10 days ago
የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን እና የሲንቄ ባንክ ስትራቴጂካዊ የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ
#ethiopia | የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን እያከናወናቸው ያሉትን የቤት ልማትና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎች ይበልጥ ለማጠናከር እንዲሁም የፋይናንስ አቅሙን ለማሳደግ የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ከሲንቄ ባንክ ጋር ተፈራርሟል።
ኮርፖሬሽኑ በሀገሪቱ የኢኮኖሚና ማህበራዊ እድገት ላይ እያበረከተ ያለውን በጎ አስተዋጽኦ ለማስፋት እና ዘመናዊ የቤት ልማት ስራዎችን ተደራሽ ለማድረግ ከሀገር ውስጥ የፋይናንስ ተቋማት ጋር ያለውን አጋርነት እያጠናከረ ይገኛል።
በዚሁ መሰረት ዛሬ የተደረሰው ስምምነት ኮርፖሬሽኑ ለሚያከናውናቸው ሰፊ የቤት ልማት ፕሮጀክቶች የሚውል የፋይናንስ አቅርቦት ማመቻቸትን የሚያካትት ሲሆን፥ ሁለቱ ተቋማት በሌሎች ስትራቴጂካዊ የኢንቨስትመንት መስኮች ላይ በቅንጅት ለመስራት ተስማምተዋል።
በስምምነት ስነ-ስርዓቱ ላይ የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ረሻድ ከማል፣ የሲንቄ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ ንዋይ መገርሣ እና የሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
በወቅቱም የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ረሻድ ከማል እንደገለጹት፤ ይህ ስምምነት ኮርፖሬሽኑ የጀመራቸውን ግዙፍ የቤት ልማት ፕሮጀክቶች በላቀ የፋይናንስ አቅም ለመደገፍ እና የተቋሙን ተወዳዳሪነት ይበልጥ ለማሳደግ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል።
#የፌደራልቤቶችኮርፖሬሽን #ሲንቄባንክ #የቤትልማት #ኢንቨስትመንት #ፋይናንስ #ባንክ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን እያከናወናቸው ያሉትን የቤት ልማትና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎች ይበልጥ ለማጠናከር እንዲሁም የፋይናንስ አቅሙን ለማሳደግ የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ከሲንቄ ባንክ ጋር ተፈራርሟል።
ኮርፖሬሽኑ በሀገሪቱ የኢኮኖሚና ማህበራዊ እድገት ላይ እያበረከተ ያለውን በጎ አስተዋጽኦ ለማስፋት እና ዘመናዊ የቤት ልማት ስራዎችን ተደራሽ ለማድረግ ከሀገር ውስጥ የፋይናንስ ተቋማት ጋር ያለውን አጋርነት እያጠናከረ ይገኛል።
በዚሁ መሰረት ዛሬ የተደረሰው ስምምነት ኮርፖሬሽኑ ለሚያከናውናቸው ሰፊ የቤት ልማት ፕሮጀክቶች የሚውል የፋይናንስ አቅርቦት ማመቻቸትን የሚያካትት ሲሆን፥ ሁለቱ ተቋማት በሌሎች ስትራቴጂካዊ የኢንቨስትመንት መስኮች ላይ በቅንጅት ለመስራት ተስማምተዋል።
በስምምነት ስነ-ስርዓቱ ላይ የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ረሻድ ከማል፣ የሲንቄ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ ንዋይ መገርሣ እና የሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
በወቅቱም የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ረሻድ ከማል እንደገለጹት፤ ይህ ስምምነት ኮርፖሬሽኑ የጀመራቸውን ግዙፍ የቤት ልማት ፕሮጀክቶች በላቀ የፋይናንስ አቅም ለመደገፍ እና የተቋሙን ተወዳዳሪነት ይበልጥ ለማሳደግ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል።
#የፌደራልቤቶችኮርፖሬሽን #ሲንቄባንክ #የቤትልማት #ኢንቨስትመንት #ፋይናንስ #ባንክ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
1 month ago
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በ9 ወር 10 ቢሊዮን ብር ገቢ ሰበሰበ
#ethiopia | የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈፃፀሙን በገመገመበት ወቅት፣ ተቋማዊ ሪፎርሙን ተከትሎ እጅግ አስደናቂ ውጤቶችን ማስመዝገቡን አስታውቋል። ኮርፖሬሽኑ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ56 በመቶ የገቢ ዕድገት አሳይቷል።
በ9 ወራት ውስጥ ከ10 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተገኝቷል። ይህም ካለፈው ዓመት የ3.4 ቢሊዮን ብር ብልጫ አለው።
በርዝመቱ ትልቁ የሆነው ባለ 27 ወለል የሱማሌ ተራ ሕንፃ እና በፒያሳ ለወርቅ ቤቶች ተብሎ የታሰበው ዘመናዊ ሞል ግንባታ ተጠናቅቀው ተመርቀዋል።
ለመጀመሪያ ጊዜ የ3ዲ (3D) ኮንክሪት ግንባታ ቴክኖሎጂ ወደ ሀገር ውስጥ ገብቶ በሙከራ ላይ ይገኛል።
በልማት ምክንያት የፈረሱ 731 ሱቆች በ"ዜሮ ኢንቨስትመንት" ተገንብተው ለደንበኞች ተላልፈዋል።
የኮንክሪት ውጤቶች (ብሎኬትና ታይልስ) ለገበያ በስፋት እየቀረቡ ሲሆን፣ በሪል ስቴት ዘርፉም ቤቶችን በአጭር ጊዜ ገንብቶ በማስረከብ ታማኝነቱን አረጋግጧል።
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የ50 ዓመት ጉዞውን በወርቅ ኢዮቤልዩ እያከበረ፣ እንዲህ ያለ የገቢና የቴክኖሎጂ ስኬት ማስመዝገቡ ለሀገራችን የግንባታ ዘርፍ ትልቅ ተስፋ ነው።
በተለይ የ3D ግንባታ ቴክኖሎጂ የቤቶችን ችግር በአጭር ጊዜ ለመፍታት ወሳኝ ሚና ይኖረዋል።
ከአሮጌው አሰራር ወደ ዘመናዊው የግንባታ ምዕራፍ!
#getu #federalhousingcorporation #ethiopianconstruction #housingdevelopement #3dconstruction #urbanrenewal #addisababacorridor #breakingnews #fhc #ኢትዮጵያ #ቤቶችኮርፖሬሽን #ግንባታ #ሪፖርት #ጌጡተመስገን #getutemesgen
#ethiopia | የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈፃፀሙን በገመገመበት ወቅት፣ ተቋማዊ ሪፎርሙን ተከትሎ እጅግ አስደናቂ ውጤቶችን ማስመዝገቡን አስታውቋል። ኮርፖሬሽኑ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ56 በመቶ የገቢ ዕድገት አሳይቷል።
በ9 ወራት ውስጥ ከ10 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተገኝቷል። ይህም ካለፈው ዓመት የ3.4 ቢሊዮን ብር ብልጫ አለው።
በርዝመቱ ትልቁ የሆነው ባለ 27 ወለል የሱማሌ ተራ ሕንፃ እና በፒያሳ ለወርቅ ቤቶች ተብሎ የታሰበው ዘመናዊ ሞል ግንባታ ተጠናቅቀው ተመርቀዋል።
ለመጀመሪያ ጊዜ የ3ዲ (3D) ኮንክሪት ግንባታ ቴክኖሎጂ ወደ ሀገር ውስጥ ገብቶ በሙከራ ላይ ይገኛል።
በልማት ምክንያት የፈረሱ 731 ሱቆች በ"ዜሮ ኢንቨስትመንት" ተገንብተው ለደንበኞች ተላልፈዋል።
የኮንክሪት ውጤቶች (ብሎኬትና ታይልስ) ለገበያ በስፋት እየቀረቡ ሲሆን፣ በሪል ስቴት ዘርፉም ቤቶችን በአጭር ጊዜ ገንብቶ በማስረከብ ታማኝነቱን አረጋግጧል።
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የ50 ዓመት ጉዞውን በወርቅ ኢዮቤልዩ እያከበረ፣ እንዲህ ያለ የገቢና የቴክኖሎጂ ስኬት ማስመዝገቡ ለሀገራችን የግንባታ ዘርፍ ትልቅ ተስፋ ነው።
በተለይ የ3D ግንባታ ቴክኖሎጂ የቤቶችን ችግር በአጭር ጊዜ ለመፍታት ወሳኝ ሚና ይኖረዋል።
ከአሮጌው አሰራር ወደ ዘመናዊው የግንባታ ምዕራፍ!
#getu #federalhousingcorporation #ethiopianconstruction #housingdevelopement #3dconstruction #urbanrenewal #addisababacorridor #breakingnews #fhc #ኢትዮጵያ #ቤቶችኮርፖሬሽን #ግንባታ #ሪፖርት #ጌጡተመስገን #getutemesgen
2 months ago
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የወርቅ ኢዮቤልዩ ተጠናቀቀ፤
የቤት አቅርቦትን በዘላቂነት ለመፍታት ቃል ተገባ
#ethiopia | ላለፉት ሦስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ምስረታ 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል ዛሬ በማጠቃለያ መድረክና ዕውቅና በመስጠት ተጠናቋል።
በኮርፖሬሽኑ የተገነቡ አዳዲስ ሕንጻዎች የተመረቁ ሲሆን፣ የተቋሙን የሪፎርም ስኬት የሚያሳይ ኤግዚቢሽን ለዕይታ ክፍት ሆኖ ቆይቷል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚው ረሻድ ከማል (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ በቀጣይ ዓመታት የቤት አቅርቦት ፍላጎትን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችሉ ሰፋፊ ዕቅዶች ተይዘዋል።
ዕውቅና፦ ለተቋሙ ግማሽ ክፍለ ዘመን ጉዞና ለተመዘገቡ ስኬቶች አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ልዩ ዕውቅና ተሰጥቷል።
ዶ/ር ረሻድ ተቋሙ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ያከናወነው የሪፎርም ሥራ ውጤታማ መሆኑን ጠቁመው፣ የቤት ፍላጎት የሰው ልጅ መሠረታዊ መብት በመሆኑ ባለድርሻ አካላት ከኮርፖሬሽኑ ጋር በቅንጅት እንዲሠሩ ጥሪ አቅርበዋል።
#getu #federalhousingcorporation #goldenjubilee #housingethiopia #drreshadkemal #realestateethiopia #urbandevelopment #addisababa #ethiopianews #የፌዴራልቤቶችኮርፖሬሽን #ወርቅኢዮቤልዩ #ቤትልማት #ሪልስቴት #አዲስአበባ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
የቤት አቅርቦትን በዘላቂነት ለመፍታት ቃል ተገባ
#ethiopia | ላለፉት ሦስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ምስረታ 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል ዛሬ በማጠቃለያ መድረክና ዕውቅና በመስጠት ተጠናቋል።
በኮርፖሬሽኑ የተገነቡ አዳዲስ ሕንጻዎች የተመረቁ ሲሆን፣ የተቋሙን የሪፎርም ስኬት የሚያሳይ ኤግዚቢሽን ለዕይታ ክፍት ሆኖ ቆይቷል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚው ረሻድ ከማል (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ በቀጣይ ዓመታት የቤት አቅርቦት ፍላጎትን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችሉ ሰፋፊ ዕቅዶች ተይዘዋል።
ዕውቅና፦ ለተቋሙ ግማሽ ክፍለ ዘመን ጉዞና ለተመዘገቡ ስኬቶች አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ልዩ ዕውቅና ተሰጥቷል።
ዶ/ር ረሻድ ተቋሙ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ያከናወነው የሪፎርም ሥራ ውጤታማ መሆኑን ጠቁመው፣ የቤት ፍላጎት የሰው ልጅ መሠረታዊ መብት በመሆኑ ባለድርሻ አካላት ከኮርፖሬሽኑ ጋር በቅንጅት እንዲሠሩ ጥሪ አቅርበዋል።
#getu #federalhousingcorporation #goldenjubilee #housingethiopia #drreshadkemal #realestateethiopia #urbandevelopment #addisababa #ethiopianews #የፌዴራልቤቶችኮርፖሬሽን #ወርቅኢዮቤልዩ #ቤትልማት #ሪልስቴት #አዲስአበባ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
Sponsored by
Surafel
Comments