11 days ago
የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን እና የሲንቄ ባንክ ስትራቴጂካዊ የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ
#ethiopia | የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን እያከናወናቸው ያሉትን የቤት ልማትና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎች ይበልጥ ለማጠናከር እንዲሁም የፋይናንስ አቅሙን ለማሳደግ የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ከሲንቄ ባንክ ጋር ተፈራርሟል።
ኮርፖሬሽኑ በሀገሪቱ የኢኮኖሚና ማህበራዊ እድገት ላይ እያበረከተ ያለውን በጎ አስተዋጽኦ ለማስፋት እና ዘመናዊ የቤት ልማት ስራዎችን ተደራሽ ለማድረግ ከሀገር ውስጥ የፋይናንስ ተቋማት ጋር ያለውን አጋርነት እያጠናከረ ይገኛል።
በዚሁ መሰረት ዛሬ የተደረሰው ስምምነት ኮርፖሬሽኑ ለሚያከናውናቸው ሰፊ የቤት ልማት ፕሮጀክቶች የሚውል የፋይናንስ አቅርቦት ማመቻቸትን የሚያካትት ሲሆን፥ ሁለቱ ተቋማት በሌሎች ስትራቴጂካዊ የኢንቨስትመንት መስኮች ላይ በቅንጅት ለመስራት ተስማምተዋል።
በስምምነት ስነ-ስርዓቱ ላይ የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ረሻድ ከማል፣ የሲንቄ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ ንዋይ መገርሣ እና የሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
በወቅቱም የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ረሻድ ከማል እንደገለጹት፤ ይህ ስምምነት ኮርፖሬሽኑ የጀመራቸውን ግዙፍ የቤት ልማት ፕሮጀክቶች በላቀ የፋይናንስ አቅም ለመደገፍ እና የተቋሙን ተወዳዳሪነት ይበልጥ ለማሳደግ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል።
#የፌደራልቤቶችኮርፖሬሽን #ሲንቄባንክ #የቤትልማት #ኢንቨስትመንት #ፋይናንስ #ባንክ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን እያከናወናቸው ያሉትን የቤት ልማትና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎች ይበልጥ ለማጠናከር እንዲሁም የፋይናንስ አቅሙን ለማሳደግ የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ከሲንቄ ባንክ ጋር ተፈራርሟል።
ኮርፖሬሽኑ በሀገሪቱ የኢኮኖሚና ማህበራዊ እድገት ላይ እያበረከተ ያለውን በጎ አስተዋጽኦ ለማስፋት እና ዘመናዊ የቤት ልማት ስራዎችን ተደራሽ ለማድረግ ከሀገር ውስጥ የፋይናንስ ተቋማት ጋር ያለውን አጋርነት እያጠናከረ ይገኛል።
በዚሁ መሰረት ዛሬ የተደረሰው ስምምነት ኮርፖሬሽኑ ለሚያከናውናቸው ሰፊ የቤት ልማት ፕሮጀክቶች የሚውል የፋይናንስ አቅርቦት ማመቻቸትን የሚያካትት ሲሆን፥ ሁለቱ ተቋማት በሌሎች ስትራቴጂካዊ የኢንቨስትመንት መስኮች ላይ በቅንጅት ለመስራት ተስማምተዋል።
በስምምነት ስነ-ስርዓቱ ላይ የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ረሻድ ከማል፣ የሲንቄ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ ንዋይ መገርሣ እና የሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
በወቅቱም የኮርፖሬሽኑ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ረሻድ ከማል እንደገለጹት፤ ይህ ስምምነት ኮርፖሬሽኑ የጀመራቸውን ግዙፍ የቤት ልማት ፕሮጀክቶች በላቀ የፋይናንስ አቅም ለመደገፍ እና የተቋሙን ተወዳዳሪነት ይበልጥ ለማሳደግ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል።
#የፌደራልቤቶችኮርፖሬሽን #ሲንቄባንክ #የቤትልማት #ኢንቨስትመንት #ፋይናንስ #ባንክ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
1 month ago
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በደቡብ ሱዳን የቤት ግንባታ ለማከናወን ስምምነት ተፈራረመ
#ethiopia | የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በደቡብ ሱዳን ጁባ ከተማ በቤት ልማት ዘርፍ ለመሰማራት የሚያስችለውን ታሪካዊ የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል።
ይህ ስምምነት የተደረገው በኢትዮጵያ እና በደቡብ ሱዳን መሪዎች መካከል የተደረሰውን የጋራ ልማት ትብብር መነሻ በማድረግ ሲሆን በኮርፖሬሽኑ እና በደቡብ ሱዳን ማዕከላዊ ኢኳቶሪያል ግዛት መካከል የተፈጸመ ነው።
ስምምነቱን የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ረሻድ ከማል እና የማዕከላዊ ኢኳቶሪያ ግዛት አስተዳዳሪ ሚስተር ኢማኑኤል አዲል በጁባ ከተማ በጋራ ፈርመዋል።
ውሉ ኮርፖሬሽኑ ያለውን የቴክኒክ ብቃት እና የዳበረ ልምድ ተጠቅሞ በጁባ ዘመናዊ መኖሪያዎችን፣ የንግድ ማዕከላትንና የመንግሥት ቢሮዎችን እንዲገነባ ዕድል ይሰጣል።
ዶክተር ረሻድ ከማል እንደገለጹት ኮርፖሬሽኑ በምሥራቅ አፍሪካና በመላው አህጉሪቱ ተወዳዳሪ ሆኖ ለመቅረብ ባቀደው መሠረት ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ተሸጋግሯል።
የማዕከላዊ ኢኳቶሪያ ግዛት አስተዳዳሪ ሚስተር ኢማኑኤል አዲል በበኩላቸው የኢትዮጵያ የከተሞች ዕድገትና የቤት ልማት ተሞክሮ ለአፍሪካውያን አርአያ መሆኑን ጠቅሰው ይህን ተሞክሮ በጁባ ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።
ይህ ትብብር የሁለቱን አገራት የኢኮኖሚ ትስስር ከማጠናከሩ ባሻገር በዘርፉ ለተሰማሩ ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ሥልጠና ለመስጠት ያስችላል።
የስምምነቱን አፈጻጸም የሚከታተልና ዝርዝር የፕሮጀክት ሰነዶችን የሚያዘጋጅ የጋራ ቴክኒክ ኮሚቴ እንዲቋቋምም መግባባት ላይ ተደርሷል።
#ደቡብሱዳን #ቤትልማት #ኮንስትራክሽን #ኢኮኖሚ #አፍሪካ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በደቡብ ሱዳን ጁባ ከተማ በቤት ልማት ዘርፍ ለመሰማራት የሚያስችለውን ታሪካዊ የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል።
ይህ ስምምነት የተደረገው በኢትዮጵያ እና በደቡብ ሱዳን መሪዎች መካከል የተደረሰውን የጋራ ልማት ትብብር መነሻ በማድረግ ሲሆን በኮርፖሬሽኑ እና በደቡብ ሱዳን ማዕከላዊ ኢኳቶሪያል ግዛት መካከል የተፈጸመ ነው።
ስምምነቱን የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ረሻድ ከማል እና የማዕከላዊ ኢኳቶሪያ ግዛት አስተዳዳሪ ሚስተር ኢማኑኤል አዲል በጁባ ከተማ በጋራ ፈርመዋል።
ውሉ ኮርፖሬሽኑ ያለውን የቴክኒክ ብቃት እና የዳበረ ልምድ ተጠቅሞ በጁባ ዘመናዊ መኖሪያዎችን፣ የንግድ ማዕከላትንና የመንግሥት ቢሮዎችን እንዲገነባ ዕድል ይሰጣል።
ዶክተር ረሻድ ከማል እንደገለጹት ኮርፖሬሽኑ በምሥራቅ አፍሪካና በመላው አህጉሪቱ ተወዳዳሪ ሆኖ ለመቅረብ ባቀደው መሠረት ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ተሸጋግሯል።
የማዕከላዊ ኢኳቶሪያ ግዛት አስተዳዳሪ ሚስተር ኢማኑኤል አዲል በበኩላቸው የኢትዮጵያ የከተሞች ዕድገትና የቤት ልማት ተሞክሮ ለአፍሪካውያን አርአያ መሆኑን ጠቅሰው ይህን ተሞክሮ በጁባ ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።
ይህ ትብብር የሁለቱን አገራት የኢኮኖሚ ትስስር ከማጠናከሩ ባሻገር በዘርፉ ለተሰማሩ ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ሥልጠና ለመስጠት ያስችላል።
የስምምነቱን አፈጻጸም የሚከታተልና ዝርዝር የፕሮጀክት ሰነዶችን የሚያዘጋጅ የጋራ ቴክኒክ ኮሚቴ እንዲቋቋምም መግባባት ላይ ተደርሷል።
#ደቡብሱዳን #ቤትልማት #ኮንስትራክሽን #ኢኮኖሚ #አፍሪካ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 months ago
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የወርቅ ኢዮቤልዩ ተጠናቀቀ፤
የቤት አቅርቦትን በዘላቂነት ለመፍታት ቃል ተገባ
#ethiopia | ላለፉት ሦስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ምስረታ 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል ዛሬ በማጠቃለያ መድረክና ዕውቅና በመስጠት ተጠናቋል።
በኮርፖሬሽኑ የተገነቡ አዳዲስ ሕንጻዎች የተመረቁ ሲሆን፣ የተቋሙን የሪፎርም ስኬት የሚያሳይ ኤግዚቢሽን ለዕይታ ክፍት ሆኖ ቆይቷል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚው ረሻድ ከማል (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ በቀጣይ ዓመታት የቤት አቅርቦት ፍላጎትን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችሉ ሰፋፊ ዕቅዶች ተይዘዋል።
ዕውቅና፦ ለተቋሙ ግማሽ ክፍለ ዘመን ጉዞና ለተመዘገቡ ስኬቶች አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ልዩ ዕውቅና ተሰጥቷል።
ዶ/ር ረሻድ ተቋሙ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ያከናወነው የሪፎርም ሥራ ውጤታማ መሆኑን ጠቁመው፣ የቤት ፍላጎት የሰው ልጅ መሠረታዊ መብት በመሆኑ ባለድርሻ አካላት ከኮርፖሬሽኑ ጋር በቅንጅት እንዲሠሩ ጥሪ አቅርበዋል።
#getu #federalhousingcorporation #goldenjubilee #housingethiopia #drreshadkemal #realestateethiopia #urbandevelopment #addisababa #ethiopianews #የፌዴራልቤቶችኮርፖሬሽን #ወርቅኢዮቤልዩ #ቤትልማት #ሪልስቴት #አዲስአበባ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
የቤት አቅርቦትን በዘላቂነት ለመፍታት ቃል ተገባ
#ethiopia | ላለፉት ሦስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ምስረታ 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓል ዛሬ በማጠቃለያ መድረክና ዕውቅና በመስጠት ተጠናቋል።
በኮርፖሬሽኑ የተገነቡ አዳዲስ ሕንጻዎች የተመረቁ ሲሆን፣ የተቋሙን የሪፎርም ስኬት የሚያሳይ ኤግዚቢሽን ለዕይታ ክፍት ሆኖ ቆይቷል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚው ረሻድ ከማል (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ በቀጣይ ዓመታት የቤት አቅርቦት ፍላጎትን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችሉ ሰፋፊ ዕቅዶች ተይዘዋል።
ዕውቅና፦ ለተቋሙ ግማሽ ክፍለ ዘመን ጉዞና ለተመዘገቡ ስኬቶች አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ልዩ ዕውቅና ተሰጥቷል።
ዶ/ር ረሻድ ተቋሙ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ያከናወነው የሪፎርም ሥራ ውጤታማ መሆኑን ጠቁመው፣ የቤት ፍላጎት የሰው ልጅ መሠረታዊ መብት በመሆኑ ባለድርሻ አካላት ከኮርፖሬሽኑ ጋር በቅንጅት እንዲሠሩ ጥሪ አቅርበዋል።
#getu #federalhousingcorporation #goldenjubilee #housingethiopia #drreshadkemal #realestateethiopia #urbandevelopment #addisababa #ethiopianews #የፌዴራልቤቶችኮርፖሬሽን #ወርቅኢዮቤልዩ #ቤትልማት #ሪልስቴት #አዲስአበባ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
Comments