ደቡብ አፍሪካውያን ከሌሎች አፍሪካውያን ጋር በፍቅር መኖር ይፈልጋሉ፤ ፕሬዚዳንት ሲሪል ራማፎሳ
#ethiopia | በደቡብ አፍሪካ የተከሰተውን ፀረ-ስደተኞች ጥቃት ተከትሎ፣ የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ሲሪል ራማፎሳ ደቡብ አፍሪካውያን ከሌሎች አፍሪካውያን ወንድሞቻቸው ጋር በሰላምና በፍቅር የመኖር ፅኑ ፍላጎት እንዳላቸው ገለጹ።
ፕሬዚዳንቱ ይህንን መልዕክት ያስተላለፉት የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ በደቡብ አፍሪካ እያደረጉት ባለው ይፋዊ የስራ ጉብኝት ወቅት ባደረጉት ንግግር ነው። የራማፎሳ የሰላም ጥሪ የመጣው በሀገሪቱ በቅርቡ በተቀሰቀሰው፣ የሰዎችን ህይወት በነጠቀውና ከፍተኛ የንብረት ውድመት ባስከተለው የፀረ-ፍልሰተኞች ተቃውሞ ማዕበል ሳቢያ መሆኑ ተገልጿል።
ይህንን ዘግናኝ ጥቃት ተከትሎ በደቡብ አፍሪካ ላይ ከአለም አቀፍ ማህበረሰብ እና ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ብርቱ ትችት፣ ውግዘትና ዲፕሎማሲያዊ ጫናዎች እየበረቱባት ይገኛል። የፕሬዚዳንቱ ንግግርም ይህንን ዲፕሎማሲያዊ ውጥረት ለማርገብና የሀገሪቱን ገፅታ ለመገንባት ያለመ እንደሆነ ተጠቁሟል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ደቡብአፍሪካ #ሲሪልራማፎሳ #ዊሊያምሩቶ #አፍሪካ አንድነት #ዜና #የሰላምጥሪ
#ethiopia | በደቡብ አፍሪካ የተከሰተውን ፀረ-ስደተኞች ጥቃት ተከትሎ፣ የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ሲሪል ራማፎሳ ደቡብ አፍሪካውያን ከሌሎች አፍሪካውያን ወንድሞቻቸው ጋር በሰላምና በፍቅር የመኖር ፅኑ ፍላጎት እንዳላቸው ገለጹ።
ፕሬዚዳንቱ ይህንን መልዕክት ያስተላለፉት የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ በደቡብ አፍሪካ እያደረጉት ባለው ይፋዊ የስራ ጉብኝት ወቅት ባደረጉት ንግግር ነው። የራማፎሳ የሰላም ጥሪ የመጣው በሀገሪቱ በቅርቡ በተቀሰቀሰው፣ የሰዎችን ህይወት በነጠቀውና ከፍተኛ የንብረት ውድመት ባስከተለው የፀረ-ፍልሰተኞች ተቃውሞ ማዕበል ሳቢያ መሆኑ ተገልጿል።
ይህንን ዘግናኝ ጥቃት ተከትሎ በደቡብ አፍሪካ ላይ ከአለም አቀፍ ማህበረሰብ እና ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ብርቱ ትችት፣ ውግዘትና ዲፕሎማሲያዊ ጫናዎች እየበረቱባት ይገኛል። የፕሬዚዳንቱ ንግግርም ይህንን ዲፕሎማሲያዊ ውጥረት ለማርገብና የሀገሪቱን ገፅታ ለመገንባት ያለመ እንደሆነ ተጠቁሟል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ደቡብአፍሪካ #ሲሪልራማፎሳ #ዊሊያምሩቶ #አፍሪካ አንድነት #ዜና #የሰላምጥሪ
2 months ago