Logo
Getu Temesgen
የኢትዮጵያ ስፔሻል ኦሎምፒክ ሀገር አቀፍ ወድድር በድምቀት ስፖርታዊ ውድድር በድምቀት ተከፈተ

‎​#ethiopia | 11ኛው የዓለም የዳውን ሲንድሮም ቀን በኢትዮጵያ “Let me win, but if I cannot win, let me be brave in the attempt" ” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀዉ ስፖርታዊ ዉድድር በዛሬዉ እለት በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ በይፋ ተከፍቷል።

‎​በዛሬዉ የመክፈቻ ስነ-ስርአት ላይ በባህልና ስፖርት ሚንስትር የስፖርትና ልማት ዘርፍ ሚኒስቴር ዲኤታ ክቡር መኪዩ መሀመድ :
‎በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር በስፖርት ማህበራት ምዝገባ ፣ ድጋፍ እና ቁጥጥር መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዳንኤል ዳኜ : የኢትዮጵያ ስፔሻል ኦሎምፒክ ፕሬዝዳንት የሆኑት አቶ ግርማ ዘውድ: የኢትዮጵያ ስፔሻል ኦሎምፒክ ብሄራዊ ፅህፈት ቤት ሃለፊ የሆኑት ወ/ሮ ትርስተወልድ አበባ አየሁን ጨምሮ ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች እና ከተለያዩ ክልሎች ተሳታፊ ስፖርተኞችና አመራሮች በተገኙበት ወድድሩ በድምቀት ተከፍቷል።

‎ስፔሻል ኦሊምፒክስ ኢትዮጵያ ከ“ፍቅር የኢትዮጵያ የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ብሔራዊ ማኅበር” ጋር በመተባበር የተዘጋጀዉ ይህ ሀገር አቀፍ ጨዋታ በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ ሶስት ቀናት የሚቀጥል ይሆናል።

‎​ዉድድሩ ሁሉንም የኦሎምፒክ ስፖርት ዓይነቶች ያካተተ ሲሆን፣ ውድድሩም የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባቸውን ተወዳዳሪዎች ባማከለ ልዩ የስፖርት ሕግ መሠረት እየተከናወነ ይገኛል።

‎የፍቅር ኢትዮጵያ ማህበር የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባቸውን ልጆች አስተምሮና አሰልጥኖ በማኅበሩ ውስጥ የሥራ ቅጥር እንዲያገኙ በማድረግ ጭምር አርአያነት ያለው ሥራ እያከናወነ ይገኛል።

‎​በአሁኑ ወቅት በአፍሪካና በኢትዮጵያ የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባቸው ወገኖች ላይ የሚደርሰው መገለልና መድልዎ ከፍተኛ በመሆኑ፣ እንዲህ ያሉ ስፖርታዊ መድረኮች ግንዛቤን ለመፍጠርና ብቸኝነትን ለመቀነስ ትልቅ ፋይዳ አላቸው።

‎በዛሬዉ የመክፈቻ መርሀ-ግብር ላይ ፊልም ደራሲ፣ዳይሬክተር እንዲሁም ፕሮዲዉሰር የሆነችዉን የራስወርቅ ግርማ የስፔሻል ኦሎምፒክ በጎ ፍቃድ አምባሳደር በመሆን ተሹማለች ።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ

5 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.