5 hours ago
የተስፋው ትውልድ አሻራ፡ ከሀገራዊ ራዕይ እስከ ዓለም አቀፍ ልዕልና
**************
ሀገር ማለት የትናንት ታሪክ፣ የዛሬ ጥረት እና የነገ ተስፋ ድምር ውጤት ናት። ዛሬ የምናሳርፈው እያንዳንዱ አሻራ ለነገው ትውልድ የምናወርሰው የእድገት እና የሰላም ተሥፋ ነው።
በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መሪነት ይፋ የተደረገው የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ በአጭር ጊዜ ውስጥ አዲስ ሀገራዊ እይታ መፍጠር ችሏል። የኢትዮጵያ መንግስት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ላይ የወሰደው ቁርጠኝነት የሚመነጨው ከጠቅላይ ሚኒስትሩ የ"መደመር" ዕሳቤ ነው።
ይህ ዕሳቤ በአረንጓዴ አሻራ በተግባር ሲተረጎም አካባቢን፣ ኢኮኖሚን እና ብሔራዊ ማንነትን በማዋሃድ አዲስ ዓይነት ስነ-ምህዳራዊ የመንግስት አስተዳደር እንዲፈጠር አድርጓል።
ታሪክ ሰሪው የመደመር ትውልድ ደግሞ ይህንን የሀገር ውስጥ ራዕይ ይዞ በመነሳት፣ ታላላቅ ሀገራዊና አህጉራዊ ብሎም ዓለምአቀፋዊ ጉዳዮችን በብቃት እየከወነ ይገኛል።
የአረንጓዴ አሻራ ጉዳይ አንድምታው ከችግኝ ተከላ የዘለለ መሆኑን በተግባር እያረጋገጠ ያለው ይህ ትውልድ፣ የራሱን አቅምና ሁለንተናዊ ብቃት በዓለም አደባባይ እያስመሰከረ ነው።
የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር የትናንት የነጻነት አርበኝነታችንን በተፈጥሮ ጥበቃ የምንደግምበት የዘመናችን ድንቅ «ዓድዋ» ነው። ይህ የዘመናችን አድዋ ደግሞ የዛሬውን «የመደመር ትውልድ» የታሪክ አሻራ እና ሁለንተናዊ አቅም የሚፈትን ታላቅ አገራዊ ጥሪ ነው።
የዛሬው የመደመር ትውልድ እውቀቱን፣ ጉልበቱንና ፍቅሩን አስተባብሮ በተከታታይ ዓመታት አገሩ አረንጓዴ እያለበሳት ይገኛል። ዛሬ በእኛ (በመደመር) ትውልድ ጥረት እየተሰራ ያለ ስራ አገራችን የምግብ ዋስትናዋ በዘላቂነት የተረጋገጠና የአየር ንብረት መዛባት የማይበግራት ጽኑ እንድትሆን ያደርጋታል።
"የችግኝ ተከላ ተግባራችን ስለ ዛፎች ብቻ ሳይሆን ለወደፊቱ ለትውልድ ጥላ እና ተስፋን ስለመፍጠር ነው።" የሚለውን የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መርህ በመከተል እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ያሉ የዘመናችንን ሜጋ ፕሮጀክቶች ከደለል የሚታደግ፣ በግብርናው ዘርፍ የምግብ ሉዓላዊነትን የሚያረጋግጥ፣ በኢንዱስትሪው ለሚፈጠሩ የግብርና ማቀነባበሪያዎች ጥሬ ዕቃ የሚያቀርብ እና በአጠቃላይ በኢኮኖሚ, በልማት እና በማህበራዊ ስነ-ልቦና ላይ ጠንካራ መሠረት የሚጥል ሁለንተናዊ የብልፅግና ጉዞ ነው።
ይህም የመደመር ትውልድ የተፈጥሮ ሚዛንን ከመጠበቅ ባሻገር ሀገራዊ የልማት ምሰሶዎችን እንዴት ማፅናት እንደሚቻል ያሳየበት ህያው ማረጋገጫ ነው።
"ተስፋን እንትከል" ሲባል መሬት ላይ ችግኝ ማፅደቃችን ብቻ ሳይሆን፣ በልጆቻችን እና በቀጣዩ ትውልድ አዕምሮ ውስጥ የሀገር ፍቅርን፣ አብሮነትን እና የማይበገር ጥንካሬን መዝራታችን ነው።
የትናንት ታሪካችን የቱንም ያህል በፈተናዎች የተሞላ ቢሆንም ዛሬ የመደመር ትውልድ በእጆቹ የሚተክለው ተስፋ፣ ለነገው ትውልድ የማያልፍ ጥላ፣ የማይነጥፍ የኢኮኖሚ በረከት እና ቀና ብሎ የሚኮራባት ቅርስ ሆኖ ይፀድቃል። ስለዚህ ተስፋችንን እንትከል፤ የነገዋን ብሩህ ኢትዮጵያ ዛሬ በጋራ እንገንባ!
በበረከት ሽመልስ
Ethiopian Broadcasting Corporation #የመደመርትውልድ #ethiopia #greenliving #አረንጓዴአሻራ #ተፈጥሮ #ኢትዮጵያ
**************
ሀገር ማለት የትናንት ታሪክ፣ የዛሬ ጥረት እና የነገ ተስፋ ድምር ውጤት ናት። ዛሬ የምናሳርፈው እያንዳንዱ አሻራ ለነገው ትውልድ የምናወርሰው የእድገት እና የሰላም ተሥፋ ነው።
በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መሪነት ይፋ የተደረገው የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ በአጭር ጊዜ ውስጥ አዲስ ሀገራዊ እይታ መፍጠር ችሏል። የኢትዮጵያ መንግስት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ላይ የወሰደው ቁርጠኝነት የሚመነጨው ከጠቅላይ ሚኒስትሩ የ"መደመር" ዕሳቤ ነው።
ይህ ዕሳቤ በአረንጓዴ አሻራ በተግባር ሲተረጎም አካባቢን፣ ኢኮኖሚን እና ብሔራዊ ማንነትን በማዋሃድ አዲስ ዓይነት ስነ-ምህዳራዊ የመንግስት አስተዳደር እንዲፈጠር አድርጓል።
ታሪክ ሰሪው የመደመር ትውልድ ደግሞ ይህንን የሀገር ውስጥ ራዕይ ይዞ በመነሳት፣ ታላላቅ ሀገራዊና አህጉራዊ ብሎም ዓለምአቀፋዊ ጉዳዮችን በብቃት እየከወነ ይገኛል።
የአረንጓዴ አሻራ ጉዳይ አንድምታው ከችግኝ ተከላ የዘለለ መሆኑን በተግባር እያረጋገጠ ያለው ይህ ትውልድ፣ የራሱን አቅምና ሁለንተናዊ ብቃት በዓለም አደባባይ እያስመሰከረ ነው።
የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር የትናንት የነጻነት አርበኝነታችንን በተፈጥሮ ጥበቃ የምንደግምበት የዘመናችን ድንቅ «ዓድዋ» ነው። ይህ የዘመናችን አድዋ ደግሞ የዛሬውን «የመደመር ትውልድ» የታሪክ አሻራ እና ሁለንተናዊ አቅም የሚፈትን ታላቅ አገራዊ ጥሪ ነው።
የዛሬው የመደመር ትውልድ እውቀቱን፣ ጉልበቱንና ፍቅሩን አስተባብሮ በተከታታይ ዓመታት አገሩ አረንጓዴ እያለበሳት ይገኛል። ዛሬ በእኛ (በመደመር) ትውልድ ጥረት እየተሰራ ያለ ስራ አገራችን የምግብ ዋስትናዋ በዘላቂነት የተረጋገጠና የአየር ንብረት መዛባት የማይበግራት ጽኑ እንድትሆን ያደርጋታል።
"የችግኝ ተከላ ተግባራችን ስለ ዛፎች ብቻ ሳይሆን ለወደፊቱ ለትውልድ ጥላ እና ተስፋን ስለመፍጠር ነው።" የሚለውን የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መርህ በመከተል እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ያሉ የዘመናችንን ሜጋ ፕሮጀክቶች ከደለል የሚታደግ፣ በግብርናው ዘርፍ የምግብ ሉዓላዊነትን የሚያረጋግጥ፣ በኢንዱስትሪው ለሚፈጠሩ የግብርና ማቀነባበሪያዎች ጥሬ ዕቃ የሚያቀርብ እና በአጠቃላይ በኢኮኖሚ, በልማት እና በማህበራዊ ስነ-ልቦና ላይ ጠንካራ መሠረት የሚጥል ሁለንተናዊ የብልፅግና ጉዞ ነው።
ይህም የመደመር ትውልድ የተፈጥሮ ሚዛንን ከመጠበቅ ባሻገር ሀገራዊ የልማት ምሰሶዎችን እንዴት ማፅናት እንደሚቻል ያሳየበት ህያው ማረጋገጫ ነው።
"ተስፋን እንትከል" ሲባል መሬት ላይ ችግኝ ማፅደቃችን ብቻ ሳይሆን፣ በልጆቻችን እና በቀጣዩ ትውልድ አዕምሮ ውስጥ የሀገር ፍቅርን፣ አብሮነትን እና የማይበገር ጥንካሬን መዝራታችን ነው።
የትናንት ታሪካችን የቱንም ያህል በፈተናዎች የተሞላ ቢሆንም ዛሬ የመደመር ትውልድ በእጆቹ የሚተክለው ተስፋ፣ ለነገው ትውልድ የማያልፍ ጥላ፣ የማይነጥፍ የኢኮኖሚ በረከት እና ቀና ብሎ የሚኮራባት ቅርስ ሆኖ ይፀድቃል። ስለዚህ ተስፋችንን እንትከል፤ የነገዋን ብሩህ ኢትዮጵያ ዛሬ በጋራ እንገንባ!
በበረከት ሽመልስ
Ethiopian Broadcasting Corporation #የመደመርትውልድ #ethiopia #greenliving #አረንጓዴአሻራ #ተፈጥሮ #ኢትዮጵያ
10 hours ago
የመደመር አንቀጽ
ትውልድ የተቀራራቢ ዕድሜ ስብስብ ነው። ዕድሜ አንድ ሰው የኖረበት ወይም አንድ ከሥተት የቆየበት የጊዜ ርዝማኔ ነው። በዚህ የቆይታ ርዝማኔ ውስጥ የሰው ልጅ በተለያዩ የዕድገት ደረጃዎች ወይም የለውጥ ሂደት ውስጥ ያልፋል።
በትውልድ ፍሰት ውስጥ እያንዳንዱ ሰው የመጪው፣ የዛሬው ወይንም ያለፈው ትውልድ አባል ተብሎ ሊቆጠር ይችላል። ትውልድ ሕዝብን በዕድሜና በዘመን ከፋፍሎ የመመልከቻ መነጽርነው።
ግለሰብን የትውልድ አባል ከሚያደርጉት የትውልድ መገለጫዎች መካከል ዕድሜ አንዱ ነው። የአንድ ትውልድ አባላት የተቀራራቢ ዕድሜ ባለቤቶች ናቸው። ከሞላ ጎደል ልጅነታቸው፣ ወጣትነታቸው፣ ጉልምስናና እርጅናቸው በተቀራራቢ ወቅት የተፈጸመ ነው።
አንድ ትውልድ የተቀራራቢ ዘመን ተጋሪ ነው። ትውልድን ያለ ዘመን መግለጽ አይቻልም። ዘመን አንድ ትውልድ ተወልዶ፤ ዕድሜውን ኖሮ፤ ለቀጣዩ ትውልድ ዐሻራ ጥሎ፤ የሚያልፍበት የጊዜ ቁራጭ ነው።
አንድ ትውልድ ለአንድ ወቅት እንጂ ለዘላለም አይኖርም። ወቅት ሲባል ካለፈው ትውልድ የተወረሰው መልካም ጉዳዮችና ችግሮች ያሉበት፤ ለቀጣዩ ትውልድ ዐሻራችንን የምናሳርፍበት፤ ተወልደን ኖረን የምንሞትበት የዘመን ሰሌዳ ነው።
እንደ ዕድሜያችን ተማሪ፣ መሪ፣ መካሪ፣ ወዘተ የምንሆንበት ወቅት የተለያየ ነው።
የመደመር ትውልድ
ገጽ - 9
Ethiopian Broadcasting Corporation #ethiopia #medemer #generations #መደመር #የመደመርትውልድ
ትውልድ የተቀራራቢ ዕድሜ ስብስብ ነው። ዕድሜ አንድ ሰው የኖረበት ወይም አንድ ከሥተት የቆየበት የጊዜ ርዝማኔ ነው። በዚህ የቆይታ ርዝማኔ ውስጥ የሰው ልጅ በተለያዩ የዕድገት ደረጃዎች ወይም የለውጥ ሂደት ውስጥ ያልፋል።
በትውልድ ፍሰት ውስጥ እያንዳንዱ ሰው የመጪው፣ የዛሬው ወይንም ያለፈው ትውልድ አባል ተብሎ ሊቆጠር ይችላል። ትውልድ ሕዝብን በዕድሜና በዘመን ከፋፍሎ የመመልከቻ መነጽርነው።
ግለሰብን የትውልድ አባል ከሚያደርጉት የትውልድ መገለጫዎች መካከል ዕድሜ አንዱ ነው። የአንድ ትውልድ አባላት የተቀራራቢ ዕድሜ ባለቤቶች ናቸው። ከሞላ ጎደል ልጅነታቸው፣ ወጣትነታቸው፣ ጉልምስናና እርጅናቸው በተቀራራቢ ወቅት የተፈጸመ ነው።
አንድ ትውልድ የተቀራራቢ ዘመን ተጋሪ ነው። ትውልድን ያለ ዘመን መግለጽ አይቻልም። ዘመን አንድ ትውልድ ተወልዶ፤ ዕድሜውን ኖሮ፤ ለቀጣዩ ትውልድ ዐሻራ ጥሎ፤ የሚያልፍበት የጊዜ ቁራጭ ነው።
አንድ ትውልድ ለአንድ ወቅት እንጂ ለዘላለም አይኖርም። ወቅት ሲባል ካለፈው ትውልድ የተወረሰው መልካም ጉዳዮችና ችግሮች ያሉበት፤ ለቀጣዩ ትውልድ ዐሻራችንን የምናሳርፍበት፤ ተወልደን ኖረን የምንሞትበት የዘመን ሰሌዳ ነው።
እንደ ዕድሜያችን ተማሪ፣ መሪ፣ መካሪ፣ ወዘተ የምንሆንበት ወቅት የተለያየ ነው።
የመደመር ትውልድ
ገጽ - 9
Ethiopian Broadcasting Corporation #ethiopia #medemer #generations #መደመር #የመደመርትውልድ
Comments