8 months ago
30ኛው የምስራቅ አፍሪካ የህግ ማህበረሰብ ጉባኤና ጥናታዊ ኮንፈረንስ በቀን 17/03/2018 እለት በድምቀት ተጀመረ ፤
* በጉባኤው ከ 800 በላይ የተለያዩ ሀገር ተወካዮች እየተሳተፉ ይገኛሉ ፤
#ethiopia | 30ኛው የምስራቅ አፍሪካ የህግ ማህበረሰብ ጉባኤና ጥናታዊ ኮንፈረንስ ትናንት ህዳር 17 ቀን 2018ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ በይፋ ሲከፈት የአፍሪካ ጠበቆች ማህበራት ህብረት PALU እና የኢትዮጵያ ጠበቆች ማህበር ፕሬዚደንት አቶ #ቴዎድሮስ ጌታቸው የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት ካስተላለፉ በኃላ የመክፈቻ ንግግራቸውን አቅርበዋል::
በንግግራቸውም "በአህጉራችን አፍሪካ እየገጠሙ ያሉ ከህግ የበላይነት መሸርሸር ጋር የህግ ባለሙያዎች ሊኖራቸው ስለሚገባው ሚና፤ የህግ ሙያ አስተዳደር በሀገራቱ መካከል ስለሚገኝበት አንፃራዊ ሁኔታ ፤ እንዲሁም በፍጥነት እየተለወጠ ላለው የህግ አገልግሎት ባህሪና አዳዲስ ተግዳሮቶች ላይ አስፈላጊ ምላሽ፤ የእፍሪካ መንግስታት የእዳ መጠን መጨመር በአግባቡ የተነደፉ ስልቶች እንደሚያስፈልጋቸው" አውስተዋል::
በመቀጠል ንግግራቸውን ያቀረቡት የምስራቅ አፍሪካ የህግ ማህበረሰብ ፕሬዚደንት ሚር #ራማዳን አቡባከር ሲሆኑ ለተደረገላቸው የተለየ አቀባበል እና የተቀናጀና ያማረ መስተንግድዎ በህግ ማህበረሰቡ ስም ይፋዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል::
በመቀጠል የእለቱን መልእክቶች ያስተላለፉት የኮመን ዌልዝ ሀገራት ረዳት ዋና ፀሃፊ የተከበሩ ፕሮፌሰር #ሉዊስ ፍራንቼሺ ሲሆኑ; ከእርሳቸው በመቀጠል የ Safari Com Group ዋና ስራ አስፈፃሚ ሚር #ዊም ቫንሄልፑቴ ናቸው::
ከዚህ በመቀጠል አጠቃላይ ተሳታፊዎች በ 3 በመከፈል በመረጧቸው ዘርፎች በአለም አቀፍ ባለሙያዎች የሚቀርቡ ፓነሎችን እየተካፈሉ ቀጥለዋል::
በርካታ ኢትዮጵያውያን የህግ ባለሙያዎች ማህበራቸው ባመቻቸው እድል በመጠቀም በሰልጣኝነት እንዲሁም በፅሁፍ አቅራቢነት እየተሳተፉ ይገኛሉ::
ጉባኤው እየቀጠለ የሚገኝ ሲሆን ተከታታይ መረጃዎችን እናቀርባለን::
መረጃውን #share #like በማድረግ እንድታጋሩልን እንጠይቃለን::
የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር
ህዳር 18 ቀን 2018ዓ.ም
አዲስ አበባ፤
* በጉባኤው ከ 800 በላይ የተለያዩ ሀገር ተወካዮች እየተሳተፉ ይገኛሉ ፤
#ethiopia | 30ኛው የምስራቅ አፍሪካ የህግ ማህበረሰብ ጉባኤና ጥናታዊ ኮንፈረንስ ትናንት ህዳር 17 ቀን 2018ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ በይፋ ሲከፈት የአፍሪካ ጠበቆች ማህበራት ህብረት PALU እና የኢትዮጵያ ጠበቆች ማህበር ፕሬዚደንት አቶ #ቴዎድሮስ ጌታቸው የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት ካስተላለፉ በኃላ የመክፈቻ ንግግራቸውን አቅርበዋል::
በንግግራቸውም "በአህጉራችን አፍሪካ እየገጠሙ ያሉ ከህግ የበላይነት መሸርሸር ጋር የህግ ባለሙያዎች ሊኖራቸው ስለሚገባው ሚና፤ የህግ ሙያ አስተዳደር በሀገራቱ መካከል ስለሚገኝበት አንፃራዊ ሁኔታ ፤ እንዲሁም በፍጥነት እየተለወጠ ላለው የህግ አገልግሎት ባህሪና አዳዲስ ተግዳሮቶች ላይ አስፈላጊ ምላሽ፤ የእፍሪካ መንግስታት የእዳ መጠን መጨመር በአግባቡ የተነደፉ ስልቶች እንደሚያስፈልጋቸው" አውስተዋል::
በመቀጠል ንግግራቸውን ያቀረቡት የምስራቅ አፍሪካ የህግ ማህበረሰብ ፕሬዚደንት ሚር #ራማዳን አቡባከር ሲሆኑ ለተደረገላቸው የተለየ አቀባበል እና የተቀናጀና ያማረ መስተንግድዎ በህግ ማህበረሰቡ ስም ይፋዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል::
በመቀጠል የእለቱን መልእክቶች ያስተላለፉት የኮመን ዌልዝ ሀገራት ረዳት ዋና ፀሃፊ የተከበሩ ፕሮፌሰር #ሉዊስ ፍራንቼሺ ሲሆኑ; ከእርሳቸው በመቀጠል የ Safari Com Group ዋና ስራ አስፈፃሚ ሚር #ዊም ቫንሄልፑቴ ናቸው::
ከዚህ በመቀጠል አጠቃላይ ተሳታፊዎች በ 3 በመከፈል በመረጧቸው ዘርፎች በአለም አቀፍ ባለሙያዎች የሚቀርቡ ፓነሎችን እየተካፈሉ ቀጥለዋል::
በርካታ ኢትዮጵያውያን የህግ ባለሙያዎች ማህበራቸው ባመቻቸው እድል በመጠቀም በሰልጣኝነት እንዲሁም በፅሁፍ አቅራቢነት እየተሳተፉ ይገኛሉ::
ጉባኤው እየቀጠለ የሚገኝ ሲሆን ተከታታይ መረጃዎችን እናቀርባለን::
መረጃውን #share #like በማድረግ እንድታጋሩልን እንጠይቃለን::
የኢትዮጵያ ፌደራል ጠበቆች ማህበር
ህዳር 18 ቀን 2018ዓ.ም
አዲስ አበባ፤
Comments