መምህሩና ተመራቂዋ መምህርት ባለቤቱ ከኮሌጅ ምረቃ ወደ ቤት ሲመለሱ በትራፊክ አደጋ አረፉ
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልልካፋ ዞን ቢጣ ወረዳ ደጋ-ኬላ የሚኖሩት መምህር አብሪሃም ግዛው እና ባለቤቱ መምህርት ራሄል አክሊሉ በዛሬው ዕለት በደረሰ አሰቃቂ የትራፊክ አደጋ ህይወታቸው ማለፉ ከዶች ኤችዲ ሰምተናል ።
መምህርት ራሄል አክሊሉ ከትናንት ወዲያ ከቦንጋ ትምህርት ኮሌጅ በስኬት ተመርቃ የነበረ ሲሆን፣ ባለቤቷ መምህር አብሪሃም ግዛው ደስታዋን ለመካፈል በዚያ ተገኝቶ አንድ ላይ በመሆን የምረቃ ሥነ-ስርዓቱን በጋራ አክብረዋል።
ከ2 ቀናት በኋላ ደስታቸውን አጣጥመው ሳይጨርሱ፣ ከምረቃው መልስ ወደ ቤት በመጓዝ ላይ እያሉ በደረሰባቸው ድንገተኛ አደጋ ሁለቱም ህይወታቸውን ማጣታቸው ብዙሃንን አሳዝኗል።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልልካፋ ዞን ቢጣ ወረዳ ደጋ-ኬላ የሚኖሩት መምህር አብሪሃም ግዛው እና ባለቤቱ መምህርት ራሄል አክሊሉ በዛሬው ዕለት በደረሰ አሰቃቂ የትራፊክ አደጋ ህይወታቸው ማለፉ ከዶች ኤችዲ ሰምተናል ።
መምህርት ራሄል አክሊሉ ከትናንት ወዲያ ከቦንጋ ትምህርት ኮሌጅ በስኬት ተመርቃ የነበረ ሲሆን፣ ባለቤቷ መምህር አብሪሃም ግዛው ደስታዋን ለመካፈል በዚያ ተገኝቶ አንድ ላይ በመሆን የምረቃ ሥነ-ስርዓቱን በጋራ አክብረዋል።
ከ2 ቀናት በኋላ ደስታቸውን አጣጥመው ሳይጨርሱ፣ ከምረቃው መልስ ወደ ቤት በመጓዝ ላይ እያሉ በደረሰባቸው ድንገተኛ አደጋ ሁለቱም ህይወታቸውን ማጣታቸው ብዙሃንን አሳዝኗል።
1 month ago