በዱባይ የሚገኙ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች በጦርነት ተዛማጅ ፖስቶች ምክንያት ለእስር ሊዳረጉ እንደሚችሉ ማስጠንቀቂያ እየደረሳቸው ነው ተባለ
በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የሚገኙ ታዋቂ የሶሻል ሚዲያ አንቀሳቃሾች ከሀገሪቱ ብሄራዊ ደህንነት እና ሰላም ጋር የሚጋጩ መረጃዎችን እንዳያጋሩ ጠንካራ ማስጠንቀቂያ ተሰጣቸው።
ዱባይ ከኢራን ጋር በተያያዘ በሚሰነዘሩ የሮኬት ጥቃቶች ስጋት ውስጥ ባለችበት በዚህ ወቅት፣ የመንግስትን ስም የሚያጠፉ ወይም ሽብር የሚፈጥሩ ምስሎችንና መረጃዎችን የሚለጥፉ ግለሰቦች እስከ 77,000 ዶላር የገንዘብ መቀጫ ወይም የእስር ቅጣት ይጠብቃቸዋል።
አንዳንድ ኢንፍሉዌንሰሮች የሚወድቁ ሮኬቶችን የሚያሳዩ ቪዲዮዎችን ከለቀቁ በኋላ በህጉ ስጋት ምክንያት ወዲያውኑ ለማጥፋት ተገደዋል።
የሀገሪቱ የሳይበር ወንጀል ህግ እጅግ ጥብቅ በመሆኑ፣ ማንኛውም ስለ ጦርነቱ የሚሰጥ አስተያየት እንደ ወንጀል ሊቆጠር ይችላል። ባለስልጣናቱ ዓላማቸው ያልተረጋገጡ መረጃዎች ስርጭትን ለመቆጣጠር እና በህዝብ ላይ ድንጋጤ እንዳይፈጠር መሆኑን ገልጸዋል።
ምንጭ: The Telegraph ጋዜጣ እና Detained in Dubai የተሰኘውን የሰብአዊ መብት ድርጅት
በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የሚገኙ ታዋቂ የሶሻል ሚዲያ አንቀሳቃሾች ከሀገሪቱ ብሄራዊ ደህንነት እና ሰላም ጋር የሚጋጩ መረጃዎችን እንዳያጋሩ ጠንካራ ማስጠንቀቂያ ተሰጣቸው።
ዱባይ ከኢራን ጋር በተያያዘ በሚሰነዘሩ የሮኬት ጥቃቶች ስጋት ውስጥ ባለችበት በዚህ ወቅት፣ የመንግስትን ስም የሚያጠፉ ወይም ሽብር የሚፈጥሩ ምስሎችንና መረጃዎችን የሚለጥፉ ግለሰቦች እስከ 77,000 ዶላር የገንዘብ መቀጫ ወይም የእስር ቅጣት ይጠብቃቸዋል።
አንዳንድ ኢንፍሉዌንሰሮች የሚወድቁ ሮኬቶችን የሚያሳዩ ቪዲዮዎችን ከለቀቁ በኋላ በህጉ ስጋት ምክንያት ወዲያውኑ ለማጥፋት ተገደዋል።
የሀገሪቱ የሳይበር ወንጀል ህግ እጅግ ጥብቅ በመሆኑ፣ ማንኛውም ስለ ጦርነቱ የሚሰጥ አስተያየት እንደ ወንጀል ሊቆጠር ይችላል። ባለስልጣናቱ ዓላማቸው ያልተረጋገጡ መረጃዎች ስርጭትን ለመቆጣጠር እና በህዝብ ላይ ድንጋጤ እንዳይፈጠር መሆኑን ገልጸዋል።
ምንጭ: The Telegraph ጋዜጣ እና Detained in Dubai የተሰኘውን የሰብአዊ መብት ድርጅት
5 months ago