የትግራይ ክልል መምህራን ማኅበር፣ በክልሉ የመምህራን ደመወዝ ለበርካታ ወራት ባለመክፈሉ መምህራን ከነቤተሰቦቻቸው በርሃብ ምክንያት እየታመሙ፣ እየተሠቃዩ እና አልፎ አልፎም ለሞት እየተዳረጉ ይገኛሉ ሲል ዛሬ ለኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር በጻፈው ደብዳቤ ገለጸ።
ማኅበሩ፣ በፖለቲከኞች መካከል በተፈጠረ የሃሳብ ልዩነት ምክንያት የመምህራን ደመወዝ መከልከል ''የግፍ ግፍ" እና "በታሪክ የሚያስወቅስ" ተግባር ነው በማለት ኮንኗል።
የክልሉ መምህራን ደመወዛቸው እንዲከፈላቸው ከዚህ ቀደም በደብዳቤና በሠማላዊ ሠልፍ ጭምር በተደጋጋሚ መጠየቁን የጠቀሠው ማኅበሩ፣ ኾኖም ለችግሩ ምላሽ የሚሠጥ አካል አልተገኘም ብሏል።
የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር ከፌዴራሉ መንግሥትና ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር ለችግሩ መፍትሔ እንዲያፈላልግም ማኅበሩ ጠይቋል።
Seledadotio
Seledadotio
ማኅበሩ፣ በፖለቲከኞች መካከል በተፈጠረ የሃሳብ ልዩነት ምክንያት የመምህራን ደመወዝ መከልከል ''የግፍ ግፍ" እና "በታሪክ የሚያስወቅስ" ተግባር ነው በማለት ኮንኗል።
የክልሉ መምህራን ደመወዛቸው እንዲከፈላቸው ከዚህ ቀደም በደብዳቤና በሠማላዊ ሠልፍ ጭምር በተደጋጋሚ መጠየቁን የጠቀሠው ማኅበሩ፣ ኾኖም ለችግሩ ምላሽ የሚሠጥ አካል አልተገኘም ብሏል።
የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር ከፌዴራሉ መንግሥትና ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር ለችግሩ መፍትሔ እንዲያፈላልግም ማኅበሩ ጠይቋል።
Seledadotio
Seledadotio
2 months ago