ኢትዮጵያውያን ለመነጋገርና ለመደማመጥ በአንድነት መሰባሰባቸው ትልቅ ምዕራፍ ነው!
- ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ለሚያካሂደው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በመዘጋጀት፣ ለተሳታፊ ተመካካሪዎች የቅድመ ምክክር ገለጻ በአድዋ ድል መታሰቢያ እየሰጠ ነው።
የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ በመክፈቻ ንግግራቸው፣ ኢትዮጵያውያን ስለ ሀገራቸው ሰላም፣ ሀገር ግንባታ፣ ሰብዓዊ መብት፣ ማኅበራዊ ጉዳዮችና ሌሎች ወሳኝ ጉዳዮች ለመነጋገርና ለመደማመጥ በአንድነት መሰባሰባቸው በኢትዮጵያ ታሪክ ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል።
ፕሮፌሰር መስፍን አክለውም፣ ሀገሪቱ በአንድነትና በመተባበር ነፃነቷን እንዳስጠበቀች ሁሉ፣ ዛሬም በረጅም የመንግሥት ግንባታ ሂደት የተፈጠሩ አለመግባባቶችንና ቁርሾዎችን በውይይት ለመፍታት መሰባሰቧ ከችግሮች ለመውጣት ያለውን ፅኑ ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ጠቁመዋል።
በዛሬው መርሃ ግብር ኮሚሽኑ ምክክሩ በሚመራበት ስልት፣ ተሳታፊዎች በሚኖራቸው ሚና እና በምክክሩ መርሆዎች ዙሪያ ሰፊ ገለጻ ሰጥቷል። በዚህም አካታችነት፣ አሳታፊነት፣ ትብብር፣ እኩልነት፣ መልካም ግንኙነት ግንባታ፣ የጋራ አስተሳሰብን ማጎልበት እና ሰፊ ስምምነትን መፈለግ እንደ መሠረታዊ እሴቶች ቀርበዋል።
በተጨማሪም የምክክር ሂደቶች፣ የቡድን አደረጃጀት፣ የጊዜ ሰሌዳ እና የተሳታፊዎች ኃላፊነት ዙሪያ ዝርዝር ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን፣ ይህ መድረክ ወደ ሀገራዊ መግባባት ለመድረስ የሚደረገውን ሂደት በይፋ ያስጀመረ መሆኑ ተገልጿል።
#ethiopia #nationaldialogue #nationalconsensus
- ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ለሚያካሂደው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ በመዘጋጀት፣ ለተሳታፊ ተመካካሪዎች የቅድመ ምክክር ገለጻ በአድዋ ድል መታሰቢያ እየሰጠ ነው።
የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ በመክፈቻ ንግግራቸው፣ ኢትዮጵያውያን ስለ ሀገራቸው ሰላም፣ ሀገር ግንባታ፣ ሰብዓዊ መብት፣ ማኅበራዊ ጉዳዮችና ሌሎች ወሳኝ ጉዳዮች ለመነጋገርና ለመደማመጥ በአንድነት መሰባሰባቸው በኢትዮጵያ ታሪክ ትልቅ ምዕራፍ መሆኑን ገልጸዋል።
ፕሮፌሰር መስፍን አክለውም፣ ሀገሪቱ በአንድነትና በመተባበር ነፃነቷን እንዳስጠበቀች ሁሉ፣ ዛሬም በረጅም የመንግሥት ግንባታ ሂደት የተፈጠሩ አለመግባባቶችንና ቁርሾዎችን በውይይት ለመፍታት መሰባሰቧ ከችግሮች ለመውጣት ያለውን ፅኑ ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን ጠቁመዋል።
በዛሬው መርሃ ግብር ኮሚሽኑ ምክክሩ በሚመራበት ስልት፣ ተሳታፊዎች በሚኖራቸው ሚና እና በምክክሩ መርሆዎች ዙሪያ ሰፊ ገለጻ ሰጥቷል። በዚህም አካታችነት፣ አሳታፊነት፣ ትብብር፣ እኩልነት፣ መልካም ግንኙነት ግንባታ፣ የጋራ አስተሳሰብን ማጎልበት እና ሰፊ ስምምነትን መፈለግ እንደ መሠረታዊ እሴቶች ቀርበዋል።
በተጨማሪም የምክክር ሂደቶች፣ የቡድን አደረጃጀት፣ የጊዜ ሰሌዳ እና የተሳታፊዎች ኃላፊነት ዙሪያ ዝርዝር ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን፣ ይህ መድረክ ወደ ሀገራዊ መግባባት ለመድረስ የሚደረገውን ሂደት በይፋ ያስጀመረ መሆኑ ተገልጿል።
#ethiopia #nationaldialogue #nationalconsensus
29 days ago