Logo
YenetaTube
"ዜንጦ" ሌቦች : በጠራራ ፀሐይ
በአዶርሰም ሕንፃ የተፈጸመው አስደንጋጭ ዝርፊያ
#ethiopia | ​በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ ሚሊኒየም አዳራሽ አካባቢ በሚገኘው አዶርሰም ሕንፃ 2ኛ ፎቅ ላይ፣ እነዚህ በፎቶው የሚታዩ የተደራጁ ወጣቶች ከፍተኛ ዋጋ ያላቸውን ንብረቶች ዘርፈው ተሰውረዋል።

​የተዘረፉ ንብረቶች፦
ከፍተኛ ዋጋ ያላቸው ላፕቶፕ ኮምፒውተሮች፣ ታብሌቶች፣ የፎቶና ቪዲዮ ካሜራዎች እንዲሁም የስልክ መሣሪያዎች።

​የሌቦቹ ሙከራ፦
የቢሮውን የደህንነት ካሜራ መረጃ (Footage) ለማጥፋት ቢሞክሩም፣ በሌሎች የደህንነት ካሜራዎች በግልጽ ሊታወቁ ችለዋል።

​ድርጊቱ የተፈጸመው መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የአድዋን ድል በሚያከብርበት ዕለት በጠራራ ፀሐይ ነው።

​የጥቆማ ጥሪ፦
​እነዚህን ግለሰቦች የምታውቁ፣ ያያችሁ ወይም በተመሳሳይ ሁኔታ ዝርፊያ የተፈጸመባችሁ ወገኖች ጥቆማ በማድረግ እንድትተባበሩ ጥሪ ቀርቧል።

ጥቆማ ለሚያደርሱ ወገኖች ወሮታ ይከፈላል።

​ጥቆማ ለማድረስ፦
​ፖሊስ ጣቢያ፦ ቦሌ አደይ አበባ ፖሊስ ጣቢያ
​ስልክ፦ 0988188890 ወይም 0907247454

​እባክዎ ሌቦቹን ለሕግ ለማቅረብ እንዲቻል ይህንን መረጃ ሼር በማድረግ ይተባበሩ!

#addisababa #bole #crimealert #securitycamera #ethiopia #theftalert #adwavictoryday #communitysafety #አዲስአበባ #ቦሌ #ዝርፊያ #ጥቆማ #ሌቦች

3 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.