Logo
SeledaPost
በሰሀራ በረሃ 49 ስደተኞች ህይወታቸው አልፎ ተገኙ።

ስደተኞቹ በህገወጥ መንገድ ሰፊውን በረሃ እያቋረጡ በነበረበት ወቅት እነሱን የያዘው ተሽከርካሪ በመገልበጡ ነው ህይወታቸው ያለፈው ተብሏል።

ከአደጋው የተረፉ ሁለት ስደተኞች 50 ኪሎሜትር ተጉዘው ለባለስልጣናት ከተናገሩ በኋላ የህይወት አድን ቡድን መሰማራታቸው ተገልጿል።

ስደተኞቹ የማሊ ዜግነት ሲኖራቸው በኒጀር እና አልጀሪያ አዋሳኝ አሳማካ ክልል ነው አደጋው የደረሰባቸው።

ይህ አሳዛኝ ክስተት በሰሀራ በረሃ እየደረሰ ያለውን አስከፊ የስደተኞች ሰቆቃ እንደሚያሳይ ተመልክቷል። #legit

Seledadotio
Seledadotio
12 hours ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.