Logo
Getu Temesgen
ታዋቂው የይዘት ፈጣሪ አቤል ብርሃኑ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የ10 ዓመት የጎልደን ቪዛ ተሸላሚ ሆነ
#ethiopia | ​ታዋቂው ኢትዮጵያዊ የይዘት ፈጣሪ አቤል ብርሃኑ (የወይኗ ልጅ) ከተባበሩት አረብ ኤምሬትስ መንግሥት የ10 ዓመት የጎልደን ቪዛ ሽልማት ማግኘቱን ይፋ አደረገ።

አቤል ይህንን ከፍተኛ ዕውቅና ያገኘው በይዘት ፈጠራ ዘርፍ ባለው ያለተቋረጠ ጉዞ ሲሆን ይህ የረጅም ጊዜ ቪዛ ወደፊት ለሚሰራቸው ዓለም አቀፍ የጉዞ ዶክመንተሪዎች እና ሌሎች ተያያዥ ሥራዎች ወርቃማ እድል እንደሆነ ገልጿል።

​ዓለምን የመዞር የልጅነት ሕልሙን እውን እያደረገ የሚገኘው አቤል፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ከሀገሩ ወጥቶ ዓለምን ማሰስ ሲጀምር የተጓዘባት ሁለተኛዋ ሀገር እንደነበረች አስታውሷል።

ለዚህ ታላቅ ስኬት መሳካት መንገዱን ላቀናለት ልዑል እግዚአብሔር ምስጋናውን ያቀረበው የይዘት ፈጣሪው ከጀርባው በመሆን ለደከሙለት፣ በማኅበራዊ ሚዲያ ሥራዎቹን ዘወትር ለሚከታተሉ አድናቂዎቹ እንዲሁም ይህንን ዕድል ለሰጠው የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ መንግሥት የላቀ ምስጋናውን አቅርቧል።

​"ሽልማቱ እና ስኬቱ የእናንተም ጭምር ነው" በማለት ደስታውን ከመላው ተከታይ ቤተሰቦቹ ጋር የተጋራው አቤል አሁንም የዓለም የማሰስ ስራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጧል።

በያፌት ገ/ህይወት

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu

2 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.