አንድ ሳንቲም የበጎ አድራጎት ድርጅት በይፋ ስራ ጀመረ
#ethiopia | በከፍተኛ የህክምና ወጪ ለሚቸገሩ ወገኖች ድጋፍ ለማድረግ ዓላማ ያነገበው "አንድ ሳንቲም" የተሰኘው ሀገር በቀል የበጎ አድራጎት ድርጅት በዛሬው ዕለት ማምሻውን በግዮን ሆቴል ስነ-ስርዓት በይፋ ስራውን ጀምሯል።
ይህ የበጎ አድራጎት ድርጅት በተለይም የልብ፣ የኩላሊት እና የካንሰር ታማሚዎችን ለመርዳት በኢትዮጵያውያን ተመስርቶ በቅርቡ ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ፍቃድ መውሰዱ በመርሃግብሩ ላይ ተገልጿል።
ድርጅቱ ከህዝብ የሚሰበሰበው መዋጮ ምንም አይነት የአስተዳደር ወጪ ሳይቀነስበት 0% የአስተዳደር ወጪ መቶ በመቶ ለታለመለት የህክምና እርዳታ ብቻ የሚውል መሆኑ ተገልጿል።
የድርጅቱ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን ሹምዬ ባደረጉት ንግግር የድርጅቱን ዋና ፍልስፍና ሲያስረዱ፦
"ድርጅታችን ከውጭ ሀገር የሚጠበቅ ምንም አይነት እርዳታ አይጠይቅም። ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥና በውጭ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ድጋፍ ብቻ የሚንቀሳቀስ ነው። ይህ መርሃ-ግብር ኢትዮጵያውያን የራሳቸውን ችግር በራሳቸው አቅም መፍታት እንደሚችሉ ማሳያ ከመሆኑም በላይ፣ በራስ የመተማመን መንፈስን የሚያጎለብት ነው" ብለዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia #charity #yeandsantim #healthsupport #selfreliance #addisababa #philanthropy
#ethiopia | በከፍተኛ የህክምና ወጪ ለሚቸገሩ ወገኖች ድጋፍ ለማድረግ ዓላማ ያነገበው "አንድ ሳንቲም" የተሰኘው ሀገር በቀል የበጎ አድራጎት ድርጅት በዛሬው ዕለት ማምሻውን በግዮን ሆቴል ስነ-ስርዓት በይፋ ስራውን ጀምሯል።
ይህ የበጎ አድራጎት ድርጅት በተለይም የልብ፣ የኩላሊት እና የካንሰር ታማሚዎችን ለመርዳት በኢትዮጵያውያን ተመስርቶ በቅርቡ ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ፍቃድ መውሰዱ በመርሃግብሩ ላይ ተገልጿል።
ድርጅቱ ከህዝብ የሚሰበሰበው መዋጮ ምንም አይነት የአስተዳደር ወጪ ሳይቀነስበት 0% የአስተዳደር ወጪ መቶ በመቶ ለታለመለት የህክምና እርዳታ ብቻ የሚውል መሆኑ ተገልጿል።
የድርጅቱ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን ሹምዬ ባደረጉት ንግግር የድርጅቱን ዋና ፍልስፍና ሲያስረዱ፦
"ድርጅታችን ከውጭ ሀገር የሚጠበቅ ምንም አይነት እርዳታ አይጠይቅም። ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥና በውጭ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ድጋፍ ብቻ የሚንቀሳቀስ ነው። ይህ መርሃ-ግብር ኢትዮጵያውያን የራሳቸውን ችግር በራሳቸው አቅም መፍታት እንደሚችሉ ማሳያ ከመሆኑም በላይ፣ በራስ የመተማመን መንፈስን የሚያጎለብት ነው" ብለዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia #charity #yeandsantim #healthsupport #selfreliance #addisababa #philanthropy
3 months ago