2 months ago
የምርጫ ቦርድ በሰልፍ ላይ ለሚገኙ መራጮች የድምፅ መስጫ ሰዓት መራዘሙን ገለጸ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዕለቱ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት ማብቂያ እስከሆነው 12:00 ሰዓት ድረስ በምርጫ ጣቢያዎች ተገኝተው በሰልፍ ላይ የነበሩ መራጮች በሙሉ ድምፅ ሰጥተው እስኪያጠናቅቁ ድረስ ሂደቱ እንደሚቀጥል አስታውቋል።
ይህ ውሳኔ የተላለፈው በምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 49 ንዑስ አንቀጽ 4 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ሲሆን፣ ቦርዱ አስገዳጅ ሁኔታዎች ሲያጋጥሙ የድምፅ መስጫ ሰዓትን ማራዘም እንደሚችል በሕጉ ላይ ተደንግጓል።
ውሳኔው የወጣው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ነው።
#nebe #ethiopianelection #electionupdate #democraticprocess #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዕለቱ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት ማብቂያ እስከሆነው 12:00 ሰዓት ድረስ በምርጫ ጣቢያዎች ተገኝተው በሰልፍ ላይ የነበሩ መራጮች በሙሉ ድምፅ ሰጥተው እስኪያጠናቅቁ ድረስ ሂደቱ እንደሚቀጥል አስታውቋል።
ይህ ውሳኔ የተላለፈው በምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 49 ንዑስ አንቀጽ 4 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ሲሆን፣ ቦርዱ አስገዳጅ ሁኔታዎች ሲያጋጥሙ የድምፅ መስጫ ሰዓትን ማራዘም እንደሚችል በሕጉ ላይ ተደንግጓል።
ውሳኔው የወጣው ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ነው።
#nebe #ethiopianelection #electionupdate #democraticprocess #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 months ago
5 months ago
🗳️ ለ7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ ከ9 ሚሊዮን በላይ መራጮች ተመዝግበዋል
#ethiopia | የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ እስካሁን ባለው ሂደት 9 ሚሊዮን 360 ሺህ 994 መራጮች በዲጂታል እና በማንዋል መመዝገባቸውን አስታወቀ። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ምሽቱን ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፣ የምዝገባ ሂደቱ ያለበትን ደረጃና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን በዝርዝር አብራርተዋል።
ዋና ዋና መረጃዎች፦
* የጣቢያዎች ሁኔታ፦ በሀገሪቱ ካሉ ከ52 ሺህ በላይ ጣቢያዎች ውስጥ 46,757 የሚሆኑት ሥራ የጀመሩ ሲሆን፣ ቀሪዎቹ 6,395 ጣቢያዎች በቁሳቁስ መዘግየት ምክንያት እስካሁን ሥራ አልጀመሩም።
* የገጠሙ ተግዳሮቶች፦ የቁሳቁስ ስርጭቱን ካስተጓጎሉ ምክንያቶች መካከል የተሽከርካሪ እጥረት፣ የነዳጅ እጥረት፣ የዝናብ ሁኔታ፣ በአፋር ክልል ያጋጠመ የቁሳቁስ መቃጠል እና የአንዳንድ ክልል አመራሮች የትብብር ማጣት ተጠቅሰዋል።
* የምዝገባ እንቅፋቶች፦ በመራጮች ምዝገባ ወቅት የመብራት እና የኢንተርኔት መቆራረጥ እንዲሁም የመራጮች የመረጃ አሰጣጥ ስህተቶች (የስም ቅደም ተከተል አለመጠበቅ) እንደ ዋና ችግር ተነስተዋል።
* የፓርቲዎች ክርክር፦ ለፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ክርክር መድረክ ዝግጅት የሚከታተል የባለሙያዎች ኮሚቴ ተዋቅሮ ሥራ መጀመሩ ተገልጿል።
የመራጮች ምዝገባ ሂደት እስከ መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ እንደሚቆይ ቦርዱ በድጋሚ አሳስቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ኢትዮጵያ #ምርጫ2018 #ብሔራዊምርጫቦርድ #የመራጮችምዝገባ #ዴሞክራሲ #ethiopiaelection2018 #nebe #electionupdate
#ethiopia | የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ እስካሁን ባለው ሂደት 9 ሚሊዮን 360 ሺህ 994 መራጮች በዲጂታል እና በማንዋል መመዝገባቸውን አስታወቀ። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ምሽቱን ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፣ የምዝገባ ሂደቱ ያለበትን ደረጃና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን በዝርዝር አብራርተዋል።
ዋና ዋና መረጃዎች፦
* የጣቢያዎች ሁኔታ፦ በሀገሪቱ ካሉ ከ52 ሺህ በላይ ጣቢያዎች ውስጥ 46,757 የሚሆኑት ሥራ የጀመሩ ሲሆን፣ ቀሪዎቹ 6,395 ጣቢያዎች በቁሳቁስ መዘግየት ምክንያት እስካሁን ሥራ አልጀመሩም።
* የገጠሙ ተግዳሮቶች፦ የቁሳቁስ ስርጭቱን ካስተጓጎሉ ምክንያቶች መካከል የተሽከርካሪ እጥረት፣ የነዳጅ እጥረት፣ የዝናብ ሁኔታ፣ በአፋር ክልል ያጋጠመ የቁሳቁስ መቃጠል እና የአንዳንድ ክልል አመራሮች የትብብር ማጣት ተጠቅሰዋል።
* የምዝገባ እንቅፋቶች፦ በመራጮች ምዝገባ ወቅት የመብራት እና የኢንተርኔት መቆራረጥ እንዲሁም የመራጮች የመረጃ አሰጣጥ ስህተቶች (የስም ቅደም ተከተል አለመጠበቅ) እንደ ዋና ችግር ተነስተዋል።
* የፓርቲዎች ክርክር፦ ለፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ክርክር መድረክ ዝግጅት የሚከታተል የባለሙያዎች ኮሚቴ ተዋቅሮ ሥራ መጀመሩ ተገልጿል።
የመራጮች ምዝገባ ሂደት እስከ መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ እንደሚቆይ ቦርዱ በድጋሚ አሳስቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ኢትዮጵያ #ምርጫ2018 #ብሔራዊምርጫቦርድ #የመራጮችምዝገባ #ዴሞክራሲ #ethiopiaelection2018 #nebe #electionupdate
Comments