመጓዝ አገልግሎት መስጠቱ የሁለቱን ሀገራት (ኢትዮጵያና ጣሊያን) ግንኙነት ይበልጥ እንደሚያጠናክር ጠቁመዋል።
በዕለቱ ምስክርነታቸውን የሰጡ ወላጆች፣ የሕክምናውን ወጪ በመሸፈን ልጆቻቸው ማሳከም ባለመቻላቸው ለዓመታት ሲሰቃዩ መቆየታቸውን ገልፀው አሁን ባገኙት ነፃ የልብ ቀዶ ጥገና ልጆቻቸው ዳግም ሕይወት ማግኘታቸውን በደስታና በምርቃት ገልጸዋል።
ይህ የህፃናት ነፃ የልብ ሕክምና አገልግሎት በቀጣይነት ወደ ኦሮሚያ፣ አማራ፥ ትግራይ፣ ሲዳማ፣ ደቡብና ሌሎችም ክልሎች በመጓዝ ቀሪዎቹን ሕፃናት ለማከም ዕቅድ መያዙን አቶ ብርሃን ተድላ ገልፀው ለዚህ ዘመቻ መሳካት ከፍተኛ አስተዋፅኦና ትብብር ላደረጉት ለጤና ሚኒስቴር፣ ለጉምሩክ ኮሚሽን፣ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ለስካይላይት ሆቴል፣ ለኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ቁጥጥር ባለሥልጣንና ለሌሎችም በዘመቻው ለተሳተፉ የህክምና ተቋማት እንዲሁም የገንዘብ ድጋፍ ላደረጉ በጎ አድራጊዎችና ለፋውንዴሽኑ የቦርድ አባላት ከፍተኛ ምስጋና አቅርበዋል። #ኢትዮኢስታንቡልሆስፒታል #የልብሕክምና #በጎአድራጎት #ጤና #ታዬአጽቀሥላሴ #ኢትዮጵያ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
4 months ago
የልብ ሕሙማን ሕፃናት ተስፋ
170 ሕፃናት በ45 ቀናት ውስጥ ነፃ ሕክምና ሊያገኙ ነው
#ethiopia | በኢትዮጵያ በልብ ሕመም ሳቢያ በሕክምና ወረፋ ላይ ላሉና ለከፋ ችግር ለተጋለጡ ሕፃናት ትልቅ የምስራች ተሰምቷል።
የኸርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ (Heart to Heart Children's Aid) ፋውንዴሽን "በኢትዮጵያውያን የልብ ሐኪሞች - ለኢትዮጵያውያን ሕጻናት ልብ ጤና!!" በሚል መሪ ቃል፣ 170 ሕፃናትን በ45 ቀናት ውስጥ ለማከም የሚያስችል ታሪካዊ ስምምነት መጋቢት 20/2018 ዓ.ም በስካይላይት ሆቴል ፈጽሟል።
የስምምነቱ ዋና ዋና ነጥቦች፦
ሕክምናው ከሚያዝያ 12/2018 (April 20) ጀምሮ ባሉት 45 ቀናት ውስጥ ተጠናቆ ለሕፃናቱ ይደርሳል።
በስምምነቱ ላይ የጤና ሚኒስቴር፣ የጥቁር አንበሳና የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታሎች፣ የኢትዮ ኢስታንቡል፣ ጣዝማና ኤሊዘር የልብ ሕክምና ማዕከላት እንዲሁም የዘርፉ ማህበራት በጋራ ለመሥራት ቃል ገብተዋል።
አቶ ብርሃን ተድላ (የፋውንዴሽኑ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ) እንደገለጹት፣ ፋውንዴሽኑ አስፈላጊውን የሕክምና ግብዓትና ወጪ በመሸፈን ተልዕኮውን ይመራል።
ከጣልያን አገር የሚመጣ የሕክምና ቡድንም የዚሁ ጥረት አካል ሲሆን፣ ለ50 ሕፃናት ሕክምና ይሰጣል።
ይህ ትብብር በሕክምና ወረፋ ብዛት ሕይወታቸው የሚያልፍ ሕፃናትን ለመታደግ ከመጣጣሩም በላይ፣ የሀገር ውስጥ የሕክምና ባለሙያዎችና ተቋማት ተቀናጅተው ትልቅ ለውጥ ማምጣት እንደሚችሉ በተግባር ያሳየ ነው።
#getu #hearttoheart #childrenshealth #cardiacsurgery #ethiopiahealth #humanitarianaid #ethioistanbulhospital #ministryofhealth #savinglives #addisababa #የልብሕክምና #ሕፃናት #በጎአድራጎት #ጤና #ጌጡተመስገን #getutemesgen
170 ሕፃናት በ45 ቀናት ውስጥ ነፃ ሕክምና ሊያገኙ ነው
#ethiopia | በኢትዮጵያ በልብ ሕመም ሳቢያ በሕክምና ወረፋ ላይ ላሉና ለከፋ ችግር ለተጋለጡ ሕፃናት ትልቅ የምስራች ተሰምቷል።
የኸርት ቱ ኸርት ቺልድረንስ ኤይድ (Heart to Heart Children's Aid) ፋውንዴሽን "በኢትዮጵያውያን የልብ ሐኪሞች - ለኢትዮጵያውያን ሕጻናት ልብ ጤና!!" በሚል መሪ ቃል፣ 170 ሕፃናትን በ45 ቀናት ውስጥ ለማከም የሚያስችል ታሪካዊ ስምምነት መጋቢት 20/2018 ዓ.ም በስካይላይት ሆቴል ፈጽሟል።
የስምምነቱ ዋና ዋና ነጥቦች፦
ሕክምናው ከሚያዝያ 12/2018 (April 20) ጀምሮ ባሉት 45 ቀናት ውስጥ ተጠናቆ ለሕፃናቱ ይደርሳል።
በስምምነቱ ላይ የጤና ሚኒስቴር፣ የጥቁር አንበሳና የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታሎች፣ የኢትዮ ኢስታንቡል፣ ጣዝማና ኤሊዘር የልብ ሕክምና ማዕከላት እንዲሁም የዘርፉ ማህበራት በጋራ ለመሥራት ቃል ገብተዋል።
አቶ ብርሃን ተድላ (የፋውንዴሽኑ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ) እንደገለጹት፣ ፋውንዴሽኑ አስፈላጊውን የሕክምና ግብዓትና ወጪ በመሸፈን ተልዕኮውን ይመራል።
ከጣልያን አገር የሚመጣ የሕክምና ቡድንም የዚሁ ጥረት አካል ሲሆን፣ ለ50 ሕፃናት ሕክምና ይሰጣል።
ይህ ትብብር በሕክምና ወረፋ ብዛት ሕይወታቸው የሚያልፍ ሕፃናትን ለመታደግ ከመጣጣሩም በላይ፣ የሀገር ውስጥ የሕክምና ባለሙያዎችና ተቋማት ተቀናጅተው ትልቅ ለውጥ ማምጣት እንደሚችሉ በተግባር ያሳየ ነው።
#getu #hearttoheart #childrenshealth #cardiacsurgery #ethiopiahealth #humanitarianaid #ethioistanbulhospital #ministryofhealth #savinglives #addisababa #የልብሕክምና #ሕፃናት #በጎአድራጎት #ጤና #ጌጡተመስገን #getutemesgen
4 months ago
የሕይወት አድን ጥሪ
ለመምህር ዘመነ በጋራ እንድረስላቸው
#ethiopia | ቃለ እግዚአብሔርን ሲያስተምሩና ሲመክሩ የኖሩት ታላቁ አባት መልዓከ ብርሃን መምህር ዘመነ፣ በአሁኑ ወቅት በጠና የልብ ሕመም ምክንያት በከባድ ሁኔታ ላይ ይገኛሉ።
ሐኪሞች ሕይወታቸውን ለማዳን በአፋጣኝ የልብ ምት መቆጣጠሪያ (Permanent Pacemaker) መለወጥ እንዳለባቸው ወስነዋል።
አስፈላጊው መሣሪያ፦ የልብ ምት መቆጣጠሪያ (Permanent Pacemaker)።
የሚያስፈልገው ገንዘብ፦
500,000 (አምስት መቶ ሺህ) ብር።
ይህ የሕክምና ወጪ ከመምህራችን አቅም በላይ በመሆኑ የእያንዳንዳችንን ርብርብ ይሻል።
ድጋፍ ለማድረግ፦
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)
1000502420384
ዓባይ ባንክ (Abay Bank)
9250885
የምትሰጡት ሳንቲም ሳይሆን የሰው ሕይወት ነው!
እንዲሉ፣ ዛሬ የምናደርገው ጥቂት እርዳታ ለታላቁ አባት የሕይወት ተስፋ ይሆናል።
እባክዎ ይህ መልእክት ለብዙዎች እንዲደርስ ሼር (Share) በማድረግ ይተባበሩን።
#getu #ethiopia #healthalert #saveteacherzemene #heartsurgery #pacemaker #charityethiopia #communitysupport #addisababa #churchteachers #መምህርዘመነ #የልብሕክምና #የሕይወትአድንጥሪ #እርዳታ #ኢትዮጵያ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
ለመምህር ዘመነ በጋራ እንድረስላቸው
#ethiopia | ቃለ እግዚአብሔርን ሲያስተምሩና ሲመክሩ የኖሩት ታላቁ አባት መልዓከ ብርሃን መምህር ዘመነ፣ በአሁኑ ወቅት በጠና የልብ ሕመም ምክንያት በከባድ ሁኔታ ላይ ይገኛሉ።
ሐኪሞች ሕይወታቸውን ለማዳን በአፋጣኝ የልብ ምት መቆጣጠሪያ (Permanent Pacemaker) መለወጥ እንዳለባቸው ወስነዋል።
አስፈላጊው መሣሪያ፦ የልብ ምት መቆጣጠሪያ (Permanent Pacemaker)።
የሚያስፈልገው ገንዘብ፦
500,000 (አምስት መቶ ሺህ) ብር።
ይህ የሕክምና ወጪ ከመምህራችን አቅም በላይ በመሆኑ የእያንዳንዳችንን ርብርብ ይሻል።
ድጋፍ ለማድረግ፦
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)
1000502420384
ዓባይ ባንክ (Abay Bank)
9250885
የምትሰጡት ሳንቲም ሳይሆን የሰው ሕይወት ነው!
እንዲሉ፣ ዛሬ የምናደርገው ጥቂት እርዳታ ለታላቁ አባት የሕይወት ተስፋ ይሆናል።
እባክዎ ይህ መልእክት ለብዙዎች እንዲደርስ ሼር (Share) በማድረግ ይተባበሩን።
#getu #ethiopia #healthalert #saveteacherzemene #heartsurgery #pacemaker #charityethiopia #communitysupport #addisababa #churchteachers #መምህርዘመነ #የልብሕክምና #የሕይወትአድንጥሪ #እርዳታ #ኢትዮጵያ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
5 months ago
አስቸኳይ የሕይወት አድን ጥሪ
የአንዲት እናትን ሕይወት እንታደግ
#ethiopia | ባለ ትዳርና የአንዲት ሴት ልጅ እናት የሆነችው ወይዘሮ መቅደስ ሰለሞን፣ በደረሰባት ጽኑ የልብ ሕመም ምክንያት ሕይወቷ አደጋ ላይ ወድቋል። ቀደም ሲል ቤተሰቦቿ ያላቸውን ጥሪት በማሟጠጥ ሕንድ አገር ድረስ ሄዳ የታከመች ቢሆንም፣ አሁን ግን የልቧ ቱቦ በመጥበቡ ምክንያት በአፋጣኝ ሌላ ቀዶ ጥገና እንዲደረግላት በታዝማ የውስጥ ደዌና ቀዶ ጥገና ማዕከል ተወስኖባታል።
ለዚህ ሕክምና ከ 800,000 (ስምንት መቶ ሺህ) ብር በላይ ያስፈልጋል። ባለቤቷ አቶ ወንድማገኝ ጌታቸው በአንድ የግል ኩባንያ ውስጥ ተቀጥሮ በሚያገኘው አነስተኛ ገቢ ይህን ከፍተኛ ወጪ መሸፈን በፍጹም የማይቻል ሆኖባቸዋል።
"ሰማይ ተደፍቶብናል" የሚሉት ቤተሰቦቿ፣ የወገን ያለህ እያሉ ይማጸናሉ።
ይህች እናት ወደ ልጇና ወደ ባለቤቷ በጤና ተመልሳ እንድትቀላቀል፣ እኛ ወገኖቿ በአቅማችን ያለውን ድጋፍ እንድናደርግላት በፈጣሪ ስም ጥሪ ቀርቧል። ዛሬ የምናደርገው ጥቂት እርዳታ የአንዲትን እናት ሕይወት ይታደጋል።
ድጋፍ ለማድረግ (በባንክ አካውንቶቻቸው)፦
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)፦ 1000361917468
አዋሽ ባንክ (Awash Bank)፦ 01349432281700
ስም፦ መቅደስ ሰለሞን / ወንድማገኝ ጌታቸው
ስልክ ቁጥሮች፦
📞 0911 74 72 53
📞 0966 98 44 11
የሰጠ አይጎድልበትም! እባክዎን ይህንን መረጃ Share በማድረግ ለሌሎች እንዲደርስ ይተባበሩን።
#የእርዳታጥሪ #መቅደስሰለሞን #የልብሕክምና #ኢትዮጵያ #savemekdes #medicalhelp #ethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
የአንዲት እናትን ሕይወት እንታደግ
#ethiopia | ባለ ትዳርና የአንዲት ሴት ልጅ እናት የሆነችው ወይዘሮ መቅደስ ሰለሞን፣ በደረሰባት ጽኑ የልብ ሕመም ምክንያት ሕይወቷ አደጋ ላይ ወድቋል። ቀደም ሲል ቤተሰቦቿ ያላቸውን ጥሪት በማሟጠጥ ሕንድ አገር ድረስ ሄዳ የታከመች ቢሆንም፣ አሁን ግን የልቧ ቱቦ በመጥበቡ ምክንያት በአፋጣኝ ሌላ ቀዶ ጥገና እንዲደረግላት በታዝማ የውስጥ ደዌና ቀዶ ጥገና ማዕከል ተወስኖባታል።
ለዚህ ሕክምና ከ 800,000 (ስምንት መቶ ሺህ) ብር በላይ ያስፈልጋል። ባለቤቷ አቶ ወንድማገኝ ጌታቸው በአንድ የግል ኩባንያ ውስጥ ተቀጥሮ በሚያገኘው አነስተኛ ገቢ ይህን ከፍተኛ ወጪ መሸፈን በፍጹም የማይቻል ሆኖባቸዋል።
"ሰማይ ተደፍቶብናል" የሚሉት ቤተሰቦቿ፣ የወገን ያለህ እያሉ ይማጸናሉ።
ይህች እናት ወደ ልጇና ወደ ባለቤቷ በጤና ተመልሳ እንድትቀላቀል፣ እኛ ወገኖቿ በአቅማችን ያለውን ድጋፍ እንድናደርግላት በፈጣሪ ስም ጥሪ ቀርቧል። ዛሬ የምናደርገው ጥቂት እርዳታ የአንዲትን እናት ሕይወት ይታደጋል።
ድጋፍ ለማድረግ (በባንክ አካውንቶቻቸው)፦
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)፦ 1000361917468
አዋሽ ባንክ (Awash Bank)፦ 01349432281700
ስም፦ መቅደስ ሰለሞን / ወንድማገኝ ጌታቸው
ስልክ ቁጥሮች፦
📞 0911 74 72 53
📞 0966 98 44 11
የሰጠ አይጎድልበትም! እባክዎን ይህንን መረጃ Share በማድረግ ለሌሎች እንዲደርስ ይተባበሩን።
#የእርዳታጥሪ #መቅደስሰለሞን #የልብሕክምና #ኢትዮጵያ #savemekdes #medicalhelp #ethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
Comments