Logo
FIDEL POST NEWS
​በሊባኖስ ውስጥ ባለፉት 10 ቀናት ብቻ ከ800,000 በላይ ሰዎች በእስራኤል ጥቃት ምክንያት ከቀያቸው መፈናቀላቸውን የኖርዌይ የስደተኞች ምክር ቤት አስታወቀ

ይህም የአገሪቱን አንድ ሰባተኛ ህዝብ ያካተተ ሲሆን፣ ተፈናቃዮቹ መጠለያ በማጣት ለከፍተኛ ችግር ተጋልጠዋል።

​የሊባኖስ ጤና ሚኒስቴር እንደገለጸው፣ በጥቃቱ የ103 ህፃናትን ህይወት ጨምሮ ከ700 በላይ ሰዎች ተገድለዋል።

እስራኤል ጥቃቱን ያጠናከረችው በኢራን የሚደገፈው ሄዝቦላህ በወሰደው የሮኬት ጥቃት ምላሽ እንደሆነ ብትገልጽም፣ ጥቃቱ የመኖሪያ አካባቢዎችንና ሆቴሎችን ጭምር ኢላማ ማድረጉ ተነግሯል።

​መንግስት ለ120,000 ሰዎች ብቻ መጠለያ ማቅረብ የቻለ ሲሆን፣ የተቀሩት በየመንገዱና በመኪና ውስጥ ለማደር ተገድደዋል።

ዓለም አቀፍ የረድኤት ድርጅቶች የፍላጎቱ መጨመር ካላቸው አቅም በላይ መሆኑን በመግለጽ የሰብአዊ ቀውስ ሊከሰት እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።
5 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.