አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬ በዶፒንግ ምርመራ የአራት ወር እገዳ ተጣለባት
#fastmereja | የዓለም 5,000 እና 10,000 ሜትር የቀድሞ ሻምፒዮን አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬ፣ በዶፒንግ ምርመራ ወቅት በሰውነቷ ውስጥ "ሌትሮዞል" የተባለ ንጥረ ነገር በመገኘቱ የአራት ወር እገዳ ተላልፎባታል።
እንደ አትሌቲክስ ዊክሊ ዘገባ በአትሌቷ የተገኘው ንጥረ ነገር የታዘዘላትን የህክምና ችግር ለመቆጣጠር ትጠቀምበት የነበረ መሆኑን በማስረጃ ማቅረቧን ተከትሎ፣ የዓለም አትሌቲክስ ጥብቅና ክፍል (AIU) ከረዥም ጊዜ ቅጣት ይልቅ የአራት ወር እገዳን እንዲወስን ስምምነት ላይ ተደርሷል።
የ29 ዓመቷ አትሌት ጉዳፍ፣ ይህን ተከትሎ የ2026 የውድድር ዓመትን የትራክ ውድድሮች በሙሉ እንደማትሳተፍ ተገልጿል።
የአትሌቲክስ ጥብቅና ክፍሉ ባወጣው መግለጫ፣ ጉዳፍ ምርመራው መገኘቱን አምና Case Resolution Agreement እንደፈረመች አስታውቋል።
#fastmereja | የዓለም 5,000 እና 10,000 ሜትር የቀድሞ ሻምፒዮን አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬ፣ በዶፒንግ ምርመራ ወቅት በሰውነቷ ውስጥ "ሌትሮዞል" የተባለ ንጥረ ነገር በመገኘቱ የአራት ወር እገዳ ተላልፎባታል።
እንደ አትሌቲክስ ዊክሊ ዘገባ በአትሌቷ የተገኘው ንጥረ ነገር የታዘዘላትን የህክምና ችግር ለመቆጣጠር ትጠቀምበት የነበረ መሆኑን በማስረጃ ማቅረቧን ተከትሎ፣ የዓለም አትሌቲክስ ጥብቅና ክፍል (AIU) ከረዥም ጊዜ ቅጣት ይልቅ የአራት ወር እገዳን እንዲወስን ስምምነት ላይ ተደርሷል።
የ29 ዓመቷ አትሌት ጉዳፍ፣ ይህን ተከትሎ የ2026 የውድድር ዓመትን የትራክ ውድድሮች በሙሉ እንደማትሳተፍ ተገልጿል።
የአትሌቲክስ ጥብቅና ክፍሉ ባወጣው መግለጫ፣ ጉዳፍ ምርመራው መገኘቱን አምና Case Resolution Agreement እንደፈረመች አስታውቋል።
2 months ago