ሁለት ሚሊየን ብር የሚገመት የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተበረከተ
#ethiopia | በቂሊንጦ ኢንዱስትሪያል ፓርክ ግቢ ህጻናትና ታዳጊዎች ላይ በርትቶ እየሰራ የሚገኘው ዳን ኢነርጂ በዛሬው ዕለት ነሀሴ 24 ቀን 2017 ዓ.ም በአርት፣ በኮዲንግ እና መሠረታዊ የኮምፒተር ስልጠና ፣ ለሶስት ወራት የተማሩ ተማሪዎችን በሚያሥመርቅበት መርሐግብር በክብር እንግድነት የተገኘው አቶ ምረትአብ ሙሉጌታ ሁለት ሚሊየን ብር የሚያወጣ ከቦርሳ ጀምሮ ሙሉ የትምህርት መማሪያ ቁሳቁስ ለ300 ተማሪዎች አስረከበ።
በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የአቬሽን ባለሙያው አቶ ዮናታን መንክር ፣ የባቡልኸይር መሥራችና ዋና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሀናን መሀመድ ፣ አቶ ምረትአብ ሙልጌታ ለተማሪዎች ሀገርን ስለ መውደድና ታዳጊዎቹ ነገ ለሀገራቸውና ለወገናቸው የሚጠቅም ስራን ይሰሩ ዘንድ የሚያነቃቃ ትልቅ ትምህርት አዘል መልዕክቶቻቸውን አስተላልፈዋል።
የዳን ኢነርጂ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳንኤል ሀይሉ ለሰልጣኞቻቸው አቶ ምረትአብ ላበረከቱት ስጦታና ሽልማት ከፍተኛ ምስጋና አቅርበው ላለፉት 8 አመት በሺህ ለሚቆጠሩ ወጣቶችና ታዳጊዎች ነጻ የኮዲንግ ስልጠና ሲሰጡ መቆየታቸውን ገልጸው ለተማሪዎቹ የተደረገው ሽልማት አበረታች በመሆኑ ተማሪዎቹ በ2018 የትምህርት ዘመን እንዲጠነክሩ አሳስበዋል።
በመጨረሻም ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ከአቶ ምረትአብ ሙሉጌታ የ120 ሺ ብር የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋለ።
#ethiopia | በቂሊንጦ ኢንዱስትሪያል ፓርክ ግቢ ህጻናትና ታዳጊዎች ላይ በርትቶ እየሰራ የሚገኘው ዳን ኢነርጂ በዛሬው ዕለት ነሀሴ 24 ቀን 2017 ዓ.ም በአርት፣ በኮዲንግ እና መሠረታዊ የኮምፒተር ስልጠና ፣ ለሶስት ወራት የተማሩ ተማሪዎችን በሚያሥመርቅበት መርሐግብር በክብር እንግድነት የተገኘው አቶ ምረትአብ ሙሉጌታ ሁለት ሚሊየን ብር የሚያወጣ ከቦርሳ ጀምሮ ሙሉ የትምህርት መማሪያ ቁሳቁስ ለ300 ተማሪዎች አስረከበ።
በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የአቬሽን ባለሙያው አቶ ዮናታን መንክር ፣ የባቡልኸይር መሥራችና ዋና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሀናን መሀመድ ፣ አቶ ምረትአብ ሙልጌታ ለተማሪዎች ሀገርን ስለ መውደድና ታዳጊዎቹ ነገ ለሀገራቸውና ለወገናቸው የሚጠቅም ስራን ይሰሩ ዘንድ የሚያነቃቃ ትልቅ ትምህርት አዘል መልዕክቶቻቸውን አስተላልፈዋል።
የዳን ኢነርጂ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዳንኤል ሀይሉ ለሰልጣኞቻቸው አቶ ምረትአብ ላበረከቱት ስጦታና ሽልማት ከፍተኛ ምስጋና አቅርበው ላለፉት 8 አመት በሺህ ለሚቆጠሩ ወጣቶችና ታዳጊዎች ነጻ የኮዲንግ ስልጠና ሲሰጡ መቆየታቸውን ገልጸው ለተማሪዎቹ የተደረገው ሽልማት አበረታች በመሆኑ ተማሪዎቹ በ2018 የትምህርት ዘመን እንዲጠነክሩ አሳስበዋል።
በመጨረሻም ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ከአቶ ምረትአብ ሙሉጌታ የ120 ሺ ብር የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋለ።
11 months ago