Logo
FastMereja
ቪዚት ሩዋንዳ የአስቶን ቪላ ዋና ስፖንሰር ሆነ
#fastmereja I የአስቶን ቪላ የእግር ኳስ ክለብ ከ"ቪዚት ሩዋንዳ" (Visit Rwanda) ጋር በታሪኩ ትልቁ የተባለውን የይፋዊ ቱሪዝም፣ የቡና አቅራቢነት እና የፊት ለፊት ማሊያ ስፖንሰርሺፕ ስምምነት በዛሬው ዕለት በይፋ ተፈራርሟል።

ይህ አዲስ ስምምነት የቪዚት ሩዋንዳ አርማ በወንዶች፣ በሴቶች እና በታዳጊዎች (አካዳሚ) ቡድን ማሊያዎች ላይ እንዲሁም በተለያዩ የስታዲየም ስፍራዎች ላይ ጎልቶ እንዲታይ ያደርጋል። ሁለቱ ወገኖች ከቱሪዝም ማስተዋወቅ ባሻገር በንግድ፣ በኢንቨስትመንት፣ በስፖርታዊ ስልጠናዎች እና በበጎ አድራጎት ስራዎች ላይ በጋራ ለመስራት ተስማምተዋል።

የአስቶን ቪላ የቢዝነስ ኦፕሬሽን ፕሬዝዳንት ፍራንቼስኮ ካልቮ ስምምነቱን አስመልክተው ሲናገሩ፣ ይህ ጥምረት ክለቡ በአለም አቀፍ ገበያ ላይ እያደረገ ላለው መስፋፋት ማረጋገጫ መሆኑን ገልጸው፣ በቱሪዝም እና ስፖርታዊ ልማት ዙሪያ ትርጉም ያላቸው ስራዎችን ለመስራት መጓጓታቸውን አስታውቀዋል። በሌላ በኩል የሩዋንዳ ኮንቬንሽን ቢሮ ዋና ስራ አስፈጻሚ ጃኔት ካሬመራ፣ ስምምነቱ ሩዋንዳን የኢንቨስትመንት እና የቱሪዝም መዳረሻ አድርጎ ለማስተዋወቅ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ጠቁመው፣ በዩናይትድ ኪንግደም እና በአውሮፓ አዳዲስ ደንበኞችን ለመድረስ እንደሚያግዝ ገልጸዋል። ክለቡ አስቀድመው የ2026/27 የውድድር ዘመን ማሊያ የገዙ ደጋፊዎች የቪዚት ሩዋንዳን አርማ በነጻ ማሊያቸው ላይ ማስተከል እንደሚችሉ አስታውቋል።

26 days ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.