Logo
EBC
ስፔን ፈረንሳይን አሸንፋ ለፍፃሜ አለፈች
***************

በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የግማሽ ፍፃሜ መርኃ ግብር ስፔን ከፈረንሳይ ያደረጉት ጨዋታ፤ በስፔን 2 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቅቋል።

ለስፔን የአሸናፊነት ግቦቹን ሚኬል ኦያርዛባል 22ኛው ደቂቃ ላይ በፍፁም ቅጣት ምት እንዲሁም ፔድሮ ፖሮ በ58ኛው ደቂቃ ከመረብ አሳርፈዋል።

በዚህም በ2010 የደቡብ አፍሪካውን ዓለም ዋንጫ ያሸነፈችው ስፔን ከ16 ዓመታት በኋላ ለውድድሩ ፍፃሜ ደርሳለች።

ወደ ፍፃሜው የተሸጋገረችው ስፔን በቀጣይ ከአርጀንቲና እና እንግሊዝ አሸናፊ ጋር እሁድ የምትጫወት ይሆናል።
#worldcup2026 #fifaworldcup2026 #fifaworldcup2026 #spain #france #semifinal #football #sports #ebc

21 days ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.