የሕግ የበላይነት ይከበር!!
#ethiopia | አንፃራዊ የዴሞክራሲ ሥርዓት በሰፈነባቸው ሀገራት የመገናኛ ብዙኃን ዐራተኛ የመንግሥት አካል ተደርገው ይወሰዳሉ ይህንንም ተግባራቸውን የሚወጡት መንግሥትን ተጠያቂ በማድረግ እና በዜጎች ላይ የሚፈፀሙ ሕገወጥ ተግባራትን በማጋለጥ ጭምር ነው።
በሀገራችን ግን የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን በቅጡ ባለመወጣታቸው እና አለአግባብ በሕግ ከተሰጣቸው መብት በላይ በመንቀሳቀሳቸው በታሪካችን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን ለማንበር እና መገናኛ ብዙኃን በነፃነት የዐራተኛ መንግሥትነት ሚናቸውን እንዲወጡ ለማድረግ አልቻልንም።
አለአግባብ ከኃላፊነታቸው በላይ ከሚንቀሳቀሱ ወይም ሕግን ከሚጥሱ እና ይህንን የዴሞክራሲ ሥርዓት ከሚያቀጭጩት መካከል የመንግሥትን ሥልጣን የያዙ አካላት ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መገንባት ወሳኝ የሆኑ የመገናኛ ብዙኃንን፣ ሐሣባቸውን በዐደባባይ የሚገልፁ ግለሰቦችን እና ፖለቲከኞችን ከሕግ አግባብ ውጪ በተለያየ መንገድ ማዋከብ ዋናው ነው።
ባለፉት ዓመታት ይህ ዓይነት ተግባር በተደጋጋሚ ሲፈጸም ተመልክተናል፤ ባለፉት ጥቂት ወራትም ይኸው ተጠናክሮ ከመቀጠሉም በላይ ዜጎች የፀጥታ አካል ነን በሚሉ ግለሰቦች አንዳንዴም በማን እንደታፈኑ እና የት እንደታሰሩ እንኳን የማይታወቅበት ሁነት በተደጋጋሚ ሲያጋጥም እየታዘብን ነው።
በመንግሥት በኩልም በተደጋጋሚ ያለአግባብ ያሠርኩት ጋዜጠኛም ሆነ ዜጋ የለም የሚል ምላሽ ሲሰጥም ተመልክተናል። የዚህ ምላሽ አሳሳቢነት አንድም መንግሥት ድርጊቱን እየፈፀመ ነገር ግን እየደበቀው ከሆነ መንግሥት ሕገወጥ ተግባራትን ሆነ ብሎ እየፈፀመ ነው የሚያስብል ሲሆን በሌላ መልኩ እነዚህ ተግባራት የሚፈፀሙት ከመንግሥት እውቅና ውጪ በሌሎች በተደራጁ አካላት ከሆነ መንግሥት በቅጡ የሀገሪቱን ፀጥታ እና የዜጎችን ደኽንነት እያስጠበቀ አይደለም የሚል ስጋት ዜጎች ላይ እንዲፈጠር ያደርጋል።
እነዚህ ሁነቶች በዋነኝነት የሚያመሩት ዜጎች ጠባቂ የለኝም ከሚል ስጋት በገዛ እጃቸው ደኽንነታቸውን ለማስከበር መሞከር ሲሆን በተጨማሪም የዜጎችን የዕለት ተዕለት ሕይወት የሚፈታተኑ ሕገወጦች እንዲበራከቱ በማድረግ የሀገሪቱን የፀጥታ ሁኔታ እና የዜጎች ደኽንነት ከፍተኛ አደጋ ውስጥ የሚከት አስፈሪ ሁነት ነው።
በአሀዱ ራዲዮ ቅዳሜ ገበያ ፕሮግራም ላይ የሚሠራው አንጋፋው ጋዜጠኛ አብዱልሰመድ መሐመድ ከነሐሴ 5/2017 ዓ.ም. ጀምሮ ደብዛው እንደጠፋ እና ባለፈው ሀሙስ የሚሰራበት ቢሮን ለማስፈተሽ ከፖሊስ ጋር መምጣቱን የሚሠራበት ተቋም ከትላንት በስቲያ ነሐሴ 09/2017 ዓ.ም. አሳውቋል።
በትናንትናው ዕለት ነሐሴ 10/2017 ዓ.ም. ደግሞ የሪፖርተር ጋዜጠኛ የሆነው ዮናስ አማረ ጭምብል በለበሱ ግለሰቦች መወሰዱን ተቋሙ በይፋ አሳውቋል።
ከዚህ ጋር ተያይዞ መንግሥትን የመሠረተው ገዢው ፓርቲ በቅርቡ ማለትም ነሐሴ 02/2017 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ እፈታቸዋለሁ ካላቸው ችግሮች መካከል በየደረጃው የሚነሡ የሕዝብ የመልካም አስተዳደር፣ የፍትሕና የኢኮኖሚ ጥያቄዎችን በኢትዮጵያ ዐቅም ልክ በየደረጃው ለመመለስ እና ተገቢውንና እውነተኛውን መረጃ ለሕዝብ በየጊዜው ለመስጠትና ሐሰተኛ መረጃዎችን ማጋለጥ ነው ቢልም በማግስቱ እንዲህ ዓይነት ተግባር መታየቱ የተገባው ቃል ከልብ አለመሆኑን በግልፅ የሚያሳይ ነው።
ኢዜማ ይህ ነገር ትኩረት እንዲሠጠው እያሳሰበ ይህንን የሚያደርገው የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ሳይሆን መንግሥት ሀገሪቱ አሁን ካለችበት ወደከፋ ችግር ውስጥ ከመግባቷ በፊት ትኩረት ሰጥቶ ማረም እንዲችል ለመወትወት መሆኑን እየገለጽን ታፍነው የተሰወሩ ጋዜጠኞች ያሉበትን ሁኔታ በግልፅ እንዲያሳውቅ በመጠየቅ ጭምር ነው።
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ ( #ኢዜማ )
#ethiopia | አንፃራዊ የዴሞክራሲ ሥርዓት በሰፈነባቸው ሀገራት የመገናኛ ብዙኃን ዐራተኛ የመንግሥት አካል ተደርገው ይወሰዳሉ ይህንንም ተግባራቸውን የሚወጡት መንግሥትን ተጠያቂ በማድረግ እና በዜጎች ላይ የሚፈፀሙ ሕገወጥ ተግባራትን በማጋለጥ ጭምር ነው።
በሀገራችን ግን የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን በቅጡ ባለመወጣታቸው እና አለአግባብ በሕግ ከተሰጣቸው መብት በላይ በመንቀሳቀሳቸው በታሪካችን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን ለማንበር እና መገናኛ ብዙኃን በነፃነት የዐራተኛ መንግሥትነት ሚናቸውን እንዲወጡ ለማድረግ አልቻልንም።
አለአግባብ ከኃላፊነታቸው በላይ ከሚንቀሳቀሱ ወይም ሕግን ከሚጥሱ እና ይህንን የዴሞክራሲ ሥርዓት ከሚያቀጭጩት መካከል የመንግሥትን ሥልጣን የያዙ አካላት ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት መገንባት ወሳኝ የሆኑ የመገናኛ ብዙኃንን፣ ሐሣባቸውን በዐደባባይ የሚገልፁ ግለሰቦችን እና ፖለቲከኞችን ከሕግ አግባብ ውጪ በተለያየ መንገድ ማዋከብ ዋናው ነው።
ባለፉት ዓመታት ይህ ዓይነት ተግባር በተደጋጋሚ ሲፈጸም ተመልክተናል፤ ባለፉት ጥቂት ወራትም ይኸው ተጠናክሮ ከመቀጠሉም በላይ ዜጎች የፀጥታ አካል ነን በሚሉ ግለሰቦች አንዳንዴም በማን እንደታፈኑ እና የት እንደታሰሩ እንኳን የማይታወቅበት ሁነት በተደጋጋሚ ሲያጋጥም እየታዘብን ነው።
በመንግሥት በኩልም በተደጋጋሚ ያለአግባብ ያሠርኩት ጋዜጠኛም ሆነ ዜጋ የለም የሚል ምላሽ ሲሰጥም ተመልክተናል። የዚህ ምላሽ አሳሳቢነት አንድም መንግሥት ድርጊቱን እየፈፀመ ነገር ግን እየደበቀው ከሆነ መንግሥት ሕገወጥ ተግባራትን ሆነ ብሎ እየፈፀመ ነው የሚያስብል ሲሆን በሌላ መልኩ እነዚህ ተግባራት የሚፈፀሙት ከመንግሥት እውቅና ውጪ በሌሎች በተደራጁ አካላት ከሆነ መንግሥት በቅጡ የሀገሪቱን ፀጥታ እና የዜጎችን ደኽንነት እያስጠበቀ አይደለም የሚል ስጋት ዜጎች ላይ እንዲፈጠር ያደርጋል።
እነዚህ ሁነቶች በዋነኝነት የሚያመሩት ዜጎች ጠባቂ የለኝም ከሚል ስጋት በገዛ እጃቸው ደኽንነታቸውን ለማስከበር መሞከር ሲሆን በተጨማሪም የዜጎችን የዕለት ተዕለት ሕይወት የሚፈታተኑ ሕገወጦች እንዲበራከቱ በማድረግ የሀገሪቱን የፀጥታ ሁኔታ እና የዜጎች ደኽንነት ከፍተኛ አደጋ ውስጥ የሚከት አስፈሪ ሁነት ነው።
በአሀዱ ራዲዮ ቅዳሜ ገበያ ፕሮግራም ላይ የሚሠራው አንጋፋው ጋዜጠኛ አብዱልሰመድ መሐመድ ከነሐሴ 5/2017 ዓ.ም. ጀምሮ ደብዛው እንደጠፋ እና ባለፈው ሀሙስ የሚሰራበት ቢሮን ለማስፈተሽ ከፖሊስ ጋር መምጣቱን የሚሠራበት ተቋም ከትላንት በስቲያ ነሐሴ 09/2017 ዓ.ም. አሳውቋል።
በትናንትናው ዕለት ነሐሴ 10/2017 ዓ.ም. ደግሞ የሪፖርተር ጋዜጠኛ የሆነው ዮናስ አማረ ጭምብል በለበሱ ግለሰቦች መወሰዱን ተቋሙ በይፋ አሳውቋል።
ከዚህ ጋር ተያይዞ መንግሥትን የመሠረተው ገዢው ፓርቲ በቅርቡ ማለትም ነሐሴ 02/2017 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ እፈታቸዋለሁ ካላቸው ችግሮች መካከል በየደረጃው የሚነሡ የሕዝብ የመልካም አስተዳደር፣ የፍትሕና የኢኮኖሚ ጥያቄዎችን በኢትዮጵያ ዐቅም ልክ በየደረጃው ለመመለስ እና ተገቢውንና እውነተኛውን መረጃ ለሕዝብ በየጊዜው ለመስጠትና ሐሰተኛ መረጃዎችን ማጋለጥ ነው ቢልም በማግስቱ እንዲህ ዓይነት ተግባር መታየቱ የተገባው ቃል ከልብ አለመሆኑን በግልፅ የሚያሳይ ነው።
ኢዜማ ይህ ነገር ትኩረት እንዲሠጠው እያሳሰበ ይህንን የሚያደርገው የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ሳይሆን መንግሥት ሀገሪቱ አሁን ካለችበት ወደከፋ ችግር ውስጥ ከመግባቷ በፊት ትኩረት ሰጥቶ ማረም እንዲችል ለመወትወት መሆኑን እየገለጽን ታፍነው የተሰወሩ ጋዜጠኞች ያሉበትን ሁኔታ በግልፅ እንዲያሳውቅ በመጠየቅ ጭምር ነው።
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ ( #ኢዜማ )
12 months ago